en
Feedback
እውነትም ሰሚነሽ ኪዳነ ምሕረት

እውነትም ሰሚነሽ ኪዳነ ምሕረት

Open in Telegram

የሰሚነሽ ኪዳነ ምሕረት ገዳም ትክክለኛ ገጽ ዘወትር እሁድ ከአዲስ አበባ የደርሶ መልስ ጉዞ እናዘጋጃለን ✟ ጉዞ ለመመዝገብ 0921137805 0912162878 ጉዞ ለመመዝገብና ፀሎት ለማስያዝ በእነዚህ ስልክ ቁጥሮች ይደውሉ

Show more
5 523
Subscribers
+224 hours
+77 days
+4430 days

Data loading in progress...

Attracting Subscribers
September '26
September '26
+23
in 0 channels
August '26
+110
in 0 channels
Get PRO
July '26
+51
in 0 channels
Get PRO
June '26
+63
in 0 channels
Get PRO
May '26
+62
in 0 channels
Get PRO
April '26
+56
in 0 channels
Get PRO
March '26
+62
in 0 channels
Get PRO
February '26
+86
in 0 channels
Get PRO
January '26
+66
in 0 channels
Get PRO
December '25
+61
in 0 channels
Get PRO
November '25
+90
in 0 channels
Get PRO
October '25
+113
in 0 channels
Get PRO
September '25
+97
in 0 channels
Get PRO
August '25
+193
in 0 channels
Get PRO
July '25
+105
in 0 channels
Get PRO
June '25
+186
in 0 channels
Get PRO
May '25
+139
in 0 channels
Get PRO
April '25
+90
in 0 channels
Get PRO
March '25
+131
in 0 channels
Get PRO
February '25
+235
in 0 channels
Get PRO
January '25
+139
in 0 channels
Get PRO
December '24
+247
in 0 channels
Get PRO
November '24
+241
in 0 channels
Get PRO
October '24
+164
in 0 channels
Get PRO
September '24
+104
in 0 channels
Get PRO
August '24
+256
in 0 channels
Get PRO
July '24
+191
in 0 channels
Get PRO
June '24
+268
in 1 channels
Get PRO
May '24
+105
in 0 channels
Get PRO
April '24
+181
in 0 channels
Get PRO
March '24
+223
in 0 channels
Get PRO
February '24
+181
in 0 channels
Get PRO
January '24
+44
in 0 channels
