5 671
Subscribers
No data24 hours
-217 days
-8130 days
Posts Archive
5 671
የማስጠንቀቂያ መልክት ለባ/ዳር ከተማ ነዋሪወች
ሁሌም ሽንፈቱን መቀበል ያቃተው አብይ አህመድ ያረጀ እና ያፈጀ የሀሰት ዶክመንታሪ እና ዘገባ በመስራት አልሳካለት ያለው የብልፅግና አገዛዝ አሁንም በባህርዳር ከተማ ህዝቡን ለተቃውሞ ሰልፍ በማስገደድ በየቀበሌው የኮታ ድልድል መስጠቱን እና ከተለያዩ ቦታወች የሐይማኖት አባቶችን አስገድዶ ማስመጣቱን ደርሰንበታል ከምንም በላይ እምነትን እያጠፋ የእምነት ተቋማትን እያወደመ ያለ ስርዓት እንደሆነ ይታወቃል።
ነገር ግን የሐይማኖት አባቶችን እና የተለያዩ የሴፍትኔት ተጠቃሚዎችን ነጠላ በማልበስ ቤተክርስቲያን ፋኖን አወገዙ ለማለት እንደሆነ አውቀናል ስለዚህ በአማራ ህዝብ ላይ እየተፈፀመ ያለውን የዘር ማጥፋት ለመደበቅ የደግፉኝ ሰልፍ ተጠርቷል ።
በመሆኑም በዚህ ሰልፍ ላይ የምትገኙ የምታስተባብሩ ለአማራ ነፃነት ሲባል በዱር በገደሉ በተሰውት ጎዶቻችን ደም እና አጥንት ላይ እንደመቀለድ ስለሆነ በዚህ ቀን ለሚደርሱ ማንኛውም አይነት ጉዳቶች ፋኖ ሀላፊነቱን የማንወስድ መሆኑን እያሳወቅን ሁሉም ሰው ባለመገኘት የትግሉ ተባባሪ እንድትሆኑ እና ከዘር አጥፊው መንጋ እንዳትቀላቀሉ በማለት መልክታችን እናስተላልፋለን።
አባቶች በዚህ ታሪካዊ ስህተት እንደማትሰለፉ ተስፋ እናደርጋለን ከቻላቹህ
< ለእውነት ሙቱ እንደ አቡነ ጴጥሮስም ሁኑ >>
ፋኖ ሐብታሙ የሱፍ የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ኃይል 1ኛ ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት ሰኔ 3/2017 ዓ.ም
5 671
የትናንቱን የድሮን ትርኢት ካቀረበው ድርጅት ጋር የነበረኝ ንግግር!
የዛሬ አመት ገደማ በአድዋ ሙዚየም ምርቃት ወቅት የአፄ ምኒልክ ንግግር በሆሎግራም ቴክኖሎጂ በሀገር ውስጥ ባለሙያዎች ተሰራ ተብሎ ስናጣራው ንግግሩን ያረገው አርቲስት ተስፋዬ ገብረሀና መድረክ ላይ ቀልጠፍ ብሎ ቆሞ መሆኑን ደረስንበት።
በወቅቱ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በአፍሪካ ለመጀመሪያ ግዜ፣ በዓለም ደግሞ እጅግ ጥቂት ሀገራት ሊያሳኩ የቻሉትን የሆሎግራም ቴክኖሎጂ ተጠቅሞ የአፄ ምኒሊክ ንግግርን አቀረበ ተብሎ ተነግሮ ነበር።
ትናንት የታየውን የድሮን ትርኢት ደግሞ የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በጋራ ያዘጋጁት እና ያቀረቡት መሆኑን ነገሩን።
ዜናውን እንደሰማሁ ድርጅቱን ማነጋገር ጀመርኩ፣ ሲንጋፖር የሚገኘው MIRS Innovate የተባለ ተቋም ትርኢቱን ኮንትራት ወስዶ እንደሰራው በግልፅ ነገሩኝ። መጀመርያ ለመናገር ባይፈልጉም አንዱን የድርጅቱን ሀላፊ ገፋ አርጌ ስጠይቀው ለስራው 200 ሺህ ዶላር (26.8 ሚልዮን ብር ገደማ) እንደተከፈላቸው ነገረኝ።
እሺ ስራው ይሰራ። ግን ውሸቱ ለምን አስፈለገ? የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ሰሩት ብሎ ከመዋሸት ስፖንሰር ያረጉት ቢባል ምን ሀፍረት አለው?
