cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

የሙጎ አህሉሱናህ ወልጀመዓ ስብስብ

የሚከተለው link(ሊንክ) ጆይን በማድረግ የጀመዓውን የቴሌግራም ቻናል በመቀላቀል ከሚለቀቁ ፅሁፎች ትምህርት እንውሰድ ፡፡ <<መሀበረሰቡን ከበዕድ አምልኮ አላቆ አለህን በብቸኝነት እንዲገዛ ሰበበን ማድረስ የሁላችንም ሀላፍትና ነው>> የሙጎ እና የአከባቢው የአህሉ ሱና ወልጀመዓ የቴሌግራም ቻናል ፡፡ በchannelu ያላችሁን አስተያየት በውስጥ መስመር @Abuhuzeyfa በሚል ማስተላለፍ ይችሃላል።

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
163
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

👆👆👆 #ውሸት ከሙናፊቆች ባህሪ ነው! ከሙመይዓ ሆነው የሱና ዓሊሞችን ከሚተቹ አካላት ማስጠንቀቅ!! ክፍል 1 🔶በደቡብ ክልል በደቡብ ክልል በስልጤ ዞን በምስራቅ ስልጤ አሹቴ ቀብሌ መንደር አንድ ዑስማን መስጂድ የተደረገ ሙሐደራ። 🎙በኡስታዝ ሻኪር ቢን ሱልጣን (ሀፊዘውላህ) 🌐 https://t.me/shakirsultan
Show all...
የሚጃጃሉ ወጣቶች!!! =≡=≡=≡=≡=≡=≡=> 🎙 በሳዳት ከማል አንደበት ➘➘➘⬇️⬇️⬇️↙️ ያ ዳ ም ጡ https://t.me/AbuImranAselefy/4866ከሁለት አመታት በፊት በከሚሴ ከተማ ለተሰበሰቡ ወንድሞች የተሰጠ ምክር ሲሆንከዚህ ምክር የተወሰኑ ነጥቦችን አጠር አድርገን እንመልከት፦ ነጥብ ❶ ሳዳት በዚህ ምክር የመርከዙ ሰዎችንና እነሱን ተከትለው ሙሪድ የሆኑ ወጣቶችን በተመለከተ እያወራ መሆኑን እንገነዘባለን። ነጥብ ❷ ሱናን ከተረዳን በኋላ ኡስታዞች ሲቀየሩ እነሱን ትተን የተረዳነውን ሱና ሙጭጭ አድርገን መያዝ እንዳለብን ይጠቁማል። ነጥብ ❸ የመርከዙ ሰዎች (ሙመይዓዎች) ከ8 አመት በፊት የነበራቸውን አቋም ቀይረው ዛሬ ሌላ አቋም እንደያዙ በሳዳት አንደበት ተገልጿል። ነጥብ ➍ የሰዎች ጥፋት ግልፅ ሆኖ ሳለ እኔ ጃሂል ነኝ እያሉ የኡስታዞቻቸውን ጥፋት ለመሸፋፈን በመሻት የሚጃጃሉ ወጣቶች ትክክል እንዳልሆኑ በሳዳት ተመክሯል። ዛሬ ላይ ከእሱ በጭፍን ለሚከላከሉ ሁሉ መልዕክት ነውነጥብ ❺ ኡስታዝ ተብየዎች እንደበግ ሲነዱህ የምትነዳ መሆን እንደሌለብህ ተጠቁሟል። የሚገርመው ግን ሳዳት በመርከዙ ሰዎች ጠንካራ አቋም ሲሮረው አንበሳ የሚሆኑ፤ ሳዳት ቀዝቀዝ ሲል እንደ ጀናዛ የሚሆኑ ሳዳት እንዳለው ጅላጅል ወጣቶች መኖራቸው ነው። ነጥብ ❻ የኢብኑ መስዑድ መርከዝ ሰዎች በፊት ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚከለክሉና አሁን እንደማይከለክሉ፤ እንዲሁም ከቢድዓ ሰዎች ጋር መራራቅ እንዳለብን የሚመክሩ ነገር ግን አሁን አቋማቸው መቀየሩ በተዘዋዋሪ በሳዳት አንደበት ተመስክሯል። ነጥብ ❼ ኡስታዞች የዱንያ ጥቅም አታሏቸው ወይም ጠመው ሲገለበጡ እኛኮ ከኡስታዞቹ አንወጣም በሚል አስተሳሰብ መጃጃል ከሱፍይ ሙሪዶች የማይሻል አካሄድ እንደሆነ ተጠቁሟል። ነጥብ ❽ የመርከዙ ሰዎች (ሙመይዓዎች) ትናንት ኢኽዋንን ከሱፍዮች ጋር ተስማማ ብለው ሲቃወሙ የነበሩ ቢሆንም ዛሬ ተገልብጠው ራሳቸው ተዘፍቀውበታል። የሚያሳዝነው የራሳቸው ሲሆን የመስለሃ ስም እንደሚሰጡት ተገልጿል። ነጥብ ❾ የመርከዙ ሰዎች (ሙመይዓዎች) ከኢኽዋን የተቃወሙትን ስምምነት ለራሳቸው ገብተውበት ለመስለሃ ነው ሲሉ ለራሳቸው {ለግላቸው} መስለሃ ሊሆን ለአክሲዮናቸው ለድርጅታቸው መስለሃ ሊሆን እንደሚችል ነገር ግን ለዲን መስለሃ እንዳልሆነ ተብራርቷል። ↪️ቆይ አንድ ጊዜ↩️ ሳዳት አሁን ላይ የመርከዙ ሰዎች (ሙመይዓዎች) ጠበቃ ከመሆኑ በፊት ስለ አክሲዮን እያወራ ነበር። በአሁኑ ሰዓት ግን ስለ አክሲዮን የሚያነሱ ሰዎችን ለአላህ ብለው አይደለም እያለ ነው። ለምን ይሆን? አስፈላጊ ከሆነ ለብቻ በሰፊው እመለስበታለሁ። ነጥብ ❿ የመርከዙ ሰዎች (ሙመይዓዎች) የተውሂድ ሰዎችን እንደሚጠሉ ወደ ተውሂድና ሱና የሚጣሩ ሰዎችን እንደሚነድፉ ተጠቁሟልነጥብ ⓫ ሱናን ከተረዱ በኋላ ጃሂል ነኝ እያሉ ወደኃላ ማፈግፈግ ወይም ማላገጥ የትም እንደማያደርስ ተጠቁሟል። ትናንት እነሳዳት በመርከዙ ሰዎች ሲናገሩ ከነሱ በልጦ ሲያነበንብ የነበረ ወጣት ዛሬ እነሳዳት ዝም ሲሉ ጃሂል ነኝ እነ ኢልያስን ለመናገር አቅሜ አይደለም የሚል ከሆነ እውነትም ጃሂል ነው። ግን አያዋጣም!!! ነጥብ ⓬ ጃሂል ነኝ ከምትል ኪታብ ቅራ ስትቀራ ኡስታዞች አቋማቸውን ሲቀይሩ አሪፍ መነፅር ስለያዝክ ቻው ኡስታዝ ከተመለስክ ወደ ድሮው ተመለስ! አለበለዚያ ትቸህ ሄጃለሁ! እንደ ድሮው ጃሂል ነኝ እያልኩ በሪሞት ኮንትሮል ቆም ስትለኝ አልቆምም እገሌን ጥላ ስትለኝ አልጠላም እገሌን ውደድ ስትለኝ አልዎድም የሚል ቆራጥ ውሳኔ መያዝ እንዳለብን ተመክሯል። ለአንዳንድ ወጣቶች ወሳኝ ምክር ነውነጥብ ⓭ ድሮ ሱንዮች ከሙሪድነት የወጡ ነበሩ። ሱፍዮች ብቻ ሸይኾቻቸው መጠጥ ሲጠጡ ብርዝ ነው ይሉላቸው እንደነበር ተገልጿል። ዛሬም አንዳንዶቹ ሰለፍይ ነኝ እያሉ ኡስታዞቻቸው ሲያጠፉ የፈለጉበት እንዲህ ነው እያሉ ስህተቶቻቸውን የማይቀበሉ ዘመናዊ ሙሪድ ሆነዋል። ነጥብ ⓮ ትናንት አገሌ ሸይኽ ኢኽዋንን ሲያስጠነቅቅ ቆይቶ ዛሬ ደግሞ ስለ ኢኽዋንን ማውራት ማለት ሚሳኤል ሆኖበታል። ይሄው ስድስት ሰባት አመት ተከርችሟል የታለ አፉ ስትለው መሻይኾቹኮ ጠንቅቀው ያውቃሉ የሚሉ መሪዶች ስለመኖራቸው ተገልጿል። በነገራችን ላይ በዚህ መልኩ እየተነገረ ያለው በመርከዙ ሰዎች [በሙመይዓወች] ላይ ስለመሆኑ ጥርጥር የለም። ነጥብ ⓯ "ትናንት ስታውቀው የነበረውን ሀቅ ዛሬ ከገለበጥከው እድገቱ ወደታች ነው" ይለናል ሳዳት ይሄ ማለትኮ መሟሟት መቅለጥ ማለት ነው። በቃ ስለ ሙመይዓዎች ጥሩ ግንዛቤ ነበረው ማለት ነውነጥብ ⓰ ኡስታዝኮ እውቀታቸው ስለጨመረ መዲና ተምረው ስለመጡ ሱዳን ደርሰው ስለመጡ ብለን እያልን ከጥፋታቸው መከላከል ተገቢ አለመሆኑ ተብራርቷል። በተለይም ኢልያስ አህመድ መዲና ተምሯል መስጂደ-ነበዊ አስተምሯል እያሉ ከስህተቱ ለመከላከል የሚጥሩ ሙሪዶችን በተመለከተ ጥሩ ምክር ነው። ነጥብ ⓱ የራሳችንን ድክመት ስንደክም ደክመናል ብለን ልናስተካክል፤ ሁሌም ያለንበት ነገር ልክ ነው እንደማይባል በሸሪዓ መመዘን እንዳለብን ተብራርቷል። ነጥብ ⓲ ሰዎች ራሳቸውን ሚዛን አድርገው ያስቀምጡና እነሱ ሲሰሩ ጊዜ ልክ ነበሩ ሲተኙም ልክ ነበሩ እነሱ ሲተኙ ሰው ሲሰራ ደግሞ ሰው ፈጥኗል ሰው ተሳስቷል ይላሉ እውነት ለመናገር ይች ንግግር በሰዓቱ ለመርከዙ ሰዎች ብትሆንም ዛሬ ለማን እንደምትሆን አስተንትኑ! በመርከዙ ሰዎች ላይ አራስ ነብር የነበሩት አካላት አሁን ላይ ሌሎችም ሲያግዟቸው እነሱ ተኙና ሌሎችን ችኩሎች ስህተተኞች ማለት ጀመሩ ↪️የጉድ አገር አሉ አበዎች↩️ ነጥብ ⓳ ዛሬ ሰዎች አቋማቸውን የሚቀያይሩበት ጊዜ ነው። አንተ ዘንድ ሲሆን ኢኽዋኖች አስቸገሩን ይላል ሌላ ቦታ ሲሄድ እነዚህ ፅንፈኞች አስቸገሩን ይላል። አዎ ከመርከዙ ሰዎች ከፊሎቹ ተግባራቸው ከዚህ የተለየ አይደለም። ዛሬ ላይ በአንዳንዶች ቢዘነጋም የወቃሾችን ወቀሳ በማይፈሩ ጀግኖች የመርከዙ ሰዎች እየተንኮታኮቱ ነው። ነጥብ ⓴ አንተጋ ሲሆን ሀፊዘከሏህ ወራዓክ እያለ በቃላት ቢከሽንህም እላይ ቢያጦዝህም ወደዚያ ዞር ያለ ቀን ከማጠልሸት አይቆጠብም። ከዚህ በቀላሉ ስሜታቸውን ከሚከተሉ ሰዎች ጋር መንቀሳቀስ እንደሌለብን እንገነዘባለን። ማጠቃለያ፦ ሳዳት ከማል በዚህ ምክር ላይ ያነሳቸውን ነጥቦች ሁሉም ወጣቶች (በተለይ ሙሪዶች) ሊተገብሩት ይገባልበተጨማሪም የመርከዙ ሰዎች ላይ እንደዚህ ጠንከር ያለ አቋም እንደሚያስፈልግ በግልፅ መረዳት ይቻላል። እነሳዳትም በነሱ ላይ በፊት እንዲሁ ጠንካሮች ነበሩ። እርምት ያለው ➘➘➘⬇️↙️ https://t.me/AbuImranAselefybot ➚➚➚ በዚህ ያድርሰኝ ዝም አንልም እኛ በህይወት እስካለንባለችው አቅማችን እንፋለማለን፤ ያበጠው ይፈንዳ ሲፈልግ ይተርተር፤ እውነት ይነገራል ቢጣፍጥም ቢመር። https://t.me/AbuImranAselefy https://t.me/AbuImranAselefy https://t.me/AbuImranAselefy
Show all...
Abu Imran Muhammed Mekonn

