en
Feedback
Fozu

Fozu

Open in Telegram

"በጊዜያቱ እምላለሁ ፤ ሰው ሁሉ በእርግጥ በኪሳራ ውስጥ ነው ፤ እነዚያ ያመኑትና መልካሞችን የሠሩት ፥ በእውነትም አደራ የተባባሉት ፥ በመታገስም አደራ የተባባሉት ብቻ ሲቀሩ" ሱረቱል ዐስር፦(1፥3)

Show more
1 005
Subscribers
No data24 hours
-97 days
-3130 days
Posts Archive
Fozu
1 005
Shad multimedia introduction || ሻድ መልቲሚዲያ https://youtube.com/watch?v=z8F63yusNLM&si=RLSrsD6g8SO3WGoZ

Fozu
1 005
Shad multimedia introduction || ሻድ መልቲሚዲያ https://youtube.com/watch?v=z8F63yusNLM&si=RLSrsD6g8SO3WGoZ

Fozu
1 005
⚠️በሐበሻ ምድር ሙመይዓዎች እነማን ናቸው❓ ✅ አስር ( 🔟 ) ጥሩ! በአንድ ሰው ላይ ሁለት ምስክሮች ቢመጡ መግደሉን ለመመስከር ይህ ሰው ለመግደሉ ሁሉም ማህበረሰብ የግድ በአጠቃላይ መስማማት አለበት! ማለቴ እከሌ እከሌን ገድሎታል ብሎ በእከሌ ላይ ለመመስከር ሁሉም ማህበረሰብ የግድ በአጠቃላይ መስማማት አለበት! ዳኛው አንድም በዲያ (በካሳ ክፍያ) ወይም በቂሷስ (በማመሳሰል እርምጃ) ላይ በአላህ ህግ መዳኘት ግዴታ አለበት፡፡ የአላህን ሸሪዓ ተፈጻሚ ማድረግ አለበት፡፡ ሙብተዲዕን ሙብተዲዕ ከማለት በጣም አደጋ በሆነው በዚህ ጉዳይ ላይ ሁሉም መስማማት መስፈርት ነው!? እነዚህ ሙመይዓ ፣ የባጢል ባለቤቶች ፣ የተንኮል ተጣሪዎች ፣ እንደሚባለው በደፈረሰ ውሃ አዳኝ ናቸው፡፡ ይህን የተበላሽ ንግግራቸውን አትስሙ፡፡ አንድ እውቀት ያለው ዓሊም ሲተች - ባረከሏሁ ፊከ - ይህን ትችት መቀበል ግድ ነው፡፡ አንድ ፍትሀዊ የሆነ ፣ ችሎታ ያለው ዓሊም ከተቃወመ ደግሞ የሁለቱ ንግግር ይጠናል ፣ ትችቱም ውዳሴውም ይታያል፡፡ ትችቱ የተተነተነ እንዲሁም ግልጽ ከሆነ የሚያወድሱት ቁጥራቸው ቢበዛም ፣ ትችቱ ከውዳሴው ይቀደማል፡፡ አንድ ዓሊም አስር ወይም አምሳ አሊሞች - ውጫዊ ገጽታን በማየትና በመልካም በመጠርጠር ምንም አይነት ማስረጃ ሳይዙ አንድን ግለሰብ ቢያወድሱ -ስለዚህ ሰው የተተነተነ ትችት ይዞ የመጣው ሰው- ማንም ቢቃወምም - ትችቱ ይቀደማል፡፡ ምክንያቱም ተችታ ከእርሱ ጋር ማስረጃ አለ ፤ ማስረጃ ደግሞ ሊቀደም ይገባዋል፡፡ ምድርን የሚሞላ ሰው ቢቃወም ማስረጃን እናስቀድማለን ! ማስረጃው ከእርሱ ጋር ሆኖ የምድር ባለቤቶች ሁሉ ቢቃረኑት ፣ ምንም ይሁን ምን ሀቁ ከእርሱ ጋር ነው፡፡ ጀማዓ ማለት ደግሞ ብቻውን እንኳ ቢሆን በሐቅ ላይ የሆነ ሰው ነው፡፡ አንድ ሰው በሱና ከሆነ ሙብተዲዕ የሆኑ የሁለት ወይም የሶስት ከተማ ሰዎች ቢቃረኑት ሀቁ ከእርሱ ጋር በመሆኑ ፣ ከሌሎች ጋር ያለው ባጢል በመሆኑ መረጃ ይቀደማል፡፡ ሀቅን ማክበር ግዴታችን ነው ፤ ማስረጃን ማክበር ይገባል፡፡ አላህ በተከበረው ቁርኣናዊ አንቀጽ የሚከተለውን ተናግሯል፡- (قُلْ هَاتُوا۟ بُرْهَٰنَكُمْ إِن كُنتُمْ صَٰدِقِينَ) “እውነተኞች እንደሆናችሁ አስረጃችሁን አምጡ” በላቸው፡፡ (አል በቀራህ፡111) (وَإِن تُطِعْ أَكْثَرَ مَن فِي الْأَرْضِ يُضِلُّوكَ عَن سَبِيلِ اللَّهِ ۚ )     “በምድርም ካሉት ሰዎች አብዛኞቹን ብትከተል ከአላህ መንገድ ያሳስቱሃል፡፡” (አል አንዓም፡116) ማስረጃ አልባ የቁጥር ብዛት ዋጋ አይስሰጠውም፡፡ ትንሽ ቁጥር ካላቸው ውጭ የምድር ሰው በአጠቃላይ በውሸት ቢሰባሰብ ማስረጃ አልባ ከሆኑ ግምት አይሰጠውም፡፡ አንድ ወይም ትንሽ ቁጥር ያላቸው ሰዎች እንኳ ተቃራኒ ቢሆኑም ከማስረጃ ጋር እስከሆነ ድረስ ሀቅን በማወቅ ፣ እርሱን አጥብቃችሁ በመያዝና ሐቅን በመቀበል አላህን ፍሩ አላህን ፍሩ !! አላህ ለሁሉም ሀቁን ይግጠም!” (شريط المنهج التميعي وقواعده للشيخ حفظه هللا)                                       -አሁንም ተጠየቁ፡ “አንድ ግለሰብ ከፊሉ ሙብተዲዕ ፣ ከፊሉ ደግሞ ሙብተዲዕ አይለውም አንዳንድ ተማሪዎች ሙብተዲዕ ያላሉትን ሰዎች ንግግር ይከተላል፡፡ እርሱን ማውገዝ ይበቃልኛል?” መልስ፡ “በርካታ ወጣቶች ሀቅን ከማወቃቸው ጋር ይህ በአሁኑ ሰዓት በአካባቢያችን የሚገኝ ፈተና ነው፡፡ ባረከሏሁ ፊከ በእርግጥ ረዘመች! በእርግጥ ረዘመች! አንድን ሰው ሙብተዲዕ ለማለት ወይም ለመተቸት የዑለሞች ስምምነት መስፈርት አይደለም፡፡ ይልቁንም ለመተቸትም ይሁን ለማወደስ የአንድ ሰው ንግግር በቂ ነው፡፡ ጀማዓዎች ከተቹት ወይም ሙብተዲዕ ካሉት ሀቅን ለሚፈልግ ሰው በቂው ነው፡፡ ዝንባሌውን የሚከተለው ሰው ከሆነ ግን በሸረሪት ድሮች ይንጠለጠላል እንጅ አንድም ነገር አይበቃውም፡፡ ሰዎች ይህን ትችት የሚባለውን ነገር አላወቁትም፡፡ ሰዎች ተጠምደዋል፡፡ ሰዎች ይህ ሰው የተተቸ መሆኑን መተቸት የሚገባው መሆኑንም ተምረዋል ፣ አውቀዋል፡፡ ምክንያቱም ውሸታም በመሆኑ ፣ ዑለሞችን በመዝለፉ ፣ የሰለፎችን መንሐጅና ባለቤቶች በመቃወሙ ፣ የተበላሹ መሰረቶችን በማበጀቱ ፍትሀዊነቱ ውድቅ ተደርጓል፡፡ ይህን ሁሉ አውቀዋል፡፡ ከምክር በኋላ አይዘንም ይላሉ፡፡ መከሩ ፣ አብራሩ ይህ ሰው እምቢ አለ፡፡ እርሱን ሙብተዲዕ ለማለት ተገደዱ! በዚህ አይነት የቀረ በሸረሪት ድሮች የሚንጠለጠል ሰው ምንድን ነው ምክንያቱ? (ወላሂ እከሌ አወድሶታል!) (ወላሂ በሙብተዲዕነቱ ዑለሞች አልተስማሙም!?) ይላሉ! ሙብተዲዕ ያላሉ ሰዎች በሁለት ይከፈላሉ፡ አንደኛው ያልተማሩ ሰዎች ናቸው ፣ እነርሱም ምክንያት ይሰጣቸዋል፡፡ ሁለተኛው የተማሩ ፣ ለውሸት የሚከላከሉ ናቸው፡፡ ከእነርሱ ዘንድ ያለውን ውሸት ምን እንደሆነ ያውቃሉ ፣ እምቢ ብለው ለዚህ ሙብተዲዕ መከላከል እንጅ ሌላ አላማ የላቸውም፡፡ እነዚህ ምንም ዋጋ አይሰጣቸውም፡፡ ዝም ባዮች ዝምታቸው መረጃ አይሆናቸውም፡፡ እነዚያ ከሰውዬው ላይ ያሉ ነገሮችን ሁሉ የተቹ ፣ በሚገባው ያብራሩ መረጃው ከእነርሱ ጋር በመሆኑ ከዚህ በፊት እንደጠቆምኩት ሐቀኛ ለሆነ ሰው ከአላህ -ዓዘ ወጀለ- ዘንድ ምንም አይነት ምክንያት የሌላቸው ለሆኑትና በሸረሪት ድሮች ላይ ለሚንጠለጠሉት ሳይሆን (መረጃው ከእነርሱ ጋር የሆነውን) ሐቅን መያዝ ግዴታ አለበት፡፡ ✍🏼 ፀሀፊ የተከበሩ ሼኽ ሁሴን ሙሀመድ አስልጢ  (ዶ/ር) ✍🏼 ተርጓሚ ኡዝታዝ ዩሱፍ አህመድ

Fozu
1 005
⚠️በሐበሻ ምድር ሙመይዓዎች እነማን ናቸው❓ ✅ አስር ( 🔟 ) ጥሩ! በአንድ ሰው ላይ ሁለት ምስክሮች ቢመጡ መግደሉን ለመመስከር ይህ ሰው ለመግደሉ ሁሉም ማህበረሰብ የግድ በአጠቃላይ መስማማት አለበት! ማለቴ እከሌ እከሌን ገድሎታል ብሎ በእከሌ ላይ ለመመስከር ሁሉም ማህበረሰብ የግድ በአጠቃላይ መስማማት አለበት! ዳኛው አንድም በዲያ (በካሳ ክፍያ) ወይም በቂሷስ (በማመሳሰል እርምጃ) ላይ በአላህ ህግ መዳኘት ግዴታ አለበት፡፡ የአላህን ሸሪዓ ተፈጻሚ ማድረግ አለበት፡፡ ሙብተዲዕን ሙብተዲዕ ከማለት በጣም አደጋ በሆነው በዚህ ጉዳይ ላይ ሁሉም መስማማት መስፈርት ነው!? እነዚህ ሙመይዓ ፣ የባጢል ባለቤቶች ፣ የተንኮል ተጣሪዎች ፣ እንደሚባለው በደፈረሰ ውሃ አዳኝ ናቸው፡፡ ይህን የተበላሽ ንግግራቸውን አትስሙ፡፡ አንድ እውቀት ያለው ዓሊም ሲተች - ባረከሏሁ ፊከ - ይህን ትችት መቀበል ግድ ነው፡፡ አንድ ፍትሀዊ የሆነ ፣ ችሎታ ያለው ዓሊም ከተቃወመ ደግሞ የሁለቱ ንግግር ይጠናል ፣ ትችቱም ውዳሴውም ይታያል፡፡ ትችቱ የተተነተነ እንዲሁም ግልጽ ከሆነ የሚያወድሱት ቁጥራቸው ቢበዛም ፣ ትችቱ ከውዳሴው ይቀደማል፡፡ አንድ ዓሊም አስር ወይም አምሳ አሊሞች - ውጫዊ ገጽታን በማየትና በመልካም በመጠርጠር ምንም አይነት ማስረጃ ሳይዙ አንድን ግለሰብ ቢያወድሱ -ስለዚህ ሰው የተተነተነ ትችት ይዞ የመጣው ሰው- ማንም ቢቃወምም - ትችቱ ይቀደማል፡፡ ምክንያቱም ተችታ ከእርሱ ጋር ማስረጃ አለ ፤ ማስረጃ ደግሞ ሊቀደም ይገባዋል፡፡ ምድርን የሚሞላ ሰው ቢቃወም ማስረጃን እናስቀድማለን ! ማስረጃው ከእርሱ ጋር ሆኖ የምድር ባለቤቶች ሁሉ ቢቃረኑት ፣ ምንም ይሁን ምን ሀቁ ከእርሱ ጋር ነው፡፡ ጀማዓ ማለት ደግሞ ብቻውን እንኳ ቢሆን በሐቅ ላይ የሆነ ሰው ነው፡፡ አንድ ሰው በሱና ከሆነ ሙብተዲዕ የሆኑ የሁለት ወይም የሶስት ከተማ ሰዎች ቢቃረኑት ሀቁ ከእርሱ ጋር በመሆኑ ፣ ከሌሎች ጋር ያለው ባጢል በመሆኑ መረጃ ይቀደማል፡፡ ሀቅን ማክበር ግዴታችን ነው ፤ ማስረጃን ማክበር ይገባል፡፡ አላህ በተከበረው ቁርኣናዊ አንቀጽ የሚከተለውን ተናግሯል፡- (قُلْ هَاتُوا۟ بُرْهَٰنَكُمْ إِن كُنتُمْ صَٰدِقِينَ) “እውነተኞች እንደሆናችሁ አስረጃችሁን አምጡ” በላቸው፡፡ (አል በቀራህ፡111) (وَإِن تُطِعْ أَكْثَرَ مَن فِي الْأَرْضِ يُضِلُّوكَ عَن سَبِيلِ اللَّهِ ۚ )     “በምድርም ካሉት ሰዎች አብዛኞቹን ብትከተል ከአላህ መንገድ ያሳስቱሃል፡፡” (አል አንዓም፡116) ማስረጃ አልባ የቁጥር ብዛት ዋጋ አይስሰጠውም፡፡ ትንሽ ቁጥር ካላቸው ውጭ የምድር ሰው በአጠቃላይ በውሸት ቢሰባሰብ ማስረጃ አልባ ከሆኑ ግምት አይሰጠውም፡፡ አንድ ወይም ትንሽ ቁጥር ያላቸው ሰዎች እንኳ ተቃራኒ ቢሆኑም ከማስረጃ ጋር እስከሆነ ድረስ ሀቅን በማወቅ ፣ እርሱን አጥብቃችሁ በመያዝና ሐቅን በመቀበል አላህን ፍሩ አላህን ፍሩ !! አላህ ለሁሉም ሀቁን ይግጠም!” (شريط المنهج التميعي وقواعده للشيخ حفظه هللا)                                       -አሁንም ተጠየቁ፡ “አንድ ግለሰብ ከፊሉ ሙብተዲዕ ፣ ከፊሉ ደግሞ ሙብተዲዕ አይለውም አንዳንድ ተማሪዎች ሙብተዲዕ ያላሉትን ሰዎች ንግግር ይከተላል፡፡ እርሱን ማውገዝ ይበቃልኛል?” መልስ፡ “በርካታ ወጣቶች ሀቅን ከማወቃቸው ጋር ይህ በአሁኑ ሰዓት በአካባቢያችን የሚገኝ ፈተና ነው፡፡ ባረከሏሁ ፊከ በእርግጥ ረዘመች! በእርግጥ ረዘመች! አንድን ሰው ሙብተዲዕ ለማለት ወይም ለመተቸት የዑለሞች ስምምነት መስፈርት አይደለም፡፡ ይልቁንም ለመተቸትም ይሁን ለማወደስ የአንድ ሰው ንግግር በቂ ነው፡፡ ጀማዓዎች ከተቹት ወይም ሙብተዲዕ ካሉት ሀቅን ለሚፈልግ ሰው በቂው ነው፡፡ ዝንባሌውን የሚከተለው ሰው ከሆነ ግን በሸረሪት ድሮች ይንጠለጠላል እንጅ አንድም ነገር አይበቃውም፡፡ ሰዎች ይህን ትችት የሚባለውን ነገር አላወቁትም፡፡ ሰዎች ተጠምደዋል፡፡ ሰዎች ይህ ሰው የተተቸ መሆኑን መተቸት የሚገባው መሆኑንም ተምረዋል ፣ አውቀዋል፡፡ ምክንያቱም ውሸታም በመሆኑ ፣ ዑለሞችን በመዝለፉ ፣ የሰለፎችን መንሐጅና ባለቤቶች በመቃወሙ ፣ የተበላሹ መሰረቶችን በማበጀቱ ፍትሀዊነቱ ውድቅ ተደርጓል፡፡ ይህን ሁሉ አውቀዋል፡፡ ከምክር በኋላ አይዘንም ይላሉ፡፡ መከሩ ፣ አብራሩ ይህ ሰው እምቢ አለ፡፡ እርሱን ሙብተዲዕ ለማለት ተገደዱ! በዚህ አይነት የቀረ በሸረሪት ድሮች የሚንጠለጠል ሰው ምንድን ነው ምክንያቱ? (ወላሂ እከሌ አወድሶታል!) (ወላሂ በሙብተዲዕነቱ ዑለሞች አልተስማሙም!?) ይላሉ! ሙብተዲዕ ያላሉ ሰዎች በሁለት ይከፈላሉ፡ አንደኛው ያልተማሩ ሰዎች ናቸው ፣ እነርሱም ምክንያት ይሰጣቸዋል፡፡ ሁለተኛው የተማሩ ፣ ለውሸት የሚከላከሉ ናቸው፡፡ ከእነርሱ ዘንድ ያለውን ውሸት ምን እንደሆነ ያውቃሉ ፣ እምቢ ብለው ለዚህ ሙብተዲዕ መከላከል እንጅ ሌላ አላማ የላቸውም፡፡ እነዚህ ምንም ዋጋ አይሰጣቸውም፡፡ ዝም ባዮች ዝምታቸው መረጃ አይሆናቸውም፡፡ እነዚያ ከሰውዬው ላይ ያሉ ነገሮችን ሁሉ የተቹ ፣ በሚገባው ያብራሩ መረጃው ከእነርሱ ጋር በመሆኑ ከዚህ በፊት እንደጠቆምኩት ሐቀኛ ለሆነ ሰው ከአላህ -ዓዘ ወጀለ- ዘንድ ምንም አይነት ምክንያት የሌላቸው ለሆኑትና በሸረሪት ድሮች ላይ ለሚንጠለጠሉት ሳይሆን (መረጃው ከእነርሱ ጋር የሆነውን) ሐቅን መያዝ ግዴታ አለበት፡፡ ✍🏼 ፀሀፊ የተከበሩ ሼኽ ሁሴን ሙሀመድ አስልጢ  (ዶ/ር) ✍🏼 ተርጓሚ ኡዝታዝ ዩሱፍ አህመድ

