en
Feedback
Yeneta Courses

Yeneta Courses

Open in Telegram

መቀመጫ | ADDIS ABABA UNVERSITY ©Yeneta Tutorial

Show more
2 787
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
❔እንዴት የAptitude ትምህርት ፈተና መዘጋጀት እንችላለን! 📢English Part ❓የ Synonyms &Antonyms ጥያቄዎችን በLogic መልስ የምናገኝበት ዘዴ ። 📢Synonymous ከ (2-4) ጥያቄ ይመጣል!መልሱን ለማግኘት መጠቀም ያለብን ዘዴዎች ➖ምርጫውን ከማየታችሁ በፊት ተራ ቀጥሩ ላይ ያለውን ፤ ቃል በሚገባ ተረዱ። ትርጉሙን ካወቃችሁት እሰየው።ካላወቃችሁት ግን ቢያንስ Negative ነው Positive ነው የሚለውን ለዩ። ➖ቃሉ Positive ከሆነ ምርጫ ውስጥ Positive የሆኑ ቃላትን ፈልጉ ፤ ቢበዛ ከሶስት አይበልጡም! ¤ሶስት ቃል ከሆኑ አንዱ ቃል Negative ቢሆን እንኳን በፍፁም ከዋና ቃሉ ጋር ካልተጣጣመ አስወግዱት።ከሁለቱ አንዱን ምረጡ! ¤ ቃሉ Positive ሆኖ ምርጫ ውስጥ Positive ቃል አንድ ብቻ ከሆነ ትርጉሙን ባታውቁ እራሱ መልሱ የቃል ነው። 📢Antonyms ከ (2-4) ጥያቄ ይመጣል!መልሱን ለማግኘት መጠቀም ያለብን ዘዴዎች ➖ምርጫውን ከማየታችሁ በፊት ተራ ቀጥሩ ላይ ያለውን ፤ ቃል በሚገባ ተረዱ። ትርጉሙን ካወቃችሁት እሰየው።ካላወቃችሁት ግን ቢያንስ Negative ነው Positive ነው የሚለውን ለዩ። ➖ቃሉ Positive ከሆነ ምርጫ ውስጥ Negative የሆኑ ቃላትን ፈልጉ ፤ ቢበዛ ከሁለት አይበልጡም! ➖አሁን ልዩነቱን በማጥበብ ከሁለቱ Negative ቃላት አንዱን መረጡ ➖ተራ ቁጥር ላይ ያለው ቃል Positive ሆኖ ምርጫው ላይ አንድ Negative ቃል የሚገኝበት አጋጣሚም አለ ።ያኔ ያንን ምርጫ አጥቁሩ ❓Analogy ጥያቄዎች ከ 5-10 ግያቄዎች ይመጣሉ። ትርጉማቸውን የማናውቃቸው ቃላቶች Aptitude ላይ አይጠፉም ፤ መልሳቸውን የምናቅበት ድንቅ ሚስጥር ፤ Analogy ጥያቄዎች ስትሰሩ ተረጋጉና የቃላቶቹን ግንኙነት ተገንዘቡ። ተራ ቁጥር ላይ ያሉት ሁለት ቃላት በመሃከላቸው በምን ግንኙነት አለ? Positive : Negative Negative : Negative Positive : Positive ሰሪ : የመስሪያ ዕቃ ሴት ፆታ : ወንድ ፆታ ብዙ : ነጠላ ወዳጅ : ጠላት ❓ተማሪዎች ብዙ ጊዜ Analogy ጥያቄ ሲመልሱ የሚፈጥሩት ስህተት ፦ ❓Now try This one. ❓Teacher : Chalk A. Carpenter : Hammer B. Dentist : Colgate C. Singer : tone D. Student : Pen የቱን ሞላችሁ? Answer : D 1⃣ኛ ስህተት : *Specific ልዩነቱን ባለመለየት ፤ መልስ ለመሙላት ይቸኩላሉ! ለምን ''A ''አልሆነም? ምክንያቱም ከትምረህርት ጋር ግንኙነት ስለሌለው ፤ Choice D ባይኖር ኖሮ ግን መልሱ 'A' ይሆን ነበር ❓Now try This one. ❓VERSE : POEM A. SPEECH : PITCH B. PARAGRAPH : SENTENCE C. ATOM : MOLECULES D. LEXI : LUXURY የቱን ሞላችሁ? ANSWER : C 2⃣ኛ ስህተት : *ቅድመ ተከተሉን በደምብ አያስተውሉም። ለምን መልሱ ''B ''አልሆነም? ጥያቄው የሚለውን በደምብ እናስተውል ፤ ስንኞች ተደምረው ግጥም ተሰጡ ፤ እንዴት አንቀፅ ተደምሮ አረፍተ ነገር ይሰጣል(❌ውድቅ ሆነ ምክንያቱም Inverse relationship order ስላለው) ❓Analytical reasoning ፤ የምንረዳበት መንገዶች። አንዳንድ Logic ጥያቄዎች ስንጠየቅ ምን ማድረግ አለብን ፦ 1⃣ የሰጠንን መረጃ በደምብ መረዳት ከዛን ጥያቄው ወደሚመራን Logicኩን መከተል።ለምሳሌ Helen ,Who is my mere sister, has, is a nice of Kidist. If the above logic is true .Which of the following is true . i. I have two Children. ii. I am a nephew of kidist. iii. Kidist as an ant called Helen A. i,ii B, i C.iii D. i,ii, iii Answer : C 2⃣Logical reasoning ለመረዳት ከባድ እና ለመረዳቴ ጊዜ ሚወስድ ከሆነ ! ፤ ስዕል ወይም ዲያግራም ማስራት የሚጠይቅ ከሆነ ማዘጋጀት። ለምሳሌ የለኛው የዝምድና አይነት ጥያቄ ቢመጣ ፤ የቤተሰብ ዘር ቅርጫፍ በመስራት ወዲያው መረዳት ይቻላል 📢Maths Part (25) ❓ምንም እንኳን ቀላል መስሎ ቢታይም የ AGE, PERCENTAGE ,PROPORTION ,GEOMETRY , ARITHMETIC &GEOMETRIC PROGRATION, እና ሌሎች Mathematical problems ማየት ተገቢ ነው! 🔗SHARE 🔗SHARE ╔══════════╗   ᗩ+ አካዳሚ (9-12):        🎖📖🎖 @Aplusacademy9_12 @Aplusacademy9_12 ▬▬▬▬▬▬▬▬