የሚጃጃሉ ወጣቶች!!! =≡=≡=≡=≡=≡=≡=> 🎙 በሳዳት ከማል አንደበት ➧ ከዚህ ምክር የተወሰኑ ነጥቦችን አጠረሰ አድርገን እንመልከት፦ ነጥብ ❶ ሳዳት በዚህ ምክር የመርከዙ ሰዎችንና እነሱን ተከትለው ሙሪድ የሆኑ ወጣቶችን በተመለከተ እያወራ መሆኑን እንገነዘባለን። ነጥብ ❷ ሱናን ከተረዳን በኋላ ኡስታዞች ሲቀየሩ እነሱን ትተን የተረዳነውን ሱና ሙጭጭ አድርገን መያዝ እንዳለብን ይጠቁማል። ነጥብ ❸ የመርከዙ ሰዎች (ሙመይዓዎች) ከ8 አመት በፊት የነበራቸውን አቋም ቀይረው ዛሬ ሌላ አቋም እንደያዙ በሳዳት አንደበት ተገልጿል። ነጥብ ➍ የሰዎች ጥፋት ግልፅ ሆኖ ሳለ እኔ ጃሂል ነኝ እያሉ የኡስታዞቻቸውን ጥፋት ለመሸፋፈን በመሻት የሚጃጃሉ ወጣቶች .... ይህንን ጨምሮ ሌሎች ⓴ ነጥቦችን በሚከተለው ሊንክ ገብተው ያንብቡ!!! ➘➴➷ ⬇️⬇️⬇️↙️↙️↙️