Fozu
1 005
Repost from N/a
🥳 ☪☪☪☪☪️ 🥳 🔡🔡አዲስ ዜና...🔡🔡 ዘገየንባችሁ ይቅርታ🌷 የዘገየነው ምክንያቱስ😇? 1ኛ ለሚወጣ ሰዉ ሽልማቱ ከፍ ብሏል። መቼም የማይለወጥ ለአማኞች መዳኛ ሆኖ በእዝነቱ ነብይ የተላከ
+1
🥳 ☪☪☪☪☪️ 🥳 🔡🔡አዲስ ዜና...🔡🔡 ዘገየንባችሁ ይቅርታ🌷 የዘገየነው ምክንያቱስ😇? 1ኛ ለሚወጣ ሰዉ ሽልማቱ ከፍ ብሏል። መቼም የማይለወጥ ለአማኞች መዳኛ ሆኖ በእዝነቱ ነብይ የተላከን የረበል ዓለሚንን ቃል በሽልማት እናበረክታለን 📖📖 ታድያ ማነዉ ይሄን መዳኛ ተሸላሚ የሚሆነው🎈🎈💌? ቁርኣንን አንብቡ አነሆ ቁርኣን የቂያም ቀን ለሳሒቡ(እሱን ለሚያነበዉ ሰዉ ) አማላጅ ሆኖ ይመጣልና🤲🦋🕊 ተሳተፉ አድድ አድርጉ የጌታቹንም ቃል ተሸለሙ⭐️🏆 2ኛ ለሚወጣ ምርጥዬ የከሰል እጣን ማጬሻ💥🎁 3, የካርድ ሽልማት 100 ወይም ፓኬጅ✨