የመንግስት ተቋማት በዚህ ደረጃ ተአማኒነታቸውን እንዲያጡ እየተደረገበት ያለው አካሄድ በእጅጉ ያስገርማል።
ጋዜጠኛ መሰረት ኤልያስ
5 671
በአማራ ክልል ውስጥ "ጎንደር ተጨቁኑዋል " የሚል የክልልነት ጥያቄ በግልጽ ከብአዴን በጎንደር ስም የተደራጁ የእስኩዋድ እና የፋፉዴን አባላት በግልጽ አጀንዳ ይዘው መጠዋል ? ማጋለጡ ይቀጥላል!
5 671
በአማራ ክልል ውስጥ "ጎንደር ተጨቁኑዋል " የሚል የክልልነት ጥያቄ በግልጽ ከብአዴን በጎንደር ስም የተደራጁ የእስኩዋድ እና የፋፉዴን አባላት በግልጽ አጀንዳ ይዘው መጠዋል ?
5 671
ሁሉቱንም_የጎጃም_ታሪክ መጻሕፍትን የምታገኙባቸው አድራሻዎች፦
#አዲስ_አበባ
1. ፒያሳ ኤዞፕ መጽሐፍ መሸጫ መደብር ከአራዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አጥር ጥግ/ከድሮው ፍ/ቤት ፊትለፊት
2. ለገሃር ተወልደ ሕንፃ ሥር ጃፋር መጽሐፍ መሸጫ መደብር
3. ጃፋር መጽሐፍ መሸጫ
አራት ኪሎ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት ፊት ለፊት
4. ጃፋር መጽሐፍ መሸጫ፤ ቸርችል መንገድ ከጥቁር አንበሳ ት/ቤት /ሌሴ ገብረማሪያ ት/ቤት ፊት ለፊት
5. ጃፋር ጀሞ ቁ.1 ናይል ነጃጅ ማደያ ፊት ለፊት
6. ጃፋር ዋቢ ሸበሌ
7. ጃፋር ሜክሲኮ ደብረ ወርቅ ሕንፃ ሥር
8. ጃፋር 4 ኪሎ አብርሆት ላይብረሪ ጎን
9. ኢትዮ ሎጎስ 4 ኪሎ
አብርሆት ላይብረሪ ጎን
10. ሀ ሁ መጽሐፍ መደብር አብርሆት ላይብረሪ ጎን
11. 4 ኪሎ ብልጽግና ጽ/ቤት ከአጥሩ ጥግ
12. ፍሬው መጽሐፍ መደብር 5 ኪሎ ከብርሃንና ሰላም ማተሚያ ጀርባ
13. መገናኛ መተባበር ሕንፃ (ይደውሉ 0913308226)
14. ፒያሳ በአዲሱ ገበያ መንገድ ከቴሌው ፊት ለፊት አቶ ቀለመወርቅ መደብር
15. አራት ኪሎ ከቅድሥት ሥላሴ አጠገብ፤ ብልጽግና ጽ/ቤት ጎን
16. አውቶብስ ተራ
#ደብረ ማርቆስ
2T(ቱቲ) ሕንፃ ከንጉሥ ተክለ ሃይማኖት አደባባይ ወደ ደብረ ማርቆስ ዩንቨርስቲ መሄጃ
ራሄል መጽሐፍ መደብር
#ባሕርዳር
አዳነ መጽሐፍ መደብር ቀበሌ 4 ዘንባባ ሕንፃ ሥር
5 671
It seems like I can’t generate any more images right now. Please try again later.
Here’s the English translation of your text:
Mengisto, a city founded 3000 years ago, was the capital of both Gojjam and Ethiopia.
During the reign of Emperor Menelik I, 12 kings ruled Ethiopia. He appointed Ephrem, son of Sam, brother of Saint David, as King of Gojjam, giving him the throne to his right, symbolizing high honor.
Starting in 982 A.M. (Ethiopian Calendar), King Ephrem governed the city called “Mengiste Semay” (Kingdom of Heaven), which corresponds to present-day Mengisto in Bichena district.
Later, King Machakel (1157–1197 A.M.) ruled under the title Tsera Qemis (He Who Fights Heresy), continuing Mengisto’s governance.
Lion of David led the city from 1460 to 1470 A.M.
His son, the heroic Ras Wesen Seged of Gojjam, held high authority from 1470 to 1520 A.M. and governed the region.
Ras Wesen Seged’s son, Kifle Yohannes, made Mengisto the city of his reign from the 1520s onward.
Mengisto was also the main capital of Ethiopia:
After heroically defending the empire during the invasion of Gragn (Ahmad ibn Ibrahim), Etige Seble Wongel, wife of Emperor Lebna Dengel, gave birth to Emperor Gelawdewos (r. 1533–1555) in Mengisto, which then became the imperial capital.
Her son Emperor Minas (r. 1555–1559) also ruled from Mengisto.