https://t.me/AbuImranAselefy/4867

እርምት ያለው ➘➘➘⬇️↙️

https://t.me/AbuImranAselefybot

➚➚➚ በዚህ ያድርሰኝ ዝም አንልም እኛ በህይወት እስካለን፤ ባለችው አቅማችን እንፋለማለን፤ ያበጠው ይፈንዳ ሲፈልግ ይተርተር፤ እውነት ይነገራል ቢጣፍጥም ቢመር። ➘➴➷➘➴➷➘➴➷

https://t.me/AbuImranAselefy

https://t.me/AbuImranAselefy

https://t.me/AbuImranAselefy

Photo unavailableShow in Telegram
⭕️መልካም ሰው ሁን ለሰዎች ብቻ ሰይሆን አሏህ ለፈጣረቸው መኽሉቅ በሙሉ ⭕️ አንተ ብቻ ንፁህ ልብ ይኑርህ ሁሌም ለሰዎች መልካም ሁን ሰዎች ለአንተ መጥፎ ቢሆኑም እንካ ምክንያቱም አሏህ ልብህን ነው የሚማላከታው መልካም ሰው በመሆንህ የመጀመረ የምትጠቀመው አንተው ነህ በመልካምነትህ ብቻ አሏህ ለአንተ ሁል ነገር ገር እንዲሆንልህ ና በደረስከባት ሚድርና ቦታ ሰዎች ለአንተ መልካም እንዲሆኑ የደርገል ምክንያቱም አሏህ መልካሞችን ይወዳልና አንተ የአሏህን ፊት ፈልጋህ መልካም ሁን ሰዎች መጥፎ ሆኑቡኝ ብላህ አብረህ ከእነሱ ጋር መጥፎ አትሁን ልዩነቱም እዚህ ጋር ነው እነሱ መጥፎ ስሆኑብህ ጀግና ከሆንካ አንተ ደሞ ጥሩ ትሆነልህ ያኔ ትልቅ ሰው ነህ ማለት ነው ። አማ እነሱ ለኔ መጥፎ ነቻው ብላህ መጥፎ ከሆነከ ታደ የአንተ ከእነሱ መሻልህ ምኑ ለይ ነው⁉️ ✍ኡሙ ዑሰይሚን https://t.me/umusaymen
Show all...
ረመዷን ብዙዎች ተውበት የሚያደርጉበት ወር ነው! ————— እርሶስ መች ነው ወደ አላህ ከልብዎት ቁርጥ ያለ ተውበት አድርገው ካሉበት ወንጀል የሚመለሱት??? በተለያዩ ወንጀሎች ውስጥ ተዘፍቀው ለሚገኙት ሁሉ አዛኙና መሃሪው አምላካቸው አላህ እንዲህ እያለ ይጠይቃል:- ﴿أَفَلا يَتوبونَ إِلَى اللَّهِ وَيَستَغفِرونَهُ وَاللَّهُ غَفورٌ رَحيمٌ﴾ الماءدة ٧٤ “ወደ አላህ ተፀፅተው አይመለሱምን? ምህረትን አይለምኑትምን?፣ አላህ መሃሪ አዛኝ ነው።” አል-ማኢደህ 74 ከወንጀል ወደ አላህ ተፀፅቶ ለመመለስ (ለተውበት) ጠንካራና አይቀሬ የሆኑ 5 መስፈርቶች አሉት። ታላቁ ሸይኽ ኢብኑ ዑሰይሚን (ረሂመሁላህ) እንደሚከተለው አስቀምጠዋቸዋል:- ① ለአላህ ብሎ ኒያን በማጥራት (በኢኽላስ) ወደ አላህ ተፀፅቶ መመለስ ነው። ኢኽላስ አምልኮን ለአላህ ብሎ ጥርት አድርጎ መፈፀም ለሁሉም የአምልኮ ዘርፍ መስፈርት ነው። ከወንጀል ወደ አላህ ተፀፅቶ መመለስ ደግሞ ከአምልኮ ዘርፎች አንዱ ነው። አላህ እንዲህ ብሏል:- ﴿وَما أُمِروا إِلّا لِيَعبُدُوا اللَّهَ مُخلِصينَ لَهُ الدّينَ حُنَفاءَ﴾ البينة ٥ “አላህን ሀይማኖትን ለእርሱ ብቻ አጥሪዎች፣ ቀጥተኞች ሆነው እንዲገዙት እንጂ በሌላ አልታዘዙም።” አል-በይነህ 5 ሰዎች እንዲያዩለት ወይም ደግሞ አላህን አልቆና ፈርቶ ሳይሆን (የሸሪዓ ሀገር ሆኖ) በባለ ስልጣኖች ቅጣት እንዳይደርስበት ፈርቶ ተውበት ያደረገ ከሆነ ተውበቱ ተቀባይነት የለውም!። ② በፈፀመው ወንጀል ላይ ተፀፃች መሆን አለበት። አላህ ያዘዘውን ነገር ባለ መፈፀም ከነበረ ወንጀል የሰራው፣ ሀያል የሆነው የአምላኩን አላህን ትእዛዝ ባለ ማክበሩ ሊቆጭና ሊፀፀት ይገባል። አልያም አላህ የከለከለውን ነገር በመፈፀም ከሆነ የተገበረው መተው እየቻለ ፈጣሪውን አላህን በማመፁ የአላህን ሀያልነት በማስታወስ እርሱ ፊት ቆሞ እንደሚጠየቅ በማስታወስ ሊቆጭና ልቡ ሊሰበር