Yeneta Courses
Open in Telegram
2 787
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
2 787
Question 31-35, ለናቹራሎች ከመሄዳቹ በፊት ይህን website እዩት 👍
https://www.examveda.com/mcq-question-on-arithmetic-ability/
2 787
#Update
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች #የመጨረሻ ቀን የፈተና መርሀ ግብር በመካሄድ ላይ ይገኛል።
ዛሬ ፈተናቸውን የሚያጠናቅቁት ተማሪዎች ከነገ ጀምሮ ወደየመጡበት አካባቢ የሚደረጉ ይሆናል።
የ2014 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ፈተና በዩኒቨርሲቲዎች እንዲሰጥ ከመደረጉ በላይ አንዳንድ ተቋማት ኩረጃን ለመከላከል ከመጀመሪያው ቀን አንስቶ የደህንነት ካሜራዎችን ሲጠቀሙ እንደነበር ለማውቅ ተችሏል።
የደህንነት ካሜራዎችን ተማሪዎች በግቢ ውስጥ ያላቸውን እንቅስቃሴ እና በፈተና ክፍል ያለው የፈተና ስርዓት ለመከታተል ነው ጥቅም ላይ እያዋሉ ያሉት።
ዘንድሮ ከታዩ በጎ በጎ ጅምሮች በተጨማሪ እንደ መጀመሪያ ጊዜም ስለሆነ #ክፍተቶች የነበሩ ሲሆን እነዚህን በቀጣይ የምናነሳቸው ይሆናል።
ትምህርት ሚኒስቴርም ፈተና እንዳለቀ አጠቃላይ የነበሩ አፈፃፀሞችን ላይ መግለጫ እንደሚሰጥ ተነግሮናል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን ፤ ተፈታኝ ተማሪዎች ፈተናቸውን እንዳይፈተኑ እና ጥለው እንዲወጡ የሚያበረታቱ የተለያዩ አክቲቪስት ነን የሚሉ አካላት ፣ የማህበራዊ ትስስር ገፆች መኖራቸውን ተመልክተናል።
የተማሪዎችን ህይወትን የፖለቲካ ቁማር መጫወቻ ለማድረግ የሞከሩም ብዙ ናቸው ፤ ድርጊቱ በነገ የሀገር ተረካቢ ልጆች ላይ ትልቅ ተፅእኖ ስላለው ቢታታረም መልካም ነው።
ገና ፈተናቸውን ያልወሰዱና ወደ መፈተኛ ተቋማት የሚገቡ በርካታ ተማሪዎች በመኖራቸው ያሉ ክፍተቶች እንዲታረሙ ለማደረግ መረባረብ እንጂ ማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ተማሪዎችን መረበሽ ፍፁም ተገቢ አይደለም።
ፎቶ ፦ አርሲ ዩኒቨርሲቲ እና ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ
🎖📖🎖
@Aplusacademy9_12
@Aplusacademy9_12
▬▬▬▬▬▬▬▬
2 787
" ተማሪዎቹ ከተሳሳተ ውሳኔያቸው እንዲመለሱና ወርቃማ ዕድላቸውን እንዲጠቀሙ የተቻለንን አድርገናል " - ዶክተር የህይስ አረጉ
የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር የህይስ አረጉ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና አንፈተንም ብለው ማዕከሉን ለወቀው በወጡ ተማሪዎች ጉዳይ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ዶ/ር የህይስ ፤ " በጤና ካምፓስ " የ12ኛ ክፍል ፈተና ከሚፈተኑ ተማሪዎች መካከል የተወሰኑ ተማሪዎች ፈተና ከበደን ወይም ቁጥጥር በዛብን በሚል ሰበብ ፈተና አቋርጠዉ ወጥተዋል ብለዋል።
አብዛኞቹ ተማሪዎች ግን ፈተናቸዉን በሰላም በመዉሰድ ላይ ይገኛሉ ሲሉ ገልፀዋል።
" ፈተና ጥለዉ የወጡ ተማሪዎች በአከባቢው አስተዳደር አማካኝነት ወደ ቤተሰቦቻቸው ተሸኝተዋል። " ያሉት ምክትል ፕሬዜዳንቱ " ከዚህ ውጭ የሚወራውና የሚዟዟረው መረጃ ፍፁም ስህተት ነዉ። " ብለዋል።
" ተማሪዎቹ ከተሳሳተ ውሳኔያቸው እንዲመለሱና ወርቃማ ዕድላቸውን እንዲጠቀሙ የተቻለንን ሁሉ አድርገናል " ሲሉም ገልፀዋል።
©Tikvah
🎖📖🎖
@aplusacademyy
@aplusacademyy
▬▬▬▬▬▬▬▬
2 787
ወደፈተና መልሷቸው!
