en
Feedback
⛪️🇪🇹@የራማው ልዑል🇪🇹 ⛪️

⛪️🇪🇹@የራማው ልዑል🇪🇹 ⛪️

Open in Telegram

ጤና ይስጥልኝ የቻናሉ ቤተሰቦች የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ዶግማና ቀኖናን የጠበቁ ሀሳቦችን እናም መዝሙሮች ያገኙበታል ሰለዚህ ውድ ወንድም እና እህቶቼ ይሄንን ....... በቻናላናችን የሚሰጡ ነገሮች መንፈሳዊ ትምህርቶች መንፈሳዊ ምክሮች መንፈሳዊ መዝሙር መንፈሳዊ ጥያቄዎች መንፈሳዊ ስዕልዎች በየለቱ ስንክሳር አስተያየት ሀሳብ እና ጥያቄ https://t.me/+uME9_xX453hk

Show more
924
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
#ህዳር_ፅዮን 21♥ እንኳን አደረሳችሁ ለፅዮን ማርያም #በዚህች ቀን የእስራኤላውያን መመኪያ በእመቤታችን ስም የተሰየመችው ታቦተ ጽዮን ዳጐን በተባለው ጣኦት ላይ ኃይሏን ክብሯን የገለጸችበት ቀን ነ
#ህዳር_ፅዮን 21♥ እንኳን አደረሳችሁ ለፅዮን ማርያም #በዚህች ቀን የእስራኤላውያን መመኪያ በእመቤታችን ስም የተሰየመችው ታቦተ ጽዮን ዳጐን በተባለው ጣኦት ላይ ኃይሏን ክብሯን የገለጸችበት ቀን ነው፤ #ቤተክርስቲያን_ጽዮን_ማርያም ስትል ዕለቱን ታከብረዋለች። ታሪክ : - አክሱም ጽዮን እንደዛሬው ድርቅ ያለ መሬት አልነበረም ባህር ነበር እንጂ፤ አብርሃና አጽብሃ ለታቦተ ጽዮን ምን ዓይነት ቤተክርስቲያን ነው የምንሰራላት ቦታውስ የት ጋር ነው የሚሆነው እያሉ ሲጨነቁ ጌታችን ተገለጸላቸው ድንጋይ ላይ ቆሞም አዩት፤ ቤተክርስቲያኗን እዚህ ባህር ላይ ስሩት ስሟንም በእናቴ ስም ሰይሟት፤ ይላቸዋል ጌታ ሆይ ይህ እኮ ባህር ነው ይሉታል ቅዱስ ሚካኤልን ከገነት አፈር ይዞ እንዲመጣ ያደርገዋል ባህሩ ላይ ነሰነሰው ደረቀ የዛሬውንም ቅርጽ ያዘ ይላል ጌታችን የቆመበት የእግሩ ምልክት ዛሬም ድረስ ይታያል ፤ ምንጭ ድርሳነ ጽዮን፤ በድንኳን ቅርጽ የተሰራው ቤተክርስቲያን ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ ያሳነጹት ሴቶችም ወንዶችም የሚገቡበት በመሐል ታቦተ ጽዮን ያለችበት እቴጌ መነን ያሳነጹት ስመ ጥምቀታ ወለተ ጊዮርጊስ በስሩ የጥንቱ ቤተመቅደስ ፍርስራሽ ይታያል በአራት መአዘን ቅርጽ ያለው አፄ ፋሲለደስ ያሳነጹት ሴቶች የማይገቡበት ጥንታዊ ቤተክርስቲያን ነው ፅዮን ማርያም እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሀገራችንን ሰላም ታድርግልን🙏 #ፅዮን_ማርያም ባልንበት ፀሎት ልመናችንን ትስማን ለመቀላቀል 👇👇👇👇 @DNESUBA @DNESUBA

"ትሑት ሰው ምንጊዜም ቢሆን የእርሱን ድካም ስለሚያውቅና የእግዚአብሔርን እርዳታ ስለሚሻ የእግዚአብሔር ኃይል በእርሱ ላይ ያድራል። በክንዱ ሳይመካ በእግዚአብሔር እርዳታ ስለተመካም ያሸንፋል።" /ብጹእ አቡነ ሺኖዳ/ @DNESSUBA

