en
Feedback
Ethiopian Electric Utility

Ethiopian Electric Utility

Open in Telegram

EEU Official Telegram Channel Web: www.eeu.gov.et

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Ethiopian Electric Utility

Channel Ethiopian Electric Utility (@eeuethiopia) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 48 885 subscribers, ranking 5 378 in the News & Media category and 686 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 48 885 subscribers.

According to the latest data from 10 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 962 over the last 30 days and by 14 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 16.57%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 10.62% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 8 098 views. Within the first day, a publication typically gains 5 191 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 18.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“EEU Official Telegram Channel Web: www.eeu.gov.et”

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 11 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

48 885
Subscribers
+1424 hours
+2207 days
+96230 days
Posts Archive
ተቋርጦ የቆየው ኃይል አቅርቦት ተመልሷል ከቤላ- አዲሱ ገቢያ -ሸጎሌ በተዘረጋው ትራንስሚሽን መስመር እና በጎፋ ኃይል ማከፋፈያ ትራንስፎርመር ኦቨር ሎድ ምክንያት 👉በእግዚአቤረሰብ ቤተክርስቲያን፣
ተቋርጦ የቆየው  ኃይል አቅርቦት ተመልሷል ከቤላ- አዲሱ ገቢያ -ሸጎሌ በተዘረጋው ትራንስሚሽን መሾመር እና በጎፋ  ኃይል ማከፋፈያ ትራንስፎርመር ኦቨር ሎድ  ምክንያት 👉በእግዚአቤረሰብ ቤተክርስቲያን፣ ድል በር፣ ፂዎን ሆቴል፣ ቁ3 አገልግሎት መስጫ ማዕከል፣ መነን ፣ 6ኪሎ ዪኒቨርስቲ ፣ አሜሪካ ኢንባሲ ሰፈሮች፣  ስፔን ኢንባሲ፣ ሽሎ ሜዳ ኪዳነ ምህረት ቤተክርስቲያን ድረስ እና አካባቢው፣ 👉ቤላ ሰብስቴሽን ጀርባ ያሉ ሰፈሮች ፤ ቤላ አቦ ቤተክርስቲያን፣ፈረንሳይ ጉራራ ኪዳነ ምህረት ቤተክርስቲያን ድረስ እና አካባቢው 👉ላፍቶ እና አካባቢው፣ ወረዳ 12 እና ጎርጎሪዎስ ቤተክርስቲያን፣ ግንቦት 20 ት/ቤት ፣ያሬድ ሜዳ፣ 58 ጫፍ ታክሲ ተራው ድረስ እና አካባቢው ተቋርጦ የነበረው የኃይል አቅርቦት ወደ አገልግሎት ተመልሷል። በኃይል ማስተላለፊያ መስመሩና በከፋፈያ ጣቢያትራንፎርመር ላይ አጋጥሞ የነበረው  የኦቨርሎድ ችግር ተስተካክሎ የኃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ ድረስ በትእግስት ለጠበቃችሁን ክቡራን ደንበኞቻችን ከልብ እናመሰግናለን። #የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

በብልሽት ምክንያት የተቋረጠ ኃይል አቅርቦት ዛሬ ጳጉሜ 05 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 1፡00 ጀምሮ በቤላ ሃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ባጋጠመው የቴክኒክ ብልሽት ምክንያት 👉በእግዚአቤረሰብ ቤተክሪስቲ
በብልሽት ምክንያት የተቋረጠ ኃይል አቅርቦት ዛሬ ጳጉሜ 05 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 1፡00 ጀምሮ በቤላ ሃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ባጋጠመው የቴክኒክ ብልሽት ምክንያት 👉በእግዚአቤረሰብ ቤተክሪስቲያን፣ ድል በር፣ፂዎን ሆቴል፣ ቁ3 አገልግሎት መስጫ ማዕከል፣ መነን ፣ 6ኪሎ ዪኒቨርስቲ ፣ አሜሪካ ኢንባሲ ሰፈሮች፣  ስፔን ኢንባሲ ፣ ሽሮ ሜዳ ኪዳነ ምህረት ድረስ እና አካባቢው፣ 👉ቤላ ሰብስቴሽን ጀርባ ያሉ ሰፈሮች ፤ ቤላ አቦ ቤተክርስቲያን፣ፈረንሳይ ጉራራ ኪዳነ ምህረት ቤተክርስቲያን ድረስ እና አካባቢው የኃይል አቅርቦት ተቋርጧል፡፡ ስለሆነም ክቡራን ደንበኞቻችን  በሃይል ማከፋፈያ ጣቢያው  ያጋጠመው የቴክኒክ ችግር በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል በኩል ተቀርፎ የኃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እናሳውቃለን፡፡ #የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ለመላው ኢትዮጵያዊያን እንኳን ለ2019 አዲስ አመት በሰላም አደረሳችሁ በዓሉ የሰላም፣ የጤና፣ የፍቅርና የተስፋ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ ! ኢንጂነር ጌቱ ገረመው ዋና ስራ አስፈፃሚ 🟡መልካም አዲስ
ለመላው ኢትዮጵያዊያን እንኳን ለ2019 አዲስ አመት በሰላም አደረሳችሁ በዓሉ የሰላም፣ የጤና፣ የፍቅርና የተስፋ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ ! ኢንጂነር ጌቱ ገረመው ዋና ስራ አስፈፃሚ 🟡መልካም አዲስ ዓመት🟡

