1 157
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
1 157
#የሃብታም_አባቶች_ምክር
እጅግ የተማረ ግን ድሃ አባት ልጁን '' ትምህርት ቤት ግባ፣ ጥሩ ውጤት ይኑርህ፣ ከዛም ደህና ክፍያ ያለው ድርጅት ውስጥ ተቀጠር '' የሚሰጠው ምክረ ሃሳብ እንዲህ አይነት የህይወት መንገድ ይሄን ይመስላል👇
ትምህርት ቤት➖➡️ ቅጥር➖➡️ ከዛም አነስተኛ የራስን ሞያ መስራት እንደ ( ዶክተር፣ ጠበቃ፣ ወይም የሂሳብ ሰራተኛ...)
የተማረና ሀብታሙ አባት ግን ለልጁ '' ትምህርት ቤት ግባ፣ ተመረቅ ከዛም የራስህን ስራ በመፍጠር ' business ' ገንባ ከዛም ስኬታማ የሆነ ' investor ' ሁን። '' በማለት የሚሰጠው ምክረ ሃሳብ እንዲህ አይነት የህይወት መንገድ ይሄን ይመስላል👇
ትምህርት ቤት ➖➡️ የንግድ ስራ ➖➡️ ገንዘብን ስራ ላይ የሚያውል investor
1 157
ሳይንስ እንዲህ ይላል፦
"ከፍተኛ የአእምሮ ብቃት እና የጨዋታ ለዛ እጅና ጓንት ናቸው"
ባለ ብሩህ አእምሮ ሰዎች ጨዋታ አዋቂ ናቸው፤ ይቀልዳሉ። ከአንስታይን እስከ ሊንከን፣ ከማርክ ትዌይን እስከ ዊንስተን ቸርችል ሁሉም ቁምነገረኞች ናቸው። ደግሞም ተጫዋች ናቸው። ተፈጥሯዊ ስሪታቸው ነው።
ደግሞም አሉ ብልህ ሆነው ፊታቸው የማይፈታ፤ ግንባራቸው የተቋጠረ፤ ስቀው የማያውቁ―"long faced" ይሏቸዋል። እነዚህ exceptions ናቸው።
ለማንኛውም ስለ ጨዋታ እና ሳቅ ከተነሳ ኦሾ እንዲህ ይላል፦
"በአለም ሶስት አይነት ሰዎች አሉ
፩) በሰው የሚስቁ
፪) በራሳቸው የሚስቁ እና
፫) ዝምብለው የሚስቁ"
ኦሾ በመጨረሻ እንዲህ ይላል፦
"ሶስተኛው ደረጃ ላይ ከደረስክ you're enlightened
በርቶልሃል ማለት ነው" (ማህበረሰቡ ግን "እብድ ነው" ነው የሚልህ)
1 157
ርዕስ:- ሰመመን
📝ደራሲ:- ሲሳይ ንጉሱ
✍ዘውግ:- የዩኒቨርስቲ ህይወት
📖የገፅ ብዛት:- 378
ከሲሳይ ንጉሱ የአእምሮ ስራ ሰመመን የሚለው መሳጭ የፍቅር ልበ ወለድ በተለይ ቀደም ባለው ዘመን የትምህርት ቤት የፍቅር ሂይዎት school life ብዙ ትዝታን አንጥፎ ያለፈ ድንቅ ስራ ነው::
ኢትዮጵያዊ ሆኖ ይሄን መፅሐፍ ያላነበበ ጥቂት ነው
ለማስታወስ ያክል ከገፀ ባህርያቶቹ
👉አቤል ጎበዝ ተማሪ እና ትእግስትን የሚያፈቅራት
👉እስክንድር የአቤል ታማኝ ጏደኛ ብስለት ያላቸው ሀሳብ አፍላቂ
👉መ/ር ዮናታን ሰው ሰው የሚሸት ወዝ ያለው ሙሁር
👉ሳምሶም(ጉልቤው)ግብዳ እስፖርተኛ ሆዱን የሚወድ ትምህርቱን ሳይጨርስ የተጫረ...................
እናንተም ጨምሩበት
1 157
ሰመመን
ጠይም ናት ፤ ካውያ ያልነካው ፀጉርዋ ከማጅራቷም ባያልፍ ለማበጠር የሚያስቸግር አይነት አይደለም። ቁመቷ አጭር ነው ፤ አለባበሷ እንደነገሩ ይመስላል ፤ ገና ሲያያት አጠገቧ ካሉት ልጃገረዶች ጋር በሆነ ጨዋታ ትሣሣቅ ነበር። ስትስቅ ጉንጮቿ ስርጉድ ይላሉ። በፈገግታ ጊዜ የሚሰረጉዱ ጉንጮች አቤል ከልጅነቱ ጀምሮ ይወዳል።
ያያት ዕለት፥ ያለ ምንም ሀሳብ ውሎ ማታ መኝታው ላይ አረፍ ሲል በሰመመን አጭር ፣ ጠይም ልጅ የሚሰረጉዱ ጉንጮቿን እያሳየች ልታጫውተው ከተፍ አለች። ያለ ምንም ማመንታት ተቀበላት። ቀን ያየውን ቁመናዋንና አለባበሷን በልቡ ደግሞ አደነቀላት።
አንሶላውን ተከናንቦ፥ አይኑን ጨፍኖ ስትስቅ በሰመመን ተመለከታት። "እየሳቀች የጉንጯን መሰርጎድ በማሳየት ብታስከፍል ዓይኑን የሚያሽ ያለ አይመስለኝም" ሲል በሀሳቡ ደመደመ። ልቡ ውስጥ ገብታ እንድትዝናና ፥ እንድትጫወት ፥እንድትቦርቅ ፥ እንድትተኛ እንድትነሳ ፥ እንደ ልቧ እንድትሆን ፈቀደላት።
ትዕግስት ከዚያን ዕለት ጀምሮ በተፈቀደላት መሠረት ልቡ ውስጥ ገብታ ፥ እግሮቿን አኮማትራ ተቀመጠች ፤ ውላ ስታድር ተንፈራጣ ተቀመጠች።ስታሰልስ በጀርባዋ ጋደም አለች። ስትከርም ጭራሹኑን ሐሳብዋን ጠቅልላ ተኛች።
መጀመሪያ በአቤል ልብ ውስጥ ትምህርቱና ትዕግስት ፀብ ሲፈጥሩ ፥ አቤል ዳኛ ሆኖ ፥"ዕረፉና ተቀመጡ ፥ ልቤ ለሁለታችሁም ይበቃል" አላቸው። ጠባቸው እየከረረ መጥቶ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ሲደርስ ፥ አቤል በትምህርቱ ፈረደና
ትዕግሥትን አነገሳት...
1 157
💍💍ቀለበቱ💍💍
**,10
ምን እንደተፈጠረ እንኩዋን የማታውቀው ሸዋዬ ግራ ተጋባች:: ይባስ ብላ ደግሞ እሌኒ ደውላ ቀጥታ ወደቤት እንዳይሄዱ...ቡና ጋብዛ ትንሽ እንድታቆያት ነገረቻት:: ምንድነው ጉዱ?...ማወቅ አለባት::
ሸዋዬ አንድ የምታውቀው ምግብ ቤት ጋ ስትደርስ በድንገት አጠምዝዛ መኪናውን ራቅ አድርጋ አቆመችና ሙዚቃውን አጠፋችው::
"ነፂ ምን እንደተፈጠረ ልትነግሪኝ ትችያለሽ?" አለች ብስጭትጭት እያለች...እንዲህ አይነት ምሽት ለማሳለፍ አልነበረም እቅድዋ...ከሆነ ደግሞ ምን እንደተፈጠረ ለምንድነው የሚደበቀው?
ነፃነት እንባዋን እየጠራረገች ዝም ብላ ተቀመጠች::
"ነፂ...ሰምተሽኛል?"
"አዎ ሻዊትዬ...ከየት እንደምጀምረው ግራ ገብቶኝ ነው"
"ኢትስ ኦኬ...ከፈለግሽበት ጀምሪ..."