ይገባል። ③ ተፀፅቶ ከተመለሰበት (ተውበት) ካደረገበት ወንጀል ሙሉ በሙሉ መላቀቅ አለበት። የፈፀመው ወንጀል ግዴታ የተደረገበትን ነገር አለመፈፀም ከነበር ያንን ነገር ሙሉ በሙሉ መፈፀም። ለምሳሌ:- አንድ ሰው ወንጀል የሰራው ዘካ በመከልከል ከነበረ ዘካውን በአግባቡ ያለፈውንም ጭምር አስቦ መስጠት ተውበቱ ተቀባይነት እንዲኖረው ግዴታ ይሆንበታል። ወይም ስርቆትን የመሰለ ሀራም ነገር የተገበረ ከሆነ ተውበቱ ተቀባይነት እንዲኖረው የሰረቀውን ገንዘብ ለባለቤቱ መመለስ አለበት። ተውበት ባደረገበት ወቅት የሚመልሰው ገንዘብ ከሌለው ሲያገኝ መመለስ ይጠበቅበታል። ባለቤቱ ከሌለ ለወራሾቹ፣ ወራሽ ዘመድ ከሌለው ለሙስሊሞች የገንዘብ ግምጃቤት (ለበይተል ማል)፣ የሙስሊሞች ግምጃቤት (በይተል ማል) ከሌለ ሙሉ ገንዘቡን ሶደቃ ያደርግለታል። ገንዘቡን ለባለቤቱ በአካል መስጠቴ ለሌላ አደጋ ሊያጋልጠኝ ይችላል ብሎ ከፈራ፣ በሌላ በማያሰጋው መንገድ በተዘዋዋሪ አድርጎ መመለስ ግዴታ ይሆንበታል። ④ ተውበት ካደረገ በኋላ፣ ተውበቱ ተቀባይነት እንዲኖረው፣ ተውበት ወዳደረገበት ወንጀል ላለመመለስ ቁርጥ ያለ አቋም መያዝ ግዴታ ይሆንበታል። ⑤ አንድ ሰው ከወንጀሉ ወደ አላህ ተፀፅቶ (ተውበት) አድርጎ የሚመለስበት ወቅት ተውበቱ ተቀባይነት የሚያገኝበት ወቅት መሆን አለበት። ይህ ማለት ሁለት ተውበት ተቀባይነት የማያገኝበት የተለያዩ ጊዜዎች አሉ፣ እናም በነዚህ ጊዜያት መሆን የለበት። እነሱም:- 1, በሰውዬው በራሱ ብቻ የተገደብ ጊዜ ነው፣ እርሱም የሞት ገርገራ ላይ ከሆነ ተውበቱ አይጠቅመውም። 2, ሁሉንም ሰው አካታች የሆነ ጊዜ ነው፣ እርሱም ፀሃይ ከገባችበት የምትወጣበት ጊዜ ነው፣ በዚህን ጊዜ የሚደረግ ተውበት ለማንም አይጠቅምም።” [ሸርህ አል-አርበዑን ኢብኑ ዑሰይሚን 1/417] ለእነዚህ መስፈርቶች ሸይኹ ኪታባቸው ውስጥ ማስረጃ ያስቀመጡ ሲሆን፣ እኔ ግን ከጊዜ አንፃር ለማሳጠር ብዬ ነው ማስረጃዎችን ያልጠቀስኳቸው፣ ማስረጃዎችን ማየት የፈለገ በተጠቀሰው ገፅ ከኪታቡ ማየት ይችላል። በዚህ ጊዜ እየታየ ያለው ትልቁ ችግር ብዙ ሰዎች ረመዷን ሲገባ ብቻ ተውበት ያደርጉና ከረመዷን በኋላ ግን ወደዚያው ሲመለሱ ይስተዋላል። ይህ ከባድ የሆነ አደጋ ነው!፣ ወንጀሉንም ሙሉ በሙሉ አያስምርለትም። ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያ (ረሂመሁላህ) እንዲህ ብለዋል:- “በረመዷን ወር ብቻ ወንጀልን በመተው ላይ ቁርጥ አቋም የያዘ ሰው፣ ከረመዷን በኋላም ያለውን ጊዜ ያላካተተ ከሆነ፣ ይህ ጥቅል በሆነ መልኩ ተውበት አድራጊ አይደለም። ነገር ግን በረመዷን ውስጥ ይህን ወንጀል ከመፈፀም ተቆጥቧል፣ ይህን ያደረገው ለአላህ ብሎና የእርሱን ህግጋት (የእስልምናን እሴት) በማላቅ ከሆነ፣ ይህን ጊዜ በማክበር እርም የተደረገበትን በመተው፣ በዚህ ተግባሩ ብቻ ነው አጅር የሚያገኘው። እንጂ እርሱ ከነዚያ ሙሉ ተውበት ከሚያደርጉትና ሙሉ ተውበት በማድረጋቸው ጥቅል በሆነ መልኩ ወንጀላቸው ከሚተውላቸው (ምህረት) ከሚደረግላቸው ሰዎች አይደለም።” [መጅሙዕ አል-ፈታዋ 10/744 ✍🏻ኢብን ሽፋ: (t.me/ibnshifa) #join ⤵️ የተለያዩ ት/ቶችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችን ⤵️ #join በማድረግ ይቀላቀሉ https://telegram.me/IbnShifa https://telegram.me/IbnShifa https://telegram.me/IbnShifa
Show all...
[ኢብን ሽፋ Ibn Shifa]