. ✝✝✝ መስቀል ኃይልነ መስቀል ጽንዕነ መስቀል ቤዛነ መስቀል መድኃኒተ ነፍስነ . 🙏🙏🙏 🌿🌿💐 እንኳን አደረሳችሁ! 💐🌿🌿
.            ✝✝✝ መስቀል ኃይልነ መስቀል ጽንዕነ መስቀል ቤዛነ መስቀል መድኃኒተ ነፍስነ .            🙏🙏🙏 🌿🌿💐 እንኳን አደረሳችሁ! 💐🌿🌿        

#ብሔራዊ_ፈተና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ኮማንድ ፖስት በፈተናው ቅድመ ዝግጅት ዙሪያ ውይይት አካሂዷል። በውይይቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ማኔጅመንት አባላት ፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፣ የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፣ የኢትዮጵያ የሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ፣ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና የፌደራል ቴክኒክና እልጠና ኢንስቲትዩት ሀላፊዎች እና የክ/ከተማ የትምህርት ጽ/ቤት ሀላፊዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ ፈተናው ከመስከረም 30 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንደሚሰጥ ቀደም ብሎ በትምህርት ሚኒስቴር የተገለጸ ሲሆን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፈተናውን ፦ - አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፤ - ኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፤ - ኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ፣ - አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ - ፌደራል ቴክኒክና እልጠና ኢንስቲትዩት ለመስጠት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑ በውይይቱ ላይ ተገልጻል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የፈተና ዝግጅት እና አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ዲናኦል ጫላ የተፈታኞችን መብትና ግዴታዎች አቅርበዋል። #የተፈታኞች_መብቶች_የሆኑት፡-  ➭ ከፈተና ጥያቄ ውጪ ማንኛውንም ያልተረዳውን ነገር ጠይቆ የመረዳት መብት አላቸው። ➭ በየኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ምግብ፣ የህክምና አገልግሎት፣ የማደሪያ ክፍል፣ ፍራሽና ትራስ የማግኘት መብት አላቸው። ➭ ማንኛውም ተፈታኝ በዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ያለውን የቤተ መጽሐፍት፣ የመጸዳጃ ቤቶች፣ የሻወር፣ የካፍቴሪያዎች፣ የሚኒ ሱፐር ማርኬቶች፣ የተለያዩ ሱቆች፣ የመናፈሻና መዝናኛ አገልግሎቶችን የመጠቀም መብት አላቸው። ➭ የኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ የጋራ የደህንነት ጥበቃ የማግኘት መብት አላቸው። ➭ በፈተና ሰዓት መፈተኛ ክፍል ገብቶ ብርሃናማ የመፈተኛ ቦታ፣ ወንበር፣ መጻፊያ ጠረጴዛ የማግኘት መብት አላቸው። ➭ ፈተና ከመጀመሩ አንድ ቀን ቀድሞ ስለፈተናው ገለጻ (ኦሬንቴሽን) የማግኘት መብት አላቸው። #የተፈታኞች_ግዴታ_የሆኑት፡- ➤ ማንኛውም ተፈታኝ በፈተና ማዕከልም ይሁን መፈተኛ ክፍል አድሚሽን ካርድ ይዞ የመገኘት ግዴታ አለበት። ➤ ማንኛውም ተፈታኝ ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲመጣ የትምህርት ቤት #ወይም የነዋሪነት መታወቂያ ይዞ መገኘት አለበት። ➤ ማንኛውም ተፈታኝ ወደ ግቢ ከመግባቱ በፊትና ወደ መፈተኛ ክፍል ከመግባቱ በፊት ሙሉ አካላዊ ፍተሻ የመፈተሽ ግዴታ አለበት። ➤ ማንኛውም ተፈታኝ በዩኒቨርሲቲ ግቢና በመፈተኛ ክፍል የተከለከሉ ቁሳቁሶችን/ዕቃዎችን መያዝ የለበትም። ➤ ማንኛውም ተፈታኝ እርሳስ፣ ላጲስና የእርሳስ መቅረጫ ይዞ መገኘት አለበት። ➤ ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ደንብን የማክበር ግዴታ አለበት። ➤ ማንኛውም ተፈታኝ በፈተና ማዕከል ውስጥና በመፈተኛ ክፍል ውስጥ የፈተና አስፈጻሚዎች የፈተና አስተዳደር ሥራን ውጤታማ ለማድረግና ሁኔታዎችን ለማመቻቸት የሚያደርጉትን ጥረት የመተባበር ግዴታ አለበት። ➤ ማንኛውም ተፈታኝ ፈተና ከመጀመሩ በፊት መፈተኛ ክፍል የመገኘት ግዴታ አለበት። ➤ ተፈታኙ ፈተናው ሳይጠናቀቅ ከፈተና ክፍል የሚወጣ ከሆነ የፈተና ጥያቄ የያዘውን ቡኩሌት ለፈታኙ የማሰረከብ ግዴታ አለበት። ➤ ማንኛውም ተፈታኝ ወደ ተመደበበት ዩኒቨርሲቲ  ሲመጣ  አንሶላ፣  ብርድልብስና  የትራስ  ጨርቅ ይዞ የመምጣት ግዴታ አለበት። ➤ #ዩኒፎርም ለብሶ መገኘት አለበት። #ለተፈታኞች_የተፈቀዱ_ነገሮች ፦ ➣ አዲስ ወይም ቀድሞ ለመማር እና ለማጥናት ሲጠቀሙበት የነበሩ ማስተወሻ  ደብተር ፣ የትምህርት መጽሐፍ፣ መንፈሳዊ/ኃይማኖታዊ መጽሐፍት፣ ባዶ ወረቀት ➣ ደረቅ ምግቦች ወይም ሰንዱች ምግቦች (ጩኮ፣ በሶ፣ ዳቦ ቆሎ፣ ቆሎ….) ➣ ገንዘብ (ብር) ➣ የልብስ ወይም የእጅ ቦርሳ፣ የግል ልብስ፣ ጫማ ➣ የግል ንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁስ (ሳሙና፣ ሞዴስ፣ የጥርስ ብሩሽ፣ የጥርስ ሳሙና፣ የገላ ማድረቂያ ፎጣ፣ ሶፍት፣ ሻምፖ፣ ኮንዲሽነር፣ ሎሽን፣ ቻፕስቲክ፣ የጸጉር ቅባት፣ የፊት ቅባት) #ለተፈታኞች_የተከለከሉ_ነገሮች ፦ ⮕ ማንኛውንም ዓይነት የጦር መሣሪያ ይዞ መገኘት የተከለከለ ነው፡፡ ⮕ ማንኛውንም ዓይነት ስለት እና ሹልነት ያላቸውን ብረታ ብረቶችና ጠንካራ ፕላስትኮች