ነገረ ማርያም( አንድምታ)
Open in Telegram
በዚህ ቻናል ሃይማኖታዊ ምስጢሮችን ያገኙበታል። " ኪሩቤል አፍራሰ ፌማ፥ ወሱራፌል ዘራማ፥ ክሉላነ ሞገስ ወግርማ ፥ ይሴብሑኪ ማርያም፥ በቃለ ጥዑም ዜማ።"/ ማርያም ሆይ የመንፈስ ቅዱስ አፍራስ ኪሩቤልና በግርማና በክብር የተጋረዱ በራማ የሚኖሩ ሱራፌል ማርያም ሆይ ጥዑም በሚሆን የዜማ ቃል ያመሰግኑሻል።
Show more2 170
Subscribers
+424 hours
+67 days
+4430 days
Posts Archive
2 171
💒✨✞ ኪዳነ ምሕረትና ሰባቱ ኪዳናት ✞✨💒
𝗧𝗵𝗲 𝗔𝘀𝘀𝘂𝗺𝗽𝘁𝗶𝗼𝗻 𝗢𝗳 𝗼𝘂𝗿 𝗟𝗮𝗱𝘆 𝗦𝘁. 𝗠𝗮𝗿𝘆
ኪዳነ ተካየድኩ ምስለ ኅሩያንየ
"ከመረጥኳቸው ጋር ቃል ኪዳንን አደረግሁ (መዝ. 88:3)
▬▬▬▬▬ ▬▬ ▬▬▬▬▬
“ይቤላ ለእሙ ማርያም እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ተካየድኩ ምስሌኪ ኪዳነ ምሕረት ከመ አድኅን ዘተአመነኪ መሐልኩ ለኪ በርእስየ ዘመሐልኩ አነ ለኖኅ ገብርየ ወለአብርሃም ፍቁርየ፤ ዘመሐልኩ አነ ለዳዊት ኅሩይየ ብእሲ ምእመን ዘከመ ልብየ መሐልኩ ለኪ በርእስየ በቅዱስ ሥጋየ ወበክቡር ደምየ መሐልኩ ለኪ በርእስየ ከመ ኢይሔሱ ማእኰትየ”
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ ማርያምን እንዲኽ አላት በምልጃሽ ያመነብሽን አድን ዘንድ ካንቺ ጋራ የምሕረት ቃል ኪዳንን ተጋባኊ፤ ለአገልጋዬ ለኖኅና ለወዳጄ ለአብርሃም ቃል የገባኊ እኔ በራሴ ማልኹልሽ፤ እንደ ልቤ ለምለው ለታመነው ለዳዊት የማልኊ እኔ በራሴ ማልኹልሽ፤ በቅዱስ ሥጋዬና በክቡር ደሜ የማልኊ እኔ ምዬ እንደማልከዳ ማልኹልሽ።
"ተካየደ' ማለት 'ተስማማ ተማማለ' እንደ ማለት ሲሆን 'ኪዳን' በቁሙ 'ውል፣ ስምምነት' እንደ ማለት ነው። ይኸውም እግዚአብሔር ከሰዎች ጋር፣ ሰዎችም ከሰዎች ጋር የሚያደርጉት ሊሆን ይችላል። ልዩነቱ የእግዚአብሔር ቃል ኪዳን ቅዱስና የማይለወጥ መሆኑ ነው። 'ኪዳን' የሚባለው ቃል «ቃል» ከሚለው ጋር እየተቀናጀ በብሉይ ኪዳን ለ280 ጊዜ ያህል ሲጠቀስ በአዲስ ኪዳን ደግሞ ከ33 ጊዜ በላይ ተጠቅሷል፡፡
እግዚአብሔር አምላክ ከሥነ ፍጥረት ጀምሮ በየጊዜው ከብዙ ወዳጆቹ ጋር ኪዳንን አድርጓል። ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም እነዚህን ኪዳናት ጥቅልል አድርጋ 7 እንደሆኑ ታስተምራለች።
እነዚህ 7 ኪዳናት የምንላቸው:
1. ኪዳነ አዳም
አዳም ማለት የእግዚአብሔር ድንቅ ፍጥረት፣ የፍጡራን አስተዳዳሪ፣ ነቢይ፣ ካህንና ንጉሥ ነው። እግዚአብሔር ከአዳም ጋር አስቀድሞ በእጸ በለስ አማካኝነት ቃል ኪዳን ነበራቸው። ነገር ግን አባታችን በዲያብሎስ ሴራ በመረታቱ ኪዳኑ ፈረሰ። (ዘፍ. 3:1)
አዳምና ሔዋን ተጸጽተው ቢያለቅሱ ግን አዲስ የኪዳን ተስፋ "ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ" የሚል ኪዳንን ተቀበሉ።
(ቀሌምንጦስ: ገላ 4:4)
2. ኪዳነ ኖኅ
ከአዳም እስከ ኖኅ ድረስ ባሉት 10 ትውልድ ዓለም በዓመፃ ተሞላች። ቅዱስ ኖኅ በደግነቱ መርከብ ሠርቶ ቤተሰቡን ሲያተርፍ ዓለም በማየ ሥራዌ ጠፋች። ከመርከቡ ከወጣ በኋላ ኖኅና እግዚአብሔር በቀስተ ደመና ምልክትነት ቃል ኪዳን ተጋቡ። "ኢያማስና ለምድር ዳግመ በማየ አይኅ" እንዲል። (ዘፍ. 9:12)
3. ኪዳነ መልከ ጼዴቅ
መልከ ጼዴቅ የእግዚአብሔር ካህኑ፣ የክርስቶስም ምሳሌው የሆነ የሳሌም ንጉሥ ነው። በ15 ዓመቱ መንኖ፣ አጽመ አዳምን ይዞ፣ በቀራንዮ በሕብስትና በወይን ያስታኩት ነበር።
እግዚአብሔር ለመልከ ጼዴቅ በሐዲስ ኪዳን ለምትሠራው ክህነትና ምሥጢረ ቁርባን ምሳሌ አድርጐ በቃል ኪዳን አትሞታል። በዚህም ተሰውሮ ይኖራል እንጂ ሞትን እስካሁን አልቀመሰም። ይህም ካህኑ መልከ ጼዴቅ ከአብርሃም ጋር በተገናኙበት ጊዜ ተገልጧል።
(ዘፍ. 14:17፣ ዕብ. 7:1)
4. ኪዳነ አብርሃም
ቅዱስ አብርሃም የሕዝብና የአሕዛብ አባት፣ ሥርወ ሃይማኖት፣ የጽድቅም አበጋዝ ነው። ስለ ፍቅረ እግዚአብሔር ሲል ከርስቱና ከወገኖቹ ተለይቶ በቅድስና ኑሯልና እግዚአብሔር "በዘርሕ አሕዛብ ይባረካሉ" አለው። (ዘፍ. 12:1) የቃል ኪዳን ምልክትም ይሆነው ዘንድ ግዝረትን ሰጠው። (ዘፍ. 17:1-14)
5. ኪዳነ ሙሴ
ቅዱስ ሙሴ የነቢያት አለቃ፣ የእሥራኤል እረኛ፣ የእግዚአብሔር ሰው እና ፍጹም ትሑት (የዋህ) ሰው ነው። በፈጣሪው ትዕዛዝ እሥራኤልን ከግብጽ ባርነት አውጥቶ ለ40 ዘመናት በበርሃ ሲመራቸው ከእግዚአብሔር የኪዳንን ጽላትና አሠርቱን ትዕዛዛት ተቀብሏል።
(ዘጸ. 20:1፣ 31:18)
6. ኪዳነ ዳዊት
ቅዱስ ዳዊት ሥርወ ነገሥት፣ ጻድቅ፣ የዋህና ቡሩክ የሆነ አባት ነው። እግዚአብሔር ከእረኝነት ጠርቶ ንጉሥ አድርጐ ሹሞት "ከሆድህ ፍሬ በዙፋንህ ላይ አኖራለሁ" (መዝ. 131:11) ሲል ምሎለታል። አክሎም ሰፊ ቃል ኪዳን ሰጥቶ "አልዋሽህም" ብሎ ሲምልለት እንመለከታለን።
(መዝ. 88:35)
7. ኪዳነ ምሕረት
በብሉይ ኪዳን የነበሩ 6ቱ ኪዳናት በዘመናቸው ክቡርና ሕዝቡን ከመቅሰፍት ይታደጉ የነበሩ ቢሆንም ከሲዖል ማዳን ግን አልቻሉም። ስለዚህም አንድ ፍጹም ኪዳን ያስፈልግ ነበር። ይህን ፍጹም ኪዳን ይፈጽም ዘንድም ከቅድስት ሥላሴ አንዱ ወልድ ከሰማያት ወርዶ በድንግል ማርያም ማሕጸን አደረ።
በፍጹም ተዋሕዶም በሕቱም ድንግልና ተወልዶ፣ አድጎ፣ ተጠምቆ፣ አስተምሮ፣ ሞቶ፣ ተነስቶና ዐርጐ ሥጋ ማርያምን በዘባነ ኪሩብ አስቀመጠው። ኪዳነ ምሕረት (የምሕረት ኪዳን) የምንለው አንዱ ታዲያ ይሔው ነው።
የጌታችን መጸነሱ፣ መወለዱ፣ መሰደዱ፣ መጠመቁ፣ ማስተማሩ፣ ሥጋውንና ደሙን መስጠቱ፣ መሰቀሉ፣ መሞቱና መነሳቱ፣ ማረጉና መንፈስ ቅዱስን መላኩ በአንድ ላይ ኪዳነ ምሕረት ይባላል። ታዲያ ይህ ሁሉ የተደረገው በሥጋ ማርያም ነውና የኪዳኑ ባለቤት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት።
የምሕረት ቃል ኪዳን ለምን ያስፈልጋል ቢባል ሕግ መተላለፍ ካለ ሁልጊዜ ተጠያቂነት ወይም ቅጣት ይኖራል፡፡ ይህም በአዳም ይታወቃል፡፡ የሰው ልጆች ደግሞ ከተጠያቂነት ነጻ የሚያደርግ አኗኗር ይዘው አይገኙም፡፡ በዚህ ምክንያት ቅጣት እንዳያገኛቸው የሚድኑበትን በርካታ መንገዶች እግዚአብሔር አዘጋጀ፡፡ ከእነዚህም ውስጥ አንዱ የምሕረት ቃል ኪዳን ነው፡፡
የእርሷ ኪዳን 6ቱን አበው ኪዳናት ፍጹም በማድረጉ የኪዳናት ማሕተም ይባላል። የድንግል ማርያም ኪዳኗ ከሲዖልና ከገሃነም ሊታደገን አቅሙ አለውና። መድኃኒታችን ክርስቶስ ለድንግል እናቱ ቃል ኪዳኑን ያጸናላት ደግሞ ካረገ ከዓመታት በኋላ ጐልጐታ ላይ ነው።
እመ ብርሃን በዚያ ቁማ ስለ ኃጥአን ስታለቅስ "እናቴ ሆይ! በስምሽ ያመነውን በቃል ኪዳንሽ የተማጸነውን እምርልሻለሁ" ብሎ ደስ አሰኝቷታልና። ይሔው በእመ ብርሃን ምልጃና ቃል ኪዳን ምዕመናን ከመቅሰፍትና ከገሃነመ እሳት ማምለጥ ከጀመሩ 2ሺ ዓመታት ሆኑ። ዛሬም እኛ ኃጥአን ልጆቿ ከእሳት እንደምታድነን አምነን በጥላዋ ሥር እንኖራለን።
" ኢትዝክሪ ብነ አበሳነ ኃጢአተነ ወጌጋየነ
ማርያም እሙ ለእግዚእነ
በኪዳንኪ ወበስደትኪ ድንግል ተማሕጸነ"
"ድንግል ሆይ!