ነፃነት አንዳንዴ በጠራ: ብዙውን እንባ በተናነቀውና ለቅሶ በቆራረጠው ድምጽ የሳምንቱን ታሪክ አንድም ሳታስቀር ነገረቻት::
"ሻዊት በጣም ነው በራሴ ያፈርኩት"
"ለምንድነው የምታፍሪው" ሸዋዬ ድምጽዋን ከፍ አድርጋ...መናደድዋ ያስታውቃል::
"ምን ማለትሽ ነው?"
"ዌልልልልል..." አለች ሸዋዬ በረጅሙ ተንፍሳ:: "ማንም ሴት ብትሆን ትጠራጠራለች...ሶ ሁዋት ኢዝ ዘ ቢግ ዲል?" እንግሉዝኛዋ ይሽቀዳደም ጀመር...ድሮም ስትናደድ...
"እና አላጠፋሽም ነው የምትይኝ?"
"እኔ ብሆን ቀለበቱን ሲሰጣት ነበር ጉሮሮዋን የማንቃት...ያኔ ሰውም ሳይሰማ እዛው ጣጣችሁን ትጨርሱ ነበር...እዛ ላይ ነው ጥፋትሽ"
"አይ ሻዊት..." የነፃነት ፈገግታ በዝናብ መሀል ብልጭ የምትል የፀሀይ ብርሀን ፍንጣቂ መሰለ::
"ኖ-ኖ-ከምሬ ነው...እነሱም ሰዎች ናቸው እንጂ መልአኮች አይደሉ...ይሄ ሁሉ ያዙኝ ልቀቁኝ አይገባኝም"
ነፃነት አንድ ወገን በማግኘትዋ ደስ አላት:: አዎን...የድሮዋ እብድ...ቁም ነገር የለሽዋ ሻዊት ዛሬ ከሁሉም በልጣ ተገኘች::
"አዎን...ግን መኩ በጣም ተናዶብኛል...እንጃ...." ነፃነት ስጋት ፊትዋ ላይ ይነበባል::
"አቦ ተይኝ....ነይ ይልቅ ቡና እንጠጣ...አንቺም ምናምን ቅመሺ" ሸዋዬ የነፃነትን እሺታም ይሁን እምቢታ ሳትጠብቅ ከመኪናው ወረደች:: ነፃነትም ተከተለቻት::
መኮንን በመንገዱ የሚያልፉት መኪናዎች መብራት ግድግዳዎቹ ላይ የሚፈነጥቃቸውን ስዕሎች እያየ በረጅሙ የሶፋ ወንበር ላይ በጀርባው ተንጋሏል:: ያ የሚወደው እንቅልፉ ዛሬ ሸፍቷል:: ነፃነት ምን እያረገች ትሆን? ገና ከአሁኑ ውል ትልበት ጀምራለች::
ላለፉት ስድስት እመታት አይኑን የምትሞላ ሌላ ሴት እንኩዋን አይቶ አያውቅም:: እውነት ፍቅር እውር ነው ወይስ እውር ያደርጋል? እንግዲህ እንቅልፍ ካልወሰደው ይፈላሰፍ እንጂ..."የኔ ሼክስፒር" እያለች ነፃነት የምትተነኩሰው ትዝ አለውና ፈገግ አለ::
<<አይ ነፂ...>> በረጅሙ ተነፈሰ:: ድምፅዋ ናፈቀው:: ምን እያረገች ይሆን? ስልኩን በዳበሳ ከትንሹ ጠረጴዛ ላይ አነሳና ሰአቱን አየ...እኩለ ሌሊት ሆኖዋል:: እንዴት እስከአሁን አስችሏት አልደወለችለትም?
ነፃነትና ሸዋዬ ምሳ አይሉት እራት በልተው የባጡን የቆጡን እያወሩ ቡናቸውን ይጋታሉ:: የነፃነት ዘና ማለትና ለቅሶ ማቆም ሸዋዬን አስደስቷት ስለፍቅር ጀብዱዎችዋ እየለፈለፈች የባሰውን ታስቃታለች::
<<ይህን ሁሉ ጊዜ ሳውቅሽ...እንዲህ አይነት ሰው መሆንሽን አላውቅም ነበር...አሁን ገና ለምን ሰላምዬ እንደምትወድሽ ገባኝ" አለች ነፃነት ቡናዋን ፉት እያለች::
<<ነፂ ነገር ለማብረድ ምናምን አይደለም...ግን ሰላሚቱ እንዳንቺ የምትወደው ሰው የለም...ደግሞ ደግ ልብ አላት:: እኔን ማንም ዞር ብሎ የሚያየኝ ሰው ባልነበረበት ጊዜ ነው አብሬያት ስለምሰራ ብቻ የቤቷን በር የከፈተችልኝ>> ዓይንዋ እንባ አቀረረ::
<<ሻዊትዬ አንድ ነገር ልጠይቅሽ? ካልፈለግሽ አትንገሪኝ>>
<<እሺ>>
<<ስለወንድምሽ ማውራት አትፈልጊም...ነገር ግን ከእሱ ጋር የተያያዘ ነገር ስታወሪ የውስጥ ህመምሽ ፊትሽ ላይ ይነበባል...እንዳንዴ ከሰው ጋር ማውራት እኮ ጥሩ ነው>>
<<አዎ ነፂ...ግን ምን ሆኖ እንደሞተ ታውቂያለሽ?>>
<<ታሞ እንደሆነ አውቃለሁ...ከእግዜር ከመጣ ምን ይደረጋል ሻዊትዬ?>>
ሻዊት እንባዋን መቆጣጠር አቃታት...ዛሬ የለቅሶ ቀን ነው እንዴ? ነፃነት ምን እንዳረገች ስላልገባት ደነገጠች::
<<ይ-ቅ-ር-ታ ሻዊትዬ...>> እንባዋ ተሽቀዳደመ::
<<አ-ን-ቺ ደ-ግ-ሞ ም-ን አ-ረ-ግ-ሽ?>> እነዛ ቀያይ አሳዛኝ ጉንጮችዋ በርበሬ መስለዋል::
<<እ ኔ ን ጃ...ብ ቻ ይ ቅ ር ታ>> በጠረጴዛው ላይ ተንጠራርታ የሸዋዬን እጅ ዳበሰች::
<<እኔ ይቅርታ ልበል እንጂ...አንቺን ማፅናናት ሲኖርብኝ...ነፂ ወንድሜ የሞተው በኤድስ ነው...ለዚህ ነው የሚያንገበግበኝ...እንዴት ያለ ደግ ሰው ነበር መሰለሽ...ሞት ለእሱ አይገባም ነበር>>
<<ኦኦኦ..ሻዊትዬ አላወኩም ነበር እኮ!>>
<<አዎን...ብዙ ሰው አያውቅም:: ለምን ሚስጥር ማድረግ እንዳስፈለገ ግን አይገባኝም...እንዲያውም ለሌላው ትምህርት ይሆን ነበር>>
<<አይይይይይ....የእኛ ሰው ከኔው ጀምሮ ከትምህርቱ ይልቅ ወደ ፍርሀቱና ሽሽቱ እናዘነብላለን...ስለዚህ ይገባኛል>>
<<ወንድሜም እንደሱ ነበር የሚለው...>>እኔስ ሂያጅ ነኝ...አንቺን ግን <<በኤድስ የሞተው ልጅ እህት>> ብለው ቅፅል ስም ይሰጡብኛል <<...እህህህህ>> እንባዋን እየጠረገች በቁጭት እራስዋን ነቀነቀች::
<<አይዞሽ ሻዊትዬ...>> ነፃነትም በለቅሶ አጀበቻት::
<<የሚቆጨኝ አንድም ቀን ለራሱ ሳይኖር...ለቤተሰብና ለጉዋደኛ እንደባከነ መሞቱ ነው...ሰው በሚፈልግበት ሰአት ግን አጠገቡ የተገኘ የለም...ሰው እንዳማረው እንዳማረው ነው የተቀጨው>>
እንባቸውን እየጠራረጉ በዝምታ ተቀመጡ:: ትንሽ ሲረጋጉም ሽዋዬ አስተናጋጅዋን ጠርታ የበሉበትን ዋጋ ለመክፈል ቦርሳዋን ስትከፍት ነፃነትም ቦርሳዋን አነሳች::
<<አርፈሽ ተቀመጪ...>> ሸዋዬ ገላመጠቻት::
<<ሆሆሆይ...ኧረ እኔም ለመግደርደር ብዬ ነው እንጂ ገንዘብ መያዜንም እንጃ...የዛሬን ውሎዬን ዝም ነው>>
ፈረንጅዋ አስተናጋጅ ሸዋዬ በደጎሰቻት ወፍራም ጉርሻ ተደስታ እየተፍለቀለቀች ምስጋናዋን ደርድራ ስትሰናበት ሽዋዬ ወደ ነፃነት ፊትዋን አዞረችና
<<ብቻሽን እንዳትሆኚ ዛሬ አብሬሽ ልደር?>>
<<ብቻሽን እ-ን-ዳ-ት-ሆ-ኚ?>> ግራ ተጋባች ነፃነት::
ሸዋዬ በረጅሙ ተነፈሰች:: የመኮንንን እነእሌኒ ቤት መሄድ አሁን እንዴት ነው የምትነገራት?