🎯በአዲስ አመት በዓልና ዋዜማ የቅድመ-ክፍያ አገልግሎት ይፈልጋሉ? ተቋማችን የ2019 አዲስ ዓመት በዓልን ምክንያት በማድረግ በበዓሉ ዋዜማና በበዓሉ ዕለት በሁሉም አካባቢዎች በተመረጡ ማዕከላት የካ
🎯በአዲስ አመት በዓልና ዋዜማ የቅድመ-ክፍያ አገልግሎት ይፈልጋሉ? ተቋማችን የ2019 አዲስ ዓመት በዓልን ምክንያት በማድረግ በበዓሉ ዋዜማና በበዓሉ ዕለት በሁሉም አካባቢዎች በተመረጡ ማዕከላት የካርድ መሙላት አገልግሎት ያመቻቸ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ የአገልግሎት መስጫ ማዕከላትን ዝርዝር ለማወቅ ይሄንን ሊንክ ይጫኑ https://www.eeu.gov.et/prepaid/detail/2553?lang=am መልካም በዓል! - የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት

🔋የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በስማርት ግሪድ (Smart Grid) ጉዞ፡ የነገው ቀን📍 ኢትዮጵያ ከወረቀት አሠራር ወደ ዲጂታል፣ እንዲሁም ከቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት ወደ ፈጣሪነት የተሸጋገረችበትን
🔋የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በስማርት ግሪድ (Smart Grid) ጉዞ፡ የነገው ቀን📍 ኢትዮጵያ ከወረቀት አሠራር ወደ ዲጂታል፣ እንዲሁም ከቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት ወደ ፈጣሪነት የተሸጋገረችበትን ታሪካዊ ምዕራፍ በጳጉሜን 5 «የነገው ቀን» ስናከብር፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሚገነባው የስማርት ግሪድ (Smart Grid) ቴክኖሎጂ የዚሁ ትልቅ ማረጋገጫ ነው። 🎯ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን የዕለት ተዕለት ባህላችን እየሆነ መጥቷል። ይህ የዲጂታል ሽግግር የአገልግሎ አሰጣጥንን የሚያቀላጥፍ፣ መረጃዎችን ተደራሽ ለማድረግ የሚረዳ እና ልዩ ልዩ ዘርፎችን የሚያዘምን እንደሆነም ይታወቃል።           ✅በተቋሙ እየተገበሩ ያሉ ዋና ዋና የቴክኖሎጂ ማሻሻያዎች፦    ➡️ስማርት ቆጣሪ (Smart Metering)፦ የቆጣሪ ንባብንና ክፍያን ሙሉ በሙሉ በዲጂታልና በኤሌክትሮኒክስ ሥርዓት በመተካት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ማረጋገጥ፣ 👉የስማርት ግሪድ ቁጥጥር፦ የኃይል ማሰራጫ መስመሮችን በዲጂታል መንገድ በመከታተል የኃይል መቆራረጥን በፍጥነት መለየትና የኃይል ብክነትን መቀነስ፣ ⚡️ይህ የስማርት ግሪድ ትግበራ የሀገሪቱን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ የሚያፋጥን፣ የአገልግሎት ጥራትን የሚያረጋግጥና የነገዋን ዘመናዊት ኢትዮጵያ እውን የሚያደርግ ትልቅ እርምጃ ነው።   #ዲጂታልትራንስፎርሜሽን #ስማርትግሪድ #ዲጂታልቴክኖሎጂ #ዘመናዊየኤሌክትሪክአውታር #የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት፣