ቅዱስ ሲኖዶስ ባስተላለፈው ውሳኔ መሰረት ከኅዳር 15 አስከ21 ቀን 2016 ዓ.ም የሚካሔደው የምህላና የጸሎት መርሐ ግብር ከላይ በተጠቀሱት ሰባት ቀናት ከማለዳው 12:00 ሰዓት እስከ ጠዋቱ 1:00
ቅዱስ ሲኖዶስ ባስተላለፈው ውሳኔ መሰረት ከኅዳር 15 አስከ21 ቀን 2016 ዓ.ም የሚካሔደው የምህላና የጸሎት መርሐ ግብር ከላይ በተጠቀሱት ሰባት ቀናት ከማለዳው 12:00 ሰዓት እስከ ጠዋቱ 1:00 ሰዓት በምሽት መርሐ ግብር ደግሞ ከምሽቱ 12:00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 1:00 ሰዓት ድረስ የሚከናወን ሲሆን ሕዝበ ክርስቲያኑ በየ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናቱ በመገኘት በመርሐ ግብሩ ላይ እንዲሳተፍ እየገለጸ አጠቃላይ መርሐ ግብሩ ቀደም ሲል በተሰጠው መግለጫ መሰረት የሚፈጸም መሆኑን ያስታውቃል። የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት

ጳጳስ እንደ አቡነ ጴጥሮስ እውነቱን ተናግሮ ይሞታል። ይህን ማድረግ ካልቻለ ደግሞ ዝም ቢል ይመረጣል። መንቀዥቀዥ የለበትም። ከፖለቲከኛ ጳጳሳት ፍትሐዊ ንግግርን መጠበቅ ጅልነት ነው። እውነተኛ ንግግ
ጳጳስ እንደ አቡነ ጴጥሮስ እውነቱን ተናግሮ ይሞታል። ይህን ማድረግ ካልቻለ ደግሞ ዝም ቢል ይመረጣል። መንቀዥቀዥ የለበትም። ከፖለቲከኛ ጳጳሳት ፍትሐዊ ንግግርን መጠበቅ ጅልነት ነው። እውነተኛ ንግግር የሚነገረው ከእውነተኛ ጳጳሳት ነው። ከፖለቲከኛ ጳጳሳት እውነትን መፈለግ እንደዚህ ሰውየ መሆን ነው። የእውነት ልክ ክርስቶስ ስለሆነ ሁልጊዜም እርሱን አብነት እናደርጋለን እንጂ በየጊዜው እንደ እስስት የሚለዋወጡ በዚህ ምድር ያሉ ጳጳሳትን፣ ቀሳውስትን፣ ፖለቲከኞችን፣ እና የመሳሰሉ አካላትን መከተል አይገባም። በተጨማሪም የዚህ ምድር ሕይወታቸውን ድል አድርገው ያለፉ ቅዱሳንን እናስባለን እንጂ ያልሞተን ሰው መከተል ፍጻሜው ውድቀት ሊሆን ስለሚችል ራሳችንን እንጠብቅ።

