SHEMA📖✝
ማርቆስ 12 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ❝²⁹ ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፦ ከትእዛዛቱ ሁሉ ፊተኛይቱ፦ እስራኤል ሆይ፥ ስማ( #Shema o Israel) ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው፥ ³⁰ አንተም በፍጹም ልብህ በፍጹምም ነፍስህ በፍጹምም አሳብህ በፍጹምም ኃይልህ ጌታ አምላክህን ውደድ የምትል ናት። ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት።❞ #we #proclaim #the #sweet #life #with #God.
Show more308Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-230 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
በጥሞና አድምጡት🎧
🗣ገጣሚ ሕሊና ደሳለኝ
ትሁቱ እረኛዬ፣ታጋሹ እረኛዬ
ደግ ልብህ ሲያርም የግልገሉን ክፋት
በአንዲት እንባ ያጥባል የዘላለም ጥፋት
የትናንቱ ብኩን ፣የትናንቱ ትቢያ
የቸርነትህ በትር አንግሦ ያጀገነኝ
የፍቅርህ ምስክር የምህረትህ ቋንቋ
#ደቀ_መዝሙርህ_ነኝ!!
°°°°°•♥•°°°°°
መልካም ሰንበት
⚜Shabbat Shalom⚜
@Dawitdeva7
Repost from SHEMA📖✝
#ምልክት_ያለው_ይድናል
“ደሙም ባላችሁበት ቤቶች #ምልክት ይሆንላችኋል፤ ደሙንም ባየሁ ጊዜ ከእናንተ አልፋለሁ፤ እኔም የግብፅን አገር በመታሁ ጊዜ መቅሰፍቱ ለጥፋት አይመጣባችሁም።”
— ዘጸአት 12፥13
ምልክት አለብኝ የእየሱስ ደም
🙌🙌🙌😍😍😍
@Dawitdeva7
¯¯¯#ምሥጢር_እነግራችኃለሁ/ I shew you a Myestry/
💎👇💎
1ኛ ቆሮንቶስ 15
⁵¹-⁵² #እነሆ፥ #አንድ #ምሥጢር_እነግራችኋለሁ፤ ሁላችን አናንቀላፋም ነገር ግን የኋለኛው መለከት ሲነፋ ሁላችን በድንገት #በቅጽበተ_ዓይን #እንለወጣለን፤ መለከት ይነፋልና ሙታንም የማይበሰብሱ ሆነው ይነሣሉ እኛም እንለወጣለን።
⁵³ ይህ የሚበሰብሰው የማይበሰብሰውን ሊለብስ ይህም የሚሞተው የማይሞተውን ሊለብስ ይገባዋልና።
…
⁵⁸ ስለዚህ፥ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ ድካማችሁ በጌታ ከንቱ እንዳይሆን አውቃችኋልና የምትደላደሉ፥ የማትነቃነቁም፥ የጌታም ሥራ ሁልጊዜ የሚበዛላችሁ ሁኑ።
@Dawitdeva7
" #My_heart_is_yours "
Amazing passion song
😍😍😍
Yes Jesus, my heart is yours, take it all🙌🙌
“My beloved is mine, and #I_am_his: he feedeth among the lilies.”
— Songs of Solomon 2:16 (KJV)
@Dawitdeva7
💎👇
"Faith never knows where it is being led, but it loves and knows the One who is leading it. "
👤Oswald Chambers
Can you say this to your Lord and saviour Jesus; 👇
" I love the way you hold me, Led me all the time and I will follow, Surrendering all🧎"
Amenn 🙌
Have a blessed day!