Get PRO
December '23
+144
in 0 channels
Get PRO
November '23
+165
in 0 channels
Get PRO
October '23
+72
in 0 channels
Get PRO
September '23
+47
in 0 channels
Get PRO
August '23
+126
in 0 channels
Get PRO
July '23
+174
in 0 channels
Get PRO
June '23
+192
in 0 channels
Get PRO
May '23
+114
in 0 channels
Get PRO
April '23
+142
in 0 channels
Get PRO
March '23
+330
in 0 channels
Get PRO
February '23
+218
in 0 channels
Get PRO
January '23
+168
in 0 channels
Get PRO
December '22
+465
in 0 channels
Get PRO
November '22
+1 187
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
07 September+3
06 September+4
05 September+6
04 September+2
03 September+2
02 September+2
01 September+4
Channel Posts
2
"ኦ ሚካኤል ኦ መተንብል፣ ካህነ አርያም ትሰመይ ቢጸ ሱራፌል፣ ዘእምርዑሳን ርዑስ ወዘእምልዑላን ልዑል፣ ጊዜ ጸዋዕኩከ ቅረበኒ በምሕረት ወሣህል፡፡" "አማላጃችን ሚካኤል ሆይ ፈጥኖ ደራሻችን ሚካኤል
"ኦ ሚካኤል ኦ መተንብል፣ ካህነ አርያም ትሰመይ ቢጸ ሱራፌል፣ ዘእምርዑሳን ርዑስ ወዘእምልዑላን ልዑል፣ ጊዜ ጸዋዕኩከ ቅረበኒ በምሕረት ወሣህል፡፡" "አማላጃችን ሚካኤል ሆይ ፈጥኖ ደራሻችን ሚካኤል ሆይ የጌታን ዙፋን ከሚያጥኑ ሱራፌል ካህናት አንዱ ሰማያዊ ካህን አንተ ነህ እኮን። የሰማያውያን ሊቃነ መላእክት ሁሉ አንተ አለቃቸው ነህ እኮን። ይልቁንም የልዑላንም ልዑል አንተ ነህና በጠራሁህ ጊዜ ሁሉ በይቅርታና በቸርነት ድረስልኝ አትራቀኝ።" (መልክአ ሚካኤል)
1 800
3
ሰኔ 12 በዚህች ቀን ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል አፎምያን ከሰይጣን እጅ ያዳነበት ቀን ነው። ዳግመኛም በዚህ ዕለት ቅዱስ ሚካኤል ባሕራንን የሞቱን ደብዳቤ ወደ ሕይወት የቀየረበት ዕለት ነው። ይህ ዕ
ሰኔ 12 በዚህች ቀን ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል አፎምያን ከሰይጣን እጅ ያዳነበት ቀን ነው። ዳግመኛም በዚህ ዕለት ቅዱስ ሚካኤል ባሕራንን የሞቱን ደብዳቤ ወደ ሕይወት የቀየረበት ዕለት ነው። ይህ ዕለት ጻድቁ ንጉሥ ቅዱስ ላልይበላ ያረፈበትም ቀን ነው። አፎምያን ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ የታደጋት ቅዱስ ሚካኤል እኛንም በጥበቃው አይለየን አሜን