Emperor Minas gave Etige Seble Wongel’s palace to his wife, prompting the dowager queen to move to Debre Tsmona, where she retired and was buried.
After Emperor Minas, Emperor Sertse Dengel ruled, though the capital is uncertain. Mengisto or nearby Yibab may have served as the capital for over 25 years for Ethiopian emperors and Gojjamite kings.
Evidence includes:
Place names, mountain ranges, and royal palace ruins like those of Emperor Susenyos, Emperor Fasil, and Emperor Bekaffa.
Ancient hand-carved symbols and Christian relics still remain.
Referenced sources:
The Martyrdom of Saint Neakutoleab
The Chronicle of Commander Tekle
History of Ethiopia and the Gojjam Dynasty from Abay to Abay
The Redemption History of Ethiopia
The Sanctuary of Saint Tekle Tsadik
And others spanning from Emperor Lebna Dengel to Emperor Tewodros.
— Abere Arefe Ayinie Adamu
5 671
የብልፅግና ፖለቲካ አማራ ላይ ያለው ከፍታና ዝቅታ የሚታየው በባህርዳሩ መንግስት በኩል እንደሆነ ይታወቃል። ከዚህ ጋር በተገናኘ ከሰሞኑ የባህር ዳር እና የአማራ ክልል ሁኔታ ማህበራዊ ሚዲያወች አንዳንድ አስተያየቶችን ተመለከትኩ እና ባህር ዳር ምን የተለየ ነገር አለ በሚል ምን እየተካሄደ እንደሆነ ለማጣራት ስሞክር አስገራሚ ተጨባጭ መረጃዎችን አግኝቻለሁ።
ላለፉት ረዥም አመታት የአማራን ፖለቲካ ሲከታተል እንደነበረ ሰው ከአማራ ክልል የብልፅግና አመራሮች ቁም ነገር የምጠብቅ ባልሆንም በሰማሁአቸው ነገሮች እጅጉን አዝኛለሁ። ህዝቡ የግል ጥቅማቸውን በሚያሳድዱና በቡድን በተደራጁ፤ የመንግስትን ቢሮ እንደ ምሽግ በሚጠቀሙ ህጋዊ ወንበዴወች፤ ተዘርዝሮ በማያልቅ ግፍና በደል ውስጥ ህይወትን እየገፋ ይገኛል። የአማራ ብልፅግና ከጥንት ብአዴንነቱ ጀምሮ የተጠናወተው የመንደርና ጎጠኝነት አስተሳሰብ ዋናው ችግር ሲሆን ሹመት እና ሌሎች ሀላፊነቶች አካባቢያዊነትን መሰረት አድርጎ መሿሿም እና የግል ጥቅምን ማሳደድ ለውጥ ከሚሉት ጊዜ በፊትም በሰፊው የነበረ ዛሬም የቀጠለ ሲሆን የክልሉ ባለስልጣናት አንዳንዱን ተቋም እንደ ግል እርስት በመቁጠር የመሰላቸውን ሲያደርጉ ቆይተዋል። አሁንም እየቀጠሉ ነው።