@Dawitdeva7
የሕይወት ሥነ ሥርዓት (Discipline of life)
💎💎👇💎💎
5- ሥራህን ተግተህ ሥራ
☑ሥራ እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ከሰጠው ጸጋ አንዱ ነው ። ሥራ ርግማን ሳይሆን በረከት ነው ። አዳም ሲፈጠር ገነትን እንዲያበጃትና እንዲንከባከባትም ነው (ዘፍ. 2 ፡ 15) ። ደግሞም ምድርን ግዛ ተብሎ ሥልጣን ሲሰጠው ትልቅ ሥራ እንደ ተሰጠው ያሳያል ። ምድር ለእርሱ ስጦታው ናትና እንደ ራሱ ገንዘብ አድርጎ መንከባከብ ይገባዋል ። ከበደል በኋላ ግን “በፊትህ ወዝ እንጀራን ትበላለህ” ተባለ (ዘፍ. 3 ፡ 19) ። ይህ ሥራ ርግማን መሆኑን የሚያሳይ ሳይሆን ከበደል በኋላ አዳም ብዙ ልፋት ጥቂት ትርፍ ይገጥመዋል ማለት ነው ። በዚህም ምክንያት እርካታ እያጣ እንደሚመጣ የሚገልጥ ነው ። እያንዳንዱ ሰው ለሚኖርበት ዓለም የሚያደርገው አስተዋጽኦ አለው ። ሰው የሁለት ዓለም ፍጡር ነውና ለምድር ኑሮው መሥራት ፣ ለሰማዩ ኑሮ ማመን አለበት ። ሥራ በረከት ነው ።
📌በአእምሮ ላይ የሚነሣውን የሰይጣንን ፈተና ለማሸነፍ ሥራና ጸሎት ሁለቱ መሣሪያ መሆናቸውን አባቶች ተናግረዋል ። ሥራ የፈታ አእምሮ ለሰይጣን መናገሻ ከተማ ነው ። ነገረኛ ሰዎች ሥራ የማይሠሩ ወይም አጉል ትርፍ የሚያገኙ ወገኖች ናቸው ። በሥራ የተጠመደ ነገርን ይሸሻል ። ንጹሕ አእምሮ ለማግኘት ሥራ መሥራት መልካም ነው ። ተነፋፍቆ ለመገናኘት ሥራ አስፈላጊ ነው ። የሰው ልጆች ያለማቋረጥ ከተያዩ ግንኙነቱ ይደፈርሳል ። በዓለም ላይ በተነሣው የቅርቡ ወረርሽኝ ሰው ሁሉ እቤቱ እስረኛ ሁኖ ነበር ። ብዙ ትዳር ፈርሷል ። ብዙ ግንኙነት ተበላሽቷል ። ወንጀሎች ተፈጽመዋል ። ሰዎች ለአእምሮ ጭንቀት ተዳርገዋል ። እስካሁን ድረስም ጠባሳው እያወከ ይገኛል ። ሥራ በረከት ነው ። አሁንም በቤታቸው ተቀምጠው የሚሠሩ ሰዎችን በተለያየ ዓለም እንሰማለን ። የሰይጣን ትልቁ ውጊያው ሰውና ሰው እንዳይገናኝ ማድረግ ነው ። ሥራ ያገናኛል ። ሥራ ከቤታችን ውጭ ሲሆን ለብሰን እንወጣለን ። ለራሳችን እንክብካቤ እናደርጋለን ። ከሰዎች ጋር በማውራት ብቻ ነጻ አእምሮ እናገኛለን ። አአምሮአችን ትልቅ ኃይል የተሸከመ ነውና ማረፊያ ያገኛል ። ማረፊያ ያላገኘ አእምሮ ዓለምን ለማጥፋት አቅም አለው ።