አንዳንድ የፈተና ጣቢያዎች 12ኛ ክፍል ተፈታኞች አንፈተንም ማለታቸውን ተከትሎ "ይሂዱ" የራሳቸው ጉዳይ" "መኮረጅ ለምደው" ምናምን የሚል አስተያየት እያየን ነው! በተቃራኒው "ደግ አደረጋችሁ ግፉ እንዳትፈተኑ" የሚሉም አሉ! እንደኔ እንደኔ ምክንያቱ ምንም ይሁን ልጆቹን በጅምላ ከመዝለፍና ከማናናቅ እንዲሁም ለሌላ ኩርፊያ መጠቀሚያ ለማድረግ ከመገፋፋት ይልቅ እንደምንም አግባብቶ ወደፈተና የመመለስ ስራ መስራቱ የተሻለ ይመስለኛል! እነዚህ ልጆች አሁን ያገኙትን የመማር እድል ማስተዋል የማይችሉ ፣ስሜታዊነት የሚገፋቸው ፣ የአሁኑ ግርግር ነገ የሚያስከፍላቸውን ዋጋ አርቀው ማየት የማይችሉ ፣በህፃንነትና ወጣትነት ድንበር ላይ ያሉ ተማሪዎች ናቸው! ከፈተናው በኋላ ማንነታቸውን ውጤታቸው ይናገር!
👉ምናልባትም የዚህ አይነት ግርግሮች ብቃት ያላቸውን ተማሪዎች ጭምር ይዘው ሊሞቱ ይችላሉና ፈታኞች ወላጆች እና የሚመለከታቸው ልጆቹን ወደፈተና ለመመለስ ብቻ ቢጥሩ የተሻለ ነው!ለትችት እና ግሳፄው ሌላ ጊዜ ይደረስበታል!
🎖📖🎖
@aplusacademyy
@aplusacademyy
▬▬▬▬▬▬▬▬
2 787
#Update
ትምህርት ሚኒስቴር የመጀመሪያው ቀን የ12ኛ ክፍል ፈተና ተጠናቆ ተማሪዎች ለቀጣዩ ቀን ፈተና እየተዘጋጁ መሆኑን አሳውቋል።
በዛሬዉ እለት የተጀመረዉ 12ኛ ክፍል ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች የመጀመሪያ ዕለት ፈተና በሰላም መጠናቀቁን የገለፀው ሚኒስቴሩ " ሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ከተፈጠረዉ አሳዛኝ ክስተት እና በመቅደላ አምባ ዩኒቨርስቲ ፈተና ሳይፈተኑ ከወጡ ተማሪዎች ሪፖርት ዉጪ አጠቃላይ ሂደቱ የተሳካ ነበር " ብሏል።
ፈተናው በመላው ሀገሪቱ በ130 የፈተና ጣቢያዎች በ128 ጣቢያዎች ነበር ሲሰጥ የዋለው።
ትምህርት ሚኒስቴር የዛሬውን ፈተና ያጠናቀቁ ተማሪዎች በነገዉ እለት ለሚኖራቸዉ ፈተና ዝግጅት እያደረጉ እንደሚገኙ ገልጿል።
@tikvahethiopia
2 787
ያው ተማሪዎቹ ፈተና ላይ ስለተቀመጡ እና እንደተባለውም ስልክ ይዘው ካልገባቡ ሊያገኙ የሚችሉበት ዕድል በጣም ጠባብ ነው almost ዜሮ ነው ማለት ይቻላል!!