Fozu
1 005
⚠️ጌታ ተወለደ❌ በዚህ ቆሻሻ ቃል ሰማይ እና ምድር አለመለያየታቸው የላቀውን አምላክ የታጋሽነት ጥግ ትልቅ ማሳያ ነው። እንጂማ 👉 አምላክ በማህፀን ተወልዶ ያድናል ለሰው ልጅ መድህን ቤዛ ሆኖ አልፏል። እያለ እሚዘሙት ሲያሻውም የሚሰክር ቂላቂል የሰው ፍጡር መቼ ይኖር ነበር። أبو نحلا https://t.me/abunehla

Fozu
1 005
‏قال شيخ الإسلام ابن تيمية رحمه الله : وأما صوم رجب بخصوصه، فأحاديثه كلها ضعيفة بل موضوعة، لا يعتمد أهل العلم على شيء منها. 📙الفتاوى 25 / 290
ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያህ ረሒመሁላህ እንዲህ ብለዋል፡- ረጀብን ነጥሎ መፆምን በተመለከተ- ሁሉም ሀዲሶቹ ደካማ እና እንዲያውም የተቀጠፉ ናቸው። የዕውቀት ባለቤቶች የትኛውንም ሀዲስ ለመረጃነት አይመረኮዙባቸውም። 📙ፈትዋ 25/290

Fozu
1 005
⭕️ የተከበሩ ሼኽ ጠያቂ እንዲህ ይላል:- እኔ ልቤ በወንጀል የተሸፈነበት ሰው ነኝ። የወንጀል አዙሪት ውስጥ እስክወድቅ ድረስ። ከልብ ተፀፅቼ ከወንጀል ብቶብትም እዛው ላይ ተመልሼ እምገኝ ሰው ነኝ። በፍላጎቴም ደካማ ሁኛለሁ። ህይወቴም በችግር የተሞላ ሆኗል። አምስት አውቃት ሶላት ያለ ኹሹዕ እሰግዳለሁ። ከዚህ ጨለማ እንድወጣ ምን ይመክሩኛል? 🟢የተከበሩ ሼኽ ኢብኑ ባዝ ረሂመሁሏህ:- አደራህን ተስፋ እንዳትቆርጥ፣ አዘውትረህ ተውበት ልታደርግ ወደ አላህ ልትመለስ ይገባል ። በሀቅ ላይ ልትፀና አላህ የከለከለህን ልትከለከል ይገበሀል። ይህንን አዘውትረህ፣አዘውትረህ፣አዘውትረህ ልትከታታል ይገባል። ወደአላህ የሚመለህ ምንም እንኳ ከአንድ ሺ ጊዜ በላይ ቢሆን አላህ ወደ እሱ የሚመለሱትን ተውበት ይቀበላል። እርግጠኛ ሁን በተውበትህ አብሽር በኸይር። አላህ እንዲህ ይላል:-
قُلْ يَا عِبَادِيَ الَّذِينَ أَسْرَفُوا عَلَىٰ أَنفُسِهِمْ لَا تَقْنَطُوا مِن رَّحْمَةِ اللَّهِ Űš ŘĽŮŮ†Ů‘ŮŽ اللَّهَ يَغْفِرُ الذُّنُوبَ جَمِيعًا Űš ŘĽŮŮ†Ů‘ŮŽŮ‡Ů هُوَ الْغَفُورُ الرَّحِيمُ በላቸው «እናንተ በነፍሶቻችሁ ላይ ድንበር ያለፋችሁ ባሮቼ ሆይ! ከአላህ እዝነት ተስፋ አትቁረጡ፡፡ አላህ ኃጢኣቶችን በመላ ይምራልና፡፡ እነሆ እርሱ መሓሪው አዛኙ ነውና፡፡"
ድምፁን ለማዳመጥ 👇👇👇👇👇👇

