en
Feedback
ነገረ ማርያም( አንድምታ)

ነገረ ማርያም( አንድምታ)

Open in Telegram

በዚህ ቻናል ሃይማኖታዊ ምስጢሮችን ያገኙበታል። " ኪሩቤል አፍራሰ ፌማ፥ ወሱራፌል ዘራማ፥ ክሉላነ ሞገስ ወግርማ ፥ ይሴብሑኪ ማርያም፥ በቃለ ጥዑም ዜማ።"/ ማርያም ሆይ የመንፈስ ቅዱስ አፍራስ ኪሩቤልና በግርማና በክብር የተጋረዱ በራማ የሚኖሩ ሱራፌል ማርያም ሆይ ጥዑም በሚሆን የዜማ ቃል ያመሰግኑሻል።

Show more
2 163
Subscribers
+124 hours
+57 days
+4430 days

Data loading in progress...

Attracting Subscribers
September '26
September '26
+16
in 0 channels
August '26
+106
in 0 channels
Get PRO
July '26
+86
in 0 channels
Get PRO
June '26
+79
in 0 channels
Get PRO
May '26
+91
in 2 channels
Get PRO
April '26
+72
in 0 channels
Get PRO
March '26
+49
in 0 channels
Get PRO
February '26
+43
in 0 channels
Get PRO
January '26
+49
in 0 channels
Get PRO
December '25
+83
in 0 channels
Get PRO
November '25
+64
in 0 channels
Get PRO
October '25
+77
in 0 channels
Get PRO
September '25
+50
in 0 channels
Get PRO
August '25
+102
in 0 channels
Get PRO
July '25
+58
in 0 channels
Get PRO
June '25
+64
in 0 channels
Get PRO
May '25
+64
in 0 channels
Get PRO
April '25
+81
in 0 channels
Get PRO
March '25
+98
in 0 channels
Get PRO
February '25
+93
in 0 channels
Get PRO
January '25
+121
in 1 channels
Get PRO
December '24
+181
in 0 channels
Get PRO
November '24
+152
in 0 channels
Get PRO
October '24
+82
in 0 channels
Get PRO
September '24
+32
in 0 channels
Get PRO
August '24
+102
in 0 channels
Get PRO
July '24
+36
in 0 channels
Get PRO
June '24
+30
in 0 channels
Get PRO
May '24
+23
in 0 channels
Get PRO
April '24
+43
in 0 channels
Get PRO
March '24
+61
in 0 channels
Get PRO
February '24
+49
in 0 channels
Get PRO
January '24
+46
in 0 channels
Get PRO
December '23
+59
in 0 channels
Get PRO
November '23
+60
in 0 channels
Get PRO
October '23
+44
in 0 channels
Get PRO
September '23
+18
in 0 channels
Get PRO
August '23
+35
in 0 channels
Get PRO
July '23
+51
in 0 channels
Get PRO
June '23
+60
in 0 channels
Get PRO
May '23
+39
in 0 channels
Get PRO
April '23
+55
in 0 channels
Get PRO
March '23
+63
in 0 channels
Get PRO
February '23
+87
in 0 channels
Get PRO
January '23
+35
in 0 channels
Get PRO
December '22
+74
in 0 channels
Get PRO
November '22
+75
in 0 channels
Get PRO
October '22
+58
in 0 channels
Get PRO
September '22
+4
in 0 channels
Get PRO
August '22
+5
in 0 channels
Get PRO
July '22
+11
in 0 channels
Get PRO
June '22
+6
in 0 channels
Get PRO
May '22
+20
in 0 channels
Get PRO
April '22
+8
in 0 channels
Get PRO
March '22
+8
in 0 channels
Get PRO
February '22
+16
in 0 channels
Get PRO
January '22
+18
in 0 channels
Get PRO
December '21
+20
in 0 channels
Get PRO
November '21
+6
in 0 channels
Get PRO
October '21
+219
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
08 September+2
07 September+2
06 September0
05 September+1
04 September+3
03 September+2
02 September+3
01 September+3
Channel Posts
ጦቢትም ፦, ወይቤሎ አቡሁ ሑር ምስለ ዝንቱ ብእሲ / ከዚህ ሰው ጋር ሂዱ ፣እግዚአብሔር ጎዳናችሁን ያቅናላችሁ ፣መልአኩ አብሯችሁ ይሂድ በማለት መርቆ ሰደዳቸው። መልአኩ በሰው አምሳል ስለሆነ ጦብያም ጦቢትም አለወቁትምና። አዛርያ(ቅዱስ ራፋኤል)  ና ጦብያም ተነስተው ጉዞ ጀመሩ / ወተለዎሙ  ከልበ ወልዶሙ/ የልጃቸው ውሻ ተከተላቸው። ወበጽሑ  ጤግሮስ/ ጤግሮስ ወንዝ ደረሱ ፣ ጦብያም ሊታጠብ ወደ ወንዙ ወረደ ፣ ወሠረረ ላዕሌሁ ዓሣ/ ዓሣው ተወርውሮ  መጣበት ፣ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ወይም በሰወኛ ስሙ አዛርያ  ጦብያን ይዘህ አውጠው አለው። ጦብያም ይዞ አወጣው፣ወምትር፣ እረደው፣ አወራርደው ልቡን ፣ጉበቱን፣ሐሞቱን ያዘው አለው። ጦብያም መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤልን/ በሰወኛ ስሙ አዛርያንን/  አንተ ወንድሜ አዛርያ ልቡ፣ጉበቱ፣ሐሞቱ ምን ይሆናል?? በማለት ጠየቀው  መልአኩም ልቡ፣ጉበቱ፣ሐሞቱ  ጋኔን ያደረበት ሰው ቢኖር ያጤሱበት እንደሆነ ለቅቆት ይሄዳል። ሐሞቱ ግን በዓይኑ ብልዝ ፣ብግር የወጣበት ሰው ቢኖር፣የኳሉት እንደሆነ ይድናል በማለት በሣራ ላይ ያለውን አስማንድዮስ የሚባለውን ጋኔን እና ያባቱን ዓይን እንደሚያድናቸው ገለጠለት። ወሶበ ቀርቡ ኀበ ራጊስ/ ወደ ራጊስ በቀረቡ ጊዜ  አንተ ወንድሜ ዛሬ ከራጉኤል ዘንድ እናድራለን፣ለአንተም ዘመድህ ነው፣ ወቦ ወለት አሐቲ ወስማ ሣራ / አንዲት ልጅ ስሟ ሣራ የሚባል አለችው ሚስት ትሆንህ ዘንድ የእሷን ነገር ልንገርህ  ላንተ ትገባሃለችና አለው መልአኩ ሩፋኤል። ጦብያም አንተ ወንድሜ አዛርያ  የእሷን ነገር ሰባት ሰዎች እንዳገቧትና ሁሉም እንደ ሞቱ ሰምቻለሁ አለው። እኔም ላባቴ አንድ ነኝ እሞታለሁ አለው። መልአኩም መልሶ / ወበእንተ ጋኔንሰ ኢያኅዝንከ / ስለ ጋኔኑስ አትዘን ፤ በዚቺ ሌሊት ላንተ ሚስት ሁና ትሰጥሃለችና አለው። ወሶበ ቦዕከ ውስተ ጽርሕ / ወደ ጫጉላ ቤት በገባህ ጊዜ  ሕራረ ዕጣን ጨምረህ ልቡን፣ ጉበቱን አጢሰው ፣በሸተተው ጊዜ ጋኔኑ ይሸሻል አለው። መልአኩ ሩፋኤልና ጦብያም ወደ ራጉኤል ቤት ገቡ ፣ ሣራም ደስ አሰኝታ ተቀበለቻቸው። አባቷ ራጉኤልም ከማን ዘርናችሁ ብሎ ጠየቃቸው፣ እነሱም ወደ ነንዌ ተማርከው ከሄዱት  ከንፍታሌም ወገን ነን አሉት ራጉኤልም ተነስቶ ሳማቸው፣ከዚህ በኋላ መልአኩና ጦብያም በጎዳና የተነጋገሩትን ነገር አወሩ። እነሱም ደስብሏቸው ሀሳባቸውን ተቀብለው ሣራን ትወስዳታለህ አለው። ሣራም ለጦብያ ሚስት ትሆነው ዘንድ ቃል ገባችለት። ጦብያም ወደ ጫጉላ ሲገቡ መልአኩ ያዘዘውን አደረገ።  በዚያን ጊዜ በጫጉላው ላይ ሆኖ የዓሣውን ልቡንና ጉበቱን ከሕራሪ ዕጣን ጋር ጨምሮ ቢያጤሰው አስማንድዮስ የሚባለው ሰይጣን ከሣራ ላይ ወጣላት። ወዐሠሮ ዝኩ መልአክ/ ጋኔኑ ሲሸሽ መልአኩ አሥሮ ከመሬት ቀበረው/ የሣራ ቤተሰቦችም በሠላም በማደራቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑ።አሥራ አራት ቀን በዓል ካደረጉ በኋላ   መልአኩ ሩፋኤልም ከገባኤል ዘንድ ብሩን አመጣ። ራጉኤልም ልጁ ሣራንና ጦብያን ወደ ጦቢት ሰደዳቸው። ቅዱስ ሩፋኤልም ጦብያን ከሣራ ቀድመን ሄደን ቤቱን እናዘጋጅ  ሐሞቱን ያዝ አለው። ወይቤሎ ሩፋኤል አነ አአምር ከመ ይትከሠት አዕይንቲሁ/ ያባትህ ዓይኖች እንዲገለጡ አውቃለሁ  አንተ ግን ዓይኑን ኳለው ፣በተኳለ ጊዜ ዓይኑን ያሸዋል  ፣ብልዙ ይቀረፋል፣ይገፈፋል አለው። ጦብያም እንደታዘዘው አደረገ።የጦቢትም ዓይን በተኳለ ጊዜ በፍጥነት ዳነ።ከዚህ በኋላ የመልአኩን ደመወዝ እኩሌታውን ይሰጠው ብለው ወሠኑ። ሩፋኤልም ሁለቱንም በመጥራት እግዚአብሔርን አመስግኑት ፣ለሱ ተገዙ ፣ወንግሩ ግብሮ ፣/ ሥራውን በክብር ተናገሩ ፣ወርእዩ፣ሥራውን አክብራችሁ  ግለጡ፣ ወናሁ ኢየኀብእ እምኔክሙ ኩሎ ነገረ/ ነገሩን ሁሉ  ከእናንተ  አልሰውረውም  አላቸው።   ወእቤለክሙ ከመ ምስጢረ መንግሥት ሠናይ ለኃቢዕ/ የቤተ መንግሥትን ምስጢር መሠወር ደግ እንደሆነ ፣የእግዚአብሔርን ሥራ ግን አክብሮ መግለጽ እንዲገባ እነግራችኋለሁ ፣ ወይእዜኒ አመ ጸለይክሙ አንተ ወሣራ መርዓትከ  አነ አባእኩ ተዝካረ ስዕለትክሙ/ አሁንም ሣራና አንተ በለመናችሁ  ጊዜ የልመናችሁ መታሰቢያ ወደ እግዚአብሔር አቀረብሁ፣ ወአንተኒ  አመ ትቀብር አብድንተ / አንተም ሬሳ ትቀብር በነበረ ጊዜ  በረድኤት አብሬህ ነበርሁ፣ ወደእግዚአብሔር ፈነወኒ ከመ እፈውስከ  / አድንኅ ዘንድ እግዚአብሔር ላከኝ፣ ወለሣራኒ ከመ እናዝዝ ኃዘና / የሣራንም ኃዘኗን አርቅላት ዘንድ ሰደደኝ በማለት አስረዳቸው ይኸን ካለ በኋላ፦ አነ ውእቱ ሩፋኤል መልአክ አሐዱ እምነ ፯ቱ ቅዱሳን መላእክት/ ከሰባቱ ቅዱሳን ሊቃነ  መላእክት አንዱ ሩፋኤል እኔ ነኝ። ወሰሚዖሙ ዘንተ ክልኤሆሙ  ወድቁ በገጾሙ/ሁለቱም ይኸን ንግግር በሰሙ ጊዜ በግንባራቸው ፍግም ብለው ወደቁ፣ ወይቤሎሙ ኢትፍርሁ፣ አትፍሩ ፈጣሪያችሁ እግዚአብሔርን አመስግኑ አላቸው፣ እስመ አኮ ሊተ አኮቴት፣ለኔ ምስጋና  የሚገባኝ አይደለምና አላ ፈቃዱ ለአምላክክሙ አምጽአኒ/ የፈጣሪያችሁ ፈቃዱ አመጣኝ እንጅ፣ ወአንሰ አስተርአይኩክሙ፣ እኔ ታየኋችሁ  እናንተም መልኬን አያችሁት፣ከእናንተ ጋራ ይረባኛል፣ይጠቅመኛል ብየ አልበላሁም፣አልጠጣሁም፣ ወይእዜኒ  እመኑ በእግዚአብሔር ፣በእግዚአብሔር እመኑ፣እኔ ወደላከኝ እሄዳለሁ፣ ወመጻእኩ እጽሕፍ እሎንተ ኵሎ ፣ይህን ሁሉ እጽሕፍ ዘንድ መጣሁ እንጅ፣ይህን ነግሯቸው ተነስቶ ሄደ፣ ወሶቤሃ ተንሥአ ወሖረ/ ያንጊዜ ተነሥቶ ሄደ፣ ወኢርእይዎ እንከ/ ዳግመኛ አላዩትም። የእግዚአብሔር መልአክ ስለታያቸው ጦቢትም ደስ የሚያሰኝ ጸሎት ተናገረ ፦ ወይቤ ይትባረክ እግዚአብሔር ዘውእቱ ሕያው ለዓለም/ ለዘለዓለሙ ሕያው ሆኖ የሚኖር እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን እያለ አመሰገነ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር....

