Yeneta Courses
Open in Telegram
2 787
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
2 787
የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ግንቦት ወር ውስት ይሰጣል
ዘንድሮ ወደ 12ኛ ክፍል ያለፉ ተማሪዎች በመደበኛው ጊዜ ማለትም ግንቦት ወር ላይ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተናቸውን ይወስዳሉ። የትምህርት ካላንደሩም ወደ ድሮው ስርአት ይመለሳል።
🎖📖🎖
@aplusacademyy
@aplusacademyy
▬▬▬▬▬▬▬▬
2 787
#Update
የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች በወጣላቸው የጉዞ መርሃ - ግብር መሰረት ለፈተና ወደየተመደቡባቸው ዩኒቨርስቲዎች እየተሸኙ ይገኛሉ።
ከዚህ ባለፈም ሰኞ ለሚጀምረው ፈተና ወደፈተና ማዕከሎቻቸው እየገቡ የሚገኙ ተማሪዎችም ያሉ ሲሆን በሚገቡበት ተቋም እንዲሁም ከመነሻቸው የፀጥታ አካላት ፍተሻ እያደረጉ ይገኛሉ።
በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚሰጠው ብሄራዊ ፈተና በሰላም እንዲጠናቀቀ እንዲሁም የተማሪዎች ደህንነት እና የተቋማት ሰላም እንዲረጋገጥ 8,000 የፌዴራል ፖሊስ ይሳተፋሉ።
NB. የእስልምና እምነት ተከታዮች መስከረም 28 የመዉሊድ በዓል አክብረዉ መስከረም 29/2015 እሁድ ጠዋት መግባት እንዲችሉ በልዩ ሁኔታ የተፈቀደላቸዉ መሆኑ ትምህርት ሚኒስቴር ማሳወቁ ይታወሳል።
🎖📖🎖
@Aplusacademy9_12
@Aplusacademy9_12
▬▬▬▬▬▬▬▬
2 787
#ሼር
የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት መስከረም 30 /2015 ከሚጀምረው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ጋር በተያያዘ የዩኒቨርሲቲ እና ዩኒቨርሲቲ ካምፓሶች አድራሻ አሰራጭቷል ፤ ከላይ ይመልከቱ።
🟢 🟢
🎖📖🎖
@Aplusacademy9_12
@Aplusacademy9_12
▬▬▬▬▬▬▬▬
2 787
ነገ ለምትሄዱ የ social science ተፈታኞ ፈተና እስከሚአልቅ ስለማንገናኝ ካሁኑ Good luck ልበላችሁ don't worry ...you will rock it! የምታውቁትን ነገር በተሰጣችሁ ጊዜ to the maximum ሰርቶ ለማጠናቀቅ ሞክሩ እና የማታውቁዋቸውን መጨረሻ ላይ አስቀርታችሁ 👌አሪፍ guessing techniques ተጠቅማችሁም ቢሆን ለመስራት ሞክሩ
በተረፈ የቻላችሁትን አድርጉ ቀሪው የ ፈጣሪ ሥራ ነው 🙏
🎖📖🎖
@aplusacademyy
@aplusacademyy
▬▬▬▬▬▬▬▬
2 787
#ማስታወቂያ
መስከረም 30/2014 ዓ.ም. ለሚጀምረው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ አገር አቀፍ ፈተና የመጀመሪያ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች መስከረም 26-28 ተጠቃለው በመግባት መስከረም 29 ስለፈተናውና ተያያዥ ጉዳዮች በየተመደቡባቸው ዩኒቨርስቲዎች ገለጻ የሚደረግበት ዕለት መሆኑን መግለጻችን ይታወሳል፡፡
ሆኖም የእስልምና እምነት ተከታዮች መስከረም 28 የመዉሊድ በዓል አክብረዉ መስከረም 29/2015 ዓም እሁድ ጠዋት መግባት እንዲችሉ በልዩ ሁኔታ የተፈቀደላቸዉ መሆኑን እና የፈተና እና ተያያዥ ጉዳዮች ገለጻ /Orientation/ ይህንን ታሳቢ ባደረገ መልኩ እሁድ ከሰዓት በኋላ እንዲሰጥ መደረጉን በአክብሮት እየገለጽን የእምነቱ ተከታይ ተማሪዎችም ይህንን አዉቃችሁ በተጠቀሰዉ ሰዓት በመገኘት ገለጻ /Orientation/ እንድትከታተሉ እናሳስባለን ፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር !
🎖📖🎖
@aplusacademyy
@aplusacademyy
▬▬▬▬▬▬▬▬
2 787
#ለወላጆች
" ወላጆች ያምኑናል ብለን ተስፋ እንደርጋለን " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ
የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ተፈታኞች ከቤተሰባቸው ርቀው ነው ፈተናውን የሚወስዱት በዚህ ወቅት ስልክን ጨምሮ ምንም አይነት የመገናኛ ቁሳቁስ ይዘው መሄድ አይችሉም ፤ ተማሪዎቹ ከቤተሰቦቻቸው ጋር መገናኘት ባለመቻላቸው የሚፈጠር #የስነልቦና_ጫና ይኖር ይሆን ? ይሄ እንዴት ይታያል ? የወላጆች ኃላፊነትስ ምንድነው ?
ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ (የትምህርት ሚኒስትር) ለብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ የተናገሩት ፦
" .... ሆን ብለው ችግሮችን ለመፍጠር ካሰቡ ብዙ ምክንያቶችን ማድረግ ይቻላል ግን አሁን እነዚህ ልጆች ማትሪክ ሲያልፉ ከቤተሰቦቻቸው ወጥተው ሊኖሩ ነው አይደለም እንዴ ለረጅም ጊዜ ፤ ለአራት ቀን ለአምስት ቀን ሲሆን እንደውም በዛ እድሜ ላይ ያሉ ልጆች ደስ እያላቸው የሚሄዱ ነው የሚመስለኝ።
ይሄ አድቬንቸርም ነው ከቤት ወጥተው ፣ ዩኒቨርሲቲ ሄደው ይፈተናሉ ይሄ አዲስ ነገር ነው። በዚህ አመት ለሚያደርጉት ይሄ ነገር የተጀመረው የመጀመሪያዎቹ ተማሪዎች ስለሚሆኑ ለልጆቻቸውም የሚነግሩት ነገር ይዘው ነው የሚሆነው ፤ ታሪካዊም ነው። ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ይሄ የተደረገው ፤ በእኛ ጊዜ ነው ይሄ የሆነው ፣ ይሄ ነገር ምን አለው የሚለውን ያያሉ።
በእኛ በኩል ዋና ኃላፊነታችን ሰላማቸው እንዲጠበቅ ማድረግ ፣ በምግብ ችግር እንዳይኖርባቸው ማድረግ ፣ ህክምና ማዘጋጀት በየዩኒቨርሲቲዎቹ ይሄንን እያዘጋጀን ነው።
ሰላም መግባታቸውን ፣ ችግር በሚኖር ጊዜ ለማሳወቅ ከየክልሉ ትምህርት ቢሮ ተወካዮች አሉ አብረው የሚመጡ ወደ ግቢ አይገቡም ፤ ግን ችግር በሚኖር ጊዜ ከእነሱ ጋር ግንኙነት እየተደረገ ለቤተሰቦቻቸው መንገር የሚቻልበትን መንገድ አስቀምጠናል።
ሁሉን ነገር ለማየት ሞክረናል ይሄ ነገር አዲስ ስለሆነ ቀላል የሎጅስቲክስ ስራ አይደለም አንድ ሚሊዮን የሚደርስ ሰው አንቀሳቅሶ ይሄን ማድረግ በተወሰነ ደረጃ እንደ ሀገርም ያውም ጦርነት እየተዋጋን ባለንበት ሁኔታ መንግስት ይሄን ማድረግ መቻሉ በእውነት የሚገርም ነው። እኛ ውስጥ ስላለንበትም እያየን ስለሆነ ነው ይሄን የምናገረው ቀላል የሎጅስቲክስ ስራ አይደለም።
እጅግ በጣም ብዙ ሰው ነው የሚሳተፍበት ወደ 8 ሺ የፌዴራል ፖሊስ ይሳተፍበታል ፣ ሰላሳ / አርባ ሺህ ፈታኞች ከየዩኒቨርሲቲው ወጥተው ይሳተፋሉ ፣ ብዙ ምግብ አብሳዮች ይሳተፋሉ። በአጠቃላይ ትልቅ ሀገራዊ እንቅስቃሴ ነው። እንደ ሀገርም ችሎታችንን አቅማችንን፣ በተወሰነ ደረጃ እየተጠናከረ ትላልቅ ነገሮችን ለመስራት ያለን ብቃት እየጨመረ የሚሄድበት ነው ፤ ስለዚህ ደስ የሚልም ነገር አለው።