Photo unavailableShow in Telegram
ታላቁ ዓሊም ሸይኽ ዐብዲል ዐዚዝ ኢብኑ ባዝ (ረሂመሁላህ) እንዲህ አሉ:- «ልክ በረመዷን ወር የሚፈፀም መልካም ተግባር (አላህን መታዘዝ) አላህ ዘንድ ምንዳው ከሌላ ጊዜው እጥፍ ድርብ እንደሆነው ሁሉ፣ በረመዷን ወር ውስጥ የሚፈፀም ወንጀልም (አላህን ማመፅ) ከሌላ ጊዜው የከፋ ነው።» መጅሙዕ አልፈታዋ 15/446 የተለያዩ ት/ቶችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችን ⤵️ #join በማድረግ ይቀላቀሉ https://telegram.me/IbnShifa https://telegram.me/IbnShifa
Show all...
ወላጆችን በሶላቱ ተራዊህ ዱዓ አንርሳቸው!! ታላቁ ዓሊም ሙሀመድ ቢን ሷሊህ አል-ዑሰይሚን (ረሂመሁላህ) እንዲህ አሉ:- “ለወላጆችህ በሶላቱ ተራዊህ አለያም በሶላቱ ተሀጁድ ወቅት የምታደርገው ዱዓ አስር ግመሎችን ከምታርድለት ይበልጣል!።” ሊቃኡል ባቢል መፍቱህ 115 #join ⤵️ https://t.me/IbnShifa
Show all...
[ኢብን ሽፋ Ibn Shifa]