የክልሉ የብልፅግና ጽ/ቤት ሀላፊው ይርጋ ሲሳይ የአመራር ሪፎርም እያደረጉ እንደሆነ እና በስፋት እስከ ታችኛው መዋቅራቸው እንደሚቀጥልም ነግሮናል ይህ መግለጫም ያለራሱ ፍላጎት በከፍተኛ አለቆቻቸው ተፅዕኖ የሰጠው ነው እየተባለ ነው። በተለይም እሱና ቡድኖቹ የሚመሩት ስብስብ ድርጅታዊ መረጃዎችንና የፈጠራ ወሬዎችን ለአክቲቪስቶች ይሰጣሉ በሚል ተገምግመዋል። ይህን ተከትሎም ጉዳዩን ለማስተባበል እሳቸው በቦርድ ሰብሳቢነት በሚመሩት የአማራ ሚዲያ በኩል መግለጫ ሰጥተዋል። ከመግለጫቸው ቀደም ባሉት ቀናት የክልሉን ፖሊስ ኮሚሽነር ደስየ ደጀን እና የክልሉን ደህንነት ቢሮ ሀላፊ ደሳለኝ ጣሰውን ከሀላፊነት ማንሳታቸው ይታወቃል። ነገር ግን የእነዚህ ግለሰቦች ከስልጣን መነሳት መነጋገሪያ መሆኑ አልቀረም ከስልጣን ለመነሳታቸው የወቅቱ የባህር ዳር ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው ስሙ በተደጋጋሚ ሲነሳ ሰንብቷል። የብአዴን የወንዜነት ፖለቲካ ከሚቀነቀንባቸው ቦታዎች አንዷ የሆነችው የክልሉ ርዕሰ መዲና ባህርዳር ሁልጊዜም የሽኩቻ ማዕከል ከመሆን አርፋ አታውቅም።
የከተማዋ ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው ነባር የብአዴን አሁንም የብልፅግና ካድሬ ሆኖ ረዘም ላለ ጊዜ ያገለገለ ግለሰብ ሲሆን ከአሁን በፊት በ2013-15 በነበረው የትግራይ ጦርነት ይህ ግለሰብ የህወሀት ወታደሮች ጋይንትን አልፈው ደብረ ታቦር አቅራቢያ በደረሱበት ጊዜ ከሌሎች ማለትም ከእነ አገኘሁ ተሻገር እንዲሁም አብርሀም አለኸኝ እና ሌሎች የክልሉ ባለስልጣናት ጋር በመሆን ቤተሰብ የምናሸሽበት በማለት ከክልሉ ፖርቲ ካዝና ከ4 ሚሊዩን ብር በላይ በመውሰዱ እሱም ሆነ ሌሎች ተገምግመው ገንዘቡን እንዲመልሱ በታዘዙበት ወቅት የትውልድ አካባቢው ዱር ቤቴ የእሱን ቢጤወች ስምሪት በመስጠት መልስ የተባለውን ገንዘብ ማህበረሰቡ በመዋጮ እንዲከፍልለት ያደርገ ለራሱም ሆነ ለወጣበት ማህበረሰብ ክብር የሌለው ከንቱ ሰው ነው። ከዚያ በፊት የምዕራብ ጎጀም ዞን አስተዳዳሪ ሆኖም በርካታ ወጣቶችን በብርሸለቆ አሰቃይቷል። አሁን በተሰጠው የባህር ዳር ከንቲባነት ብዙ ያልቆየ ቢሆንም የክልሉን ወቅታዊ ሁኔታ በመጠቀም በገነቡት ነባር የዝርፊያ መዋቅርን ተጠቅመው ባህር ዳር ከተማ ውስጥ ከ540 በላይ መሬቶች በህገ ወጥ መንገድ በግለሰቦች መያዛቸው በክትትል የተገኙ ሲሆን አሁን ላይ ታግደው ይገኛሉ የከተማ አስተዳደሩ ይሄን የመሬት ዝርፊያ ተከታትሎ ለቁም ነገር ማድረሱ የሚያስመሰግነው ቢሆንም ጥቅማቸው የተነካባቸው አካላት ደግሞ በአንፃሩ ዘመቻ ከፍተው ይገኛሉ። እንዲህ ያለውን ጉዳይ ከግለሰቡ ሳይሆን ከመሬቱ ጥቅም አንፃር መተንተን ተገቢ ነው። ከአሁን በፊትም ነፍሱን ይማረው እና ዶ/ር አምባቸው መኮንን እየተከተለ ስልጣን ሲደረጎት የነበረው መላክ የተባለ የከተማዋ መዘጋጃ ሀላፊ በስርቆት ተጠርጥሮ ሲታሰር ለምን ተብሎ ሰልፍ እስከመውጣት ተደርሶ ነበር። ከዚህም ተሻግሮ ከ50 መኪና በላይ ህዝብ ከጋይንት መጥቶ የፍርድ ሂደቱ ላይ ጫና እንዲያሳድር ተሞክሮ እንደነበር አይዘነጋም። ከተማዋ ላይ እየተሰጡ ያሉ ሰሞነኛ ትችቶችም ከተደራጀ የጥቅም ዝርፊያ ጋር የሚገናኝ እንጅ ከህዝብ ከመቆርቆር የመጣ እንዳልሆነ ይታወቃል።