ኃጢአታችን፣ አበሳችንና በደላችንን አታስቢብን ዘንድ በስደትሽና በኪዳንሽ ተማጽነናል።"
የአርያም ንግሥት፣ የሰማያውያንና ምድራውያን ኁሉ እመቤት፣ የአምላክ እናት፣ ቅድስት፣ ስብሕት፣ ክብርት፣ ልዕልት፣ ቡርክት፣ ፍስሕትና ጥዕምት የሆነች ድንግል ማርያም የድኅነታችን መሠረት ላመኑባት አንገት የማታስደፋ እውነተኛ አማላጅ ናት።
የካቲት 16 ስለ ወገኖቿ የሰው ልጆች ፍቅር በእንባ ያቀረበችውን ልመና የባሕርይ አምላክ የሆነ ልጇ ተቀብሎ በማይዋሽ ንጹሕ አንደበቱ ቃል ኪዳን ገብቶላታል።
በስምሽ ያመነ በቃል ኪዳንሽ የተማመነ እሳት አያይም ብሏታል።
2 171
ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ ደባትረ ብርሃን ኀበ ተተክሉ
ለገነተ ፅባህ በማዕከሉ
ውድስት አንቲ ወስብሕት በአፈ ኲሉ
እምነ ፃድቃን ዘታህቱ ወእምነ ትጉሃን ዘላእሉ
ማርያም ለኪ ስብሐተ አደሉ፡፡
እመቤቴ ማርያም ሆይ በምሥራቃዊ ተክለ ገነት መካከል የብርሃን ድንኳኖች ወደ ተተከሉበት ለዐረገ ሥጋሽ ስላምታ ይገባል፡፡
ድንግል ሆይ በሁሉ አንደበት መመስገን የተገባሽ ስለሆነ በሰማይ ካሉ መላእክትና በምድር ከሚኖሩ ደቂቀ አዳም ሁልጊዜ ምስጋና ይቀርብልሻል፡፡
2 171
#ሥርዓተ_ማኅሌት_ዘነሐሴ_ኪዳነ_ምሕረት
፩/ ነግሥ ( ለኲልያቲክሙ )
ሰላም ለኵልያቲክሙ እለ ዕሩያን በአካል፤
ዓለመክሙ ሥላሴ አመ ሐወፀ በሣህል፤
እምኔክሙ አሐዱ እግዚአብሔር ቃል፤
ተፈጸመ ተስፋ አበው በማርያም ድንግል፤
ወበቀራንዮ ተተክለ መድኀኒት መስቀል፡፡
ዚቅ፦
ወታስተሥርዪ ኃጢአተ ሕዝብኪ ተበውሐ ለኪ ፣
እም አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ፣ ከመ ትኵኒ ተንከተመ ለዉሉደ ሰብእ፣ ለሕይወት ዘለዓለም ፣
ለኪ ይደሉ ከመ ትኵኒ መድኀኒቶሙ ለመሐይምናን ሕዝብኪ፣
ኦ መድኀኒተ ኵሉ ዓለም ወልድኪ ሣህሎ ይክፍለነ ሰአሊ ለነ ቅድስት፡፡
፪/ ነግሥ ( እምጌቴሴማኒ ፈለሰት )
እምጌቴሴማኒ ፈለሰት ኀበ ዘሉዓሌ መካን፤
ውስተ ቤተ መቅደስ ረባቢ ዘመሳክዊሁ ብርሃን፤
አንቀጸ አድኅኖ ማርያም ጽላተ ኪዳን፤
ኵሉ ይብልዋ በአኅብሮ ዘበዕብራይስጢ ልሳን፤
ዕፀ ጳጦስ ይእቲ እንተ በአማን ቅድስተ ቅዱሳን፤
እመቅድሀ ከርሣ ተቀድሐ አስራባተ ወይን፤
ወበውስቴታ ተሠርዓ ቊርባን፡፡
ዚቅ፦
ዕፀ ጳጦስ እንተ በአማን መዝገቡ ለቃል፣
ዕፀ ጳጦስ እንተ በአማን አንቀጸ ብርሃን፣
ዕፀ ጳጦስ እንተ በአማን ጽጌ ደንጐላት፣
ሐረገ ወይን ዘእምነገደ ይሁዳ፣
እንተ ሠረፀት ለሕይወት፡፡
፫/ ለፍልሰተ ሥጋኪ ( መልክአ ኪዳነ ምሕረት )
ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ ኀበ ሕንጻ ሕይወት ተሐደሰ፤
እምቅድመ ዝኒ ኀቤሁ ሥጋ ወልድኪ ፈለሰ፤
ቤዛዊተ ዓለም ማርያም አስተበቊዓኪ አንሰ፤
ትቤዝዊ በኪዳንኪ ዘዚአየ ነፍሰ፤
እስመ በሥራይኪ ለቊስልየ ቀባዕክኒ ፈውሰ፡፡
ዚቅ፦
ደብተራ ፍጽምት ዘጳውሊ፣
ወማኅደሩ በጽድቅ ዘገብራ ከሃሊ፣
ፈለሰት እምዘይበሊ ኀበ ኢይበሊ፣ በመሰንቆሁ እንዘ የኃሊ፣
ዳዊት አቡሃ ዘወልዳ ወዓሊ።
ወረብ፦
ደብተራ ፍጽምት ዘጳውሊ ፈለሰት እምዘይበሊ ኀበ ኢይበሊ፤
በመሰንቆሁ እንዘ የሐሊ ዳዊት አቡሃ ዘወልዳ ወዓሊ።
፬/ ለዝክረ ስምኪ ( መልክአ ማርያም )
ሰላም ሰላም ለዝክረ ስምኪ ሐዋዝ፤
እምነ ከልበኒ ወቊስጥ ወእምነ ሰንበልት ምዑዝ
ማርያም ድንግል ለባሲተ ዐቢይ ትእዛዝ፤
ይስቅየኒ ለለጽባሑ ወይነ ፍቅርኪ አዚዝ፤
ከመ ይሰቅዮ ውኂዝ ለሠናይ አርዝ፡፡
ዚቅ፦
ሰላም ለኪ ማርያም እመ አምላክ፣ ወልድኪ ይጼውዓኪ፣
ውስተ ሕይወት ወመንግሥተ ክብር፡፡
ወረብ፦
ሰላም ለኪ ማርያም እመ አምላክ ማኅደረ መለኮት፤
ወልድኪ ወልድኪ ይጼውዓኪ ውስተ ሕይወት ወምንግሥተ ክብር።
፭/ ለእስትንፋስኪ ( መልክአ ማርያም )
ሰላም እስትንፋስኪ ዘመዐዛሁ ሕይወት፤
ከመ መዐዛ ዕፅ ኅሩይ ዘውስተ ገነት፤
ማርያም ድንግል ቤተ ቅድሳት፥
ጽንሕኒ ውስተ ሠናይ ወሰውርኒ እሞት፤
በአክናፍኪ ርግብየ ኅሪት፡፡
ዚቅ፦
ንዒ ኀቤየ እንቲአየ ሠናይት ርግብየ፣ መዓዛ አፉሃ ከመ ኮል፣
ወኵሉ ነገራ በሰላም፡፡
ወረብ፦
ንዒ ኀቤየ እንቲአየ ሠናይት ርግብየ ፤
መዓዛ አፉሃ ከመ ኮል መዓዛ አፉሃ ታንሶሱ፡፡
፮/ ለፍልሰተ ሥጋኪ ( መልክአ ፍልሰታ )
ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ ዘኢይቀብል ሞገሱ፤
ወዘኢይነጽፍ ባሕርየ ተውዳሱ፤
ማርያም ታዕካ ለእግዚአብሔር ጽርሐ መቅደሱ፤
ተበሃሉ በሰማያት እለ ኪያኪ አፍለሱ፤
ማርያምሰ እንተ በምድር ታንሶሱ ፡፡
ዚቅ፦
ማርያም ጽርሕ ንጽሕት ማኅደረ መለኮት ፣
እኅቶሙ ለመላእክት ሰመያ ሰማያዊት፣ እንተ በምድር ታንሶሱ፡፡
ወረብ፦
ማርያም ጽርሕ ንጽሕት ፤
ማኅደረ መለኮት ጽርሕ ንጽሕት።
አንገርጋሪ
ትርሢተ ወልድ መለኮት ወፍቅር ኀደረ ላዕሌሃ፤
ይቤላ ርግብየ ወይቤላ ሠናይትየ፥
ፀቃውዕ ይውኅዝ እምከናፍሪሃ ፡፡
ወረብ ዘአመላለስ፦
ትርሢተ ወልድ መለኮት ወፍቅር ኀደረ ላዕሌሃ፤
ይቤላ ርግብየ ወይቤላ ወይቤላ ሠናይት ፡፡
እስመ ለዓለም
በአልባሰ ወርቅ ዑጽፍት ወኁብርት እኅትየ መርዓት አዳም አጥባትኪ እምወይን መዓዛ ዕፍረትኪ እምኲሉ አፈው እትፌሣሕ ወእትኃሠይ ብኪ ናፍቅር አጥባተኪ እምወይን ርቱዕ አፍቅሮትኪ ኲለንታኪ ሠናይት እንተ እምኀቤየ አልብኪ ነውር ወኢምንትኒ በላዕሌኪ ፃዒ እምሊባኖስ እኅትየ መርዓት።
ተፈጸመ ።
+++ የዓመት ሰው ይበለን!!! +++
2 171
ማኅሌት ዘነሐሴ ኪዳነ ምሕረት
ዋዜማ
እግዝእትየ እብለኪ ወእሙ ለእግዚእየ እብለኪ ወተወልደ ቃለ ጽድቁ ለአብ፤
ማርያምሰ ተሐቱ፤ ውስተ ከርሡ ለአዳም፤
ከመ ባሕርይ ፀዓዳ ፤ ፆረቶ እግዝእቱ ለአዳም
ማርያምሰ ተሐቱ፤ ውስተ ከርሡ ለአዳም፤
ከመ ባሕርይ ፀዓዳ ፤ ድንግል ተሐቱ በከርሠ አዳም
ድንግል ተሐቱ በከርሠ አዳም፡፡
+++
በሐምስ
ሰአሊ ለነ ማርያም እንተ እግዚእ ኀረያ ሰአሊ ለነ ማርያም
+++
እግዚአብሔር ነግሠ
ደብተራ ፍጽምት ዘጳውሊ፤ ወማኅደሩ በጽድቅ ዘገብራ ከሃሊ፤
ፈለሰት እምዘይበሊ ኀበ ኢይበሊ ፤
በመሰንቆሁ እንዘ የኃሊ፤ ዳዊት አቡሃ ዘወልዳ ወዓሊ
በሐምስ
ዕፀ ጳጦስ ይእቲ እንተ በአማን ይብልዋ ቅድስተ ቅዱሳን
ዕፀ ጳጦስ ይእቲ እንተ በአማን፡፡
+++
ይትባረክ
እግዝእትየ እብለኪ ወእሙ ለእግዚእየ እብለኪ ቃል ቅዱስ ኀደረ ላዕሌኪ፡፡
ሰላም
ሃሌ ሉያ (3) ፃዒ እምሊባኖስ ሥነ ሕይወት
ርቱዕ አፍቅሮትኪ፤ ቡርክት አንቲ እምአንስት
ማኅደረ መለኮት ፃዒ እምሊባኖስ ሥነ ሕይወት
ሰላም ለኪ ማርያም እመ አምላክ፤ ወልድኪ ይጼውዓኪ፤
ውስተ ሕይወት ወመንግሥተ ክብር፡፡
2 171
ጸሎተ ሃይማኖት ድቅድቅ ጨለማ በሞላው ዓለም እያበራን ወደ ሕይወት የምንጓዝበት የብርሃን ፋና ነው። ጸሎተ ሃይማኖት የመንፈሳዊ ሕይወታችን መራኄ ፍኖት (compass) ነው። ጸሎተ ሃይማኖት አባቶቻችን ሐዋርያት ያቆዩልንን እውነት የምንጠብቅበት የእምነት ጋሻችን ነው። ጸሎተ ሃይማኖት ንጽሕት እምነታችንን ትውልድን የሚያሻግርና ትውልድን ከትውልድ የሚያስተሳስር የእምነት ሀረግ ነው። ጸሎተ ሃይማኖት አዕማደ ምስጢራትንና ምስጢራተ ቤተ ክርስቲያንን የምንረዳበት መክፈቻ ቁልፍ ነው። ጸሎተ ሃይማኖት እምነታችን ንጽሕትና የማትናወጽ ሆና የቆመችበት ጽኑዕ አለት ነው። ጸሎተ ሃይማኖት አባቶቻችን በጥበብ ያነጹት የማይናወጥ ግንብ የተተከለበት፣ የእውነተኛው የአስተምህሮ ቅፅር የሚጠበቅበት የእምነት ድንበር ነው። ጸሎተ ሃይማኖት የምንጠቅሰው መዝገብ ብቻ ሳይሆን የምንኖረው የክርስትና ሕይወት፣ የምንጋደልለት እውነትና የዘላለም ሕይወትን የምናገኝበት እምነት ነው። ጸሎተ ሃይማኖት እውነት ያሸነፈችበትና የምታሸንፍበት የድል ዓርማ ነው። ስለዚህ ጸሎተ ሃይማኖትን በሚገባ ልንረዳው፣ የእውነተኛ አስተምህሮ መለኪያ አድርገን ልንጠቀምበት፣ መንፈሳዊ ማንነታችንን ልናንጽበት፣ ለትውልድ ልናሻግረው፣ በየዕለቱ ልንጸልየው፣ በሕይወት ልንኖረውና በጽናት ልንጋደልለት የሚገባ የእምነታችን መሠረት ነው።
አነሳስቶ ያስጀመረን አስጀምሮም ያስፈጸመን ልዑል እግዚአብሔር ክብርና ምስጋና ይግባዉ ለዘለዓለሙ አሜን።
2 171