1 979
4
በዓለ ኀምሳ የተባለውም ቀን በደረሰ ጊዜ፥ ሁሉም በአንድ ልብ ሆነው አብረው ሳሉ፥ ድንገት እንደሚነጥቅ ዓውሎ ነፋስ ከሰማይ ድምፅ መጣ፥ ተቀምጠው የነበሩበትንም ቤት ሁሉ ሞላው። እንደ እሳትም የተከፋ+5
በዓለ ኀምሳ የተባለውም ቀን በደረሰ ጊዜ፥ ሁሉም በአንድ ልብ ሆነው አብረው ሳሉ፥ ድንገት እንደሚነጥቅ ዓውሎ ነፋስ ከሰማይ ድምፅ መጣ፥ ተቀምጠው የነበሩበትንም ቤት ሁሉ ሞላው። እንደ እሳትም የተከፋፈሉ ልሳኖች ታዩአቸው፤ በያንዳንዳቸውም ላይ ተቀመጡባቸው።በሁሉም መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው፥ መንፈስም ይናገሩ ዘንድ እንደ ሰጣቸው በሌላ ልሳኖች ይናገሩ ጀመር። የሐዋርያት ሥራ 2:1-4
2 859
5
“ያደረግሁትን ሁሉ የነገረኝን ሰው ኑና እዩ” በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 4 የምናገኛት ሳምራይቱ ሴት ውኃ ልትቀዳ ወደ ያዕቆብ ጕድጓድ እንደመጣች እንመለከታለን፡፡ ነገር ግን የክብር ንጉሥ፣ የዓለሙ መድኃኒት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ልቧ ሰተት ብሎ ሲገባ “ማድጋዋን ትታ ወደ ከተማ ሄደች”፡፡ መጽሐፍ “ሊከተለኝ የሚወድ እርሱ መስቀሉን ተሸክሞ ይከተለኝ” ይላል፡፡ በእውነቱ ሐዋርያት መረባቸውን፣ መንጠቆዋቸውን ትተው የምሥራችን ለዓለም ለመንገር እንደወጡ ይህቺ ሴትም ማድጋዋን ትታ በሐሴት ሠረገላ ተጭና ወንጌሉን ለመንገር ስትሯሯጥ እናያታለን፡፡ “ለሰዎችም ያደረግሁትን ሁሉ የነገረኝን ሰው ኑና እዩ፤ እንጃ እርሱ ክርስቶስ ይሆንን?” እያለች መላ ከተማውን ጠራርጋ ታመጣቸው ነበር። የሚገርመው ሴቲቱ የምታመጣቸው ሰዎች እንደ እንድርያስ ወይም ደግሞ እንደ ፊሊጶስ አንድ ወይም ሁለት ሰዎች ብቻ አይደሉም፡፡ መላ ከተማውን እንጂ፡፡ ትጋቷም ከኒቆዲሞስ በላይ ነው፡፡ ኒቆዲሞስ በወልደ እግዚአብሔር ቢያምንም እንደ እርሷ ግን በግልጥ ለመመስከር አልወጣም፡፡ ሐሳብዋን ብቻ ይግለጥላት እንጂ እንዴት እንደምትነግራቸው የቃላት ምርጫ አታደርግም፡፡ እናም “ያደረግሁትን ሁሉ የነገረኝን ሰው ኑና እዩ፤ እንጃ እርሱ ክርስቶስ ይሆንን?” ትላቸዋለች፡፡ ተጠራጥራ አይደለም፤ መጥተው ራሳቸው ለራሳቸው እንዲወስኑ እንጂ፡፡ ስለዚህም “ኑና እዩ፤ አይታችሁም እመኑ” እያለች ከነፍሳቸው እረኛ ጋር እንዲገናኙ ትፈልጋቸው ነበር፡፡ ሰዎቹም የምትነግራቸውን ነገር ለማየት “ከከተማ ወጥተው ወደ ጌታችን ይመጡ ነበር”። ይህች ሴት በጠዋት አዋልደ ሰማርያን ላለማየት ብላ በጠራራ ፀሐይ ውኃን ለመቅዳት የመረጠች ሴት ነበረች፡፡ አሁን ግን እውነተኛው ፀሐይ ሲነካት ሐፍረቷ እንደ በረዶ ተኖ ጠፋ፡፡ ስለዚህም ቀድሞ ወደምታፍራቸው ሰዎች በመሄድ “አንድ ነብይን ትመለከቱ ዘንድ” ሳይሆን “ያደረግሁትን ሁሉ፣ ምሥጢሬን ሁሉ የነገረኝን ሰው ትመለከቱ ዘንድ ኑ” እያለች ሕዝቡን ጠራቻቸው፡፡ እነርሱም መጡ፡፡ ትጋቷ እንዴት ድንቅ ነው? ቅናቷ እንዴት ግሩም ነው? ዛሬ የዚህችን ሴት ዜና መዋዕል ከመናገር በላይ እኛ ምን እንማራለን? ምን ያህል ቀናተኞች እንሆን? የራሳችንን ጨምሮ ምን ያህል ነፍሳት በእጃችን እንዳሉ እናውቅ ይሆን? ወንድሞቼ “ያደረግሁትን ሁሉ የነገረኝን፤ ያደረግሁትን ሁሉ የፋቀልኝን፤ በነጻ ሥርየተ ኃጢአት የሰጠኝን፤ በነጻ ልጅነት የሰጠኝን፤ በነጻ የራሱን ሥጋና ደም የሰጠኝን… ትመለከቱ ዘንድ ኑ” ብለን የምንመሰክር ስንቶች እንሆን? መክሊታችንን የቀበርን ስንቶች እንሆን? … መጽሐፍ “ባልሰሙትስ እንዴት ያምናሉ?” ይላል… ወንድም እኅቶቼ! የምናውቃትን ያህል ከመመስከር ወደኋላ አንበል፡፡ የታመመን ሰው ሕክምና መውሰድ ያለብንን ያህል እንዲሁ ራሳችንን ጨምሮ ብዙዎችን ከመድኃኒተ ነፍሳቸው ጋር ልናገናኛቸው ያስፈልጋል፡፡ ይህን እንድናደርግ እኛን በመውደድ ሰው የሆነው ክርስቶስ ይርዳን አሜን፡፡ /መቅረዝ ዘተዋህዶ /
3 549
6
ፕሬዝደንቱ " ዩኒቨርሲቲው የግእዝን ትምህርት በስልጠናም ሆነ በመደበኛ ትምህርት ለመስጠት ማጽደቁን ተናግረው ይህም በርካታ ታሪካዊ መዛግብትን ለመመርመር ጉልህ ሚና አለው" ብለዋል። በዚህ ላይ የጉባኤ ቤቱ አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ጨምረው ተናግረዋል። የደብረ ታቦር ደብረ ልዑላን መድኃኔዓለም የ፬ቱ ትርጓሜ መጻሕፍት ምስክር ጉባኤ ቤት መምህር መምህረ መምህራን በጽሐ ዓለሙ በበኩላቸው " ጉባዔ ቤታችን ጥበብና ዕውቀትን ከአባቶቻችን ለልጆቻችን ለማስተላለፍ ራዕይ አንግቦ እየሰራ ይገኛል ፤ ዘመናዊውን ዕውቀት ከነባሩ ዕውቀት አስተሳስሮ ሀገርን እና ትውልድን በዕውቀትና በሥነ-ምግባር ለማነፅ ከደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ጋር ስምምነት አድርገናል " ብለዋል። መምህረ መምህራን በጽሐ ዓለሙ " እኛም እየሰጠናችሁ እናንተም እየሰጣችሁን " በጋራ እንሠራለን በማለት ጉባኤ ቤቱና ዩኒቨርሲቲው ከ፪፳፲፪ ዓ/ም ጀምሮ በጋራ እየሠራ ያለ ቢሆንም የዛሬው የውል ስምምነት ግን በመደበኛነት ለመሥራት ከማስቻሉም በላይ ከዩኒቨርሲቲው ጋር የነበራቸውን ግንኙነት ይበልጥ እንደሚያጠናክር ገልጸዋል። የደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የአለቃ ገብረሃና የባህል ጥናትና ልማት ክፍል በማቋቋቋም ማኅበረሰባዊ አገልግሎት ሲሰጥ እንደቆየ የተነገረ ሲሆን የዛሬው ስምምነት ዋነኛ ዓላማም የጥናትና ምርምር ሥራዎችን ማከናወን መሆኑ ተሰምሮበታል። የዩኒቨርሲቲው የአለቃ ገብረሃና የባህል ጥናትና ልማት ዳይሬክተር የሆኑት መምህር መሠረት ወርቁ እነሰደተናገሩት የሁለቱ ተቋማት ስምምነት