HU MODEL SCHOOL STUDENTS UNION
Open in Telegram
This is official channel of HUMS Students Union. Any comment 👉 @HUModel_Schoolbot In this channel you can get :- -Information updates -PDF files -Short notes -Quizes Invite you friends, your class mates and families ☺️
Show more1 967
Subscribers
+224 hours
+127 days
+4830 days
Posts Archive
+2
Congratulstions! Our students, teachers and community of Haramaya University. Grade 12 EAES Top scorer students are; 1.Yanet Asrat Birhanu 534.67/600.
2.Fami Elias Ali 516.92/600.
3.Bonson Buzayew Chalchisa 513.33/600.
@HUMSSU
በኢትዮጵያ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ታሪክ እጅግ አነጋጋሪ የሆነ ዝቅተኛ ውጤት ተመዘገበ::
በአገር አቀፍ ደረጃ ይፋ የተደረገውን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት ተከትሎ፣ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ ሰፊ አጀንዳ የሆነና በርካታ ተከታታዮችን ያስገረመ የውጤት ዝርዝር ይፋ ሆኗል።
በማኅበራዊ ሚዲያ የመረጃ ገጾች (ጉርሻ ፔጅን ጨምሮ) ከተሰራጩት የውጤት ሰነዶች ማረጋገጥ እንደተቻለው፣ በሶሻል ሳይንስ (Social Science) ዘርፍ ፈተናውን የወሰደው የ22 ዓመት ወንድ ተፈታኝ፣ ከጠቅላላ 600 ነጥብ 20.67 ብቻ በማስመዝገብ በአማካይ 3.45% አስመዝግቧል።
ይህም በኢትዮጵያ የትምህርት ታሪክ ውስጥ በታችኛ ደረጃ ከተመዘገቡት ውጤቶች መካከል እጅግ አነስተኛው እና ያልተለመደው ተብሎ ተጠቅሷል።
ለሕዝብ ይፋ የተደረገው የተፈታኙ የትምህርት ዓይነቶች ውጤት ዝርዝር የሚከተለውን ይመስላል፦
1ኛ. እንግሊዝኛ (English): 8.00
2ኛ. የተፈጥሮ ዝንባሌ ፈተና (Scholastic Aptitude Test): 5.00
3ኛ. ታሪክ (History): 4.00
4ኛ. ጂኦግራፊ (Geography): 2.00
5ኛ. ሒሳብ (Mathematics): 1.67
6ኛ. ኢኮኖሚክስ (Economics): 0.00
የተፈታኙ ግላዊ መብትና ብሔራዊ የውሂብ ጥበቃ ደንቦችን ለማክበር ስሙ ያልተጠቀሰው ይህ ተማሪ ያስመዘገበው እጅግ ዝቅተኛ ውጤት፣ በማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎችና በትምህርት ባለሙያዎች ዘንድ ሰፊ መነጋገሪያ ሆኗል።
@HUMSSU
#ከታች በተቀመጠው #link መሰረት አሁን ውጤታችሁ ማየት ትችላላችሁ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤታችሁን ለማየት የEAES ኦፊሴላዊ የውጤት መመልከቻ አማራጮችን ብቻ ይጠቀሙ።
🌐 result.eaes.et
🌐 result.neaea.gov.et
📱 SMS: 6284
@HUMSSU
ውጤት መቼ ይታያል ?
ተማሪዎች ውጤታቸውን ከሰኞ ጠዋት ወይም ማክሰኞ ከሰዓት ጀምሮ መመልከት ይችላሉ።
በውጤታቸው ላይ ቅሬታ የሚኖራቸው ከሆነም 5/6 ቀናት ቅሬታ የማቅረቢያ ጊዜ የሚሰጣቸው ይሆናል።
@HUMSSU
ከፍተኛ ውጤት !
በማኅበራዊ ሳይንስ ወንድ 576.2 ከዶዶላ ኢፋ ቦሩ ት/ቤት ተመዝግቧል።
በሴት 569.1 ከቦሌ ሱፐር ሆሊሴቪየር ት/ቤት ተመዝግቧል።
@HUMSSU
" ዘንድሮ ካለፉት ዓመታት ውጤት ጋር ሲነጻጸር የተሻለ ተማሪ ቁጥር ያለፈ በመሆኑ የምንቀበለው የሬሚዲያል ተማሪ ቁጥር ይቀንሳል። ስንት ይሆናል የሚለውን በተመለከተ ግን መቁረጫ ነጥቡ ወደፊት የሚገለጽ ይሆናል። " - ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ (የትምህርት ሚኒስትር)
@HUMSSU
ከፍተኛ ውጤት !
በተፈጥሮ ሳይንስ ወንድ 591.6 ከ600 ተመዝግቧል። ተማሪው የኦዳ ስፔሻል ቦርዲንግ - አዳማ ተማሪ ነው።
ከሴት ደግሞ 583 ከ600 ሲሆን ከእንጅባራ አገው ምድር ትምህርት ቤት ነው።
@HUMSSU
ዘንድሮ በአጠቃላይ ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል ማለፍ የቻሉት 70 ሺ 544 ናቸው።
ካለፉት መካከል በተፈጥሮ ሳይንስ 16.5 በመቶ ሲሆኑ በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ 8.33 በመቶ ናቸው።
@HUMSSU
በዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና 563 ሺ 960 ተማሪዎች ተመዝግበው 550 ሺ 210 ተማሪዎች ፈተናውን ወስደዋል።
ፈተናውን ከወሰዱት ውስጥ 12.8 በመቶ የሚሆኑት ተማሪዎች 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ ማምጣት ችለዋል።
@HUMSSU
August 6, 2026 (GC) – Haramaya University Model School
A discussion was held at Haramaya University Model School on the implementation of the summer tutorial program and the 2019 E.C. teaching–learning activities for Grade 12 students.
During the discussion, parents acknowledged the remarkable improvements and significant progress the school has achieved over the past four years. They also expressed their appreciation for the school's continuous efforts to improve the quality of education.
Furthermore, the parents affirmed their commitment to supporting the school in every way possible and pledged to play their part in strengthening the teaching–learning process for the benefit of the students.
@HUMSSU