ታሪክ፦ ከጉባዔ ኒቅያ እስከ ጉባዔ ቍስጥንጥንያ ሃምሳ አምስት ዓመት ነው። በዚህ ጊዜ መቅዶንዮስ ለአብ መንበር እንዳለው እግዚአብሔርሰ ይነብር ዲበ መንበሩ ቅዱስ ተብሎ ተነግሯል። ለወልድ መንበር እንዳለው መንበርከ እግዚኦ ለዓለመ ዓለም ተብሎ ተነግሯል። ለመንፈስ ቅዱስ ግን መንበር እንዳለው የተነገረበት ቦታ የለምና ሕፁፅ ነው ብሎ ተነሣ። ንጉሡ ዘየዓቢ ቴዎዶስዮስ ነው ። በቍስጥንጥንያ ጉባዔ ይሁን ብሎ አዋጅ ነገረ። በዚህ ምክንያት መቶ ሃምሳ ሊቃውንት ተሰብስበዋል አፈ ጉባዔው ጢሞቴዎስ ዘአልቦ ጥሪት ነው ኢይቤ ሠናየ ይቤ አብ ኢይቤ ሠናየ ይቤ ወልድ አላ ይቤ፤ ይቤ ሰናየ መንፈስ ቅዱስ በአፈ ኢሳይያስ ነቢይ በዓመተ ሞተ ዖዝያን ንጉሥ ርኢክዎ ለእግዚአብሔር እንዘ ይነብር ዲበ መንበሩ ነዋኅ ወብሩህ ያለውን ይህን ባለመንበር ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ መንፈስ ቅዱስ ብሎ ተርጉሞብሃል ብሎ ረትቶበታ። በዚህ ጊዜ እሱን ተከራክረው ረትተው አውግዘው ለይተው ወነአምን በመንፈስ ቅዱስ ብለው ጨምረውበታል፡፡
⭕️ ወነአምን በአሐቲ ቅድስት ቤተክርስቲያን እንተ ላዕለ ኲሉ ጉባዔ ዘሐዋርያት፡፡
ሐዋርያት ባነጽዋት ከምኲራበ አረሚ ከምኲራበ አይሁድ በላይ በምትሆን ክብርት ንጽሕት ጽንዕት ልዩ በምትሆን ባንዲት ቤተክርስቲያን እናምናለን።
ሐተታ፦ አሐቲ አለ በወርቅ በብር በጭቃ በጨፈቃ ቢሠራ በግብጽ በእስክንድርያ በጻድቃን በሰማዕታት በእመቤታችን ስም ቢሠራ አንድ ነውና በወርቅ በብር የተሠራ ቤተክርስቲያን ሥጋውን ደሙን ይለውጣል። በጭቃ በጨፈቃ የተሠራ ቤተክርስቲያን ሥጋውን ደሙን አይለውጥም አያከብርም ብለዋልና አሐቲ አለ።
አንድም ሐዋርያት ያስተማሯት ያሳመኗት ያጠመቋት ከምዕመናነ አሕዛብ በላይ የምትሆን ክብርት ንጽሕት በምትሆን ባንዲት ምዕመን እናምናለን፡፡
ሐተታ፦ አሐቲ አላቸው ምዕመናንን አንድ እምነት ያምናሉ አንድ ጥምቀት ይጠመቃሉ አንድ ሥጋውን ደሙን ይቀበላሉና አንድም ምዕመናንን በሚያስተምሩ ባንድ መምህራን እናምናለን፡፡
ሐተታ፦ መምህራንን አሐቲ አላቸው አንድ እምነት ያሳምናሉ አንድ ትምህርት ያስተምራሉ፡፡ አንድ ሥጋውን ደሙን ያቀብላሉና፡፡
አንድም በቤተክርስቲያን ምዕመናንን በሚያስተምሩ ባንድ በመምህራን እናምናለን፡፡
ሐተታ፦ ሲያስተምሩ ሲያሳምኑ ሲያጠምቁ በቤተክርስቲያን ነውና ቅድስትን እንደ ሃይማኖተ አበው አትት፡፡
⭕️ ወነአምን በአሐቲ ጥምቀት ለሥርየተ ኃጢአት፡፡
ኃጢአት በሚሠረይባት ባንዲት ጥምቀት እናምናል፡፡
ሐተታ፦ በአብ ስም በወልድ ስም በመንፈስ ቅዱስ ስም ቢጠመቁ አንድ ነውና በዐርባ ቀን በሰማንያ ቀን በዐርባ ዘመን በሰማንያ ዘመን ቢጠመቁ አንድ ነውና፡፡
አንድም በሊቀ ጳጳስ በጳጳስ በኤጲስ ቆጶስ በቄስ እጅ ቢጠመቁ አንድ ነውና።
አንድም በዐቢይ ባሕር በማዕከላዊ ባሕር በንዑስ ባሕር ቢጠመቁ አንድ ነውና፡፡
⭕️ ወንሴፎ ትንሣኤ ሙታን፡፡
ከፈረሱ ከበሰበሱ በኋላ አካል አግኝተው ታድሰው ሙታን እንዲነሡም እናምናለን።
አንድም አንዘ ንሴፎ ይላል ሙታን እንዲነሡ አምነን ባንዲት ጥምቀት እናምናለን፡፡
ሐተታ፦ ማጥመቅ ትንሣኤ ሙታን ካሳመኑ በኋላ ነውና።
⭕️ ወሕይወተ ዘይመጽእ ለዓለመ ዓለም፡፡
ሐይው ከመ መላእክት እንዳለ እናምናለን፡፡
የጸሎተ ሃይማኖት የመጨረሻው አንቀጽ “ወንሴፎ ትንሣኤ ሙታን ወሕይወተ ዘይመጽእ ለዓለመ ዓለም” የሙታንንም መነሣት ተስፋ እናደርጋለን፤ የሚመጣውንም ሕይወት ለዘላለሙ ማለቱ በቀደሙት አንቀጾች ወነአምን (እናምናለን) ሲል መጥቶ እዚህ ላይ ወንሴፎ (ተስፋ እናደርጋለን) ማለቱ ትንሣኤ ሙታን (ትንሣኤ ዘጉባዔ) ወደፊት በተስፋ የምንጠባበቀው መሆኑን ለማመልከት ነው። ስለዚህም ክርስቶስ ለሙታን ሁሉ በኩር ሆኖ ተነሥቶ አብነት ሆኖናል። ከትንሣኤ ዘጉባዔም በኋላ የሚመጣ ዘላለማዊ ሕይወትን ተስፋ እንደምናደርግ ይህ አንቀጽ ያስረዳናል። የሥጋ ሞት የሕይወት መጨረሻ (ማብቂያ) አይደለም፣ መሻገሪያ እንጂ። ምክንያቱም የማትሞት የማትበሰብስ ነፍስ በውስጣችን አለችና። ከሥጋ ጋር የማትሞትና የማትጠፋ ነፍስ በሥጋችን ውስጥ እንዳለች እናስተውል እንዲል አመክንዮ ዘሐዋርያት። በትንሣኤ ዘጉባዔም እውነተኛ የእግዚአብሔር ፍርድ ትደረጋለች፣ እያንዳንዱም እንደየ ሥራው ይከፈለዋል (ራእይ 20:11-13)። ከዚያም በኋላ በአዲሲቷ ኢየሩሳሌም የሚመጣው ተብሎ የተገለጸው፣ በእግዚአብሔር መንግሥት ዘላለማዊ ሕይወት እንዳለ እናምናለን።
መጨረሻ ላይ መቀመጡ አንድም በመጨረሻው ዘመን የሚፈጸም ስለሆነ ነው። አንድም የእምነታችን መደምደሚያ (ማሠሪያ) አንቀጽ ስለሆነ ነው። ያለ ትንሣኤ ሙታን እምነታችን ከንቱ ናት።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “ትንሣኤ ሙታንስ ከሌለ ክርስቶስ አልተነሣማ፤ ክርስቶስም ካልተነሣ እንግዲያስ ስብከታችን ከንቱ ነው እምነታችሁም ደግሞ ከንቱ ናት፤ ደግሞም ክርስቶስን አስነሥቶታል ብለን በእግዚአብሔር ላይ ስለመሰከርን ሐሰተኞች የእግዚአብሔር ምስክሮች ሆነን ተገኝተናል፤ ሙታን ግን የማይነሡ ከሆነ እርሱን አላስነሣውም። ሙታን የማይነሡ ከሆነ ክርስቶስ አልተነሣማ፤ ክርስቶስም ካልተነሣ እምነታችሁ ከንቱ ናት፤ እስከ አሁን ድረስ በኃጢአታችሁ አላችሁ። እንግዲያስ በክርስቶስ ያንቀላፉት ደግሞ ጠፍተዋላ። በዚች ሕይወት ብቻ ክርስቶስን ተስፋ ያደረግን ከሆነ፥ ከሰው ሁሉ ይልቅ ምስኪኖች ነን።” (1ኛ ቆሮ 15:13-19) በማለት እንዳስተማረው የሙታን ትንሣኤ ከሌለ እምነታችን ከንቱ ናት።
ጸሎተ ሃይማኖት የሐዋርያዊት እምነታችን ማረጋገጫ ነው። እኛ የምናምነው እምነት የቀደሙት አባቶቻችን ያመኗት እምነት መሆኗን የምናረጋግጥበት የእምነት መለኪያ እውነተኛ ሚዛን ጸሎተ ሃይማኖት ነው። ጸሎተ ሃይማኖት የመንፈሳዊ አገልግሎቶች ሁሉ መሠረት ነው። የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ አምልኮ የተመሠረተው በጸሎተ ሃይማኖት በሠፈረው እምነታችን ላይ ነው። ከዘወትር ጸሎት ጀምሮ፣ ሥርዓተ ቅዳሴን ጨምሮ ያሉት የሥርዓተ አምልኮ አገልግሎቶች ሁሉ በዚህ እምነታችን ላይ የተመሠረቱ ናቸው። ጸሎተ ሃይማኖት የክርስትና አስተምህሮ መመሪያም ነው። የክርስትና አስተምህሮ ማዕከል ጸሎተ ሃይማኖት ነው። የክርስትና አስተምህሮ ዓላማ የሰው ልጆች በጸሎተ ሃይማኖት የተቀመጠውን እምነት እንዲያምኑ፣ በዚህ እምነት ላይ የታነጸውን ሥርዓተ አምልኮ እንዲፈጽሙና ለመንግሥተ ሰማያት እንዲበቁ ማስቻል ነው።
ጸሎተ ሃይማኖት የክርስቲያናዊ አንድነታችን መገለጫ ነው። ከሌሎች አኃት አብያተ ክርስቲያናት ጋር አንድ መሆናችን ወይም ከሌሎች ቤተ እምነቶች መለየታችን የሚታወቀው በመሠረተ እምነት ነው። በመሠረተ እምነት ላይ ተለያይተን በሌሎች ጉዳዮች አንድ ልንሆን አንችልም። በመሠረተ እምነት አንድ ከሆንን ደግሞ ሌሎች ልዩነቶች አይለያዩንም። ክርስትና ስንነሳ (ስናነሳ) – ወደ ቤተ ክርስቲያን አንድነት ስንጨመር – የምንመሰክረው (የምንጸልየው) ይህንን ጸሎተ ሃይማኖት ነው። ጸሎተ ሃይማኖት የኦርቶዶክሳዊት እምነት መጠበቂያ ነው። የአንድ አስተምህሮ እውነተኛነት የሚመዘነው በዚህ በጸሎተ ሃይማኖት ላይ በሠፈሩት አንቀጾች ይዘት መሠረት ነውና። ልክ አባቶቻችን እነ አርዮስንና መቅዶንዮስን አውግዘው እምነታቸውን በጸሎተ ሃይማኖት እንዳጸኑት ዛሬ እኛም እምነታችንን የምንጠብቀው (ዕቅበተ እምነት የምናከናውነው) በጸሎተ ሃይማኖት ነው።
2 171
ጸ ሎ ተ ሃ ይ ማ ኖ ት ት ር ጓ ሜ ነአምን በ፩ዱ አምላክ፡፡
በባሕርይ በሕልውና ከወልድ ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ አንድ አምላክ በሚሆን፡፡
⭕️ እግዚአብሔር አብ፡፡
በእግዚአብሔር አብ እናምናለን፡፡
⭕️ አኃዜ ኲሉ ገባሬ ሰማያት ወምድር፡፡
ሁሉን የሚገዛ፡፡
አንድም ሁሉን የፈጠረ እግዚእ አኃዜ ኲሉ ዓለም እንዲል፡፡
አንድም ሁሉን እንደ ጥና እንደ እንቁላል በመሐል እጁ የያዘ፡፡
ሰማይን ምድርን የፈጠረ ሰማየ ሰማያት ለእግዚአብሔር ብሎ ምድረሰ በሀበ ለእጓለ እመሕያው ካለው ሲለይ፡፡
አንድም ኢትፍርህዎሙ ለእለ ይቀትሉ ሥጋክሙ ወለ ነፍስክሙሰ ኢይክሉ ቀቲሎታ ካለው ሲለይ አንድም መላእክትን ደቂቀ አዳምን የፈጠረ
⭕️ ዘያስተርኢ ወዘኢያስተርኢ።
የሚታየውን ግዙፋኑን የማይታየውን ረቂቁን የፈጠረ፡፡
ዘያስተርኢ
ሐተታ፦ የሚታየው ግዙፋኑ ወዘኢያስተርኢ የማይታዩት ረቂቃኑ በርኅቀት በርቀት። በርኅቀት አድማስ ናጌብ ብሄሞት ሌዋታን በርቀት ነፍሳት ነፋሳት መላእክት ናቸው።
አንድም ዘያስተርኢ በዘፈቀደ የሚገለጥ ወዘኢያስተርኢ፡፡ በባሕርዩ የማይገለጥ።
አንድም ለበቁት የሚገለጥ ላልበቁት የማይገለጥ፡፡
አንድም ዘይርኢ ወዘኢያስተርኢ ይላል፡፡ የሚጠብቅ ሲጠብቅ የማይታይ፡፡
⭕️ ወነአምን በ፩ዱ እግዚእ ኢየሱስ ክርስቶስ