የግእዝ እና የአማርኛ ቋንቋ ድርሣናትን ወደ ሌሎች ቋንቋዎች በመተርጎም፤ በጥንታዊ የብራና ጽሑፎች ውስጥ የሚገኙ የሕክምና፣ የአስትሮኖሚ፣ የትምህርትና መሰል ጥበቦችን ማውጣትና ጥቅም ላይ ማዋል፤ በመዛግብትና ሙዚየም ማደራጀት፣ በቅርስ ጥበቃ፣ በቱሪዝም፣ በሥነ-ምግባር፣ በታሪክ፣ በግብረ-ገብ እና በሰላም ግንባታ ዙሪያ በጋራ መስራት፤ የንባብ ባህልን ማዳበር፣ በቤተ-መጻሕፍት እና በተለያዩ አቅም ማጠናከሪያ ስልጠናዎች ዙሪያ በጋራ ለመሥራት ዓለማ ያለው ነው ብለዋል ። በፊርማ ሥነስርዓቱ የዩኒቨርሲቲው የተለያዩ የሥራ ዘርፍ ኃላፊዎችና ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ተገኝተዋል።
2 337
7
ጉባኤ ቤቱና ዩኒቨርሲቲው በጋራ ለመሥራት ተስማሙ። ማኅበረ ቅዱሳን ግንቦት ፲፮ ፪፳፲፰ ዓ/ም የደብረ ታቦር ደብረ ልዑላን መድኃኔዓለም የ፬ቱ መጻሕፍት ትርጓሜ ጉባኤ ቤት ከደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ጋር+5
ጉባኤ ቤቱና ዩኒቨርሲቲው በጋራ ለመሥራት ተስማሙ። ማኅበረ ቅዱሳን ግንቦት ፲፮   ፪፳፲፰ ዓ/ም የደብረ ታቦር ደብረ ልዑላን መድኃኔዓለም የ፬ቱ መጻሕፍት ትርጓሜ ጉባኤ ቤት ከደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ጋር በጋራ ለመሥራት ግንቦት ፲፭ ፪፳፲፰ ዓ/ም ተፈራረሙ። ፊርማው በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ዶ/ር ሰሎሞን አበጋዝ እና በደብረ ታቦር  ደብረ ልዑላን መድኃኔዓለም የ፬ቱ ጉባኤያት መጻሕፍት ትርጓሜ ምስክር ጉባኤ ቤት መምህር መምህረ መምህራን በጽሐ ዓለሙ መካከል የተከናወነ ሲሆን ሁለቱ ተቋማት በጋራ የሚያሠራቸውን የሰነድ ርክክብም አድርገዋል። በሁለቱ ተቋማት በኩል የተፈረመው ሰነድ ሳይንስን ከሀገር በቀል እውቀት ጋር ለማስተሳሠር እና ሐገራዊ ጉዳዮች ላይ ለመሰራት የሚያስችል ታሪካዊ ሰነድ (ስምምነት) ነው ተብሏል። ይህ ታሪካዊ ስምምነት ዩኒቨርሲቲው ሳይንሱን ጉባኤ ቤቱ ደግሞ ሀገር በቀል የሆነውን እውቀት በመስጠት ሳይንሱን ከሐገር በቀል እውቀት ጋር የማስተሳሠር ሥራዎችን በመሥራት ሀገራዊ ግዴታቸውን እንዲወጡ በር የከፈተ ትልቅ እድል መሆኑ ተነግሯል። በፊርማ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ሰለሞን አበጋዝ " ዩኒቨርሲቲው ከሚሰጣቸው የማኅበረሰብ አገልግሎቶች መካከል ከጉባኤ ቤቱ ጋር ለመሥራት የሚያስችለውን  ስምምነት  ተፈራርመናል " ብለዋል። " ዩኒቨርሲቲያችን ስምምነቱን በተግባር ለመተርጎም ሙሉ ቁርጠኛ ነው" ያሉት ዶ/ር ሰሎሞን... " ሀገር በቀል ዕውቀትን መሠረት ያደረጉ ስምምነቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ትኩረት እየተሰጣቸው የመጡ ሲሆን እንደ ኢትዮጵያ ባሉ የበለጸገ ባህል፣ ታሪክ እና የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ዕውቀት ባላቸው ሀገራት ዘንድ ሕጋዊ ማዕቀፍ የሚፈጥሩ ትልቅ ፋይዳ ያላቸው ናቸው" ሲሉ ጨምረው ተናግረዋል።