ይዞ መገኘት የተከለከለ ነው። ⮕ ማንኛውም ድምጽ የሚቀዳ፣ ፎቶ የሚያነሳ፣ ቪዲዮ የሚቀርጽ፣ ከቴሌ መስመርም ሆነ ከቴሌ መሾመር ውጭ መልዕክት በዲጂታል መንገድ የሚሰጥ ወይም የሚቀበል የግል ዕቃ/መሳሪያ /ቴክኖሎጂ ውጤት፣ ስልክ፣ አይ-ፓድ፣ ታብሌት፣ ኮምፕዩተር፣ ላፕቶፕ፣ ስማርት ሰዓት፣ ማጂክ ብዕር/እስክሪብቶ፣ ማጂክ ኮት/ጃኬት እና  ሌሎች  ማንኛቸውም  ፎቶ፣  ምስል  እና  ድምጽ የሚቀርጹ የኤሌክትሮኖክስ መሣሪያዎችን በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥም ሆነ ግቢ  ዙሪያ  ይዞ መገኘት ወይም መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡ ⮕ በዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ማንኛውንም ዓይነት የግል ፍላሽ ዲስክ፣ ሃርድ ዲስክ፣ ሲዲ፣ ሚሞሪ፣ ሚሞሪ ሪደር፣ ኦ-ቲጂ ኮንቨርተርና መሰል ዕቃዎችን ይዞ መገኘት  ወይም  መጠቀም  የተከለከለ ነው፡፡ ⮕ ማንኛውም አደንዛዥ እጾች (ጫት፣  ሲጋራ፣  በሓኪም  ማዘዣ  የሌለው  መድኃኒት  (በሽሮፕም ይሁን በታብሌት፣ ህክምና መስጫ መርፌ)) መያዝ ወይም መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡ ⮕ ማንኛውም ዓይነት የአልኮል መጠጥ ይዞ መገኘት ወይም መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡ ⮕ ማንኛውም ዓይነት የአንገት ሐብል፣ የጸጉር ጌጥ፣ የጆሮ ጌጥ፣ የጣት ቀለበት፣ የእጅ አንባር፣ አድርጎ ወይም ይዞ መገኘት የተከለከለ ነው፡፡ (ከልሙጥ የጋብቻ ቀለበት በስተቀረ) ⮕ ፈተና ከተጀመረ ከ30 ደቂቃ በኋላ ወደ ፈተና ክፍል መግባት እና ፈተናው ተጀምሮ  45 ደቂቃ ሳይሞላ ከፈተና ክፍል መውጣት የተከለከለ ነው፡፡ ⮕ ተፈታኙ ፈተናው ሳይጠናቀቅ ከፈተና ክፍል የሚወጣ ከሆነ የፈተና ጥያቄ የያዘውን ቡኩሌት ይዞ መውጣት ተከለከለ ነው፡፡ ⮕ በፈተና ሰዓት በመፈተኛ ክፍል ውስጥ ማስቲካ መያዝም ሆነ መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡ ⮕ በዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ በግልም ሆነ በቡድን መጮህ ወይም በጣም ከፍተኛ ድምጽ ማሰማት የተከለከለ ነው፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 49,203 ተማሪዎች ፈተናውን ለመውሰድ የተመዘገቡ ሲሆን ፈተናው ከመስከረም 30 ጀምሮ በቅድሚያ የሶሻል ሳይንስ ተማሪዎች ተፈትነው ሲጨርሱ የናቹራል ሳይንስ ተማሪዎች ቀጥለው ይፈተናሉ። ተፈታኝ ተማሪዎች በፈተና ወቅት የምግብና የመኝታ አገልግሎቶችን በየተቋማቱ ያገኛሉ። (የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ)       🎖📖🎖 @aplusacademyy @aplusacademyy ▬▬▬▬▬▬▬▬