በተለየ አካሉ አንድ በሚሆን አንድም በባሕርይ በሕልውና ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ አንድ በሚሆን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እናምናለን፡፡
⭕️ ወልደ አብ ዋሕድ፡፡
ተቀዳሚ ተከታይ በሌለው የአብ የባሕርይ ልጁ በሚሆን፡፡
⭕️ ዘህልው ምስሌሁ እምቅድመ ይትፈጠር ዓለም
ዓለም ሳይፈጠር በሱ ሕልውና፡፡ አንድም ከሱ ጋራ እንደሱ በነበረ፡፡
⭕️ ብርሃን ዘእምብርሃን፡፡
ከብርሃን ከአብ በተገኘ በብርሃን በወልድ፡፡
⭕️ አምላክ ዘእምአምላክ ዘበአማን፡፡
ከባሕርይ አምላክ ከአብ በተገኘ በባሕርይ አምላክ በወልድ፡፡
⭕️ ዘተወልደ ወአኮ ዘተገብረ፡፡
በተወለደ ወአኮ ዘተገብረ ባልተፈጠረ፡፡
ሐተታ፦ አርዮስ ሸክላ ሠሪ መሥሪያውን ሠርታ እንድትሠራ ደበናንሳ መዶሻውን ሠርቶ ዘመደ ሐፃውንትን እንዲሠራ ፈጥሮ ፈጠረበት ይላልና ወአኮ ዘተገብረ አለ፡፡
⭕️ ዘዕሩይ ምስለ አብ በመለኮቱ፡፡
በሥልጣን በጌትነት በባሕርይ ከአባቱ ጋራ አንድ በሚሆን፡፡
⭕️ ዘቦቱ ኲሉ ኮነ፡፡
ሁሉ በእርሱ ቃልነት በእሱ ህልውና የተፈጠረ
⭕️ ዘእንበሌሁሰ አልቦ ዘኮነ
ያለሱ ቃልነት ያለሱ ህልውና የተፈጠረ የሌለ፡፡
⭕️ ወኢምንትኒ፡፡
ምንም የተፈጠረ የሌለ፡፡
ሐተታ፦ አርዮስ ፈጥሮ ፈጠረበት ይላልና ወኢምንትኒ አለበት፡፡
⭕️ ዘበሰማይኒ ወዘበምድርኒ፡፡
በሰማይ ያሉ ፀሐይ ጨረቃ ከዋክብት መላእክት በምድር ያሉ ዕፀው አዕባን እንስሳት አራዊት ሰውም ቢሆን ያለሱ የተፈጠረ ምንም የሌለ፡፡
⭕️ ዘበእንቲአነ ለሰብእ ወበእንተ መድኃኒትነ
ዘበእንቲአነና ወበእንተ መድኃኒትነ ወረደ እምሰማያት ፩ድ ወገን ስለ እኛ እኛን ለማዳን ከሰማየ ሰማያት ወርዶ፡፡
⭕️ ተሰብአ ወተሰገወ እመንፈስ ቅዱስ፡፡
ወተሰብአ እመንፈስ ቅዱስ ይላል አብነት እም፡ በ፡ ነው በግብረ መንፈስ ቅዱስ፡፡
ሐተታ፦ የከፈለ ያነፃ ያዋሐደ መንፈስ ቅዱስ ነውና
⭕️ ወእማርያም እምቅድስት ድንግል፡፡
እም እና እም አንድ ወገን ነው እመቤታችን ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ሰው የሆነ፡፡
አንድም መንፈስ ቅዱስ ከመክፈሉ የተነሣ እመቤታችን ይኩነኒ በከመ ትቤለኒ ከማለቷ የተነሣ ሰው የሆነ፡፡
⭕️ ኮነ ብእሴ፡፡
የሠላሳ ዓመት ጎልማሳ ሆነ፡፡ ወአመ ኮንኩ ብእሴ አውሰብኩ ብእሲተ ከመ ኲሉ ሰብእ እንዲል፡፡
⭕️ ወተሰቅለ በእንቲአነ በመዋዕለ ጲላጦስ ጰንጤናዊ፡፡
የጳንጦስ ሰው ጲላጦስ ነግሦበት በነበረ ወራት ስለእኛ የተሰቀለ፡፡ ሐተታ፦ እንደ ሰማዕታት ዕሤት ሽቶ እንደ ሌባ እንደ ወምበዴ ስቶ አይደለምና በእንቲአነ አለ፡፡
⭕️ ሐመ ወሞተ፡፡
ስለእኛ መከራ ተቀብሎ ሞተ፡፡
⭕️ ወተቀብረ
ተቀበረ፡፡
⭕️ ወተንሥአ እሙታን አመ ሣልስት ዕለት በከመ ጽሑፍ ውስተ ቅዱሳት መጻሕፍት፡፡
ንጹሐት ክቡራት በሚሆኑ መጻሕፍት እንደተጻፈ በሦስተኛው ቀን ተነሣ ነሥአ ደዌነ ወጾረ ሕማመነ እሁብ እኩያነ ህየንተ ሞቱ ወአብዕልተ ህየንተ መቅበርቱ ወልድየ ዕርግ እምህዝዓትከ ተብሎ እንደ ተጻፈ።
አንድም በከመ ጽሑፍ ዓርገ ይላል፡፡
⭕️ ዓርገ በስብሐት ውስተ ሰማያት፡፡
በብርሃን በቅዳሴ በክብር በሥልጣን ዐረገ፡፡
⭕️ ወነበረ በየማነ አቡሁ፡፡
ባባቱ ዕሪና ኖረ፡፡
ሐተታ፦ ንጉሥ የተጣላውን ሰናፊል አትታጠቅ በትር አታንሣ እንዲህ ካለ ቦታ አትውጣ ብሎ ቦታ እንዲወስንበት ቦታ ወሰነበት ማለት አይደለም፡፡ በምልዓት ሲል ነው እስመ ብሂለ የማን ይመርኅ ኀበ ተዋሕዶቶሙ በክብር እንዲል ነበረ የእንግድነት የማን የባለቤትነት ነው፡፡
አንድም ነበረ የባለቤትነት ነው፡፡ እንግዳን ንበር ይሉታል እንጅ ነበረ ይሉታልን፡፡
⭕️ ዳግመ ይመጽእ በስብሐት፡፡
ዳግመኛ በብርሃን በሥልጣን በቅዳሴ ይመጣል፡፡
⭕️ ይኰንን ሕያዋነ ወሙታነ፡፡
በሕያዋን በሙታን ይፈርድ ዘንድ አንድም ሕያዋንን ሙታንን ይገዛ ዘንድ፡፡
ሐተታ፦ ሕያዋን ያላቸው ጻድቃን ናቸው በነፍስ ሕያዋን ናቸውና።
አንድም በነፍስ ሕያዋን የሚሆኑበትን ሥራ ይሠራሉና አንድም የሕያው የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ ናቸውና ሙታን ያላቸው ኃጥአን ናቸው። በነፍስ ሙታን ናቸውና።
አንድም በነፍስ ሙታን የሚሆኑበትን ሥራ ይሠራሉና።
አንድም የምውት የዲያብሎስ ማደሪያ ናቸውና።
አንድም ኃጥአንን ሕያዋን አላቸው ጸላእትየሰ ሕያዋን ወይኄይሉኒ እንዲል በዚህ ዓለም ሕያዋን ናቸውና ጻድቃንን ሙታን አላቸው። ምውት አነ በኀበ ዓለም ወዓለምኒ ምውት በኀቤየ እንዲል የሹትን አያገኙትም።
አንድም ኃጥአንን ሕያዋን ሙታን አላቸው። ሕያዋን እስከዕለተ ምጽአት ሙታን ከዕለተ ምጽአት በኋላ።
አንድም ሕያዋን አላቸው በዚህ ዓለም ሙታን አላቸው በወዲያው ዓለም አንድም ሕያዋን አላቸው በሥጋ ሙታን አላቸው በነፍስ።
አንድም ጻድቃንን ሕያዋን ሙታን አላቸው ሙታን አላቸው እስከ ዕለተ ምጽአት ሕያዋን አላቸው ከዕለተ ምጽአት በኋላ።
አንድም ሙታን አላቸው በሥጋ ሕያዋን አላቸው በነፍስ አንድም ሙታን አላቸው በዚህ ዓለም ሕያዋን አላቸው በወዲያው ዓለም፡፡
⭕️ ወአልቦ ማኅለቅት ለመንግሥቱ፡፡
ለመንግሥቱም ፍጻሜ የለውም
ሐተታ፡፡ ዳዊት ሰሎሞን ቢገዙ ዐርባ ፤ ዐርባ ዘመን ነው ያውም እስከ ዳን እስከ ቤርሳቤህ ነው የሱ ግን ፍጻሜ የለውምና፡፡
⭕️ ወነአምን በመንፈስ ቅዱስ እግዚእ ማኅየዊ፡፡
የባሕርይ ገዢ በሚሆን በመንፈስ ቅዱስ እናምናለን፡፡
⭕️ ዘሠረፀ እምአብ፡፡
ከአብ አካል ዘእምአካል ባሕርይ ዘእምባሕርይ የሠረፀ፡፡
⭕️ ንስግድ ሎቱ ወንሰብሖ ምስለ አብ ወወልድ፡፡
ከአብ ከወልድ ጋራ እንስገድለት እንደ አብ እንደ ወልድ እናመስግነው፡፡
⭕️ ዘነበበ በነቢያት፡፡
ምስለ አብ ወወልድ ዘነበበ በነቢያት ብለህ ግጠም ከአብ ከወልድ ጋራ በነቢያት አድሮ የተናገረ ንሰብሖ ምስለ አብ ወወልድ ከአብ ከወልድ ጋራ እናመስግነው፡፡
2 171
እስመ ኃረያ እግዚአብሔር ለጽዮን ወአብደራ ከመ ትኲኖ ማኅደሮ ዛቲ ይእቲ ምዕራፍየ ለዓለም እግዚአብሔር ጽዮንን መርጧታልና፥ ማደሪያውም ትሆነው ዘንድ ወድዷታልና፥ እንዲህ ብሎ። ይህች ለዘላለም ማረፊያዬ ናት፤ መርጫታለሁና በዚህች አድራለሁ።
መዝሙር (Psalm)፦ 131(132) : 13―14
2 171
⭕️ ዳዊት ዘነግሠ ለእስራኤል አመይትነሥኡ ላዕሌሁ ዕልዋን። ፈትወ ይስተይ ማየ እምዓዘቅተ ቤተ ልሔም፡ ፍጡነ ተንሥኡ መላሕቅተ ሐራሁ ወተቃተሉ በውስተ ትዕይንተ ዕልዋን። ወአምጽኡ ሎቱ ውእተ ማየ ዘፈተወ ይሰተይ፡ ወሶበ ርእየ ውእቱ ጻድቅ ከመ አጥብዑ ወመጠው ነፍሶሙ ለቀትል በእንቲአሁ፡ ከዐወ ውእተ ማየ ወኢሰትየ እምኔሁ፡ ወእምዝ ተኈለቈ ሎቱ ጽድቅ እስከ ለዓለም። አማን መነኑ ሰማዕት ጣዕማ ለዛ ዓለም ወከዓው ደሞሙ በእንተ እግዚአብሔር ወተዐገሡ ሞተ መረረ በእንተ መንግሥተ ሰማያት። ተሥሃለነ በከመ ዕበየ ሣህልከ። ሰአሊ ለነ ቅድስት።
፮. ለእሥራኤል የነገሠ ዳዊት ኢሎፍላውያን በጠላትነት በተነሡበት ጊዜ ከቤተልሔም ምንጭ ውሃ ይጠጣ ዘንድ ወደደ፡፡ ዳዊት ታመመ፤ ቢታመም ዘመዶቹቀሳ አወጡት፡፡ ኢሎፍላውያን ይህን ሰምተው ቤተ ልሔምን አልፈው ሰፈሩ፡፡ ዳዊትም “ከቤተልሔም ምንጭ ውሃ ማን ባመጣልኝ?” አለ፡፡ ከእናንተ መካከል፡- “ስለምን ከቤተልሔም የተቀዳ ውሀ ይጠጣ ዘንድ ወደደ?” የሚል ሊኖር ይችላል፡፡ እኛም እንዲህ ብለን እንመልስለታለን፡- ከላይ ለመግለጽ እንደሞከርነው ታምሞ ስለነበር የቤተ ልሔም ውሀ ደግሞ ማየ ፈውስ ናትና።
/፪ኛ ነገ.፳፫፡፲፭-፲፯፣ አንድምታውን ይመልከቱ/
ስለኾነም የጭፍራ አለቆች አዲኖን ኢያቡስቴ ኤልያናም አፍ አፋቸውን ታጥቀው፣ ዘገራቸውን ነጥቀው፣ ራዋታቸውን ጭነው “የማን ጌታ በውሃ ጥም ይሞታል?” ብለው ፈጥነው ተነሡ፡፡ በኢሎፍላውያን ከተማ ተዋጉለት፡፡ ይጠጣ ዘንድ የወደደውንም ውሀ አመጡለት፡፡ ብጹዕ ዳዊት ግን ስለ ርሱ ሰውታቸውን ለሞት አሳልፈው እንደ ሰጡ በየ ጊዜ የራዋቱን ውሀ አፈሰሰው፡፡ በማለፊያው ቀድተው የሰጡትን አልጠጣም፡፡ “የናንተን ደም መጠጣት ነው” ብሎ አፍሶታል፡፡ አንድም ውሀውን መሥዋዕት አድርጐ ለእግዚአብሔር አፈሰሰው፡፡ ከእናንተ መካከል፡- “ዳዊት ንጉሥ ሲኾን መሥዋዕት የሚኾን ላም በግ አጥቶ ነውን?” ብሎ የሚጠይቅ ሊኖር ይችላል፡፡ በፍጹም! እግዚአብሔር የወደዱትን ቢተዉለት ስለሚወድ ነው እንጂ።
/መዝ.፶፬፡፮፣ ዝኒ ከማሁ፣ ገጽ ፻፵፭/፡፡