2 589
8
ዝምታ አንዳንድ ጊዜ ዝምታ ከቃላት ይልቅ ውጤታማ፣ ይበልጥ ተገቢና እጅግ ጠቃሚም ነው። ወይም ደግሞ ቢያንስ - ቢያንስ ተናግሮ ከሚመጣ ጉዳት ይልቅ ሳይናገሩ የሚመጣ ጉዳት ይሻላል። በዝምታ ውስጥ ጥበብና ጥንካሬ ከመኖራቸው በተጨማሪ ክብርና ሞገስም አሉ፡፡ አንዳንድ ጊዜ እግዚአብሔር ይናገር ዘንድ እኛ ዝም እንላለን፣እኛ ልንናገር ከምንወደው ከማንኛውም ነገር የበለጠ የእግዚአብሔር ቃል እጅግ ኃያል ነውና። መጽሐፍ ቅዱስ ይህን አስመልክቶ የተናገረው ቃል ምንኛ ድንቅ ነው! «እግዚአብሔር ስለ እናንተ ይዋጋል፤እናንተም ዝም ትላላችሁ. . » ዘጸ 14፥14። መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በጲላጦስ ፊት በዝምታ ቆይቷል። በዚያን ጊዜ እርሱ  አፉን አልከፈተም ራሱንም አልተከላከለም። ጌታ ዝምታን በመረጠ ጊዜ ጲላጦስ «ይህን ጻድቅ ሰው የምወነጅልበት ምንም ዓይነት ምክንያት አላገኘሁም» በማለት ተናግሮ ነበር፡፡ ዝምታ ትርፍ አስገኚ ይሁን እንጂ የተወሰነ መመሪያ አይደለም፡፡ ወርቃማው መመሪያ፡- ሰው ሊናገር የሚገባው በትክክለኛው ጊዜ መሆኑና ዝም ማለት የሚገባውም ዝም ማለት በሚገባው ትክክለኛ ጊዜ መሆኑ ነው። ሰው ዝም ሲል ልቡ ከእግዚአብሔር ጋር እንዲነጋገር ስለሚፈቅድ በእርሱ ፈንታ ጌታው እንዲናገር ይጠይቃል ማለት ነው፡፡ (አቡነ ሽኖዳ ሣልሳዊ - የሕይወት ልምድ ገጽ 14 - በአያሌው ዘኢየሱስ የተተረጎመ)
2 413
9
ሁለት ጓደኛሞች በጫካ ውስጥ ሲጓዙ አንድ ትልቅ ድብ መጣባቸው። አንደኛው ሮጦ ዛፍ ላይ ወጣ። ሁለተኛው ግን መሮጥ ስለማይችል መሬት ላይ እንደ ሞተ ሰው ተኝቶ ትንፋሹን ዋጠ። ድቡም መጥቶ ጆሮው ላይ
ሁለት ጓደኛሞች በጫካ ውስጥ ሲጓዙ አንድ ትልቅ ድብ መጣባቸው። አንደኛው ሮጦ ዛፍ ላይ ወጣ። ሁለተኛው ግን መሮጥ ስለማይችል መሬት ላይ እንደ ሞተ ሰው ተኝቶ ትንፋሹን ዋጠ። ድቡም መጥቶ ጆሮው ላይ አሸተተውና ሞቷል ብሎ ትቶት ሄደ። ዛፍ ላይ ያለው ወርዶ "ድቡ ጆሮህ ላይ ምን ብሎህ ነው የሄደው?" አለው። እርሱም "በችግር ጊዜ ጥሎህ የሚሄድን ሰው ጓደኛዬ ነው አትበል አለኝ" ብሎ መለሰለት። ​ ፦ እውነተኛ ጓደኛ በደስታ ጊዜ የሚቆጠር ሳይሆን በችግር ጊዜ የሚገኝ ነው። ✞ @Mikre_haymanot ✞                ✞⌲                       ˢʰᵃʳᵉ
3 219
10