እራስህን ሁል ጊዜ ለቁርኣንና ለሀዲስ ተጎታች አድርግ! በአንድ ነገር ላይ ከቁርኣንና ከሀዲስ ማስረጃ ሳታገኝ አቋም አትያዝ! ሁሌም ለሰዎች መልካምን ተመኝ! ለሀቅ እንጂ ለሰዎች ወጋኝ አትሁን

س٤.من أين نأخذ عقيدتنا؟ ج. من القرآن الكريم، والسنة النبوية، والسلف الصالح. https://t.me/nahar_asunna
Show all...
➜ረ መ ዷ ን ⓸ ኛው ቀን ➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫➫ ክፍል አንድን ለማግኘት ⬇️⬇️ https://t.me/AbuYehyaAselefy/6487 ክፍል ሁለትን ለማግኘት ⬇️⬇️ https://t.me/AbuYehyaAselefy/6507 ክፍል ሶስትን ለማግኘት ⬇️⬇️ https://t.me/AbuYehyaAselefy/6526 #ርዕስ፦➘➘➘➘➘➘➘➘ ⓷ የረመዷን ወር ትሩፋቶች 🎤 #በታላቁ ሸይኽ ዐብዱልሐሚድ አል-ለተሚ (ሀፊዘሁሏህ) ➘➘➘➘➘➘➘➘ ✅ https://t.me/abdulhamhttps://t.me/abdulhamhttps://t.me/abdulhamhttps://t.me/AbuYehyaAselefy/6538
Show all...
⏫🎤 #مقطع_صوتي ڪيف نڪون مــن أهــل الآخــرة ⁉️ الشيخ / #محمد_مختار_الشنقيطي ➣ @sogiaalarowah
Show all...
✅ #ረመዷን ሶስተኛው (⓷) ቀን #ርዕስ፦➴➴➴ (❷) የረሡል ( ﷺ) ሕይዎት በረመዷን ➢ ረሡል ( ﷺ) ስንት ረመዳኖችን ፆመዋል? ➢ ረሡል ( ﷺ) አብዛኛውን ጾም የፈቱት በስንት ነው?... 🎤 #በታላቁ ሸይኽ ዐብዱልሐሚድ አል-ለተሚ (ሀፊዘሁሏህ) ➴➴➴➴➴ ✅ https://t.me/abdulhamhttps://t.me/abdulhamhttps://t.me/abdulham
Show all...