en
Feedback
ዘመድኩን በቀለ

ዘመድኩን በቀለ

Open in Telegram

የዘመድኩን በቀለ ጦሟሩን እንደወረደ የሚለቀቅበት ስለሆነ ሁላችሁም ዘመዴን አድናቂዎች ተቀላቀሉት ጆይን አድርጉት ሸሩን ትታችሁ ሼር አድርጉት

Show more
3 220
Subscribers
No data24 hours
-97 days
-7630 days
Posts Archive
"ያደረ ርእሰ አንቀጽ" "…በትናንትናው ርእሰ አንቀጻችን እስራኤል እግዚአብሔርን በመበደላቸውን፣ በበደላቸውም፣ በኃጢአታቸውም ምክንያት እግዚአብሔር ለጠላት አሳልፎ እንደሰጣቸው። ጠላትም በላያቸው ላይ እንደሰለጠነባቸው፣ የዘሩት እህል፣ ያረቡት ከብት ሳይቀር በጠላት እጅ እንዲወድም እግዚአብሔር እንደተዋቸው አይተናል። ከመጨነቅ፣ ከመስጋታቸው የተነሳ በአደባባይ ላይ በነፋስ እየታገዘ የሚወቃውን ስንዴ ጌዴዎን በወይን መጥመቂያ ዋሻ፣ ወይ ገንዳ ውስጥ ይወቃ እንደነበርም ተመልክተናል። በዚሁ አንጻር እንደ ሀገር ኢትዮጵያ፣ እንደ ሕዝብ በተለይ ዐማራውና ኦርቶዶክሱ በዘመናችን እየደረሰባቸው ያለው መከራ እና ግፍ ከዚያ ዘመን ጋር ማነጻጸር ተገቢ ነው። ለምን ላልተማሩ ጨካኞች አሳልፎ ፈጣሪ ሰጠን ብሎ የጠየቀ ሰው መልሱን ያገኛል። የኃጢአታችን፣ የክፋታችን፣ የጥጋባችን መልስ ነው። ይሄን አምኖ መቀበል ያስፈልጋል። እግዚአብሔር የነጠቀህን ፀጋ ለማስመለስ መጀመሪያ በቅድሚያ ንስሀ መግባት ያስፈልጋል። ከግል እስከ ሕዝብ ነው ንስሀ የሚያስፈልገው። ያኔ እግዚአብሔር መልአኩን ይልካል፣ አንድ ሰው አስነሥቶ ሥራውን መሥራት ይጀምራል። ይሄንን ነው ትናንት የተመለከትነው። "…ጌዴዎን ከሚልዮን እስራኤላዊ መካከል ነው የተመረጠው። መራጩ ራሱ እግዚአብሔር ነው። የምርጫ መስፈርቱንም የሚያውቀው ራሱ እግዚአብሔር ነው። የድምጽ ብልጫ፣ ዲፕሎማና ዲግሪ፣ የሥራ ልምድ አይጠይቅም እግዚአብሔር ሲመርጥህ፣ መታዘዘህን፣ ቅንነትህን፣ እምነትህን ብቻ ነው የሚያየው እግዚአብሔር ሲመርጥ። ኃጢአተኛም ልትሆን ሁላ ትችላለህ ሲመርጥህ መጨረሻህን አይቶ ነው የሚመርጥህ። አንዳንዴ እግዚአብሔር ከመረጠህ በጉልበት በኃይል ሁላ ይልክሃል። የአንተ ያደርግሃል። ጫት እየቃምክ፣ ዝሙት ላይ ተጥደህ፣ ሌባ፣ ወንበዴ ሆነህ፣ ቀማኛ ዘራፊ ሆነህ፣ አጫሽ ሆዳም ሁላ ሆነህ ሰው የሚያየውን ኮተትህን ትቶ የተደበቀ የውስጥ ቅንነትህን ተመልክቶ አንተን በኃይል አጥቦና ጨምቆ አራግፎ አስጥቶህ አድርቆም አጣጥፎ ሽቶ ቀብቶህ አርከፍክፎብህ ቅዱስ አድርጎ ይጠቀምብሃል። ቅዱስ ጳውሎስን ያህል አሳዳጅ ሰው አልነበረም። እግዚአብሔር ሲመርጠው ግን ቅንአቱን አይቶ ተመልክቶ ይሄን ያልተገባ ቅናት ለእኔ እንዲቀና ባደርገው እኮ ለዓለሙ ሁሉ ብርሃን ይሆናል በማለት በደማስቆ ሜዳ ላይ አጠናግሮ አይኑን አጥፍቶ እውር አድርጎ ጨለማ ካለበሰው በኋላ ነው አይኑን መልሶ አብርቶለት ስሙንም ከሳውል ወደ ጳውሎስ ቀይሮለት ቅዱስ ጳውሎስን የዓለም ብርሃን ያደረገው። እግዚአብሔር እንዲህ ነው። አሁን ይሄን መልእክቴን እያነበብክ፣ እያነበብሽ ያለሽው ወንድሜና እህቴ እስቲ ለአንድ ደቂቃ እዚህ ጋር ማንበቡን አቁሙና ራሳችሁን ተመልከቱ፣ ለአንድ ደቂቃ ማንነታችሁን ፈትሹ። አዎ ኃጢአተኛ ነን። ነገር ግን በውስጣችን የሆነች ብርሃን ነገር አለች። እግዚአብሔር 99% የረከሰውን ማንነታችንን አይደለም የሚያየው 1% ቷን በውስጣችን ያለችዋን ብርሃን ነው የሚመለከተው። እግዚአብሔር ብርሃን ስለሆነ ጨለማን አያውቅም። አያይምም። ያቺን ብርሃን አብዝቶ ጨለማውን ከላያችን ማስወገድ ይችላልና ወደ እግዚአብሔር እንቅረብ። አንተ ሀገር መምራት፣ ለሕዝብ ሁሉ ብርሃን የሆነ ሥራ ለመሥራት ከእገሌና እገሌ አታንስም። ይሄን እመን። "…ትናንት ጌዴዎን ሲመረጥ እግዚአብሔርን የምር መርጠኸኝ ከሆነ ምለክት ስጠኝ፣ ሰይጣንም ሰውም ሊያደርገው የማይችል ምልክት ስጠኝ ብሎ ምልክት መጠየቁን አይተናል። ሦስቴም ጠየቀው ሦስቴም እግዚአብሔር ሳይሰለች የተጠየቀውን ፈጸመለት። የመጀመሪያው ያለ ክብሪት እሳት ወርዶ ጌዴዎን ያቀረበውን መስዋእት ተቀበለው። ሁለተኛም ጊዜ ፀምር አቅርቦ የበግ ቆዳ ማለት ነው። አንደዜ ዝናብ በምድሪቱ ላይ ሁላ ይዝነብ ዝናቡ ግን ፀምሯ ላይ ሳይዘንብ መሬቱ በዝናብ ይራስ አለው። እንደጠየቀው ተደረገለት፣ የመጨረሻ ብሎ ነገር በሦስት ይፀናልና ዝናብ ይዝነብ ምድር ሁሉ ይራስ ፀምሪቱ ላይ ግን አይዝነብ አለው። እግዚአብሔርም እንደተጠየቀው አደረገ። የጌዴዎንም እምነቱ 100% ሆነ። አሁን አምላኬ እንደሆንክ አረጋግጫለሁ አይደለም ከምድያማውያንን ለምን ከኔቶ ጋር አይሆንም አንተ ከእኔ ጋር ከሆንክ አሸናፊው እኔ ነኝ ብሎ ፈቃደኛ መሆኑን አይተናል። ተመልክተናል። "…ከዚያ በኋላ እንግዲህ እግዚአብሔርም የመረጠውን ሰው ይፈጽምለት ዘንድ የሚፈልገው ነገር አለና ያን ፍላጎቱን በተራው መጠየቅ አለበት። እንደዚያው ነው ያደረገው። ሄደህ በአባትህ ቤት፣ በአንተ ሰፈር፣ መንደር ያለውን የጣኦት መሰዊያ ሁሉ አፍርስ አለው። ጥያቄው ቀድሞ እግዚአብሔርና ጌዴዎን ሳይተማመኑ፣ የጌዴዎንም እምነት በእግዚአብሔር ላይ 100% ባይሆን ኖሮ ለጌዴዎን ይሄን የአምላክ ትእዛዝ መቀበል ሊከብደው ይችል ነበር ብለን ብንገምት አይፈረድብንም። ነገር ግን ጌዴዎንና እግዚአብሔር ተፈታትነው ስለጨረሱ ጌዴዎን አሁን የታዘዘውን ከመፈጸም በቀር ሌላ ምክንያት ማቅረብ አይችልም። ሰው ምን ይለኛል፣ የቀበሌው ሊቀመንበርስ፣ መቶ አለቃ ማንትስዬ፣ የደኅንነት ኃላፊውስ? እነ ሳንቾ፣ እነ ቾምቤ፣ እነ ጋንጩሬ፣ እነ ሳቡሬስ ቢሆኑ ሄጵ ቢሉብኝ፣ ማለት አይችልም። ከሥጋ አስተሳሰብ ወጥቷላ። ፍርድቤት ብቀርብስ፣ ሚሊሻ ወታደሩን ጁላ ቢልክብኝስ ብሎ ለማሰብ እንኳ አላመነታም የታዘዘውን አደረገ። ሕዝቡም ለጊዜው ሄጵ አለ። ነገሩ በረደ። እንዲያውም በድፍረት ይሄን ያደረገው ጌዴዎን ይልቅ ጠላት መጥቷል ተከተሉኝ እንውጋ ብሎ ሲል ሳያቅማሙ ተከተሉት። ምክንያቱም እግዚአብሔር መሪ አድርጎ፣ ቀብቶ ካስነሣህ የአንተ ሥራ መከተል ብቻ ነው። "…ጌዴዎን ከተመረጠ በኋላ ስሙ ነው የተቀየረው። ከጌዴዎን ወደ ይሩበኣል ተቀየረ። ጣኦታትን ባደቀቀበት የጀግንነት ስም ተሰጠው። በማን? በእግዚአብሔር። ይሄ ደግሞ እግዚአብሔር ከጥንት ጀምሮ ሲሠራበት የቆየ ልማድ ነው። ያእቆብን እስራኤል፣ ሳውልን ጳውሎስ፣ ስምኦንን ጴጥሮስ ሺ ምንተ ሺ ልንጠራ እንችላለን። የቀደመ ማንነታችን ከነ መታሰቢያ ስሙ ነው የሚቀየረው። ዱርዬ፣ ዘማዊ፣ ሰካራም፣ ወንበዴ፣ አጫሽ፣ ቃሚ፣ ዘራፊ፣ ቀማኛ ወዘተረፈ የነበረው ስምህ ወዲያው ነው የሚቀየረው። ከዚያ በኋላ ሰዎች በሚያውቁህ ስምህ ሳይሆን እግዚአብሔር በሚያውቀው በአዲሱ ማንነትህ ነው የምትጠራው። የምትታወቀውም። እግዚአብሔር በሚከብርበት፣ ሕዝቡም ሁሉ በሚያርፍበት ስምህ ትጠራለህ። ስምህ ከተቀየረ በኋላ በቀጥታ ወደ ውጊያ ነው የምትገባው። እያንዳንዱ ሰው የራሱ ሰልፍ፣ የራሱ ጦርነት አለው። የራሱ የፍልሚያ ሜዳም አለው። ትጥቅ የለኝም፣ ልምድ የለኝም፣ መሳሪያ የለኝም፣ ስንቅና ትጥቅ የለኝም። ምዕራባውያን ካልደገፉኝ፣ አረቦቹ እና እነ ቻይና ካላገዙኝ፣ አውሮጳ ኅብረት ካልረዳኝ ብሎ ነገር የለም። መዝመት ነው በሕይወት ሰልፍ ሁሉ። ጌዴዎን ስንዴ የሚወቃበት ዱላ ይዞ ነው የወጣው፣ የተመረጠውም። ያለህን ይዘህ ነው የምትዘምተው። ብእር ያለህ በብእርህ፣ ሌላም ሌላም ባለህ ሙያ፣ ዕውቀት ሁሉ ነው ዘመቻው። እስከዚህ ድረስ በትናንትናው ዕለት ርእሰ አንቀጻችን ላይ አይተናል። ዛሬ የምናየው ደግሞ የጦሩን አሰላለፍና የወታደሮች ምርጫ ነው። ተከተሉኝ።👇① ✍✍✍

መልካም… "…የትላንትናው የጀመርኩላችሁን ርእሰ አንቀጽ ገና አሁን ጽፌ ጨረስኩ። እንዴት እንደደከምኩ አትጠይቁኝ። ደስ እያለኝ ነው የጨረስኩት። "…እህሳ እናንተስ በወንድ አቅሜ በትበት ብዬ ያዘጋጀሁ
መልካም… "…የትላንትናው የጀመርኩላችሁን ርእሰ አንቀጽ ገና አሁን ጽፌ ጨረስኩ። እንዴት እንደደከምኩ አትጠይቁኝ። ደስ እያለኝ ነው የጨረስኩት። "…እህሳ እናንተስ በወንድ አቅሜ በትበት ብዬ ያዘጋጀሁላችሁን ርእሰ አንቀጽ አጣጥማችሁ ለመብላት፣ ዝግጁ ናችሁ? ረዘመ አጠረ ብሎ ነገር የለም። ቁርጥምጥም አድርጋችሁ፣ ጣታችሁን እስክትልሱ ድረስ ሁሉንም አጣጥማችሁ መብላት ነው። "…እኔ ጦማሩን ያዘጋጀሁት ለእኔ ወዳጆች ነው። በእኔ የተከፋችሁ፣ የተበሳጫችሁ፣ የተናደዳችሁ ሸንጎና እስኳድ፣ ግንቦቴና ኦሮሙማ፣ ወየንቲቲ፣ መኔ ወሄም ታገሱ። ሥነ ሥርዓትም ያዙ። እምቢ ካላችሁ በ BLOCK ሰይፌ ወገብ ዛላህን ቆምጬ ነው የማሰናብትህ። ሰው አትረብሽ። ብልግናህን በቤትህ። ምድረ ወመኔ ሰምተሃል። • አላችሁ አይደል? ዝግጁ…?