Teftagn yhonachu yeamna nw

በአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ የተዘጋጀ ለ12ኛ ክፍል ተፈታች ተማሪዎች የተዘጋጀ ሞዴል ፈተና ፕሮግራም 🎖📖🎖 @aplusacademyy @aplusacademyy ▬▬▬▬▬▬▬▬
በአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ የተዘጋጀ ለ12ኛ ክፍል ተፈታች ተማሪዎች የተዘጋጀ ሞዴል ፈተና ፕሮግራም 🎖📖🎖 @aplusacademyy @aplusacademyy ▬▬▬▬▬▬▬▬

+7
#ANSWER

+3
#ANSWER

+7
#ANSWER

👉 የ12ኛ ክፍል History ሞዴል ፈተና 👉 ተማሪዎች እራሳችሁን ፈትሹበትና 👉2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የተዘጋጀ       🎖📖🎖 @aplusacademyy @aplusacademyy ▬▬▬▬▬▬▬▬

#ብሔራዊ_ፈተና ከመፈተኛ ዩኒቨርሲቲ ከ50 ኪሎ ሜትር በላይ ለሆኑ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች የትራንስፖርት ወጪን ትምህርት ቤቶቻቸው የሚገኙባቸው ወረዳዎች እንደሚሸፍኑ የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈ
+1
#ብሔራዊ_ፈተና ከመፈተኛ ዩኒቨርሲቲ ከ50 ኪሎ ሜትር በላይ ለሆኑ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች የትራንስፖርት ወጪን ትምህርት ቤቶቻቸው የሚገኙባቸው ወረዳዎች እንደሚሸፍኑ የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል። ከመስከረም 30 እስከ ጥቅምት 17 ቀን 2015 ዓ.ም በሁለት ዙር ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ፈተና በቂ ቅድመ ዝግጅት መደረጉን አገልግሎቱ ገልጿል። የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር እሸቱ ከበደ ለ ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት (ኤፍ ቢ ሲ) የሰጡት ቃል ፦ - ፈተና ማተም ጨምሮ ሌሎች አስፈላጊ ዝግጅቶች ከወዲሁ ተጠናቀዋል። - ከመፈተኛ ዩኒቨርሲቲዎች በ50 ኪሎሜትር ርቀት ውስጥ ያሉ ተፈታኝ ተማሪዎች የትራንስፖርት ወጪን በራሳቸው ይሸፍናሉ፤ ከ50 ኪሎ ሜትር ርቀት #በላይ የሚገኙ ተማሪዎች ደግሞ ትምህርት ቤቶቻቸው የሚገኙባቸው ወረዳዎች ወጪያቸውን ይሸፍናሉ። - ተፈታኝ ተማሪዎች መያዝ #የሚፈቀዱላቸው ፦ • መጽሐፍት፣ • ሲያጠኗቸው የነበሩ ማስታወሻወች፣ • የንጽህና