🕊 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ 🕊  †  ኅዳር ፎ [ 6 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት  †  🕊 ✞ 🌹በዓለ ደብረ ቁስቁዋም🌹 ✞ የአርያም ንግሥት: የፍጥረታት ሁሉ እመቤት ድንግል ማርያም የባሕርይ አምላክ ልጇን አዝላ ወደ ምድረ ግብፅ ወርዳለች:: በወንጌል ላይ [ማቴ.፪፥፩-፲፰] እንደተጻፈው ጌታችን በተወለደ በ፪ ዓመቱ የጥበብ ሰዎች [ሰብአ ሰገል] ወደ ቤተ ልሔም መጥተው ሰግደውለት ወርቅ: እጣን: ከርቤውን ገበሩ: አገቡለት:: ንጉሥ ተወልዷል መባሉን የሰማ ሔሮድስ መቶ አርባ አራት ሺህ [144,000] ሕጻናትን ሲፈጅ በቅዱስ ገብርኤል ትዕዛዝ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ፊ አምላክ ልጇን አዝላ: በአንዲት አህያ ጥቂት ስንቅ ቁዋጥራ: ከዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር ስደት ወጣች:: ከገሊላ ተነስታ በጭንቅ: በመከራ: በረሃብና በጥም: በሐዘንና በድካም: በላበትና በእንባ ተጉዛ በዚሕች ቀን ምድረ ግብፅ ገብታለች:: - የአምላክ እናቱ እሳትን አዝላ በብርድ ተንገላታለች:: - ለእኛ የሕይወት እንጀራን ተሸክማ እርሷ ተራበች:: - የሕይወትን ውሃ ተሸክማ ተጠማች:: - የሕይወት ልብስን ተሸክማ ተራቆተች:: - የሕይወት ፍስሐን ተሸክማ አዘነች:: - እመ አምላክ ተራበች: ተጠማች: ታረዘች: ደከመች: አዘነች: አለቀሰች: እግሯ ደማ: ተንገላታች:: ለሚገባው ይሕ ሁሉ የተደረገው ለእኛ ድኅነት ነው:: በእውነት ይህንን እያወቀ ለድንግል ማርያም ክብር የማይሰጥ ሰይጣን ብቻ ነው:: አራዊት: ዕፀዋትና ድንጋዮች እንኳ ለአመላክ እናት ክብር ይሰጣሉ:: አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍና ቅድስት ሰሎሜ ደግሞ የክብር ክብር ይገባቸዋል:: ከአምላክ እናት ከድንግል ማርያምና ከቸር ልጇ ጋር መከራ መቀበልን መርጠዋልና:: "መድኃኔ ዓለም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለምን ተሰደደ? ለምን ስደቱን ወደ ግብፅና ኢትዮዽያ አደረገ?" ፊ. ትንቢቱን ይፈጽም ዘንድ:: በፈጣን ደመና ወደ ግብፅ እንደሚወርድ ተነግሯልና [ኢሳ.፲፱፥፩, ዕን.፫፥፯] ፪. ምሳሌውን ለመፈጸም:: የሥጋ አባቶቹ እነ አብርሃም: ያዕቆብ [እሥራኤል] : ኤርምያስ ወደዚያው ተሰደዋልና:: ፫. ከግብፅ ጣዖት አምልኮን ያጠፋ ዘንድ:: [ኢሳ.፲፱፥፩] ፬. የግብፅና የኢትዮዽያ ገዳማትን ይቀድስ ዘንድ:: ፭. ሰው መሆኑ በአማን እንጂ ምትሐት እንዳልሆነ ለማጠየቅ:: [ሰው ባይሆን ኑሮ አይሰደድም ነበር:: ሔሮድስ ቢያገኘው ደግሞ ሊገድለው አይችልም:: ያለ ፈቃዱና ያለ ዕለተ ዐርብ ደሙ አይፈስምና::] ፎ. ስደትን ለሰማዕታት ባርኮ ለመስጠት:: እና ፯. የአዳምን ስደት በስደቱ ለመካስ ነው:: እመ ብርሃን ድንግል ማርያም ለ፫ ዓመታት ከ፮ ወራት [ወይም ለ፵፪ ወራት] በስደት የቆየችባቸው ቦታዎች አሉ:: ድንግል ማርያም ከርጉም ሔሮድስ ስትሸሽ መጀመሪያ የሔደችው ከገሊላ ወደ ሶርያ ደንበር [ደብረ ሊባኖስ] ነው:: በዚያ የሸሸጋት ቅዱስ ጊጋር መስፍኑ በሔሮድስ ሲገደል ወደ ምድረ ግብጽ ወረደች:: በግብጽም ለብዙ ጊዜ ከአንዱ ወደ ሌላው ስትሸሽ ቆየች:: "እንዘ ከመ በግዕት ግድፍት አመ ሳኮይኪ ውስተ ምድረ በዳ" እንዲል:: [እሴብሕ ጸጋኪ] ቀጥላም በሰሜኑ የሃገራችን ክፍል ገብታ ደብረ ቢዘን ላይ [አሁን ኤርትራ ውስጥ ነው] ዐረፈች:: ከደብረ ቢዘን በደብረ ዳሙ: አክሱም: ደብር ዓባይ: ዋልድባ አድርጋ እየባረከች ጣና ደርሳለች:: በጣና ገዳማትም: በተለይ በጣና ቂርቆስ ለ፻ ቀናት ቆይታ ቀጥታ በጐጃም ወደ ሽዋ ሒዳ ደብረ ሊባኖስን ቀድሳለች:: ቀጥላም እስከ ደብረ ወገግና ደብረ ሐዘሎ ደርሳለች:: በእግሯ ያልደረሰችባቸውን የሃገራችን ክፍሎች በደመና ተጭና ዐይታ ባርካቸዋለች:: ከልጇም በአሥራትነት ተቀብላለች:: ሔሮድስ መሞቱን መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል የነገራትም እዚሁ ኢትደዮዽያ ውስጥ መሆኑን ትውፊት ያሳያል:: እመ ብርሃንም ከሃገራችን ሰዎች [ከሰብአ ኦፌር] የተቀበለችውን ስንቅና ስጦታ በ፭ ግመሎች ጭና ከቅዱሳኑ ዮሴፍና ሰሎሜ ጋር በዚህች ቀን ደብረ ቁስቁዋም ውስጥ ገብተው ከድካም ዐርፈዋል:: ሐሴትንም አድርገዋል:: ዳግመኛም ከክርስቶስ ስደት ፬፻ ዓመታት በኋላ በዚህች ቀን የግብጿ ደብረ ቁስቁዋም ታንጻ ተቀድሳለች:: የቅዱሳን ማደሪያም ሁናለች:: ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ:- ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በ፫፻፺ዎቹ አካባቢ ድንግል እናቱን: ቅዱሳን ሐዋርያትን: አእላፍ መላእክትን: ጻድቃን ሰማዕታትን: አስከትሎ ወረደ:: የወቅቱ የግብጽ ፓትርያርክ ቅዱስ ቴዎፍሎስና ሊቁ ቅዱስ ቄርሎስ ቤተ ክርስቲያኑን አንጸው: ሕዝቡን ሰብስበው ይጠብቁት ነበርና ወርዶ ቀድሶላቸው ታላቅ ደስታ ሁኗል:: ስደቷን መሳተፍን ሽተው አበው :- "እመ ኀሎኩ በጐይዮቱ ውእተ መዋዕለ: እምተመነይኩ ኪያሁ በዘባንየ ሐዚለ: ወበልሳንየ እልሐስ ዘአእጋሪሁ ጸበለ: ወከመ አዕርፍ ምስሌሁ በትረ ዮሴፍ ኀበ ተተክለ: ለወልደ ማርያም በሐጸ ፍቅሩ ልቡናየ ቆስለ::" እንዳሉ:: [ሰቆቃወ ድንግል] እኛም እመ ብርሃንን ልንሻት ያስፈልገናል:: ይህቺ ቀን ለእኛ ለክርስቲያኖች ሁሉ እጅግ የደስታ ቀን ነውና ሐሴትን እናድርግ:: የሰማይና የምድር ጌታ ለእኛ ሲል ካደረገው ስደቱ በዚህች ቀን ተመልሷልና:: ስደቷን አስበን ካዘንን: መመለሷን አስበን ደስ ልንሰኝ ይገባልና:: "አብርሒ አብርሒ ናዝሬት ሃገሩ: ንጉሥኪ በጽሐ ዘምስለ ማርያም መጾሩ" ልንልም ይገባል:: +" 🌷አባ ጽጌ ድንግል ዘወለቃ 🌷 "+ ጻድቁ አቡነ ጽጌ ድንግል በ፲፬ኛው መቶ ክ/ዘመን የነበሩ ሊቅና ገዳማዊ ናቸው:: የዘር ሐረጋቸው ምንም ከቤተ እሥራኤል እንደሚመዘዝ ቢታወቅም ኢትዮዽያዊ ናቸው:: አስቀድመው አይሁዳዊ በመሆናቸው ኢየሱስ ክርስቶስንና ድንግል እናቱን አያምኑም ነበር:: የተማሩትም ብሉይ ኪዳንን ብቻ ነበር:: በጊዜውም "ክርስቶስ አልተወለደም: ትክክለኛው እምነት ይሁዲ ነው" እያሉ ከክርስቲያኖች ጋር ይከራከሩ ነበሩ:: አንድ ቀን ግን ከታላቁ ሊቅና ገዳማዊ አቡነ ዜና ማርቆስ ጋር ተገናኙ:: ጻድቁን ስላልቻሏቸው ተሸንፈው በክርስቶስ አመኑ:: አቡነ ዜና ማርቆስም አስተምረው ክርስትና ሲያነሷቸው /ሲያጠምቁዋቸው 'ጽጌ ድንግል' አሏቸው:: ሲመነኩሱም 'ጽጌ ብርሃን' ተብለዋል:: ቀጥለውም በጾምና በጸሎት ሲጋደሉ: እመቤታችንንም ሲለምኑ ምሥጢር ተገለጠላቸው:: የእመ ብርሃንን ስዕለ አድኅኖ በአበባ ተከባ: በብርሃንም ተውጣ ተመለከቱ:: በዚህ ምክንያትም ዛሬ በጣፋጭነቱ የሚታወቀውን ማኅሌተ ጽጌን ፻፶ ዓርኬ አድርግው ደረሱ:: እስከ ዕለተ ዕረፍታቸውም እመቤታችንና ልጇን በገዳማቸው [ወለቃ አካባቢ የሚገኝ] ሲያመሰግኑ ኑረዋል:: ጻድቁ ያረፉት ጥቅምት ፳፯ ሲሆን ዛሬ የቃል ኪዳን በዓላቸው ነው:: ቸሩ መድኃኔ ዓለም የድንግል እናቱን ስደት አስቦ ከመንግስተ ሰማያት ስደት ይሠውረን:: ከስደቱ በረከትም ያድለን:: 🕊 [ † ኅዳር ፎ [ 6 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ] ፊ. ቅድስት ደብረ ቁስቁዋም [ሚጠታ ለማርያም] ፪. ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ ፫. ቅድስት ሰሎሜ ቡርክት ፬. ቅዱስ ዮሳ [ወልደ ዮሴፍ] ፭. ቅዱስ ቴዎፍሎስ ሊቅ ፎ. አባ ጽጌ ድንግል ዘወለቃ ፯. አባ ፊልክስ ዘሮሜ