<< ኦኬ ነፂ...እኔን ታቂኛለሽ...ሚስጥር... ምናምን...ይሄ ይነገራል...ይሄ አይነገርም...ገለመሌያችሁ አይገባኝም...>>
<<የምትነግሪኝ ነገር ካለ ንገሪኝ>> ኮስተር አለች ነፃነት::
<<ኦኬ...መኮንን ለዛሬ እነእሌኒ ቤት ነው የሚያድረው>>
አላለቀም
ታሪኩን አንበብበው ከወደዱት 👍👍👍React ይጫኑት
1 157
ህልም
አንድ ቀን ጥዋት ሚስት በጠዋት ትነሳና
እንደዚህ አለች
"በህልሜ በፍቅረኛሞች ቀን የዳይመንድ ሀብል ስትሰጠኝ አየሁ ።"
"የህልሜ ፍቺ ምን ይመስልሃል ?"
"ምን አልባት ዛሬ ምሽት ታገኚ ይሆናል....... ።" አላት ።
በዚያን ምሽትም ባልም ወደ ቤት በሽልማት ወረቀት የተጠቀለለ ትንሽ ዕቃ ይዞ ይመጣና ለሚስቱ ይሰጣታል ።
በጣም በደስታ ተቀብላው ከፈተችው
ስትከፍተው በወረቀት ላይ የተፃፈ "የህልም አፈታት" የሚለውን መፅሀፍ አንብቢው ይላል።
😄😄😄
1 157
💍💍ቀለበቱ💍💍
......9
✍.....መኮንን ሰፊው ጎዳና ላይ አይኑን ተክሎ መኪናዋን ሲያከንፋት በረከት አጠገቡ መኖሩን የዘነጋ ይመስላል:: ለብዙ ደቂቃት ሁለቱም ዝምታቸውን ተጎናጽፈው እንደተጓዙ መኮንን ወደ ቤንዚን መቅጃ ታጥፎ መኪናውን ጥግ ይዞ አቆማትና በረጅሙ ተነፈሰ::
<<በረከት ተከትለኸኝ ስለመጣህ አመሰግናለሁ...ግን በጣም ደህና ነኝ...እሌኒ ጋ ልመልስህ::>>
<<አንተስ ወዴት ልትሄድ ነው?>>
<<እኔንጃ...እቤት ማደር ግን አልፈልግም...ትንሽ ጊዜ ለብቻዬ እፈልጋለሁ>>
<<ተው አይሆንም...ንፋስ ማስገባት ይሆናል>>
<<አይይይ...አሁንማ ምኑ ውስጥ ነው ንፋስ የሚገባው>>
<<አሁን ስለተናደድክ ነው...ረጋ ብለህ አስብበት>>
<<እኮ! አሁን ከአንድ ጣራ ስር ተኳርፎ መጋፋቱን ጠልቼ እኮ ነው...ወይም ጭቅጭቅ ተነስቶ የሚጸጽተኝ ነገር እናገራትና...>> ግራ በገባው መንፈስ እየዋዠቀ ጽጉሩን በጣቶቹ አረሰው::
<<ቆየኝ አንዴ...>> በረከት የእጅ ስልኩን እየደወለ ከመኪናው ወርዶ በሩን ከሁዋላው ጠረቀመው::
ከመኪናው ጀርባ እየተንጎራደደ ሲያወራ መኮንን በፊት ለፊቱ መስታወት ውስጥ እያየው የሚለውን ባይሰማም ስለሱው እንደሚያወራ ገብቶታል:: ይቺ ቀን...ይቺ ህይወት...የራስዋ ቀለበት ውስጥ አስገብታ እያሽከረከረችው ነው::
ዛሬ ጠዋት ሲነቃ የነበረውን ደስታና ጉጉት አሰበና በረጅሙ ተነፈሰ:: ያቺ ነፂስ እንዴት ሆና ይሆን? <<እስዋ እኮ ክፋት አታውቅም ነበር>> ብሎ አሰበና ልቡ እዝን አለ:: በረከት አጠገቡ ሲቀመጥ ከነጎደበት የሀሳብ ኮረኮንች ተመልሶ መኪናውን አስነሳ::
<<ከእሉ ጋር ተነጋግረናል...ሁኔታዎች እስኪረጋጉ እኛ ቤት ታርፋለህ>>
<<ለምን?...ሆቴል እከራያለሁ>>
<<ኖ...ኖ...እኛ እያለን? ደግሞም ሆቴል ነገር ማባባስ ነው>>
<<በራሴ ጣጣ እናንተን ማስቸገር አልፈልግም>>
<<እንዴ...አንተ እኮ አልጠየከንም...እኛ ነን የወሰነው>>
መኮንን አመነታ::
<<መኩ ሌላ ምርጫ የለህም...እንዳልከው ጊዜ መስጠቱ ጥሩ ነው:: ስለዚህ ሌላ ቦታ አትሄድም...ጉዋደኞችህ ጋ ታርፋለህ>>
<<ግዴታ ነው?>> አለ መኮንን ሳቅ ብሎ...በረከትም ፈገግ ሲል በማየቱ ደስ አለው::
<<አዎን ግዴታ ነው>> አለ ኮስተር ብሎ <<ጄኔራል እሌኒ ያስተላለፉት ትእዛዝ...>> ተሳሳቁ::
<<ይልቅ አሁን ወደቤትህ ሄደን ቅያሪ ልብስ አምጣ>>
መኮንን ሰፈሩ ሲደርሱ ልማድ ሆኖበት በአይኑ የነፃነትን መኪና በአይኑ ፈለገ...የለችም:: ብትኖር ይሻል ነበር? እሱም አያውቀውም:: የተደበላለቀ ስሜት...በጣም ተናዶባታል...ሊያናግራትም አይፈልግም...ግን ቢያያት ደስ ባለው ነበር...እንደው ደህና መሆንዋን ቢያውቅ...እስዋን የሚጠላ አንጀት የለውም...ግን እኮ በጣም የሚያስቆጣ ነገር ነው ያረገችው...ምን አሳሰባት ግን? አህህ...መቼ የምትናገረውን ሰማና...መንጭቆዋት አይደል የወጣው...በእሱ ግን አይፈረድም...እስዋ ነች ጥፋተኛ::
ከራሱ ጋር እየተሙዋገተ የፊት ለፊቱን በር ከፍቶ ወደመኝታ ቤቱ አመራ:: ደግነቱ ነገ ቅዳሜ ነው...ብዙም ኮተት አያስፈልገውም:: ለመረጋጊያም ፋታ ይሰጠዋል:: ትንሽ የምትንጠለጠል ሻንጣ ከቁም ሳጥኑ መደርደሪያ ላይ አወረደና አንድ ሁለት ካልሲዎች፣ የውስጥ ልብሶች፣ ጂንስ ሱሪና ካኔቴራዎች። ከመታጠቢያ ቤት ደግሞ ፎጣ፣ የጥርስ ብሩሽ፣ የጺም መላጫ፣ ማበጠሪያና የብብት ቅባት ወረወረና ዚፑን ዘግቶ እየተጣደፈ ወጣ::
ነፃነት ሻንጣ ይዞ ሲወጣ ብታገኘው ምን ትል ይሆን? በረከትም እሌኒ ለሸዋዬ ደውላ ነፃነትን እንድታዘገያት እንደምትነግራት አልነገረውም...አላስፈላጊ ዝርዝር ነው::
ነፃነት ሸዋዬና አቤል ከሰላማዊት ቤት እንደወጡ
"ቤቢዬ...በቃ አንተ ወደቤት ሂድ...እደውልልሀለሁ" አለች ሸዋዬ ጉዋደኛዋ ወገብ ላይ እየተጠመጠመች::
"አብራችሁ ሂዱ...እኔ ደህና ነኝ"
"በያ አስገድይኝ" አለች ሸዋዬ "እቤትዋ አድርሺያት ነው ያለችኝ እማማ እሌኒ...እንደውም ቁልፍሽን አምጪ...እኔ ነኝ የምነዳው"
አቤልን ስማ አሰናበተችውና ወደ ነፃነት መኪና አመሩ:: ቅድም ነፃነት በቁጣ ፈረስ ላይ ተፈናጣ የተከለከለ ቦታ ላይ አጉል መኪናውን አንጋዳ ማቆሙዋን ሸዋዬ አይታ በመገረም አንገትዋን ነቀነቀች::
"ወይ ጉድ...እድለኛ ነሽ ሳይቀጡሽ መድረሳችን"
"አይ እድለኛ" እንባዋ አቀረረ የነፃነት::
"ማ-ለ-ቴ..." እንዴት አረፍተ ነገሩን እንደምትጨርሰው ግራ ገብቷት አንጠልጥላ ተወችው::
በሸዋዬ ሹፌርነት መንገድ እንደጀመሩ ያንዣበበውን የዝምታ ጥላ ለመግፈፍ ሸዋዬ ሙዚቃ ከፈተች:: ጥበቡ ውርቅዬም ቅድም ነፃነት አፉን ከዘጋችበት ቦታ ቀጥሎ አሳዛኝ ድምጹን ያንቆረቁረው ጀመር::
"ያየን እስኪደነቅ...ማመን እስኪያቅተው
እንዲህም አይነት ፍቅር...አለ ወይ እስኪል ሰው
ሳይቸግረን ያኔ...ከአይን ውስጥ ገብተናል
ጥላው ሄደች ሲባል...አሁን ሰው ምን ይላል..."