Fozu
1 005
⚠️በሐበሻ ምድር ሙመይዓዎች እነማን ናቸው❓ ✅ ክፍል ዘጠኝ (9⃣) “የተተነተነ ትችትን እንዲሁም አንድን ሰው ሙብተዲዕ ለማለት የዑለሞች ስምምነት መስፈርት ነው” በማለት ሙመይዓዎች የሚያሰራጩትን ብዥታ ከንቱ የሚያደርግ የሱና ዑለሞች ንግግር የሚወሳበት ርዕስ 1. ሸይኽ አልዓላማ አልሙሐዲስ ሙሐመድ ናሲሩ ዲን አልአልባኒ I “የተተነተነ ትችት ከውዳሴ እንደሚቀደም” ፣ ይህ ህግና መርሆ ደግሞ ከሙሀዲሶች ዘንድ ስምምነት ያለበት መሆኑን በሚከተሉት በሰነዶች እና በመትኖች ላይ ተኽሪጅ ፣ ተህቂቅ እና ከላም በስፋት ባለባቸው በተለይም በ ሲልሲለቲ ሶሂሃ ፣ አድዶዒፋ ፣ ኢርዋእ ፣ ሶሂህ አቢዳውድ ፣ ዶኢፍ አቢዳውድ ፣ እና ሌሎችም ኪታቦች በቋሚነት ጽፈዋል፡፡ - የተተነተነ ትችትን አለመያዝ የጀርህና ተዕዲል እውቀትን ባዶ ማስቀረት እንደሆነ አልባኒ (አድ' ዶኢፋ 7/293) በተባለው ኪታባቸው ላይ ገልጸዋል፡፡ - “ዋቂዲይ” የተባለውን ግለሰብ በተመለከተ የሚከተለውን ተናግረዋል፡- እርሱን ታማኝ በማለት ባዘነበሉ ሰዎች አትሸወድ፡፡ ምክንያቱም “የተተነተነ ትችት ከውዳሴ ይቀደማል” የሚለውን ሙሐዲሶች የተስማሙበትን ህግና መርሆ ተቃርነውታል፡፡ (ሲልሲለቱል አሃዲሲ አድዶኢፋ ወልመውዱዓ (2/146))፤ ((አልቃኢደቱ አልሙተፈቅ አለይሃ ኢንደ አልሙሀዲሲን)) በሚባሉ ኪታቦች ንግግራቸውን ተመልከት፡፡ አሁንም በተጨማሪ የሚከተለውን ተናግረዋል፡- “ትችት ከውዳሴ እንደሚቀደም በሙስጦለህ (በሐዲስ ዕውቀት) ተረጋግጧል በተለይም ከሰበቡ መብራራት ጋር ተቆራኝቶ ከመጣ፡፡” (ኢርዋእ አልገሊል ፊ ተኽሪጅ አሃዲሲ መናሪ አስሰቢል ፡ (1/209)) አልባኒ የዓብደላህ ብን ዓብዲረህማን አጧኢፊይ ታሪክን አስመልክቶ የኑቃዶችን (የሐዲስ አጣሪዎችን) ንግግር ወስዶ አቅርቧል፡፡ ከዚያም የሚከተለውን ተናግሯል፡- ከፊሎቹ ታማኝ ነው ብለውታል! ነገር ግን እነዚያ መሪዎች ደካማ ብለው የወሰኑትን ውሳኔ በመቃረኑ እነርሱ ታማኝ ማለታቸው ሚዛን የለውም በተለይም የተተነተነ ትችት ከውዳሴ ይቀደማልና፡፡ (ዶዒፍ አቢ ዳውድ አልኡም (2/70)) - አልባኒ ሾለ “ዋቂዲይ” የሚከተለውን ተናግረዋል፡- “ትችት - በተለይም የተተነተነ ከሆነ - ከውዳሴ እንደሚቀደም በሐዲስ እውቀት የተረጋገጠ ጉዳይ ነው፡፡ አንዳንድ ለእርሱ ጎጠኞች የሆኑና ከሀነፍያ የሆኑ ሌሎች ሰዎች ለመጽሐፎቹ ተቅዲም በማድረጋቸውና ታማኝ በማለታቸው አትሸወድ፡፡ ምክንያቱም እርሱ ከሙሐዲሶች ዘንድ በታወቀው -ግልጽ የሆነው ትችት ከውዳሴ ይቀደማል ከሚለው- ህግ ጋር ይጋጫል፡፡” (ሲልሲለቱል አሃዲሲ አድዶዒፋ ወልመውዱዓህ ፡ (1/13)) የዚህ አይነት በእርሳቸው ኪታብ I በጣም በርካታ ነው፡፡ ሁሉም መጽሐፎቻቸው በዚህ ሰለፍይ በሆነ ህግና መርሆ ላይ የተመሰረቱ ናቸው፡፡ ሙመይዓ ካልሆነ በቀር ይህን ህግ የሚተች የለም፡፡ 2. ሸይኽ አልዓላማ አልሙሐዲስ ረቢዕ ብን ሀዲ አልመድኸሊ ሸይኽ ረቢዕ አልመድኸሊ የሚከተለውን ተናግረዋል፡- “በአሁኑ ሰዓት በዚህ ፈተና ውስጥ ከአንዳንድ ሰለፍዮች ዘንድ ሳይቀር አስቸጋሪ የሆነው እነርሱን የሚቃረናቸው አካል ከእርሱ ጋር ማስረጃ ቢኖረው እንኳ “እከሌ ይህን አለ” ፣ “እከሌ ይህን አለ!”.. የሚለው አመለካከት ነው፡፡ ይህ የጥመት ባለቤቶች መንገድ ነው፡፡ የሰለፎች ጎዳና ሰውየው ደረጃው የፈለገው ቢሆን በዚህ አካሄድ አያምንም፡፡” አንድ ሰው መረጃ በሌለው ንግግር ፈትዋ ቢሰጥ ወይም ቢናገር እርሱን እናከብረዋለን ፣ ምክንያት እና የመሳሰሉ ነገሮችን እንሰጠዋለን እንጅ ንግግሩ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ ነገር ግን ማንኛውም ከረሡል صلى الله عليه وسلم ውጭ ያለ ሰው ንግግሩ ተቀባይነት ሊያገኝ ወይም ሊመለስበት ይችላል፡፡ ከእርሱ ጋር ከአላህ ወይም ከረሡል صلى الله عليه وسلم ማስረጃ ያለውን ሰው ንግግሩ ሊመለስበት አይገባም …” (መጅሙዕ ኢራኢቅ ፡ ገጽ 397) - ሸይኽ ረቢዕ -ሀፊዞሁሏህ- “የቢድዓ ባለቤቶችን ለመተቸት በዘመኑ ያሉ ሰዎች መስማማት መስፈርት ነው? ወይስ አንድ ዓሊም ብቻ ይበቃል?” የሚል ጥያቄ ተጠየቁ፡፡ መልስ፡-“ይህ ቆሻሻ የሆነው ሙመይዕ ህግና መርሆ ነው - ባረከሏሁ ፊኩም - በየትኛው ዘመን ነው ለዚህ ጉዳይ የዑለሞች ስምምነት መስፈርት የተደረገው? ለዚህ መስፈርት ምንድን ነው መረጃው? በአላህ ኪታብ ውስጥ የሌለ መቶ መስፈርት እንኳ ቢሆን መስፈርቱ ብልሹ ነው፡፡ ኢማም አህመድ ብን ሐንበል I ወይም የህያ ብን መዒን I ሙብተዲዕን ቢተቹ “በዓለም ያለ የሱና መሪ ሁሉ ሙብተዲዕ መሆኑን ሊስማሙበት ግድ ነው እላለሁ!!! ኢማም አህመድ ይህ ሰው ሙብተዲዕ ነው ካሉ ሁሉ ነገር አበቃ ፣ ኢማም አህመድ ይህ ሰው ሙብተዲእዕ ነው ካሉ ሁሉም ሰው ለእርሱ ያስረክባል ፣ ከጀርባው ይጓዛል፡፡ ኢብን መዒን I፡ ይህ ሙብተዲዕ ነው ካለ አንድም ሰው የሚጨቃጨቀው የለም፡፡ ሁሉ መስማማት አለበት የሚለው መስፈርት በማንኛውም ሸሪዓዊ አህካም ሊሆን የማይችል እብለት ነው፡፡ ✍🏼 ፀሀፊ የተከበሩ ሼኽ ሁሴን ሙሀመድ አስልጢ  (ዶ/ር) ✍🏼 ተርጓሚ ኡዝታዝ ዩሱፍ አህመድ

Fozu
1 005
⭕️ ትውልድን እያደናቀፉ የምን ማሻገር ነው? " እናሻግራችሁ ሲሉ አንፈልግም እኛው እራሳችን እንሻገራለን ማለት አይከፋም"
⭕️ ትውልድን እያደናቀፉ የምን ማሻገር ነው? " እናሻግራችሁ ሲሉ አንፈልግም እኛው እራሳችን እንሻገራለን ማለት አይከፋም"