"…ምክራቸውን ጥልቅ አድርገው ከእግዚአብሔር ለሚሰውሩ፥ ሥራቸውንም በጨለማ ውስጥ አድርገው ማን ያየናል? ወይስ ማን ያውቀናል? ለሚሉ ወዮላቸው! ኢሳ 29፥15 "…እንደምን አደራችሁ? "…እንደምን አረ
"…ምክራቸውን ጥልቅ አድርገው ከእግዚአብሔር ለሚሰውሩ፥ ሥራቸውንም በጨለማ ውስጥ አድርገው ማን ያየናል? ወይስ ማን ያውቀናል? ለሚሉ ወዮላቸው! ኢሳ 29፥15  "…እንደምን አደራችሁ? "…እንደምን አረፈዳችሁ? "…እንደምን ዋላችሁ? "…እንደምን አመሻችሁ? "…እግዚአብሔር ይመስገን ብቻ ‼

ወይ ፍንክች…! "…አይደለም የጠቀስካቸው ለምን የተባበሩት መንግሥታት አያወያይህም። በዐማራ ጉዳይ የሚቀየር ነገር የለም። የጎንደር አንድ መሆን፣ የወሎም ወደ አንድ መምጣት፣ የሸዋም ጠንክሮ መውጣት፣
ወይ ፍንክች…! "…አይደለም የጠቀስካቸው ለምን የተባበሩት መንግሥታት አያወያይህም። በዐማራ ጉዳይ የሚቀየር ነገር የለም። የጎንደር አንድ መሆን፣ የወሎም ወደ አንድ መምጣት፣ የሸዋም ጠንክሮ መውጣት፣ የአስረስ መዓረይ ሴራ በጎጃም መክሸፍ ነው እንዲህ መርዝ እንደበላች ውሻ የሚያራውጣችሁ። ወፍ የለም። "…እኔ ጎጃም ገብቼ ከዐማራ ፋኖ በጎጃም ከነቁት፣ ከባነኑት ጋር ሆኜ አስረስ መዓረይና ክሊኮቹን ማንቁርታቸውን አንቄ ፀረ ዐማራ መርዛቸውን አስተፋቸዋለሁ፣ ጎጃም ከሊቃውንቱ ሀገር ከላይ እታች፣ ከምሥራቅ ምዕራብ፣ ከሰሜን ደቡብ አምነሸነሽበታለሁ፣ አዳሜና ሔዋኔ ዓይኑን እኔ ላይ ተክሎ ለሃጩን ሲያዝረበርብብኝ ሌሎቹ ሥራ ላይ ይበረታሉ። "…እኔ ዘመድኩን ነቀለ፣ አመድኩን ነቀለ፣ መራታው፣ እብድ፣ ቀውስ፣ ጃል ቆቱ ወዲ አስገዶም አዳሜና ሔዋኔ እኔ ላይ እኚኚ እንዲሉብኝ አደርጋለሁ። አስጓራቸዋለሁም። ሌሎቻችሁ ሥራችሁን ወጥራችሁ ቀሪ የቤት ሥራችሁን በሚገባ ሥሩ። እኔ እንደ ጦስ ዶሮ በአገው ሸኔ በቅባት ስቀጠቀጥላችሁ እናንተ አምልጡ። እንደሻማ ቀልጬም ቢሆን የዐማራን ትግል ከልቡሠ ሥጋ ጋኔሎች እከላከልላቸዋለሁ። የጎጃም ፋኖን የተቆጣጠረውን የፓስተሮች መዓት እተናነቃቸዋለሁ። ቀልድ የለም። "…የእስላም ቃልቻ በዚህ ግባ በዚህ ውጣ የሚለው መከራው፣ በሪፐብሊካን ጋርድ የሚጠበቀው እስክድር፣ ከአስረስ መዓረይ ጋር የሚሞዳሞዱት ማስረሻና ጌታ አስራደ፣ ምስኪኑና በጌታቸው አሰፋ ምክትል ተጠርንፎ ጠባቂዎቹ ሲቀሩ ሠራዊቱ ሁሉ ወደ ምሬ ወዳጆ የገባ የፈለሰበት ሙሀባው፣ በአበበ በላው የሚዘወረው የማከብረው ፋኖ ደረጀ በላይ ተደራድረው ዐማራን ሲወክሉ፣ ከዚያ አበበ በለው ባህል ሚንስቴር፣ ሀብታሙ አያሌው ማስታወቂያ ሚንስቴር ሊኮን። ሊበላ። እግርህን ብላ። • ጃል ቆቱ ወዲ አስገዶም ነኝ ከዲማ ጊዮርጊስ።

መልካም… "…ይሄን 20 ሺ ሰው አንብቦት 46 ሰው ብቻ ጓ 😡 ብው ያለበትን የዛሬውን የዕለተ አርብ ርእሰ አንቀጻችንን በመቀጠል እናንተ ደግሞ አስተያየት ትሰጡበት ዘንድ የአስተያየት መስጫ ሰንዱቁን
መልካም… "…ይሄን 20 ሺ ሰው አንብቦት 46 ሰው ብቻ ጓ 😡 ብው ያለበትን የዛሬውን የዕለተ አርብ ርእሰ አንቀጻችንን በመቀጠል እናንተ ደግሞ አስተያየት ትሰጡበት ዘንድ የአስተያየት መስጫ ሰንዱቁን ክፍት ወደማድረግ እሄዳለሁን። "…የሚገርም ነው። እጅግ ድንቅም ነው። መቼም ሁላችሁ እንደምታወረቁት እኔ ሲያመኝ ጤና የለኝምና ምናቸውን እንደነካሁት እንጃባቴልኝ ምድረ አገው ሸንጎ አገው ሸኔ ቅባቴ ሁላ እንደ አዲስ ቀፎው እንደተነካበት ንብ ተበትነው በየፔጁ እርርር ዝዝዝ እያሉብኝ ነው ውለው ያመሹት። እኔምለው በጣም ነው እንዴ ግን የነካኋቸው? ወይ ዕዳዬ። 😂 "…የእኔን ፔጅ አታንብቡ መንጋቸውን ያስጠነቅቁና እነርሱ ግን እኔው በፔጄ ላይ የጻፍኩትን ራሳቸው መልሰው ለሕዝባቸው በትንተና መልክ ሲያቀርቡት ሳይ ወይ አንተ የዐማራ አምላክ መቼም ሥራህ እኮ እጅግ ድንቅ እኮ በማለት እዚያው ዲማ ጊዮርጊስ ጸሎቴን በርከክ ብዬ እያቀረብኩ እገኛለሁ።🙏🙏🙏 …ፎቶዬ ነሽ ምኔ ቀራቸው? ስሜማ በየቦታው በዝቶ በስቅታ ልሞት ነው። ደና ናቸው ግን? 😂 "…እናም ተቀስፋችሁ ከቤቴ ተባርራችሁ ሼክና ቄስ ልካችሁ ከማለቃቀሳችሁ በፊት በጨዋ ደንብ ተንፒሱ… እንደ እነ የሸበሉ፣ ዊኪሊክ ብልጥ ሁኑ። እነሱ እናንተን ሂዱ ተሳደቡ እያሉ እናንተን አስቀስፈው እነርሱ እኔ ቤት ሲኮመኩሙኝ ነው የሚውሉት? በይዘዌ 😂 አልማዝ ባለጭራና የቲክቶክ ተንታኞቿ በሙሉ ስታይል ነው። ባይዘዌ 😂… ባይዘዌ የሳታለይት ቴሌቭዥናችንን ጉዳይም ሰሞኑን በይፋ ቦርድ አቋቁመን ወደ ሥራ እንገባለን። እስከዚያው በጨዋ ደንብ ተንፒሱ። • 1…2…3…ጀምሩ ✍✍✍

👆⑥✍✍✍ "…ታሪኩ ጣፋጭ ነው ይቀጥላል። ጌዴዎን እግዚአብሔር ያዘዘውን ፈጸመ። በቤተሰቡ፣ በጎረቤቶቹ፣ በወዳጅ ዘመዶቹ ጭምር ነው የተጠላው። ለእግዚአብሔር ብሎ፣ እግዚአብሔር ያዘዘውን ተቀበሎ። ሰምቶና አድምጦ ትእዛዙን ፈጸመ። ቀጥሎ የሚመጣው በስሜ ትጠላላችሁ፣ ያሳድዱአችኋል፣ ወደ ፍርድ አደባባይም ያወጧችኋል ነው። ከዚያ ቆራጥ ቤተሰብ ሲገኝ ደግሞ "ልጅህን አሳርፈው፣ ተው በለው፣ ከዕድሩ ከማኅበር ከፅዋው እንዳትወጣ፣ ተው በለው ቀባሪ እንዳታጣ ብለው ሲመጡ ዞር በሉ የሚል ስታገኙ አሸወይና ነው የሚሆነው። አሁን የዓለሙ ሁሉ ችግር እውነት ይዛችሁ ስትነሱ ወዳጅ፣ ዘመድ፣ ጓደኛ ነን የሚሉ በሚስት፣ በአባትና በልጅ ይመጡባችሁና "ኧረ ተው፣ ተው ግን፣ ተው ሰው እየሸሸህ ነው፣ ሰብስክራይበር እየቀነሰ ነው ይሏችኋል። እጅ ከሰጠህ አለቀልህ። ልብህን አድምጠህ ከእውነት ጋር ቀጥል። እውነት እግዚአብሔር ነው። እግዚአብሔር ደግሞ አሸናፊ ነው። አለቀ። "…ምድያማውያንም አማሌቃውያንም ሁሉ የምሥራቅም ሰዎች አንድ ሆነው ተሰበሰቡ፥ ዮርዳኖስንም ተሻገሩ፥ በኢይዝራኤልም ሸለቆ ሰፈሩ።" ሊጀመር ነው ጦርነቱ። ምድያማውያንም አማሌቃውያንም ሁሉ የምሥራቅም ሰዎች አንድ ሆነው ተሰበሰቡ ነው የሚለው። ከወዱህ ወገን የተመረጠው አንድ ሰው ብቻ ነው። እሱም ቢሆን ገና ከፈጣሪው ጋር እየተደራደረ ነው። እየተፈታተኑ ነው። እነርሱ ሠራዊት ካደራጁ ቆዩ። ጦርና ጋሻ፣ ፈረሰኛውም ለጉድ ነው። እዚህ ደግሞ ገና ተደብቆ በወይን መጥመቂያ ውስጥ ስንዴ የሚወቃ ጌዴዎን የተባለ ወጣት ነው ያለው። ጠላት እየቀረበ ነው። ዮርዳኖስንም ተሻገረው፥ በኢይዝራኤልም ሸለቆ ሰፈረዋል። እናም የመረጠው እግዚአብሔር፣ አሸናፊው የእግዚአብሔርም መንፈስ በጌዴዎን ገባበት፥ እርሱም ቀንደ መለከቱን ነፋ፤ የአቢዔዝርም ሰዎች ተጠርተው በኋላው ተከተሉት። ወደ ምናሴም ነገድ ሁሉ መልክተኞችን ሰደደ እነርሱም ደግሞ ተጠርተው በኋላው ተከተሉት፤ መልክተኞችንም ወደ አሴርና ወደ ዛብሎን ወደ ንፍታሌምም ሰደደ፥ እነርሱም ሊገናኙአቸው ወጡ። ለምን የእግዚአብሔር መንፈስ ስላደረበት፣ የጠራው ሁሉ ይከተላዋል፣ ያምነዋል። ከዚህ በፊት የጦር መሪ ያልነበረውን ጌዴዎንን ሁሉ እንዲያምነው፣ እንዲከተለው አደረገ እግዚአብሔር። እንቀጥል። "…ጌዴዎን ይሄን ሁሉ እግዚአብሔር አሟልቶለት፣ ስሙን ቀይሮለት፣ ጣኦታትን አጥፍቶ፣ መስዋእቱንም በልቶለት፣ ተቀብሎትም ግን ደግሞ አሁንም የመጨረሻ አምላኬ አንተ መሆንህን ላረጋግጥ። አንደዜ ልፈትንህ። በሰው አእምሮ የማይቻል ጥያቄ ልጠይቅህ፣ እሱን ከመለስክልኝ በቃ በደስታ ወደላከኸኝ ቦታ፣ ሥፍራ እሄዳለሁ ብሎ ጠየቀው። ለመነውም። ጌዴዎንም እግዚአብሔርን፡— እንደ ተናገርህ የእስራኤልን ልጆች በእኔ እጅ ታድን እንደ ሆነ፥ እነሆ፥ በአውድማው ላይ የተባዘተ የበግ ጠጕር አኖራለሁ፤ በጠጕሩ ብቻ ላይ ጠል ቢሆን በምድሩም ሁሉ ደረቅ ቢሆን፥ እንደ ተናገርህ የእስራኤልን ልጆች በእኔ እጅ እንድታድናቸው አውቃለሁ፡ አለ። እንዲሁም ሆነ፤ በነጋውም ማልዶ ተነሣ፥ ጠጕሩንም ጨመቀው፥ ከጠጕሩም የተጨመቀው ጠል ቆሬ ሙሉ ውኃ ሆነ። የጌድዮን እምነቱ 90% ሆነ። ጥርጣሬ እየተፋቀለትም ሄደ። በዚህ ሳያበቃ አሁንም እግዚአብሔርን ሌላ ጥያቄ ጠየቀው። "ጌዴዎንም እግዚአብሔርን፡— እኔ ይህን አንድ ጊዜ ስናገር አትቈጣኝ፤ እኔ ይህን አንድ ጊዜ በጠጕሩ፥ እባክህ፥ ልፈትን፤ አሁንም በጠጕሩ ብቻ ላይ ደረቅ ይሁን፥ በምድሩም ሁሉ ላይ ጠል ይሁን፡ አለው። እግዚአብሔርም በዚያ ሌሊት እንዲሁ አደረገ፤ በጠጕሩ ብቻ ላይ ደረቅ ነበረ፥ በምድሩም ሁሉ ላይ ጠል ነበረ። የጌዴዎንም እምነት 100% ሆነ። አበቃ ወደፊት ብቻ… "…ከዚያ ምን ሆነ…? ከዚያማ የሆነው ነገ በዕለተ ቅዳሚት ሰንበት ጠዋት 1ሺ ሰው እግዚአብሔር ይመስገን ብሎ በጽሑፍ ካመሰገነ በኋላ ጣፋጩን ታሪክ ከሕይወታችን ጋር እያዛመድን እተርክላችኋለሁ። • ድል ለዐማራ ፋኖ…! • ድል ለተገፋው ለዐማራ ሕዝብ…! • ይደፈርሳል… ግን ደግሞ ይጠራል…✊ ••• ሻሎም…!  ሰላም…! ዘመድኩን በቀለ ነኝ። አሸበርቲው/አስነቀልቲው ጥር 16/2017 ዓም ከራየን ወንዝ ማዶ።