የነፃነትም እንባ ሊያጅበው በጠይም ጉንጮችዋ ላይ መንቆርቆር ሲጀምር ሸዋዬ ደንገጣ ልታጠፋው እጅዋን ዘረጋች::
"ተ-ተ-ይ-ይ-ይ-ውውው" አለች ነፃነት ሲቃ በተናነቀው ድምጽ::
"በትንሽ ትንሹ ...አርገው ከወሰዱት
አይገልም ይባላል...መርዝም ከለመዱት
ባይሆን ቀስ በቀስ...ውስጤን እንዳይከብደው
ባክሽ ትንሽ ቆዪ...ስቃዩን ብለምደው"
ምን እንደተፈጠረ እንኩዋን የማታውቀው ሸዋዬ ግራ ተጋባች:: ይባስ ብላ ደግሞ እሌኒ ደውላ ቀጥታ ወደቤት እንዳይሄዱ...ቡና ጋብዛ ትንሽ እንድታቆያት ነገረቻት:: ምንድነው ጉዱ?...ማወቅ አለባት::
አላለቀም
አብሮነታችሁን በ Like አሳውቁኝ
1 157
…
“በሰው ልጆች ከንፈር ላይ እጅግ ውብ የሆነው ቃል“ እናቴ ”የሚለው ሲሆን ፤ እጅግ በጣም የሚያምረው ጥሪ ደግሞ “ እማ ”የሚለው ነው ፡፡ ቃሉ በተስፋ እና በፍቅር የተሞላ ፣ ከልብ ስር የሚወጣ ጣፋጭ እና ደግ ቃል ነው።
… እናም እናትነት የሁሉም ህልውና ምሳሌ ፣ በውበት እና በፍቅር የተሞላ ዘላለማዊ መንፈስ ነው። ”
--
Broken Wings
Kahlil Gibran
1 157
እየተጣደፍኩ ነበር፤
የሆነ የማገባውን ሰው ፍለጋ ፣ የሆነ ወድጄው ያልፈለገኝን ለመርሳት፣ የሆነ ፈልጎኝ ያልፈለኩትን ለመውደድ ትግል ላይ ነበርኩ ።
"አለም ላይ ያገባ እና የወለደ ብቻ ነው እድለኛ" እያልኩ ነበር።
ፍላጎቴን ዳር ለማድረስ እየተውተረተርኩ ነበር፣ የቤተሰቤን ውትወታ ለመቋጨት ስጥር ምርጫዬን እየቀነስኩ ነበር ። የማገኘውን ሁሉ ለባልነት እየመለመልኩ ነበር ።
ልረጋጋ አልቻልኩም ነበር ።
ስመዝን ነበር የምውለው ።
የሚሆን የመሰለኝን ግለሰብ ጥያቄ ማስተናገድ ህልሜን እውን የሚያደርገው ስለሚመስለኝ ላለማንገራገር እሞክር ነበር ።
"የፍላጎቴ መናር የምፈልገውን እያራቀው ይሆን !?
ፍላጎቴ ላይ ሙጭጭ ማለቴ እያዳለጠኝ ይሆን?፣
አይኔ ላይ ያለው ጉጉት እያራቃቸው ይሆን?፣
እጅግ መፈለጌ ተፈላጊ መሆኔን እያስረሳ ይሆን?
ብቻ ሩጫዬ ከድካም በቀር ለውጥ አላመጣም ነበር ። "
የሆነውን ሁነት ሁሉ ፣ እንቅስቃስዬን ሁሉ፣ ህመሜን ሁሉ ፍላጎቴን አንድ ሳላስቀር ትልቁ ግራር ስር ለማይጠፉት ሞገሳም አባት አጫወትኳቸው ።
ከአፍታ ዝምታ በኋላ
<<ልጄ
አይዝሽ.. አይዞሽ ..ሁሉም ጥሩ ይሆናል
ራስሽ ላይ ደግሞ ትኩረት አድርጊ ፣ አትጣደፊ ፣ ህይወት በጥድፊያ አይሳካም ። ያሉሸን በረከቶች ተመልከቺ ፣
ረጋ በይ ሌጄ ፦
ሁሉም በግዜው ይሆናል ። በሩጫ ጥሩ ህይወት አይያዝም ፣ ሩጫ ማስተዋልን ይነጥቃል ፣ መጥፎ ህይወት እና ልምድ ውስጥ ይከትሻል ።
ረጋ በይ ልጄ ።
ልታሳኪው የምትፈልጊው ነገር ውጤት ላይ አትመሰጪ ፣ ውጤት ያለ ሂደት አይመጣም ። ከመጣሽበት የምትሄጂበት መንገድ ቅርብ አይሆንም ።
አይዞሾ ልጄ ሁሉም ይስተካከላል ።
ላለሽ በጎ ነገር አመስግኚ ፣
የምትፈልጊውን ነገር በትህትና አምላክሽን ተንበርክከሽ ጠይቂ ፣ ቀጥሎ በእርጋታ ጠብቂ ፣ ከዛ ለፀሎትሽ መልስ ታገኛለሽ... የሰማይ አባትሽ የሚጠቅምሽን ነገር ሊከለክልሽ አይችልም።
እሺ ልጄ
ደሞ
ያለሽ ከሌለሽ ይበልጣል። >>
Adhanom Mitiku
1 157
ያሳዝኑኛል፦
ሁሉ ነገር ላይ ክችች የሚሉ ፣ ሁሉ ነገር ላይ እውቀታቸውን እና ያላቸውን ነገር አንዲታይላቸው የሚፍጨረጨሩ ፤ ጥቃቅን ነገር ላይ ሳይቀር እየተከታተሉ የሚነዛነዙ ።
የማይስቁ ፣ ሁሉን ነገር ከክብር ጋ የሚያይዙ ፣ ሁሌ ምንም ሁኔታ ውስጥ ቁጠባ ፣ እቅድ ምናምን እያሉ ወዛ ፈዛዛ ጣልቃ የማያስገቡ ።
የሰሩትን ፣ የነኩትን ሁሉ ለሁሉም የሚያትቱ ፣ የጠሉትን ፣ የማይወዱትን ሁልጊዜ የሚከታተሉ ፣ የሚያጣጥሉ ።
ስላላቸው ነገር ደስ የማይሰኙ ጌታ ከእናንተ ጋ ይሁን 🙏
ደግሞ ሌላ ❤
ጨዋታ የሚገባው ፣ ፈገግታ የማይለየው ፣ ከት ከት ብሎ የሚስቅ ፣ ነገር የማያከር ፣ ከልግስና ጋ ያልተጠማመደ ፣ ይቅርታ የሚያደርግ ፣ የሰው ልጅ ሁሉ ክብር ይገባዋል የሚል
ባለው የሚደሰት ፣ ጉራው አብሮት ያለውን ያማከለ ፣ በትንሹ ፣ በትልቁ የማይዋሽ ፣ በትንሹ ፣ በትልቁም የማይዶከክ ፣ እራሱን ከሌላ ጋ የማያወዳድር ፣
ሲቀለድበት የሚስቅ ፣ የታባቱ ብሎ ምን ይመጣል ብሎ ራሱን ሬስቶራንት ወስዶ ምስር ወጥ የሚጋብዝ ፣ ትችት የማያስደነግጠው ፣ ለጠላቱም የሚያዝን ።
የካደችው ፍቅረኛ ተጎሳቁላ ሲያገኛት የሚያዝንላት ፤ አምሮባት ሲያይ እሰይ ከእኔ ጋ ብትሆን ታክ ነበር ብሎ የሚያላግጥ
የምድር ህይወት ከክብደቷ በላይ አትከብዳችሁም እና ይመቻቹ ❤
አሉ ደሞ 😥
ሱስ ያስበለጣቸው ፣ያፈዘዛቸው ፣ ቀፋይ ያደረጋቸው ፣ያጎሳቆላቸው ፣ ያጠወለጋቸው ፣ ሞገስ አልባ ያደረጋቸው ፣ ነገ የሚባልን ነገር የገደለባቸው ፤ ህልማቸውን የበላባቸው ፤
ጨርሳቹ እጅ አትስጡ ፣ ትንሽ ታገሉ ነገን ማን ያውቃል 🙏😍
ደሞ ሌላም አሉ❤ ፦