2
ጦቢት ተማርኮ በሄደ ጊዜ  ስልምናሶር በወገኖቹ ላይ ሹሞታል ፣ ያን ጊዜ ተሹሞ ሳለ  በራጊስ "ዘሜዶን" ከምትባል ሀገር ከገባኤል ዘንድ አሥር መክሊት ብር አደራ አስቀመጠ። # ስልምናሶር ሞቶ ልጁ ሠናክሬም ነገሠ። ሠናክሬምም ጦቢትን ከሹመቱ አወረደው፣ ጦቢትም ወደሚድያም መሄድ የማይቻለው ሆነ፥ የጦቢትም ግብሩ የሞተ መቅበር ነበር፣ ከዕለታት አንድ ቀን  በበዓለ ጰንጠቆስጤ ልጁን ጦብያን ጠርቶ ፦ ሑር አምጽእ ዘረከብከ እምአኃዊነ  ቢጸ ነዳያን/ ከወንድሞቻችን አንድ ሰው አምጣ እስኪመጣ ድረስ እጠብቅሃለሁ አለው። ጦብያም ቢሄድ አንድ ሰው ሙቶ ወድቆ አገኘ። ጦብያም ተመልሶ ለአባቱ ለጦቢት ነገረው። ጦቢትም ተነሥቶ ሄዶ ሬሣውን አንሥቶ ከቤት አግብቶ ፣እጁን ታጥቦ፣እህል ቀምሶ ፀሐይ ከገባች በኋላ ሄዶ ቀበረው። ወበይእቲ  ሌሊት ቤትኩ ስኩብየ ውስተ ዓረፍት/ በዚያች ሌሊት ከቅጥሩ ተኝቸ አደርኩ አለ።ጦቢትም ፊቱን ተገልጦ ተኝቶ ሳለ አዕዋፍ ትኩስ ፋንድያ ጣሉበት፣ያ ትኩስ የአዕዋፍ ኩስም ከጦቢት ዓይን ላይ ስላረፈ እንደ ብልዝ ያለ ወጠባት ፣ዓይኑም ጠፋ። ሚሲቱ ሐናም የሙያ ሥራ እየሠራች ትውል ነበር ፣ወፍጮ እየፈጨች እያመጣትች ባሏን ጦቢትን ትረደው ነበር። ከዕለታት አንድ ቀን ከምትሠራባቸው ከጌቶቿ ዘንድ አንድ ጠቦት ሰጥተዋት ወደ ጦቢት ይዛ መጣች።  እሷም በግ አመጣሁ እያለች ታወራ ጀመር፣ባሏ ጦቢትም  እንዲህ አላት / ወለ እመ ሰረቂዮ አብኢዮ ለባዕሉ/ ሰርቀሽ አምጥተሽው እንደሆነ  ለባለ ገንዘቡ ስጭው አላት። እሷም ሚስቱ ሐና በቁጭት ጦቢትን / አይቴ ውእቱ ምጽዋትከ ወጽድቅከ / በጎነትህ  ምጽዋትህ  ያዳነህ የት አለ?  በማለት ገሠጸችው። / ናሁ ተዓውቀ ኩሉ ዘላእሌከ/ እንሆ ክፋትህ ሁሉ ተገለጸብህ አለችው። ጦቢትም በዚህ ንግግሯ ምርር ብሎ በማልቀስ እንዲህ አለ፦ " ወአዝዝ ዘይትሜጦ መንፈስየ ከመ እሠዓር/" ከዚህ ዓለም በሞት እለይ ዘንድ ነፍሴን ከሥጋዬ  የሚለይ መልአክ እዘዝ በማለት ጸለየ። እስመ ይኄይስኒ ሞት እምሐዪው / ክፉ ነገር እየሰሙ ከመኖር ሞት ይሻለኛል አለ። ይቺ ጸሎት ነች እንግዲህ ቅድመ እግዚአብሔር የደረሰችው። ## በዚችም ቀን ጦቢትን ሚስቱ በተናገረችው እለት  የራጉኤል ልጅ ሣራ ተግዳሮት ገጠማት / ወበይእቲ ዕለት ረከባ ለወለተ ራጉኤል ሣራ/ በዚህ ቀን የራጉኤልን ልጅ ሣራን ተግዳሮት  አገኛት። ወተአየራሃ አዕማተ አቡሃ / ያባቷ ባሮች ተገዳደሯት፣ ወይቤላሃ ኢተአምሪኑ እንዘ ይትሐነቁ አምታትኪ/ ባሎችሽ እየታነቁ  እንደሞቱ  አታውቂምን?  እንሆ ሰባት ሰዎች አግብተውሽ ነበረ፣ ወአሐዱ እምኔሆሙ ኢተለወኪ/ ከእነዚህ ሁሉ አንዱ አልተከተለሽም፣ እኛስ በነዚያ ምክንያት ምንያክል ያዘንን ይመስልሻል፣ ሑሪ ምስሌሆሙ/ አንቺም እንደ ባሎችሽ በሞት ሂጂ፣ ወኢንርአይ ወልደ ወወለተ እምኔኪ/ ካንቺ ወንድ ልጅ፣ሴት ልጅ ተወልዶ ማየት ይቅርብን አሏት፣ ወሶበ  ሰምዓት ዘንተ ተከዘት ጥቀ/ ይህንን ነገር በሰማች ጊዜ ፈጽማ አዘነች። ወይእዜኒ እግዚኦ አዕይንትየ  ለከ መጠውኩከ / አቤቱ ዓይኔ ልቡናዬ ደነገጠ ፣ልቡናዬን ወደአንት መለስሁ፣ ወእብለከ ሠዐረኒ እምነ ምድር ከመ ኢይስማዕ ትዕይርተ/ ተግዳሮትን እንዳልሰማ  ከዚህ ዓለም በሞት ለየኝ እልሃለሁ በማለት  ምርር ብላ አለቀሰች። እንግዲህ ሁለቱ ያለቀሱበት እና ያጋጠማቸው ችግር አሳዛኝ በመሆኑ ጸሎታቸው ቅድመ እግዚአብሔር ደረሰላቸው። ❤የሁለቱም ጸሎት ተሰማ ቅድመ እግእግዚአብሔርደረሰ የተባለ አዚህ ላይ ነው። የእኛንም ጸሎት መሐሪው እግዚአብሔር ይስማን!!!!   እግዚአብሔር  ሁለቱንም ያድናቸው ዘንድ መልአኩ ሩፋኤልን ላከላቸው። ወለጦቢትኒ ከመ ያሰስል ጢሰ ዓይኑ/ የጦቢትንም በዓይኑ ላይ ያለውን ብልዙን፣ብግሩን  ያጠፋለት ዘንድ። ወለሣራኒ ወለተ ራጉኤል ከመ የሀባ ለጦብያ / የራጉኤልን ልጅ ሣራንም ለጦቢት ልጅ ለጦብያ ይሰጣት ዘን  መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተላከ። ## ይኸስ እንደምንድ ነው ቢሉ? ነገሩን ከዚህ ያመጠዋል፦ ወበይእቲ ዕለት ተዘከረ ጦቢት በእንተ ብሩር ዘአማኅፀነ  በኀበ ገባኤል/ በዚያች ዕለት ከገባኤል ዘንድ ያኖረውን የብሩን ነገር አሰበ። ይኸን ብር ስልምናሶር በሾመው ጊዜ ያስቀመጠው ነበር። ጦቢትም ልጀን ጦብያን ጠርቼ  ሳልሞት የብሩን ነገር ነገር ለምን አልነግረውም አለ። እንዳሰበም  አልቀረ ነገረው። ጦቢቱም ለልጁ ለጦብያን ፦ ልጀ  በሞትሁ  ጊዜ  አክብረህ ቅበረኝ ፣እናትህንም  አክብራት ፣በሞተች ጊዜ ከኔ ደርባት፣ / ዑቅ ርእስከ  ኦ ወልድየ እምኩሉ  ዝሙት/  ልጅ ከዝሙት ራስህን ጠብቅ!! ወቅድም ለከ ነሢአ ብእሲት  እምዘርዐ አበዊከ / አስቀድመህ  ካባቶችህ ወገን ሚስት  አግባ ፣ከባዕድ ወገን አታግባ ፣እኛ የደጎች ሰዎች ወገኖች ነንና በማለት ነገረው። ወይእዜኒ እነግረከ በእንተ መካልየ  ብሩር ዐሠርቱ ዘአዕቀብኩ  ኀበ ገባኤል/ከገባኤል ዘንድ  አደራ ያኖርሁት የብሩን ነገር አሁንም  እነግርሃለሁ በማለት ደጋግሞ ነገረው። ጦብያም መልሶ አባቴ ያዘዝከኝን ሁሉ አደርጋለሁ አለው። ወባሕቱ እፎ እክል ነሢኦቶ ለውእቱ ብሩር ዘኢየአምሮ፣/ ሀገሩን አላውቅ፣ሰውን አላውቅ፣ብሩን ለማምጣት እንደምን ይቻለኛል?? አለው። ጦቢትም ( ወወሀቦ መጽሐፈ ጦማር) ደብዳቤ ጽፎ ሰጠው። ደብዳቤውን ከሰጠው በኋላ አብሮህ የሚሄድ ሰው ፈልግ ፣ደመወዙን እሰጠዋለሁ አለው። ጦብያም ያባቱን ትዛዝ በመቀበል አብሮት የሚሄድ ሰው ሊፈልግ ሄደ። ወሖረ ይሕሥሥ ወረከቦ ለሩፋኤል / ሰው ሊፈልግ ሄዶ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤልን አገኘው።መልአኩም በአምሳለ ብእሲ ነበር የተገናኘው። መልአክ እንደሆነም አላወቀም። ጦብያም ቅዱስ ሩፋኤልን እንዲህ በማለት አናገረው፦ ወይቤሎ ትክልኑ ሐዊረ ምስሌየ ራጊስ  ዘሜዶን / የሜዶን አውራጃ ወደምትሆን  ወደ ራጊስ ከኔ ጋራ አብሮ ለመሄድ ትችላለህ? አለው።ወይቤሎ ትክልኑ ሐዊረ ምስሌየ ራጊስ  ዘሜዶን / የሜዶን አውራጃ ወደምትሆን  ወደ ራጊስ ከኔ ጋራ አብሮ ለመሄድ ትችላለህ? አለው።ወይቤሎ ውእቱ መልአክ አሐውር ምስሌከ / መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤልም  ይሁን ከአንተ ጋር አብሬህ እሄዳለሁ ፣ጎዳናውንም አውቀዋለሁ፣ከገባኤል ዘንድ ነበርኩ  አለው። ጦብያም ለአባቴ እነግረው ዘንድ ቆየኝ  አለው።  ጦብያም ላባቱ ለጦቢት አብሮት የሚሄድ ሰው ማግኘቱን ነገረው። ጦቢትም ከማን ወገን እንደሆነ አውቅ ዘንድ ነዓ በለው አለው። መልአኩም ወደ ጦቢት ወደመወዜ እንጅ ከሀገሬ፣ከወገኔ ምን አለህ አለው። ምክንያቱም መልአክ ዘርና ብሔር የለውምና ይኸን ተናገረው። ጦቢትም  አንተ ወንድሜ  ዘመድህን፣ወገንህን አውቅ ዘንድ እወድዋለሁ አለው። መልአኩም  ወይቤሎ   አንሰ አዛርያ ዘመደ አናንያ  ዓቢይ እኁከ/ የታላቅ ወንድምህ   የአናንያ ወገን አዛርያ እባላለሁ  አለው። ጦቢትም ሰላምታ ሰጠው። አንተስ ከደግ ሰው ወገን ነህ አለው ነገር ግን የምሰጥህን ደመወዝ ንገረኝ አለው፣ዕለት ዕለት አንድ  አንድ ድሪም እንስጥህ ፣ምግብህን ደግሞ ከልጀ ጋር ነው አለው።
103
3
[ጳጉሜን 3 በዓሉ የሚከበርለት የሊቀ መላእክት የቅዱስ ሩፋኤል ታሪክ] ✍️በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ ♥️ ቅዱስ ሩፋኤል ቊጥሩ ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት ሲኾን፤ ሩፋ ማለት ሐኪም፤ ኤል ማለት እግዚአብሔር ማለት ሲኾን ሩፋኤል ማለት “እግዚአብሔር ሐኪሜ ነው” ማለት ነው፤ ሄኖክም “በሰው ቁስል ላይ የተሾመ ከከበሩ መላእክት አንዱ ቅዱስ ሩፋኤል ነው” ይለዋል (መጽሐፈ ሄኖክ 6፥3):: ♥️ ይኽ መልአክ በራማ ሰማይ ያሉ ነገደ መናብርትን የሚመራቸው ነው፡፡ ነገደ መናብርት ያላቸው ቅዱስ ሩፋኤል የሚመራቸው በራማ ሰማይ የሚኖሩ ነገደ መላእክት ናቸው፡፡ ♥️ ቅዱስ ኤጲፋንዮስም በሥነ ፍጥረት መጽሐፉ ላይ “ወለዳግም ጾታ ዐሠርቱ ስሞሙ መናብርት ወሊቆሙ ሩፋኤል እሉ እሙንቱ እለ ይቀልል ሩጸቶሙ እምነፋስ ወእለ ይጸውሩ ወላትወ መብረቅ ወኲናተ እሳት ዘይነድድ ወአንበሮሙ በዳግሚት ሰማይ” ይላል በራማ ሰማይ የሚገኘውን ኹለተኛውን ዐሥሩን ነገድ መናብርት ሲላቸው አለቃቸው ቅዱስ ሩፋኤል ነው፤ እነዚኽም ረቂቅ የኾነ የመብረቅ ጋሻ የእሳት ጦር ይዘው ከነፋስ ይልቅ የፈጠኑ ሲኾኑ በራማ በኹለተኛው ክፍል ላይ አስፍሯቸዋል፡፡ ቅዱስ ሩፋኤል ከሚመራው ከዚኽ ነገድ 24ቱ ካህናተ ሰማይ ወጥተዋል፡፡ ♥️ አባ ጊዮርጊስም በሰዓታቱ ላይ ስለነዚኽ መላእክት ፡- “ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር ጽርሐ አርያም ማኅፈዱ መካነ ትጉሃን ዐጸዱ ካህናተ ሰማይ ቅዉማን በዐውዱ አክሊላቲሆሙ ያወርዱ ቅድመ መንበሩ እንዘ ይሰግዱ ይርዕዱ ወኢይዝብጦሙ ሶበ ይበርቅ ነዱ” (ጽርሐ አርያም አዳራሹ፤ የትጉሃን መኖሪያ ቦታው የሚኾን እግዚአብሔር ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ ተብሎ በአንድነት በሦስትነት ይመሰገናል፤ ካህናተ ሰማይ በዙሪያው ይቆማሉ፤ በዙፋኑ ፊት እየሰገዱ አክሊሎቻቸውን ያወርዳሉ፤ እሳትነቱ (ባሕርዩ) በሚበርቅ፣ ወገግ በሚል ጊዜ እንዳይመታቸው ይንቀጠቀጣሉ) ይላል ♥️ ሊቁ እንደጠቀሰው በዕለተ እሑድ ሥሉስ ቅዱስ ሰባቱን ሰማያት ፈጥረዋል፤ ከዚያም ልዑል እግዚአብሔር በዕለተ እሑድ ሰባቱን ሰማያት ከፈጠረ በኋላ ሊቁ በአክሲማሮስ እንደገለጸው ከቅዱሳን መላእክት መኻከል፡- “ወእምዝ ነሥአ እግዚአብሔር እምሰራዊተ ሩፋኤል ፳ወ፬ተ ሊቃናተ ወአቀሞሙ ዐውደ መንበሩ፤ ወሰመዮሙ ለእሙንቱ ካህናተ ሰማይ ወወሀቦሙ ማዕጠንታተ ዘእምወርቀ እሳት ወአክሊላተ ብርሃን ዘእምጳዝዮን ወአብትረ ዘከተማሆን መስቀል ወአልበሶሙ አልባሰ ክህነት” እንዲል ከሰራዊተ ሩፋኤል ፳፬ት ሊቃናትን መርጦ በመንበረ ስብሐት በመጋረጃዋ ውስጥ ዙሪያዋን ክንፍ ለክንፍ ገጥሞ አቁሟቸዋል (ሕዝ ፩፥፲፩-፲፪)። ♥️ ቊጥራቸውን ኻያ አራት ማድረጉ በኻያ አራቱ ጊዜያት ጸልየው ሌላውንም ራሳቸውንም ጠብቀው ዋጋቸውን ተቀብለው የሚኖሩ በመኾናቸው ሲኾን እነዚኽንም መላእክት “ካህናተ ሰማይ” ሲላቸው የእሳት የወርቅ ጽና ሲያሲዛቸው የብርሃን አክሊል ጳዝዮን የሚባል የብርሃን ዘውድ ደፍቶላቸዋል፤ የብርሃን ዘንግ ማኅተሙ መስቀል የኾነ ሲያሲዛቸው የብርሃን ካባ ላንቃ ሕብሩ መብረቅ የመሰለ አልብሷቸዋል ( ራእ ፬፥፬-፭፤፲-፲፩)። ♥️ እነዚኽ ከሰራዊተ ሩፋኤል የወጡ ሰማያውያን ካህናት በአንድ ላይ ባጠኑ ጊዜ ዛሬ በክረምት ጊዜ ጉም ተራራውን እንደሚሸፍነው ከማዕጠንታቸው የሚወጣው ጢስ መልኩ መብረቅ፣ ድምፁ ነጐድጓድ፣ መዐዛው መልካም የኾነና ጽርሐ አርያም፣ መንበረ መንግሥት የተባሉትን የብርሃን ሰማያት የሚሸፍንና የሚጋርድና ከጢሱ ጋር የቅዱሳን ጸሎት ዐብሮ ወደ እግዚአብሔር ፊት ይወጣል። ✍️ “ሌላም መልአክ መጣና የወርቅ ጥና ይዞ በመሠዊያው አጠገብ ቆመ፤ በዙፋኑም ፊት ባለው በወርቅ መሠዊያ ላይ ለቅዱሳን ኹሉ ጸሎት እንዲጨምረው ብዙ ዕጣን ተሰጠው የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሳን ጸሎት ጋር ከመልአኩ እጅ በእግዚአብሔር ፊት ወጣ” እንዳለ ዮሐንስ በራእዩ (ራእ ፰፥፫-፭)፡፡ ♥️ ቅዱስ ኤጲፋንዮስ በአክሲማሮስ ላይ “ወቦ ኪሩቤል ይቀውሙ በየማን በአምሳለ ቀሳውስት ወሱራፌል ይቀውሙ በአምሳለ ዲያቆናት ወድኅሬሆሙ ካህናተ ሰማይ ወቦ እልፍ አእላፋት ወትእልፊተ አእላፋት መብረቅ ወነጐድጓድ ወሠረገላሆሙኒ ምሉኣነ አዕይንት” እንዳለ ★ ኪሩቤል በቀኝ ሱራፌል በግራ ከፍ ብለው የሩፋኤል ሰራዊት ካህናተ ሰማይ ክንፍ ለክንፍ ገጥመው በስተኋላቸው ሲታዩ በሰማይ ውዱድ ዙሪያ እልፍ አእላፋት መብረቅ፣ ነጐድጓድ፣ ሠረገላ፣ እንደ መስታየት ብሩህ የኾነ ሲኖርበት እነዚኽ ቅዱሳን መላእክትም ሳያቋርጡ “ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ እግዚአብሔር” እያሉ ፈጣሪያቸውን በአንድነቱ በሦስትነቱ ያመሰግኑታል (ራእ ፬፥፰)፡፡ ♥️ ይኽ መልአክ ሩፋኤል ጦቢትን የተራዳ መልአክ ነው፤ ይኽ ጦቢት ዐሥሩ ነገድ በ፯፻፳ ቅድመ ልደተ ክርስቶስ ሲማረኩ ዐብሮ የተማረከ ጻድቅ ሰው ነው፤ ይኽ ሰውን በመርዳት በደግነቱ የታወቀው ጦቢት ከመንገድ ወድቆ የተገኘ በድን ቀብሮ፤ በዚያው ሌሊት ከቅጥሩ አጠገብ ፊቱን ተገልጦ ተኝቶ ሳለ አዕዋፍ ትኩስ ፋንድያ ዐይኑ ላይ ጥለውበት እንደ ብልዝ ያለ ወጥቶበት ዐይኑ ጠፋ፤ ሚስቱም ባለማስተዋል “አይቴ ውእቱ ምጽዋትከ ወጽድቅከ” (በጐነትኽ ምጽዋትኽ ያዳነኽ ወዴት ነው?) በማለት በተናገረችው ጊዜ ዐዝኖ ሞትን ተመኘ (ጦቢ ፪፥፲፬)፡፡ ♥️ ያን ጊዜ መልአኩ ሩፋኤል ባሎቿ ስለሞቱባት ቤተሰቦቿ ያንቋሽሿት የነበረችውን የራጉኤል ልጅ ሳራን ለማዳን ተልኮ በመምጣት አስቀድሞ በርሷ ላይ ዐድሮ ባሎቿን ይገድልባት የነበረውን ጋኔን አስወጥቶላት የጦቢት ልጅ ጦብያ እንዲያገባት አድርጓል፤ በዚኽም “ፈታሔ ማሕፀን” ተብሏል "ለሰብእ ወለእንስሳ ፈታሔ ማሕፀኖሙ አንተ" እንዲለው፡፡ ♥️ በኋላም ወደ ጦቢት በመኼድ ረዥም ዘመን የታወረ ዐይኑን አብርቶለት “አነ ውእቱ ሩፋኤል መልአክ አሐዱ እምነ ሰብዐቱ ቅዱሳን መላእክት” (ከሰብዐቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ ሩፋኤል እኔ ነኝ) ብሏቸው ተሰውሯል (ጦቢ ፲፪፥፲፭)፡፡ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።❤❤❤ እንኳን  ለመልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!!!❤❤❤ ❤❤ መጽሐፈ ጦቢት ምዕ ፭÷፩__❤ ### ወተሰምዐ ጸሎቶሙ ለክልኤሆሙ#// የሁለቱም ልመናቸው ከእግዚአብሔር ዘንድ ደረሰ፣// ከዚህ ርዕስ በመነሳት እንግዲህ የሁለቱ ጸሎት ከእግዚአብሔር ዘንድ ደረሰ የተባለው የነማን ጸሎት ነው?  የሚለውን እግዚአብሔር እንደፈቀደ አዘጋጀውላችሁ! '' ነገርን ከሥሩ ውሃን ከምንጩ ''እንዲሉ አበው፦ የሁለቱ ጸሎት ወደ እግዚአብሔር የደረሰው እንግዲህ የራጉኤል ልጅ የሣራና የጦቢት ጸሎት ነው ቅድመ እግዚአብሔር የደረሰው። እንዴት ጸሎታቸው ተሰማ የሚለውን እንደሚከተለው ነው። ## ጦቢት ማለት ሠናይ ማለት ነው፣ /ወርእየ እግዚአብሔር ከመ ሠናይ/ እንዲል ከመ ቀለመ ጸሐፊ ዘጠበጠበ / የሚለውን ሠናየ ብለው እንደተረጎሙት ሁሉ። አንድም ጦቢት ማለት ጠቢብ ማለት ነው። ጤት ማለት ጠቢብ ማለት እንደሆነ ሁሉ፣ ነገዱ ፣ትውልዱ  ከነገደ ንፍታሌም ነው። በሀገሩ ሳለ ከዘመዶቹ ተለይቶ በሕግ በአምልኮት ጸንቶ  አሥራት በኩራት፣ ቀዳምያት ያወጣ ነበር ፣ለዕቤራት(ለባልቴቶች) ፥ ለዕጓለ ማውታ(ወላጅ ለሌላቸው) ዘመድ ይሆናቸው ነበር፥ ሁሌም ጽድቅን የሚከተል ሰው ነበር። ከዓመት ሦስት ጊዜ ለበዓል ይወጣ ነበር። ጦቢት አሥሩ ነገድ ሲማረኩ አብሮ ተማርኮ ሄዷል። ጻድቃንን ከኃጥአን ጋር ስለምን ያስማርካቸዋል ቢሉ? ስለ ሦስት ነገር  ተማርከው በሄዱበት ሀገር  ወደ ኃጢአት፣ወደ ጣዖት እንዳይሄዱ ይመክራቸው ነበር ፣ ያስተምራቸው ነበር፣
100
4
No text...
201
5
🌼 🌻 ወ ር ኀ ጳ ጕ ሜ ን እ ና በ ዐ ላ ቶ ቿ 🌻 🌼 ▬▬▬▬▬ ▬▬ ▬▬▬▬▬ ጳጒሜን 1 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት፦ ፩. ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ (የታሠረበት) ፪. ቅዱስ ዑቲኮስ ሐዋርያ (ከ፸፪ቱ አርድእት) ፫. ቅዱስ ብሶይ ቀሲስ (ሰማዕት) ፬. አባ ዻኩሚስ / ባኹም (የ,፴፻ ቅዱሳን አባት) ፭. አባ ሰራብዮን / ሰራፕዮን (የ፲፼ ቅዱሳን አባት) ጳጕሜን 2 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1. ቅዱስ ቲቶ ሐዋርያ (ከሰባ ሁለቱ አርድእት) ጳጕሜን 3 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1. ርኅወተ ሰማይ (የሰማይ መከፈት) 2. ቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላእክት 3. ቅዱስ መልከ ጼዴቅ ካህን 4. አፄ ዘርዓ ያዕቆብ ንጉሥ (የእመቤታችን ወዳጅ) 5. ቅዱስ ሰራጵዮን ዘሰንዱን 6. ቅዱስ አኖሬዎስ 7. ቅዱስ ቴዎፍሎስ 8. አባ ዮሐንስ 9. ቅዱስ ጦቢት 10. ቅዱሳን ጦብያና ሣራ ጳጕሜን 4 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1. ቅዱስ አባ ባይሞን (ጴሜን) 2. ስድስቱ ወንድሞቹ (አብርሃም: ያዕቆብ: ዮሴፍ: ኢዮብ: ላስልዮስና ዮሐንስ) 3. ቅዱስ ሊባርዮስ ሊቅ ጳጕሜን 5 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1. ታላቁ አባ በርሶማ 2. ቅዱስ አሞጽ ነቢይ 3. ቅዱስ ያዕቆብ ዘምስር 4. አባ መግደር (እግዚአብሔር በጸሎቱ ይማረን)
225
6
No text...
233
7
https://t.me/Courhhbot?start=_tgr_2nFsidc2MjJk
228
8
No text...