👆⑤✍✍✍"…ከዚያ ወደ ምርጫ ገባ እግዚአብሔር። ለዚህ ሕዝብ ማንን ልላክ? ብሎም ወደ ምርጫ ገባ። ምርጫ ሲመጣ እንግዲ መስፈርቱን የሚያውቀው መራጩ ነው። እናም መራጩ እግዚአብሔር ይመርጥ ዘንድ የላከውን የእግዚአብሔር መልአክ ሂድ ወደ ተባለበት ስፍራ ላከው ይለናል መጽሐፍ ቅዱስ። "የእግዚአብሔርም መልአክ መጥቶ በዖፍራ ባለችው ለአቢዔዝራዊው ለኢዮአስ በነበረችው በአድባሩ ዛፍ በታች ተቀመጠ፤ ልጁም ጌዴዎን ከምድያማውያን ለመሸሸግ በወይን መጥመቂያው ውስጥ ስንዴ ይወቃ ነበር። የእግዚአብሔርም መልአክ ለእርሱ ተገልጦ፡— አንተ ጽኑዕ ኃያል ሰው፥ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነው፡ አለው። ተገኘ ተመራጩ። ያውም እኮ ከጠላት ተደብቆ ወይን ከሚጠምቅበት ዋሻ ድረስ ገብቶ ነው የመረጠው። መልአኩም መልእክተኛ ነውና ይሄን በእግዚአብሔር የተመረጠ ሰው ተገልጦለት ነው "አንተ ጽኑዕ ኃያል ሰው፥ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነው ብሎ ያለው። ደስ ሲል መታደል እኮ ነው በእግዚአብሔር ተመርጦ በመልአኩ አንደበት "አንተ ጽኑዕ ኃያል ሰው፥ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነው" መባል። አወይ መታደል። "…ጌዴዎንም፡— ጌታዬ ሆይ፥ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ከሆነ ይህ ነገር ሁሉ ለምን ደረሰብን? አባቶቻችንስ፡— እግዚአብሔር ከግብፅ አውጥቶናል፡ ብለው ይነግሩን የነበረ ተአምራቱ ወዴት አለ? ወዴት አለ? አሁን ግን እግዚአብሔር ትቶናል፥ በምድያማውያንም እጅ አሳልፎ ሰጥቶናል፡ አለው ይለናል። አንተ እንደምትለው እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ካለ፣ አባቶቻችንም ይነግሩን የነበረው አስደማሚ ታሪክ ሁላ የት አለ? ተአምራቱስ ወዴት አለ? እግዚአብሔር በእውነት አለ? ካለ ታዲያ የት አለ? ይሄ ሁላ መከራ፣ ግፍ ሲደርስብን ቢኖር ኖሮ ይታደገን ነበር። አባቶቻችን ይነግሩን የነበረው ሁሉ ተረት እየመሰለን ነው። የት አለ ብሎ ከመልአኩ ጋር ሙግት ጀመረ። ልብ በሉ ይሄ ሁላ የሚደረገው ሚልዮን እስራኤላውያን በሞሉበት ሀገር፣ ካህናቱ በመቅደስ መሰዊያው ፊት እያመሰገኑ፣ እየዘመሩ ባለበት ሀገር ነው ተደብቆ ስንዴ ከሚወቃ አንድ ጎልማሳ ወጣት ጋር እግዚአብሔር መልአኩን ልኮ የሚያዘጋጀው። "…ይቀጥልናም "እግዚአብሔርም ወደ እርሱ ዘወር ብሎ፡—በዚህ በጕልበትህ ሂድ፥ እስራኤልንም ከምድያም እጅ አድን፤ እነሆ፥ ልኬሃለሁ፡ አለው። ይለናል።  እርሱም፡— ጌታ ሆይ፥ እስራኤልን በምን አድናለሁ? ወገኔ ከምናሴ ነገድ ከሁሉ ይልቅ የተጠቃ ነው፤ እኔም በአባቴ ቤት የሁሉ ታናሽ ነኝ፡ አለው። እኔ እኮ ኦሮሞ ነኝ፣ እኔ እኮ የደሀ ልጅ ነኝ፣ እኔ እኮ ከሚጠቃው ከዐማራ ወገን ነኝ፣ እኔ እኮ እንዲህና እንዲያ ነኝ። እንዴት አድርጌ ነው የቱርክ ድሮን፣ የዱባይ ጥይት፣ የአረብ ቦንብ ከታጠቀ ሠራዊት ጋር የምገጥመው። ኦሮሞ ያሰለጠነውን፣ ትግሬ ለወረራ ያዘጋጀውን እያየህ እንዴት እኔን ትልከኛለህ። እሳት ውስጥ ባዶ እጅህን ግባ እንዴት ትለኛለህ። ትግሬ ዛራ ቲቪ፣ ትግራይ ቲቪ፣ ድምጺ ወያኔ ወዘተ አላቸው፣ ኦሮሞው የትየለሌ የቴሌቭዥን ጣቢያ አለው፣ እስክንድር ከአቅሙ እንኳ ምኒልክ፣ ጣና፣ አዲስ ድምፅ ሚዲያ አለው። አክቲቪስቶቻቸውን የምታያቸው ናቸው። ገንዘቡ በእጃቸው ነው። እንዴት ነው እኔ ስንዴ የምወቃበት ዱላ ብቻ ያለኝ ሰው ከዚህ ሁሉ ጋር የምገጥመው እንዳለ ቁጠሩት። ነገር ግን ይሄ ሁሉ በእግዚአብሔር ዘንድ ምንም ማለት ስላልሆ ጌዲዮንን እንዲህ ይለዋል። "እግዚአብሔርም፡— በእርግጥ ከአንተ ጋር እሆናለሁ፥ ምድያምንም እንደ አንድ ሰው አድርገህ ትመታለህ፡ አለው።" አለቀ። እኔ ከአንተ ጋር እሆናለሁ። ይሄን ሁሉ ግሪሳ ምድያማዊ እንደ አንድ ሰው አድርገህ እንድትመታ አደርግሃለሁ። በእኔ እመን፣ ተማመን አለው። አቤት መታደል። እግዚአብሔር እኮ ከምር ይችላል። እሱ ካለ አለ ነው አበቃ። "…ጌድዮንም ከእግዚአብሔር እርሱም፡— በአንተ ዘንድ ሞገስ ካገኘሁ፥ የምትናገረኝም አንተ እንደ ሆንህ ምልክት አሳየኝ አለው። ማረጋገጫ ስጠኝ። አንተ ቅዱሱ የእግዚአብሔር መልአክም እግዚአብሔርም ካልሆንክስ? ድምፅ ሰማሁ ብዬ፣ መልአክ ተገለጠልኝ ብዬ፣ እግዚአብሔር ተናገረኝ ብዬ ዝም ብዬ ከመሬት ተነሥቼ ብወጣና ጉድ ብሆንስ? እናም ምልክት ስጠኝ። አንተ እግዚአብሔር ከሆንክ ምልክት ስጠኝ። ወደ አንተም እስክመለስ ድረስ፥ ቍርባኔንም አምጥቼ እስካቀርብልህ ድረስ፥ እባክህ፥ ከዚህ አትላወስ፡ አለው። እርሱም፡— እስክትመለስ ድረስ እቆያለሁ፡ አለ።" ጌዴዎን ገባ የፍየሉንም ጠቦት የኢፍ መስፈሪያም ዱቄት የቂጣ እንጎቻ አዘጋጀ፤ ሥጋውን በሌማት አኖረ፥ መረቁንም በምንቸት ውስጥ አደረገ፥ ሁሉንም ይዞ በአድባሩ ዛፍ በታች አቀረበለት። የእግዚአብሔርም መልአክ፡— ሥጋውንና የቂጣውን እንጎቻ ወስደህ በዚህ ድንጋይ ላይ አኑር፥ መረቁንም አፍስስ፡ አለው። እንዲሁም አደረገ። የእግዚአብሔርም መልአክ በእጁ ያለውን የበትሩን ጫፍ ዘርግቶ ሥጋውንና የቂጣውን እንጎቻ አስነካ፤ እሳትም ከድንጋዩ ውስጥ ወጥቶ ሥጋውንና የቂጣውን እንጎቻ በላ። የእግዚአብሔርም መልአክ ከዓይኑ ተሰወረ። ጌዴዎንም የእግዚአብሔር መልአክ እንደ ሆነ አየ። አረጋገጠ ማለት ነው። ወዲያው ጌዴዎንም፡— አቤቱ አምላኬ ሆይ፥ ወዮልኝ፤ የእግዚአብሔርን መልአክ ፊት ለፊት አይቻለሁና፡ ብሎ አለቀሰ፣ ደነገጠ። እኔ ኃጢአተኛው እንዴት በእግዚአብሔር ልመረጥ ቻልኩ ብሎ እሪሪ ወየው ወየውም አለ። "…እግዚአብሔርም፡— ሰላም ለአንተ ይሁን፤ አትፍራ፤ አትሞትም፡ አለው። ጌዴዎንም በዚያ ለእግዚአብሔር መሠዊያ ሠራ፥ ስሙንም፡— እግዚአብሔር ሰላም ብሎ ጠራው። እርሱም እስከ ዛሬ ድረስ ለአቢዔዝራውያን በምትሆነው በዖፍራ አለ። ከእግዚአብሔር ጋር ከተማመኑ በኋላ እግዚአብሔር ደግሞ ጌዲዎንን ያዝዘው፣ ይፈትነውም ጀመር። እግዚአብሔርም በዚያ ሌሊት፡— የአባትህን በሬ፥ ሰባት ዓመት የሆነውን ሁለተኛውን በሬ፥ ውሰድ፥ የአባትህ የሆነውንም የበኣል መሠዊያ አፍርስ፥ በእርሱም ዙሪያ ያለውን የማምለኪያ ዐፀድ ቍረጥ፤ በዚያም ኮረብታ አናት ላይ ለአምላክህ ለእግዚአብሔር መሠዊያ አሳምረህ ሥራ ሁለተኛውንም በሬ ውሰድ፥ በዚያም በቈረጥኸው በማምለኪያ ዐፀዱ እንጨት ላይ የሚቃጠለውን መሥዋዕት አቅርብ፡ አለው። ጌዴዎንም ከባሪያዎቹ አሥር ሰዎችን ወስዶ እግዚአብሔር እንዳለው አደረገ፤ የአባቱን ቤተሰቦች የከተማውንም ሰዎች ስለ ፈራ ይህን በቀን ለማድረግ አልቻለም፥ ነገር ግን በሌሊት አደረገው። የከተማውም ሰዎች ማልደው ተነሡ፥ እነሆም፥ የበኣል መሠዊያ ፈርሶ፥ በዙሪያው ያለውም የማምለኪያ ዐፀድ ተቈርጦ፥ በተሠራውም መሠዊያ ላይ ሁለተኛው በሬ ተሠውቶ አገኙት። "…እርስ በርሳቸውም፡— ይህን ነገር ያደረገ ማን ነው? ተባባሉ። በጠየቁና በመረመሩም ጊዜ፡— ይህን ነገር ያደረገ የኢዮአስ ልጅ ጌዴዎን ነው፡ አሉ። የከተማውም ሰዎች ኢዮአስን፡— የበኣልን መሠዊያ አፍርሶአልና፥ በዙሪያውም ያለውን የማምለኪያ ዐፀድ ቈርጦአልና እንዲሞት ልጅህን አውጣ፡ አሉት። ኢዮአስም እርሱን የተቃወሙትን ሁሉ፡— ለበኣል ትምዋገቱለታላችሁን? ወይስ እርሱን ታድናላችሁን? የሚምዋገትለት ሁሉ እስከ ነገ ይሙት፤ እርሱ አምላክ ከሆነ መሠዊያውን ካፈረሰው ጋር ለራሱ ይምዋገት፡ አላቸው። ስለዚህም በዚያ ቀን፡— መሠዊያውን አፍርሶአልና በኣል ከእርሱ ጋር ይምዋገት ብሎ ጌዴዎንን፡— ይሩበኣል ብሎ ጠራው።👇⑤✍✍✍