ዳዊት የወደደውን ውሀ ስለ እግዚአብሔር ብሎ ስላፈሰሰውም ጽድቅ ኾኖ ተነገረለት፡፡ አዲኖን፣ ኢያቡስቴ፣ ኤልያና ስለ ዳዊት ብለው ጣዕመ ዓለምን እንደናቁ፤ ዳዊትም ስለነርሱ አንድም ስለ እግዚአብሔር ብሎ ጣዕመ ማይን እንደናቀ ሰማዕታት ጣዕመ ዓለምን ናቁ፡፡ አዲኖን፣ ኢያቡስቴ፣ ኤልያና ዳዊትን ብለው ደማቸውን እናፍስ እንዳሉ፤ ዳዊትም ውሀውን እንዳፈሰሰ፤ ሰማዕታትስለ እግዚአብሔር ብለው ደማቸውን አፈሰሱ፡፡ አዲኖን፣ ኢያቡስቴ፣ ኤልያና ስለ ዳዊት ብለው መራራ ሞትን እንታገሥ እንዳሉ፡ ዳዊትም ጽምዓ ማይን ልታገሥ እንዳለ ሰማዕታት መራራ ሞትን ታገሡ፡፡ ቸር አባት ሆይ! እኛስ እንደ ሰማዕታት ከዓላውያን ነገሥታት፣ ከዓላውያን መኳንንት ገብተን መከራውን ታግሠን ተቀብለን፤ እንደ ምዕመናንም ከፍትወታት ከእኩያት ኃጣውእ ተዋግተን ድል ነሥተን መዳን አይቻለንምና እንደ ቸርነትህ ብዛት ይቅር በለን፡፡
ቸርና ይቅር ባይ ከሚባል ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣ ለምኚልን፡፡
⭕️ አሐዱ ዘእምቅድስት ሥላሴ፤ ርእዮ ትሕትናነ አጽነነ ሰማየ ሰማያት፡ መጽአ ወኅደረ ውስተ ከርሠ ድንግል፡ ወኮነ ሰብአ ከማነ ዘእንበለ ኃጢአት ባሕቲታ፡ ወተወልደ በቤተልሔም በከመ ሰበኩ ነቢያት፡ አድኃነነ ወቤዘወነ ወረስየነ ሕዝበ ዚአሁ። ሰአሊ ለነ ቅድስት።
፯. ከሦስቱ አካል አንዱ አካል በእግረ አጋንንት መረገጣችንን መጠቅጠቃችንን አየና ባሕርዩን ዝቅ አድርጎ ሰው ኹኖ በድንግል ማኅፀን አደረ /ኢሳ.፶፱፡፮/፡፡ ባሕርየ መላእክትን ባሕርይ አላደረገም፤ ባሕርየ ሰብእን ባሕርይ አድርጎ በድንግል ማኅፀን አደረ እንጂ /ዕብ.፪፡፲፮/፡፡ ከብቻዋ ከኃጢአት በቀርም እንደኛ ሰው ኾነ /ዕብ.፬፡፲፬/፡፡ ሚክያስና ዳዊት በቤተ ልሔም ይወለዳል ብለው እንደ ተናገሩ በቤተልሔም ተወለደ፡፡ “ይሙት ቤዛነ በትስብእቱ ወየሀበነ መድኃኒተ ዘከመ መለኮቱ” እንዲልም እንደ አምላክነቱ አዳነን እንደ ሰውነቱም ቤዛ ኾነን /ኤፌ.፩፡ ፯/፡፡ ዳግመኛም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ፡- “እናንተ አስቀድሞ በሥጋ አሕዛብ የነበራችሁ፥ በሥጋ በእጅ የተገረዙ በተባሉት ያልተገረዙ የተባላችሁ፥ ይህን አስቡ፤ በዚያ ዘመን ከእስራኤል መንግሥት ርቃችሁ ለተስፋውም ቃል ኪዳን እንግዶች ኾናችሁ በዚህም ዓለም ተስፋን አጥታችሁ ከእግዚአብሔርም ተለይታችሁ ያለ ክርስቶስ ነበራችሁ። አሁን ግን እናንተ በፊት ርቃችሁ የነበራችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ ኾናችሁ በክርስቶስ ደም ቀርባችኋል” /ኤፌ.፪፡፲፩-፲፫/ እንዲል ወገኖቹ ያልነበርን እኛን ወገኖቹ አደረገን፡፡ ወገኖቹ ካደረገን ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣ ለምኚልን፡፡
ይኸን ሲጨርስ በያዘችው መስቀለ ብርሃን ባርካው ወደ ሰማይ ታርጋለች፡፡ እርሱም ተባርኮ እጅ ነሥቶ ይቀራል፡፡
አነሣሥቶ ላስጀመረን አስጀምሮም ላስጨረሰን ለልዑል እግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይግባው አሜን!!!
ለአባ ሕርያቆስ ፤ ለቅዱስ ኤፍሬም፤ ለቅዱስ ያሬድ ፤ ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የተገለጽሽ እመቤታችን ጽንዕት በድንግልና ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን።
እመቤታችን እኛንም በበረከት እና በረድኤት ትጎብኘን ፤ ከልጇ ከወዳጇ ከመድኃኔዓለም ዘንድ ታማልደን፤
ሃገራችንን ኢትዮጵያ ከጥፋት፣ ቤተክርስቲያንን ከመ*ናፍቃን፣ ሕዝቦቿን ከስደት ትጠብቅልን።
ጾሙን ጾመ ሥርየት፤ ጾመ መድኃኒት ያድርግልን ፣ ሱባኤያችንን በሠላም አስፈጽሞ ለትንሣኤዋ እና ለእርገቷ በሠላም ያድርሰን
2 171
አንድም ወርቅ ጽሩይ ነውና “ባንተ ያመኑ ምዕመናን ጽሩያነ ምግባር ወሃይማኖት ናቸው” ሲሉ ወርቅ አመጡለት፡፡ ዕጣን ምዑዝ ነውና “ባንተ ያመኑ ምእመናንም ምዑዛነ ምግባር ወሃይማኖት ናቸው” ሲሉ ዕጣን አመጡለት፡፡ ዳግመኛም በዕለተ ሞቱ ያቀምሱታልና ከርቤ አመጡለት፡፡ ቸርና ሰው ወዳጅ የኾነ አንድ እርሱ ብቻ ነው፡፡
ቸርና ሰው ወዳጅ ከኾነ ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
⭕️ ኦ ዝ መንክር ነሥእ ፩ድ ዐፅመ እምገቦሁ ለአዳም ወለሐኮ እምኔሁ ብእሲተ ወኩሎ ፍጥረተ እጓለ እምሕያው፡ ተውህበ እግዚእ ቃለ አብ ተሰብአ እምቅድስት ድንግል ወተሰምየ አማኑኤል ወበእንተዝ ንስአል ኅቤሃ ኩሎ ጊዜ ከመ ታስተሥር በእንቲአነ ፍቅር ወልዳ፡ ዔርት ይእቲ በኅበ ኩሎሙ ቅዱሳን ወሊቃነ ጳጳሳት እስመ አምጸት ሎሙ ዘኪያኡ ይጸንሑ፡ ወለነብ ኢያትኒ አምጽአትሎሙ ለዘበእንቲአሁ ተነበዩ፡ ወለሐዋርያትኒ ወለደት ሎሙ ዘሰበኩ በሱም ውስተ ኩሉ አጽናፈ ዓለም፡ ለሰማዕት ወለመሃይማን ወፅአ እምኔሃ ዘተጋደሉ በእንቲአሁ ኢየሱስ ክርስቶስ ብዕለ ጸጋ ጥበቡ ዘኢይትዐወቀ፡ ንኅሥሥ ዕበየ ሣህሉ ስጽአ ወአድኃነነ። ሰአሊ ለነ ቅድስት።
፬. ከአዳም ጎን አንድ ዐፅም መንሣቱ ምን ይረቅ? ምን ይጠልቅ? “በእምነት ዓይን ከማየት በቀር ይህ ከኅሊናት በላይ የኾነውን ድንቅ ነገር በቋንቋ መናገር አይቻለንም” /St. John Chrysostom, Homily 15 on Genesis/፡፡ ከእርሱ (ከአዳም) ሔዋንን ፈጠረ፡፡ ፍጥረትንም ኹሉ ከአዳምና ከሔዋን ፈጠረ፡፡ እንዲህም አድርጎ የአብ አካላዊ ቃል ለኵነተ ሥጋ (ለሕማም ለሞት) ተሰጠ፡፡ ከልዩ ድንግልም ሰው ኾነና አማኑኤልም ተባለ፡፡ “ኦ ለዝንቱ መንክር ልዑል ላዕለ ኵሉ ሕሊናት ብእሲት ምድራዊት ወለደቶ ለእግዚአብሔር ቃል ዘኮነ ሰብአ… - ከኅሊናት ኹሉ ለራቀ ለዚህ ድንቅ ምሥጢር አንክሮ ይገባል፤ ምድራዊት ሴት ሰው የኾነ እግዚአብሔር ቃልን ወለደችው፡፡ ድንግል ፈጣሪዋን ወለደችው፤ እርሱም እናቱን ፈጠረ፡፡ ከእርሷም እርሱ የፈጠረውን ሥጋ ተዋሐደ” /ሃይ.አበ.፵፯፡፪/፡፡
ስለዚህ ነገር ከልጅዋ ከወዳጅዋ ታማልደን ዘንድ ኹል ጊዜ እርስዋን እንለምን፡፡ በቅዱሳን ዘንድ ቸር ናትና እርሷን እንለምን፡፡ ለሊቃነ ጳጳሳት አስበ ጵጵስናችን (የጵጵስናችን ዋጋ) ይሰጠናል ብለው ደጅ የሚጠኑትን ወልዳላቸዋለችና ከልጅዋ ከወዳጅዋ ታማልደን ዘንድ ኹል ጊዜ እርስዋን እንለምን፡፡ ነቢያት አስበ ትንቢታችንን ይሰጠናል ብለው “ይወርዳል፤ ይወለዳል” ብለው ትንቢት የተናገሩለትን ወልዳላቸዋለችና ከልጅዋ ከወዳጅዋ ታማልደን ዘንድ ኹል ጊዜ እርስዋን እንለምን፡፡ ሐዋርያት አስበ ሰብከታችንን ይሰጠናል ብለው “ውስተ ኵሉምድር ወፅአ ነገሮሙ ወእስከ አጽናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ - መምህራነ ሐዲስ ሐዋርያት ለምእመናነ ሐዲስ ወረደ ተወለደ ብለው አስተማሩ” እንዲል /መዝ.፲፰፡፬/ ጽንፍ እስከ ጽንፍ ዙረው ወረደ ተወለደ ብለው ያስተማሩለትን ወልዳላቸዋለችና ከልጅዋ ከወዳጅዋ ታማልደን ዘንድ ኹል ጊዜ እርስዋን እንለምን፡፡ ሰማዕታ ከዓላውያን ነገሥታት፣ ከዓላውያን መኳንንት ገብተው አስበ ትዕግሥታችንን ይሰጠናል ብለው መከራውን ታግሠው የተቀበሉለትን፣ ምዕመናን አስበ ተጋድሏቸውን ይሰጠናል ብለው ከፍትወታት ከእኩያት ኃጣውእ የተዋጉለት ኢየሱስ ክርስቶስን ወልዳቸዋችና ከልጅዋ ከወዳጅዋ ታማልደን ዘንድ ኹል ጊዜ እርስዋን እንለምን፡፡ ሰው ኹኖ አድኖናልና በጥበቡ እየሰፈረ የሚሰጠው፣ ዳግመኛም የጸጋው ብዛት የማይታወቅ የቸርቱን ብዛት መርምረን እንወቅ፡፡
ሰው ኹኖ ካዳነን ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እዳይነሣን ለምኚልን፡፡
⭕️ መሐለ እግዚኣብሔር ለዳዊት በጽድቅ ወኢይኔስሕ፡ እስመ እምፍሬ ከርሥከ አነብር ዲበ መንበርከ፡ ወሶበ ተወክፎ ውእቱ ጽድቅ ከመ እምኔሁ ይትወለድ ክርስቶስ በሥጋ፡ ፈቀደ ይኅሥስ ወይርከብ ማኅደሮ ለእግዚአብሔር ቃል ወፈጸመ ዘንተ በዐቢይ ትጋህ፡ ወእምዝ ጸርሐ በመንፈስ ወይቤ፡ ናሁ ሰማዕናሁ በኤፍራታ ወማኅደሮ ለአምላክ ያዕቆብ፡ እንተ ይእቲ ቤተ ልሔም ዘኅረያ አማኑኤል ይትወለድ ውስቴታ በሥጋ ለመድኃኒተ ዚአነ፡ ካዕበ ይቤላ ካልእ እምነብያት ወአንቲኒ ቤተልሔም ምድረ ኤፍራታ ኢትቴሐቲ እምነገሥተ ይሁዳ፡ እስመ እምኔኪ ይወፅእ ንጉሥ ዘይርዕዮሙ ለሕዝብየ እስራኤል፡ ኦዝ ነገር ለእሉ እለ ተነበዩ ዘበአሃዱ መንፈስ በእንተ ክርስቶስ ሎቱ ስብሓት፡ ምስለ ኄር አብሁ፡ ወመንፈስ ቅዱስ እምይእዜ ወእስከ ለዓለም። ሰአሊ ለነ ቅድስት።
፭. ተናግሮ የማያስቀር፣ ምሎ የማይከዳ እግዚአብሔር፡- “ከባሕርይህ የተከፈለ ልጅህ (ክርስቶስን) በዙፋንህ አስቀምጥልሃለሁ” ብሎ ለዳዊት በእውነት ማለለት /መዝ.፻፴፩፡፲፩/፡፡ ዳዊትም ክርስቶስ በሥጋ ከእርሱ እንዲወለድ ባመነ ጊዜ የአካላዊ ቃል ማደርያውን መርምሮ
ያውቅ ዘንድ ወደደ፡፡ ቀኖናም ገባ፡፡ ከዚህም በኋላ “ናሁ ሰማዕናሁ በኤፍራታ ወረከብናሁ ውስተ ዖመ ገዳም - በኤፍራታ ተወልዶ፤ በጎል ተጥሎ፤ በጨርቅ ተጠቅልሎ በግዕዘ ሕፃናት ሲያቅስ ሰማነው” አለ /መዝ.፻፴፩፡፮/፡፡ ይህቺውም እኛን ስለማዳን ይወለድባት ዘንድ የመረጣት ቤተልሔም፣ ቤተ ኅብስት የተባለች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት፡፡ ከሰማይ የወረደው ኅብስት እርሱ ነውና /ዮሐ.፮፡፶፩/፡፡
ከነቢያት አንዱ የሚኾን ሚክያስም ዳግመኛ እንዲህ አላት፡- “አንቺም የኤፍራታ ዕፃ የምትኾኝ ቤተ ኅብስት ቤተልሔም እመቤታችን ሆይ! በይሁዳ ከነገሡ ነገሥታት ብትበልጭ እንጂ አታንሺም፡፡ እሥራኤል ዘነፍስን የሚጠብቅ ንጉሥ ባንቺ ይወለዳልና እንዲህ እንደኾንሽ አትቀሪም፡፡ ንጉሥ ይወለድብሻል፤ ቅዳሴ መላእክት ይሰማብሻል፤ የብርሃን ድንኳን ይተከልብሻል፤ መቶው ነገደ መላእክት ደጅ ይጠኑብሻል፡፡ አሕዛብ ይገብሩብሻል” ብሏታል /ሚክ.፭፡፪/፡፡ ጀሮም የተባለ ቅዱስ አባት ይህን አንቀጽ ሲተረጕም፡- “ከሰማይ የወረደ ኅብስት /ዮሐ.፮፡፶፩/ የተወለደብሽ ቤተ ኅብስት ሆይ! ሰላምታ ይገባሻል፡፡ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የተወለደብሽ ምድረ ፍሬ፣ ምድረ ምውላድ (ኤፍራታ) ሆይ! ሰላምታ ይገባሻል፡፡ በዘመነ ብሉይ ሚክያስ ነቢይ ስለ አንቺ ሲናገር እንዲህ ብሎ ተናግሮ ነበርና፡- ‘ወአንቲኒ ቤተ ልሔም ምድረ ኤፍራታ ኢትቴሕቲ እም ነገሥተ ይሁዳ - አንቺም የኤፍራታ ዕፃ የምትኾኝ ቤተልሔም ከይሁዳ ገዢዎች ከቶ አታንሺም /ማቴ.፪፡፮/፡፡ ኢይወጽእ ምስፍና ወምልክና እም አባሉ ለይሁዳ - በትረ መንግሥት ከይሁዳ አይጠፋም እንዲል /ዘፍ.፵፱፡፲/ ከባሕርይ አባቱ ከአብ ጋር ቅድመ ዓለም የነበረ፣ ከዲያብሎስ አስቀድሞ ቀዳማዊ የኾነ እሥራኤል ዘነፍስን የሚጠብቅ ንጉሥ ከአንቺ ይወጣል (ይወለዳልና)” ብሏል።
/St. Jerome, Letter 108:10/
ወዮ! ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዕለተ ምጽአት ድረስ ከአብ ከባሕርይ አባቱ ከመንፈስ ቅዱስ ከባሕርይ ሕይወቱ ጋራ ክብር ይግባውና በአንድ በመንፈስ ቅዱስተገልጾላቸው የክርስቶስን ነገር የተናገሩ ሚክያስና ዳዊት የተናገሩት ነገር ምን ይረቅ? ምን ይጠልቅ? አንድም ሚክያስና ዳዊት ለተናገሩት ነገር አንክሮ ይገባል፡፡
ከአብ ከባሕርይ አባቱ ከመንፈስ ቅዱስ ከባሕርይ ሕይወቱ ጋር ክብር ከሚገባው ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
2 171
ወዮ! ሰውን የሚወድ ሰውም የሚወደው እግዚአብሔር፣ ማኅደርም ኀዳሪም ያይደለ አካላዊ ቃል፣ ሳይለወጥ ቅድመ ዓለም የነበረ እግዚአብሔር ወልድ፣ ከአብ አንድነት ሳይለይ መጥቶ ንዕድ ክብርት ከምትኾን ከእመቤታችን ሰው ኾኗልና፤ እርሱንም ከወለደችው በኋላ እንደ ቀድሞ ማኅተመ ድንግልናዋ ሳይለወጥ ኑራለችና፤ ስለዚህም ነገር አምላክን የወለደች እንደኾነች በጎላ በተረዳ ነገር ታውቃለችና ለርሷ ድንቅ ኾኖ የሚነገረውን ነገር መናገር የሚቻለው ምን አንደበት ነው? መስማትስ የሚቻለው ምን ጆሮ ነው? ማወቅስ የሚቻለው ምን አእምሮ ነው? የእግዚአብሔር የጥበቡ ምላት ስፋትስ ምን ይረቅ? ምን ይጠልቅ? አንድም ለእግዚአብሔር ለጥበቡ ምላት ስፋት አንክሮ ይገባል፡፡ “በፀነስሽ ጊዜ ጭንቅሽን እጅግ አበዛለሁ፤ በጭንቅ ትወልጃለሽ፤ ፈቃድሽም ወደ ባልሽ ይሆናል፥ እርሱም ገዥሽ ይሆናል” /ዘፍ.፫፡፲፮/ ብሎ የፈረደባት ማኀፀን የሕይወት፣ የድኅነት መገኛ ኾነች፡፡ ዕንቆ ጳዝዮን የተባለ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም፡- “እስመ ቀዳሚኒ ሔዋን ኮነት ድንግል ወአስሐታ ዲያብሎስ ለማርያምሂ ድንግል አብሠራ ገብርኤል ወባሕቱ ለሔዋንሰ አስሐታ ዲያብሎስ ወወለደት ቃየልሀ ዘውእቱ ምክንያተ ሞት ወማርያምሰ ሶበ አብሠራ መልአክ ወለደት ቃለ በሥጋ ዘውእቱ መራሔ ኵሉ ኀበ ሕይወት ዘለዓለም - ቀድሞም ሔዋን ድንግል ነበረችና ዲያብሎስ አሳታት እንጂ፤ ድንግል ማርያም ግን ገብርኤል አበሠራት፡፡ ነገር ግን ሔዋንን አሳታት፤ የሞት ምክንያት የሚኾን ቃየልን ወለደች፤ ማርያም ግን መልአክ ባበሠራት ጊዜ ኹሉን ወደ ዘለዓለም ሕይወት የሚመራ አካላዊ ቃልን በሥጋ ወለደች፡፡ የሔዋንን ልብላ ልብላ ማለቷ ዕፀ በለስ የሞት ምክንያት እንደኾነ አስረዳ፡፡ በዚያም አዳም ተድላ ደስታ ካለበት ከገነት ወጣ፡፡ ከድንግል የተወለደ አካላዊ ቃል ግን ዕፀ መስቀል የድኅነት ምክንያት እንደኾነ ገለጠ፡፡ በዚያም መስቀል ቀማኛ ወንበዴ የነበረው ሰው ከአባቱ ከአዳምና ከቀደሙ አባቶች ኹሉ ጋር ተድላ ደስታ ወዳለበት ገነት ገባ” ብሏል /ሃይ.አበ.፷፯፡፫-፭/፡፡
ከባሕርያችን መርገመ ሥጋን መርገመ ነፍስን የሚያጠፋልንን ጌታን ዘር ምክንያት ሳይኾናት ወለደችው፡፡ ስለዚህ ነገር “ሰውን የምትወድ ሰው የሚወድህ አቤቱ ክብር ላንተ ይገባል” እያልን እናመስግነው፡፡ “ኄር ዘበህላዌሁ ዘልማዱ ኂሩት - በባሕርይው ቸር የኾነ፤ ቸርነትን ማድረግም ልማዱ የኾነ” እያልን እናመስግነው፡፡
ኄር ዘበህላዌሁ ዘልማዱ ኂሩት ከሚባል ልጅሽ ጸንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
⭕️ ኦ ዝ መንክር ወዕፁብ ኃይል ከርሣ ለድንግል ወላዲተ አምላክ ዘእንበለ ዘርእ ስምዐ ኮነ መልአክ ዘአስተርአዮ ለዮሴፍ እንዘ ይብል ከመዝ፡ እስመ ዘትወለድ እምኔሃ እመንፈስ ቅዱስ ቃለ እግዚአብሔር ዉእቱ ተሰብአ ዘእምበለ ውላጤ፡ ወለደቶ ማርያም ምክዕቢተ ዝንቱ ፍሥሓ፡ ወይቤ ትወልዲ ወልደ ወይሰመይ አማኑኤል ዘበትርጓሜሁ እግዚአብሔር ምስሌነ፡ ወዓዲ ይስመይ ኢየሱስሃ ዘይድኅኖም ለሕዝቡ እምኃጢአቶም ያድኅነነ በኃይሉ ወይሥረይ ኃትጥያትነ እስመ ጥዩቀ አእምርናሁ ከመ አምላክ ውእቱ፡ ዘኮነ ሰብአ ሎቱ ስብሐት እስከ ለዓለም፡ ኦዝ መንክር ልድተ አምላክ እማርያም እምቅድስት ድንግል፡ አግመረቶ ለቃል ኢቀደሞ ዘርእ ለለደቱ ወኢአማሰነ በልደቱ ድንግልናሃ፡ እምኅበ ወፅአ ቃል ዘንበለ ድካም፡ ወእምድንግል ተወልደ ዘእምበለ ሕማም፡ ሎቱ ሰገዱ ሰብአ ሰገል፡ አምጽኡ ዕጣነ ከመ አምላክ ውእቱ፡ ወርቀ እስመ ንጉሥ ውእቱ፡ ወከርቤ ዘይትወሀብ ለሞቱ ማሕየዊ በእንቲኣነ ተወክፈ በፈቃዱ፡ ፩ዱ ውእቱ ባሕቲቱ ኄር ወመፍቀሬ ሰብእ። ሰአሊ ለነ ቅድስት።
፫. ዘር ምክንያት ሳይኾናት አምላክን የወለደች ድንግል፣ የማኅፀንዋ ሥራ ምንይረቅ? ምን ይጠልቅ? አንድም ለድንግል ለማኅፀኗ ሥራ አንክሮ ይገባል፡፡ ለዮሴፍ የነገረው መልአክ ሳይለወጥ ሰው የኾነ አካላዊ ቃል ከርሷ የሚወለድ በግብረ መንፈስ ቅደስ እንደኾነ መስክሯልና /ማቴ.፩፡፳/፡፡ ማርያም የዚህ ደስታ ዕፅፍ ድርብ የሚኾን ጌታን ወለደችው፡፡ ሴቶች ልጅ ትወልዳላችሁ ሲባሉ ደስ ይላቸዋል፤ ይልቁንም ወንድ ትወልዳላችሁ ሲሏቸው ደስ ይላቸዋል፡፡ እመቤታችን ግን ከዚሁ ኹሉ ያለፈ አምላክን ወልዷለችና ደስታዋ ዕፅፍ ድርብ ኾነላት፡፡ መልአኩ፡- “ልጅ ትወልጃለሽ፤ ስሙም አማኑኤል ይባላል” አላት፡፡ አማኑኤልም ማለት እግዚአብሔር ከሥጋችን ሥጋ ከነፍሳችን ነፍስ ነሥቶ ከኛ ጋራ አንድ ባሕርይ ኾነ ማለት ነው፡፡ ዳግመኛም ወገኖቹን ከኃጢአታቸው ፍዳ የሚያድናቸው መድኃኒት ይባላል አላት /ማቴ.፩፡፳፩/፡፡ በመኾኑም በክሂሎቱ (በከሃሊነቱ) ያድነን ዘንድ፣ ኃጢአታችንን ያስተሠርይልን ዘንድ (እስከ ዕለተ ምፅአት ድረስ ክብር ይግባውና) ሰው የኾነ እርሱ አምላክ እንደኾነ በተረዳ ነገር አወቅነው፡፡ አምላክ ብቻ ቢኾን ባልታመመ ነበርና፤ ሰውም ብቻ ቢኾን ባላደነን ነበርና፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም ከዚህ ጋር አያይዞ ፡- “ፍቁራን ሆይ! ምንም እንኳን ለዚህ ክብር የተገባን ኾነን ባንገኝም አባታችን በከኀሊነቱ እንዲሁ ከኀጢአታችን አድኖናልና ይህን ክብር፣ ይህን ጸጋ በፍጹም ልናክፋፋው (ልናቆሽሸው) አይገባንም፡፡ ልጅነት እንዲሁ ሳይሰጠን ለምረረ ገሃነም የተገባን የቁጣ ልጆች ከነበርን፤ ይህ ከኅሊናት በላይ የኾነ ጸጋ ከተቀበልን በኋላማ ፍዳችን እንደምን የበዛ አይኾን?