ለቤተሰቦች የምንለው በተቻለን መጠን የልጆቻችሁን ኃላፊነት ወስደን ነው ይሄን ነገር የምንሰራው። እንደ ልጆቻችን ልንጠብቅ ፣ እንደ ልጆቻችን እንዳይራቡ እንዳይጠሙ ልናደርግ ፤ ምንም አይነት የደህንነት አደጋ ውስጥ እንዳይገቡ ተጠንቅቀን ነው ይሄንን ነገር የምናደርገው። ያ ማለት ግን ምንም ነገር አይፈጠርም ማለት አይደለም መቶ በመቶ ማረጋገጫ መስጠት አይቻልም።
ማንኛውም ተማሪ ወደዚህም ቦታ ባይመጣ ቤቱም ሆኖ ሊታመም ይችላል ግን በእኛ በኩል ከህክምና ጋር በተያያዘ የጤና ባለሞያዎችን በየቦታዎቹ ላይ አስቀምጠናል ፤ ችግር በሚኖር ጊዜ ልጆቹ ህክምና እንዲያገኙ።
ቁርሳ ፣ ምሳ እንዲሁም እራታቸውን እንመግባቸዋለን ፤ ምግብ እንኳን ስናዘጋጅ የሃይማኖት ፤ የባህል ነገሮችም እንዳይመጡ እሱን ሁሉ ጥንቃቄ እያደረግን ነው። ወላጆች ያምኑናል ብለን ተስፋ እንደርጋለን።
...ወላጆች ትልቅ ኃላፊነት አለባቸው። ልጆቻቸው ወደ ፈተና በሚሄዱበት ጊዜ ትብብር ማድረግ ፤ ፈተናውን ለመፈተን በሚሄዱበት ጊዜ የተከለከሉ ነገሮችን ይዘው እንዳይሄዱ ከቤት ነው ይሄ ነገር የሚጀምረው ምክንያቱም የ12 ዓመት ጥረት አፈር ነው የሚገባው አንድ የተከለከለ ነገር ይዘው ቢገቡ ፤ ስለዚህ እኛ እንደውም ፍተሻው ፖሊስ ጋር መጥቶ ከመድረሱ በፊት ቤት ወላጆች ናቸው አይተው መላክ ያለባቸው።
ወላጆች ለልጆቻቸው የሚሰጧቸው የሚያስፈልጋቸው ነገሮች ይኖራሉ ለምሳሌ ፦ እንደ ደረቅ ምግብ ድንገት ለሊት ሲያጠኑ ቢያስፈልጋቸው ቆሎም ይሁን ሌላ የሚሰጧቸው ነገር ካለ ፣ አንሶላ፣ ብርድልብስ እነዚህን እንደሚያዚዟቸው ሁሉ የዛን ያህል የተከለከሉ ነገሮችን እንዳይዙ መቆጣጠር አለባቸው፤ ይህንንም ያደርጋሉ ብለን እናምናለን።
ከዛ ውጭ በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የሚጮኸውን አለመስማት ነው ፤ ምክንያቱም ዋነኛው ስራቸው በእንዲህ አይነት ነገር ማህበረሰብን ማሸበር እንደ ችሎታ እና እንደእውቀት የወሰዱ ጤነኛ ያልሆኑ ብዙ ሰዎች ያሉበት ዘመን ላይ ነው ያለነው።
ወላጆች የልጆቻችሁን ጉዳይ በሚመለከት በቀንጥታ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር፤ የምንነግራችሁ ቁጥሮች አሉ፣ የምንልካቸው የአካባቢው ትምህርት ተወካዮች አሉ በዛ በኩል መገናኘት ያስፈልጋል።
አንድ ነገር ቢፈጠር #በእርግጠኝነት የምንነግራችሁ ፤ ከእኛ ውሸት አትጠብቁ የሆነውን ነገር ይሄ ነው የሆነው ብለን እንነግራችኃለን። ምንም የምንደብቅበት ምክንያት የለም።
ይሄ የፖለቲካ ስራ አይደለም ፤ ይሄ የትምህርት ስራ ነው። የትምህርት ስራ ደግሞ ሁላችንንም የሚያገናኝ እና የሚያጣብቅ ስራ ነው።
ወላጅን ከአስተማሪዎች፣ አስተማሪዎችን ከአጠቃላይ የትምህርት ስርዓቱና ከትምህርት አስተዳዳሪዎች ጋር የሚያይዘው ውስጣችን ለልጆቻችን ጤንነት ፤ ለልጆቻችን የእውቀት ጥማት እና ህይወትን ለማሻሻል የሚያደርጉትን ጥረት ከማገዝ በላይ ምንም ሌላ ነገር የለም ከዚህ የሚገኝ የፖለቲካ ጥቅም ሆነ ትርፍ የለም።
ይሄን ማወቁ ምንም የፖለቲካ ልዩነቶች እንኳን ቢኖሩ ትምህርትን የዛ መጠቀሚያ አናድርገው ፣ ትምህርትን ከዛ ውስጥ እናውጣው ትምህርት ስለልጆቻችን ነው። "
🟢 🟢
🎖📖🎖
@Aplusacademy9_12
@Aplusacademy9_12
▬▬▬▬▬▬▬▬