ከሀላፊነት የተነሳው እና የጎጠኝነቱን መንደር በበላይነት ሲመራ የነበረው ኮሚሽነር ደስየ ደጀን በሀላፊነት ለብዙ አመታት የቆየ ሲሆን በቅርቡ በ2015 ሚያዝያ ላይ የክልሉ ልዩ ሀይል እንዲፈርስ ከበላዩቹ ከባለጊዜወች ትህዛዝ ደርሶት በታዘዘው መሰረት ልዩ ሀይሉን በማዘናጋት ለማፍረስ ከበታች አመራሮቹ ጋር በመሆን ሲዘጋጅ የአማራ ልዩ ሀይል መፍረስ ያንገበገባቸው ሌሎች ሀቀኛ አማራወች ሚሲጥሩን በማውጣት ሰራዊቱ እንዲያውቅ አድርገዋል። ደስየ ለዚህ እኩይ ተልእኮው ከተረኞቹ ባለስልጣናት አዲስ አበባ ገርጂ ከሚባል አካባቢ 500 ካሬ የተበረከተለት ሲሆን ቀጥሎም የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር እንደሚሆን ቃል ተገብቶለት ነበር። በሌላም በኩል ከወልቃይት የእርሻ መሬቶች ከአካባቢው አስተዳደሮች ጋር በመቆራኘት ሰፊ ጥቅም የሚያገኝ ሲሆን የሚያገኘውን ሀብትም ውጭ ሀገር ባሉ የስጋ ዘመዶቹ አካውንት ያከማች እንደነበር ለማወቅ ተችሎአል።
ሚሊሻው ደሳለኝ ጣሰው ደግሞ የትግራይ ጦርነት በሚቀሰቀስበት ወቅት የምዕራብ ጎንደር ሀላፊ ሆኖ ያገለግል በነበረበት ጊዜ የጦርነቱን አጋጣሚ በመጠቀም ዳንሻ ላይ ከህወሀት ታጣቂወች በልዩ ሀይሉ የተማረከ 5 ዲሽቃ 12 መትረጊስ 36 ክላሽ ልዩ ሀይሉ ወደፊት በሚሄድበት ጊዜ መሳሪያወቹን በማውጣት ለአየር ባየር ነጋዴወች የሸጠ ሲሆን ሲጠየቅም ግዳጅ በሄድንበት መጋዝን ተሰብሮ ተዘርፏል ብሎ መልስ የሰጠ ሲሆን ምርመራ ተጣርቶበት በደስየ ትእዛዝ ምርመራው እንዲቆም ተደርጓል። ለጦርነቱ ድጋፍ ከሌሎች የክልሉ አካባቢዎች የሚሄዱ የእህልና የእንስሳት ድጋፎችም በጦርነቱ በጀት የተገዙ በማስመሰል ሲያወራርድ እንደነበር ታሪኩ ያስረዳል። እንዲሁም በዳንሻ ከተማ የነበረ የትግራይ ተወላጆች ሀብት የሆኑ ሁለት ቮልቮ ሎደር እና ሶስት ቶዩታ ሀይሉክስ መተማ በመውሰድ እና በመሸጥ ለግል ጥቅሙ ያወለ ሲበዛ ለዝርፊያ አይኑን የማያሽ ግለሰብ ነው። በደብረብርረን ከተማ የኢንቨስትመንት ቦታ ወስዶ ፋብሪካ የገነባ መሆኑም ተረጋግጧል። እነዚህ የተደራጁ ዘረፋዎችም ወንጀላቸው ተዘርዝሮ ለፌደራሉ መንግስት ተደራጅተው ገቢ መደረጋቸውን ሰምተናል። በባህርዳር ከተማ የራሱን አፋኝ ቡድን አደራጅቶም ውምብድና ሲፈፅም የነበረ የለየለት ዘራፊ እንደሆነም ይነገራል። ታዲያ እንደዚህ የግል ጥቅማቸውን ሲያሳድዱ ለኖሩ ግለሰቦች ነው የህዝብ ተቆርቋሪ ተብሎ የሚቀሰቀስላቸው። የብአዴን ብልፅግና የብልሽት ጣሪያውን የጨረሰ በመሆኑ በውግንና ከመቆም ይልቅ እስከወዲያኛው አሰናብቶ በነፃነት መኖር ተገቢ ነው።
5 671
Repost from ይኸነው የሸበሉ ( ክንዴ )
የአማራ ብሔርተኝነት መሪን ያለ ዘመነ ካሴ ማሰብ ክርስትናን ያለ ኢየሱስ ክርስቶስ ፤ እስልምናን ያለ ነብዩ መሀመድ እንደመስበክ ማለት ነው !
ኮሎኔል መንግስቱ የሚባል የኦሮሞ ብሔርተኛ መሪ በ1966 ዓ.ም ከፀሃፊ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ ጀምሮ እስከ ፓትሪያርኩ ድረስ ከ60 በላይ የአማራ ሙህራንን ከረሸናቸው በኋላ ዋነኛው የአማራ ህዝብ ችግር እስካሁን ባካሄዳቸው ትግሎች መሪን መፍጠር ላይ ነበር። አማራን እኮ የኤርትራው በረከት ስምዖን፣ ትግሬው ህላዌ ዮሴፍ፣ የሲዳማው ተፈራ ዋልዋ ፣ የሀረሩ ኦሮሞ አዲሱ ለገሰም ጭምር የመሩት ከአማራ ሰው ጠፍቶ ሳይሆን መሪ የመፍጠር ችግራችን ነበር። በእርግጥ አሁንም በእጅ አዙርም ቢሆን ባንዳ በየቦታው በመሾም እየመሩን ቅይተዋል። አሁን ግን በፋኖ ትግል አማራ በልጆቹ መመራት ሊጀምር ነው። ወደድህም ጠላህም አሁን ጠልፈህ በሆድህ የምትሸጠው ትግል የለም። እህህህ... መጀመሪያ መሪነቱን ማን ሰጥቶህ ትሸጠዋለህ?