ላሊበላ ፡- የብራና መጽሐፍ ነው ይነበባል ፡ ታሪክ ነው ይጠናል ፡ ቅርስ ነው ይጠበቃል ፡ መቅደስ ነው እንሳለመዋለን ፡፡ የላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናት መተኪያ የሌላቸው ውድ ማንነቶቻችን ናቸው
ላሊበላ ፡- የብራና መጽሐፍ ነው ይነበባል ፡ ታሪክ ነው ይጠናል ፡ ቅርስ ነው ይጠበቃል ፡ መቅደስ ነው እንሳለመዋለን ፡፡ የላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናት መተኪያ የሌላቸው ውድ ማንነቶቻችን ናቸው ማንነታችን አሻግረን የምንመለከትባቸው ዘመናትን የተሻገሩ ነጸብራቆች ናቸው፡፡ ጥንቃቄና ትኩረት ይሻሉ ልንጠብቃቸው ይገባል፡፡                  ሊቀ ሊቃውንት ስምዐኮነ መልአክ

" በእሸቅድምድም ሥፍራ የሚሮጡት ሁሉ እንዲሮጡ: ነገር ግን አንዱ ብቻ ዋጋውን እንዲቀበል አታውቁምን? እንዲሁም ታገኙ ዘንድ ሩጡ:: የሚታገልም ሁሉ በነገር ሁሉ ሰውነቱን ይገዛል:: እነዚያም የሚጠፋውን አክሊል ሊያገኙ ነው:: እኛ ግን የማይጠፋውን::" [፩ቆሮ.፱፥፳፬] † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   đŸ•Š                    đŸ’–

ሰላም ማጣት ማለት የአእምሮ ምስል ከሚዳሰሰው ጋር አልገጥም ሲልና መቀበል ሲያቅተን ነው! ሌሎች የማያዩት የማይረዱልን ከባድ ሕመም!!!

"ሲዖልን ማራኪ ማድረግ እንደማይቻል ዲያብሎስ ጠንቅቆ ያውቃል ስለዚህ ያለው አማራጭ ወደሲዖል የሚወስደውን መንገድ በቀላሉ የሚለመድ ሳቢ ውብና ማራኪ አድርጎ ማሳየት ነው።  መንገዱ የተመቸ ሁሉ መዳረሻውም ምቹ ላይሆን ይችላልና በሕይወት መንገድ ላይ አለን የምንል መንፈሳዊ ተጓዦች ቆም ብለን እንደቃሉ መመራት አለመመራታችንን እናስብ።" ታላቁ ቅዱስ ባስልዮስ

"አንቺ ሱላማጢስ ሆይ ተመለሽ ተመለሽ እናይሽ ዘንድ ተመለሽ" መኋ 7 ÷1 💐🌹🌺 ምሴተ ጥበብ ዘፍቁረ እግዚእ💐🌷🌺 📆 💐 ጥቅምት 26 ቀን 2016 ዓ.ም ⌚️🌺 ከቀኑ 11:30 ጀምሮ ⛪️
"አንቺ ሱላማጢስ ሆይ ተመለሽ ተመለሽ እናይሽ ዘንድ ተመለሽ" መኋ 7 á1  đŸ’đŸŒšđŸŒş ምሴተ ጥበብ ዘፍቁረ እግዚእ💐🌷🌺 📆 💐 ጥቅምት 26 ቀን 2016 ዓ.ም          ⌚️🌺 ከቀኑ 11:30 ጀምሮ                ⛪️🌹በሰንበት ት/ቤቱ አዳራሽ         🌾💐ሁላችሁም ተጋብዛችኋል።💐🌾

"እኛ ግን ይህን እንቃወም ከኃጢያት በቀር ምንም ክፉ ከበጎ ሥራ በቀርም ምንም በጎ እግዚአብሔርንም ደስ የሚያሰኘው ነገር እንዴሌለ ለይተን ልናውቅ ይገባናል። ደስታን የሚያመጣው መንፈሳዊ ጸሎት እንጂ
"እኛ ግን ይህን እንቃወም ከኃጢያት በቀር ምንም ክፉ ከበጎ ሥራ በቀርም ምንም በጎ እግዚአብሔርንም ደስ የሚያሰኘው ነገር እንዴሌለ ለይተን ልናውቅ ይገባናል። ደስታን የሚያመጣው መንፈሳዊ ጸሎት እንጂ ጽኑ መጠጥ አይደለም ደስታን የሚያመጣው ቃለ እግዚአብሔር እንጂ ወይን አይደለም..ወይን የነፍስ መታወክ ያመጣል ፡ቃለ እግዚአብሔር ግን ጸጥታን ያመጣል።ወይን የነፍስ ሁከትን ያመጣል፡ ቃለ እግዚአብሔር ግን ሁካታን ያርቃል። ወይን ዓይነ ልቡናን ያጨልማል ፡ ቃለ እግዚአብሔር ግን የጨለመውን ዓይነ ልቡና ያበራል። ወይን (ስካር) ቀድሞ ያልነበሩትን ኀዘናት ያመጣል፣ ቃለ እግዚአብሔር ግን ቀድሞ የነበሩትንም ሳይቀር ያርቃል። #ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ @DNESUBA @DNESUBA@DNESUBA