2 787
የትምህርት ሚኒስቴር የብሔራዊ ፈተናን በተመለከተ ፦
(ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ - የትምህርት ሚኒስትር)
- የፈተና ንክኪው በእጅጉ ተቀንሷል።
- ከዚህ በፊት በፈተና አሰጣጥ ወቅት የነበረውን " የኔ አካባቢ ሰው ፣ የኔ ዘመድ " የሚለውን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት ማንኛውም የአንድ አካባቢ ተወላጅ እዛው አካባቢ ያሉ ተማሪዎችን አይፈትንም። ማንኛውም የአንድ ዩኒቨርሲቲ አስተማሪ እራሱ የሚያስተምርበት ዩኒቨርሲቲ ውስጥ አይፈትንም።
- ተማሪዎች አንዴ ዩኒቨርሲቲ (ካምፓስ) ከገቡ በኃላ ከሌለው የውጪ ማህበረሰብ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት አይኖራቸውም። ምንም ስልክ ወይም ሌላ የግንኙነት ነገር ይዘው አይገቡም።
- ተፈታኝ ተማሪዎች ለ4 ቀናት ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲገቡ እናበላቸዋለን ፣ እናጠጣቸዋል፣ እንከባከባቸዋለን ነገር ግን በፍፁም ከሌላው ዓለም ጋር አይገናኙንም።
- ተማሪዎች ከሚነሱበት ቦታ የተከለከሉ ነገሮችን ይዘው እንዳይሄዱ የክልል የፀጥታ ኃላፊዎች የፍተሻ ስራ ይሰራሉ፤ የክልል የፀጥታ አከላት ስራ ተማሪዎቹ ዩኒቨርሲቲ በር ላይ እስኪደርሱ ብቻ ነው ከዛ በኃላ ያለውን የፍተሻ እና ጥበቃ ስራ የፌዴራል ፖሊስ አባላት ይሆናሉ።
- ስልክ ይዞ አንድ ተማሪ ቢገኝ ስልክ ይቀማል ሳይሆን ሙሉ በሙሉ ፈተናውን እንዳይወስድ ይደረጋል።
- ተማሪዎች በምንም ሁኔታ ፈተና ከሚወስዱበት ግቢያቸው ውጭ መውጣት አይችሉም፤ ከማንም ጋር መገናኘት አይችሉም።
- ከፍተኛ ዝግጅት እያደረግን ስለቆየን ችግር ይኖራል ብለን አናምንም።
- በእስር ላይ ላሉ፣ በውጭ ላሉ የኮሚኒቲ ት/ቤቶች ፣ በፀጥታ ምክንያት ፈተናውን ለመውሰድ ለማይችሉ ሌላ ሁለተኛ ፈተና ተዘጋጅቶላቸዋል። በአንድ ወር ውስጥ ይሰጣቸዋል።
የተፈጥሮ እና ሶሻል ሳይንስ ተማሪዎች በተለያየ ጊዜ መፈተናቸውን ተከትሎ ተመሳሳይ የሆኑ ትምህርቶች እንዴት ይሰጣሉ ?
በትምህርት ሚኒስቴር መግለጫ ላይ እንደተገለፀው የፈተና ስርቆትን ለማስቀረት እና ኩረጃን ለመከላከል በ2ቱ ዙር ተፈታኞች መካከል ምንም አይነት ግኝኑነት አይኖርም።
የመጀመሪያው ዙር ተፈታኞች ፈተናቸውን ጨርሰው ከወጡ ከቀናት በኃላ ነው ሁለተኛው ዙር ተፈታኞች የሚፈተኑት።
ሁለቱም የሚወስዷቸው (የናቹራል እና ሶሻል) አንድ አይነት ትምህርቶች ላይ ጥንቃቄ ተደርጎ የተለያዩ ፈተናዎች ናቸው የተዘጋጁት።
ተማሪዎች ስልክ ይዘው ባለመሄዳቸው ከወላጆቻቸው ጋር እንዴት ይገናኛሉ ?
ትምህርት ሚኒስቴር ኩረጃን እና ስርቆት ለመከላከል ሲባል ተማሪዎች ወደ ሚፈተኑበት ተቋም ስልክ ይዘው መግባት እንደማይችሉ አሳውቋል።
ተማሪዎች ብቻ ሳይሆኑ ፈታኞችም የፈተና ክፍሎች አቅራቢያ እና ፈተናው የሚሰጥበት አካባቢ ስልክ ይዘው መገኘት አይችሉም።
በየዩኒቨርሲቲዎቹ አንድ አንድ ተወካይ የሚኖር ሲሆን በተወካዩ አማካኝነት ወላጆች ልጆቻቸውን ያሉበትን ሁኔታ ለማወቅ ይችላሉ።
የህትመት ዝግጅቱ ምን ይመስላል ? የፈተናው ኮዶች ስንት ናቸው ?