ዝም ብለው የሚወዱ ፣ መስጠት ፣ ማድረግ ፣ ማገዝ ግዴታ የሚመስላቸው ፣ advantage ሲወሰድባቸው የማይረዱ ፣ የሚያምኑ ፣ ለማጣጣል የማይጣደፉ ፣ መውደድ ላይ የሚያተኩሩ ፣ ነገር የማይገባቸው ፣ ክፉ ክፉ የማይታያቸው፣ ሁሉንም የሚያቆላምጡ ፣ ለወደቀ ፣ ለተሸነፈ ልባቸው የሚራራ ፤ የሚወደድ ነፍስ ጌታ አዳልቶ የቸራቸው እናንተ ደግሞ ብዙ ተባዙልን🙏🙏
አሁን በበዓል ይጠጣል እንጂ ይፃፋል 😥
1 157
💍💍💍.....ቀለበቱ...??💍💍💍
........ 7
።
📖📖መልካም ንባብ📖📖
✍....<<ዛሬ መቼም ገደለችን>> አለች ነፃነት ሰዓትዋን እያየች: ከሰላማዊት ቤት ደጃፍ ሲደርሱ::
<<ታዲያ ምን ለውጥ አለው...ጉዋደኛሽ ሁሌም ነጭናጫ ነች።>> አለ መኮንን እየሳቀ::
"ዋ...ዛሬ ናይስ ሁንላት...ኦኬ ቤቢዬ?" አለች። እየተለማመጠች::
ወዲያው ሰላማዊት የሁዋለኛውን በር ከፍታ መኪናው ውስጥ እየገባች
<<እናንተ...ጉደኞች ናችሁ...የት ጠፋችሁ
?>> አለቻቸው ።
<<እግዚያብሄር ይመስገን!>> አለ መኮንን የተንኮል ሳቁን እየሳቀ:: ቀጥሎም <<እባክሽን በሩን ቀስ ብለሽ ዝጊው>> ነፃነት ጎሸመችው::
<<አዪዪዪዪ...ደሞ ለዚህ ድብኝት መኪናህ>>
<<ኦ ይቅርታ ነፂ...ዛሬ ከሚስቴ ባትበልጭም አምሮብሻል>>
<<ከ-ሚ-ስ-ቴ???>> አለች ሰላማዊት ድምፅዋን ከፍ አድርጋ። ወዴት እየሄደች እንደሆን ገብቶቷል:: ሰላማዊት የሁለቱን ሳይጋቡ አብሮ መኖር በግልፅ ነው የምትቃወመው:: ለወንድ ገነቱ ለሴት ልጅ ግን ከንቱ ነገር ነው ትላለች::
<<አዎን ልክ ነሽ...ሚስትነት ያንሳታል>> አለና የነፂን እጅ ሳብ አርጎ ሳመው::
<<ሆሆሆይ... ሰውየው አረ መንገዱን እያየህ ንዳ...እኔም ለእናቴ ልኑርላት::>>
"ቂቂቂቂ...ክርክር አይሰለቻችሁም?" አለች ነፃነት መጨቃጨቂያ ሰበብ አለማጣታቸው ገርሟት::
ዘግይተው ቢደርሱም የሙዚቃው አዳራሽ ዙሪያ የተደረደሩት ክብ ጠረጴዛዎች ግማሾቹ ባዶ ናቸው:: መኮንን የነፃነትን እጅ ይዞ ወደአንደኛው ጠረጴዛ አመራ:: ገና አዲስ የወጣ የአማርኛ ዘፈን በሰፊው ተከፍቶ አዳራሹን ያናጋዋል::
<<ያ ሁሉ ጥድፊያ ለዚሁ ነው አይደል?>> አለ መኮንን ሁለቱንም እያየ::
<<ግን የኛ ዘፋኞች መቼ ነው በጊዜ የሚገኙት?>> ነፃነት ሰአትዋን አየች።
<<ለነገሩ ቆነጃጅቱን ማየቱ ራሱ...>> የሰላማዊትን ግልምጫ ሲያይ ሳቁ አፈነው ።
<<ዋ! አንገትህን እንዳልሰበረው>> ነፃነት ዛተች::
<<እኔ አንቺን ብሆን ወደጀርባው ነበር የምጠመዝዘው>>
<<እሱማ ጥሩ ነበር...ያለመሳቀቅ በደንብ እንዳያቸው>>
ሶስቱም ከት ብለው ሳቁ::
መኮንን መጠጥ ሊያመጣላቸው ሲሄድ ነው ሰላማዊት እንደሻው ከፊታቸው ካለው ጠረጴዛ አሻግሮ ሲያያቸው ልብ ያለችው:: በስሱ ፈገግ ብላ ወደነፃነት ዞረችና
<<ነፂ ቀስ ብለሽ ከፊት ለፊቴ ያለውን ጠረጴዛ ቼክ አርጊ>>
<<ቀልጣፋዋ ጉዋደኛዬ...ገና ካሁኑ>> ነፃነት መኮንን በአይንዋ የምትፈልግ መስላ እንደሻውን ቃኘችው:: አይኑን ሰላማዊት ላይ ተክሎ እስዋን አላያትም::
<<ኧረ አፍጦብሻል... ሽበላ ነው>>
<<አይይይይ... እስቲ ገና ይገመገማል... ሸፋፋ ቢሆንስ>>
"ቂቂቂቂቂ..." ሁለቱም ተሳሳቁ::
ሰላማዊትና እንደሻው የአይን እንካ ሰላንቲያውን አጦፉት:: እሱም የተቀመጠው ከአንድ ወንድና ሴት ጋር ነበረና እንደስዋው አጃቢ መሆኑን ገምታለች:: በድንገት አብራው የተቀመጠችው ሴት <<ውርዬዬዬ>>አለች።
ሰላማዊትን እያየች አፍዋን ይዛ:: በድንገት ተነስታ ወደነሱ ተወረወረች:: ደግማ <<ውርዬዬዬ አይደለሽ...ውርዬ ነጋሽ >>
መኮንን ይቺን አግኝቶ ነው...ድምፁን ቀስ አርጎ <<ውሮ ቂቂቂቂቂቂ>> ነፃነት ቆነጠጠችው:: እስዋም ግን ሳቅዋ መቷል::
ሰላማዊት እሌኒን ትንሽ አተኩራ አየቻትና
<<ጩኒኒኒኒዬዬዬ...>> ብላ ላይዋ ላይ ተጠመጠመች:: ካዛማ ምኑ ቅጡ...የሰፈራቸው ሰው የህይወት ታሪክ አንድ በአንድ ይተነተነው ጀመር:: መኮንንም፣ ነፃነትም፣ በረከት እና እንደሻውም ተረሱ::
<<ጉዋ...ጉዋ...ጉዋ...ድም...ድምድምድም>> በሩ ተንጓጓ::
ሰላማዊት፣ እሌኒና በረከት ተያዩ::
<<እንዴ! ማነው እሱ እንዲህ...>> ሰላማዊት ፊትዋን አኮሳተረች::
<<ግውግውግው...ድምድምድምድምድምድምድም>> በሩ የሚገነጠል ይምስል ተርገበገበ::
ሰላማዊት ልትከፍት ወደበሩ ስትሄድ በረከት ተከተላት...ለማንኛውም..የሽብር ኩዋኩዋታ ይመስላል...አሊያም የፖሊስ::
<<እንዴዴዴዴ?>> አለች። ሰላማዊት በበሩ ማጮለቂያ ቀዳዳ አጨንቁራ እያየች::
<<ማነው እሱ?>> አለ በረከት::
<<ነፂ ነች፣ ምን ታደርጋለች አሁን?..ደሞስ...>>
<<ድምድምድምድምድምድምድምድምድምድምድምድምድምድ>>
አሁንም ሶስቱ ተያዩ... ባልተጠበቀችበት ሰዓት ከመምጣትዋ..በሩን መቀጥቀጥዋ...::
ሰላማዊት በሩን ገርበብ አድርጋ ከፈትችና...