ተክለሃይማኖት | ዘማሪ ቀሲስ እስክንድር ወልደማርያም @Orthodox_Mezmur_For_All @Orthodox_Mezmur_For_All

+ ''ስለዚህ እንለምንሃለን ከቸርነትህም እንሻለን፤ሰውን የምትወድ ሆይ ክብርት የምትሆን ይህችን እለት እንድንፈፅም ስጠን፤ የህይወታችንን ዘመን ሁሉ በፍፁም ሰላም አንተን ከመፍራት ጋራ።''         ሥርዓተ ቅዳሴ

አንዳንድ ሰዎች ሰውን መውደድ ስህተትን መደበቅ ለእርሱ መከራከር ይመስላቸዋል ። ነገር ግን እውነተኛ ፍቅር ሰውን ከስህተቱ መጠበቅ ስህተቱን እስኪተው ድረስ መገሰፅ ሊሆን ይችላል። @DNESUBA @D
አንዳንድ ሰዎች ሰውን መውደድ ስህተትን መደበቅ ለእርሱ መከራከር ይመስላቸዋል ። ነገር ግን እውነተኛ ፍቅር ሰውን ከስህተቱ መጠበቅ ስህተቱን እስኪተው ድረስ መገሰፅ ሊሆን ይችላል።                           @DNESUBA @DNESUBA @DNESUBA

ምትጎላው ትንሽ ስህተት እንጂ መልካሙ ተግባርህ አይደለም! አየህ አንተ ብዙ ጊዜ እነርሱን ለማስደሰትና ለጥሩ ነገር ስትሰራ እነርሱ ግን አንተ ላይ ስህተት ለማግኘት ሲሰሩ ነበር ማለት ነው!!! መልካ
ምትጎላው ትንሽ ስህተት እንጂ መልካሙ ተግባርህ አይደለም! አየህ አንተ ብዙ ጊዜ እነርሱን ለማስደሰትና ለጥሩ ነገር ስትሰራ እነርሱ ግን አንተ ላይ ስህተት ለማግኘት ሲሰሩ ነበር ማለት ነው!!! መልካም አዳር! @DNESUBA @DNESUBA@DNESUBA