መጠበቂያዎች • የሌሊት ልብስ ከተፈቀዱት ቁሳቁስ መካከል ናቸው። ተማሪዎች ማንነታቸውን የሚገልጽ የቀበሌ መታወቂያ ፣ የመፈተኛ ካርድ ወይም አድሚሽን ካርድ መያዝ ይኖርባቸዋል። - ተፈታኝ ተማሪዎች መያዝ #የሚከለከሏቸው ቁሳቁስ፦ • ማንኛውንም የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ • ከጋብቻ ቀለበት ውጪ የተለየ ፈርጥ ያላቸው ቀለበቶች፣ • ሀብሎች ፣ • የጸጉር ጌጦች • ድምጽ የሚያወጡ ጃኬቶች መያዝ አይቻልም። - የመፈተኛ ዩኒቨርሲቲዎች ለተፈታኝ ተማሪዎች የመኝታና የምግብ አገልግሎት ያመቻቻሉ። ©tikvahethiopia

ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ!! የሁለተኛ ደረጃ ማጠናቀቂያና ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ተፈታኞች በሙሉ:- ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ 2014/15 የኢትዮ ዩኒቨርሲቲ መግቢያና የሁለተኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና ተፈታኞች ወደ ተመደቡበት ካምፖስ ጉዞ ሲያደርጉ #መያዝ #የተፈቀደላቸው፣#መያዝ #የተከለከሉ እና #የጊዜ #ሠሌዳ እንደሚከተለው ያለው ሲሆን ተማሪዎች ከወዲሁ ራሣችሁን እንድታዘጋጁ ይሁን።       ❶#መያዝ #የተፈቀደላቸው ✡️አንሶላ፣ ✡️ትራስ ጨርቅ፣ ✡️የማታ ልብስ፣ ✡️ደረቅ ምግብ፣ ✡️ልብስ፣ቦርሳ፣ ✡️የመፈተኛ ካርድ፣እርሳስ፣ላጲስ፣የማስታወሻ ደብተር፣ባዶ ወረቀት፤መጽሐፍ      ❷፣#መያዝ #የተከለከሉ ☸️ማንኛውም ድምፅ የሚቀዳ፤ቪዲዮ የሚቀዳ  ወይም ፎቶግራፍ የሚያነሳ፤ ☸️ካሜራ ☸️ማንኛውም ከቴሌ መስመርም ይሁን ከቴሌ ውጭ መልዕክት በድጂታል ቴክኖሎጂ መቀበያ ወይም ማስተላለፊያ ውጤቶች(ታብሌት፣ኮሚፕዩተር፣ላብቶፕ፣ ስልክ፣አይፓድ፥ሃርድ ዲስክ፣ፍላሽ)         ❸ #የጊዜ #ሠሌዳ ✡️ማህበራዊ ሳይንስ $social science dep't ➤26_28/1/2015 ዩኒቨርስቲ መግቢያ ➤29/01/2015 ኦሬንተሽን ➤30/01/2015_02/02/2015 ፈተናው የሚሰጥበት ጊዜ ይሆናል። ✡️የተፈጥሮ ሳይንስ Natural Science dep't ➤05_06/2/2015 ዩኒቨርስቲ መግቢያ ➤07/02/2015 ኦሬንተሽን ➤08/02/2015_11/02/2015 ፈተናው የሚሰጥበት ጊዜ ይሆናል።      ተማሪዎች መረጃው እንዲደርሳቸው ሟር ያድርጉ። መረጃው ከትምህርት ሚኒስተር ነው የተገኘው።        🎖📖🎖 @Aplusacademy9_12 @Aplusacademy9_12 ▬▬▬▬▬▬▬▬     