🎖📖🎖
@Aplusacademyy
@Aplusacademyy
▬▬▬▬▬▬▬▬
2 787
የአንድ ተማሪ ህይወት አልፏል
#Update
" እስካሁን ባለው የአንድ ተማሪ ህይወት ሲያልፍ ፤ ሁለት ከባድ ጉዳት እና ሌሎች መጠነኛ ጉዳት የደረሰባቸው ተማሪዎች በሀዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል ህክምና ላይ ይገኛሉ " - የሲዳማ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ
ዛሬ ጠዋት የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ዋናውን ግቢ እና የቴክኖሎጂ ካምፓስ ግቢን የሚያገኛኘው ድልድይ ተደርምሶ በ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች ላይ ጉዳት መድረሱንና በደረሰው ጉዳት ማዘኑን የሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ሰላምና ጸጥታ ቢሮ አስታውቋል፡፡
የሲዳማ ክልል የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቲዎስ ለደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት እንዳስታወቁት ፤ እስከአሁን ባለው ሂደት በጉዳቱ የአንድ ተማሪ ህይወት ሲያልፍ፣ ሁለት ከባድ ጉዳት እና ሌሎች መጠነኛ ጉዳት የደረሰባቸው ተማሪዎች በሀዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸዉ ይገኛል፡፡
እንደዚህ አይነት ሁኔታዎች ሲከሰቱ ተማሪዎች፣ የተማሪ ወላጆችና ህብረተሰቡ ትክክለኛ መረጃ ከሚመለከተው አካል ብቻ በማግኘት እንዲያረጋግጡና እንዲረጋጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
SRTA
2 787
#
በመቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ በምስራቅ ጎጃም እናርጅና እናውጋ ወረዳ ተማሪዎች ፈተናው ከመጀመሩ በፊት " #አንፈተንም " በሚል ለቀው ወጥተዋል።
@aplusacademyy
▬▬▬▬▬▬▬▬
2 787
ብሔራዊ ፈተናው መሰጠት ተጀምሯል
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ዛሬ መስከረም 30 መሰጠት ተጀምሯል።
ዛሬ ፈተናውን መውሰድ የጀመሩት የመጀመሪያ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ናቸው።
🎖📖🎖
@aplusacademyy
@aplusacademyy
▬▬▬▬▬▬▬▬
2 787
#Hawassa
" የተማሪ ወላጆች ተረጋጉ " - የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር
የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የተማሪ ወላጆች እንዲረጋጉ ጥሪ አቀረበ።
ዛሬ ጥዋት በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በደረሰው የድልድይ መደርመስ ምክንያት የተወሰኑ ተማሪዎች ላይ ጉዳት ደርሷል ያለው ከተማ አስተዳደሩ ጉዳት የደረሰባቸው ተማሪዎች በጤና ተቋማት በልዩ ሁኔታ ህክምና እንዲያገኙ እየተደረገ ነው ብሏል።
በመሆኑንም የተማሪ ወላጆች እንዲረጋጉ የከተማው አስተዳደር ጥሪ አቅርቧል።
🎖📖🎖
@aplusacademyy
@aplusacademyy
▬▬▬▬▬▬▬▬
2 787
#Update
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ድልድዩ የፈረሰው መሸከም ከሚችለው በላይ ተማሪ ወጥቶበት መሆኑን ገልጿል።
ዩንቨርስቲው ይህ የገለፀው ባወጣው መግለጫ ነው።
" ዛሬ ጥዋት የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች ከዋናው ግቢ ወደ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሲሸጋገሩ ሁለቱን ግቢዎች የሚያገናኘው ድልድይ ላይ ድልድዩ መሸከም ከሚችለው አቅም በላይ ተማሪዎች ሲወጡበት በመውደቁ አደጋ አጋጥሟል " ብሏል ዩኒቨርስቲው።
" በዚህ አደጋ ምክንያት ጥቂት ተማሪዎች ላይ መጠነኛ ጉዳት ደርሷል " ያለው ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጉዳት የደረሰባቸው ተማሪዎች የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑን ገልጿል።