ልጆቼ! ይህን የምለው እንዲሁ ለመናገር ያህል አይደለም፡፡ ዳግም ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ከማኅፀነ ዮርዳኖስ ከተወለዱ በኋላ ብዙ ክርስቲያኖች በኀጢአት፣ በስንፍና፣ ለምግባርና ለትሩፋት ሳይሽቀዳደሙ ታክተው ስለምመለከት ነው እንጂ” ሲል ይመክረናል /St. John Chrysostom, Homily on the Gospel of St. Matthew, Homily IV/፡፡
ወዮ! ንዕድ ክብርት ከምትኾን ከእመቤታችን ይህ የአምላክ መወለድ ምን ይረቅ? ምን ይጠልቅ? ቃልን ወሰነችው፡፡ ለልደቱም ዘርዕ ምክንያት አልኾነውም፡፡ በመወለዱም ማኅተመ ድንግልናዋን አልለወጠውም፡፡ ከአብ አካል ዘእምአካል ባሕርይ ዘእም ባሕርይ ድካም ሳይሰማው የተወለደ እርሱ ፭ ሺሕ ከአምስት መቶ ዘመን ሲፈጸምም ከድንግል ሕማም ሴቶች የሚሰማቸውን ሕማም ሳይሰማት እርሱን ሕፃናትን የሚሰማቸው ሕማም ሳይሰማው ተወለደ እንጂ፡፡ ሰብአ ሰገል ሰገዱለት፡፡
አምላክ ነውና አምላክ እንደኾነ ለማጠየቅ ዕጣን አመጡለት፡፡ ንጉሥ ነውና ንጉሥ እንደ ኾነ ለማጠየቅ ወርቅ አመጡለት፡፡ ማኀየዊ የሚኾን የሞቱ ምሳሌ ከርቤንም አመጡለት፡፡
አንድም “ይኸን ወርቅ እንገብርላቸው የነበሩ ነገሥታት ቀድሞም ፍጡራን ኋላምኀላፍያን ናቸው፤ አንተ ግን ቀድሞም ያልተፈጠርህ ኋላም የማታልፍ ነህ” ሲሉወርቅ አመጡለት፡፡ “ይኽን ዕጣን እናጥናቸው የነበሩ ጣዖታት ቀድሞም ፍጡራን ኋላም ኃላፊያን ናቸው፤ አንተ ግን ቀድሞም ያልተፈጠርህ ኋላም የማታልፍ ነህ” ሲሉ ዕጣን አመጡለት፡፡ “ምንም ቀድሞ ያልተፈጠርህ ኋላም የማታልፍ ብትኾን በሰውነትህ መራራ ሞትን ትቀምሳለህ” ሲሉ ከርቤ አመጡለት፡፡
አንድም ወርቅ ጽሩይ ነውና “ጽሩየ ባሕርይ ነህ” ሲሉ ወርቅ አመጡለት፡፡ ዕጣን ምዑዝ ነውና “አንተም ምዑዘ ባሕርይ ነህ” ሲሉ ዕጣን አመጡለት፡፡ ዳግመኛም “ከርቤ የተሰበረውን ይጠግናል፤ የተለያየውን አንድ ደርጋል፡፡ አንተም ከማኀበረ መላእክት የተለየ አዳምን አንድ ታደርገዋለህ፤ ጽንዓ ነፍስ ሰጥተህ ታጸናዋለህ” ሲሉ ከርቤ አመጡለት፡፡
2 171
የኃሙስ ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ ውዳሴሃ ለእግዝእትነ ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ ዘይትነበብ በዕለተ ኃሙስ
⭕️ ዕፀ እንተ ርእየ ሙሴ በነደ እሳት ውስተ ገዳም ወአዕፁቂሃ ኢትውዒ፡ ትመስል ማርያም ድንግል ዘእንበለ ሩኩስ ተሰብአ እማኔሃ ቃለ አብ፡ ወኢያውዐያ እሳት መለኮቱ ለድንግል፡ እምድኅረ ውለደቶ ድንግልናሃ ተረክበ። ወመለኮቱ ኢተወለጠ ኮነ ወልደ ዕጓለ እምሕያዉ አምላክ ዘበአማን መጽአ ወአድኃነነ። ሰአሊ ለነ ቅድስት።
ይህ ዕለት ለምስጋና አራተኛ ለፍጥረት አምስተኛ ቀን ነው፡፡ በዚህም ቀን እመቤታችን ትመጣለች፤ የብርሃን ድባብ ይዘረጋል፤ የብርሃን ዙፋን ይነጸፋል፡፡ ከዚያ ላይ ኹናም ሊቁን ባርካው ምስጋናዉን ጀምሯል፡፡ ከወትሮ ይልቅም ነቢያትንና ሐዋርያትን አስከትላ መጥታለች፡፡
፩. ነደ እሳት ሰፍሮባት፣ በነደ እሳት ተከባ፣ ጫፎቿ ሳይቃጠሉ ሙሴ በደብረ ሲና ያያት ዕፅ ድንግል ማርያምን ትመስላለች /ዘጸ.፫፡፩-፫/፡፡ አካላዊ ቃል ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ሰው ኹኗልና፤ ባሕርየ (እሳተ) መለኮቱም አልለወጣትምና (አላቃጠላትምና) ሐመልማላዊቱ ዕፅ እመቤታችንን ትመስላለች፡፡ ዳግመኛም እርሱን ከወለደችው በኋላ ማኀተመ ድንግልናዋ አልተለወጠምና ሐመልማላዊቱ ዕፅ እመቤታችንን ትመስላለች፡፡ እርሱም ምንም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷም ነፍስ ነስቶ ፍጹም ሰው ቢኾንም ባሕርየ መለኮቱ አልተለወጠምና እሳቱን ይመስላል፡፡ ሰውም ቢኾን ባሕርየ መለኮቱ አልተለወጠምና ሰው ኾኖ ያዳነን የባሕርይ አምላክ ነው፡፡
ሰው ኾኖ ካዳነን ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን፡፡
⭕️ ናዐብየኪ ኩልነ ኦ እግዝእትነ ወላዲተ አምላክ እስመ ሣህልኪ ይኩን ላዕለ ኩልነ።
ትምክሕተ ኩልነ ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክ ዘበእንቲአሃ ተሥዕረ ዘቀዳሚ መርገም እንተ ኃደረት ዲበ ዘመድነ፡ በዕልወት ዘገበረት ብእሲት በልዐት እምዕፅ፡ ወበእንተ ሔዋን ተዐፅወ ኆኅተ ገነት፡ ወበእንተ ማርያም ድንግል ተርኅወ ለነ ዳግመ፡ ከፈለነ ንብላዕ እምዕፀ ሕይወት፡ ዘውእቱ ሥጋሁ ለክርስቶስ ወደሙ ክቡር፡ በእንተ ፍቅረ ዚአነ መጸ ወአድኃነአነ፡ አይ ልቡና፡ ወአይ ነቢብ፡ ወአይ ሰሚዕ፡ ዘይክል አእምሮ ዝንቱ ምሥጢር መንክታተ ዘይትነበብ ላዕሌሃ። እግዚአብሔር መፍቀሬ ሰብእ ፩ዱ ውእቱ ባሕቲቱ ቃለ አብ ዘሀሎ እምቅድመ ዓለም በመለኮቱ፡ እንበለ ሙስና እም፩ዱ አብ መጽአ ወተሰብአ ወልድ ዋሕድ እምቅድስት እሙ፡ እምድኅረ ወለደቶ ኢማሰነ ድንግልናሃ፡ ወበእንተዝ ግህደ ኮነት ከመ ወላዲተ አምላክ ይእቲ፡ ኦ ዕሙቅ ብዕለ ጥበቡ ለእግዘአብሔር ከርሥ ዘፈትሐ ላዕሌሃ ትለድ በፃዕር ወሕማም ወኃዘነ ልብ፡ ወኮነት ፈልፈለ ሕይወት ወወለደት ዘእንበለ ዘርአ ብእሲ ዘይስዕር መርገመ እምዘመድነ። ወበእንተዝ ንሰብሖ እንዘ ንብል ስብሕት ለከ ኦ መፍቀሬ ሰብእ ኄር ንፍሳቲነ። ሰአሊ ለነ ቅድስት።
፪. ይቅርታሽ (ምልጃሽ) ለኹላችን ይኾን ዘንድ አምላክን የወለድሽ እመቤታችን ሆይ! ኹላችን እናከብርሻለን፤ እናገንሻለን፡፡ ሔዋን ባደረገችው ዐመፅ በባሕርያችን ጸንቶ የነበረ መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ በእርሷ ምክንያት የጠፋልን አምላክን የወለደች ድንግል ማርያም የኹላችን መመኪያ ናት፡፡ “ሔዋን ምን አደረገች?” ትለኝ እንደኾነም ዕፀ በለስን በልታለች እልሃለሁ፡፡ “ወአዘዞሙ ለኪሩቤል ወሱራፌል ዘውስተ እደዊሆሙ ሰይፈ እሳት እንተ ትትመያየጥ ከመ ይዕቀቡ ፍኖተ ዕፀ ሕይወት - ወደ ሕይወት ዛፍ የሚወስደውንም መንገድ ለመጠበቅ ኪሩቤልንና የምትገለባበጥ የነበልባል ሰይፍን በዔደን ገነት ምሥራቅ አስቀመጠ” እንዲል /ዘፍ.፫፡፳፬/ በሔዋን ምክንያት የገነት ደጅ ተዘጋ፡፡ “ወአግኃሦ ለሱራፊ ዘየዐቅብ ፍና ዕፀ ሕይወት፤ ወአእተተ እምእዴሁ ኵናተ እሳት - ” እንዲልም በድንግል ማርያም ምክንያት ዳግመኛ ተከፈተልን፡፡ ቅዱስ ያዕቆብ ዘስሩግም፡- “አዳምን እንዲሞት ያደረገች ያቺ ቀን ተለወጠች፡፡ እርሱም ከሞት የሚድንባት ሌላ ቀን መጣች፡፡ እባቧ ሳትኾን መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ይናገር ዘንድ ተነሣ፡፡ ሔዋን ሳትኾን ድንግል ማርያምም ቃሉን ትቀበል ዘንድ ተዘጋጀች፡፡ በተንኰል የሚያስተው ሳይኾን ሕይወትን የሚያውጀው ቃል ወጣ፡፡ በሞት ዛፍ መካከል የሞት ዕዳዋን በጻፈችው ሔዋን ፈንታ ልጇ (ማርያም) የአባቷን ዕዳ ኹሉ ከፈለች፡፡ ሔዋንና እባቡ በቅድስት ድንግል ማርያምና በቅዱስ ገብርኤል ተተኩ፡፡ ያ ከመጀመርያው የተበላሸው ነገር አሁን ተስተካከለ፡፡ የሔዋን ጀሮና ቀልብ አታላዩ በሚናገርበት ጊዜ እንደምን እንዳዘነበለ አስተውሉ፤ ያ በገነት ሲመለከታቸው የነበረው መልአክ አሁን በድንግል ማርያም ጀሮ የድኅነትን ተስፋ ሲያሰርጽና የእባቡን ከፉና መርዛማ ቃል ሲያጠፋ ደግሞ አስተውሉ፡፡ ሔዋን ያፈረሰችው ሕንፃ ገብርኤል ገነባው፡፡ በዔደን ገነት ውስጥ ኹና ሔዋን ያፈረሰችውን መሠረት ዳግሚት ሔዋን ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህ ምድር ኹና ገነባችው፡፡ ከኹለት መልእክተኞች መልእክት የተቀበሉ ኹለት ደናግላን ኹለት ትውልድን ቀጠሉ፡፡ አንዱም የአንዱ ተቃራኒ ኾነ፡፡ በእባብ ምክንያት ሰይጣን ምሥጢርን ለሔዋን ላከ፡፡ በሌላ ቅዱስ መልአክ አማካኝነት ደግሞ ጌታ የምሥራቹን ወደ ቅድስት ድንግል ማርያም ላከ፡፡ እባብ ለሔዋን የሐሰትን ቃል ለሔዋን ስትናገር ቅዱስ ገብርኤል ግን የእውነትን ቃል ለቅድስት ድንግል ማርያም ተናገረ፡፡ እውነትን በሚናገር አንደበቱ የቀደመውን የእባብ ቃል አደሰው፡፡ እውነትን ተናገረና ሐሰቱን አስወገደው፡፡ አስቀድሞ ሐሰትን ከራሱ አንቅቶ ሰይጣን ሔዋንን በዔደን ገነት አታለላት፡፡ ይህንንም ታላቅ ስሕተት በጀሮዋ አልፎ እንዲሰማት ፈቀደች፡፡ አሁን