የበዓል ቅድመ ዝግጅትና መልካም የምስራች ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት  ! የ2019 አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ፣ በዓሉ የብርሃንና የደስታ እንዲሆንልዎ እየተመኘን የቴክኒክ ቡድኖቻችንን በሁሉም ሪጅኖች ሙሉ በሙሉ ወደ ሼል አሰማርተናል።     ✅ ለበዓሉ ያደረግናቸው ዋና ዋና ዝግጅቶች 📌የትራንስፎርመሮች አቅም የማሻሻልና ሰፊ የጥገና ሥራዎች ተከናውነዋል፣ ➡️በበዓሉ ዋዜማ እና ዕለት በተመረጡ የአገልግሎት መስጫ ማዕከላት የካርድ መሙላት አገልግሎት ይሰጣል ፣ ትንሽ ጥንቃቄ ለትልቅ እፎይታ፡ 🎯 የኃይል ጭነትን ለማመጣጠን ከምሽቱ 4፡00 እስከ ንጋቱ 11፡00 ባለው ሰዓት የኤሌክትሪክ ቁሳቁሶችን ይጠቀሙ ፣ 👉ደንበኞቻን ኃይል ቆጣቢ የኤሌክትሪክ ቁሳቁሶችን በመጠቀም የሃይል ብክነትን እንዲከላከሉና ከኤሌክትሪክ አደጋ እራሳቸውን በመጠበቅ የ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመትን በሰላም፣ በደስታና በደህንነት እንዲያከብሩ ተቋሙ መልካም ምኞቱን ይገልጻል። #የአዲስዓመትበዓል፣ #ቅድመዝግጅት፣ #የኤሌክትሪክደህንነት፣ #የኢነርጂቁጠባ፣  #የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት፣

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፦ የብዝሃነት እና የፍትሃዊ ተደራሽነት ማሳያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የመላው ሀገሪቱን ብዝሃነት ያገናዘበ፣ ፍትሃዊ እና አካታች የኤሌክትሪክ ተዳራሽነትን በማ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፦ የብዝሃነት እና የፍትሃዊ ተደራሽነት ማሳያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የመላው ሀገሪቱን ብዝሃነት ያገናዘበ፣ ፍትሃዊ እና አካታች የኤሌክትሪክ ተዳራሽነትን በማረጋገጥ የሀገሪቱን አጠቃላይ የልማት ጉዞ እያፋጠነ ይገኛል። ተቋሙ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች እኩል ተጠቃሚ ለማድረግ በግሪድና ከግሪድ ውጪ ደግሞ በኦፍ ግሪድ (በፀሐይ) ሃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን በመገንባት ሁሉንም የሃገሪቱ ህዝቦች የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ እያደረገ ይገኛል፡፡ ተቋሙ የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን እውን ለማድረግ ከጫፍ እስከ ጫፍ በሚያከናውነው የመሰረተ ልማት ዘርጋታ፣ ፍትሃዊነትን እና ተዳራሽነትን ዋና መርሁ በማድረግ እየሰራ ነው። በዚህም መሰረት ሀገራዊ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽ የሆኑትን ግዙፍ የኢንዱስትሪዎችን በአስተማማኝ ሃይል ከማንቀሳቀስ ባሻገር የገጠር የብርሃን እና የዘመናዊ ሃይል ባለቤት የሚያደርጉ የኃይል ማዳረስ ፕሮጀክቶች በስፋት እየተከናወኑ ይገኛሉ። በተጨማሪም የህብረተሰቡን ልዩ ልዩ ፍላጎቶች እና የባህል ብዝሃነት ያገናዘበ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ አሰራር እና የደንበኞች አገልግሎት በመዘርጋት፣ ተቋሙ አሰራሩን ይበልጥ ቀልጣፋ እና ተዳራሽ አድርጓል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሁሉንም የሀገሪቱን ክፍሎች በፍትሃዊነት በብርሃን የማስተሳሰር ሃላፊነት የተጣለበት ሃገራዊ ተቋም ነው፡፡ #የኤሌክትሪክተደራሽነት #አስተማማኝየኃይልአቅርቦት #ብርሃንለሁሉም #የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

በብልሽት ምክንያት የተቋረጠ ኃይል ዛሬ ጳጉሜ 03 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10፡50 ጀምሮ በፊንጫ 230 ትራንስሚሽን መስመር ለይ ባጋጠመው የቴክኒክ ብልሽት ምክንያት በፌንጫ ስኳር ፋብርካና አከባቢው የ
በብልሽት ምክንያት የተቋረጠ ኃይል ዛሬ ጳጉሜ 03 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10፡50 ጀምሮ በፊንጫ 230 ትራንስሚሽን መስመር ለይ ባጋጠመው የቴክኒክ ብልሽት ምክንያት በፌንጫ ስኳር ፋብርካና አከባቢው የኃይል አቅርቦት ተቋርጧል፡፡ ስለሆነም ክቡራን ደንበኞቻችን በትራንስሚሽን መስመሩ ላይ ያጋጠመው ችግር ተቀርፎ የኃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እናሳውቃለን፡፡ #የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