የዛሬውን ፈተናው መፈተን ያልቻሉ ተማሪዎች ሌላ ዕድል ከት/ት ሚኒስቴርና የፈተናዎች ድርጅት ጋር በመነጋገር እንደሚመቻችላቸውም አሳውቋል።
🎖📖🎖
@Aplusacademy9_12
@Aplusacademy9_12
▬▬▬▬▬▬▬▬
2 787
#Update
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ድልድዩ የፈረሰው መሸከም ከሚችለው በላይ ተማሪ ወጥቶበት መሆኑን ገልጿል።
ዩንቨርስቲው ይህ የገለፀው ባወጣው መግለጫ ነው።
" ዛሬ ጥዋት የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች ከዋናው ግቢ ወደ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሲሸጋገሩ ሁለቱን ግቢዎች የሚያገናኘው ድልድይ ላይ ድልድዩ መሸከም ከሚችለው አቅም በላይ ተማሪዎች ሲወጡበት በመውደቁ አደጋ አጋጥሟል " ብሏል ዩኒቨርስቲው።
" በዚህ አደጋ ምክንያት ጥቂት ተማሪዎች ላይ መጠነኛ ጉዳት ደርሷል " ያለው ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጉዳት የደረሰባቸው ተማሪዎች የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑን ገልጿል።
የዛሬውን ፈተናው መፈተን ያልቻሉ ተማሪዎች ሌላ ዕድል ከት/ት ሚኒስቴርና የፈተናዎች ድርጅት ጋር በመነጋገር እንደሚመቻችላቸውም አሳውቋል።
🎖📖🎖
@Aplusacademy9_12
@Aplusacademy9_12
▬▬▬▬▬▬▬▬
2 787
#HawassaUniversity
ዛሬ ጠዋት መስከረም 30/2015 ዓም በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የሚፈተኑ የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች የዩኒቨርስቲዉን ሁለት ካምፓሶች የሚያገናኝ ድልድይ በመፍረሱ ምክንያት ድልድዩን ሲሻገሩ በነበሩ ተማሪዎች ላይ ጉዳት መድረሱን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
ጉዳት የደረሰባቸው ተማሪዎች በሀዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸዉ እንደሚገኝ ሚኒስቴሩ ገልጿል።
" ሁኔታቸዉን መላዉ የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ እና የትምህርት ሚኒስቴር ግብረሀይል በቅርበት እየተከታተለ " ነው ያለው ትምህርት ሚኒስቴር " ወላጆች እንዳይደናገጡ እንጠይቃለን " ብሏል።
ጉዳት የደረሰባቸዉ ተማሪዎች በቀጣይ በሚሰጠዉ ፈተና የሚፈተኑ መሆኑን የገለፀው ሚኒስቴሩ ሌሎች ተማሪዎች በአጋጣሚዉ ሳይረበሹ ተረጋግተዉ እንዲፈተኑ አሳስቧል።
ሁኔታዉን በሚመለከት ዝርዝር መረጃዎችን በቀጣይ እንደሚያሳውቅም የትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።
@tikvahethiopia
2 787
በህዳሴ ግድብ፣ አረንጓዴ አሻራ እና የስንዴ ምርት ያየነውን ውጤት በትምህርት ጥራት እንደግመዋለን - ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ
----------------------------------------------
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በመላው አገሪቱ የሚገኙ የ12ኛ ክፍል ፈታኝ መምህራንን በበየነ መረብ አግኝተው መልዕክት አስተላልፈዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የፈተና ስርዓቱ በባለፋት አመታት ባልተገባ ሁኔታ የተለያዬ ፍላጎት ባላቸው አካላት ለችግር የተጋለጠ እንደነበር ጠቅሰው ዘንድሮ ከዚህ ችግር ለመላቀቅ በተደረገው ጥረት የመምህራን ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ሃላፊነታቸውን በታማኝነት እንዲወጡ አደራ ብለዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በበኩላቸው እስካሁን በፈተናው ሂደት ከቅድመ ዝግጅት ጀምሮ የነበረው ዝግጅት የተሳካ እንደሆነ ገልጸው በተጀመረው መንገድ በስኬት እንዲጠናቀቅ ፈታኝ መምህራንን ጨምሮ በሂደቱ ድርሻ ያላቸው አካላት በመተባበርና በፍጹም የሃላፊነት ስሜት እንዲሰሩ አሳስበዋል ።
አሁን በሁሉም 12ኛ ክፍል ፈታኝ ዩኒቨርስቲዎች ለፈታኞች ገለጻ እየተደረገ የሚገኝ ሲሆን ከሰዓት በኋላ ደግሞ የተፈታኞች ገለጻ የሚደረግ ይሆናል።
2 787