ግን በመጀመርያዋ ድንግል ፈንታ ሌላ ድንግል ተመረጠች፡፡ በዚህች ድንግል ጀሮም ከአርያም የተላከ የእውነት ቃል ገባ፡፡ ሞት በገባበት በዚያ በር (ጀሮ) ሕይወት ገባ፡፡ ክፉው (ዲያብሎስ) ያጠበቀው ጽኑ የሞት ማሰርያም ተፈታ፡፡ ኀጢአትና ሞት ሠልጥነውበት በነበረ ቦታ ጸጋ ከመጠን ይልቅ በዝቶ ታየ፡፡ … እባብ የስሕተትን ዜማ ለሔዋን ዘመረላት፤ ሐሰትንም ረጨባት፡፡ በተፈጥሮዋ ገና ድንግል በምትኾን በሔዋን ላይ ክፉ ምክርና ስሕተት አፈሰሰባት፡፡ በመርዝ የተለወሰና ደምን የተጠማ ክፉ ምክር በአዳም ቤት ውስጥ አስገባ፡፡ ኃይለ ልዑል የላከው መልአክ ግን እነዚህን የክፋት ሰይፎች ለመቆራረጥ ክንፉን እያማታ እየበረረ መጣ፡፡ ለሰው ኹሉ የሚኾን የድኅነት ሰነድ ይዞ መጥቶም ለድንግሊቱ (ለማርያም) አበሠራት፡፡ ሰገደላት፡፡ ሕይወትን በውስጧ አሰረጸ፡፡ ሰላም ዐወጀ፡፡ በፍቅር ቀረባት፡፡ የቀድሞውን የሞት ዳባ በጣጠሰው፡፡ እባብ የገነባውን የማታለል ግንብ ዳግም ላይገነባ በወልደ እግዚአብሔር እንደሚናድ ነገራት፡፡ በእባብ የታጠረው የሞት ቅጽር በወልድ መውረድ እንደሚሰባበር ቀጠሮው እንደደረሰ ነግሮ የምሥራች አላት” በማለት ከማር የጣፈጠ ትምህርቱን እያነጻጸረ አስተምሯል፡፡
ከዕፀ ሕይወትም እንበላ ዘንድ አደለን፡፡ ይኸውም እኛን ስለ መውደድ ሰው ኾኖ ያዳነን የክርስቶስ ቅዱስ ሥጋውና ክቡር ደሙ ነው፡፡
2 171
⭕ እዌድሰኪ ኦ ድንግል ምልእተ ውዳሴ መጠነ ይክል አፉየ አስተበፅዕ እበየኪ ማርያም፡፡
ክብር ምስጋናን የተመላሽ ድንግል ሆይ አንደበቴ የሚችለውን ያህል አንቺን እያመሰገንሁ ገናንተሽን አደንቃለሁ፡፡
⭕ ልሳነ ኪሩቤል ኢይክል አብጽሖ ውዳሴኪ ወአፈ ሱራፌል ኢይፌጽም ነጊረ ዕበየኪ ማርያም፡፡
እመቤታችን ሆይ የኪሩቤል አንደበት ምስጋናሽን ማድረስ አይቻለውም
⭕ ትትሌዓሊ እምአድባር ወእምአርስተ አውግር ነዋኀት ናዓብየኪ ኦ ቡርክት ማኅፈደ መለኮት ማርያም፡፡
ከታላላቆቹ ተራሮች ማለት ከደጋጎቹ አባቶችሽ ትበልጫለሽ የመለኮት ማደሪያው ክብርት እመቤታችን ሆይ እናከብርሻለን፡፡
⭕ ጽበተ ከርስኪ ሰፍሐ እምርኅበ ሰማይ ወጸዳልኪ አብርሀ እምብርሃነ ፀሐይ አስከሬነ ወርቅ ጽሩይ መዝገበ ባሕርይ ቡርክት አንቲ ማርያም፡፡
የማኅፀንሽ ጽበት ከሰማይ ስፋት ይልቅ የበዛ ነው ብሩህነትሽም ከፀሐይ ብርሃን ይልቅ የበለጠ ነው፡፡
ክብርት እመቤታችን የጠራ የወርቅ ሳጥን የዕንቊ ማኖሪያ አንቺ ነሽ፡፡
⭕ ውድስት አንቲ በአፈ ነቢያት ወስብሕት በሐዋርያት አክሊለ በረከቱ ለያዕቆብ ወትምክህተ ቤቱ ለእስራኤል፡፡
በነቢያት በሐዋርያት አንደበት የተመሰገንሽ የያዕቆብ የበረከቱ ዘውድ የእስራኤል ወገን መመኪያ አንቺ ነሽ፡፡
⭕ ሠርጸ መንግሥት ዘእምሥርወ ዕሴይ ወጽጌ ንጽሕት ዘእምጕንደ ዳዊት ወብኪ ይትሜዓዙ ኵሎሙ ቅዱሳን፡፡
ከዕሴይ ሥር የተገኘሽ የመንግሥት ቡቃያ ከዳዊት ግንድ የተገኘሽ ቅዱሳን የሚቀቡሽ (የሚከብሩብሽ) ንጽሕት አበባ አንቺ ነሽ፡፡
⭕ ንሰግድ ለኪ ኦ ንግሥት ወናንቀዓዱ ኀበ ወልድኪ አኃዜ ዓለም ስፍሒ እዴኪ ወባርኪ ላዕሌለነ ለለ አሐዱ አሐዱ ለአግብርትኪ፡፡
ንግሥት ሆይ ላንቺ እንሰግዳለን ዓለሙን ጨብጦ ወደያዘ ልጅሽም እንለምናለንና እያንዳንዳችን እኛ አገልጋዮችሽን እጅሽን ዘርግተሸ ባርኪን፡፡
ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በመጽሐፈ ሰዐታት
ጽንዕት በድንግልና ሥርጒት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኝልን። አእምሮውን፣ ለብዎውን፣ ጥበቡን በልቡናችን ሳዪብን፤ አሳድሪብን ።
2 171
⭕ እዌድሰኪ ኦ ድንግል ምልእተ ውዳሴ መጠነ ይክል አፉየ አስተበፅዕ እበየኪ ማርያም፡፡
ክብር ምስጋናን የተመላሽ ድንግል ሆይ አንደበቴ የሚችለውን ያህል አንቺን እያመሰገንሁ ገናንተሽን አደንቃለሁ፡፡
⭕ ልሳነ ኪሩቤል ኢይክል አብጽሖ ውዳሴኪ ወአፈ ሱራፌል ኢይፌጽም ነጊረ ዕበየኪ ማርያም፡፡
እመቤታችን ሆይ የኪሩቤል አንደበት ምስጋናሽን ማድረስ አይቻለውም
⭕ ትትሌዓሊ እምአድባር ወእምአርስተ አውግር ነዋኀት ናዓብየኪ ኦ ቡርክት ማኅፈደ መለኮት ማርያም፡፡
ከታላላቆቹ ተራሮች ማለት ከደጋጎቹ አባቶችሽ ትበልጫለሽ የመለኮት ማደሪያው ክብርት እመቤታችን ሆይ እናከብርሻለን፡፡
⭕ ጽበተ ከርስኪ ሰፍሐ እምርኅበ ሰማይ ወጸዳልኪ አብርሀ እምብርሃነ ፀሐይ አስከሬነ ወርቅ ጽሩይ መዝገበ ባሕርይ ቡርክት አንቲ ማርያም፡፡
የማኅፀንሽ ጽበት ከሰማይ ስፋት ይልቅ የበዛ ነው ብሩህነትሽም ከፀሐይ ብርሃን ይልቅ የበለጠ ነው፡፡
ክብርት እመቤታችን የጠራ የወርቅ ሳጥን የዕንቊ ማኖሪያ አንቺ ነሽ፡፡
⭕ ውድስት አንቲ በአፈ ነቢያት ወስብሕት በሐዋርያት አክሊለ በረከቱ ለያዕቆብ ወትምክህተ ቤቱ ለእስራኤል፡፡
በነቢያት በሐዋርያት አንደበት የተመሰገንሽ የያዕቆብ የበረከቱ ዘውድ የእስራኤል ወገን መመኪያ አንቺ ነሽ፡፡
⭕ ሠርጸ መንግሥት ዘእምሥርወ ዕሴይ ወጽጌ ንጽሕት ዘእምጕንደ ዳዊት ወብኪ ይትሜዓዙ ኵሎሙ ቅዱሳን፡፡
ከዕሴይ ሥር የተገኘሽ የመንግሥት ቡቃያ ከዳዊት ግንድ የተገኘሽ ቅዱሳን የሚቀቡሽ (የሚከብሩብሽ) ንጽሕት አበባ አንቺ ነሽ፡፡
⭕ ንሰግድ ለኪ ኦ ንግሥት ወናንቀዓዱ ኀበ ወልድኪ አኃዜ ዓለም ስፍሒ እዴኪ ወባርኪ ላዕሌለነ ለለ አሐዱ አሐዱ ለአግብርትኪ፡፡
ንግሥት ሆይ ላንቺ እንሰግዳለን ዓለሙን ጨብጦ ወደያዘ ልጅሽም እንለምናለንና እያንዳንዳችን እኛ አገልጋዮችሽን እጅሽን ዘርግተሸ ባርኪን፡፡
ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በመጽሐፈ ሰዐታት
ጽንዕት በድንግልና ሥርጒት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኝልን። አእምሮውን፣ ለብዎውን፣ ጥበቡን በልቡናችን ሳዪብን፤ አሳድሪብን ።
2 171
✍️እዌድሰኪ ኦ ድንግል ምልእተ ውዳሴ መጠነ ይክል አፉየ አስተበፅዕ እበየኪ ማርያም፡፡
ክብር ምስጋናን የተመላሽ ድንግል ሆይ አንደበቴ የሚችለውን ያህል አንቺን እያመሰገንሁ ገናንተሽን አደንቃለሁ፡፡
✍️ ልሳነ ኪሩቤል ኢይክል አብጽሖ ውዳሴኪ ወአፈ ሱራፌል ኢይፌጽም ነጊረ ዕበየኪ ማርያም፡፡
እመቤታችን ሆይ የኪሩቤል አንደበት ምስጋናሽን ማድረስ አይቻለውም
✍️ ትትሌዓሊ እምአድባር ወእምአርስተ አውግር ነዋኀት ናዓብየኪ ኦ ቡርክት ማኅፈደ መለኮት ማርያም፡፡
ከታላላቆቹ ተራሮች ማለት ከደጋጎቹ አባቶችሽ ትበልጫለሽ የመለኮት ማደሪያው ክብርት እመቤታችን ሆይ እናከብርሻለን፡፡
✍️ጽበተ ከርስኪ ሰፍሐ እምርኅበ ሰማይ ወጸዳልኪ አብርሀ እምብርሃነ ፀሐይ አስከሬነ ወርቅ ጽሩይ መዝገበ ባሕርይ ቡርክት አንቲ ማርያም፡፡
የማኅፀንሽ ጽበት ከሰማይ ስፋት ይልቅ የበዛ ነው ብሩህነትሽም ከፀሐይ ብርሃን ይልቅ የበለጠ ነው፡፡
ክብርት እመቤታችን የጠራ የወርቅ ሳጥን የዕንቊ ማኖሪያ አንቺ ነሽ፡፡
✍️ ውድስት አንቲ በአፈ ነቢያት ወስብሕት በሐዋርያት አክሊለ በረከቱ ለያዕቆብ ወትምክህተ ቤቱ ለእስራኤል፡፡
በነቢያት በሐዋርያት አንደበት የተመሰገንሽ የያዕቆብ የበረከቱ ዘውድ የእስራኤል ወገን መመኪያ አንቺ ነሽ፡፡
✍️ ሠርጸ መንግሥት ዘእምሥርወ ዕሴይ ወጽጌ ንጽሕት ዘእምጕንደ ዳዊት ወብኪ ይትሜዓዙ ኵሎሙ ቅዱሳን፡፡
ከዕሴይ ሥር የተገኘሽ የመንግሥት ቡቃያ ከዳዊት ግንድ የተገኘሽ ቅዱሳን የሚቀቡሽ (የሚከብሩብሽ) ንጽሕት አበባ አንቺ ነሽ፡፡
✍️ ንሰግድ ለኪ ኦ ንግሥት ወናንቀዓዱ ኀበ ወልድኪ አኃዜ ዓለም ስፍሒ እዴኪ ወባርኪ ላዕሌለነ ለለ አሐዱ አሐዱ ለአግብርትኪ፡፡
ንግሥት ሆይ ላንቺ እንሰግዳለን ዓለሙን ጨብጦ ወደያዘ ልጅሽም እንለምናለንና እያንዳንዳችን እኛ አገልጋዮችሽን እጅሽን ዘርግተሸ ባርኪን፡፡
ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በመጽሐፈ ሰዐታት
ጽንዕት በድንግልና ሥርጒት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኝልን። አእምሮውን፣ ለብዎውን፣ ጥበቡን በልቡናችን ሳዪብን፤ አሳድሪብን ።
2 171
ሙሴ በታቦር እመ ትሬኢ ደመና፤
ኢይምሰልከ እስኩ ዘይወርድ መና፤
ርደተ መና ጥዑም አምጣነ ተርፈ በሲና😎
ሙሴ ሆይ ..
በከለለህ ጊዜ በታቦር ደመና
ፍጹም እንዳይመስልህ የሚወርድ መና
ጣፋጩ መናኮ ቀረ ደብረ ሲና
(ዘአበው)
* መና ይወርድልናል ብለው ተስፋ ለሚያደርጉ....
ደብረ ታቦር🙏🙏🙏