#ጭንቀት - አባታዊ ምክር እኛ ከእግዚአብሔር እድንርቅ ካደረጉን ነገሮች አንደኛው ጭንቀት ነው። ኦክስፎርድ ጭንቀት የሚለውን ሲተረጉመው "ከቁሣዊ ነገሮች ፍላጎት የሚመጣ ግፊት ወይም ውጥረት ይለዋል"  የተሻለው ትርጉሙ ግን አላስፈላጊ ነገሮችን ከመፈለግ የተነሣ የአእምሮ ወይም የስሜት ድካም፣ ውጥረት ወይም ሕመም ማለት ነው። ጭንቀት ለሕይወታችን  ከምንፈልጋቸው ወይም አላስፈላጊ ከሆኑ ነገሮች ፍላጎት የሚመጣ ግፊት ወይም ውጥረት ነው። ስለሆነም የጭንቀት መንስኤው ምንድን ነው? ስንል ተስፈኝነት ሆኖ እናገኝዋለን። በአጠገባችን ካሉ ሰዎች ቃል ከገቡልን፣ ከሚቀርቡን፣ ከቤተሰቦቻችን ወዘተ የምንጠብቀው አለ። ተስፈኝነት በሁለት መንገዶችሊመጣ ይችላል። ✞ስለ ሰወች ያለን ተስፈኝነት አለ። ሌላው ✞ሰዎች ሾለ እኛ አላቸው ብለን የምናስበው ነው። በማንኛውም መንገድ የተጨነቀ ሰው ከገጠማችሁ ከሁለቱ በአንዱ ምክንያት እነደሆነ ታረጋግጣላችሁ። ሌላ ሰው ለእኛ ዝቅተኛ ግምት ሠጥቶን ሊሆን ይችላል። ወይም እኛ ራሳችንን ዝቅ አድርገነው ሊሆን ይችላል። ወይም እግዚአብሔር እንደተወን አድርገን ልንወስድ እንችላለን። ወይም ከእግዚአብሔር እንደራቅን ሊሠማን ይችላል። ጭንቀት ከእነዚህ የአንዱ ስሜት ውጤት ነው። የቁስ እቃ ፍላጎት እንድንጨነቅ ያደርጋል። ምን ማድረግ እንዳለብን አናውቅም አንዳንድ ጊዜ አወንታዊ በሆነ መልኩ ለስሜቱ ምላሽ እንሰጣለን። አንዳንድ ጊዜ ደግሞ አሉታዊ መልስ እንሰጣለን። ሌላ ጊዜ ደግሞ አወንታዊም አሉታዊም  ሳይሆን ይቀራል። ከጭንቀት ለመላቀቅ የሚረዳ ዋነኛው ዘዴቤተ ተፈጥሮአዊ ማንነታችንን ማሰብ ነው። ቁሣዊ ሆነን አልተፈጠርንም። የተፈጠርነው በእግዚአብሔር አርአያ እና አምሳል ነው።  መቅደሱ ሆነን ነው የተፈጠርነው። ከእግዚአብሔር ጋር ለመኖር ነው የተፈጠርነው። ግፊቱም፣ ጭንቀቱም፣ ሕመሙና፣ ውጥረቱ፣ በመጣ ጊዜ ለእግዚአብሔር አሳልፈን መስጠት ይኖርብናል። ከእግዚአብሔር  ኃይል በላይ የሆነ ግፊት ወይም ውጥረት የለም። ስለሆነም እኔ ተሸክሜ ከምጨነቅ እግዚአብሔር እኔን ሆኖ እንዲሸከም አደርጋለሁ። እርሱ ጫናወቻችንን ያቀላል። ዮሴፍ በብዙ ጫናወች ውሰጥ ይኖር ነበር። ወድሞቹ ጉድጓድ ላይ ሲጥሉት ምናልባት መረዳት በማይችልበት በሕፃንነቱ ጊዜ ነበረ። እንደገናም ለባርነት ሸጡት። ከቤተሰቡም ጋር ተለይቶ መኖር ጀመረ። የንጉሱ የፈርኦን ሚስት በሐሰት ከሰሰችው። በዚህም የተነሳ እስር ቤት ተጣለ። በእስር ቤት እያለ ማንም የሚያስታውሰው አልነበረም። ይህ እንግዲህ መጠነ ሰፊ ወደ ሆነ ጫና ውስጥ ያመጣዋል። ሆኖም ግን ዮሴፍ እነዴት ለመፍታት ሞከረ? ችግሩን እነዴት ተቋቋመው? በእያንዳንዱ ሁኔታ ዮሴፍ ልሹ ዮሴፍ ነበረ። አልተለወጠም። በሁሉም ሁኔታዎች ተመሣሣይ፣ ማንነት፣ ፍቅር፣ እምነት፣ ነበረው። እግዚአብሔርን አዘውትሮ ይጠራ እና ይለምን ነበረ። እግዚአብሔርም ሁል ጊዜ አጠገቡ ነበረ። አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ

+++ "ለዚህ መች ጸለይን?" +++ በግብጽ ቤተ ክርስቲያን ቤተሰባዊ የሆኑ ችግሮችን ለመቅረፍ እንዲረዳ የተቋቋመ የካህናት (የቀሳውስት) ጉባኤ ነበረ። የቀድሞው የቅብጥ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ አቡነ ሺኖዳም ይህን ስብስብ እንዲቀላቀሉ ለአባ ሚካኤል ባቀረቡላቸው ጥሪ መሠረት የዚህ ጉባኤ አባል ሆኑ። ታዲያ አንድ ቀን አባ ሚካኤልን ጨምሮ የጉባኤው የበላይ ኃላፊ የሆኑት ጳጳስና ሌሎችም ካህናት የተጣሉ ባልና ሚስትን ሊያስታርቁ ተሰበሰቡ። ይሁን እንጂ የባልና የሚስትየው ጠብ እንዲህ በቀላሉ ሊበርድ የሚችል አልነበረምና ጳጳሱም ሆኑ ቀሳውስቱም ሁለቱን ለማስማማት ብዙ ቢጥሩም ግን አልተሳካላቸውም። በስተመጨረሻም ጳጳሱ ወደ አባ ሚካኤል እየጠቆሙ "አባ ሚካኤል ለምን ዝም ብለው ተቀመጡ? እስኪ እርሶ ይሻላል ብለው የሚያስቡትን ይንገሩን?" አሏቸው። አባ ሚካኤልም "ብፁዕነትዎ፣ እንጸልይበት!" አሉ። ጳጳሱም "ይህን ጉባኤ ከመጀመራችን በፊት እኮ ጸልየናል" ቢሏቸው አባ ሚካኤል "አዎን አባታችን፤ ለዚህ ችግር ግን አልጸለይንም" አሉ። ከዚያ ሁሉም ለጸሎት ተነሡ። በጳጳሱ ፈቃድ በአቡነ ሚካኤል መሪነት ጸሎት አደረጉ። ጸሎቱ እንዳለቀም እነዚያ የተጣሉት ባልና ሚስት ክርክራቸውን ሁሉ ትተው በጉባኤው ፊት በፍቅር ተቃቀፉ። ሰላም አወረዱ። ይህን ጊዜ ከቀሳውስቱ አንዱ "አባታችን ከመጀመሪያ እንዲህ ቢሉን ምን ነበር?! አሳረፉን እኮ" ብለው ጉባኤውን ፈገግ አሰኙት። እኛስ ያልጸለይንባቸው ስንት ችሮች አሉብን? ብዙ ቋጠሮ የሚፈታው ግን በብዙዎች የሚረሳው ትልቁ መፍትሔ፣ ጸሎት!!! (አባ ሚካኤል ኢብራሂም (1899-1975) የግብጽ ቤተ ክርስቲያንን ለበርካታ ዓመታት በትጋት ያገለገሉና እጅግ የሚያስቀና የጸሎት ሕይወት የነበራቸው አባት ናቸው።) @DNESUBA @DNESUBA @DNESUBA