Fozu
1 005
⚠️በሐበሻ ምድር ሙመይዓዎች እነማን ናቸው❓ ✅ ክፍል ስምንት (8⃣) “ያፈነገጠ አላህ እሳት ውስጥ ይከተዋል ፣ ማፈንገጥ ማለት ሐቅን የተቃረነ መሆኑን ተቃራኒዎች አላወቁም፡፡ አንዱ ብቻ ቀርቶ ሁሉም በእርሱ ላይ ቢሆን እነርሱ አፈንጋጭ ናቸው፡፡” በኢማም አህመድ I ዘመን ትንሽ ሰዎች ሲቀሩ ሁሉም አፈንግጦ ነበር፡፡ እነርሱም ጀማዓዎች ሆኑ፡፡ ኢማም አህመድ ብቻውን ነበር ጀማዓ የነበረው፡፡ ያንጊዜ የነበሩ ቃዲዎች ፣ ሙፍቲዎች ፣ መሪዎችና ተከታዮቻቸው አፈንጋጮች ናቸው፡፡ ሰዎች ይህ ነገር ለአቅላቸው ሲከብዳቸው የሚከተለውን ለመሪው ነገሩት፡ “የሙእሚኖች መሪ ሆይ! ቃዲዎችህ ፣ ሀላፊነት የሰጣሀቸው ባለስልጣኖችህ ፣ ፉቀሃዎችህ ፣ ሙፍቲዎችህ ሁሉም በአጠቃላይ ትክክለኛ ሳይሆኑ አህመድ ብቻውን በሀቅ ላይ ይሆናል?” ለዚህ ነገር እውቀቱ አልሰፋውም፡፡ ከረጅም እስር በኋላ በአለንጋና በቅጣት መቅጣት ጀመረ፡፡ ላኢላሃ ኢልለሏህ ሌሊቱን ከትናት ምሽት ጋር ምን አመሳሰለው!! አህለሱና ወልጀማዓዎች ጌታቸውን እስኪገናኙ ድረስ ቀደምቶቻቸው ባለፉበት ለመጓዝ አስፈሪ መንገድ ነው፡፡ የእነርሱ ምትኮችም ይጠባበቋታል፡፡ مِنَ Ř§Ů„Ů’Ů…ŮŘ¤Ů’Ů…ŮŮ†ŮŮŠŮ†ŮŽ ŘąŮŘŹŮŽŘ§Ů„ŮŒ ŘľŮŽŘŻŮŽŮ‚ŮŮˆŘ§ Ů…َا ŘšŮŽŘ§Ů‡ŮŽŘŻŮŮˆŘ§ Ř§Ů„لَّهَ ŘšŮŽŮ„َيْهِ ۖ فَمِنْهُمْ مَنْ Ů‚َ؜َىٰ Ů†ŮŽŘ­Ů’Ř¨ŮŽŮ‡Ů ŮˆŮŽŮ…ŮŮ†Ů’Ů‡ŮŮ…Ů’ مَنْ ŮŠŮŽŮ†Ů’تٮظِرُ Ű– وَمَا Ř¨ŮŽŘŻŮ‘ŮŽŮ„ŮŮˆŘ§ ŘŞŮŽŘ¨Ů’دِيلًا ď´żŮ˘ŮŁď´ž ከአማኞቹ በእርሱ ላይ ለአላህ ቃል ኪዳን የገቡበትን በእውነት የፈጸሙ ወንዶች አልሉ፡፡ ከነርሱም ስለቱን የፈጸመ (ለሐይማኖቱ የተገደለ) አልለ ፤ ከነርሱም ገና የሚጠባበቅ አልለ፡፡(የገቡበትንም ቃል) መለወጥንም አልለወጡም፡፡ ”  ( አል አህዛብ፡ 23) ወላሃውለ ወላቁወተን ኢልላ ቢላሂ አልዓልይል ዓዚም ( ኢዕላም አልሙቂዒን ዓን ረቢል ዓለሚን ፡ 3/309-310) እኔም አልኩ፡ ይህን ጉዳይ  ማለትም “አንድን ሰው ሙብተዲዕ ለማለት የዑለሞች ስምምነት መስፈርት ነው” የሚለው አመለካከት አዲስ ፈሊጥ መሆኑን ወደቀደምቶችም ይሁን ቀጥለው ወደመጡ አህለሱና ዑለሞች ንግግር በመመለስ የተገነዘበ ሰው ፣ ሙመይዓንና በጥቅልም ይሁን በዝርዝር እነርሱ የሚጓዙበትን ቆሻሻ መንሐጅ (ጎዳናቸውን) በአላህ ፈቃድ ይገነዘባል፡፡ - በመቀጠል የሱና ዑለሞችን ንግግር አቀርባለሁ፡፡ በተጨማሪ ሙመይዓዎች ለፈጠሩት “አንድን ሰው ሙብተዲዕ ለማለት የዑለሞች ስምምነት መስፈርት ነው” ለሚለው አዲስ መርሆ የሱና ዑለሞች የሰጡትን መልስና የበፊቶችም ይሁኑ የኋለኞቹ አዲስ ሙሙዓዎች የሱና ዑለሞችን መቃረናቸውን ግልጽ አደርጋለሁ፡፡ የሐዲስ እውቀት ሙጀዲድ የሆኑት ሸይኽ አልአላማ አልሙሐዲስ ሙሐመድ ናሲሩ ዲን አልአልባኒ ፣ በትክክል የጀርህና ተዕዲል ሰንደቅ አላማ ተሸካሚ የሆኑት ሸይኽ አልአላማ ረቢዕ አልመድኸሊ ፣ የየመን አገር ሙሐዲስ የሆኑት ሸይኽ ሙቅቢል አልዋዲዒ ፣ የደቡብ ግዛት ሙሐዲስና ሙፍቲ የሆኑት ሸይኽ አህመድ ብን የህያ አንነጅሚ ፣ የኢትዮጵያ ሙፍቲ የሆኑት ሙሐመድ ሸይኽ ሙሐመድ ብን ዓሊ አደም አልኢትዮጵይ ፣ ሸይኽ አልዓላማ ዑበይድ አልጃቢሪ ፣ አሸይኽ አልዓላማ ሷሊህ አልፈውዛን እና ሸይኸ አልዓላማ ሙሐመድ ብነ ሀዲ አልመድኸሊ “ተንትኖ የተቸ አወዳሽ ከሆነው ሰው መቀደሙ ግዴታ እንደሆነ” ሁሉም ተስማምተዋል፡፡ “በትችት እና በተብዲዕ ላይ የዑለሞች ስምምነት መስፈርት ነው” ማለት በቀደምት ሰለፎች መንሐጅ መሰረት የለውም፡፡ ይልቁንም ፣ ወደ ማስረጃ ፊታቸውን የማያዞሩ ፣ አንድን ሰው ሙብተዲዕ ለማለት የዑለሞች ስምምነት መስፈርት ነው በሚሉ አልዓላማ ተቃራኒ በሀዲስ ዝግጅት ፣ በጀርህ በተዕዲል ሙያ ፣ በአጠቃላይ በሐዲስ ሙያ የሙእሚኖች መሪ የሆኑት ሙሐመድ ኢብን ኢስማዒል አልቡኻሪ “በተረጋገጠ ማስረጃ ካልሆነ በቀር የአውሪታው ፍትሀዊነት ውድቅ አይደረግም” በሚለው አመለካከት የሐዲስ ባለቤቶች ስምምነት እንዳላቸው መንቀሉ ተዘግቧል፡፡ ቡኻሪ Iየሚከተለውን ተናግሯል፡- “ኢብራሒም በሸዕብይ ዙሪያ ፣ ሸዕብይ ደግሞ በኢክሪማ ፣ ከእነርሱ በፊት ባሉትም ዙሪያ ተነገረ ተብሎ በሚወራው የአንዳንድ ሰዎች ወሬ እንዲሁም የሰዎችን “ዒርድ” እና “ነፍስ” በሚመለከት የአንዳንድ ሰዎችን ተእዊል (ትንታኔ) በተመለከተ በርካታው ሰው ነጃ (ነጻ) አይወጣም፡፡ በእንደዚህ አይነቱ ነገር የእውቀት ባለቤቶች ፊታቸውን አላዞሩም፡፡ በማስረጃና በማብራሪያ ካልሆነ በቀር ፍትሀዊነታቸው ውድቅ አልተደረገም፡፡ በዚህ ዙሪያ የመጣው ንግግር ብዙ ነው፡፡” (አልቂርአቱ ኸልፈል ኢማም ሊል ቡኻሪ ፡ ገጽ 39) - ከሙመይዑ ኸድር ከሚሴ ዘንድ ፡ መሰረቱ ሱና ለሆነ ሰው “የፈለጋችሁትን ሾሊ በእርግጥ ለእናንተ ምሬያለሁ” እንደተባለው አምሳያ ፣ መሰረቱ ሱና የሆነ ሰው በተረጋገጠ ማስረጃ ቢሆን እንኳ ከሱናነቱ ንቅንቅ አይልም ፣ እንዴውም (እነርሱን ነጻ የሚያደርጉ) ምክንያቶችን ቆጥረን ልንደረድር ይገባል፡፡ ለእርሱ ስንል መወዛገብ የለብንም!! የሚል አቋም ነው፡፡ ከማህይምነትና ዝንባሌን ከመከተል በአላህ እንጠበቃለን፡፡ መሰረቱ ሱና ሆኖ ግልጽ ከሆነ ቢድዓ ላይ የወደቀ ሰው ምንድን ነው ብይኑ? ለምሳሌ ቁርኣን ፍጡር ነው ያለ ሰው ፣ ሶሃባን የተቸ ሰው ፣ ለቢድዓ ሰዎች ጥብቅና የቆመ? ከማስረጃ እና ብዥታን ከማስወገድ ውጭ ሌላ ምክንያት ሰለፎች እንደዚህ ነበሩ? ቁርኣን ፍጡር ነው ብሎ የሚል አስገዳጅ በመጣበት የፊትና ዘመን የሱናን ሰንደቅ አላማ ተሸካሚ የነበረው ኢማም አህመድ መሰረቱ ሱና የሆነ መሰረቱ ሱና ያልሆነ እያለ ይከፋፍል ነበር? ኢማም አህመድ በቁርኣን ዙሪያ (አቋም ግልጽ ባለማድረግ) የቆመውን የዕቁብ ብን ሸይባንን ወደመሰረቱ (ሱንይነቱ) ፊቱን ሳያዞር “የዝንባሌ ባለቤት ፣ ሙተበዲዕ” በማለት ነበር የተናገረው፡፡ - ኢብን አልጀውዝይ I የሚከተለውን ተናግሯል፡- ኢማም አቡዓብዲላህ አህመድ ብን ሀንበል ሱናን በመያዝና ቢድዓን በመከልከል ብርቱ ከመሆኑ የተነሳ ከምርጥ ጀማዓዎች ዘንድ አንዳንድ ሱናን የሚቃረን ነገር ሲከሰት ይናገር ነበር፡፡ ንግግሩ ለዲን ባለው ተቆርቃሪነትና ምክር ተደርጎ ይወሰድ ነበር፡፡ መናቂብ አልኢማም አህመድ ፡ ገጽ ፡235) ✍🏼 ፀሀፊ የተከበሩ ሼኽ ሁሴን ሙሀመድ አስልጢ  (ዶ/ር) ✍🏼 ተርጓሚ ኡዝታዝ ዩሱፍ አህመድ

