Wegoch
አዳዲስ ወጎችን እና ትረካዎችን ያገኙበታል ለሃሳብ እና አስተያየት @Rediet_badie
Show moreThe country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
331
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
Repost from ወግ ብቻ
«… አምስት፣ ስድስት፣ ሰባት …»
አንድ ወቅት ላይ ለተወሰኑ ቀናት … ወደኾነ የሀገራችን ክፍል የመሄድ ዕድል አገኘኹ።
ከመሄዴ በፊት …ስለቦታው አንድ ኹለት ያኽል ደስ የሚሉ ዘፈኖች ሰምቼ ነበርና …ቦታውን ለማየት በጣም ጓጓኹ።
እንዲኽ የተዘፈነለት፣ ግጥምና ዜማ የተሠራለት ቦታ እንዴት ያለ ቢኾን ነው የሚልን ሀሳብ እያሰብኹ፣ ወደ መንገድ ዳር ወጥቼ ባጃጅ ተሳፈርኩ።
«እስቲ እንትን የሚባለው ቦታ አድርሰኝ»
«እሺ ግባ»
የተወሰኑ ደቂቃዎች እንደነዳ የመንገዱን ጥግ ይዞ ቆመ።
«ምነው?»
«ደረስንኮ»
«እንትን የሚባለው ቦታ ይኼ ነው እንዴ?» ማመን አልቻልኹም…
«አዎ»
ወርጄ ሳይ ወዲያና ወዲኽ ተራርቀው አምስት ቤቶች፣ ስድስት ዛፎችና፣ ሰባት ሰዎች ብቻ ይታዪኛል። … የቀረው ቁጥቋጦ የወረረው በረሃና የተራቆተ ተራራ ነው። ክው ነው ያልኹት። በጉጉት የተሞላው ልቤ በኩርፊያ ኩምሽሽ አለ።
«በቃ ይቺው ናት?» አልኹት ባለማመን
«ምን ፈልገኽ ነበር?» አለኝ እየሳቀ …
…
አንዳንድ ደስታዎች እንዲኽ አይደሉም ወይ? አብዛኛው መሻትና ፍላጎታችን ጉም እንደመጨበጥ አይደለም ወይ? አንዳንድ ነገሮች በጥበብ ስም፣ በዕውቀት ስም፣ በፋሽን ስም፣ በሥልጣኔ ስም፣ በወጣትነት ስም፣ በሀገር ስም የተጋነኑ ናቸው። እዚኽ ካልደረስክ «ፋራ» የሚያስብሉ … ስንደርስ ግን ኹሉም በጋራ መስማማት እውነት የተደረጉ ውሸቶች መኾናቸውን እንረዳለን። ሀቀኞች ሮጠው ወደመጡበት ይመለሳሉ። ፈሪዎች ግን ራሳቸውን እየዋሹ መኖር ይቀጥላሉ።
አንዳንድ ሰዎች ሲታዪ ረዥም ይመስሉና ደርሳችኹ አጠገባቸው ስትቆሙ አያጥሩባችኹም? ስብዕናቸውም እንደዚያው የኾኑ አሉ። ስታውቋቸው ወርደው ተዋርደው ቅልል የሚሉ እንደገለባ … ምነው ባላውቃቸው ኖሮ የሚያስብሉ አሉ።
አንዳንዴ የኾነን ነገር ደርሶ ከማየት በጉጉት መኖር የተሻለ ነው። አስቡት ዕድሜ ልካችኹን አንድን ነገር ስታሳድዱት ከርማችኹ የደረሳችኹበት ቀን ምንም ሲኾን? … አምስት ምንም፣ ስድስት ከንቱ፣ ሰባት ባዶ … ሲኾን
እና ጥቂት የጥርጣሬ ሥፍራ መተው አሪፍ ነው መሰለኝ።
—————
By 𝙷𝙴𝚗𝚘𝚌𝚔 𝙱. 𝙻𝚎𝚖𝚖𝚊
@wegoch
@wegoch
@paappii
የመጨረሻ ክፍል - ሁቱትሲ - ክፍል 26
━━━━━━✦✗✦━━━━━━━
✍🏽 በ ኢማኪዩሌ አሊባጊዛ | ትርጉም: መዘምር ግርማ
🎥 በ ተራኪ (የሞባይል መተግበሪያ) - የተሠናዳ
ትረካ:ረድኤት ባዴ
━━━━━━✦✗✦━━━━━━
⇲⇲⇲⇲ ሼር ያድርጉ!! ⇲⇲⇲⇲
አዘጋጅ፦⇨ @terakiapp
⇨ @Ethio_Tereka
@wegoch22
@wegoch22
━━━━━━✦✗✦━━━━━━
ተፈፀመ!!!
━━━━━━✦✗✦━━━━━━