የብርሃን ባለአደራዎች የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሠራተኞች የማይበገር ፅናት ከእያንዳንዱ የልማት እንቅስቃሴ ጀርባ ኤሌክትሪክ አለ፤ ይህን ወሳኝ የሆነ አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ ደግሞ የኢትዮጵ
የብርሃን ባለአደራዎች የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሠራተኞች የማይበገር ፅናት ከእያንዳንዱ የልማት እንቅስቃሴ ጀርባ ኤሌክትሪክ አለ፤ ይህን ወሳኝ የሆነ አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ ደግሞ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሠራተኞች ሃላፊነት ነው፡፡ የሀገራችንን ከተሞች ለማብራት፣ የልማትና የኢንዱስትሪዎችን እንቅስቃሴ ለማስቀጠል እንዲሁም የቤተሰቦችን ህይወት በብርሃን ለመሙላት ትልቅ መስዋዕትነት እና ፅናት ይጠይቃል፡፡ ብዙ ጊዜ ይህን የሥራ ፅናት ልንዘነጋው እንችላለን።ነገር ግን በየተራራውና በየሸለቆው፣ከባድ በሆነ ፀሐይና ዝናብ ውስጥ የሚያልፉ ብርቱ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሠራተኞች አሉ። እነዚህ ሠራተኞች ቀላል የሚባለውን መንገድ ትተው፣ አደጋ የተሞላበትንና ከፍተኛ ሀገራዊ ኃላፊነት የሚጠይቅን ሥራ በፅናትና በሥራ ፍቅር ይወጣሉ። በቅጽበት በሚቀያየር የአየር ጠባይ እስከ ሰማይ በሚደርሱ የኮንክሪትና የእንጨት ምሰሶዎች ላይ ወጥተው ከፍተኛ ኃይል የሚሸከሙ አዳዲስ መስመሮችን ይዘረጋሉ፤ የተበላሹትንም ይጠግናሉ። ይህ ድፍረታቸው ደግሞ ከሥራ በላይ የሙያና የሀገር ፍቅር መገለጫ ነው። ስለሆነም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሠራተኞች የቴክኒክ ባለሙያዎች ብቻ አይደሉም፤ሀገራቸውን ከጨለማ የሚጠብቁ፣ የልማትና የዕድገት ጉዞ እንዳይቆም ባላቸውና በቁርጠኝነታቸው የሚያንቀሳቅሱ የብርሃን ባለአደራዎች ናቸው። ፅናታቸው፣ ድፍረታቸውና የማይበገረው መንፈሳቸው ሀገራችንን ወደፊት የሚያስጉዝ ታላቅ የፅናት ማሳያ ነው! #የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት #የብርሃንባለአደራዎች #የማይበገርፅናት #የሙያፍቅር

⚡️ #Beeksisa Addaan Cituu Dhiyeessii Elektirikii Boru Qaammee 3, 2018 A.L.I.,Bu’uuraalee misoomaa elektirikii irratti hojii fooyya’iinsaa fi suphaa raawwachuuf, bakkeewwan armaan gaditti tarreeffamanitti tajaajilli elektirikii yeroo murta’eef adda cita. ✅ Ganama 2:30–Waaree Booda 9:00 tti 👉 Alam Bank, Polii Tekinikaa, Aqaaqii, Leebuu safara Muziqaa fi naannawa isaa, ✅ Ganama 6:01– Waaree Booda 11:01-tti 👉 Askoo Carataa, Warshaa Birchiqoo, Fuuldura Koondominiyeemii Birchiqoo 40/60, Xaaroo Sillaasee, Masjiida Xaaroo, Buufata Fayyaa Kolfee fi naannawa isaa, ✅ Ganama 3:30– Waaree Booda 9:30-tti 👉 Magaalaa Xaafoo, Laga Dadhii gartokkoon, 44 Maazooriyaa, CDC, Koseroo fi naannawa isaa, ✅ Ganama 1:30– Waaree Booda 9:30-tti 👉 Wolayitaa Soddoo Magaalaa Gunuunoo, fi naannawa isaa, ✅ Ganama 2:30– Waaree Booda 6:00tti 👉 Magaalaa Arbaa Mincii, Yuunivarsiitii Arbaa Mincii, Bonkee, Gachoobabaa, Ziigitii fi naannawa isaa, ✅ Ganama 3:30– Waaree Booda 9:30tti 👉 Baha Daar, ganda 10, Biiroo Bulchiinsa Naannoo Amaaraa, Poolii Yuunivarsiitii, Masobii fi naannawa isaatti dhiyeessiin anniisaa elektirikii addaan ni cita. Kanuma hubachuun, maamiltoonni bakkeewwan armaan olitti eeramanitti argamtan, qophii barbaachisu taasisuun hojichi xumuramee tajaajilichi hanga bakkatti deebi'utti obsaan akka nu eegdan kabajaan isin gaafanna, #Tajaajila Elektirikii Itoophiyaa

photo content

የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት ነገ ጳጉሜ 4 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች ፡- ✅ ከጠዋቱ 2፡30-9፡00 👉 ዓለም ባንክ
የጥገና ሼል ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት ነገ ጳጉሜ 4 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሼል ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች ፡- ✅  áŠ¨áŒ á‹‹á‰ą 2፡30-9፡00 👉 ዓለም ባንክ፣ ፖሊ ቴክኒክ፣ አቃቂ ጥጥ መጋዘን፣ ለቡ ሙዚቃ ሰፈርና አካባቢው ✅  áŠ¨áŒ á‹‹á‰ą 3፡30-9፡30 👉 ለገጣፎ ከተማ ፣ ለገዳዲ በከፊል፣ 44 ማዞሪያ፣ ሲዲሲ፣ ኮሰሮና አካባቢው ✅  áŠ¨á‰€áŠ‘ 6፡01-11፡01 👉 አስኮ ጨረታ፣ ብርጭቆ ፋብሪካ፣ ብርጭቆ 40/60 ኮንዶሚኒየም ፊትለፊት፣ ጠሮ ስላሴ፣ ጠሮ መስጊድ፣ ኮልፌ ጤና ጣቢያና አካባቢው   ✅  áŠ¨áŒ á‹‹á‰ą 1፡30-9፡30 👉 በወላይታ ሶዶ ጉኑኖ ከተማና አካባቢው ✅  áŠ¨áŒ á‹‹á‰ą 2፡30-6፡00 👉 በአርባ ምንጭ ከተማ፣ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ፣ ቦንኬ፣ ገቾበባ፣ ዚጊቲ እና አካባቢው ✅  áŠ¨áŒ á‹‹á‰ą 3፡30-9፡30 👉 በባህርዳር ቀበሌ 10፣ አማራ ክልል ቢሮ፣ ፖሊ ዩኒቨርሲቲ፣ መሶብና አካባቢው የኃይል አቅርቦት ይቋረጣል፡፡   ስለሆነም በአካባቢው የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንኑ በመገንዘብ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡

የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት ነገ ጳጉሜ 4 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች ፡- ከጠዋቱ 2፡30-9፡00 ዓለም ባንክ፣ ፖሊ
የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት ነገ ጳጉሜ 4 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች ፡- ከጠዋቱ 2፡30-9፡00 ዓለም ባንክ፣ ፖሊ ቴክኒክ፣ አቃቂ ጥጥ መጋዘን፣ ለቡ ሙዚቃ ሰፈርና አካባቢው ከጠዋቱ 3፡30-9፡30 ለገጣፎ ከተማ ፣ ለገዳዲ በከፊል፣ 44 ማዞሪያ፣ ሲዲሲ፣ ኮሰሮና አካባቢው ከቀኑ 6፡01-11፡01 አስኮ ጨረታ፣ ብርጭቆ ፋብሪካ፣ ብርጭቆ 40/60 ኮንዶሚኒየም ፊትለፊት፣ ጠሮ ስላሴ፣ ጠሮ መስጊድ፣ ኮልፌ ጤና ጣቢያና አካባቢው ከጠዋቱ 1፡30-9፡30 በወላይታ ሶዶ ጉኑኖ ከተማና አካባቢው ከጠዋቱ 2፡30-6፡00 በአርባ ምንጭ ከተማ፣ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ፣ ቦንኬ፣ ገቾበባ፣ ዚጊቲ እና አካባቢው ከጠዋቱ 3፡30-9፡30 በባህርዳር ቀበሌ 10፣ አማራ ክልል ቢሮ፣ ፖሊ ዩኒቨርሲቲ፣ መሶብና አካባቢው የኃይል አቅርቦት ይቋረጣል፡፡ ስለሆነም በአካባቢው የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንኑ በመገንዘብ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡ #የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ለ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመት የኃይል መቆራረጥን ለመቀነስ ሰፊ የቅድመ ዝግጅት ሥራ ተከናውኗል - (2 ሺህ 110 ኪ.ሜ የኃይል መስመርና ከ8 ሺህ በላይ ትራንስፎርመሮች ተፈትሸዋል) የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመትን ህብረተሰቡ በደስታና በመረጋጋት እንዲያከብር የኃይል መቆራረጥን ለመቀነስና ድንገተኛ ችግሮች ሲያጋጥሙ ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ሰፊ የቅድመ ዝግጅት፣ የኔትዎርክ ፍተሻና የጥገና ሥራዎችን አከናውኗል። በዓሉ ዋዜማና በዓሉ ዕለት ሊከሰቱ የሚችሉ የኃይል መቆራረጦችን በከፍተኛ ሁኔታ ለመቀነስ በመላ አገሪቱ የሚገኙ የተቋሙ መዋቅሮች ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር በቅንጅት የተደራጀ ሥራ እያከናወኑ ይገኛሉ። 24 ሰዓት ፈጣን ምላሽ የሚሰጥ የቴክኒክ ቡድን ተዘጋጅቷል በአዲስ ዓመት በዓል ወቅት የሚያጋጥሙ የኃይል ችግሮችን በፍጥነት ለመፍታት ከበዓሉ ዋዜማ ጀምሮ እስከ በዓሉ ዕለት ድረስ 24 ሰዓት ፈጣን ምላሽ የሚሰጥ የቴክኒክ ቡድን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር በመቀናጀት ወደ ሥራ ገብቷል። በተጨማሪም በሁሉም የአገልግሎቱ ሪጅኖችና የአገልግሎት መስጫ ማዕከላት አጣዳፊ የጥገና ሥራዎችን ለማከናወን ዝግጁ የጥገና ቡድኖች ተደራጅተዋል። ሰፊ የኔትዎርክ ፍተሻና የጥገና ሥራ ተከናውኗል በነሐሴ ወር በመላ አገሪቱና በአዲስ አበባ በተከናወኑ ሰፊ የፍተሻና የጥገና ሥራዎች 2 ሺህ 110 ኪ.ሜ የመካከለኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተፈትሿል። በፍተሻው የተለዩ 10 ሺህ 308 የኃይል መቆራረጥ ሊያስከትሉ የሚችሉ ግኝቶችም ሙሉ በሙሉ ተስተካክለዋል። እንዲሁም ከ8 ሺህ በላይ ትራንስፎርመሮች የተፈተሹ ሲሆን፣ በ6 ሺህ 877 ትራንስፎርመሮች ላይ የተለዩ የቴክኒክ ችግሮች እንዲስተካከሉ ተደርጓል። በበዓሉ ዋዜማ ሊፈጠር የሚችለውን ተጨማሪ የኃይል ጭነት ለመቋቋም 178 ትራንስፎርመሮች አቅማቸው የተሻሻለ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ 88ቱ በአዲስ አበባ እና 90ዎቹ በክልል ከተሞች የሚገኙ ናቸው። ከ3 ሺህ በላይ ትራንስፎርመሮችም በዘይት ማነስ ምክንያት አደጋና ጉዳት እንዳይደርስባቸው የዘይት መሙላትና ጥገና ሥራ ተከናውኗል። ለደንበኞች የኃይል ቆጣቢነትና ጥንቃቄ ጥሪ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስፈላጊውን የቅድመ ዝግጅት ሥራ ቢያጠናቅቅም፣ በበዓሉ ወቅት የሚፈጠረውን ከፍተኛ የኃይል ፍላጎትና ጭነት ለማመጣጠን ደንበኞች ኃይል ቆጣቢ ቁሳቁሶችን እንዲጠቀሙና የኤሌክትሪክ ቁሳቁሶቻቸው ለአደጋ የማያጋልጡ መሆናቸውን እንዲያረጋግጡ ጥሪ ያቀርባል። በተጨማሪም የኃይል ጭነት በማይበዛበት ሰዓት፣ በተለይም ከምሽቱ 4፡00 እስከ ንጋቱ 11፡00 ባለው ጊዜ የኤሌክትሪክ ቁሳቁሶችን መጠቀም የተሻለ አማራጭ መሆኑን ተቋሙ ይገልፃል። የካርድ መሙላትና የደንበኞች ግንኙነት አገልግሎቶች በአዲስ አበባ በሚገኙ ሁሉም የአገልግሎት መስጫ ማዕከላትና በሪጅን ማዕከላት የካርድ መሙላት አገልግሎት በበዓሉ ዋዜማ እስከ ምሽቱ 12፡00 ሰዓት ድረስ ይሰጣል። በበዓሉ ዕለትም በተመረጡ ማዕከላት የካርድ መሙላት አገልግሎት ክፍት ይሆናል። ደንበኞች በበዓሉ ወቅት ድንገተኛ የኤሌክትሪክ አደጋ ሲያጋጥማቸው ወይም የጥገና ጥቆማና አስተያየት ለመስጠት 905 በመደወል በነፃ ማሳወቅ ይችላሉ። ከዚህ በተጨማሪ በተቋሙ የፌስቡክና ቴሌግራም የዲጂታል ማዕከል በኩል ፈጣን መረጃና ምላሽ ማግኘት ይችላሉ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ህብረተሰቡ ከተቋሙ ጋር በመተባበር የኃይል ቆጣቢነትንና የኤሌክትሪክ ደህንነትን በመጠበቅ የ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመትን በሰላም፣ በደስታና በደህንነት እንዲያከብር መልካም ምኞቱን ይገልጻል።