የኒቨርስቲዎች በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና አሰጣጥ ዙሪያ ኦረንቴሽን እየሰጡ ነው።
------------
ዩኒቨርስቲዎች የ12ኛ ክፍል ፈተና ለመፈተን ለተመደቡ የፈተና ጣቢያ ኃላፊዎች፣ ለሱፐርቫይዘሮች፣ ለፈታኞች፣ ማየት ለተሳናቸው ተፈታኝ አንባቢዎችና ለመልስ ወረቀት ቆጣሪዎች ኦሬንቴሽን እየሰጡ ነው።
ዩኒቨርስቲዎቹ በተመሳሳይ ለተፈታኝ ተማሪዎች ስለ ፈተና ሰርዓቱ ኦረንቴሽን በመስጠት ላይ ናቸው።
የ12ኛ ክፍል ፈተና ተፈታኞች ከመስከረም 26 ጀምሮ ወደየተመደቡበት ዩኒቨርስቲ ሲገቡ መቆየታቸው ይታወሳል።
የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከነገ ጀምሮ የሚሰጥ ይሆናል።
🎖📖🎖
@Aplusacademy9_12
@Aplusacademy9_12
▬▬▬▬▬▬▬▬
2 787
የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ(ዶ/ር) መልዕክት ለ12ኛ ክፍል ተፈታኞች
የሀገራችን የነገ ተስፋዎች ሆይ
ኢትዮጵያ እናንተን ስታይ ተስፋ ነው የሚታያት። ይህ የምትፈተኑት የ12ኛ ክፍል ፈተና ለኢትዮጵያ እውነተኛ ተስፋዎች መሆናችሁን የምታረጋግጡበት እንደሚሆን አምናለሁ። እናንተን እዚህ ለማድረስ ወላጆች፣ መምህራን እና መላው ማኅበረሰብ ለዓመታት ለፍቷል። ውጤቱን የምታሳዩት ከኩረጃና ከስርቆት ነጻ ሆናችሁ፣ በራሳችሁ ተማምናችሁ፣ ፈተናውን ስትፈተኑ ነው።
የተሰጣችሁን መመሪያ አክብሩ፤ ተረጋግታችሁ ፈተናችሁን ሥሩ፤ በምንም አትሸበሩ፤ የኢትዮጵያ አምላክ ዕውቀቱን ይግለጥላችሁ።
2 787
#ማሳሰቢያ:-
ተፈታኞቻችን ወደ መፈተኛ ማዕከላት ገብተዋል፡፡ የተከለከሉ ነገሮችን ማንም ተፈታኝ ይዞ እንዳይገባ ከወረዳ ጀምሮ ገለጻ ተደርጓል፡፡ በተጨማሪም አካላዊ ፍተሻ ተደረጓል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ የተለያየ የማጭበርበሪያ ዘዴዎችን በመጠቀም የተከለከሉ ነገሮችን በተለይም ተንቀሳቃሽ ስልክን ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ይዘው የተገኙ ተፈታኞች በህግ ቁጥጥር ስር ይገኛሉ፡፡ ድርጊቱ ከፍተኛ የፈተና ደንብ ጥሰት በመሆኑ ውሳኔው ከሁሉም ፈተና የሚሰረዙ ይሆናል፡፡
በተመሳሳይ ከዚህ በኃላም የተከለከሉ ነገሮችን መፈተኛ ማዕከላት (የኒቨርሲቲ) ግቢ ውስጥ ማንኛውም ተፈታኝ ይዞ ቢገኝ ከሁሉም ፈተና የሚሰረዝ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ገለጻውን ባለመቀበልና አካላዊ ፍተሻዎችን በማጭበርበር ስለፈጸመው ጉዳይ ተጨማሪ ህጋዊ ምርመራ የሚካሄድ ሲሆን እንደግኝቱም ተመጣጣኝ ህጋዊ እርምጃ የሚወሰድ ይሆናል፡፡
ፈተና የሁሉም ማህበረሰብ ሀብት በመሆኑ ሁሉም ዜጋ ለፈተና ደህንነትና ፍትኃዊነት የበኩሉን አዎንታዊ ድርሻ እንዲወጣ ጥሪ እናቀርባለን፡፡
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
🎖📖🎖
@Aplusacademy9_12
@Aplusacademy9_12
▬▬▬▬▬▬▬▬
2 787
የ85 ዓመት ዕድሜ ባለጸጋው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኝ...
አቶ ባፋ ባጋጄ ኦሊቶ ይባላሉ ውልደታቸው እና ዕድገታቸው በወላይታ ዞን ባይራ ኮይሻ ወረዳ ልዩ ስሙ ቦካማ ፌቃቃ በሚባል ስፍራ ነው።
አቶ ባፋ ባጋጄ ዛሬ ላይ የ85 ዓመት ዕድሜ ባለጸጋ ሲሆኑ፤ የስምንት ልጆች አባትም ናቸው ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ለ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከተቀበላቸው ተፈታኞች መካከል በዕድሜ አንጋፋ ሆነው ተገኝተዋል።
በዚህ ዕድሜዎ ለትምህርት ምን አነሳሳዎት ተብለው ሲጠየቁ “በአካባቢው በሚገኝ ትምህርት ቤት ልጆቼን ለትምህርት ልኬ አልማርም ብለው ሲመለሱ እነርሱን ለማበረታታ እንዲሁም በአካባቢያችን በተለያዩ ምክንያቶች ከትምህርት ወደኋላ የቀሩትን ነዋሪዎች ለማበረታታት ነው በዚህ ዕድሜዬ ትምህርት የጀመርኩት” ሲሉ ተደምጠዋል።
የእርሳቸውን ፈለግ በመከተል ትምህርታቸውን አቋርጠው የነበሩ ልጆቻቸው አሁን እየተከታተሉ እንደሆነም መናገራቸውን ከወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
Via- tikvah magazine
🎖📖🎖
@Aplusacademy9_12
@Aplusacademy9_12
▬▬▬▬▬▬▬▬