በአጠቃላይ የህትመት ዝግጅቱ በቴክኖሎጂ የታገዘ እና ጥንቃቄ የተደረገበት ሲሆን የፈተናው ኮዶች በፊት ከነበረው " 4 ኮድ " ወደ " 12 ኮድ " ከፍ ተደርጓል።
ለወላጆች የተላለፈ መልዕክት ፦
ወላጆች ተማሪዎች ይዘው መሄድ የሌለባቸው ፣ እና ስለሚጠበቅባቸው ግዴታቸው አስገንዝበው መላክ አለባቸው።
via- tikvahethiopia
🎖📖🎖
@aplusacademyy
@aplusacademyy
▬▬▬▬▬▬▬▬
2 787
የፈተና ኮሮጆዎች ከዛሬ ጀምሮ ወደ መፈተኛ ጣቢያቸው ይጓጓዛሉ ፤ጐስለሆነም ከዩንቨርስቲዎች ግቢ አካባቢ ያለ ምክንያት መቆም፣ ፎቶ ማንሳት ፈጽሞ የተለከለ ነዉ።
ከብርሃንናሰላም ማተሚያ በ ፈተናዎች አገልግሎት አመራርነት ና በፌዴራል ፖሊስ እጀባ ወደ ጣቢያ ይላካሉ ።
ፕ/ር ብርሀኑ ነጋ ከ2008 ጀመሮ እስከ አምናው ፈተና ድረስ ፈተናዎች በ ሚጓጓዙበት ወቅት ከስርጭት አንጻር ስርቆት እንዳለ መናገራቸው ይታወሳል
ዘንድሮ ይህ እንዳይደገም ከ2100 በላይ የነበረው የመፈተኛ ጣቢያቁጥር ከ150 በታች ወርዶ ስርጭቱ በተሳለጠ መንገድ ለማከናወን ዝግጅት መጠናቀቁን ሚንስትር መሥሪያቤቱ አስታውቋል ።
2 787
የፈተና ኮሮጆዎች ከዛሬ ጀምሮ ወደ መፈተኛ ጣቢያቸው ይጓጓዛሉ
ስለሆነም ከዩንቨርስቲዎች ግቢ አካባቢ ያለ ምክንያት መቆም ፣ ፎቶ ማንሳት ፈጽሞ የተለከለ ነዉ።
ከብርሃንናሰላም ማተሚያ በ ፈተናዎች አገልግሎት አመራርነት ና በፌዴራል ፖሊስ እጀባ ወደ ጣቢያ ይላካሉ ።
2 787
🔟 መረጋጋትና በጎ በጎውን ማሰብ
እስካሁን የተዘረዘሩትን ነገሮች ሁለ ተግባራዊ ካደረጋችሁ ምንም የሚያሳስባችሁ ነገር ሊኖር አይገባም። ዘና ብሊችሁ ወደ ፈተና መግባት ብቻ ነው የሚቀራችሁ። ምናልባት ጥሩ ያልሆነ አጋጣሚ ቢገጥማችሁ እንኳን እሱን ረስታችሁ ለቀጣዩ በጥሩ መንፈስ ለመዘጋጀት ሞክሩ።
በተለይ ደግሞ ለማህበራዊ ሚዲያ ጆሮ አትስጡ።
በመጨረሻም በእያንዳንዱ ጥሩ የፈተና ጊዜ ለራሳችሁ ሽልማት መስጠት አትርሱ።
1⃣1⃣ የሚጠቅምህን አድርግ😃
በመጨረሻም, ሁሉም ሰው የተለየ ነው. አንዳንድ ሰዎች በፈተና ዙሪያ ብቻቸውን መሆን ይወዳሉ፣ ምናልባት አንተ ለዕድል የእነሱን አንጸባራቂ ጥንድ ረጅም ጫማ መልበስ የምትወድ ሰው ትሆን ይሆናል። በተሻለ የአእምሮ ማእቀፍ ውስጥ የሚያስገባዎትን ማንኛውንም ነገር ያድርጉ እና ፈተናውን ለመጨረስ በትክክል ይዘጋጃሉ።
in short በራስዎ አለም ይመሰጡ ( enter your own world men 😌)
ካለኝ ግዜ ላይ ሰውቼ ይቺን ትንሽ መጣጥፍ ጀባ ያልኳችሁ ወንድማችሁ Fitsum helina ( Academic Therapist ) ነበርኩ መልካም ፈተና ተመኘሁ
አ መ ሰ ግ ና ለ ሁ
I WISH ALL THE BEST FOR YOU !
IF you like it 👍 share for your friends 👬
ⒸFitsumi Helina
👇👇👇👇👇👇👇👇
🎖📖🎖
@aplusacademyy
@aplusacademyy
▬▬▬▬▬▬▬▬
2 787
♻️እባካችሁ ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ሼር አድርጉ!!