<<ነፂ...ምን...?>>
ነፃነት አላስጨረሰቻትም:: ወደውስጥ አሽቀነጠረቻት:: ሰውነትዋ በንዴት ይሁን በቅናት ይንቀጠቀጣል::
<<አንቺ...አንቺ...አንቺ...ነሸ...>> ስድቡ ከአፍዋ አልወጣ አላት:: ድሮ የሰፈር ባለጌ ልጆች ሲሰዳደቡ የሚሰቀጥጣት ስድብ ነበር:: ቀጠለች...
<<ወንድ አጥተሽ ነው ከመኩ ጋር የምትጋደሚው አንዳች...>>
<<ም-ን-ን-ን-ን-ን-ን-ን? ? ?>> ሰላማዊት ጭንቅላትዋን መርዶ እንደተነገረው ሰው በሁለት እጆችዋ ያዘች::
<<ዛሬ ጠዋት አይቻችሁዋለሁ...ቀለበት ሲሰጥሽ...ደግሞ ሰሞኑን...>>
<<ውይይይይ...ያንቺን ቀለበት?" ሰላማዊት ጩኸትዋን አቀለጠችው::
<<እረ ቆይ...ረጋ በሉ!>> አለች እሌኒ ከተጋደመችበት ቀስ ብላ እየተነሳች:: ባሏ ሊደግፋት ሮጠ::
እንዴ? የስዋን ቀለበት... በረከትና እሌኒስ ምን ይሰራሉ እዚህ? በቁጣ ፈረስ ስትጋልብ መኖራቸውን እንኳን ልብ አላለችም ነበር::
ወዲያው መኮንን ገባ::
<<ምን ሆነሻል?>> አይኑን ነፃነት ላይ አፍጦ... መልስ ሲያጣ ወደሰላማዊት ዞረና
<<ምን ተፈጠረ?>>
የሁለቱም እንባ ይዝረከረካል:: አንደኛዋ የፀፀት...ሌላኛዋ የትዝብት::ግራ የገባው መኮንን በረከትን አየው እሱም በትከሻው የእንጃ ምልክት አሳየው:: <<እፎይይይ>> አለ በልቡ:: የሞተ ሰው ቢኖር በረከት ያውቅ ነበር:: አፍዋን ይዛ ወደ ቆመችው እሌኒ ፊቱን አዞረ::
<<እሌኒ...ምንድን ነው ጉዱ?>>
እንዴት ብላ ነው የምትነገረው? ለወሬ የማይመች ነገር...ስታመነታ ሰላማዊት ቀደመቻት::
<<እህ-እህ-እህ-እህእህእህ...ነፂ ካንተ ጋር ተኛሽ ብላ ጠረጠረችኝ...እህ-እህ-እህ...እኔን ነፂ?..እኔን?...ድሮስ ባዳ አይደለሁ...እህእህእህ>>
<<ምምንንንንንንንን? ?>> መኮንን አንባረቀ:: ፊቱን በመፀየፍ አኮፋትሮ ወደነፃነት ዞረና መልስ ሲያጣ ትከሻዋን ይዞ ወዘወዛት::
<<ምንድን ነው ያልሽው???>> እንደዚህ ተቆጥቶ በጭራሽ አይታው አታውቅም::
አላለቀም
ደጋግሜ ተናግሪያለሁ እጃችሁን አይጎዳም አንድ ጊዜ ብቻ 👉 👍 ጫን ማድረግ
1 157
እመንገድ ላይ አየኋት ። ወፍራለች ፣ ጡቷ እንድድሮው አይደለም ። ቦርጫም ሆናለች፣ ትልቅዬ የጭቃ መከላከያ ጫማ ተጫምታለች
ልጅ አቅፋለች ። ብዙ አመት አብረን ተንዘላዝለን ተጨቃጭቀን ..
ተዋደን ...
ተዳርተን...
ተማምተን፣ ተሳስበን ሙሉ ቀን ተጠፋፍተን ምነው የት ጠፋህ የት ጠፋሽ ተባብለናል ። ተለያየን ብለን ታርቀናል ፣ተበዳድለን ይቅርታ ተባብለናል
ትክዝ አልኩ ፦
ልጅነቷ ውስጥ ልጅነቴ ነበር። ጠረኗ ውስጥ ትዝታዬ ተወሽቋል ። እንድተለያየን ሁለት ወር ሳንቆይ ከኔ ጋ እያለች ከሚጀነጅናት ጋ መሰለኝ
አብራው መኖር ጀመረች አራት ወር እንደቆዩ ተለያዩ ሲጣሉ አርግዛ ነበር መሰለኝ ብዙ ሳትቆይ ወለደች ልጁም የሱ ነው ተባለ ።
ምን አለ ልጁ የኔ ቢሆን ...!