👆④✍✍✍ "…400 ሺ የቴሌግራም ተከታታዮችን ይዤ ዋልድባ ገዳም እንዲረዳ ሳደርግ በእርዳታው ላይ የተሳተፉት 1,700 አከባቢ ሰዎች ናቸው። እነዚህ ሰዎች ናቸው 23 ሚልዮን ብር በ3 ቀን ውስጥ አውጥተው ተአምር የሠሩት። ጎንደር ቀበሮ ሜዳ በርዳታ ሥራው የተሳተፉት 700 ምናምን ሰዎች ናቸው። 300 ሺ ሰው ባለበት የቴሌግራም ግሩፕ ውስጥ 7 መቶ ሰው ነው ከ11 ሚልዮን ብር በላይ ወጪ አድርጎ ድሆቹን፣ ስደተኞቹን የታደገለኝ። እናም እኔ በብዛት ሳይሆን በጥራት ነው የማምነው። እስከዛሬም በዚሁ መስመር ነው የመጣሁት። ዓለም የተቀየረው በአንዱ ጌታ ትምህርት፣ በ12ቱ ሓዋርያት፣ በ36ተ ቅዱሳት አንስት፣ በ72ቱ አርድዕት፣ በ120ው ቤተሰብ ነው። አለቀ። አንዱ ቅዱስ ጳውሎስ በመልእክታቱ፣ በጻፈው ደብዳቤ ዓለሙን በወንጌል አማኞች እንዲጥለቀለቅ አድርጎታል። እውነትን ይዘህ ስትቆም፣ ድርቅ ስትል የሚጠብቅህ ምርቃት፣ ሽልማት፣ ሹመት አይደለም። እንደ ጌታ ትሰቀላለህ። እንደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ተወግረህ፣ እንደ ቅዱስ ጳውሎስ ተሰይፈህ፣ እንደ ቅዱስ ጴጥሮስ የቁልቁል ተሰቅለህ፣ እንደ ቅዱስ ጊዮርጊስ በመንኮራኩር ትፈጫታለህ። እውነትን፣ ሃቅን ይዘህ ሽልማት ብሎ ነገር የለም። ዓለም ለሰገደላት ነው ብልጭልጭ የምትሸልመው። ከእውነት ጋር ከተጣበቅክ ጥቂት አጋር ብዙ ጠላት ነው የምታፈራው። ምርጫው የአንተ ነው። "…ወደራሴ ስመለስ ለምሳሌ እኔን አገልግሎትህን ቀጥል፣ እንዳታቋርጥ ብለው በወር ደሞዜን በሉት የሚከፍሉኝ ሰዎች ከሦስት ደርዘን አያልፉም። አይበልጡም። የቤት ኪራዬን ብቻ የምትሸፍነው አንዲት እህቴ ናት። አንተ ታገል፣ በጎደለህ በኩል እንቆማለን ብለውኝ ከጎኔ የቆሙት በጣም ጥቂት ሰዎች ናቸው። እስከአሁን በምንም ከፋን፣ እገሌን ተናገርክብን ብለው ከጎኔ ንቅንቅ ያላሉት፣ ጆኒ፣ ሀረግ፣ ቲጂ፣ ምኒልክ፣ መክሊት፣ ቲጂ ወዘተ ብዬ በስም የምጠራቸው ጥቂት ሰዎች ናቸው። 300 ሺ ሰው በፔጄ ላይ ተወዝፎ ተቀምጦ ፍሬ ያላቸው ግን በጣም ጥቂቶች ናቸው። ይሄ ብቻ አይደለም። እኔ ወዳጆቼና አብረውኝ ይቀጥላሉ የምላቸው በቁጥር ከ2ሺ አይበልጡም። እነርሱም ጠዋት ጠዋት እግዚአብሔር ይመስገን የሚሉቱ ብቻ ናቸው። እነዚህ የልብ ወዳጆቼ ናቸው። ለእኔ እነሱ ብቻ በቂ ናቸው። እነ እድሪስን የመሰሉ ጓዶች ይዤ ውጤት ነው የማመጣው። መንጋው ተወዝፎ ይቆይና ዝም ብሎ አድፍጦ ይቆይና ልክ ጎጡና የራሴ የሚለው አካል ሲነካ ተንቀዥቅዦ ይገባና ይሳደባል፣ ወዲያውም ይቀሰፋል። አለቀ በሌላ ሲም ካርድ ካልመጣ በቀር አለቀለት። እናፍቀዋለሁ። በወሬ ጠኔ ይደፋል። እናም አየጠላኝ የሚከተለኝ፣ እየረገመኝ ከስሬ የማይጠፋ፣ እየበሰጨብኝ ግን ደግሞ ሱስ የሆንኩበት ነው የሚበዛው። እናም እያስነጠስኩት እቀጥላለሁ። መሃይም ነው እርሱን አትስሙት፣ እብድ ነው አትከተሉት እያሉም ከስሬ ግን አይጠፏትም። እኔ ግን እንደ ቃሉ የኢትዮጵያንም፣ የዐማራንም ትንሣኤ በራሴ የሳታላይት ቴሌቭዥን አበሠራለሁ። አከተመ። "…ዲማ ጊዮርጊስ ከመጻሕ መምሩ አጠገብ ተቀምጬ የዛሬ 27 ዓመት አካባቢ ቀሲስ ብርሃኑ ጎበና እንጦጦ ኪዳነ ምህረት የፍልሰታ ጾም ላይ ሲሰብክ ቁጭ ብዬ የሰማሁትንና በአእምሮዬ ጓዳ ያስቀመጥኩትን የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ ነው ላቅርብላችሁ። መንጋ ግሪሳ ቁጭ ብለህ ስማ። ርእሱ "የፈራ የደነገጠም ከገለዓድ ተራራ ተነሥቶ ይመለስ" የሚል ነበር። ታሪኩ የሚገኘው በመጽሐፈ መሳፍንት ምእራፍ 6 እና 7 ላይ ነው። ተከታተሉኝ። "…መጽሐፈ መሳፍንት ም 6 ከቁጥር 1-7 ላይ የኋለኛው ታሪክ መግፍኤ ምክንያት በመዘርዘር ነው የሚጀምረው። የእስራኤልም ልጆች በእግዚአብሔር ፊት ክፉ ሥራ ሠሩ፤ እግዚአብሔርም በምድያም እጅ ሰባት ዓመት አሳልፎ ሰጣቸው። የምድያምም እጅ በእስራኤል ላይ ጠነከረች፤ ከምድያምም የተነሣ የእስራኤል ልጆች በተራራ ላይ ጕድጓድና ዋሻ ምሽግም አበጁ። እስራኤልም ዘር በዘሩ ጊዜ ምድያማውያን አማሌቃውያንም በምሥራቅም የሚኖሩ ሰዎች ይመጡባቸው ነበር፤ በእነርሱም ላይ ይሰፍሩ ነበር፥ እስከ ጋዛም ድረስ የምድሩን ቡቃያ ያጠፉ ነበር፥ ምግብንም ለእስራኤል አይተዉም ነበር፤ በግ ወይም በሬ ወይም አህያ ቢሆን አይተዉም። እንስሶቻቸውንና ድንኳኖቻቸውን ይዘው በብዛት እንደ አንበጣ ሆነው ይመጡ ነበር፤ ለእነርሱና ለግመሎቻቸውም ቍጥር አልነበራቸውም፤ ምድሪቱንም ያጠፉ ዘንድ ይመጡ ነበር። ከምድያምም የተነሣ እስራኤል እጅግ ተጠቁ፤ የእስራኤልም ልጆች ወደ እግዚአብሔር ጮኹ ነው የሚለው። በቃ ሊጠፉ ሲሉ በስተመጨረሻ ነው ፈጣሪ ትዝ ያላቸው። እሱ ደግሞ እንደሰው አይደለም፣ የት ነበርክ እስከዛሬ አይልም፣ በመጣን ጊዜ የሚቀበለን፣ በጠራነው ጊዜ ሁሉ የሚሰማን አባት ነውና የእስራኤልን ጩኸት ልመና ሰምቶ እንዲህ አላቸው። "…እንዲህም ሆነ፤ የእስራኤል ልጆች በምድያም ምክንያት ወደ እግዚአብሔር በጮኹ ጊዜ፥ እግዚአብሔር ወደ እስራኤል ልጆች ነቢይ ላከ፥ እርሱም አለ፡— የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፡— እኔ ከግብፅ ምድር አወጣኋችሁ፥ ከባርነትም ቤት አስለቀቅኋችሁ፤ ከግብፃውያንም እጅ፥ ከሚጋፉአችሁም ሁሉ እጅ አዳንኋችሁ፥ ከፊታችሁም አሳደድኋቸው፥ አገራቸውንም ሰጠኋችሁ፤ እናንተንም፡— እኔ አምላካችሁ እግዚአብሔር ነኝ፤ በምድራቸው የተቀመጣችሁባቸውን የአሞራያውያንን አማልክት አትፍሩ አልኋችሁ። እናንተ ግን ድምፄን አልሰማችሁም። አላቸው። እናንተ ናችሁ የተዋችሁኝ፣ የረሳችሁኝ እንጂ ቀድሞውኑም እኔ አይደለሁም ከቱርካውያንና ከጣሊያናውያን ወረራ፣ ዶጋሊ እስከ አድዋ፣ እስከ ማይጨው፣ ከሱማሌም ወረራ ያዳንኳችሁ እኔ አልነበርኩም ወይ? እኔን ትታችሁ በራሳችሁ መመካት ስትጀምሩ ነው የተውኳችሁ። ሱዳን መሬት ርስታችሁን፣ አልሸባብና ሸአቢያም የደፈሯችሁ እኔን ስለተዋችሁ ነው። ያ ብቻ አይደለም የጉምዝ ቀስተኞች፣ የትግሬ ተዋጊዎች፣ የኦሮሞ ወራሪዎች ልክ ያስገቧችሁ፣ በግሬደር የቀበሯችሁ ከእኔ ፈቀቅ ስላላችሁ ነው። እነ ፓስተር ምስጋናው ዳዊትህን ጣል፣ መስቀልህን አውልቅ፣ ስላሉህ አንተም እነሱን ሰምተህ እኔን ከማመስገን ፈቀቅ አልክ እንደማለት ነው መልእክተኛው የነገራቸው ለእስራኤላውያኑ።👇④✍✍✍