Fozu
1 005
⚠️በሐበሻ ምድር ሙመይዓዎች እነማን ናቸው❓ ✅ ክፍል ሰባት (7⃣) ኡስታዝ ዶክተር አህመድ ባዝሙል የሚከተለውን ተናግረዋል፡- “ሀለብይ ከሚያጸድቃቸው ውድቅ ከሆኑ ህግና መርሆዎች መካከል “የተተነተነ ትችትን መመለሾ ፣ ለትችት የኡለሞች ስምምነትን መስፈር ማድረግ” ናቸው፡፡ የሰለፎች መንሐጅ የሆነውን የተተነተነን ትችት (ከውዳሴ ማስቀደም) ፣ የቢድዓና የዝንባሌ ባለቤቶችን ማኩረፍ የሚያፈርስ እና ዲናቸውን በእነርሱ ላይ ለማምታታት ሰለፍዮች ሶፍ ውስጥ ቢድዓን እና ሙብተዲዖችን የሚያስገባ በር ለመክፈት አደገኛ ህግ መሆኑ የሚያጠራጥር አይደለም፡፡” (ሲያነቱ ሰለፍይ ሚን ወስወሰቲ ወተልቢሳቲ ዓልይ አልሀለብይ ፡ ገጽ 92 ዶክተር አህመድ ባዝሙል) ዶክተር ዓብዱል ሀሚድ አልሀዷቢ የሚከተለውን ተናግረዋል፡- “ይህ- ሙብተዲዕ ለማለት የዑለሞች ስምምነትን መስፈርት ማድረግ - ቀጥተኛ የሆነውን የዲን መሰረት እርሱም ወላእና በራእን (ለአላህ ብሎ መውደድና መጥላት) የሚያፈርስ ፍጻሜዋ በተለያየንበት አንዱ ለአንዱ ምክንያት ይስጥ - ወደሚለው የኢኽዋን መርሆ የሚመለስ- የአህለል አህዋ እና አህለል ቢድዓን ጎዳና ከጋለቡ የተምይዕ የግርግር ባለቤቶች ካልሆነ በቀር የእውቀት ባለቤቶች የማያውቁት የሚያስጠላና ውድቅ የሆነ ህግ ነው፡፡ ይህ “ከሌላው ጋር ያለው ውዝግባችን በመካከላችን ላለው ውዝግብ ምክንያት አይሁን” ከሚለው የሐለብይ ህግ ጋር ይመሳሰላል፡፡” ሐጅ አትተምይዕ አልኸለፍይ ፡ ገጽ 31-33) አብዱል ሀሚድ አልሀዷቢ ተቅዲም ኡስታዝ ዶክተር አህመድ ብን ዑመረ ባዝሙል እኔም አልኩ፡ ይህ ነው የቀድሞዎችም ይሁን አዲሶቹ ሙመይዓዎች በተለየ ሁኔታ ዘወትር የሚወተውቱት፡፡ በተብዲዕና በትችት እንዲሁም በተተነተነ ትችት ዙሪያ የማስረጃን አንገብጋቢነት በሙሓዶራቸው ሰምታችኋልን???? ተከልከል!(ነገሩ እንደዚያ አይደለም) ለማንኛውም ውዝግብ እና ልዩነት ከዲን ፣ ከዓቅል እና ከሙሩአ ትንሽ እንኳ ግንዛቤ ላለው ሰው ማስረጃው ዳኛ ከመሆኑ ጋር እነዚህ ሶስት ሙመይዖች እና በእነርሱ ምህዋር የሚሽከረከሩት አቋም ከመቀየራቸው በፊት “ጀማዓ ማለት ብቻህን እንኳ ብትሆን ሀቅን የገጠመ ነው” የሚለውን የብን መስዑድን  ንግግር ያውቁ ነበር፡፡ “ማስረጃን ያወቀ ካላወቀው ይቀደማል” ፣ “ካራቋች አጽዳቂ ይቀደማል” ፣ “ማስረጃን የሀፈዘ ካላሀፈዘው ይቀደማል” የሚሉ ህጎችንም ያውቁ ነበር፡፡ ኢማም ብን አልቀይም I የሚከተለውን ተናግረዋል፡- ኑዓይም ብን ሀማድ የሚከተለውን ተናግሯል፡- “ጀማዓ ሲበላሽ ብቻህን እንኳ ብትሆን ጀማዓው ከመበላሸቱ በፊት በነበረው ሁኔታ ላይ መሆን አለብህ፡፡ ያን ጊዜ አንተ ጀማዓ ነህ” በይሐቅይና ሌሎችም አውስተዋል ከሐዲስ መሪዎች አንዱ የሚከተለውን ተናግሯል -ለእርሱ “ሰዋዱል አዕዞም” (ነጃ የምትወጣዋ ጀማዓ) ተወሳለት- የሚከተለውንም ተናገረ፡- “ሰዋዱል አዕዞም ምን እንደሆነ ታውቃለህ? እርሱ ሙሐመድ ብን አስለም አጡሲዩ እና ባልደረቦቹ ናቸው፡፡” “ሰዋዱል አዕዞም” እና ማስረጃ ተደርገው ሲቆጠሩ የነበሩ (የሐቅ) ተቃራኒዎች ሁሉ ተሰረዙ፡፡ ጀማዓዎች ጁምሁሮች (አብዛኞቹ ዑለሞች) ሆኑ ፣ እነርሱን ለሱና መመዘኛ አደረጓቸው፡፡ (የሐቅ) ባለቤቶች በማነሳቸውና በየዘመኑ ፣ በየከተሞች ብቸኛ በመሆናቸው ምክንያት (ሰዎች) ሱናውን ቢድዓ ፣ መልካሙን መጥፎ አደረጉ፡፡ ✍🏼 ፀሀፊ የተከበሩ ሼኽ ሁሴን ሙሀመድ አስልጢ  (ዶ/ር) ት ✍🏼 ተርጓሚ ኡዝታዝ ዩሱፍ አህመድ