🏆 ፈተናን በተሻለ ሞራል ለመስራት ከ EUEE 1ቀን በፊት ማታና የፈተና ቀን ጠዋት ብናደርግ የሚመረጡ ነገሮች :-
💡በ FITSUM HELINA ( fitsumhelina ) የተፃፈ
የፈተና ሰሞን እማደል ትንሽ እንባባላ 😇
1⃣ ጊዜዎችዎን በጥበብ ይጠቀሙ⌚️
መብራቱን ከማጥፋትዎ በፊት ያሉት ጥቂት ደቂቃዎች ለማስታወስ በጣም ጥሩ ጊዜ ነው። ከመተኛቱ በፊት መማር የማስታወስ ችሎታን በእጅጉ ያሻሽላል - ስለዚህ አልጋ ላይ ሲቀመጡ በጣም አስፈላጊ የሆኑትን እውነታዎች፣ እኩልታዎች ወይም ቃላት በፍጥነት ያንብቡ። ከዚያ ያጥፉ።
ያው እኔ አዳሬን እቸክላለሁ አታጥፋብኝ የሚል ካለም መቻል ነው ለ 1 ሳምንት ምንም ማድረግ አይቻልም
2⃣ ጥሩ ምግብ ተመገብ/ቢ🍔
ጥሩ ቁርስ የ ጥሩ ቀን ምልክት ነው !
( የ ዩንቨርስቲ ምግቦችን አያጠቃልልም )
የካፌህን ምግብ ጥርግ አርገህ በልተህ መሔድ አለብህ/ሽ
የ ካርቦሀይድሬት content ያላቸውን ምግብ መመገብ ለ አእምሮ ጠቃሚ ነው so, እንደ ዳቦ መሰል የ ካርቦሀይድሬት ምግቦችን ተመገቡ
ቀለል ያለ ቁርስ ደስታ እንዲሰማዎት ያደርግዎታል እና ለፈተናው ዝግጁ እንዲሆኑ ማበረታቻ ይሰጥዎታል።
ያው ይሄ ነገር እቤት ቢሆን ነበር ለምርጫ አሪፍ የሚሆነው ግቢ ያው የሰጡህን ነው የምትበላው ነገር ግን በተቻላችሁ አቅም ወደ ግቢ ስትሄዱ በደረቅ ምግብ መልክ አዘጋጅታችሁ ለመያዝ ሞክሩ
3⃣ ሳቅ /ቂ🤣
እንደ ኮሜዲ ትዕይንት መመልከት፣ የኪካቦውት ማድረግ ወይም በ tiktok ላይ ካሉ video መዞርን የመሰለ አንድ አስደሳች ነገር ያድርጉ ምናምን ልል ነበር ለካ ስልክ ወፍ so ለዚህ ደግሞ ምን ታረጋላችሁ መሰላችሁ ከ ጓደኛ ጋር ማውራት ከዚህ በፊት ያያችኋቸውን ቀልዶች እያነሱ ፈታ ማለት
መሳቅ ያዝናናዎታል, ጭንቀትን ይቀንሳል እና ጥሩ እንቅልፍ ለማግኘት ይረዳዎታል.
እርሶ በሚዝናኑበት መንገድ መርጠው መዝናናት ይችላሉ!
4⃣ መንቃትዎን ያረጋግጡ🤓
ለዶርም አባል ወይም ጓደኛ ይናገሩ እንዲቀሰቅሶት። በ ግዜ ወደ ፈተና መድረስዎን ያረጋግጡ።
ቀድሞ መጀመር ተረጋግቶ ለመጨረስ ይረዳል ። ደግሞ ጠዋት የካፌ ሰልፍ እና ወከባ ስላለ ቀደም ብለህ ተነስተህ ፊትህን ፋፈሽ ታደርግና ጥርስህ ቦርሸህ ላንተ በቃህ አንቺ ጸጉርሽን ታስተካክይና ምናምን ምናምን .... welcome to የካፌ ሰልፍ
ቁርስ ካመለጠህ አመለጠ ነው ማንም ላንተ አስቦ የሚጨነቅ በቃ ቡሀላ ትበላለህ የሚልህ የለም እሱ እናትህ ጋር ቀረ
ከዛም ቀኖን በማመስገን ይጀምሩ ያው ማመስገን የሁል ግዜም ስራ ነው መሆን ያለበት ፈተናው ሲያልፍ እንዳትረሱት ደግሞ😜
5⃣ መቼ ማቆም እንዳለብዎት ይወቁ😎
ጠዋት ላይ ጥሩ ቁርስ ይበሉ እና ከዶርም ከመውጣትዎ በፊት በጣም አስፈላጊ የሆኑትን እውነታዎችዎን ይመልከቱ። ከዚያም እንደገና ወደ ፈተና መንገድ ላይ. የፈተና አዳራሽ ስትደርስ አእምሮህን መጠቀም አቁም( ማለቴ ማታ ያነበብካቸውን ለማስታወስ ብለህ አትጨናነቅ ራስህን ዘና አድርገው )። ነገሮችህን እስከ አሁን የማታውቅ ከሆነ በፍፁም አታውቅም! ከደቂቃዎች በፊት በጣም ብዙ የመጨረሻ ደቂቃ መጨናነቅ አንጎልዎን ወደ ሽክርክሪት ሊልክ ይችላል።