"ኃጢአትን ብትሠራ እንኳ አትውደቅ፤ ከወደቅህም ተነሥ እንጂ አትደንግጥ። ዕለት ዕለት ብትበድል ዕለት ዕለት ንስሐ ግባ። እንደ ሰውነታችን ዕለት ዕለት እንበድላለን፡፡ በጥምቀት ያገኘነውን ልጅነት እናቆሽሸዋለን፡፡ አዲሱን ሰውነታችን ብሉይ (አሮጌ) እናደርገዋለን፡፡ ነገር ግን ይህን ዕለት ዕለት ማደስ ይቻላል፡፡ ​አንድ ቤት እያረጀ ቢሄድ እንደ አዲስ እንሠራዋለን፡፡ ክዳኑን፣ ቀለሙን፣ ምንጣፉን እድሳት እናደርግለታለን፡፡ እኛም በኃጢአት ባረጀው ሰውነታችን ላይ እንዲህ ልናደርግ ይገባናል በንስሐ፡፡ ቤት ሲያረጅ ፈርሶ እንደማይጣል ሁሉ፣ ሰውም በኃጢአት ስለወደቀና ስለቆሸሸ ተስፋ ቆርጦ ሊጠፋ አይገባውም። ባለቤቱ መጥቶ እንደሚያድሰው፣ እኛም በንስሐ ወደ እግዚአብሔር ስንቀርብ እርሱ በቸርነቱ ያድሰናል።" (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ኤፌሶን 4 በተረጎመበት ድርሳኑ)
2 888
11
በኃጢአት በወደቅህ ጊዜ ተስፋ ቆርጠህ ጸሎትህን እንዳታቆም። ንስሓ እስከምገባ ድረስ ብለህ ጸሎት ካቆምክ መቼም ንስሓ አትገባም። ምክንያቱም ጸሎት ራሱ የእውነተኛ ንስሓ መግቢያ በር ነው። (ቅዱስ ቄርሎስ ሳድሳዊ -የኤፍራጥስ ወንዝ ገጽ 87)
3 099
12
እንኳን ለወላዲተ አምላክ ለእመ ብርሃን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም በዓለ ልደታ በሰላም አደረሳችሁ! "እመቤቴ ሆይ የሚወድዱሽ የተወደዱ ናቸው" ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ https://youtu.be/oxBriM50JOA?si=kPJsMLxIRnihwWjo
3 537
13
(የማርያም ለቅሶ) እመቤታችን ድንግል ማርያምም ዮሐንስ ሆይ በዕፀ መስቀሉ ላይ ሳለ በእውኑ ልጄ ሞተን አለችው:: እርሱም አጎንብሶ እመቤቴ ሆይ አዎን ሞተ አላት:: ድንግልም እንደገና አብዝታ ታለቅስ
(የማርያም ለቅሶ) እመቤታችን ድንግል ማርያምም ዮሐንስ ሆይ በዕፀ መስቀሉ ላይ ሳለ በእውኑ ልጄ ሞተን አለችው:: እርሱም አጎንብሶ እመቤቴ ሆይ አዎን ሞተ አላት:: ድንግልም እንደገና አብዝታ ታለቅስ ጀመር:: የልብ ኃዘኗም ስለፀናባት ይህ ሁሉ ሕማማተ መስቀል ስለተቀበልክ ወዮ:: መበደሌን የሚመለከት ሹም የልቤን ሐዘንም የሚረዳኝ ዳኛ አላገኝውም:: ላሐ ማርያም ዘዕለተ ረቡዕ
2 250
14
#አዘክሪ አዘክሪ ድንግል አዘክሪ ለልጅሽ አሳስቢ አዘክሪ ለኃጥአን አኮ ለጻድቃን ከአንቺ መወለዱን - - - አዘክሪ በቤተልሔም - - - አዘክሪ በጨርቅ መጠቅለሉን - - - አዘክሪ መኝታው ግርግም - - - አዘክሪ ለኃጥአን አኮ ለጻድቃን አዝ= = = = = በዚያ በብርድ ወራት - - -አዘክሪ የገበሩለትን - - - አዘክሪ የአድግና የላህም - - - አዘክሪ እስትንፋሳቸውን - - - አዘክሪ ለኃጥአን አኮ ለጻድቃን አዝ= = = = = በግብጽ በረሃ - - - አዘክሪ መሰደድሽን - - - አዘክሪ የአሸዋውን ግለት - - - አዘክሪ ረሃብና ጥሙን - - - አዘክሪ ለኃጥአን አኮ ለጻድቃን አዝ= = = = = በመቃብሩ ዘንድ - - - አዘክሪ ባለቀሽው እንባ - - - አዘክሪ አሳስቢ ድንግል ሆይ - - - አዘክሪ ገነት እንድገባ - - - አዘክሪ ለኃጥአን አኮ ለጻድቃን @MEZMURA