📌ሥራው አለቃ የሆነለት ሰው ውጤታማ ነው ። ሥራ ብዙ እንቅልፍን የሚጠላ በመሆኑ ሠራተኛ ሰው ማልዶ መነሣት አለበት ። ሥራ አካላዊ ፣ ሥነ ልቡናዊና መንፈሳዊ በረከትን ይሰጣል ። አካላችን የሚጠነክረው በሥራ ነው ። የምድር ተግዳሮትን የሚቋቋሙ ሰዎች ሠራተኛ ሰዎች ናቸው ። የዓለም መንግሥታት ትልቅ ስኬታቸውን የሚለኩት የሥራ ዕድልን በመፍጠራቸው ነው ። በአጭር ቋንቋ እግዚአብሔር ሰነፍ ልጅ የለውምና ሥራን መውደድ ይገባናል ። የሐዋርያው ቃልም ቁርጥ ያለ ነው፡- “ሊሠራ የማይወድ አይብላ ።” (2ተሰ. 3 ፡ 10) ። ስብሰባ ፣ ኮሚቴ ፣ ቃለ ጉባዔ የሚሉ ሰዎች አብዛኛዎቹ ሥራ የማይወዱ ፣ ቁጭ ብለው መነዛነዝ የሚያፈቅሩ ናቸው ። ሕይወትን ቀለል አድርጎ መኖር የሚቻለው በስብሰባ ሳይሆን በሥራ ነው ። ጨካኝ መንግሥታት ሕዝባቸውን በስብሰባ ያደነዝዛሉ ። መሪ የሆኑት ደግሞ ሕዝባቸውን ለሥራ ያነሣሣሉ ። ሕዝብን በሥራ መወጠር ከሁከትም ይጋርዳል ።
📌አዎ ሥራህን በታማኝነት ሥራ ። ጸልየህ ያገኘኸውን ሥራ በትጋት አለመሥራት እግዚአብሔርን ማሳዘን ነው ። ሥራ ታማኝነትና ትጋት ይፈልጋል ። ታማኝነቱ ትጋት ከሌለው ፣ ትጋቱ ታማኝነት ከሌለው አደገኛ ነው ። ሥራህ የሃይማኖትህ ቦታ አይደለም ። በሥራህ ቦታ ሥነ ምግባርን እንጂ አምልኮን ልፈጽም አትበል ። ጉቦን ተጸየፍ ። ደመወዝህ እንዲባረክ ጸልይ ። ጉቦ ያለህንም ይዞት የሚሄድ ፣ ልጆችህንም የሚያሳብድ ነው ። ጉበኞች የብዙዎችን እንባና ደም ተሸክመው ይሄዳሉ ። ሰው ወዶና ፈቅዶ እንጂ ተጨንቆ የሚሰጠን ነገር ርግማን የሚያመጣ ነው ። የሥራ ሰዓትህን አክብር ። ደመወዝህ አነስተኛ በመሆኑ ባለጉዳዩን ማንገላታት አይገባህም ። ባለጉዳይህን ፣ ያንተን ሙያ የሚፈልገውን እግዚአብሔርን እንደምታገለግል አድርገህ አገልግለው ። የሙያህ ባለቤት እግዚአብሔር ነው ። በሙያህ ሰውን አታጉላላ ። አንድ ቀን ይህ አእምሮህ ላይሠራ ይችላል ። እጆችህ ላይሠሩ ይችላሉ ። በሚያልፈው አካልህ የማያልፍ ሥራ ሥራበት ። በሙያ ሰውን ማስደሰት መታደል ነው ። ካንተ የሆነ ምንም ነገር የለም ።
📌ሥራ የምትሠራው አሥራትህንም ለማውጣት ነው ። ባንተ የሥራ ትርፍ የእግዚአብሔር ቤት ይገነባል ። ብዙዎች ወንጌል ይሰማሉ ። ልጆችህ ጠግበው ያድራሉ ። ትዳርህ አይታወክም ። የብዙ ትዳር ሁከትም የገቢ ማነስ ነው ። ሥራ ትልቅና ትንሽ የለውም ። በምድር ላይ የሚያሳፍረው ቆሻሻ መጥረግ ሳይሆን ቆሻሻ ጠባይ መያዝ ነው ። ጌታችን ለእኛ አርአያ ለመሆን አናጢነትን ሠርቷል ። ቅዱሳን ሁሉ ሥራቸውን በትጋት ሲሠሩ ለሰማያዊ ግዳጅ የተጠሩ ናቸው ። ትጉ ሠራተኛ ትጉህ ሐዋርያ ሊሆን ይጠራል ። ትጋት ተወዳጅ ያደርጋል ። ለክብር ለመታጨት ያበቃል ።
እግዚአብሔር የእጅህን ሥራ ይባርክ !