አባትህ እንዲ መጥቶ፣ ሰርቶ ፣ሄዶ ፣በድሎኝ፣ ጠቅሞኝ፣ ገለመሌ እንዲ ሆነን ተጣብሰን ተዋደን ብዙ ግዜ ቆይተን ገለመሌ ትላለች
እኔም የልጄ እናት እንዲ አድርጋ እንዲ ሄደን፣ ወጥተን ወርደን እንዲ አቶድም እሷ እንዲ ናት እያልኩ ለልጄ እነግረው ነበር ።
ምን አለ እኔጋ እያለች ሙሉ እንድሆንላት ተመስጣ ባትደምር ባትቀንስ ፣ ምናለ እኔስ ባልፈለሳሰፍ ዝም ብዬ ገፋፍቼ አታልዬ አስርግዣት ቢሆን ።
ህፃን ልጅ አቅፋ ጎስቁል ብላ ልጅነቷን በልጇ ተሸሽጋ እየሸኘችው ነው ።
ውዱን ጊዜያችንን አብረን ነበርን ። ምን አለ ያቀፈችው ልጅ ከኔ ቢሆን፣ ምን አለ ያረገብኩት ጡቷ በኔ ልጅ ምክንያት ቢወድቅ ።
ልጇ እሷን አይመስልም። ምን አለበት ሌላው ይቅር ልጆ እሷን ቢመስል ።
ውድድ ...ሳምምም... እቅፍፍ ...ባደርገው ።
አብሮነታችን ምንም ቋሚ የሚናገር ነገር ሳይገነባ አለፈ ።
እሷ ግን ታድላ መኖርያ ምክንያት አገኘች ።
በድርበቡ ሰላም ብያት ልጆን እጁን ስሜው አይን አይኖን እያየሁ ከላይ ከላይ ካወራን ቀጥሎ
"ለኔም ውለጂልኝ" አልኳት ሳቀች ሳቋ ውስጥ ልጅነቷ ወጣ ፣
በማርያም.... እ....?🙏
ስለት አሳዘንኳት መሰለኝ ፊቷ ቅር አለው፣ "በዚህ ልጅ የበላውት ፍዳ ብታቅልኝ ኖሮ.... "አለች
መንገዷ አባጣ ጎርባጣ እንደነበረው ብዙ ነገሯ ይናገራል
ግዴለም ሁን ያለው ነው የሚሆንው ።እኔም ስንት መከራ ሳይገለኝ ምሮኛል ፣ሰንት ሞት አምልጫለሁ
መጥፎ ነገር ብቻ የሚያልፈኝ በእውነቱ እኔ ማነኝ?!
ባይልልን ነው !
1 157
እመንገድ ላይ አየኋት ። ወፍራለች ፣ ጡቷ እንድድሮው አይደለም ። ቦርጫም ሆናለች፣ ትልቅዬ የጭቃ መከላከያ ጫማ ተጫምታለች
ልጅ አቅፋለች ። ብዙ አመት አብረን ተንዘላዝለን ተጨቃጭቀን ..
ተዋደን ...
ተዳርተን...
ተማምተን፣ ተሳስበን ሙሉ ቀን ተጠፋፍተን ምነው የት ጠፋህ የት ጠፋሽ ተባብለናል ። ተለያየን ብለን ታርቀናል ፣ተበዳድለን ይቅርታ ተባብለናል
ትክዝ አልኩ ፦
ልጅነቷ ውስጥ ልጅነቴ ነበር። ጠረኗ ውስጥ ትዝታዬ ተወሽቋል ። እንድተለያየን ሁለት ወር ሳንቆይ ከኔ ጋ እያለች ከሚጀነጅናት ጋ መሰለኝ
አብራው መኖር ጀመረች አራት ወር እንደቆዩ ተለያዩ ሲጣሉ አርግዛ ነበር መሰለኝ ብዙ ሳትቆይ ወለደች ልጁም የሱ ነው ተባለ ።
ምን አለ ልጁ የኔ ቢሆን ...!
አባትህ እንዲ መጥቶ፣ ሰርቶ ፣ሄዶ ፣በድሎኝ፣ ጠቅሞኝ፣ ገለመሌ እንዲ ሆነን ተጣብሰን ተዋደን ብዙ ግዜ ቆይተን ገለመሌ ትላለች
እኔም የልጄ እናት እንዲ አድርጋ እንዲ ሄደን፣ ወጥተን ወርደን እንዲ አቶድም እሷ እንዲ ናት እያልኩ ለልጄ እነግረው ነበር ።
ምን አለ እኔጋ እያለች ሙሉ እንድሆንላት ተመስጣ ባትደምር ባትቀንስ ፣ ምናለ እኔስ ባልፈለሳሰፍ ዝም ብዬ ገፋፍቼ አታልዬ አስርግዣት ቢሆን ።
ህፃን ልጅ አቅፋ ጎስቁል ብላ ልጅነቷን በልጇ ተሸሽጋ እየሸኘችው ነው ።
ውዱን ጊዜያችንን አብረን ነበርን ። ምን አለ ያቀፈችው ልጅ ከኔ ቢሆን፣ ምን አለ ያረገብኩት ጡቷ በኔ ልጅ ምክንያት ቢወድቅ ።
ልጇ እሷን አይመስልም። ምን አለበት ሌላው ይቅር ልጆ እሷን ቢመስል ።
ውድድ ...ሳምምም... እቅፍፍ ...ባደርገው ።
አብሮነታችን ምንም ቋሚ የሚናገር ነገር ሳይገነባ አለፈ ።
እሷ ግን ታድላ መኖርያ ምክንያት አገኘች ።
በድርበቡ ሰላም ብያት ልጆን እጁን ስሜው አይን አይኖን እያየሁ ከላይ ከላይ ካወራን ቀጥሎ
"ለኔም ውለጂልኝ" አልኳት ሳቀች ሳቋ ውስጥ ልጅነቷ ወጣ ፣
በማርያም.... እ....?🙏
ስለት አሳዘንኳት መሰለኝ ፊቷ ቅር አለው፣ "በዚህ ልጅ የበላውት ፍዳ ብታቅልኝ ኖሮ.... "አለች
መንገዷ አባጣ ጎርባጣ እንደነበረው ብዙ ነገሯ ይናገራል
ግዴለም ሁን ያለው ነው የሚሆንው ።እኔም ስንት መከራ ሳይገለኝ ምሮኛል ፣ሰንት ሞት አምልጫለሁ
መጥፎ ነገር ብቻ የሚያልፈኝ በእውነቱ እኔ ማነኝ?!
ባይልልን ነው !
1 157
#እባብ_እና_አንዳንድ_ጠቃሚ_የቤት_እንስሳት…🤣😂
⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳
.......................
ልጅ ሳለሁ አንድ ጓደኛ ነበረኝ - አባቱ ምትሀተኛ (Magician) ናቸው፡፡ ጥሩ ቢዝነስ አላቸው፡፡ ቢዝነሳቸው ምን መሰላችሁ - ጥቂት እባቦች አሏቸው፡፡ ቤታቸው አዘውትሬ እሄድ ስለነበር ቀስ በቀስ 97 ፐርሰንት ያህል እባቦች መርዝ እንደሌላቸው ተረዳሁ፡፡ 3 ፐርሰንቱ ብቻ ናቸው መርዝ ያላቸው፤ ከነዚህም ውስጥ አንድ ፐርሰንት የሚሆኑት ኮብራዎች ናቸው በጣም አደገኞቹ፡፡
ኮብራ ከነደፈህ መዳን ከባድ ነው፡፡ ሞት እርግጥ ነው ማለት ይቻላል፡፡ እባቦች ደግሞ በጣም ነው የሚመሳሰሉት፡፡
አባትዬው መርዝ የሌላቸው እባቦች ነበሯቸው፡፡ እናም ልጃቸውን፣ ጓደኛዬን፣ እባብ ሰው ቤት እንዲጥል ይልኩታል፡፡ እኔም አብሬው እሄዳለሁ፡፡
እኔ እና ጓደኛዬ እባቦቹን ሰዎቹ ቤት ጊቢ ውስጥ እንጥላለን፡፡ ጥቂት ቆይተው አባትዬው ለእባብ መያዣ የሚጠቀሙባቸውን የሙዚቃ መሳሪያዎቻቸውን ይዘው በዛ ሰፈር እያለፉ፣ “ቤቱ ውስጥ እባብ ገብቶ ያስቸገረው … ባለሞያዎች ነን እንይዛለን” እያሉ ይለፍፋሉ፡፡
የሙዚቃ መሳሪያዎቻቸውን መጫወት ሲጀመሩ እኛ ጊቢ ውስጥ የለቀቅናቸው እባቦች ወደ ሰውዬው መምጣት ይጀምራሉ፡፡ ለሰጡት አገልግሎትም የቤቱ ባለቤት ደስ ብሎት እያመሰገነ ይከፍላል፡፡ ይሄ ነው መተዳደሪያቸው፡፡
የቤቱ ባለቤት ገንዘቡን እየከፈለ፣ “እግዛቤር ይስጦት አባባ … እስኪ እንዲሁ እየመጡ ይያዙልን … እኛ አትክልት ቦታው ውስጥ እባብ እንዳለ መች አውቀን” ይላል፡፡
…
መርዝ የሌላቸው እባቦች የትኞቹ እንደሆኑ ስለማውቅ፣ በኪሴ እባብ ይዤ ትምህርት ቤት እሄድ ነበር፡፡ ከዛም እባቡን ክፍሉ ውስጥ አስተማሪው ጠረጴዛ ላይ ቁጭ ሳደርገው አስተማሪው ጮሆ ወንበሩ ላይ ወጥቶ፣ “አድኑኝ” ይላል፡፡ ተማሪው ሁሉ በሩጫ ከክፍሉ ይወጣል፡፡ እና ታዲያ ማን ሊያድነው ነው - ከእኔ ውጪ ?