photo content
+2

ማንሠራራት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የትራንስሚሽን እና ዲስትሪቢዩሽን ኔትወርክ ማሻሻያ እና ማስፋፊያ ፕሮጀክቶች          🔋አዲስ አበባ ትራንስሚሽን እና ዲስትሪቢዩሽን መልሶ ግንባታና አቅም ማሳደግ (AATDRUP) ፕሮጀክት 📌ሽፋን ፡- በአዲስ አበባ እና በዙሪያዋ በ50 ኪ.ሜ ራዲየስ ውስጥ፣ 👉አፈፃፀም፡ 97.91% 🎯የአዲስ አበባ ከተማ 4ኛ ምዕራፍ የዲስትሪቢዩሽን ኔትወርክ ማጠናከሪያ ፕሮጀክት፡- ➡️መግለጫ፡- ከዚህ በፊት በነበሩት የአዲስ አበባ የመልሶ ግንባታ እና አቅም ማሳደግ ፕሮጀክቶች ውስጥ ያልተካተቱ የዲስትሪቢዩሽን መስመሮችን በማካተት የሚከናወን ⚡️አፈፃፀም፡ 61.12%፣    📌አስሩ (10) ከተሞች የዲስትሪቢዩሽን ኔትወርክ መልሶ ግንባታና አቅም ማሳደግ ፕሮጀክት፡- 📣 የተካተቱ ከተሞች፡- አሰላ፣ ዲላ፣ ሆሳዕና፣ ቢሾፍቱ፣ ሱሉልታ፣ ደብረብርሃን፣ አምቦ፣ ነቀምቴ፣ አሶሳ እና ጅግጅጋ ከተሞች መልሶ ግንባታና አቅም ማሳደግሥራ፣ 📍ፕራይም - 1 ፕሮጀክት (በሁሉም ክልሎች የሚተገበሩ 72 ከተሞች መልሶ ግንባታ ፕሮጀክት)፡- #የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት ነገ ጳጉሜ 3 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች ፡- ✅ከጠዋቱ 2፡00-9፡30 👉ግብፅ ኤምባሲ፣
የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት ነገ ጳጉሜ 3 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች ፡- ✅ከጠዋቱ 2፡00-9፡30 👉ግብፅ ኤምባሲ፣ 6 ኪሎ ዩኒቨርስቲ ፣ የካቲት 12 ሆስፒታል፣ ኤፍቢ ግቢ፣ ናይጄሪያ ኤምባሲ፣ 20 ቀበሌ ፣ አፍንጮ በር ፣ ቀጨኔ ጉቶ ሜዳ ፣ ቤላ ኮሪያ ሰፈር ( ቤላ 05 ) ፣ ጃንሜዳ ፣ ጃንሜዳ መከላከያ እና አካባቢው 👉አለምባንክ ፣ ኢንዲያና ት/ቤት አካባቢ ፣ ታፍ ማደያ ፣ አቃቂ ብሩህ ተስፋ ት/ቤት ፣ ኮፊ ሲቲ ድረስ እና አካባቢው ✅ከጠዋቱ 4፡00-9፡00 👉ፉሪ ፣ አለምገና ፣ ሰበታ ፣ዲማ ፣ ሜታ ፣ ክሬቸር ፣ ኪዳነ ምህረት 👉 ሜታ አካባቢ ፣ ሰበታ ከተማ ፣ አለምገና ሚካኤል አካባቢ ፣ ገዳም ሰፈር ፣ ዳለቲ ኢንዱስትሪ ፣ ዳለቲ ቄራ ፣ ገዳምባ ፣ አለምገና ኢንዱስትሪ እና አካባቢው 👉ዓለምገና፣ዳለቲ እና አካባቢው የኃይል አቅርቦት ይቋረጣል ፡፡ ስለሆነም በአካባቢው የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንኑ በመገንዘብ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡

የአዲስ ኃይል ጠያቂ መስተንግዶ በማንሰራራት ቀን ዛሬ ጳጉሜን 2 በማንሠራራት ቀን አፋር ሪጅን አዲስ የኤሌክትሪክ ኃይል ጠያቂ ደንበኞችን በአንድ ቀን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ አስታወቀ፡፡ አዲስ ቆጣሪ
+2
የአዲስ ኃይል ጠያቂ መስተንግዶ በማንሰራራት ቀን ዛሬ ጳጉሜን 2 በማንሠራራት ቀን አፋር ሪጅን አዲስ የኤሌክትሪክ ኃይል ጠያቂ ደንበኞችን በአንድ ቀን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ አስታወቀ፡፡ አዲስ ቆጣሪ ጠያቂ ደንበኞችን በአንድ ቀን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችል ትራንስፎርመር ተከላ፣ የመካከለኛና የዝቅተኛ መስመር ዝርጋታ አስቀድሞ መዘጋጀቱን የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ሳሊሕ ማኅመድ ገልፀዋል፡፡ ዳይሬክተሩ አክለውም በሪጅኑ ሥሩ ባሉት በሁሉም አገልግሎት መስጫ ማዕከላት አገልግሎት ፈልገው ሚመጡ ደንበኞች በግብዓት አቅርቦት እንዳይቸገሩ የኤስቲኤስ (STS) ቆጣሪ፣ የቆጣሪ መለጠፊያ ቦርድ፣ ኬብል እና ሌሎች ግብዓቶች ተዘጋጅተዋል ብለዋል፡፡ በተያያዘ በዚህ ወቅት በክልሉ ያለውን ከፍተኛ አውሎ ንፋስና ዝናብ ከግምት ውስጥ በማስገባት የኃይል መቆራረጥን ለመቀነስ 122 ኪ.ሜ መካከለኛ መስመር እና 32 ኪ.ሜ ዝቅተኛ መስመር የቅድመ ጥገና ሥራ የተሠራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በዚህም ከሚሌ - ኤሊ ውሃ፣ ከኤሊ ውሃ- አሳጊታ፣ ሳቡሬ፣ ከቦራ - ደዌ፣ ከሰመራ ሰብስቴሽን እስከ ዱብቲ መግቢያ፣ መልካ ወረርና መልካ ሰዲ ከተሞች ኮምፖሳይትና አክሰሰሪ የመቀየር ሥራዎች መከናወናቸውን አብራርተዋል፡፡ በአዲሱ ዓመት በዓል የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝ ለማድረግ በዱብቲ፣ በገዋኔ፣ በአዋሽ 7 ኪሎ፣ በዲጂኦቶ እና በሎግያ አገልግሎት ማዕከላት ሥር የሚገኙ የረገቡ መስመሮችን የመወጠር፣ ለኃይል መቆራረጥ መንስኤ ሆኑ ዛፎችን የመቁረጥ እንዲሁም የትራንስፎርመሮች ዘይት ሙሌት መሠራቱን ተናግረዋል፡፡ ዳይሬክተሩ በሪጅኑ የሚገኙ ደንበኞች ይህን አጋጣሚ ተጠቅመው የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ #የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ማንሰራራት በኤሌክትሪክ አገልግሎት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2018 በጀት ዓመት የኤሌክትሪክ ተደራሽነትበማስፋት፣ 205 አዳዲስ የገጠር መንደሮችንና ከተሞችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ማድረግ ችሏል። 📌ዋናው ግሪድ (የኤሌክትሪክ መረብ) ተደራሽነት:- ከዋናው ግሪድ ጋር በማገናኘት 179 የገጠር ቀበሌዎችና መንደሮች ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል። ይህም የአዲሱ ዓመት አጠቃላይ ተደራሽነት ትልቁን ድርሻ (87.3 በመቶ) ይይዛል። ➡️ኦፍ ግሪድ (የፀሃይ ኃይል) አማራጭ:- ከዋናው ግሪድ ርቀት ላይ የሚገኙ 26 የገጠር ቀበሌዎችና ከተሞች በፀሃይኃይል (Off-grid) አማራጭ የኤሌክትሪክ አገልግሎት አግኝተዋል። 📍በሁለቱም አማራጮች (በግሪድ እና በኦፍ ግሪድ)፡-በጠቅላላው 205 የገጠር ቀበሌዎችና መንደሮችን ለአገልግሎት በቅተዋል። 👉የዕድገት መጠን:- ከባለፈው በጀት ዓመት (155 ቀበሌዎችና መንደሮች) ጋር ሲነፃፀር የ32 ነጥብ 3 በመቶ ዕድገት አሳይቷል። 🔋አጠቃላይ አዲስ ተደራሽ የሆኑትን ጨምሮ እስካሁን በገጠር ኤሌክትሪፊኬሽን አቅርቦት ፕሮግራም ኤሌክትሪክ ተጠቃሚ የሆኑ የገጠር ከተሞችና መንደሮች ቁጥር 7 ሺህ 908 ደርሷል። ​#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት #የብርሃንእምርታ #የገጠርኤሌክትሪፊኬሽን