በአማራ ብሔርተኝነት ታሪክ ውስጥ የፕሮፌሰር አስራት ወልደዬስ መስዕዋትነት ጀምሮ በቅርቡ እንኳ ስንት ተዓምር የሚመስል ክህደት አይተናል። በዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ፕሬዝዳንትነት ጣና ላይ የተመሰረተው "አብን" ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ከመሰረቱት የመላው ዓማራ አንድነት ድርጅት ቀጥሎ 2ኛው ተስፋ የተጣለበት እና አማራን ከጫፍ እስከ ጫፍ ያንቀሳቀሰ ብሔርተኛ ፓርቲ ነበር። በአብን ደጋፊነት ስም ከወለጋ እስከ ጅማ ፣ ከድሬዳዋ እስከ አሶሳ ስንቶች ታሰሩ፣ ተሳደዱ፣ ስንቶችስ ተረሸኑ ? ስንቶችስ ሀብት ንብረታቸውን ሸጠው ለፓርቲው አዋሉ? የትየለሌ ነበር። መጨረሻው ግን ድርጅቱን ከመስራቾቹ ከእነ ዶ/ር ደሳለኝ ነጥቆ ፣ የብሔርተኝነቱ ጠንሳሾችን እነ ክርስትያን ታደለ የመሰሉ ፖለቲከኞችን መቀመቅ በማውረድ በምስር ወጥ እና በፖስተኝነት ክፍያ ወደ ጨፍጫፊው አብይ አህመድ ጉያ ስር ለጠፉት።
በመጨረሻም አብን ዳግማዊ መኢሶን ሆነ ። እንደ ምሳሌ "አብን"ንን አነሳሁ እንጅ በቅርቡ እንኳን የአማራ ሴቶች የጋብቻ ቀለበታቸውን ጭምር ሸጠው የተመሰረተው የአማራ ሚዲያ "ዓስራት" በክፍለ ሀገር ኮታ ስም የገቡ ትቂት መዥገሮች የድርጅቱን ካሜራ ሳይቀር ይዘውት እንደጠፉ እና ሚዲያውም ከአየር ላይ መውረዱ ይታወቃል። የአማራ ባንክ ጉዳይም በይደር ይዘነው እንጅ እንደ ብአዴን የልማት ድርጅት እንደሚባሉት አልማ፣ አመልድ፣አብቁተ/ፀደይ ባንክ፣ጥቁር አባይ ትራንስፖርት እና ሌሎች የጥረት/ንጋት ኮርፖሬት ድርጅት የአንድ መንደር ብአዴኖች ቀድሞ በፈጠሩት ኔትወርክ ተጠራርተው እንደያዙት እና በስም አማራ ከመባል እና ከአማራ እናት መቀነት በግዴታ ጭምር ገንዘብ ከመሰብሰብ ውጭ ምንም የአማራነት ለዛም ይሁን ተግባር እንደሌላቸው ይታወቃል።
ይሄ ሁሉ ስግብግብነት እና በአማራ ህዝብ ደም መቆመር ግን ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ በፋኖ ትግል አክትሟል። ከዚህ በኋላ እዚያው ብአዴን ውስጥ ሆነህ ሲያሻህ ምስር ወጥ ፣ ደስ ሲልህ ሰሊጥ ፣ መቀመጡ ሲሰለችህ ደግሞ ፖስታ ማመላለስ ትችል ይሆናል እንጅ ፋኖ ውስጥ እጄን አስረዝሜ ልክ እንደ አብን "በለጠ ሞላ ዳግማዊን" ሾሜ የአማራ ፋኖን ዳግማዊ አብን አደርጋለሁ ብለህ የምትጋጋጥ ባለሁለት እግር አሳማ አትድከም ፣ እንደ ደስዬ ደጀን ቀይ ካርድ እስከሚያሳዩህ አርፈህ አረቄህን ጠጣ።
የአማራ ፋኖ እንደ ባህታዊ የመነኑ መሪወች አሉት። ስልጣን የማያሳሳቸው፣ ብር ሲያዩ የማይደነግጡ ፣ እውቀት የዘለቃቸው ፣ ሁሉ ነገራቸውን ለአማራ ህዝብ ብለው የተው እንደ ዘመነ ካሴ አይነት ቆራጦች አሉበት።