Answers 1,A 2,B 3,D 4,A 5,C 6,A.......እዚ ጋር involvement የምትለው word third partyው impartial ወይም ሌሎች neutral መሆኑን በሚገልጹ ቃል እስካልደገፈው ድረስ mediation ሊሆን አይችልም ።

photo content

1When was me Organization of African Union (OAU) transformed into African Union (AU)? A. 2002 B. 2004 C. 2006 D. 2009 2. Which African countries joined the League of Nations besides Ethiopia? A. Kenya and Tunisia. B. Liberia and South Africa. C. Algeria and Egypt. D. Ghana and Nigeria. 3. Who was the leader of the black civil rights' movement killed in April was after addressing his last speech? A. Rosa Parks. B. Allan John. C. Mohandas Gandhi. D. Martin Luther King. 4. What is meant by treating others the way you want to be treated as well as impartial treatment of people? A. Fairness B. Truthfulness C. Honest D. Courage 5. When did Ethiopia become the member of the League of Nations? A. 1920 B. 1921 C. 1923 D. 1925 6. Which of the following is a peaceful way of settling disputes with the involvement third party? A. Arbitration B. Negotiation C. Mediation D. Litigation

🔵 እንደባሪያ ሰርተህ አንደ ንጉስ ኑር 🔰 ስለ አባከናችሁት ግዜ አታስቡ ⭕️ከ ራሳችሁ ሀሳብ በቀር የማንም ሀሳብ ማራገፊያ አትሁኑ ♻️ social media አጠቃቀማችሁ የተስተካከለ ይሁን ❓social media በመገልገሌ ምን እጠቀማለሁ ⭕️ 12 ተኛ ክፍሎች በዚህ በቀረው ሰአት ማድረግ የሚገቧችሁ ነገሮች ©Fitsum Helina 🎖📖🎖 @Aplusacademy9_12 @Aplusacademy9_12 ▬▬▬▬▬▬▬▬

ቀን መስከረም 10/2015 ዓ.ም ማስታወቂያ ጉዳዩ፡ የ12ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና ፕርግራም ማሳወቅን ይመለከታል፤ ከላይ በርእሱ ለመጥቀስ እንደተሞከረው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትም/ቢሮ በ2014
ቀን መስከረም 10/2015 ዓ.ም               ማስታወቂያ ጉዳዩ፡ የ12ኛ ክፍል ሞዴል ፈተና ፕርግራም     ማሳወቅን ይመለከታል፤ ከላይ በርእሱ ለመጥቀስ እንደተሞከረው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትም/ቢሮ በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል በተደጋጋሚ ሞዴል ፈተናን በማዘጋጀት እየተሰጠ መሆኑ ይታወቃል ፡፡ በመሆኑም አሁን የተዘጋጀውን ሞዴል ፈተና ሚስጥራዊነቱን በጠበቀ ሁኔታ በማባዛትና የተዘጋጀውን የፈተና ፕሮግራም በመጠበቅ ፈተናውን ከመስከረም 18/2015 ዓ.ም እስከ መስከረም 20/2015 ዓ.ም ድረስ ፈተናው እንደሚሰጥ እየገለፅን አስፈታኝ ትምህርት ቤቶች ከወዲሁ ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን '' ከሰላምታ ጋር

FRAUD
Anonymous voting

DOMESTIC
Anonymous voting

EXTRAORDINARY
Anonymous voting

SENTENCE COMPLETION Given the ability of modern technology to destroy the environment, it's clear that if we are not careful, the race of man may soon be as -..............- as dinosaur.
Anonymous voting