ይቀጥላል
✍ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
@Dawitdeva7
A blessing Worship🔥
“ጻድቅ ግን በእምነት ይኖራል ወደ ኋላም ቢያፈገፍግ፥ ነፍሴ በእርሱ ደስ አይላትም።”
— ዕብራውያን 10፥38
Happy Sabath
⚜ Shabat Shalom⚜
@Dawitdeva7
#ለትልቅ_ምክንያት_መኖር
(Live for the greater cause)
“አልሞትም #በሕይወት_እኖራለሁ እንጂ፥ #የእግዚአብሔርንም_ሥራ #እናገራለሁ።”
— መዝሙር 118፥17
📌የመኖር ምክንያታችን ስላልሞትን ወይንም እስትንፉሳችን መቀጠሉ ብቻ ከሆነ ቆም ብለን ማሰብ አለብን።
📌 ዳዊት 'አልሞትም ' ያለው ሞትን ስለሚፈራ ወይንም መኖርን ስለሚወድ ሳይሆን ሊኖርለት የተገባ አንድ #ትልቅ_ምክንያት ስላለ ነው ።እርሱም " #የእግዚያብሄርን_ስራ_መናገር " ብሎ በህይወቱ ያወጀው ዓላማው ነው።
📌ለትልቅ ምክንያት የሚኖርን ሰው ጥቂቱ ና ጊዜያዊ መከራ አያስቆመውም። ህይወቱም በትናንሽ አስተሳሰቦች አይያዝም።
📌 የማይገባውን ምህረት፣ፀጋ እና ፍቅር እንደተቀበለ የተረዳ ሰው በህይወት ሳለ ማድረግ የሚገባውን ከማድረግ ወደ ኃላ አይልም። ሁለንተናውን ለሰጠን ጌታ ምናችንን እንከለክለዋለን??
2ኛ ቆሮ 5
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹³ እብዶች ብንሆን፥ ለእግዚአብሔር ነው፤ ባለ አእምሮዎች ብንሆን፥ ለእናንተ ነው።
¹⁴ ይህን ስለቆረጥን #የክርስቶስ #ፍቅር_ግድ_ይለናልና፤ አንዱ ስለ ሁሉ ሞተ፤ እንግዲያስ ሁሉ ሞቱ፤
¹⁵ #በሕይወትም_ያሉት ስለ እነርሱ ለሞተውና ለተነሣው እንጂ ወደ ፊት #ለራሳቸው_እንዳይኖሩ ስለ ሁሉ ሞተ።
ፀጋ ከሁላችን ጋር ይሁንን🙌🙌
❤️❤️❤️
🌤🌤 መልካም ሠንበት🌤🌤
( Shabat shalom )
@Dawitdeva7
Wise Counsel of Paul 💎
👇👇👇👇
“ስለዚህ፥ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ ድካማችሁ በጌታ ከንቱ እንዳይሆን አውቃችኋልና #የምትደላደሉ፥ #የማትነቃነቁም፥ #የጌታም_ሥራ_ሁልጊዜ_የሚበዛላችሁ_ሁኑ።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 15፥58
ሰማያዊው ህይወት የገባው ሰው፦
☑የተደላደለ ነው፤ ምንም ነገር አያስደንቀውም ከጌታው ክብር ውጪ
☑የማይነቃነቅ ነው ፤በምንም አይነት የህይወት ወጀብ ውስጥ
☑የጌታ ስራ ሁሌ የበዛለት ታታሪ ነው፤ ብድራቱን ትኩር ብሎ ይመለከታልና።
ፀጋ ይብዛልን!🙌
@Dawitdeva7
ጋሽ ገዛኽኝ ሙሴ🎧
ሁሉም እንደዘበት ሊጠፋ ሁሉም እንደዘበት ሊያልፍ ነው
በጌታ በእየሱስ የፀና ፅዩን ሊገባ ነው
ሊያርፍ ነው!🔥
••••♥••••
“ይህም ሊሆን ሲጀምር ቤዛችሁ ቀርቦአልና አሻቅባችሁ ራሳችሁን አንሡ።”
— ሉቃስ 21፥28
@Dawitdeva7