228
9
መ ዝ ሙ ር ዘ ሰ ን በ ት ✞✨💒 የዓመቱ የመጨረሻ መዝሙር [ጳጒሜን ለእመ ኮነ በእሑድ...] ከመ አንተ መብረቅ ዘይወጽእ እምጽባሕ፤ ወያስተርኢ እስከ ዓረብ፤ ከማሁ ምጽአቱ ለወልደ እግዚአብሔር፤ ምስለ ኃይለ ሰማያት፤ በንጥረ መባርቅት፤ ከማሁ ምጽአቱ ለወልደ እግዚአብሔር፤ ምስለ አዕላፍ መላእክት፤ ወኵሎሙ ሊቃነ መላእክት፤ ከማሁ ምጽአቱ ለወልደ እግዚአብሔር፤ አክሊለ አክሊላት፤ ዲበ ርእሶሙ ለካህናት። መብረቅ (ፀሐይ) ከምሥራቅ ወጥቶ እስከ ምዕራብ እንዲታይ የሰው ልጅም አመጣጡ እንዲሁ ነው። ከሰማይ ኃይላት ጋር በመባርቅት ብልጭታ። ከአእላፍ መላእክትና ከሊቃነ መላእክት ሁሉ ጋር። የአክሊላት አክሊል በካህናት ራስ ላይ አለ። ምስባክ እግዚአብሔርሰ ገሐደ ይመጽእ። ወአምላክነሂ ኢያረምም። እሳት ይነድድ ቅድሜሁ። እግዚአብሔር ግልጽ ሆኖ ይመጣል። ዝምም አይልም። እሳት በፊቱ ይነድዳል። (መዝ ፵፱ : ፪ /49 : 2) #ምሥጢር፦ እግዚአብሔር በሰባ ዘመን በረድኤት ተገልጦ ይመጣል፤ መጥቶም ዝም አይልም በበጎዎቹ አድሮ ይፈርዳል አንድም በበጎዎቹ ካህናት አድሮ ክፉዎችን ካህናት ይዘልፋል፤ እሳት በፊቱ ይነዳል ማለት ክፉዎች የሚጠፉበትን መቅሠፍት መናገር ነው፤ አንድም እግዚአብሔር አምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን ሲፈጸም በሥጋ ማርያም ይገለጣል፤ መጥቶ ዝም አይልም ወንጌልን ያስተምራል አንድም አሌ ለክሙ ጸሐፍት ወፈሪሳውያን - ጻፎችና ፈሪሳውያን ወዮላችሁ እያለ ይዘልፋል። አይሁድ የሚጠፉበት መቅሠፍት በፊቱ ነው፤ አንድም በዕለተ ምጽአት የተወጋበትን ኲናት/ጦር የተቸነከረበትን ቀኖት አስይዞ ይመጣል፤ ጻድቃንን ንዑ ኀቤየ ብሎ ይጠራል ኃጥአንን ሑሩ እምኔየ ብሎ ያሰናብታል፤ ጻድቃን የሚድኑበት ሕይወት ኃጥአን የሚቀጡበት መቅሠፍት በፊቱ አለ።
229
10
የቱብ ዜና ብቻ የሚያነብ ሰው ካለ በውስጥ
427
11
✍️ መ ዝ ሙ ር ዘ ሰ ን በ ት ለክረምት ፲፩ኛ እሑድ እም፳ወ፪ ለነሐሴ እስከ ፳ወ፮ ለነሐሴ በ፫ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ይሁበነ ዝናመ በጊዜሁ፤ ይሁበነ ዝናመ በጊዜሁ ወይሁበነ እክለ በረከት፤ ይሁበነ ዝናመ በጊዜሁ ያርኁ ክረምተ ይገብር ምሕረተ ወይሁበነ ዝናመ በረከት፤ ይሁበነ ዝናመ በጊዜሁ ከሢቶ ዓይኖ ሰፊሖ የማኖ ይፌኑ ሣህሎ ወበዘአእመረ ይሴባሕ፤ ይሁበነ ዝናመ በጊዜሁ፤ ወሠርዐ ሰንበተ ለሰብእ ዕረፍተ ወብውህ ሎቱ ይኅድግ ኃጢአተ፤ ይሁበነ ዝናመ በጊዜሁ፤ ዓይነ ኵሉ ነፍስ ይሤፎ ኪያከ (ኪያሁ)፤ ይሁቦሙ ሲሳዮሙ በጊዜሁ። ✍️ ትርጉም ዝናምን በጊዜው የእህል በረከትን በወቅቱ ይሰጠናል፤ ክረምትን ያመላልሳል ምሕረትን ይሰጣል፤ የበረከትን ዝናምም ይቸራል። ዓይኑን ገልጦ (ተመልክቶ) ቀኝ እጁን ዘርግቶ ምሕረቱን ላከልን። ለሰው ሰንበትን ሠርቶ ኃጢአትንም ይቅር አለ። ፍጥረት ሁሉ ወደ አንተ ያንጋጥጣል። ምግባቸውንም በወቅቱ ይሰጣቸዋል። ✍️ ምሥጢር፦ የሰው ሁሉ ሰውነት አንተን ተስፋ አለኝታ ያደርጋል። በየጊዜው ምግባቸውን ትሰጣቸዋለህና በዘር ጊዜ ዘሩን በመከር ጊዜ መከሩን። አንድም የበልጉን በበልግ የመከሩን በመከር ትሰጣቸዋለህና። እጀ ሰፊ ነህና እጅህን ዘርግተህ በሥርዓትህ ጸንተው ለሚኖሩ ለእንስሳት ምግባቸውን ሰጥተህ ደስ ታሰኛቸዋለህ። ከሰው በቀር ከሥርዓቱ የወጣ የለምና። ✍️ ምስባክ ዓይነ ኲሉ ነፍስ ይሴፎ ኪያከ። አንተ ትሁቦሙ ሲሳዮሙ በጊዜሁ። ትሰፍሕ የማንከ ወታጸግብ ለኲሉ እንስሳ ዘበሥርዓትከ። የሁሉ ዓይን አንተን ተስፋ ያደርጋል፤ አንተም ምግባቸውን በየጊዜው ትሰጣቸዋለህ። አንተ እጅህን ትዘረጋለህ፥ ሕይወት ላለውም ሁሉ መልካምን ታጠግባለህ። (መዝ ፻፵፬ : ፲፭ - ፲፯ /144:15-17)
467
12
💒✨✞ ሥርዓተ ማኅሌት ዘነሐሴ ተክለሃይማኖት ✞✨💒 ▬▬▬▬▬ ▬▬ ▬▬▬▬▬ ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገአርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወኢትሚጥ ገጸከ እምኔየ፡ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ እዝነከ ኀቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል። መልክዐ ሥላሴ ሰላም ዕብል ለንዋየ ውስጥ ምሕረትክሙ: ትሩፋተ ገድል ኲኑኒ ሥላሴ አምጣነ ትሩፋት አንትሙ: ሶበ ሖርኩሰ ከመ እሳተፍ ገድሎሙ: ጊዮርጊስ ኢወሀበኒ መጠነ ነጥበ ጠል እምደሙ: ወተክለሃይማኖት ከልአኒ ስባረ እምዐጽሙ፡፡ ዚቅ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር ዘኢይነውም ትጉህ: በውስተ ቅዱሳን ስቡሕ: ከመ ቀስተ ደመና የዓውዶ ሱራሄ: ሎቱ ለባሕቲቱ ይደሉ ስባሔ፡፡ ነግሥ ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘመንክር ጣዕሙ: ለወልድኪ አምሳለ ደሙ: መሠረተ ሕይወት ማርያም ወጥንተ መድኃኒት ዘእምቀዲሙ: ኪያኪ ሠናይተ ዘፈጠረ ለቤዛ ዓለሙ: እግዚአብሔር ይትባረክ ወይትአኮት ስሙ፡፡ ዚቅ አመ ኖኅ ይእቲ መድኃኒት እንተ ኮነት አንቀጸ ሕይወት: ማርያም ቅድስት፡፡ ወረብ ማርያም ቅድስት አንቀጸ ሕይወት አመ ኖኅ አንቀጸ ሕይወት ማርያም ቅድስት/፪/ ይእቲ መድኃኒት "እንተ ኮነት"/፪/አንቀጸ ሕይወት/፪/ መልክዐ ተክለሃይማኖት ሰላም ለዝክረ ስምከ ዘጥንተ ፊደሉ መስቀል: ስም ክቡር ወስም ልዑል: ተክለሃይማኖት ማቴዎስ በዓለ ቀዳማይ ወንጌል: ከመ እወድሰከ መጠነ አውሥኦተ እክል: ማዕሠረ ልሳንየ ትፍታሕ ማርያም ድንግል። ዚቅ ወንጌለ መለኮት ሰበከ: ስምዓ ጽድቅ ኮንከ: ወበእንተዝ ተክለ ሃይማኖት ተሰመይከ፡፡ ወረብ ወበእንተዝ "ተሰመይከ"/፪/ተክለሃይማኖት/፪/ "ስምዓ ጽድቅ ኮንከ"/፪/ተክለሃይማኖት/፪/ መልክዐ ተክለሃይማኖት ሰላም ለአዕይንቲከ ዘአርያኣሆን ሐዋዝ: እለ ጽዱላት እማንቱ ከመ ሠርቀ ቤዝ: ተክለ ሃይማኖት ኅብአኒ እሞተ ኃጢአት አዚዝ: ለከሰ አኮ ከመዝ: ኢይረክበከ ሞት ዳግም እምዝ፡፡ አመላለስ ዳግም እምዝ/፬/ ኢይረከቦ ሞት ለተክለ ሃይማኖት/፪/ ዓዲ ወረብ "ዳግም እምዝ"/፪/ኢይረከቦ ከመዝ ሞት ለተክለ ሃይማኖት/፪/ ኢይረከቦ እምዝ ሞት ለተክለሃይማኖት/፪/ መልክዐ ተክለሃይማኖት ሰላም ለኲልያቲከ ዘፈተኖን በትዕግስት: ኢየሱስ ክርስቶስ አበ ብርሃናት: ተክለ ሃይማኖት ሰጋዲ ከመ መላእክት: ጸሎትከ ዘገበርካሃ እስከነ ኈልቊ ምዕት ዓመት: መድኃኒተ ትኩነኒ እምግሩም ቅሥት፡፡ ዚቅ ተክለ ሃይማኖት ሰማዕት ሰባኬ መድኃኒት: ጸሎትከ ትኩነነ ፀወነ እመንሱት: ተክለ ሃይማኖት ሰማዕት ሰባኬ መድኃኒት፡፡ ወረብ ሰማዕት ሰባኬ መድኃኒት ተክለ ሃይማኖት/፪/ ጸሎትከ ትኩነነ "ፀወነ እመንሱት"/፪//፪/ መልክዐ ተክለ ሃይማኖት ሰላም ለፀዐተ ነፍስከ በስብሐተ አዕላፍ እንግልጋ: ለዓለም ዛቲ እምግብርናቲሃ ወጹጋ: ተክለ ሃይማኖት ቶማስ ለመርአስ ዐቃቤ ሕጋ: ለእለ ገብሩ ተዝካረከ እንዘ ሀለዉ በሥጋ: ሀቦሙ እግዚእየ ሞገሰ ወጸጋ፡፡ ዚቅ ወወጽአት መንፈሱ ሶቤሃ: ወተቀበልዎ መላእክት በስብሐት ወበማኅሌት: እንዘ ይብሉ ሃሌ ሉያ: ወአብዕዎ ኢየሩሳሌም ሰማያዊተ፡፡ መልክዐ ተክለ ሃይማኖት ሰላም ለበድነ ሥጋከ ኤልሳዕ መምህር ዘገነዛ: በሠናይ ፄና መዓዛ: ተክለ ሃይማኖት ሰባኪ ፊልጶስ ዘብሔረ ጋዛ: ለሥጋየ መሬታዊት እመ የኀልቅ እዘዛ: ስብረተ ዐፅምከ ይኩነኒ ቤዛ፡፡ ዚቅ ሖረ ኀቤሁ ለተክለ ሃይማኖት ቀዲሙ ሌሊተ: ኤልሳዕ ስሙ መልአኮሙ ለአርድዕት: ውእቱኒ አምጽአ ከርቤ አፈዋት: ገነዝዎ በሰንዱናት ለተክለሃይማኖት። መልክዐ ተክለሃይማኖት ሰላም ለግንዘተ ሥጋከ በዘቦቱ ይትመኀፀኑ: ነገሥተ እስራኤል ኄራን ዘአስተሣነይዎ በበዘመኑ: ተክለ ሃይማኖት ሠዋዒ ለእግዚአብሔር ካህኑ: አድኀነኒ እምጸብአ ከይሲ ዘዐሥር ቀርኑ: ወእምብእሲ ዘክልኤ ልሳኑ፡፡ ዚቅ መላእክት አእመሩ ሃይማኖተከ: ነገሥት ሐነፁ መካነከ: አባ ተክለሃይማኖት ክርስቶስ ዘአፍቀርከ፡፡ መልክዐ ተክለሃይማኖት ሰላም ለመቃብሪከ እምቅድመ ትኑም ውስቴታ: ታቦተ ማርያም ድንግል ዘአንበርከ በውሳጢታ: ተክለሃይማኖት አቡየ ለወልድከ ዕጓለ ማውታ: ለበረከትከ ይከልለኒ ረድኤታ: ወይዑደኒ ዘጽድቅከ ወልታ። ዚቅ ጸለየ ተክለ ሃይማኖት እንዘ ይብል ኀበ ተቀብረ ሥጋየ ወተክዕወ ደምየ ህየ ይኩን በረከት፡፡ ወረብ ጸለየ ተክለ ሃይማኖት እንዘ ይብል ኀበ ተክዕወ ደምየ/፪/ "ህየ ይኩን"/፪/በረከት/፪/ አንገርጋሪ ሞቶሙሰ ለጻድቃን ሕይወቶሙ ውእቱ እስመ ለጻድቅ ይትሌዓል ቀርኑ በክብር ጻድቃን እለ አስመርዎ ለእግዚኦሙ ምድረ ብርህተ ወጽዱተ ይወርሱ፡፡ አመላለስ፦ ገነተ ትፍሥሕት ኪያሃ አውረሶሙ ወአቀቦሙ ከመ ብንተ ዐይን ለጻድቃን/2/ እለ ሎቱ ተቀንዩ በሕይወቶሙ/4/ ወረብ፦ አሜሃ ይቤሎ"እለ በየማኑ"/2/ /2/ ንዑ ለአቡየ ቡሩካኑ ለአቡየ ንዑ/2/ እስመ ለዓለም ደሪዖሙ ተአጊሦሙ: መጠዉ ነፍሶሙ ለሞት: እለ ሎቱ ተቀንዩ በሕወቶሙ: እምፀሐይ ይበርህ ገጾሙ: እለ አጥረይዋ ለትዕግስት: እለ...: እፎ አምሰጥዎ ለመድብብ ከመ ይባዕዎ ለመርኀብ: እለ...: ዕፎ አመሠጥዎ ለሞት: ዓደዉ እሞት ውስተ ሕይወት: እለ...: እለ ጸውዖሙ ወይቤሎሙ: ንዑ ለአቡየ ቡሩካኑ: እለ...: አመ ያቀውም አባግዐ በየማኑ: ወአጣሌ በጸጋሙ: እለ...: አሜሃ ይቤሎሙ ለእለ በየማኑ: ንዑ ለአቡየ ቡሩካኑ: እለ...:ወያወርሶሙ ምድረ ሐዳሰ: እንተ ታውኀዝ ሀሊበ ወመዓረ: እለ...:ገነት ትፍሥሕት ኪያሃ አውረሶሙ ወዓቀቦሙ ከመ ብንተ ዓይን ለጻድቃን: እለ ሎቱ ተቀንዩ በሕይወቶሙ፡፡