በአጠቃላይ ዶ/ር ደሳለኝን በጫጫታ ከፕሬዚዳንትነት አውርደን በምስር ወጥ ትግል የሚሸጥን እና በተወዳደረበት ቀጠና እንኳ በህዝብ ተመርጦ ፓርላማ መግባት ያልቻለውን በለጠ ሞላን የሾምንበት፤ እንቁ ብሔርተኞችን ክርስቲያን ታደለንና ቴዎድሮስ ሃይለማርያምን ከሽሮ ቤት ወደ ፖስተኝነት የስራ እድል ማግኛ በሚል ወህኒ ቤት ሲያወርዱት ቁጭ ብለን ያየንበት ዘመን አብቅቷል። ከዚህ በኋላ ባይመረጥም እንኳ በታላላኪነቱ ተሹሞ "ህዝብ ማዳበሪያ አጥቶ ተቸግሯል " ብለህ ስትጠይቀው "No comment" የሚል ሱፐር ባንዳ የአማራ መሪ ሊሆን በጭራሽ አይቻለውም። እንግዲህ በተላላኪነት እንኳ ሌላ አዲስ ተላላኪ ሲተካብህ ወይም አንጃዬ ነው የምትለው የሆነ ቡድን በጌቶቹ ሲጠለዝብህ እንደምታደርገው " የበጌምድር ክልል፣ የግዮን ክልል፣የወሎ ክልል... የዳምጠው ክልል" የማለት መብትህ የተጠበቀ ነው። በነገራችን ላይ ጌትነት አልማው የቀድሞው የግዮን ፓርቲ መስራች እና የግዮን ክልል አቀንቃኝ ነበር😂። ከዚህ ጋር ብልፅግና አማራ ክልልን ወደ 6 ደካማ ክልሎች እከፋፍለዋለሁ ብሎ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን አትዘንጉ።
በአማራ ፋኖ እንቅስቃሴ ውስጥ ብዙ እንቁ አርበኞች አሉን። ከእነዚህም ግንባር ቀደሙ ለትግል የመነነውና የወጣትነት ዘመኑን ለአማራ ህዝብ የሰጠው፣ ወንበር ለምኔ ብሎ የኤርትራ በረሃን የመረጠው አርበኛ ዘመነ ካሤ ይገኝበታል። ከወርቅ ላይ ወርቅ ደራርቦ ዩኒቨርሲቲዎችን አስገርሞ የተመረቀ፣ የመንግስትን ሹመትና ማባበያ ከአማራ ህዝብ አይበልጥብኝም ብሎ የኤርትራ በረሃ መግባት እንዲህ ብልፅግና በተከራየላቸው ገስት ሀውስ ውስጥ ተቀምጦ ኪቦርድ እንደመቀጥቀጥ ቀላል የሚመስላቸው አሉ። አርበኛ ዘመነ ካሴ ክላሹን ያነሳው የዛሬ 15 ዓመት መሆኑንም የማያውቁም አይጠፉም እኮ።
አርበኛ ዘመነ ካሴ በአማራ ፋኖ የነፃነት ትግል የመሪነት ሚና ውስጥ እያበረከተ ያለው አስተዋፅዖ የማይተካ ብቻ ሳይሆን የአማራ ብሔርተኝነትን ያለ ዘመነ ካሴ ማሰብ ክርስትናን ያለ ኢየሱስ ክርስቶስ ወይም እስልምናን ያለ ነብዩ መሀመድ እንስበክ እንደማለት ነው።
አርበኛ ዘመነ ካሴ ከከፈለው መስዕዋትነት እና ከልፋቱ አንፃር እንደ መቱሳላ እድሜ ቢሰጠው የአንድ ዘመን ብቻም ሳይሆን የምንጊዜውም የብሔርተኛው የአማራ ትውልድ መሪ ቢሆን ጥቅሙ ለአማራ ህዝብ ብቻ አይደለም።
ከልጅነት ዕድሜው ጀምሮ ለአማራ ነፃነት እያደረገ ያለው ትግልና አመራር ሰጪነት በታሪክ ሲዘከር የሚኖር ለመሆኑ ከኤርትራ በረሃ ጀምሮ የአማራን ህዝብ በማንቃትና ወዶ ገብ ባሪያዎችን ጭምር ከፀረ-አማራዎች መንጋጋ ፈልቅቆ በማውጣት እያስመዘገበ የሚገኘው የትግል ተሳትፎና መሪነት ጉልህ የታሪክ ሥፍራ የሚይዝ ቋሚ ምሥክሩ ነው፡፡
አሁን እየበሰጨኝ ያለው አርበኛ ዘመነ ካሴን ያህል መላ የኢትዮጵያ ህዝብ አንጋጦ በተስፋ የሚጠብቀው መሪ " የአማራ ፋኖ በጎጃም" በሚባል ክ/አገር ፋኖ ሰብሳቢነት ብቻ የሚያዩት ነገር ነው። የሁሉም የአማራ ብሔርተኞች (ዕውነተኞቹ) በልባቸው የተቀመጠ መሪ ብቻ ሳይሆን ንጉስ ነው።
5 671
Repost from ይኸነው የሸበሉ ( ክንዴ )
የአደረጃጀት ዜና!