ከዛ በመፈተኛ ሰአትህ ገረባ በብብትህ ይዘህ ሰንደል ሰክተህ መዞር ይሄንን ነው የምትፈልገው so
ማቆም ባለብህ ሰአት አቁም
6⃣ ቦታውን ይጠቀሙ👌
በፈተና ክፍል ውስጥ ሲሆኑ፣ በምቾት ይቀመጡ እና ፈታ ብለው በተዝናና መልኩ መቀመጥ ። በአካል ራሳችንን ትልቅ ስናደርግ፣ እጆቻችንን ዘርግተን ወይም ወንበር ላይ በመደገፍ፣ ይህ የበለጠ በራስ መተማመን እንዲኖርዎ የሚያደርግ የሆርሞን አይነት እንደሚለቀቅ ተረጋግጧል። ይሰራል - ቃል እንገባለን.
ይቺኛዋ ዘዴ ብዙ ሰው ያልተጠቀማት የተጠቀሟት ደግሞ ያመሰገኑኝ ዘዴ ናት ከ ፈተና በፊት እና በፈተና ሰአት የራስ መተማመን ወሳኝ ነገር ነው ።
አንዴ ወንበሩ ላይ ስትቀመጡ እኮ የናንተ ሆኑዋል ማንም አይቀማችሁም ለምን ተጨንቃችሁ የሚሰበር ይመስል ጫፍ ላይ ወይ ወደጎን ብቻ ትቀመጣላችሁ ማንም እኮ አይቀማችሁም
both your aptitude and altitude decide your score ባይዘዌይ እኔ ነኝ የፈለሰፍኳት
ስለዚህ ፈተና ስትገቡ እና ወንበራችሁ ላይ ስትቀመጡ በስርአት ዘና ብላችሁ በራስ መተማመን የሚፈጥር አይነት አቀማመጥ ተቀመጡ የፈተና ቀንም ገላችሁን ታጥባችሁ ፀዳ ያለ ልብስ ልበሱ ያ በራስ መተማመናችሁን ያጎላዋል
caution ‼️
የፈተና ቀን ጠዋት ታጥበህ በብርድ ተቆራምደህ እየተርበተበትክ እንዳትፈተን ደግሞ አለ አደል ቀደም ብላችሁ ማታ ወይም በሚመቻችሁ ሰአት ብቻ ፈተናን በማያስታጉል መልኩ ይሁን
7⃣ ብዙ አትጠጡ😏
ከፈተና በፊት ባሉት ሳምንታት ከ ሱስ የፀዳ ማንነት ጥሩ ነው ስለዚህ የ አልኮል ነገሮች መቅስ አይደለም ማሽተት የለቦትም ‼️
እንዲያው ነገሩን እንጂ ላሽትት ብትልስ ከየት አባህ ልታመጣው ነው የ ግቢ ቧንቧ ውሀ እንጂ ድራፍት አይወጣው
ደብረ ብርሀን ለሚመደቡ ግን አረቄ መፈቀድ አለበት ባይ ነኝ ብርዱ ዋዛ አይደለማ 😔
በዛላይ የፈተና ቀን ገስረህ ገስረህ ሽንቴ መጣ ብትል 😁😁😁 እኔ የለሁበትም
እረ ሼም ነው በዛላይ ፈታኙም አያስወጣሽም አንዴ ከተጀመረ ከ 45 ደቂቃ በፊት ወፍ እና ወጥሮሽ የምትፈተኝው ፈተና አንጂ የ ሽንትቤት ወረፋ መሰለሽ እንዴ የያዝሽው
8⃣ የጥናት ቡድን ከጓደኞች ጋር አደራጅ
የጥናት ቡድኖች የሚፈልጉትን መልሶች እንዲያገኙ እና ስራዎችን በፍጥነት እንዲጨርሱ ሊረዱዎት ይችላሉ። ቡድኑ በጉዳዩ ላይ ያተኮረ መሆኑን እና በቀላሉ የማይበታተኑ መሆናቸውን ብቻ ያረጋግጡ።
ይሄ ዘዴ በቀላሉ ለማንበብ ትኩረት ለማድረግ ጥያቄ ለመስራት ያግዛል
ደግሞ ገና ለገና ቀሰም ብላለች ብለህ 50 ሆኜ አጠናለሁ ብለህ ጊዜህ ቢባክን እኔን መጥተህ እንዳትወቅስ ።
ጓደኛህ ከ ጥናት የማያስተጓጉልህ ቀለሜ ቢሆን ይመረጣል ወኬ