536
13
አርጋኖን ዘረቡዕ ምዕራፍ ፩ ፩. ስለ ጌታችን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ አስቀድሜ እግዚአብሔርን አመግናለሁ፡፡ ስላንቺም፡፡ (ሮሜ ፩-፰) ፪. የውዳሴሽ ወሬ በዓለም ሁሉ ተሰምቷልና በመንፈስ ቅዱስ እንደተናገርሽ እንዲህ ስትይ እነሆ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ያመሰግኑኛል፡፡ (ሉቃ፣ ፩፣ ፵፰) ፫. በውነት ምስጋና ይገባሻል፡፡ የእግዚአብሔር እናቱ ሁነሻልና በውነት መደነቅ ይገባሻል፡፡ ዓለምን ሁሉ በመሐል እጁ የያዘ እርሱን ወልደሻልና በዕውነት ብፅዓን ይገባሻል ለዕውነተኛ ፀሐይ መውጫ ሆነሻልና፡፡ ፬. በዕውነት መመስገን ይገባሻል ለማለዳው ኮከብ ምሥራቅ ሆነሻልና በውነት መደነቅ ይገባሻል፡፡ ለጥምቀት ልጆች መመከያ ሆነሻልና፡፡ በውነት ብፅዕና ይገባሻል፡፡ ለሃይማኖት መሠረት ጽናተ ሆነሻልና፡፡ ፭. ከኪሩቤል ክብር ገናንነት ላንቺ ይገባል፡፡ ከሱራፌልም ውዳሴ ከመላእክትም እልልታ ከመላእክት አለቆችም ዝማሬ ላንቺ ይገባል፡፡ ሆነሻልና፡፡ ፭. ከኪሩቤል ክብር ገናንነት ላንቺ ይገባል፡፡ ከሱራፌልም ውዳሴ ከመላእክትም እልልታ ከመላእክት አለቆችም ዝማሬ ላንቺ ይገባል፡፡ ፮. ከነቢያት ትንቢት ከሐዋርያት ስብከት ላንቺ ይገባል፡፡ ከቅዱሳን ሰማዕታት እናታችን መባል ከመሐይምናንም እመቤታችን መባል ከክርስቲያንም ሁሉ አፍ የመድኃኒታችን ቀንድ መባል ላንቺ ይገባል፡፡ ፯. ከመሲሓውያን ነገስታት አፍ ንግሥታችን መባል ከልዑላንም መላእክት በላይ ከፍ ከፍ ማለት ከታችኞችም ፍጡራን ላንቺ መገዛት ይገባል፡፡ እንግዲህ አንቺ ከሰማይ ትበልጫለሽ ከተራሮችም ከፍ ትያለሽ፡፡ ስለ አንቺም እንዲህ እላለሁ ከፀሐይ ብርሃን ከጨረቃም ድምቀት አንቺ ትበልጫለሽ፡፡ ፰. ስለ አንቺ እንዲህ እላለሁ፡፡ ከአርዮብ መልክ ከመብረቅም ብርሃን አንቺ ታበሪያለሽ፡፡ ስላንቺ ደግሞ እንዲህ እላለሁ በሰማይ ካሉ ትጉሃን መላእክት ትከብሪያለሽ፡፡ ከመናብርትም ከሥልጣናትም ትቀደሻለሽ፡፡ ፱. ስላንቺም እንግዲህ እንዲህ እላለሁ መልኩ አስተያየቱ ልዩ ልዩ ከሚሆን አበባ ፍሬ ትሸቻለሽ፡፡ (አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ)
314
14
ሐተታ፦ ፋራን ማለት ኀያላን ማለት ነው። ኃያላንም ማለት ሥላሴ ናቸው። የሥላሴ ማደሪያ አንቺ ነሽ። ዕንባቆም ማለት ጠቢብ ማእምር ለባዊ ማለት ነው። ትውልዱ ከነገደ ስምዖን። ምሥራቅ ዕፁት ዘሕ ቅኤል ። ሕዝቅኤል በጽኑ መቆለፊያ የተቆለፈች አዳራሽ ያየብሽ ምሥራቅ አንች ነሽ። ታሪክ፦ ሕዝቅኤል ከምሥረቅ ወደ ምዕራብ ከቤተ መቅደስ ሲገባ ታላቅ አዳራሽ በጽኑ መቆለፊያ ተቆልፋ ቀይ ጎልማሳ አፋውን ታጥቆ ሳይከፍት ገብቶ ሳይከፍት ሲወጣ በዓለሙ ቍራ መልቶ ያን ቍራ በሰይፍ እየቀላ ሲጥለው አይቷል። አዳራሽ የእመቤታችን ቁልፍ የማኅተመ ደንግልናዋ ቀይ ጉልማሳ የጌታችን እንደ ተቆለፈች ሳይከፍት ገብቶ ሳይከፍት መውጣቱ በሕቱም ድንግልና ተፀንሶ በሕቱም ድንግልና ለመወለዱ ምሳሌ። አፋ የሥልጣን ቍራ የአጋንንት በሰይፍ እየቀላ መጣሉ አጋንንትን የማጥፋቱ ምሳሌ ነው። ሕዝቅኤል ማለት ጽኑዕ ጽንዐ እግዚአብሔር ማለት ነው። በጥሬው አዘቅማዘቅ ይላል ያልተመለሰ ንባብ ነው። ትውልዱ ከነገደ ሌዊ ነው። ወሙጻአ ሕግ ዘቤተ ልሔም ወምድረ ኤፍራታ ዘሚክያስ ። የሕግ መገኛ። አንድም ሕግ ይወፅእ እምጽዮን አንሶሰወተ ወአስተርአየት ሕግ እንዲል የጌታ መገኛየምትሖኚ። ሚክያስ ወአንቲኒ ቤተልሔም ምድረ ኤፍራታ ኢትቴሐቲ እምነገሥተ ይሁዳ ብሎ የተናገልሽ አንች ነሽ። ሚክያስ ማለት መኑ ከመ እግዚአብሔር ማለት ነው። ነገዱ ከነገደ ንፍታሌም። ዕፀ ሕይወት ዘሲሎንዲስ። ሲሎንዲስ የሚያድንባት ዕፀ ሕይወት አንች ነሽ። ሐተታ ፦ ሲሎንዲስ ፈላስፋ ነው። ሁለት ዕፀው አሉት ባንዲቱ ይገድልባታል በአንዲቱ ያድንባታል። እመቤታችንንስ በፈላስፋ እንጨት አይመስላትም ብሎ ምዕመን ነው አምኖ ተጠምቆ ብዙ ሥራ ሠርቷል። ብዙ ድርሳን ብዙ መጽሐፍ ጽፏል። ሊቃውንትም በየድርሳናቸው ሲሎንዲስሂ ሰመያ ፅፀ ሕይወት ወዕፀ መድኃኒት እግዝእትነ ማርያም እያሉ ወስደውታል። አንድም የሰሎሞን የፍልስፍና ስሙ ነው። ዕፀ ሕይወት ይእቲ ለእለ ይትመረጐዙ ባቲ ብሎ የተናገረልሽ አንች። ይት ወፈዋሲተ ቍስሉ ለናሆም ። ናሆም ከቍስለ ኀዘኑ የዳነብሽ ባቢሎን ኵሕሰ ጸልዕኪ ወአልቦ ዘይፌውሰኪ ብሎ የተናገረልሽ አንች ነሽ። ናሆም ባቢሉን አንችን የሚያድንሽ የለም እኔን ግን ጌታ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ሰው ሆኖ ያድነኛል ብሎ ተናግሯልና። ናሆም ማለት ፈውስ ፈዋሲ ፈውሰ እግዚአብሔር ማለት ነው። ትውልዱ ከነገደ ዛብሎን። ትፍሥሕት ዘዘካርያስ። ዘካርያስ አብርሂ አብርሂ ጽዮን ተፈሥሒ ተፈሥሒ ኦ ወለተ ጽዮን እስመ ናሁ ንጉሥኪ በጽሐ እንዘ ይጼዐን ዲበ ዕድግት ወዲበ ዕዋለ አድግ ብሎ የተናገረልሽ አንች ነሽ። ዘካርያስ ማለት ዝኵር ዝክረ እግዚአብሔር ማለት ነው። ትውልዱ ከነገደ ሌዊ። ጽርሕ ንጽሐት ዘሚልክያስ ። ሚልክያስ ተፈሥሒ ቤተ እሥራኤል ወተኃሠዪ ቤተ ይሁዳ ብሎ የተናገረልሽ አንች ነሽ። ሚልክያሰ ማለት መልአክ ሐዋርያ ማለት ነው ትውልዱ ከነገደ አሴር ነው። ፴ ፯. ኦ ድንግል አምሳል ወትንቢት ዘነቢያት ። ነቢያት ትንቢት የተናገሩልሽ ምሳሌ የመሰሉልሽ አንች ነሽ። ሞገሶሙ ለሐዋርያት ። የሐዋርያት ባለሟላቸው ባለሟል የምታደርጊያቸው አንች ነሽ። አንድም ባለሟል የምታደርጊያቸው እመቤታችን በምን እንመስልሻለን። እሞሙ ለሰማዕት ። የሰማዕታት እናታቸው። ሐተታ ፦ ሰማዕትነት ብቻ እሳት ስለት አይደለም ስደትም ሰማዕትነት ነው። ሰደትን ባርካ ጀምራ የሰጠቻቸው እሱዋ ናት። ወእኅቶሙ ለመላእክት ። የመላእክት እኅታቸው እመቤታቸን በምን እንመስላሻለን። ሐተታ ፦ እኅቶሙ አለ በንጽሕና በቅድስና ትመስላቸዋለችና። አንድም እኅትነ ነያ እያሉ ያመስግኗታልና። ትምክሕቶሙ ለወራዙት ወደናግል ወመነኮሳት እለ ይተግሁ በውስተ አናቅጺሃ መዓልተ ወሌሊተ ። ውስተ ታቦታቲሃ ይላል። ታቦተ በአታ ታቦተ ልደታ ታቦተ ኪዳነ ምሕረት ዛሬ ነው ብለው ቤተ ክርስቲያን ለመሳለም በመዓልትም በሌሊትም የሚተጉ። አንድም ውስተ ደርሳናቲሃ ይላል። ድርሳኗን ለመስማት። አንድም ውስተ መምህራኒሃ ይላል። ያንሳህልል ሰኰናከ ውስተ መዽረኸ ኆኅት እንዲል። የእመቤታችንን ምስጋና ሲያስተምሩ ከመምህራን ዘንድ ሂዶ ለመስማት። አንድም ውስተ ሕዋሳቲሃ ይላል። በእንተ አእዳዊሃ እለ ገሠሣከ። ወበእንተ አብራኪሃ እለ ሐቀፋከ። ወበእንተ አጥባቲሃ እለ ሐፀናከ እያሉ ሕዋሳቶቿን አማላጅ አድርገው ለማመስገን በመዓልትም በሌሊትም የሚተጉ። ወራዙት ዕድሜ ትሰጠናለች ዐስበ ድንግልናችንነ ታሰጠናለች። መነኮሳት በምንኩስና ታጸናናለች ምንኩስናችንን ታስፈጽመናለች ብለው የሚመኩብሽ እመቤታችን በምን እንመስልሻለን። አንድም የሚመኩብሽ አንቺ ነሽ።
380
15