ቀን 27/0702017ዓ.ም
የአማራ ፋኖ በጎጃም ፩ኛ ክፍለ ጦር የአራቱም ብርጌድ ማለትም የኮሎኔል ታደሰ ሙሉነህ ብርጌድ፣ የሻለቃ አንሙት ያዛቸው ብርጌድ፣ የባህርዳር ብርጌድና የጣናው መብረቅ ብርጌድ አመራሮች እንዲሁም የአማራ ፋኖ በጎጃም ከፍተኛ አማራሮች የሆኑት አርበኛ ተፈሪ ካሳው፣ ፋኖ እሸቱ ጌትነት፣ ፋኖ በለጠ አብርሀም፣ ጠበቃ ቻላቸው ታፈረና ፶ አለቃ ይበልጣል መላካሙ በተገኙበት ጥልቅ የሆነ ውይይትና ግምገማ አካሂዶ ለወቅቱና ቀጠናው የሚመጥኑ አመራሮችን በአዲስ አደረጃጀት ሪፎርም ሰተሰርቷል።
በዚህም መሰረት:-
1. ፋኖ መንግስቱ አማረ------ሰብሳቢ
2. ፋኖ ሙሉሰው የኔአባት-------ምክትል ሰብሳቢ
3. ፋኖ አለልኝ አያና-------የጽ/ ቤት መምሪያ ሀላፊ
4. ፋኖ ሀብታሙ የሱፍ---------የህ/ግ መምሪያ ሀላፊ
5. ፋኖ ታደለን ልየው --------ፓለቲካ መምሪያ ሀላፊ
6. ፋኖ ወርቁ ድልነሳ -----አደረጃጀት ዘርፍ መምሪያ ሀላፊ
7. ፲ አለቃ ቻላቸው አስናቀው-----ወታደራዊ አዛዥ
8. መ/ አ አበራ አግማስ-----------ም/ ወታደራዊ አዛዥ
9. ፋኖ ላመነው ሰጠኝ ---------ዘመቻ መምሪያ ሀላፊ
10. ፋኖ አዳሙ ተናኘ ----ም/ዘመቻ መምሪያ ሀላፊ
11. ሻ/ባ አይንሞኝ ተመስገን---ሎጅስቲክ መ/ ሀላፊ
12. ፋኖ እዮብ አራምዴ-----ፋይናንስ መምሪያ ሀላፊ
13. ፶ አለቃ መኳንንት አለም --------ስልጠና መምሪያ ሀላፊ
14. ፋኖ አንዷምላክ አማረ---------ኦርዲናንስ
15. ዶ/ር እስጢፋኖስ------ጤና መምሪያ ሀላፊ
16. መቶ አለቃ አማኑኤል የሹ----------ሰው ሀይል ሀላፊ
17. ፶ አለቃ ዘውዱ አሞኘ------ወታደራዊ አስተዳደር
18. ፋኖ በላይ ሽቴ-------ቀጠናዊ ትስስር መምሪያ ሀላፊ
19. --------------------መረጃና ደህንነት መምሪያ ሀላፊ
20. ፋኖ እንዳለው ወለላው ---------ግዥ
21. ፋኖ ከፍያለው ጌትነት--------ኦዲተር
22. ፋኖ ስማቸው ምንችል ------ሒሳብ ሹም
23.ፋኖ መኮነን ደሴ -----------ገንዘብ ያዥ ሆነው ተመድበዋል።
አዲስ ትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!
[ የአማራ ፋኖ በጎጃም]
መጋቢት 27/2017 ዓ.ም
5 671
Repost from ይኸነው የሸበሉ ( ክንዴ )
በዚህ ወር ብቻ ለ3ኛ ጊዜ አማራዎች ታግተዋል። ካልሆነ ይሄን መንገድ መዝጋት ይሻላል። አማራዎች ይታገታሉ ገንዘብ ይጠየቃሉ ይከፈላል ወገኖቻችንም በሰላም አይለቀቁም። የአገዛዙ የገንዘብ መሰብሰቢያ ሌላኛው አማራጭ እየሆነ ነው።