👆③✍✍✍ "…እኔ ዘመዴ ጥጋበኛ ነኝ። እኔ ተከታታዮቼ ራሳቸውን በራሳቸው እያረኩ፣ በውሸት፣ በሀሰት ሰበር ዜና ጆሮአቸው ሰብቶ፣ ወፍሮ፣ ደንድኖ እንዲቀመጥ አልፈቅድም፣ አላደርግምም። የመጣሁበት የመሮጫ ትራክ ሪከርዴ የሚያሳየውም እንደዚያ ነው። እኔ አደባባይ የወጣሁት ሰው እኔን ተከታትሎ፣ እያደነኝ እንዲሰማኝ፣ እንዲያነበኝ፣ እንዲመለከተኝ እንጂ እኔ እሱን እንድከተለው፣ እንድሰማው አይደለም። እኔ ሓሳብ ሻጭ ነኝ። ባለ ሱቅ ነኝ። ደንበኞቼን በር ዘግቼባቸው "ኧረ ዘመዴ ክፈትልንና እንሸምት" እንዲሉኝ፣ በአቦ በሥላሴ፣ በሚካኤል በገብርኤል፣ በማርያም፣ ስሞትልህ ብለው ለምነውኝ በር አደግድገው ከእኔ እንዲሸምቱ እንጂ እኔ ለምኜው እና እባክህ ና ሓሳቤን ግዛኝ ብዬ የምለው፣ የምለምነው። የምማጸነውም ሰው የለም። ተኮልኩሉ፣ ሱቄን እስክከፍት ድንጋይ ወረፋ አስይዞ የሚጠብቀኝ ሕዝብ፣ ቤተሰብ፣ ደንበኛ ነው ያፈራሁት። "…እኔ ደንበኞቼን ልካቸውን ነግሬ ነው የማስተናግዳቸው። ወዳጆቼ ሆነው ከርመው ድንገት ወዳጃቸውን ስነካ የሚያኮርፉ አሉ። "ዘመዴ ሌላውን እንደፈለግክ መምር ግርማን ብቻ አትንካብን፣ እስክንድርን ተውልን" የሚሉ ሁሉ ነክቼባቸው ገሚሱ አኩርፎ ርቋል፣ ገሚሱ ምን ይደረጋል ብሎ ከእኔ ጋር ቀጥሏል። የቤቴን፣ የመንደሬን፣ የሓሳብ መሸጫ ሱቄን ደንብና ሕግ የማያከብር ማንኛውንም ሰው በአለንጋ ዠልጬ ነው ሁለተኛ ድርሽ እንዳይላት ገርፌ የማባርረው። ለሕዝብም፣ ለቤተ ክርስቲያንም ርዳታ እንኳ ለመርዳት የሚመጣውን ሰው መጀመሪያ በደንብ ወልውዬው ነው የሚሰጠው። በጉቦ፣ ደሀ በማስለቀስ፣ በዝሙት፣ ነፍስ አጥፍቶ፣ ሰርቆና ዘርፎ፣ በርበሬ ውስጥ ሸክላ፣ ማሩን ስኳር አቅልጦ፣ በቅቤው ውስጥ ሙዝ፣ በጤፍ ውስጥ አሸዋ፣ በከሰል ውስጥ ድንጋይ ጨምሮ፣ አጭበርብሮ፣ በእንጀራ ውስጥ ጀሶ ከትቶ የስንት ሰው ጤና አቃውሶ ያመጣውን ገንዘብ ሀብቴ ነው ብሎ በኩራት እንዳይሰጥ ነግሬው ነው ንስሀ አስገብቼ የምልከው። ኧረ ዘመዴ ገንዘቡ ይምጣ እንጂ ስለ ሌላው ምን አስጨነቀህ የሚለኝን የሌባ ተቀባይ ቄስ ይሁን ጳጳስም እዚያው ልክ አይደለም ብዬ ተጋፍጬ ነው የምወርደው። እኔ እንዲህ ነኝ። ግን ውጤታማ ነኝ። "…ለስላሳ ሓሳብ እሸጥ በነበርኩ ጊዜ በቴሌግራም ውስጥ 425 ሺ መንጋ ይርመሰመስ ነበር። ቃሪያ በሚጥሚጣ መሸጥ ስጀምር ግርር ብለው መውጣት ልማዳቸው ነው። ኖሩም፣ ሄዱም ግን እኮ ለደንታቸው እንደሆነ አያውቁም። ምህረተ አብን ስነካው መንጋው ለምን ብሎ ፎገላ ቀንድሼ፣ ቀንድሼ ስጥለው ድራሽ አባቱ ጠፋ። እነ ሄኖክ ኃይሌን፣ እነ እስክንድር ነጋን፣ እነ  ግንባሩን፣ እነ ፌክ ኢትዮጵያኒስቱን ስነካም ጓ ያሉትን እያጸዳሁ ቀጠልኩ። ሸዋ ስገባ፣ ጎንደር ወሎም ስገባ ጓ የሚሉትን፣ ፀያፍ ስድብ የሚሳደቡትን፣ የመንደሬን ነዋሪዎች የተከበረ ዓይን ለማቆሸሽ የሚውተረተሩትን ባለጌ ስድአደጎች በሙሉ ቀንድሼ፣ ቀንድሼ በመላክ ነው ከፔጄ ያጸዳኋቸው። አንዳቸውም በራሳቸው ፈቃድ ከፔጄ አይለቁም። እኔው ነኝ የማጸዳቸው። ከፔጄ ካጸዳኋቸው ውስጥ ተመልሰን እንግባ የሚለምኑኝ የትየለሌ ናቸው። ከ3 ሚልየን በላይ ተሳዳቢ፣ ባለጌ፣ ረኸጦችን ከፔጄ ላይ አጽድቻለሁ። አባርሬአለሁም። አልቅስ። እሪሪ ብለህ እኔ ፈልገኸኝ የወሬ ሱስህን የማረካልህ፣ ከወሬ ጠኔ የምገላግልህ ነኝ እንጂ አንተ ተጎልተህ ሓሳብ ሳታዋጣ ምንአባህ ጥቅም ትሰጣለህና ነው መጣህ ቀረህ ብዬ የማስበው? ጉልቻ ራሱ በስንት ጣዕሙ። "…ወደ ገደለው ስመጣ እኔ ዘመዴ የእኔን ጦማር እነ አስረስ መዓረይና እነ ጥላሁን አበጀ፣ ካነበቡልኝ ሌላው መንጋ አነበበ አላነበበ ምን ሊረባኝ? እኔ የአስረስ መዓረይ የሚዲያ ሠራዊት እነ ጠቋር ጥልሚያኮስ አማኑኤል አብነት፣ እነ ሥጋ ቆራጭ ይኸነው የሸበሉ፣ እነ አልማዝ ባለጭራዋ ካነበቡልኝ ስለሌላው ኮልኮሌ ምን አግብቶኝ? እኔ ሰጣርጌ ስለ እኔ እያነበቡ የቴሌግራም ተከታታዮቹ ቁጥር ቀነሰ፣ ጨመረ ብለው ካላዘኑ፣ ዘመዴ ዛሬ እንዲህ ብሎ ጽፏል ብለው በቲክቶክ መቶም ሁለት መቶም ሰው ሰብስበው እያነበቡ ላልሰማ ካሰሙልኝ፣ ከራቡልኝ እኔ ምን እፈልጋለሁ? እነ መዓረይ ማንበብ አቁመው ስለ እኔ ማንሳት እስካላቆሙ ድረስ ስለሌላው ጫታም መንደሬ ጎጠኛ ምን አገባኝ? በሰላም፣ በፀባይ በቤቴ ከኖረ ሰው አደርገዋለሁ፣ እቀርጸዋለሁ፣ እውነትን ሃቅን እግተዋለሁ። ሄጵ ካለ፣ ጓ ካለ ደግሞ እንዲናፍቀኝ አድርጌ በብሎክ ሰይፌ ወገብ ዛላውን ቆርጬ አስተክዘዋለሁ። ፈልጌው አልሄድኩ፣ ፈልጎኝ ከመጣ በኋላ ሳሎኔ ውስጥ ጥሬ ካካውን ልዘፍልል ካለ አሳየዋለሁ። እናም ከብዛት ጥራት ወዳጄ። "…ሌላው በአንድ ቀን በሁለት መንገድ የቴሌግራም ተከታታይ መንጋ ማብዛት ይቻላል። ቀላልም ነው። እስቲ ፌስቡከሮችን፣ ቴሌግራመሮችን፣ ዩቲዩበሮችን በሙሉ ተመልከቷቸው። የመልእክታቸው መጨረሻ ላይ ምን ያስቀምጣሉ? አዎ የቴሌግራም፣ የዩቲዩብ፣ የቲዊተር፣ የፌስቡክ፣ የቲክቶክ ወዘተ ሌንኮችን ያስቀምጣሉ። አስቀምጠውም ሰው ጋብዙልን ይላሉ። ከሚጢጢዎቹ እስከ ግዙፎቹ ድረስ እንደዚያ ነው የሚያደርጉት። እናስ ይሄ ነገር እኔጋር አለ? የለም። ለምን በነፃ የማቀርበውን መረጃ ደግሞ ተለማምጬ ለምኜው፣ ይሆናል እንዴ? ኧረ በጭራሽ። አላደርገውም። እኔ እነ በለጠ ካሣን፣ ኢትዮ ቤተሰብ የእኔው ስለሆነ፣ ሞገሴ ሽፈራውን ተከተሉት ብዬ ሊንክ አስቀምጬላቸው በአንድ ቀን ተጥለቅልቀው አድረዋል። እናንተም ምስክሮች ናችሁ። እኔ ግን በእኔ ላይ አላደርገውም። አድርጌ ግን ማሳያት እችላለሁ። በጣም ቀላል ነው። "…አሁን ተራው የጎጃሞች ነው። ጎጃም አገው ሸንጎና ቅባቴው። እየተንጫጫ ያለው እሱ ነው። ልክ እንደ ስኳድ፣ ልክ እንደ ግንባሩ ነው የሚንጫጫው። ዘመዴን አትስሙት፣ አትከተሉት እያለ ዋይ ዋይ እያለ ነው። እኔ ሌላውን ስተች አንበሳ ያወርድልኝ የነበረው የጎጃም ሸኔ አሁን እሱን መቆንጠጥ ስጀምር እንቅልፍ አጥቶ እየባከነ፣ እየባዘነም ነው። የተሳካለት የመሰለው ወዳጄ ግርማ ካሣን ይዞ በሳምንት አንድ ቀን በመረጃ ቲቪ የማቀርበውን ነጭ ነጯን ከዘመዴ ጋር የሚለውን ሳምንታዊ ተወዳጅ መርሀ ግብሬን መሰናክል ፈጥሮ እንዳላቀርብ ለጊዜው ማስደረጉ ነው። ይሄም ደግሞ ለበጎ ነው። እንዲያውም በራሴ ስም፣ የራሴን የሳተላይት የቴሌቭዥን መርሀ ግብር እንድጀምር ነው የሚያደርገኝ። ያደረገኝም እንደዚያ ነው። ስለዚህ ከወዳጆቼ ከመረጃ ቲቪ ከቤተሰቦቼም ቡራኬ ተቀብዬ በአጭር ቀን ውስጥ ቦርድ አቋቁሜ፣ የቆመውን ፈቃድ አስቀጥዬ፣ በዓለማዊውም፣ በመንፈሳዊውም የተዋጣለት የቴሌቭዥን መርሀ ግብር ለመጀመር ዕድልና በር ነው የከፈቱልኝ። ክፉ ጎረቤት ዕቃ ያስገዛል አይደል? እንደዚያ ነው የማደርገው። የፈረሱ ገዳማትን፣ የተቸገሩና የተፈናቀሉ ወገኖቼን አስተባብሬ የማሠራበት ግዙፍ የቴሌቭዥን ጣቢያ ነው የምከፍተው። ቅደሚ ከፊት ከኋላዬ የምላት ወላዲተ አምላክም ትረዳኛለች። ታግዘኛለችም። ይሄን አምናለሁ። ተአምር ነው የምሠራው። በዚህም የጎጃም አገው በኔዎችን በታሪክ ሳወሳቸው እኖራለሁ።👇③ ✍✍✍