“አድንሃለሁ … ግን ሕይወትህን እንዳዳንኩት ማስታወስ አለብህ፡፡ ሁለተኛ ታስቸግረኛለህ? ቃል ግባ !!!”
እባቡ ጠረጴዛው ላይ ሆኖ ማንኛውንም ቃል ማስገባት ይቻላል፡፡
በመጨረሻ ጉዳዩ ርዕሰ መምህሩ ጋር ደረሰ፡፡ የማይሆን የማይሆን ነገር ያደርጋል ብሎ አስማሪው ከሰሰ፡፡ ግን ርዕሰ መምህሩም ያው ነው፡፡
ወደ ቢሮው ሲጠራኝ ሁለት እባቦች በኪሴ ይዤ ሄድኩና ጠረጴዛው ላይ ቁጭ አደረግኳቸው፡፡ ዘሎ ወንበሩ ላይ ቆመ፡፡ የትምህርት ቤቱ ሰው ሁሉ እየሆነ ያለውን በመስኮት እያየ ነው፡፡
“እሺ … የምትለኝ ነገር አለ ?” አልኩት፡፡
“የለም … የለም … ይሄን ነገር ብቻ ከቢሮዬ ይዘህልኝ ውጣ” አለ ርዕሰ መምህሩ፡፡
“እኔ ራሴ ፈልጌ አይደለም የመጣሁት፡፡ አንተ ነህ የጠራኸኝ፡፡ መቼም እንደማታስቸግረኝ ቃል ካልገባህልኝ አልሄድም - እባቦቹም እዚሁ ይሆናሉ”
“እንዴ ምን አይነት ነገር ነው … በቃ ቃል እገባለሁ … አላስቸግርህም”
“እሺ … በዚህ ከተስማማን እኔም እስቲ እባቦቹን አባብዬ ይዣቸው ልሂድ፡፡ ለነገሩ እነሱም ትምህርት ቤት መምጣት አይፈልጉም፡፡ አንተ ነህ በግድ ና ብለኸኝ፡፡ ወይስ እዚሁ ይሁኑ እንዴ…” ስለው፣
“ኧረ እባክህ ይዘህልኝ ሂድ” ይጮሃል ርዕሰ መምህሩ፡፡
…
ሰዎች በመሰል ፍርሃት ውስጥ ኖረዋል፡፡ ምንጊዜም በፍርሃት እንደተከበቡ ነው፡፡ የትኛውም ነገር ፍርሃት ይፈጥርባቸዋል፡፡ ግን እኮ ሰውዬው እንደው በትንሹ እንኳ ነገሩን ቢያየው … እኔ እባቦቹን ከያዝኳቸው የሆነ ማጭበርበር አለ ማለት ነው፡፡ ምንም የሚያስፈራ ነገር የለም ማለት ነው፡፡ ግን፣ እባብ የሚለው ቃል ብቻውን በክፍለዘመናት በሰው ልጅ ውስጥ የታመቀውን ፍርሃት ይቀሰቅስባችኋል፡፡
…
ያደረግኩትን ለአባቴ ነገሩት፡፡ “ልጅህ ከጊዜ ወደ ጊዜ በጣም አደገኛ ነገሮች እያደረገ ነው” ሲሉት፤ አባቴ እንዲህ አለ፣ “ምንም ማድረግ አልችልም፡፡ ቃል ገብቼለታለሁ፡፡ ልክ እናንተ ቃል እንደገባችሁለት እኔም ላላስቸግረው፣ በእሱ ጉዳይ ጣልቃ ላልገባ ቃል ገብቼለታለሁ፡፡ አለበለዚያ እነዚያኑ እባቦች ነው ቤት ይዞብኝ የሚመወጣው”
****
Source: Osho
1 157
#ዝምታህ_በደሌን_ዘካሪ ሀውልት እኮ ነው እባክህ ማነሽ በለኝና አፍርሰው።
አውቃለው ድንገት ጥዬህ በመሄዴ ያረፈብህ የናፍቆት በትር አግሎህ ቀጥቅጦህ ሌላ አድርጎሃል አግሞህ አቅልጦህ ቀያይሮሃል ። እንጂማ እኮ ያኔ ከሰዎች መሃል በሩቅ አይተህ ታውቀኛለህ፣ በብዙ ሽታ በታወደ አየር ውስጥ ጠረኔን ትለየዋለህ! ከብዙ ጫጫታ መሃል ድምጼን ታውቀዋለህ።
እስኪ እባክህ ማነሽ ምንድነሽ በለኝ ለጥያቄቅ አልበረግግም ፣ማነሽ በለኝ ልንገርህ ምንድነሽ በለኝ በልቤ የያዝኩትን ሀቄን በነብሴ ያመቅኩት እውነቴን ልንግርህ ።
አቤት...እነዚን ሁሉ አመታት ምን እያሰብክ ይሆን? በፍቅር ስንቀብጥ ተዛዝለን የወደቅንበትን ቀን? ልፊያችንን? ኩርፊያችንን? ሳቃችንን? ደስታችንን? ቁጣዬን? ንዴትህን? ለኔ ለመስጠት የቀጠፍካቸውን አበቦች? የጻፍክልኝን ግጥሞች? የሰማናቸውን የፍቅር ዘፈኖች? አብረን ያመሸናቸውን ምሽቶች? አብረን ያለምናቸውን ህልሞች?
እባክህ የኔ ጌታ ዝምታህ በደሌን ዘካሪ ሀውልት እኮ ነው እባክህ ማነሽ ብለህ አፍርሰው። ከእድሜህ ቀድሞ የከሰመው ውበትህ እኮ አላኖር ያለኝ ሞቴ ነው ምንድነሽ በለኝና አባረው።
እስኪ ተናግረህ ኮንነኝ ሰው ይስማክ፣ እንዲ አንደበትህን የለጎመህን ግብሬን ገፍትረህ አጩለህ ግለጸውና ከሚጠዘጥዘኝ ጸጸት ልዳን። እባክህ ማነሽ በለኝ ማነሽ መባል ናፍቆኛል፣ ምንድነሽ በለኝ...
ያኔ ተነፋፍቀን ስንገናኝ ምናወራቸውን ምስቅልቅል መሻቶቻችንን ዜማ እንስጣቸው ተናገር! የሻገተ የፍቅር ብሩሻችንን ቀለም ነክረን ፍቅርን ዳግም እንሳለው ማነሽ በለኝ! እባክህ ያ ብሩህ ምናብህ ይለኮስና ውበትን ዘምርልኝ ምንድነሽ በለኝ።...ማነሽ በለኝ
Sami Kibe
1 157
ራሴን ፊት ነሳለሁ...ለራሴ ሚበቃ የምነሳው ፊት ባይኖረኝም እንኳን ባለችኝ እሞክራለሁ...አይኔን ካንተ ላይ አነሳለሁ...ድምፄም ካንተ ሩቅ ነው...አታስብ አስቀያሚ ፊቴንም አታይም...ምን አለፋህ ኑረቴን አታውቅም...
በመሀላችን ላለው ገደል ደፍሮ ድልድይ የሚሰራ የለም...እኔና አንተ መሀል የተንጣለለ ባህርም አለ..ለርቀቱ ወስን ለማብቂያውም ገደብ የሌለው...
የእኔና ያንተ ሙሴ እንዲሁ በቀላሉ አይነሳም...ምን አልባት እንደ ራሄል እምባ እምባዬ የፀባኦትን መንበር ካንኳኳ ማን ያውቃል....አንተ በዚኛው ጠረፍ ...እኔ ደግሞ በዚህ...ሙሴያችን እስኪመጣ...ባህሩን እስኪከፍለው...
✍shewitdorka