3 505
15
ማን ነው የሚተካህ ? 😥 ያንተ እኮ ልዩ ነው መምህር ዘለዓለም 😥
ማን ነው የሚተካህ ? 😥 ያንተ እኮ ልዩ ነው መምህር ዘለዓለም 😥
3 919
16
እጅግ የምናከብራቸው መምህር ዘላለም ወንድሙ ዕረፍት እጅግ ጥልቅ ኀዘን ይሰማናል:: በጽናት ወዳገለገሉት አምላካቸው በመጠራታቸው ምክንያት የሚበልጠውን ዋጋ እንደሚቀበሉ እያመንን ለኦርቶዶክሳውያን ሁሉ+1
እጅግ የምናከብራቸው መምህር ዘላለም ወንድሙ ዕረፍት እጅግ ጥልቅ ኀዘን ይሰማናል:: በጽናት ወዳገለገሉት አምላካቸው በመጠራታቸው ምክንያት የሚበልጠውን ዋጋ እንደሚቀበሉ እያመንን ለኦርቶዶክሳውያን ሁሉ መጽናናትን እንመኛለን:: የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ
3 799
17
"እግዚአብሔርም ከክፉ መንገዳቸው እንደተመለሱ ሥራቸውን አየ፤ እግዚአብሔርም ያደርግባቸው ዘንድ በተናገረው ክፉ ነገር ተጸጽቶ አላደረገውም" ዮናስ 3:10 የነነዌ ሰዎች በእግዚአብሔር ፊት ማረን ብለው
"እግዚአብሔርም ከክፉ መንገዳቸው እንደተመለሱ ሥራቸውን አየ፤ እግዚአብሔርም ያደርግባቸው ዘንድ በተናገረው ክፉ ነገር ተጸጽቶ አላደረገውም" ዮናስ 3:10 የነነዌ ሰዎች በእግዚአብሔር ፊት ማረን ብለው በመውደቃቸው እግዚአብሔር መዓቱን በምሕረት ቁጣውን በትዕግሥት ለውጦ ምሕረት እንዳደረገላቸው ጾሙን እግዚአብሔር የምሕረት ያድርግልን:: እንደ ቸርነትህ አቤቱ ማረን እንደ ምሕረትህ ይቅርታን ሥጠን ከኃጢአቴም አንጻኝ ከክፉ በደሌ ለዚያች ክፉ ኃጢአት እንዳልሆናት ሎሌ እኔስ አመጻዬን በደሌን ሳውቀው ፍጹም የሚያድነኝ ቸርነትህ ነው አንተን ብቻ በደልሁ ክፉም አደረግሁ አሁን ይቅር በለኝ ከፊትህ ወደቅሁ ከፊትህ ወድቄ ስለምን አንተን መውደቄን ተመልከት አምላከ ብርሃን መነሻ :- መዝሙር ፶ ግጥም :- ዶ/ር ኢሳይያስ ዓለሜ ዝማሬ :- በኩረ መዘምራን ኪነ ጥበብ ወልደ ቂርቆስ ታኅሣሥ 28 2018 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ እንደዘመሩት ሊንኩን ተጭነው ይመልከቱ https://youtu.be/ej5PKZRIo8E?si=C3-oUUnAN4N1hbZv
3 466
18
'በጎል በጎል' - 2018 የአእላፋት ዝማሬ መዝሙር- በጃን ያሬድ ኅብረ ዝማሬ የተዘመረ https://t.me/+1rCQMEj6K2kzM2E8
2 607
19
No text...
2 281
20
'ግሩም ድንቅ ነህ ' - ዘማሪ ዳግማዊ ደርቤ- 2018 የአእላፍት ዝማሬ መዝሙር- በጃን ያሬድ ኅብረ ዝማሬ የተዘመረ https://t.me/+1rCQMEj6K2kzM2E8
2 226