አንድም የዳዊት ወንድም ነው ይሉታል። ለዳዊት ሀብተ በገና እንደተሰጠው ለእሱም ሀብተ ሠረገላ ተሰጥቶታል። አንድም አሚ ትፍፍ። ናዳብ መንፈስ ቅዱስ ነው። የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ አንች ነሽ። መሰንቆሁ ለዳዊት። የዳዊት መሰንቆ አንቺ ነሽ። ሐተታ ፦ ዳዊት መሰንቆ ሲመታ በገና ሲደረድር ብዙ ድውያን ይፈወሱ ነበር። ሳኦልም መንፈሰ ሰይጣን አድሮበት ነበርና ሲጸናበት ዳዊትን በገና ደርድረልኝ ይለው ነበረ። ይህ ሁሉ መደረጉ ጌታ እመቤታችን በጉልበቱ ቢኖሩ ነውና። አንድም ለዳዊት የሃይማኖቱን ዋጋ የምታሰጭው አንች ነሽ። መሰንቆ ይእቲ ሃይማኖት እንተ ለበስዋ ሰማዕት እንዲል። ዳዊት ማለት ልበ አምላክ ኅሩይ ፍቁር ማለት ነው። ትውልዱ ከነገደ ይሁዳ ነው። ወአክሊሉ ለሰሎሞን ። የሰሎሞን ሐቲም ቀለበቱ አንች ነሽ። ታሪክ፦ ሰሎሞን ሐሩራኤል ጭርዋቅ የሚል ስመ አምላክ የተቀረጸበት ሐቲም ቀለበት ነበረው። ትእምርተ መንግሥቱ ግርማ ሞገሱ እሱ ነው። ከሴት ሲደርስ አንበሳ መደብ ሲወጣ ከዙፋኑ አኑሮ ነውና። አንበሳ መደብ ወጥቶ ሲመለስ ሰይጣን ለምቀኝነት አያርፍምና ማንሣት የማይቻለው ቢሆን ከነዙፋኑ ጠቅሎ ወስዶ ከባሕር ጣለው። ሰሎሞን ቢመለስ ዙፋን ቤቱ ከለከለው። እሱ ሂዶ ከዙፋኑ ተቀመጠ። እረ እኔ ሰሎሞን ነኝ አሥገባኝ ቢለው መልካም ከተሜ ሰሎሞን ከዙፋኑ ተቀምጦ ሰሎሞን ነኝ ትላለህን እረ ወግድ አለው። እርሱም ወጥቶ ሄደ። ያም የማይፈርድ የማይናገር ሆነ። እኅቱም ሚስቱም ቢሉ። አንድም ሳቤላ ለምትባል ነቢዪት እንዲህ ሆነብን ብለው ነገሯት። ዳግም ሕግን ከፊቱ ሆናችሁ እያጠፋችሁ አንብቡ እሱ አንደ ሆነ ይመልሳችኋል ሌላ እንደ ሆነ ዝም ይላችኋል አለቻቸው። ከፊቱ ሆነው እያጠፉ ቢያነቡ ዝም አላቸው ጊዜ ይግለጠው ብለው ትተውታል። ከዚህ በኋላ ከገዛ ከተማው ሁለት ሰምንት ያህል ለምኑዋል። ሰይጣን የሰው ልቡና አጽንቶበት የሚዘከረው አጥቶ ከመሠግራነ ዓሣ ሂዶ ስም እግዚአብሔር ጠራ ይህ ዘብዛባ ብሎ የሞተ ዓሣ ጣለለት። ሆድ ዕቃውን አውጥቶ ለመመገብ ቢቀደው ቀለበቱን አገኘ ንጉሡን ከዚህ ምን አመጣው ብለው ክብብ ክብብ አድርገውታል። እሱም ወጥቼ እሄዳለሁ ሲል ወዴት ትሄዳለህ ብሎ በህንድ በኩል ምድረ አስቆፍሮ ቀብሮታል። እንዳይወጣ መርበብተ ሰሎሞን የሚባል ስመ አምላክ አትሞበታል። እሱንስ ከዚህ ሁሉ ያደረሰው ምንድን ነው ቢሉ ከዕለታት ባንዳቸው የተራበ ሰው ስመ እግዚአብሔረ ሲጠራ ሰምቶ ይህ ሰው ምን ሆኗል አለ። ተርቦ ነው ብለውታል። ረኀብ ምንድር ነው ብሎ ነበርና ይቅመሰው ብሎ። ፍርዱ እንጂ ነው ቀድሞ በሞግዚት አደገ ኋላም በመንግሥት ሁኖ በየት ይወቀው። የሰሎሞን መንግሥት በቀለበት ምክንያት እንደ ተመለሰ በአዳም የሄደ ልጅነት በእሷ ምክንያት ተመልሷ የሰሎሞን ቀለበት አንች ነሽ አለ። አንድም የሰሎሞን ዘውድ አንድ ነሽ። ሐተታ ፦ ዘውድ እንዲያስከብር የምታስከብሪው አንድ ነሽ። ሰሎሞን ማለት መስተሳልም ማለት ነው። ገነት ዕፁተ ዓዘቅት ኅትምት ። በውስጥ በአፍአ የታጠረች ተክል በውስጥ በአፍአ በደንጊያ የተገጠመች የውሃ ጉድጓድ አንቺ ነሽ። ሐተታ ፦ ይህን ተክል ሌባ እንዳይደርስበት አውሬ እንዳይተነፍስበት በውስጥ በአፍአ ያጥሩታል። ይህንም ጉድጓድ ጠላት መርዝ ንስናሽ እንዳይጥልበት ለኃምሳ ለስሳ የማይነሣ ደንጊያ ይገጥሙታል። ጠላት መርዝ ንስናሽ እንዳይጥልበት ለኃምሳ ለስሳ የማይነሣ ደንጊያ እንዲገጥሙት በእመቤታችንም ልማደ አንስት ዘርዐ ወራዙት የለባትምና። ተክልን ሌባ እንዳይደርስበት አውሬ እንዳይተነፍስበት በውስጥ በአፍአ እንዲያጥሩት በእመቤታችንም የሀልዮ ኃጢአት የለባትም አጋንንት ድል አይነሷትምና። መንፈስ ቅዱስ ዐቀባ እምከርሰ እማ እንዲል። ገነት የእመቤታችን ተክል የጌታ ቅጽር የረድኤተ እግዚአብሔር ምሳሌ። ፴ ፭. መሶበ ወርቅ እንተ ኤልያስ ። የኤልያስ መሶበ ወርቅ አንች ነሽ። ታሪክ፦ እንደ ውዳሴ ማርያም። ትርፍ ኤልያስ ከኤልዛቤል ጋራ ተጣልቶ በከተማ ተቀምጦ ሳለ ኤልዛቤል በዚህ ከተማ ወይ እኔ ኑሬበት ወይ አንተ ኑረህበት ነው እንጂ መኗኗርን አለ ብላ ላከችበት። ከዚህ በኋላ መልአኩ መጥቶ ከነብር ትፋዘዢ እንቅልፍ ታበዢ እንዲሉ። ኤልያስ ከንግሥቲቱ ከኤልዛቤል ጋራ ተጣልተህ ከዚህን ተቀምጠሃል ተነሥተህ ሂድ አለው። ደንግጦ ተነሥቶ ሲሄድ ደክሞት ወነበረ ታሕተ ዕፀ ከርሚን እንዲል። ከደደሆ ጥላ ዐረፈ። አንቀላፍቶት ተኛ መልአኩ መጥቶ ቀስቅሶት ቢነሣ ከራስጌው እንጀራ ባገልግል ውሃ በመንቀል ተዘጋጅቶ አገኘ። ያን ተመግቦ ተመልሶ ተኛ ዳግመኛ ቀሰቀሰው በልቶ ተኛ። ዳግመኛ ቀስቅሶ ብላዕ እሰከ ትጸግብ እስመ ርኁቅ ፍኖትከ አለው። ያን ተመግቦ ወሖረ በኀይለ ውእቱ እክል ፵ መዓልተ ዐርባ ሌሊተ እንዲል ዐርባ መዓልት ዐርባ ሌሊት ሂዶ ይኸው ጽንዕ ሀኖት ዐርጓልና። የኤልያስ መሶበ ወርቅ አንች ነሽ አለ። መሶብ የእመቤታችን ወርቅ የንጽሕናዋ የቅድስናዋ ኅብስት የሥጋው ደሙ ኤልያስ የምዕመናን ምሳሌ ነው። ኤልያስ ማለት ዘይት ማለት ነው። ወገደፈቶ ታሕተ አሐቲ ዕፀ ኤልያስ ወአሐቲ መስፈርተ ኤልያስ ታገምር ዐሠርተ ምክያዳተ ወይን እንዲል። ትውልዱ ከነገደ ሌዊ ነው። መስብክት ዘኤልሳዕ ። የኤላሳዕ ልሕኵት አንች ነሽ። ታሪክ ፦ በዘመነ ረኃብ ዲቂቀ ነቢያት ተሰብስበው ከኤልሳዕ ዘንድ ሄዱ። ተጨዋውተው ሲሄዱ ደቀ መዝሙሩ ግያዝ ይባላል ጠርቶ ቅጠል ለቅመህ ቀቅለህ ስጣቸው አለው። እሱም ክፉና በጎ ሳይለይ ለቅሞ አምጥቶ ቀቅሎ ሰጣቸው። ሕምዝ ባቲ በልሕኩተ ነቢይ። በኤልሳዕ ሸክላ መርዝ አለባት እያሉ ጮሁ። የስንዴ ዱቄት አምጥተህ አላትነህ ስጣቸው አለው። አላትኖ ቢሳጣቸው ምረቱ ጠፍቶላቸው ጣፍጧቸው ተመግበዋል። ልሕኵት የእመቤታችን ቅጠል የትስብእት ላተን የመለኮት ምረት የፍዳ የመርገም ምሳሌ ነው። ኤልሳዕ ማለት መልአክ ዐቃቤ ሀገር ማለት ነው። ትውልዱ ከነገደ ይሳኮር ነው። ፅንስ ምስለ ድንግልና ዘኢሳይያስ ። ኢሳያይስ ናሁ ድንግል ትፀንስ ወትወልድ ወልደ ብሎ የተናገረልሽ አንች ነሽ። ኢሳይያስ ማለት መድኃኒት ቅቡዕ እምቅብዐ ትንቢት ማለት ነው። አባት እናቱም የኋላ ሰዎችም ቢሉ በትንቢቱ እንዲረባ እንዲጠቅም ዐውቀው አውጥተውለታል። ትውልዱ ከነገደ ስምዖን። ብኵ ርና እንበለ ሩካቤ ዘዳንኤል ። ዳንኤል እብን ዘተበትከ እምደብር ነዋህ ዘእንበለ እድ ወይትቀባዕ ቅዱሰ ቅዱሳን ወይትሐተም ራእየ ነቢያት ብሎ የተናገልሽ አንች ነሽ። ታሪክ፦ ዳንኤል በባቢሎን በግበ አናብስት ወድቆ ሳለ ዕንባቆም ወአብሰለ ተብሲለ ከመ ይሰድ ምሳሐ ለእለ የዓጽዱ እንዲል። ላጫጆች ምሳ ይዞ ሲሄድ መልአክ መጥቶ ሰድ ዘንተ ምሳሐ ለዳንኤል ዘሀሎ ውስተ ግበ ባቢሎን አለው። አይቴ ሀሎ ዳንኤል ወለባቢሎንኒ ኢየአምራ አለው። ወነሥኦ በሥእርተ ድማኁ እንዲል ሴት በማንጠልጠያ ባንዲት ጣቷ የቅቤ ቅሏን እንድትይዝ አንዲት ጠጉሩን ይዞ ወስዶታል። እሱም ሳይከፍት እንደ ተቆለፈ ገብቶ መግቦት እንደ ተቀለፈ ወጥቷል። ዳንኤልም ትንኝን በምግብ የሚያስብ እግዚአብሔር አሰበኝ ብሏል። ግብ የእመቤታችን ዕንባቆም የመለኮት ዳንኤል የምእመናን ሳይከፍት ገብቶ ሳይከፍት እንደ ወጣ በሕቱም ድንግልና ተፀንሶ በሕቱም ድንግልና የመወለዱ ምሳሌ ነው። ዳንኤል ማለት ዳኛ እግዚአብሔር ማለት ነው። ትውልዱ ከነገደ ይሁዳ ነው፡ ፴ ፮. ወደብረ ፋ ራን ዘዕንባቆም ። ዕንባቆም እግዚአብሔርሰ እምቴማን ይመጽእ ወቅዱስኒ እምደብረ ፋራን ወእምአህጉረ ይሁዳ ብሎ የተናገረልሽ አንች ነሽ።
296
16
ያዕቆብ ከምድር እስከ ሰማይ ደርሳ በላይዋ ዙፋን ተነጽፎባት በዚያ ላይ ንጉሥ ተቀምጦባት መላእክት ሲወጡባት ሲወርዱባት በፍኖተ ሎዛ ያያት የወርቅ መሰላል አንች ነሽ። ታሪክ፦ እንደ ውዳሴ ማርያም። ያዕቆብ ማለት አዕቃጼ ሰኰና አኃዜ ሰኰና ማለት ነው። ወናዛዚቱ ለዮሴፍ። ዮሴፍን ከወንድሞቹ ከብእሲተ ጲጥፋራ የምታረጋጊው የምታጽናኚው አንቺ ነሽ። ታሪክ ፦ ዮሴፍ ሲገባ ደረቱን ሲወጣ ባቱንእያየች ብእሲተ ጲጥፋራ በሐፀ ዝሙት ተነደፈች። ከዕለታት ባንዳቸው ከዕቃ ቤት ገብቶ ያልገባውን ሲያስገባ የገባውን ሲያናፍስ አንተ ባሪያ ዛሬ አለቀቅሁህም ብላ ተራምዳ ያዘችው። ጌታዬ በሁሉ ሲያሠለጥነኝ ባንች አላሠለጠነኝም ብሎ ወጥቼ እሄዳለሁ ሲል ከወደኋላው ቀሚሱ ተቀደደ ብታፍር ጮኸች። መጥተው ምን ሆንሽ አሏት። ሰው ባሪያ ሲገዛ አፍንጫ ጎራዳ ፊተ ጨምዳዳ ራሰ ቆርዳዳ ይገዛል እንጂ መልከ መልካም ባሪያ ገዝቶ ልድፈርሽ አለኝ። አይሆንም ብለው ቀሚሱን ቀዶት ሄደ አለቻቸው። አሕዛብ ፍርድ ጠንቃቂዎች ናቸውና ፈቃዱስ ያንች ይመስላል። ያማ ቢሆን የሱ ከወደፊቱ ያንች ከወደኋላሽ ባልተቀደደም ነበር። ነገር ግን ደስ ይበልሽ ብለው አሰሩት። ለንጽሕና አብነት ሆኗልና ከብእሲተ ጲጥፋራ የምታረጋጊው አንች ነሽ አለ። ዮሴፍ ማለት ገበገብ ማለት ነው ልያ ባላ ከወለዱ በኋላ ወልደዋለችና ዓመት ዓመት ድገመኝ ስትል ገበገብ ብለዋለች። ዛሬ የጋፋት ሰው ዓመት ዓመት ድገመኝ ሲል ሐዲስ እህል በቀመሰ ጊዜ ገበገባኒ እንዲል። ፴፫. ጽላት ዘሙሴ። የሙሴ ጽላት አንች ነሽ። ዕፀ ጳጦስ ዘሲና። በሲና ያያት ዕፀ ጳጦስ አንች ነሽ። ሐተታ፦ ሲን የሚባል እንጨት ስለበቀለባት። አንድም ሙሴ ደብረ ሲና ሐመልማል ከነበልባል። ነበልባል ከሐመልማል ተዋሕዶ ያያት ዕፀ ጳጦስ አንች ነሽ። ሙሴ ማለት ዕጓለ ማይ ማለት ነው። ተርሙት ወለተ ፈርዖን እማይ ዘረከብክዎ እማይ ዘአውፃእክዎ ስትል ዕጓለ ማይ ብለዋለችና። ጸናጽል ዘውስተ ልብሱ አ ሮን ካህን ። በአሮን በልብሰ እንግድዓ በልብሰ መትከፍ ያለሽ ሻኩራ አንች ነሽ። ታሪክ ፦ ጌታ ሙሴን ወንድምህ አሮን ወደ ቤተ እግዚአብሔር ሲገባ ወርቁን እንደ ኳስ አሠርቶ ስድስቱን በፊት ስድስቱን በኋላ አድርጎ ድምፅ ያለው ልብስ ለብሶ ያንን እያሰማ ገብቶ ይጸልይ አለው። መላእክት እንዳይቀሥፉት። አንድም