Elon Academy plc ኤሎን አካዳሚ
EVERY STUDENT,EVERY CHANGE,EVERY DAY AT ELON!!! For more information u can join our Facebook page @elon12 or call to us with one of these numbers, 0921 01 57 48 or 0915 5607 77. Txs
Show more4 235
Subscribers
+324 hours
+467 days
+8030 days
Posts Archive
Photo unavailableShow in Telegram
🎉ለ8ተኛ ክፍል የዘንድሮ ክልላዊ ፈተና ተፈታኞች በሙሉ መልካም ፈተና እንላለን። እንተማመንባችኃለን💪🎉
❤ 7
✍ ከዓመቱ የማጠቃለያ ፈተና ጋር በተያያዘ የሚከተሉትን ነጥቦች ልብ ይበሉ✍
👉 ከሰኞ ሰኔ 3-ዓርብ ሰኔ 7 ድረስ የተማሪዋች ለማጠቃለያ ፈተና ዝግጅት እንዲያደርጉ የክለሳ ቀናት ይሆናሉ። ማንም ተማሪ በእነዚህ ቀናት መቅረት አይፈቀድለትም። ከየትኖቹም ኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዋችም ተማሪዋች ነፃ እንዲሆኑ ይጠበቃል።
👉ሰኞ ሰኔ 10፦ትምህርት ስለማይኖር ተማሪዋች በቤት ዉስጥ ይቆያሉ።
👉 ከማክሰኞ ሰኔ 11 አንስቶ የአመቱ የማጠቃለያ ፈተና ይሰጣል። ለሙሉ መረጃዉ በኮምኒኬሽን በኩል የተላከዉን ደብዳቤ ይመልከቱ።
👉 ዐረብ ሰኔ 14 የእርማት ቀን ስለሆነ ተማሪዎች በቤት ይቆያሉ።
👉 ሰኞ ሰኔ 17 የፈተና ወረቀት የሚመለስበት ቀን ሲሆን ተማሪዋች ከጠዋቱ 2:00-6:00 ብቻ ት/ቤት ተገኝተዉ ይወስዳሉ።
🔖 ልዩ ማስታወሻ፦ ቅዳሜ ሰኔ 15 ተማሪዋች የአመቱን የእስፖርት እና የመዝናኛ ቀናቸዉን በት/ቤታቸዉ ተኝተዉ ያሳልፋሉ ።(።ዝርዝር ሁኔታዉ ወደፊት የሚገለጽ ይሆናል።)
🔖 እባክዋን ፈተናዉን ለመዉሰድ የትምህርት ቤት ክፍያን አጠቃሎ በወቅቱ መክፈል የግድ መሆኑን አይዘንጉ።
🎒ተባብረን በመስራት ለዉጥ እናመጣለን🎒
📖ጤና ቆዩን 🙏❤️🙏📖
👍 11
Photo unavailableShow in Telegram
የሚኒስትሪ መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም መመሪያ ለተማሪዎች
➊ የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡
❷ በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን ክብ ብቻ መጠቆር አለበት፡፡
➌ ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው ክብ ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡
❹ ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን ክብ በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡
❺ በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ ክብ ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡
❻ ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡
❼ ለመፃፍ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ተፅፎ ወይም ትንሽ ጭረት እና ነጥብ ከተገኘ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
❽ መልስ በሚጠቆርበት ጊዜ እርሳሱ ከተሰጠው የክብ ሳጥን መውጣት የለበትም። ከወጣም በማጥፊያ (Eraser/Rubber) ማጥፋት ይጠበቅባችኋል።
❾ መልስ መስጫ ኮርነር ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካትም ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡
➓ ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡
👍 5👏 3❤ 2
Todays Students Trip....Grade 1-4 both Branches
7.87 MB
👍 4