👆②✍✍✍ "…በየትኛውም ማኅበራዊ ሚዲያም ሆነ የዐውደ ምህረት ስብከት ላይ በዚህ ዘመን ተዋናይ የሚሆኑ የማኅበራዊ ሚዲያም ሆነ የዐውደ ምሕረቱ ተዋናዮች ልክ እንደ ነጋዴም እንደ ሴተኛ አዳሪም ነው የሚሆኑት። ለገበያ፣ ለቢዝነስ፣ ለሆነ ጥቅም ስለሆነ ወደ አደባባይ የሚወጡት ተጠንቅቀው ነው የሚኖሩት። ብልጭልጭ፣ አጓጊ፣ ግመጡኝ፣ ግመጡኝ የሚል ሜካፕ ተቀብተው ነው ራሳቸውን ለመሸጥ የሚወጡት። የዩቲዩብ፣ የፌስቡክ፣ የቴሌግራምና የቲክቶክ ባለቤቶች በሙሉ ተለማማጮች ናቸው። በዜል፣ በካሽ አፕ እርዱን ብለው የሚለምኑ ዘመናዊ ለማኞችም ናቸው። "ደንበኛ ክቡር ነው" በሚለው የነጋዴ መመሪያ መሠረት ነው የሚመሩት። እናም የሚያተኩሩት ተከታታይ ማብዛት ላይ ነው። ተከታታዮቻቸውን ላለማጣት ሲሉ በብዙ ይጠነቀቃሉ። ለዚህም ሲባል እውነትን፣ መራር ሃቅን ሳይሆን መርህ አድርገው የሚከተሉት ተከታዮቻቸውን በሐሰት፣ በፈጠራ ወሬ ራሳቸውን በራሳቸው እያረኩ እዚያው በፔጆቻቸው ላይ ተዝረክረክርከው ደንዝዘው፣ ሌላ ነገር እንዳያስቡ ሳሙና እያቀረቡ አጃጅለው ማስቀረትን ነው ሥራዬ ብለው የሚይዙት። ላም አለኝ በሰማይ ወተቷንም አላይ ነገሮች ናቸው። ይደብራል ይሄ ነውር ነው። ይሄ ኃጢአትም፣ ግፍም ነው። "…የአብዛኛው የማኅበራዊ ሚዲያ አክተሮች የሚጠነቀቁት ተከታታዮቻቸው እንዳይከፉባቸው ነው። እሱን ነው ሲጠነቀቁ የሚውሉት። ለእውነት፣ ለሃቅ፣ ለመርህ፣ ለለውጥም ግድ የላቸውም። ደንታቸውም አይደለም። ብቻ ሰብስክራይበሮቻቸው እንዳይቀንሱ፣ የተመልካቾቻቸው ቁጥር ከፍቷቸው እንዳይወርዱ ነው የሚደክሙት። ኡጋንዳ የተሰደደው፣ አሜሪካ የገባው ሰብስክራይበሮችን ተስፋ አድርጎ ነው። ሰብስክራይበሮች ምንድነው የሚያስደስታቸው? ምን ብንነግራቸው ጮቤ ይረግጣሉ በሚለው ጉዳይ ላይ ነው ሲደክሙ፣ ሲለፉ የሚኖሩት። እኔ ግን እንደዚያ አይደለሁም። እኔ ታማኝነቴ ለህሊናዬና ለእውነት ነው። እውነት ደግሞ እግዚአብሔር ነው። ሰው ምን ያደርገኛል? ቀራንዮ እኮ የምትሄደው መስቀል ተሸክመህ ብቻህን ነው። ደረት የሚደቃልህ፣ ራቅ ብሎ የሚያለቅስልህ ሊኖር ይችል፣ ይኖርም ይሆናል እንጂ መስቀሉን አግዞህ አብሮህ ባይሰቀል እንኳ እንደ ቀሬናው ሰው ሊያግዝህ የሚመጣ አንድ ሰው ቢመጣ፣ ቢረዳህ ነው። እናም የበለጠውን እያሰብክ የዓለምን ጫጫታ ንቀህ ከእውነት ጋር መጣበቅ ነው አሸናፊ የሚያደርግህ እንጂ መንጋ መከተል፣ የመነረጋ ስሜት ማርካት ሲኦል ነው የሚያወርድህ፣ ለገሀነመ እሳት ነው የሚዳርግህ። "…ዐውደ ምሕረት ላይም ያሉት የሰባኬ ወንጌላውያኑ ችግርም ተመሳሳይ ነው። ልብስ ብቻ። ቀሚስ ብቻ። ከስብከታቸው ልብሳቸው ያምራል። የተሰቀለውን እውነት በጭራሽ እንዲህች ብለው አይሰብኩትም። ስብከቱ ሁሉ ያልበላህን ማከክ ነው። ታቦት ቆሞ 4 እና 5 ሰዓት ሙሉ ልመና ነው። ገንዘብ አምጡ ነው። ገንዘብ፣ ወርቅ፣ ሀብል፣ ቼክ፣ ዶላር፣ ዩሮ፣ ፓውንድ ወዲህ በሉ ነው። በቃ እዬዬ ነው። እዬዬ። በዕለቱ ለወንጌል ስብከት መምህራነ ወንጌል አይጋበዙም። ምርጥ ለማኝ፣ በኮሚሽን የሚሠራ ሁላ ሊሆን ይችላል እሱ ነው የሚጋበዘው። ኪስ ማውለቅ፣ በአፍ ጅዶ እንደኔ የተካነ ሞላጫ ኪስ አውላቂ ነው የሚጋበዘው። ፓትርያርኩ ለምን አይሆኑም እንዲያስተምሩ አይፈቀድላቸውም። ታዲያ በዚህ መሃል ስለ ንስሀ፣ ስለተግሳጽ የሚያስተምርም የለም። የንስሀ ዐዋጅም ዐያውጁም። ምእመናን እንዳይከፋቸው ስለ ኃጢአት፣ ስለ ክፉት፣ ስለ ዝሙት፣ ስለ ገሀነመ እሳት አስፈሪነት፣ ስለ ጌታ መምጣት ዐያውጁም። ምክንያቱም ላሜ ቦራው፣ ገንዘብ ብቻ የሚታለበው ምእመን ደንግጦ ይቀራል። ይሸሻል ብለው ስለሚያስቡ ምእመኑን በንስሀ ለእግዚአብሔር መንግሥት አያዘጋጁትም። የምእመኑን ልቡን ሳይሆን ኪሱን፣ ቦርሳውን ነው የሚያጥቡት። በአንዳንድ ሀገራት እንደውም ምእመኑ ነው ካህኑንና ጳጳሱን የሚያሽቆጠቁጠው። በአሜሪካና በካናዳ እንዲያውም ጳጳሳቱ እና ካህናቱ የምእመናኑ ቅጥረኞች ናቸው። "…ከሁሉ ከሁሉ የሚከፋው እንዲያውም አንዳንድ አድባራት ላይ በሥርዓተ ቅዳሴው ላይ ከግብዓተ መንጦላእትና ከቅዳሴው ንባብ ክፍል ቀጥሎ በፍሬ ቅዳሴው መግቢያ ላይ ካህኑ ከቤተ መቅደሱ ወጥቶ እጁን ወደ ምእመናኑ አዙሮ በብርት እና ኩስኩስት ወይም በማንቆርቆሪያ ውኃ ዲያቆኑ እየጨመረለት እጁን እየተናፃ ወይም እየታጠበ የሚያውጀው "…ንፁህ የሆነ ከቁርባኑ ይቀበል ንጹሕ ያልሆነ ግን አይቀበል ለሰይጣንና ለመልእክተኞቹ በተዘጋጀ በመለኮት እሳት እንዳይቃጠል። በልቦናው ቂምን የያዘ ልዩ ሀሳብና ዝሙት ያለበት ቢኖር አይቀረብ። እጄን ከአፋዊ እድፍ ንጽሕ እንዳደረኩ ከሁላችሁም ደም እንዲሁ ንጹሕ ነኝ። ደፍራችሁ ወደ ክርስቶስ ሥጋና ደም ብትቀርቡ ለመቀበላችሁ እኔ መተላለፍ የለብኝም በራሳችሁ ይመለሳል እንጂ በንጽሕና ሆናችሁ ባትቀርቡ እኔ ከበደላችሁ ንኝ።" የሚለውን ዐዋጅ ስለሚያስፈራ፣ ምእመናንም ይሄን ዐዋጅ ፈርተው ሊቀሩ ስለሚችሉ እናለዝበው በማለት በሌላ የቀየሩት እንዳንዶች አሉ። አሻሽለውት በራሳቸው መንገድ ለምእመናን በሚመች መልኩ እያቀረቡ ያሉ አሉ። ይሄ የሚያሳየው እንኳን ምድራዊና ሀገራዊ ጉዳይ ይቅርና መንፈሳዊ አገልግሎቶች እንኳ ልፍስፍስ እንዲሆኑ እየተደረገ ነው። እኔ ግን እዚህ ውስጥ የለሁበትም። "…ወደ ቴሌግራም ፎሎወር ብዛት እንምጣ። ወደ ቲክቶክና ወደ ዩቲዩብ፣ ወደ ፌስቡክም ተከታታዮች ብዛት እንምጣ። ብዙዎች የሚደነግጡት፣ የሚደሰቱትም ብዙ የሰብስክራይበር ቁጥር ሲያዩ ነው። ብዛት ብቻውን አሸናፊ አያደርግም። ከነ አባባሉም ከብዛት ይልቅ የሚያስፈልገው ጥራት ነው። ይሄ መጽሐፍ ቅዱሳዊም ነው። ሚልዮን ፎሎዎር ኖሮህ መልእክትህን ስታስተላልፍ 600 ሰዎች ላይክ ካደረጉህ ችግር አለ ማለት ነው። የአቢይ አሕመድን የፌስ ቡክ ፎሎዎር ቁጥርና እሱ ፖስት ሲያደርግ የሚሳተፈውን ሰው ብዛት ስታይ የቁጥር ተራነት ይገባሃል። ሚልዮን ሰው ተወዝፎ ሓሳብ ካልሰጠ፣ ካልተንቀሳቀሰ፣ ክፉ ደግ ካላወራ ቁጥር ብቻውን ምን ይሠራል? ምንም አይሠራም። በበዛ እኮ አይደለም። አንሶ ጥራት ካለው በቃ አሸናፊ ነህ። ለምሳሌ የኢትዮጵያ ቡና እግር ኳስ ክለብ ደጋፊው ስታዲየም ሙሉ ነው። ያ ሁሉ ግን የተመዘገበና ወርሀዊ ከፋይ ለክለቡ የሚከፍል አይደለም። ቢከፍልም በጣም ትንሽ ነው። በአንጻሩ የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብም ቁጥሩ ብዙ ነው። ሁሉም ደጋፊ ወርሀዊ ቋሚ የአባልነት ከፋይ ባይሆንም እንኳ ነገር ግን አንድ አላሙዲ ብቻ በቂያቸው ነው። ከብዛት ጥራት የምልህ እንደዚህ ነው። "…ወያኔ በሕዝብ ማዕበል ለማሸነፍ ከመቀሌ እርጉዝ ነፍሰ ጡሮችን ሁላ ሳይቀር አሰልፋ መንገድ ጀመረች። በአንድ መኪና ላይ 400 እና 500 ወጣቶች ተጭነው ሁላ ነበር ወደ ውጊያ የገቡት። ሲታዩ የበረሀ አንበጣ ስለሚመስሉ እጅግ ያስፈሩም ነበር። ነገር ግን አንድ ድሮን ብቻ መቶዎቹን ለመደምሰስ በቂ ነበር። ብዛት ብቻውን አዋጭም አይደለም። አስር እስራኤላዊ ሺ ፍልስጤማዊ እንደሚያሳድድ መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል። ሳምሶም በአህያ መንጋ ብቻውን ሺውን ያጋደመው እግዚአብሔር ስለረዳው ነው። እናም ኮዝህ ነው ወሳኙ። ከዚያ የእግዚአብሔር እርዳታ ካንተ ጋር ከሆነ ዓለሙ ሁሉ ለምን ሱናሚ ሆኖ አይነሳብህም። ወይ ንቅንቅ። ወይ ፍንክች። አበቃ። እስራኤል በዙሪያዋ በቢልዮን የሚቆጠሩ ጠላቶች አሉባት። ነገር ግን እንደምታዩት ነው።👇②✍✍✍