እኔ አባታችሁና መምህራችሁ ነኝ፥ ሁላችሁ ልጆቼ ትእዛዜን አዳምጡ፤ በቅድስት ሥላሴ ማመንን እንድትከተሉና እንድትጸኑ እነግራችኋለሁና፤ የተወደዳችሁ ልጆቼ እርስ በእርሳችሁ በእውነተኛ ፍቅር ትዋደዱ ዘንድ እለምናችኋለሁ። የተወደዳችሁ ልጆቼ በፍጹም ሰብአዊነት መልካምን አንድታደርጉ እለምናችኋለሁ፤ ልጆቼ ዓለም እንድታታልላችሁ አትፍቀዱላት፤ በእግዚአብሔር አገልግሎት ዳተኞችና ቸልተኞች አትሁኑ ብዬ እለምናችኋለሁ። የተወደዳችሁ ልጆቼ ያለማቋረጥ እና_ያለ መታከት እንድትጸልዩ እለምናችኋለሁ፤ ልጆቼ መለያየትን ከሚያመጣ ንግግር አንደበታችሁን እንድትጠብቁ እለምናችኋለሁ። የተወደዳችሁ ልጆቼ የተጠመቃችሁባትን ቅድስቲቱን ጥምቀት እንድትጠብቋት እለምናችኋለሁ፤ የተወደዳችሁ ልጆቼ ሰውነታችሁን ለጌታ ንጹሕ አድርጋችሁ እንድትጠብቁ እለምናችኋለሁ። ልጆቼ መብራታችሁ ፈጽሞ እንዲጠፋ አትፍቀዱ ይልቅስ ብርሃንን እንዲሰጥ እንድታደርጉት እለምናችኋለሁ፤ ልጆቼ እግዚአብሔር የሰጣችሁን ትእዛዝ እንድትጠብቁ እለምናችኋለሁ። ልጆቼ  እግዚአብሔርን መፍራት ከእናንተ ጋር እንዲሆን እለምናችኋለሁ፤ የነገርኳችሁን ሁሉ ከጠበቃችሁ የእባቡንና የዘንዶውን ልሾ ትቀጠቅጣላችሁ፤ ያልኋችሁን ካደረጋችሁ የምድርን በረከት ትበላላችሁ፤ ብርሃናዊያን ኪሩቤል ይጠብቋችኋል፡፡ #ብፁዕ_አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ @DNESUBA @DNESUBA @DNESUBA

ከአገራችንም አልፈን አለምን ሰላም ያድርግን !🙏 ❝ሰማይንና ምድርን የፈጠርኽ ፥ ተስፋ የሚያደርጉኽን የማተው ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ዘንዶውን ድል እንዳደርግ ራሱንም እንድቀጠቅጥ ስለአደረከኝ አመሰግንሃለኹ ! ለባሪያዎችኽ ዕረፍት ስጣቸው፣ የጠላቶቻችን ግፍ የመጨረሻ ሰለባ ተጠቂ ነኝና ይኽን ዕረፍት ስጠኝ ! ለቤተክርስትያንኽ ሰላምን ስጣት ፥ ከዲያብሎስ ጨቋኝነት ንጠቃት። አሜን።        ÂŤ ቅዱስ ቴዎዶጦስ ዘዕንቆራ» @DNESUBA