አሪፍ የጥናት ቡድን ከ 3 ባይበልጥ ይመከራል ላለመረባበሽ 🧍♀🧍♂🧍♀እሺላ
50 ሆነህ ወሬ ስታቦካ ብትውል ፍፁም ከ ደሙ ንፁህ ነው 😜
አለ አደል ማታ ማታ ወይ ዶርም ቁጭ ብላችሁ ወይ ላይብረሪ በጋራ መፍለጥ ነው በቃ 🥰
9⃣ የ እንቅልፍ ጉዳይ 😴
ይሄ ያው ምንም የሚያጠያይቅ አይደለም ያንን ሁሉ ግዜ ተሰጥቷችሁ ካላነበባችሁትን የፈተና ቀን ማታ በምን ተአምር ልትጨርሰው ነው አፍጥጠህ የምታድረው ።
አእምሮትኩረቱን መልሶ ለማግኘት እንዲረዳው መደበኛ እረፍቶች ያስፈልጉታል ። ረጅም ሰዓታትን ለማጥናት በጣም ጥሩው ዘዴ አይደለም ምክንያቱም የረጅም ጊዜ እውቀትን ማቆየት ፈጽሞ የማይቻል ነው. በጣም አስፈላጊው የጥናት ክፍል ከጥናትዎ ዘይቤ ጋር የሚስማማ መደበኛ አሰራርን ማዘጋጀት ነው።
በተለይ በተለይ ...
ከፈተና በፊት ያለችውን ምሽት ጥሩ እንቅልፍ አግኝቶ ማሳለፍ ተገቢ እንደሆነ ብዙዎች ይስማማሉ። ነገር ግን ጥሩ እንቅልፍ ፈተናው ሲቃረብ ብቻ ሳይሆን ከሳምንታት በፊት ገና ዋናው ጥናት ሲደረግና ክለሳ በሚደረግበት ወቅትም እጅግ ወሳኝ ነው። በጠዋት ተነስቶ ውጤታማ የክለሳ ጥናት ካደረጉ በኋላ በጊዜ ተኝቶ ጥሩ እንቅልፍ ማግኘት ሰውነታችንና ጭንቅላታችን በደንብ ተግባብተው እንዱሰሩ ይረዳቸዋል። ሌሊቱን በሙሉ ለማጥናት ሙከራ አታዴርጉ ይላሉ የዘርፉ ባለሙያዎች። ምክንያቱም ራሳችን ላይ ጫና እያሳደርን ስለሆነ።
2 787
#ብሔራዊ_ፈተና
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከቀናት በኃላ መሰጠት ይጀምራል።
ፈተናው በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እንደሚሰጥ ይታወቃል። ተማሪዎች መብታቸው ፣ ግዴታቸው፣ ወደ ዩኒቨርሲቲ ይዘው መሄድ የሚችሉት እና የተከለከሏቸው ነገሮችን ከላይ በምስሉ በዝርዝር ተቀምጧል።
በተጨማሪም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና የጊዜ ሰሌዳ እንደሚከተለው ቀርቧል።
➤ የመጀመሪያ ዙር (የሶሻል ሳይንስ) ፦
🗓 ከመስከረም 26 - 28 (ተፈታኞች ወደ ዩኒቨርሲቲ ይገባሉ)
🗓 መስከረም 29 (ኦረንቴሽን ይሰጣል)
🗓 ከመስከረም 30 - ጥቅምት 2 (ፈተና ይሰጣል)
🗓 ከጥቅምት 3 - ጥቅምት 4 (ተፈታኞች ወደየአካባቢያቸው ይመለሳሉ)
➤ ሁለተኛ ዙር (የተፈጥሮ ሳይንስ) ፦
🗓 ከጥቅምት 5 - ጥቅምት 6 (ተፈታኞች ወደ ዩኒቨርሲቲ ይገባሉ)
🗓 ጥቅምት 7 (ኦረንቴሽን ይሰጣል)
🗓 ከጥቅምት 8 - ጥቅምት 11 (ፈተና ይሰጣል)
🗓 ከጥቅምት 12 - ጥቅምት 13 (ተፈታኞች ወደየአከባቢያቸው ይመለሳሉ)
(ትምህርት ሚኒስቴር / የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት)
ᗩ+ አካዳሚ (9-12):
🎖📖🎖
@Aplusacademy9_12
@Aplusacademy9_12
▬▬▬▬▬▬▬▬