"ርእሰ አንቀጽ" "…ሰሞኑን የጎጃሙን አገው ሸኔ በተራው ልክ እንደ ግንባሩ፣ እንደ ጎንደሩ ስኳዱ፣ እንደ ግንቦቴው፣ እንደ ኦሮሙማው አራጅ፣ እንደ ወየንቲቲው እየገረፍኩት ስለሆነ የሌለ እየተንጫጫ ነው። ጫጫታው ደግሞ እንደ ሌላው ተመሳሳይ ቢሆንም የዚህኛው ግን ክፉ ሴራውን፣ ተደብቆ አስብቶ አራጅነቱን፣ በፎቶ ሾው ፒፕሉን አደንዝዞ ካስቀመጠበት ሥፍራ ስላነቃሁበት፣ የለበሰውን የበግ ለምድ ጭምብሉን ገፍፌ ተኩላነቱን ስለገለጥኩበት። የጎጃም ዐማራና አገውን ዐማርኛ እየተናገረ የሸወዳቸውን እንዲባንኑበት ስላደረግኩት ጩኸቱ የተለየ ነው። ገንዘብ ስላለው፣ ደፋር ፈጣጣ ስለሆነ፣ ሼምም ስለማያውቅ ጩኸቱ አደንቋሪ ነው። ቀድሜ የጎጃም ዐማራን አንቅቼ ከአጠገቤ ስላሰለፍኩም፣ የአገው ልጆችም ከእኔው ጋር ስለሆኑ ይሄ አድፍጦ የነበረው አናሳው አገው ሸንጎ ሸኔው ጨርቁን ጥሎ ማበድ ነው የቀረው። አርቲክሎች በእኔ ላይ መጻፍ፣ ፎቶዬን አንዴ የጅብ፣ አንዴ የቆማጣ፣ አንዴ የጭራቅ አድርጎ ማንቋረሩን ተያይዘውታል። ሲያስቁኝ እኮ ለጉድ ነው። በዐማራ ካባ አማርኛ እየተናገሩ የጎጃም ዐማራን ከጀርባ እየመቱ፣አገው ኦርቶዶክሳውያንን እያጸዱ እንደሆነ በመግለጤና የጎጃም ዐማራና አገው ለምን ማለት ስለጀመረ ነው ያበዱት። ገና አስነጥሳቸዋለሁ። "…ከዚህ በፊት እንደማደርገው ሁላቸውም በጭቃ ዥራፍ እሳት በሚተፋው ብዕሬ ስዠልጣቸው የሚያወሩት አንድ ዓይነት ነገር ነው። ፎቶዬን መዘቅዘቅ፣ ቆቱ ነው ጋላ ነው ማለት፣ ብፅፅግና ነው ወያኔ ነው ማለት፣ አሳዳጅ ነው፣ እነ በጋሻውን አሳድዶ ጴንጤ ያደረገ ነው ማለት፣ እንዳትሰሙት፣ እንዳትከተሉት ማለት ነበር። አሁን ግን ይሄ የጎጃሙ አገው ሸኔ ደረጃውን ከፍ አድርጎ ነው የመጣው። እስከዛሬ ጎንደር፣ ጎጃም፣ ሸዋ፣ ወያኔ ትግሬ ሁሉ በነፃነት በሃቅ ስተችበት የመበረውን የመረጃ ቲቪ ጭምር ነው የነቀነቁት። የበጠበጡት። አስረስ መዓረይ ከግርማ ካሣ ጋር ተጣምረው መረጃ ቲቪን አሸበሩት። ዘመዴ የጎጃሙን አቁም። በናትህ አቁም እስክባል ድረስ መረጃ ቲቪን አመሱት። እኔም የፍትሃዊነት፣ የእውነት ሚዛኔን ሳልስት በአቋሜ ፀናሁ። መረጃ ቲቪ ይቀጥል እኔ ግን በቴሌግራሜ ውጊያዬን እቀጥላለሁ። ዋናው ሰንኮፍ ያለው ጎጃም ነው። ዋናው ዘንዶ ያለው ጎጃም ነው። እናም እርሱን ልፋለም ብዬ አስፈቀድኩ። አይ አይሆንም ዘመዴ። በቴሌግራምም፣ በቲክቶክም ጎጃምን አትንካ ስባል ባሰብኝ። የአስረስ መዓረይ ሴራ በቶሎ ለማክሸፍ ጊዜ የለም በሚል የምወደውን መረጃ ቴቪን ለቅቄ፣ በቴሌግራምና በቲክቶክ ወደ ፍልሚያው ገባሁ። "…መጀመሪያ ደስ አላቸው። ጮቤ ረገጡ። ከቴሌቭዥኑ እንኳን ወረደልን እንጂ ቲክቶክና ቴሌግራም ላይ እንደፈለገ ይፈንጭ ብለው ተረጋግተው ተቀመጡ። እንደ ጀብዱም ራሴ በገዛ ፈቃዴ ምርጫዬን መርጬ የተውኩትን ጣቢያዬን ልክ እነሱ እንዳሸነፉኝ፣ ከዚህ በኋላ ምንም አቅም፣ ኃይል እንደሌለኝ አድርገው ወበሩ። ጨፈሩም። ብዙም አልቆዩ እሪሪ ማለት ጀመሩ። ቲክቶኩን እናዘጋ፣ ቴሌግራሙን እናዘጋ ብለው ተደራጁ። ዋይ ዋይ አሉ። ገና ሥልጣን ሳይዙ አፋኝ፣ ጨቋኝ፣ በነፃነት የመናገርን ነፃነት ለማፈን ተራወጡ። አንዱ እኔን ዘመዴን መቅበር አማራቸው። ከአባታቸው ከወያኔ፣ ከአለቃቸው ከሻአቢያ የቀሰሙትን ልምድ በእኔ ላይ ለመተግበር ተቅበዘበዙ። በሰለጠነ ሀገር ተቀምጠው ማይም ደንቆሮ ሆኑ። ቅማንቴው አበበ በላው "99.9% ከዚህ በኋላ በዘመድኩን ጉዳይ አልመለስም። የመረጃ ቲቪ ቦርድ ጩኸታችንን ሰምቶ ዘመዴን ድምፁን ስላፈነልን፣ ከአየርም ስላወረደልን እናመሰግናቸዋለን ብሎ እስኪናገር፣ በቴሌቭዥን እስኪጮህ ድረስ ተደስተውም ነገር ግን አሁንም በቲክቶክ፣ በቴሌግራም የምጽፈውን እያዩ መጨሳቸውን አላቋረጡም። ከዘመዴ የቴሌግራም ገፅ ውጡ። ከዘመዴ ጋር የምትገናኙ የፋኖ መሪዎች ጥቁር ውሻ ውለዱ፣ እየዬ፣ እዬ፣ ወየው ወየው ደከሙ። ሥራ ነው የሆንኩባቸው። ያልገባቸው ነገር ግን ከእኔ ፔጅ ራሱን በራሱ የሚያወጣ አለመኖሩ ነው። አብዛኛውን ድራሽ አባቱን የማጠፋው፣ ቆምጬ ከፔጄ ቀስፌ የማባርረው እኔው ራሴ ነኝ። "…አሁን ደግሞ ትናንትና ዛሬ እንደ አዲስ አስረስ መዓረይ ለተቀላቢ አክቲቪስቶቹ መመሪያ ሰጥቶ፣ በቃ ዕቅዳችንን ውኃ በላው፣ ህልማችን ጨነገፈ፣ ተበላን በቃ። ከሰርን በሚል ሂሳብ እንደ አዲስ ማኅበራዊ ሚዲያው ላይ ድንኳን ጥለው፣ ነጠላ ዘቅዝቀው፣ ሙሾ እያሞሹ፣ ፀጉራቸውን እየነጩ፣ ፊታቸውን እየሞነጨሩ፣ ደረታቸውን እየደቁ፣ እየተነሡ እየፈረጡ ዋይ ዋይ እያሉ ነው። እኔ ዘመዴ አስረስን ያስፈራው ነገር በደንብ ነው የማውቀው። አስረስ መዓረይ የጎንደር፣ የሽዋ እና የወሎ ዐማራ አንድ ከሆነ ዐማራን የሚያቆመው ኃይል ስለማይኖር ብሎ ፈርቶ እየቀዘነ እንደሆነ የሚገባው እኔን ብቻ ነው። አገው ሸኔ እና የአስረስ ቡድን ከብልፅግና ጋር ሆነው እንኳን ወደ አንድ የሚመጣውን ፋኖ ማስቆም ስለማይችሉ ነው መዓረይ አስረስ የመላው ዐማራ ፋኖ እንዳይመሰረት ሲያሴር የከረመው። አገው ሸንጎዎች እና የስኳድ ኃይሎች የዐማራ ኃይል እንዲኖር አይፈልጉም። ዐማራው አንድ ኃይል ከፈጠረ አይደለም አገው ሸንጎንና ስኳድን ለብልፅግናም ዕድሜ ማጠር ትልቅ አስተዋፆ እንደሚኖረው ያምናሉ፣ ያውቃሉም። ስለሆነም በተለይ በጎንደር በጎጃም በሽዋ ያሉት የዐማራ ፋኖዎች ከእነ አስረስ ቡድን ጋር የሚያደርጉት ግኑኝነት ጥንቃቄ ማድረግ ስለጀመሩ፣ ለእነ አስረስ መዓረይ አንታዘዝም የሚሉ የፋኖ መሪዎች በግልፅ መውጣት ስለጀመሩ፣ ሴራው እየተገለጸላቸው መምጣት ስለጀመረ፣ በሰበር ዜና አደንዝዘው በጊጃም ያለው ኃይል ገናና አስመስለው የሣሉት ሥዕል፣ ያወሩት ወሬ ድባቅ ስለተመታባቸው አበዱ። የሚሆኑትንም አጡ። የሚገርመው አገው ሸኔም ሆነ የጎንደሩ እስኳድ ሁለት ባላ ነው ያለው አንዱ ሲሰበርበት ቤላው ያዘግማል። ሲፈልግ ዐማራ ነኝ ብሎ በዐማራ ላይ ተሹሞ በዐማራ ስም ዐማራን አፈር ከደቼ ያበላዋል። እሱን ነገር ነው አሁን እኔ አንቄ ፈጥርቄ የያዝኩት። በሁለት ቢለዋ መብላት የለም ነው እያልኩ ያለሁት። አርበኛ ዮሐንስ አለማየሁን ጨምሮ እስከዛሬ በሴራ የተበሉት የጎጃም ዐማራ ፋኖዎች ቢያሳዝኑኝም አሁን ግን የጎጃም ዐማሮች መጠንቀቅ መጀመራቸውን ሳይ አምላኬን አመሰግነዋለሁ። "…እኔ ዘመዴ አሸናፊ ነኝ። ማንም እስከዛሬ ያልሞከረውን ሞክሬ ቢያንስ ሰው ሁሉ እንዲወያይ፣ ውይይት፣ ንግግር እንዲጀመር አድርጌአለሁ። የውሸት ሰበር ዜና ሙሉ በሙሉ ቀርቷል። ትግሉ የደረሰበትን ደረጀ ከቀደዳ፣ ከሀሰት ፕሮፓጋንዳ አውጥቼ፣ አላቅቄዋለሁ። ሰውን በውሸት መዝረፍ፣ ጎፈንድሚ፣ በአዳራሽ ሰብስቦ ማለብ ለጊዜውም ቢሆን ቆሟል። በመሬት ላይ ዘረፋ፣ ሕዝብን መግደል፣ ማፈን ቀንሷል። ገበሬው፣ ነጋዴው ከመሳደድ ተርፏል። መምህራንና ኃኪሞችን የሚገድለው የአስረስ መዓረይ ቡድን አሁን አደብ ገዝቷል። ይሄ ሁሉ የሆነው በእኔ በዘመዴ፣ በጃል ቆቱ በወዲ አስገዶም ነው። ያድጋል፣ ውይይቱ፣ ጥያቄው፣ ለምን ብሎ መጠየቁ እያደገ ነው የሚሄደው። ስለ እኔ በሚጻፉ የተቃውሞ፣ የስድብ፣ የማዋረድ ልጥፎች ስር ሕዝቡ የሚሰጠውን አስተያየትና አጋርነትንም በሚገባ እያየሁ ነው። ደስም እያለኝ ነው። የዐማራው በዚህ መጠን ከጎኔ መቆም ለእኔ ትልቅ ግብአት ነው የሆነኝ። ከጎኔ ባይቆምም ለደንታው ነው። እኔ ቆመልኝ አልቆመልኝ አይሞቀኝ አይበርደኝ። ግን በመንጋነት የሚያስብ ጠፍቶ፣ ሸደቦ የሚነዳ ጠፍቶ በአእምሮው እያሰበ ሓሳብ የሚሰጥ ዐማራ ስላየሁ ደስ ነው ያለኝ። እቀጥላለሁ።👇①✍✍✍

መልካም… ቆየሁባችሁ አይደል…? "…ምን የመሰለ ክሽን ያለ ጣት የሚያስቆረጥም ጦማር እየጻፍኩላችሁ ስለሆነ ነው። ዲማ ቅዱስ ጊዮርጊስ አይደል ያለሁት። ለሳምንት የሚበቃ ርእሰ አንቀጽ ነው እያዘጋጀሁላ
መልካም… ቆየሁባችሁ አይደል…? "…ምን የመሰለ ክሽን ያለ ጣት የሚያስቆረጥም ጦማር እየጻፍኩላችሁ ስለሆነ ነው። ዲማ ቅዱስ ጊዮርጊስ አይደል ያለሁት። ለሳምንት የሚበቃ ርእሰ አንቀጽ ነው እያዘጋጀሁላችሁ ያለሁት። እምጣጣሃ… አቤት ሲጣፍጥ። ጨዉም ልክ ነው። • እጃችሁን ታጥባችሁ ጠብቁኝ። አዳራሹ ውስጥ የአገው ሸኔ፣ ቅባቴ ረባሽ ተሳዳቢ ካያችሁ 👉🏿 BLOCK የሚል ቀለም እየቀባችሁ ምልክት አድርጋችሁ ጠብቁኝ። ስመጣ ለቅሜ ድራሽ አባቱን ነው የማጠፋላችሁ። እዚያው ቅዳሜ ገበያ እንዲጎለት ነው የማደርግላችሁ። • እየጠበቃችሁ…መጣሁ…

መልካም… "…ጎጃም በታላቁ የተዋሕዶ ሊቃውንት መፍለቂያ በሆነው ዲማ ጊዮርጊስ ነው የምገኘው። ምሽት ላይ ከሕዝቡና ከሊቃውንቱ ጋር ስብሰባ ቢጤ ነበረኝ። የሚገራርሙ ሓሳቦችም ሲንሸራሸሩ አምሽተዋል። "
መልካም… "…ጎጃም በታላቁ የተዋሕዶ ሊቃውንት መፍለቂያ በሆነው ዲማ ጊዮርጊስ ነው የምገኘው። ምሽት ላይ ከሕዝቡና ከሊቃውንቱ ጋር ስብሰባ ቢጤ ነበረኝ። የሚገራርሙ ሓሳቦችም ሲንሸራሸሩ አምሽተዋል። "…ዘመዴ አሉኝ ዲማ ጊዮርጊሶች ዘመዴ ለምንድነው በተለቭዥን የማትመጣ? እኛ እኮ በሬአችንን ሁላ ሽጠን ሳታላይት ዲሽ ያስገባነው የአንተን ነጭ ነጯን ብሮግራም ለመከታተል ብለን ነው። እናም አሁን በምታስፈልገን በዚህ ሰዓት ለምነ የማትመጣ? ምጣ ምጣ እንጄ ዘመዴ ብለው ወጥረው ሲወተውቱኝ ነው ያመሹት። እኔም ምን ሽግር አለው ብያቸዋለሁ። ደግሞ ለመምጣት…? ሃኣ "…እዚያው ዲማ ጊዮርጊስ መጻሕፍት ቤት ነኝ። ማር ከአፋቸው ከሚንጠባጠበው ከየኔታ አፍ የሚገርም አንድ የብሉይ ኪዳን ታሪክ በአንድምታ እየኮሞኮምኩ ነው። እሱን ታሪክ ነው ዛሬ በርእሰ አንቀጽ መልክ የምጽፍላችሁ። ጠብቁኝ። ትወዱታላችሁ። "…ወያኔ ጦሯን ወደ ወልቃይት እያስጠጋች ነው። ጎንደር፣ ወሎና ሸዋ አንድነት ፈጥረው ሳለ የጎጃሙ አስረስ መዓረይ ግን ጎጃምን ከዐማራ አንድነት እንዳይገባ ሾተላይ ሆኖ አንቆታል። እናም ወያኔ ጦርነት ከጀመረች የጎጃሙ አፍቃሬ ወያኔ አስረስ መዓረይ ሌላ ታሪክ ሊፈጥር ሁላ የተዘጋጀ ነው የሚመስለኝ። "…ከዙህ በፊት "ወያኔ ዳግም ብትመጣ አንዲትም ጥይት ተኩሰን ከወያኔ ጋር አንዋጋም ያለው ማነው?፣ በጎጃም ታስረው የነበሩ የወያኔ የጦር መኮንኖችንና አሁንም በቅርቡ ከነ የሬድዮ መገናኛው ተማረከ ተብሎ "ሴትና ጫት" ሲቀርብለት ከርሞ ጠፋ በሚል ምክንያት ፈትቶ ወደ ትግራይ የላከው ማነው? እናም ጎጃም ያለው የወያኔ ክሊክ ደቡብ ጎንደርና ደቡብ ወሎ ካለው ጋር አይቀናጁም ማለትም አይቻልም። • እስከዚያው ግን በጎጃም ያላችሁ የዐማራ ፋኖዎች እንደ ፋኖ ዮሐንስ እንዳትበሉ ተጠንቀቁ። • እየተወያያችሁ ጠብቁኝ

"…በበሬና በአህያ በአንድነት አትረስ። ዘዳ 22፥10 "…እንደምን አደራችሁ? "…እንደምን አረፈዳችሁ? "…እንደምን ዋላችሁ? "…እንደምን አመሻችሁ? "… መልሱ እግዚአብሔር ይመስገን ብቻ ‼
"…በበሬና በአህያ በአንድነት አትረስ። ዘዳ 22፥10 "…እንደምን አደራችሁ? "…እንደምን አረፈዳችሁ? "…እንደምን ዋላችሁ? "…እንደምን አመሻችሁ? "… መልሱ እግዚአብሔር ይመስገን ብቻ ‼

"…በጣም ያሳዝናል ከምር ከፍቶኛል። "…እኔ ዘመዴ በጀርመን ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጋር ያወራሁት በምስጢር ነው። እዚያ ኤምባሲ ድረስ ሄጄ ስነጋገርም በከፍተኛ ጥንቃቄና በከባድ ምስጢር በጥቁር መስታወት በታሸገ መኪና ነው የሄድኩት። ደግሞም ከአንድ ሰው በቀር ማንም አላየኝም። አላናገርኩምም። እና እንዴት ይሄን የመሰለ ከባድ ምስጢር ወጥቶ አዝማሪ እስክስ አቤ ጋር ሊደርስ ቻለ? ይሄ እጅግ ወሳኝ ጥያቄ ነው። እንደ ቀልድም የሚታይ አይደለም። "…ኤምባሲውንም የኢትዮጵያ መንግሥትንም በሕዝቡ ሁሉ ፊት ነው የምጠይቀው። የምፋረደው። ከእኔ ጋር እየተደራደራችሁ በጎን በኩል ደግሞ ለዚህ ከሲአይኤ፣ ከሞሳድ የበለጠ መረጃ ለማያልፈው ለሚያስፈራው ለከቤው ለከባዱ ለአቤ ዶላር በላው እንዴት ልታደርሱት ቻላችሁ። ለዚህ ሰው ምስጢር መንገር በእውነት ኤምባሲው የደረሰበትን ዝቅጠት ያሳያል። ምስጢር የባቄላ ወፍጮ ነው እንዴ? ልክ አይደለም።😡 "…አሁን አንተ አቤስ ብትሆን የፈለገ ብንጣላ፣ የፈለገ በእንጀራህ ብመጣ፣ የፈለገ ከዶላር ባናጥብህ፣ በቃ የፈለገ ይሁን ይሄን ሕይወቴን የሚቀይር፣ መቼም ያማላገኘውን ዕድል። ያውም በከፍተኛ ምስጢር ይዤው እተደራደርኩበት ያለሁትን ጉዳይ እንዴት በተለቭዥን በአደባባይ ወዳጆቼም ጣላቶቼም ይስሙት ብለህ ይፋ ታወጣብኛለህ? ከምር ዕድሌን ነው ያጨለምከው። በእውነት በኤምባሲውም በአንተም ላይ የዶላር አምላክ ይፍረድ። ዶላር ይጠርርባችሁ። ሌላ ምንም አልልም። "…ወገኖቼ እስቲ አቤን ሰምታችሁ ፍረዱኝ። የፈለገ ብንጣላ፣ በዚህ ዕድሜው እንዲህ በእንጀራዬ መምጣቱ አግባብ ነው ትላላችሁ? ሰምታችሁ ፍረዱኝ። አስተያየታችሁን እጠብቃለሁ።😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😡😡😡😡😡😡😡😡😡😡😡😡😭😭😭😭😭😭😭