ደዌያት እንዲከለከሉ። ይኸውም ምሳሌ ነው። ልብስ የእመቤታችን ዐሥራ ሁለቱ አዕናቁ ያሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ከዚያ ድምፅ መሰማቱ ሐዋርያት ወላደተ አምላክ ብለው የማስተማራቸው ምሣሌ። አንድም ሻኩራ የእመቤታችን ልብስ የንጹሓን አበው ምሳሌ። ከዚያ ድምፅ ሰምተው ደዌያት ይከለከሉ እንደ ነበረ ጌታ ከእመቤታችን ሰው ከሆነ ወዲህ ፍዳ መርገም ጠፍቷልና። አሮን ማለት ደብር ደብራዊ መደብር ደብረ እግዚአብሔር ማለት ነው። ሙሴና አሮን ትውልዳቸው ከነገደ ሌዊ ነው። ወዓዲ በትር እንተ ሠረፀት ወጸገየት ወፈረየት ። ዳግመኛም ሳይተክሏት በቅላ ውሃ ሳያጠጧት አብባ ለውዝ ገውዝ በኵረ ሎሚ አፍርታ የተገኘች በትረ አሮን አንች ነሽ። ፍሬው አንድ ነው ቢሉ ያንድነተ ፫ ነው ቢሉ የሦስትነት ፲፪ ነው ቢሉ ያሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ምሳሌ ነው። ክፍል ፩ ። ፴ ፬. ሐ ውልተ ስምዕ ዘኢያሱ ። የኢያሱ የምስክርነቱ ደንጊያ አንች ነሽ። ኢያሱ እሥራኤልን የሞዓብን አምላክ ታመልኩ ወይስ የእሥራኤልን አምላክ አላቸው። እኛስ የእሥራኤልን አምላክ እናመልካለን እንጂ የሞዓበን አምላክ አናመልክም አሉት። አሁን የሞዓብን አሞላክ እናመልካለን ቢሉት የሚተዋቸው ሁኖ አይደለም። አስወድዶ ለማድረግ ነው እንጂ። ምን ምልክት ይሁንባችሁ አላቸው። አንተ ያልኸው ይሁንብን አሉት። ፫ ገጽ ያላት ደንግያ አምጥቶ ተክሏል። የወጣ የወረደው ያለፈ ያገደመው ሁሉ ኢያሱ ከእሥራኤል ጋራ የተማማለባት ደንጊያ ናት እያለ ያያታል። ሐውልት የእመቤታችን። ፫ ገጽ የሦስቱ ድንግልናዋ። አንድም ከሥር ፩ ነው ያንድነት። ሦስቱ የሦስትነት። ሐውልት የእመቤታችን ምሳሌ አንድነት ሦስትነት የታወቀ ጌታ ከእመቤታችን ሰው ከሆነ ወዲህ ነውና። ወአልቦ ዘአእምሮሙ ለሥሉስ ቅዱስ ዘእንበለ እምድኅር ተሠገወ ወልድ ዋሕድ እምቅድስት እሙ እንዲል። አንድም ሐውልተ ስም ይላል። የኢያሱ የስሙ መታወቂያ አንች ነሽ። ኢያሱ መድኃኒት ማለት ነው። የኢያሱ የመድኃኒትነቱ ምሳሌ የሚሆን ኢየሱስ ከእሷ ተወልዶ ዘያድኅኖሙ ለሕዝቡ እምኃጢአቶሙ ባለው ታውቋልና ኢያሱ ትውልዱ ከነገዱ ኤፍሬም ነው። ፀምር ዘጌዴዎን ። የጌዴዎን ብዝት አንች ነሽ። ጌዴዎንን መልአኩ ጌታ ባንተ አድሬ እሥራኤልን ከምድያም ሰዎች አድናቸዋለሁ ብሎሃል ሂድ አለው። እንኪያስ ቆየኝ መሥዋዕት ልሠዋ ብሎት ሄደ መሥዋዕት ሠውቶ ሥጋውን በቅርጫት ደሙን በብርት አድርጎ አቀረበ።ደንጊያውን ጸፈጸፈ እንጨቱን ረበረበ ሥጋውን እዚያ ላይ አደረገው። መልአኩ በዘንግ ቢነካው ተቃጥሏል። እሳት የመቅሰፍተ እግዚአብሔር ሥጋው የአሕዛብ ሕለት የኵናተ ጌዴዎን ምሳሌ ነው። ሁለተኛ ጸምር ልዘርጋ ጠል ከብዝት ላይ ይውረድ ዳርና ዳሩ ይቡስ ይሁን አለው ይሁንልህ አለው። ሦስተኛ ፀምር ልዘርጋ ጸምር ይቡስ ይሁን ጠል በዳርና በዳር ይውረድ አለው ይሁንልህ አለው። ሁሉም ሆኖለታል። ለጊዜው ፀምር የእሥራኤል ጠል የረድኤተ እግዚአብሔር ምሳሌ ጠል ከፀምር መውረዱ እሥራኤልን የመርዳቱ በዳርና በዳር አለመውረዱ አሕዛብን ያለመርዳቱ ምሳሌ ነው። አንድም ፀምር አይለወጥም የእሥራኤል ጠል የመቅሰፍተ እግዚአብሔር። ጠል ከፀምር አለመውረዱ እስኤልን ያለማጥፋቱ። በዳርና በዳር መውረዱ አሕዛብን የማጥፋቱ ምሳሌ ነው። ፍጻሜው ግን ፀምር መውረዱ ጌታ በእመቤታችን የማደሩ ምሳሌ ነው። በዳርና በዳር አለመውረዱ ጌታ በሌሎች ሴቶች ያለማደሩ። ፀምር ይቡስ መሆኑ እመቤታቸን እንበለ ዘርዕ የመውለዷ ምሳሌ ነው። በዳርና በዳር መውረዱ ሌሎች ሴቶች በዘር በሩካቤ የመወለዳቸው ምሳሌ። ጌዴዎን ማለት ጽንዕ ጽንዐ እግዚአብሔር ኀያል ማለት ነው። ትውልዱ ምድረ ርስት ከገቡት ከመንፈቀ ነገደ ምናሴ ነው። ሙዳየ ዕፍረት ወቀርነ ቅብዕ ዘሳሙኤል ። የሽቱ ዕቃ። ሳሙኤል ነገሥታቱን እየቀባ የሚያነግሥበት ሽቱ ያኖረባት ቀንድ አንቺ ነሽ። ሐተታ፦ ዐራቱን ሽቱ አምስተኛ ዘይት አጣፍጠው ያኖሩበታል። ኋላ ክህነት የሚገባው ከቤተ ሌዊ የተወለደ ቀኝ ቀኝ አካሉን ተቀብቶ ክህነት። መንግሥት የሚገባው ከቤተ ይሁዳ የተወለደ ቀኝ ቀኝ አካሉን ተቀብቶ መንግሥትን ገንዘብ ደርጋል። ጌታም ከእመቤታችን ዐራቱን ባሕርያት አምስተኛ ባሕርየ ነፍስን ነሥቶ ክህነትን መንግሥትን ገንዘብ አድርጓልና። አንድም ይህ ቅብዕ ሠያሚነት ያለው ነው። ጌታም ሠያሜ ነገሥት ሠያሜ ካህናት ነውና። ሳሙኤል ማለት ሰምዐኒ እግዚአብሔር ማለት ነው። ትውልዱ ከነገደ ሌዊ ነው። ሥርው ዘዕሤይ እንተ ባቲ ተመክሐ ። ወኢይኵን ዘእንበለ ሥርው እንዲል። ዕሤይ ደስ የተሰኘባት ልጅ አንች ነሽ። ወእምከመ አድማዕነ ንትሜካህ እንዲል። አንድም የተመካባት የዕሤይ ልጅ አንች ነሽ። ሐተታ ፦ የተመካበት ምክንያት አላታወቀም። አንድም በሷ እድናለሁ ብሎ ይመካባት ነበርና። ዕሤይ ማለት ዕሴት ዕሡይ ርኩብ ማለት ነው። ትውልዱ ከነገደ ይሁዳ ነው። ወሠረገላተ አሚናዳብ ። የአሚናዳብ ሠረገላ አንቺ ነሽ። እመቤታችንን በበጎ ነገር ይመስላታልና። ሐተታ፦ የዚህ የአሚናዳብ ሠረገላ ልዝብ ፈጣን ነው። እመቤታችንም በንጽሕና በቅድስና የለዘበች ናት። ፈጣን እንደ ሆነ እሱዋንም አፍጣኒተ ፈድኤት ማርያም በጊዜ ምንዳቤ ወዐፀባ ይላታልና። ትውልዱ ነገዱ አልታወቅም።
284
17
ተናግዶቱ ለአብርሃም ። አብርሃምን ባራቱ ማዕዘን በሄደ ጊዜ ዘመድ ዘመድ የምታሰኝው አንች ነሽ። አንድም ሃይማኖቱ ሲል ነው። ለአብርሃም የሃይማኖቱን ዋጋ የምታሰጭው አንች ነሽ። የአብርሃም አባት ታራ ጣዖት እየጠረበ ይሸጥ ነበረ። ከዕለታት ባንዳቸው አብርሃምን ይህን ጣዖት ሽጠህ ና ብሎ ሰደደው። ከጎዳና ሲደርስ ራበኝ አብላኝ ጠማኝ አጠጣኝ አለው ዝም አለው። ይህም ባይሆን አጫውተኝ አለው ዝም አለው። ከገበያ ሄዶ ዐይን ሳለው የማያይ እጅ ሳለው የማይጨበጥ እግር ሳለው የማይሄድ አምላክ አለላችሁ ግዙ አላቸው። የሚያውቁት አብርሃም አእምሮውን አጣ ብለው ዘበቱበት። የማያውቁት እሱ ያዋረደውን ምን ዋጋ ያዋጣልኝ ብሎ ይዞት መጣ ብለው ነገሩን እንደ ዋዛ አዩበት። ተመልሶ ሄዶ ከጎዳና ሲደርስ ራበኝ አብላኝ ጠማኝ አጠጣኝ ይህም ባይሆን አጫውተኝ አለው። ዝም አለው። ከዚህ በኋላ እኔ ባላውቅ ነው እንጂ በዕለተ ሠሉስ የተፈጠርህ ዕንጨት አይደለህምን ብሎ ከላይ ከታች ደንጊያ አድርጎ ቀጠቀጠው። አምላኩን ቀጥቅጧልና አምላክ ይሻል። ነፋስ ረቂቅ ነው የሚሄድበት የሚመጣበት አይታወቅም። ኀያል ነው ባሕር ይገሥፃል ዛፍ ያናውጣል ይህን ላምልክ ብሎ አሰበ። ቢመረምር ዐረፍት ደፈር ሲከለክልው አይቶ ሕፀፅ አገኘበት። እሳት ረቂቅ ነው አይያዝም። ኀያል ነው እርጥቡን ደረቁን አንድ አድርጎ ያቃጥላል ይህን ላምልክ ብሎ አሰበ። ቢመረምረው እርሻ ገደል ሲከለክለው ሕፀፅ አገኘበት። ውሃ ሲያጠፋው አየ። ውሃ ቢጠመቁት ያነጻል ቢጠጡት ትኩሳት ያበርዳል ይህን ላምልክ ብሎ አሰበ። ቢመረምር ባፈር በሣር ሲገደብ ከወሰዱት ቦታ ሲሄድ ሕፀፅ አገኘበት። ፀሐይ ብርሃኑ ጽንፍ እስከ ጽንፍ ይደርሳል። የበረደውን ያሞቃል የረጠበውን ያደርቃል ይህን ላምልክ ብሎ አሰበ። መዓልትና ሌሊት ሲፈራረቀው ደመና ሲጋርደው አይቶ አምላከ ፀሐይ ተናበበኒ አለ። በዚህ ጊዜ ጌታ ሃይማኖቱን ለማጽናት አብርሃም አብርሃም ፃእ እምብሔርከ ወተፈለጥ እምአዝማዲከ ብሎታል። አብርሃም እንዲህ አድርጎ በፀሐይ ተመራምሮ ፈጠሪውን ዐውቋል። ጌታም እንዲህ ብሎ መልሶለታልና የሃይማኖቱን ዋጋ የምታሰጭው አንቺ ነሽ አለ። አንድም ተአንግዶቱ ይላል። ለአብርሃም የእንግድነቱን ዋጋ የምታሰጭው አንቺ ነሽ። ወደ ፈርዖን ወደ አቤሜሌክ በሄደ ጊዜ ዘመድ ዘመድ ብለው ተቀብለውታል። ይህ መሆኑ ጌታ እመቤታችን በባሕርዩ ቢኖሩ ነውና። አንድም ተአንግዶቱ ይላል። ለአብርሃም እንግዳ የመቀበሉን ዋጋ የምታሰጭው አንቺ ነሽ። ታሪክ፦ አብርሃም ቤቱን ከተመሳቀለ ጎዳና ሠርቶ የወጣ የወረደውን ያለፈ ያገደመውን ሲቀበል ይኖር ነበር። ሰይጣን ተመቅኝቶ ራሱን ገምሶ ደሙን አፍሶ አጥንቱን ከስክሶ ከጎዳና ቆይቶ ወዴት ትሄላችሁ ይላቸዋል። ከአብርሃም ቤት ይሉታል። የወትሮ አብርሃም መሰላችሁን እኔ ያበላኛል ያጠጣኛል ብዬ ብሄድ ራሴን ገምሶ ደሜን አፍሶ አጥንቴን ከስክሶ ልብሴንም ገፎ ሰደደኝ ይላቸዋል። እንዲህ እያለ ሦስት ቀን እንግዳ ከለከለበት። አብርሃምም ማዕደ እግዚአብሔርን ያለ ምስክር እመገባለሁ ብሎ ግብር ሳያገባ ሦስት ቀን አደረ። በሦስተኛው ቀን ሥላሴ በአምሳለ ዕደው ተቀምጠው አገኛቸው። ገሀሡ አጋዕዝትየ ቤተ ገብርክሙ ጌቶች ከቤት ገብታችሁ ዕረፉ አላቸው። ደክሞናልና ካላዘልከን አይሆንም አሉት። አንዱን አዝሎ ገባ ሁለቱ በግብር አምልካዊ ገብተው ተገኝተዋል። እሱም ሦስት እንደ ሆኑ ዐውቆ ሳራን ሦስት መስፈሪያ ዱቄት አአምጥተሽ አንድ አድርገሽ ጋግሪ አላት እንዳዘዛት አድርጋለች። ከዚህ በኋላ ወይፈን አርዶላቸዋል። አቅረበ ሎሙ ሐሊበ ወዕቋነ ወዕጒለ ላህም እንዲል። ዕርጎ አንቋሊት አቅርቦላቸው ተመግበዋል። መብላቸውም እሳት ቅቤ በላ እንደ ማለት ነው ይህም ምሳሌ ነው። ሦስት መስፈሪያ የሦስትነት አንድ መሆኑ ያንድነት ምሳሌ ነው። በዚህ ጊዜ ልደተ ይስሐቅን ነግረውት ሲሄዱ ከሦስቱ አንዱ አመ ከመ ዮም እገብ ኀቤከ ብሎ ተስፋውን ነግሮታልና ለአብርሃም እንግዳ የመቀበሉን ዋጋ የምታሰጭው አንቺ ነሽ አለ። አብርሃም ማለት አበ ብዙኃን ማለት ነው ነገዱም ከነገደ ሴም ነው። መዓዛሁ ለይስሐቅ ። ለይስሐቅ የመሠዋዕቱን ዋጋ የምታሰጭው አንቺ ነሽ። ጌታ ብየ ዐርክ በዲበ ምድር አብርሃም ፈቁርየ አለ። መላእክት ሰምተው ወኮና ቃላት በሰማያት እንዲል። አብርሃም ፍቁረ እግዚአብሔር አብርሃም ዐርከ እግዚአብሔር ብለው አመሰገኑ። ሰይጣን ይህን ሰምቶ ለምቀኝነት አያርፍምና ወዳጄ ወዳጄ ትለዋለህ እንጂ ካረጀ በኋላ የወለደው የሚወደው አንድ ልጅ አለው ሠዋልኝ ብትለው አይሠዋልህም አለው። ጌታም የአብርሃም ጽድቁን የሰይጣን ሐሰቱን ለመግለጥ ከዋለበት ሳለ አብርሃም አብርሃም ሡዕ ሊተ ይስሐቅሃ ወልደከ ዘታፈቅር አለው። ስምዖን ስምዖን አልዓዛር አልዓዛር ማርታ ማርታ እንዲል። ለእብራውያን ደጊመ ቃለ ልማዳቸው ነው። አንድም የሥጋህ የነፍስህ ፈጣሪ ነኝ ሲል። አንድም ለአጽንዖተ ነገር ነው። ለናቱ የነገርኋት እንደ ሆነ ይዋል ይደር ትለኛለች ታዳክመኛለች ብሎ ከውሎው እንዳለ በቅሎውን አስጭኖ ለሁለቱ ባሮቹ ዕንጨቱን አሸክሞ እሳቱን ሾተሉን ለልጁ አሲዞ ሦስት ቀን ገሰግሷል። ሦስት ተራሮች አሉ ከመካከለኛው የብርሃን ዓላማ ተተክሎ ይጠቅሰዋል። አነ ወወልድየ ሰጊደነ ንገብዕ ብላቴኖቹን እኔና ልጄ እጅ ነሥተን እንመለሳለን እናንተ ከዚህ ቆዩ አላቸው። ለጊዜው ለማታለል ነው ፍጻሜው ግን ተገልጾለት ትንቢት ተናገረ። ሾተሉን እሳቱነ እሱ ይዞ ዕንጨቱን ለልጁ አሸክሞ ወጡ። ከማእከለ ደብር ሲደርሱ አባቴ አንተ እሳት ሾተል ይዘሃል እኔ ዕንጨቱን ተሸክሜያለሁ። መሥዋዕቱ ወዴት አለ አለው። በግዑሰ ኀበ ሀሎ ለሊሁ የአምር ወልድየ። ልጄ መሥዋዕቱስ ያለበትን ባለቤቱ ያውቃል እንውጣ አለው ወጡ። ደንጊያውን ጸፈጸፈ ዕንጨቱን ረበረበ እርሱም አባቴ ሁሉን አዘጋጀህ መሥዋእቱ ወዴት አለ እኔን ልትሠዋኝ ነው መሰለኝ አለው። የምትጎዳበት አይደለም እንጂ አወን አለው። እንኪያስ አንተ አረጋዊ ነህ እኔ ህፃን ነኝና እንዳላስቸግርህ አስቀድምህ እጅ እግሬን እሰረኝ አለው። እጁን እግሩን አሰረው። ፊቴን አይተህ ራርተህ ትተኸኝ ከፈጣሪህ ጋር እንዳትጣላ ደፍተህ አስተኛኝ አለው ወአስከቦ በከብዱ ይላል ደፍቶ አስተኛው። ሾተሉን ከአንገቱ አሳርፎ ስለት አሰማለሁ ብሎ እስባለሁ ሲል ቁርጥ ኅሊናውን አይቶ ተው ዓለም የሚድን በኃያሉ በእኔ ልጅ ደም ነው እንጂ በደካማው በአንተ ልጅ ደም አይደልምና ተው አለው። ሽቅብ ቢያይ በግዕ በእፀሳቤቅ ተይዞ ወረደለት እሱን ፈትቶ ያንን ተቀብሎ ሠውቷል። ይስሐቅ የዚህ ዓለም በግዕ የጌታ ምሣሌ። በግዕ ቤዛ ይስሐቅ ሆኖ እንደተሠዋ ጌታም ቤዛ ዓለም ሆኖ ተሠውቷል። አንድም ይስሐቅ የመለኮት በግዕ የትስብእት ሾተል የሥልጣነ እግዚአብሔር ስለት የሕማም የሞት ምሳሌ። ስለት ከበግዕ እንጂ ከይስሐቅ እንዳልደረሰ በተዋሕዶ ሲሆን ነው እንጂ በተዐቅቦ ሲሆን ሕማም ሞት ከትስብእት እንጂ ከመለኮት ላለመድረሱ ምሳሌ። ኅሊና አብርሃም የመቃብር ይስሐቅ በኅሊና አብርሃም በተሠዋ በሦስተኛው ቀን ድኗል። ጌታም ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት በከርሠ መቃብር ኑሮ ተነሥቷልና። እሳት የመንፈስ ቅዱስ ዕንጨት የመስቀል። ፪ ባሮች የ፪ ወንበዶች ምሳሌ ሲሄድ ፫ ቀን ሲመጣ ፫ ቀን ነው። የ፮ ቀን ሰሙነ ሕማማት ምሳሌ። በግዕ የተገኘ ከአብርሃም መንጋ ነው ያሉ እንደ ሆነ ከቤተ አብርሃም ሰው መሆኑን ያጠይቃል። እምኀበ አልቦ ነው ያሉ እንደ ሆነ ቀዳማዊ ልደቱ አለመመርሩን መናገር ነው። ይስሐቅ ማለት ትፍሥሕት ማለት ነው። ወሰዋስዊሁ ለያዕቆብ ።
337
18
እስመ ኃረያ እግዚአብሔር ለጽዮን ወአብደራ ከመ ትኲኖ ማኅደሮ ዛቲ ይእቲ ምዕራፍየ ለዓለም.እግዚአብሔር ጽዮንን መርጧታልና፥ ማደሪያውም ትሆነው ዘንድ ወድዷታልና፥ እንዲህ ብሎ። ይህች ለዘላለም ማረፊያ
እስመ ኃረያ እግዚአብሔር ለጽዮን ወአብደራ ከመ ትኲኖ ማኅደሮ ዛቲ ይእቲ ምዕራፍየ ለዓለም.እግዚአብሔር ጽዮንን መርጧታልና፥ ማደሪያውም ትሆነው ዘንድ ወድዷታልና፥ እንዲህ ብሎ። ይህች ለዘላለም ማረፊያዬ ናት፤ መርጫታለሁና በዚህች አድራለሁ። መዝሙር (Psalm)፦ 131(132) : 13―14
337
19
መ ዝ ሙ ር ዘ ሰ ን በ ት ✍️ንዒ ርግብየ ሠናይት — ውቢቱ ርግብ ሆይ ነዪ ​ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ንዒ ርግብየ ሠናይት፤ ርግብየ ይቤላ በእንተ አርምሞታ፣ ንዒ ርግብየ ሠናይት ወይቤላ መልአክ ተፈሥሒ ፍሥሕት ቡርክት አንቲ እምአንስት ንዒ ርግብየ ሠናይት፤ መንፈስ ቅዱስ ይመጽእ ላዕሌኪ ወኃይለ ልዑል ይጼልለኪ፤ ንዒ ርግብየ ሠናይት ጽርሕ ንጽሕት አግዓዚት፣ ሠመያ ማኅደረ መለኮት፣ ከመ ፍሕሶ ቀይሕ ከናፍርኪ ከመ ዘውገ ማዕነቅ ኅንብርትኪ፣ ንዒ ርግብየ ሠናይት መላትሕኪ ከመ ወይን፣ ወጼና እንፍኪ እምኵሉ አፈው፣ ንዒ ርግብየ ሠናይት ወትወፅእ እምግበበ አናብስት፤ እምታዕካ ዘነገሥት እምቅደመ ሃይማኖት፣ ንዒ ርግብየ ሠናይት ኵለንታኪ ሠናይት፤ አልብኪ ነውር፤ ወኢምንትኒ በላዕሌኪ ንዒ ርግብየ ሠናይት፤ ንዒ ርግብየ ሠናይት። ✍️​ውቢቱ ርግብ ሆይ ነዪ (ተመለሽ)። የውሃ ባለቤት በመሆኗና በጸጥታዋ (በስክነቷ) የተነሣ "ርግቤ" አላት። እርስዋ በእውነት ቅድስተ ቅዱሳን የሚሏት የዕፀ ጳጦስ (የማይነደው ቍጥቋጥ) ምሳሌ ናት። ​መልአኩም "ደስ ይበልሽ፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽና ደስ የተሰኘሽ ነሽ" አላት። "መንፈስ ቅዱስ ወዳንቺ ይመጣል፤ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል" አላት። ንጹህ ግንብ፣ ነጻ አውጪ (አግአዚት) የሆነችውን የመለኮት ማደሪያ ብሎ ጠራት። ​ከናፍሮችሽ እንደ ቀይ ሐር (ቀይ ሉል) ናቸው፤ እምብርቴሽን (ኅንብርትሽ) እንደ ጌጥ ማዕነቅ ነው። ጉንጮችሽ እንደ ወይን ፍሬ (ወይን ጠጅ) ናቸው፤ የአፍንጫሽ ሽታ ከማንኛውም ሽቱ ይበልጣል። ከአንበሶች ጉርብትና (ዋሻ)፣ ከንጉሥ መኖሪያ (ታዕካ)፣ ከሃይማኖት ፊት ትወጣለች። ​ሁለንተናሽ ውብ ነው፤ በእነርሱ ላይ ምንም ነውር (ጉድለት) የለብሽም። ውቢቱ ርግብ ሆይ ነዪ። ❖ ምስባክ፦ ክነፈ ርግብ በብሩር ዘግቡር። ወገበዋቲሃኒ በሐመልማለ ወርቅ። አመ አዘዘ ሰማያዊ ንጉሥ ላዕሌሃ። በከብር እንደ ተሠሩ እንደ ርግብ ክንፎች፥ በቅጠልያ ወርቅም እንደ ተለበጡ ላባዎችዋ ትሆናላችሁ። ሰማያዊ ንጉሥ በላይዋ ባዘዘ ጊዜ፥ [መዝ ፷፯ ፥ ፲፫ / 67(68) ፥ 13]
537
20
«ከመረጥኳቸው ጋር ቃል ኪዳኔን አደርጋለሁ» ባለው መሠረት ጌታ ከእመቤታችን ጋር ብዙ ቃል ኪዳን አድርጓል፡፡ እርሷ የተመረጠች ብቻ ሳትሆን ከተመረጡትም ሁሉ የተመረጠች ናትና፡፡ ከቅዱሳን ሁሉ እመቤታችን ድንግል ማርያም በሁሉም ረገድ ስለምትበልጥ ከተሰጣቸውም የምሕረት ቃል ኪዳን ለሷ የተሰጣት ኪዳን ኪዳነ ምሕረት ተብሎ ተለይቶ ይታወቃል፤ ማለትም ትጠራበታለች፤ ኪዳነ ምሕረት ትባላለች፡፡ የምሕረት ቃል ኪዳን ሁሉ በጎ እንድንሠራ የሚያበረታታ ነው፡፡ ፈጣሪ ስለ ፈራጅነቱና ስለ መሐሪነቱ ሲናገር «በሚጠሉኝ እስከ ሦስተኛና አራተኛ ትውልድ ድረስ የአባቶችን ኃጢአት በልጆች ላይ የማመጣ ለሚወዱኝ ትእዛዜን ለሚጠብቁ እስከ ሺሕ ትውልድ ድረስ ምሕረትን የማደርግ እኔ እግዚአብሔር አምላክህ ቀናተኛ አምላክ ነኝ፡፡» ይላል፡፡ /ዘጸ.20÷2-6/ ሰላም ለአዕዛንኪ እለ ተበስራ ኪዳነ፤ እምአፈ ፈጣሪ ወልድኪ ዘባሕርየኪ ተከድነ፤ አምሕለኪ ማርያም ከመ ኢታርእይኒ ደይነ፤ እንበለ ምግባር ባሕቱ እመ ኢይጸድቅ አነ፤ ቦኑ ለከንቱ ኪዳንኪ ኮነ። "እንበለ ምግባር ባሕቱ እመ ኢይጸድቅ አነ። ቦኑ ለከንቱ ኪዳንኪ ኮነ" ለጽድቅ የሚያበቃ በጎ ምግባር ባይኖረኝም እንኳ የገሀነምን ደጅ እንዳታሳይኝ እማልድሻለሁ። ቃል ኪዳንሽ እንዲሁ በከንቱ አይደለምና። ክነፈ ርግብ በብሩር ዘግቡር ወገበዋቲሃኒ በሐመልማለ ወርቅ አንቲ ምሥራቅ ወወልድኪ ፀሐየ ጽድቅ አማን ኪዳንኪ ኢየሐልቅ በብር የተሠራች የርግብ ክንፍ ጐኖቿ በወርቅ ዐመልማሎ የተሸለመች አንቺ በምሥራቅ ስትመሰዪ ልጅሽ የእውነት ፀሐይ ነው፡፡ በእውነት ቃል ኪዳንሽ አያልቅም፡፡ ቸሩ ልጇ ከበረከተ ኪዳኗ አይለየን። በዓሉንም የሰላም፣ የፍቅርና የበረከት ያድርግልን ‼
510