"…አልሚ ግን በሰላም ነው…? "…የእኔ ተናግሮ አናጋሪ፣ የእኔ የወርቅ እንቁላል ጣይ ዶሮዬ ምኖናኖ? …ድራሽ አባቷ ከጠፋ እኮ 24 ሰዓት ሊሞላት ነው። እንዴኤኤ ሰው ያስባል አይባልም እንዴ…? አሌክ
"…አልሚ ግን በሰላም ነው…? "…የእኔ ተናግሮ አናጋሪ፣ የእኔ የወርቅ እንቁላል ጣይ ዶሮዬ ምኖናኖ? …ድራሽ አባቷ ከጠፋ እኮ 24 ሰዓት ሊሞላት ነው። እንዴኤኤ ሰው ያስባል አይባልም እንዴ…? አሌክሶ ሂድበት…🏃‍♂ ቴምር ሂጂበትም ናፈቀኝ እኮ።🏃‍♀‍➡️ "…ጠቋር ጥልሚያኮስ አማኑኤል አብነት፣ ሥጋ ቆራጭ ይኸነው የሸበሉ፣ አልማዝ ባለጭራዋ ከሌሉ ማን ሊያናግረኝ ነው? …የጦስ ዶሮዎቼማ ዝም ማለት የለባቸውም። ከምር ግፍ ነው። በእንጀራዬ እንደመጣችሁ ነው የምቆጥረው። ሥነ ሥርዓት። "…ቲክቶክም ላይ ጠፋችሁ፣ ፌስቡክም ላይ ጠፍታችሁ እንዴት ይሆንልኛል። ተዉ ግድየለም ጨከን ብላችሁ፣ ወገባችሁን ታጠረቃችሁ፣ እህል ነገር ቀምሳችሁ ብቅ በሉ። አመድኩን ነቀለ፣ ጎጃም ይከብድሃል፣ አስረስ መዓረይን አትችለውም፣ ድራሽህን ነው የምናጠፋው ብላ ብላ በሉኝ እንጂ። ኧረ በአባ ጃሌው። ተዉ እንጂ…? "…የማይነካ ነካህ፣ እናሳይሃለን፣ አትከተሉት፣ አትስሙት ኡኡ ጫጫታው ምነው ቀዘቀዘ? አንድ ዘመዴን ያውም በቴሌግራም ጽሑፍ መግጠም ያቅታችኋል? ኧረ ጠንከር በሉ። ስድብ ካጣችሁ ሞጣ ቀንሶ ይሽጥላችሁና ተመለሱ። ሳንቲም ካጠራችሁ "የተራበ አለ ብለን፣ በራብተኛ ስም እንሰብስብላችኋለን" ብቻ እናንተ አትጥፉ። "…ቱ… አንድ ዘመድኩን ያቅታችሁ…? ሞታችኋታላ…! …ገና የሚዘገንን፣ የሚሰቀጥጥ የውጊያ ካርዴን ሳልመዝ፣ አንገት የሚያስደፋ፣ ኡኡ የሚያስብል የተደበቀ አረመኔያዊ ድርጊት ይፋ ሳላወጣ ምነው ተብረከረካችሁ። ከምር አዝንባችኋለሁ። • በሉ በርታ በርታ በሉና እያነከሳችሁም ቢሆን ግጠሙኝ። 🙏🙏🙏 ብሊስ😂

+3
• መግለጫውን ያላወጣሁበት ምክንያት…! "…ተስፋዬ ወ/ሥላሴ እና ፓስተር ምስጋናው አንዷለም በፌስቡክ ገጻቸው ከመለጠፋቸው በፊት ነው ፕሮፌሰር ኢያሱ ከትግል ሜዳ ቀድሞ መግለጫውን ያደረሰኝ። ነገር ግን ጥያቄ ስላለኝ አልለጠፍኩትም። ጥያቄዬንም አሁንም በእናንተ ሁሉ ፊት አቀርባለሁ። "…ጎንደር ከሁለትነት ወደ አንድነት መጥቷል። አኩርፎ የቀረው ፋፍዴንና በግል የምወደው አርበኛ ደረጀ በላይ ብቻ ነው። እነ ደረጀ፣ እነ ኢያሱ ከእስክንድር ነጋው ሕዝባዊ ድርጅት ከአበበ ዶላር በላው ጥርነፋ አልወጡም። ተቀፍድደው ነው የታሰሩት። እናም በዚያ ፌካፌካም ፀረ ዐማራ ድርጅት፣ ፀረ ጎንደር ድርጅት ስር ታቅፈው ሳለ፣ አምሳሉን በማንትስ ቀይረነዋል ብለው እየለፈለፉ እየሰማሁአቸው፣ ትንሽ ገንዘብ ብናገኝ ፍርስርሱን ነው የምናወጣው የሚሉ ባሉበት ሀገር ምን ይሁነኝ ብዬ ነው የምለጥፈው? ይሄ ልክ አይደለም። "…አበበ በላው የጎንደሮችን አንድነት አይተነፍሳትም። እስክንድር ስር እያተሶቶሰ ይኖራታል። ፓስተር ምስጋናው የፋፍዴን የውጭ ተወካይ ነው። እስክንድር ነጋን የሚደግፍ አንድ ሰው እንኳ ቢጠፋ እኔ እስከሞት ከእሱ ጋር ነኝ ብሎ ቃለመሃላ በቲክቶክ ለሕዝቡ ሁሉ የፈጸመ ነው። እናም ምን ይሁነኝ ብዬ ነው የመርዝ ብልቃጥ ሰዎች ባሉበት ቦታ ከፍቼ የማስቀምጠው? "…አንድነት የግድ ነው። ጎጃምን አንድ ማድረግ ትቶ በሴራ ከወሎ፣ ከጎንደርና ከሸዋ ለይቶ አስረስ መዓረይ በትናንትና መግለጫው ስለጎንደር አንድ መሆን ሳይሆን እሱ በድብቅ ንግግር ጀምሮባቸው የነበሩት እነ ፕሮፌሰር ጌታ አስራደን ነበር ሲለማመጥ የታየው። ደላንታ ላይ ፍየል አርደው ከምክክር ኮሚሽኑ፣ ከአፍሪካ ህብረትና ከብልፅግና ጋር እየመከሩ በጎን ስለ አንድነት ማውራት አይነፋም። "…አንድነት የግድ ነው። የግድ ሲባል ግን ከነመርዝህ አንድነት የለም። ሃላስ።

+2
የድረሱላት ጥሪ… "…የጎጃም ዐማራ ተወላጅ ናት። ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በመሠረተው ባልደራስ ውስጥም በአመራርነት ሠርታለች። እስክንድር ወደ ቂሊንጦ ሲወርድም እሷም ከአስቴር ስዩም (ቀለብ) ጋር አብራ ታስራለች። ከእስር ከተፈቱ በኋላ የባልደራስን አካሄድ ነቅፋ ከፓርቲው ለቃለች። የዐማራ ፋኖ የትጥቅ ትግል ሲጀመር ወደ ትውልድ ሀገሯ በመሄድ የትጥቅ ትግሉን ተቀላቅላለች። "…ፋኒት አስካል ደምሌ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በዐማራ ፋኖ በጎጃም ውስጥ ያለውን ዝቅጠት፣ የትግሬውን ኮሎኔል መጥፋት፣ የሠራዊቱን ተስፋ መቁረጥና መበትን ከሌላ ጓድ ጋር በእንባ ስትወያይ የድምጽ ቅጂ ከተበተነ በኋላ በዐማራ ፋኖ በጎጃም ጥርስ ተነክሶባት በቁጥጥር እንድትውል ተደርጋለች። "…እኔም በቁጥጥር ስር የመዋሏን ዜና ከተናገርኩ ጀምሮ እንደ ድመት ወገኑን መግደል ሱስ የሆነበት ይሄ ገዳይ በዐማራ ፋኖ በጎጃም ውስጥ ያለ ቡድን ጫጫታውን ፈርቶ ከመግደል ተቆጥቧል። "…ተቋማችን በዓለም ደረጃ እንዲጠቆር አድርገሻል ስለዚህ የድርጅቱ መሪ አርበኛ ዘመነ ካሴ አምጧት ብሏል በማለት መጀመሪያ ከአጉት ወደ ቋሪት ካመጧት በኋላ ከቋሪት ወደ ዘመነ ጋር እንወስድሻለን በማለት መንገድ ከጀመሩ በኋላ ምን እንደሆነ ሳይታወቅ መልሰው ወደ ቋሪት አምጥተዋታል። ፋኒት አስካለን ፋኖ በሽታዬ አስታጥቄ የምትጠበቅ ቢሆንም ዘመነ ካሤ ስለጉዳዩ ይወቅ አይወቅ የታወቀ ነገርም እንደሌለ የመረጃ ምንጮቼ ገልጸውልኛል። "…ክልገደሏት ምን ሊያደርጓት ይችላሉ ብዬ ላቀረብኩላቸው ጥያቄም… ምን አልባት እየደፈሩ ቪድዮ ቀርጸው በማስፈራራት ከትግሉ ሊያስወጧት ወይም በደፈጣ መከላከያ ገደላት ብለው ሊያስወግዷት ይችሉ ይሆናል ብለዋል። አርበኛ ዘመነ ካሤም ሆኑ አስረስ መዓረይ ፍትህ ለጎጃም ዐማራዋ ለአስካል ደምሌ እንዲሰጡ እማጸናለሁ። • ፍትሕ ለፋኒት አስካል ደምሌ።

የድረሱልን ጥሪ…! "…በጎጃም ቋሪት የአንዲት በዐማራ ፋኖ በጎጃም ዘግናኝ አደጋ ተደቅኖባት የድረሱልኝ ጥሪ ያቀረበች አንዲት ነፍስ ጥሪ ላቀርብላችሁ ነው። "…ሁላችሁም የፔጄ ተከታታዮች ድምፅ ትሆኗት
የድረሱልን ጥሪ…! "…በጎጃም ቋሪት የአንዲት በዐማራ ፋኖ በጎጃም ዘግናኝ አደጋ ተደቅኖባት የድረሱልኝ ጥሪ ያቀረበች አንዲት ነፍስ ጥሪ ላቀርብላችሁ ነው። "…ሁላችሁም የፔጄ ተከታታዮች ድምፅ ትሆኗትም ዘንድ ጥሪ ላቀርብ ነኝ። • ዝግጁ ናችሁ…?

"…A few moments later አለ ሱሬ… "…ዛሬ ደግሞ አገው ሸኔዋ ኃይልሻ ምን ብትል ጥሩ ነው? "…ያን ወፈፌ ዘመድኩን 90% በሚባል ደረጃ የሚከታተለው አማራ 87 % አካባቢ የሚጨሰውም አማራ
+1
"…A few moments later አለ ሱሬ… "…ዛሬ ደግሞ አገው ሸኔዋ ኃይልሻ ምን ብትል ጥሩ ነው? "…ያን ወፈፌ ዘመድኩን 90% በሚባል ደረጃ የሚከታተለው አማራ 87 % አካባቢ የሚጨሰውም አማራ (3% ያው ተራ የሚጠብቅ ጎጤ ስለሚደግፈው ነው 🙄)  ግራ የገባኝ ስልካቸው ኢንተርኔታቸው ምናምን በሱ ቁጥጥር ስር ነው ወይ ?  ከሱ ብትሸሹ ችት ያደረጋችሁበት ያክል ነው ወይ ሚሰማችሁ ? 😂 "…አማርኛ ተናጋሪ አገው ሸንጎን እየቀጠቀጥኩት ነው ማለት ነው። የጎጃም ዐማራ ፋኖን እና የጎጃም አገው ጀግኖችን በተለይ ኦርቶዶክሳውያኑን ከጀርባ እየመታ፣ በሴራም እያስገደለ የዐማራ ፋኖ በጎጃምን ያለ ጀግና እያስቀረ ያለውን አውርቶ አደር የፎቶ ቦለጢቀኛ በሙሉ በዳዴ እያስኬድኩት ነው ማለት ነው። "…ደግሞ እኮ አገው ሸኔ ሆና ዲያቆን ነኝ እያለች የሕዝብ ሁላ ብድር እንደ ኢትዮጵያ ዕዳ ተሸክማ የምትዞር ናት አሉ። ይህቺ ሚጢጢ ብድራም። 😂 • ወጥር ዘመዴ…💪✊