Fozu
1 005
ድብቁ የሙስሊም እህቶቻችን የእርቃን ፎቶ ንግድ! ሰሞኑን ከአንድ የስራ ባልደረባዬ ጋር ስናወራ ዲጂታል መፅሄት ላይ የሠፈረ አንድ ጥናታዊ ፅሁፍ ላከልኝ። ጸሀፊው ምንተስኖት ደስታ ይባላል በሥነ-ሕብረተሰብ (ሶሲዮሎጂ) ከሐረማያ ዩንቨርስቲ የተመረቀ ሲሆን በአሁን ሰዓት በስንቅ ዩዝ ኢኒሼቲቭ ፕሮጀክት ማናጀር ነው ጥናታዊ ፅሁፉም ቴሌግራም ላይ ቻናል ግሩፕ ከፍተው የታዋቂ ሴቶችን ወይንም የድሮ የዝሙት ጓደኞቻቸውን እርቃን ፎቶ እየለቀቁ ብር ስለሚያስከፍሉ የቻናብ ባለቤቶች ያትታል። ለአንድ እርቃን ፎቶ ከ 3000- 6000 እንደሚያስከፍሉም በጥናታዊ ፅሁፉ ሰፍሯል። እኔን ቀልቤን የሳበኝ እና ከባልደረባዬ የሰማሁት የሙስልም እህቶቻችን ከዚህም በላይ ከፍ ያለ ዋጋ እንዳለው ነው። በእርግጥ ለማመን ቢከብደኝም በገበያው ብዙም ስለማይገኝ ይሁን ለሙስሊም እህቶች ያላቸው መጥፎ እሳቤ በውድ ዋጋ እንደሚቸበቸብ ለዚህ ዋነኛ ተጠቂዎች የአረብ ሀገር እህቶች እና የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች እንደሆኑ ነው የሰማሁት። በእርግጥ ግቢ ውስጥ በነበርንበት ሰአቶችም ይሁን ከግቢ ከወጣን በኋላ አንዳንድ ሽምግልናዎችን ታዝበናል። ከዛም አልፎ ህግ ደረጃ የደረሱም ነበሩ። ሽያጭ ደረጃ ይደርሳል የሚል ምንም አይነት ግምት አልነበረኝም። በእርግጥ በሰላም ጊዜ ፍቅር ውስጥ በነበሩበት ጊዜ የሚላላኩዋቸው ልቅ ምስሎች ናቸው በኋላ በጠብ ጊዜ ህይወታቸውን የሚያመሰቃቅሉት። ከሁሉም የከፋው ደግሞ. . . 🔴 እህቶቻችን በማያውቁት መንገድ አብረው ከሚኖሯቸው ሙስሊም ካልሆኑ እህቶች ወይንም ዲናቸውን ጠንቅቀው በማያውቁ ሙስሊም እህቶች ተቀርፀው የሚላኩ ምስሎች ናቸው። በተለይ ሙተነቂብ ሲሆኑ ደግሞ በካሜራ ያድኗቸዋል አሳልፈው ለባዕድ ወንድ ይሰጧቸዋል። 🟢 ይሁን እና ብዙ ኡዝታዞች እና መሻይኾች ይህንን ጉዳይ ዘርዘር አድርገው ህዝበ ሙስሊሙን ቢያነቁበት ባይ ነኝ። መፅሄቱን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ 👇👇👇👇👇 https://concepthub.net/article/4

Fozu
1 005
🔷 ለጥንቃቄ በቴሌግራም መረጃዎች እየተመዘበሩ እንደሆነ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር / ኢንሳ አሳውቋል። ኢንሳ በዛሬው ዕለት በቴሌግራም መረጃዎች እየተመዘበሩ በመሆኑ ተጠቃሚዎች ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ሲል አሳስቧል። ኢንሳ ብዙ የቴሌግራም አካውንቶች በተለያዩ ማስገሪያ (ፊሺንግ ሊንክ) አማካኝነት መረጃዎች እየተመዘበሩ እንደሆነ ገልጷል። በመሆኑንም ከማንኛውም የቴሌግራም ተጠቃሚ (ከሚያውቁትም ሆነ ከማያውቁት) ግለሰብ ሊንክ ቢላክ መክፈት ተገቢ እንዳልሆነ እና ወዲያውኑ ማጥፋት እንደሚገባ አሳስቧል። መረጃው የቲክቫህ ኢትዮዽያ ነው ። https://t.me/bahruteka

Fozu
1 005
🟢አላህ ይጠብቀን ‏قال الإمام ابن كثير رحمه الله: والذنوب والمعاصي والشهوات ، تخذل صاحبها عند الموت مع خذلان الشيطان له“. 📙البداية والنهاية(9/179)

Fozu
1 005
✅ ስለ ሙመይዓ ✅ ሙብተዲዕን አትናገሩብን። ✅ ለሙብተዲዕ ለስላሳ ለ ሰለፍዮች እሾህ ስለሚሆኑ ሰዎች። ✅ ስለ አልይ ሀለቢ ቃኢዳ። ✅ ሰለፍዮችን ሀዳድይ ስለሚሉ ሰዎች። ✅ ጤፍ እሚቆላ ምላስ ስላለው ሰው። ሼኽ አቡዘር 📜. https://t.me/abunehla

Fozu
1 005
⚠️በሐበሻ ምድር ሙመይዓዎች እነማን ናቸው❓ ✅ ክፍል ስድስት (6⃣) ሸይኹ I የሚከተለውን ተናግረዋል፡- “ይህ የሙሐዲሶች የጥናት ጭብጥ አይደለም ፣ እንዴውም እርሱ ደካማ መሆኑን የሚገልጸውን ንግግር ማውሳቱ ግዴታ ነው፡፡ ከዚያም ጀርህን ወይም ተዕዲልን በማስቀደም ዙሪያ ሙሐዲሶች በተናገሩት ንግግር መስራት ግዴታ ነው፡፡ ትክክለኛ አስተውሎት ይኑርህ ፤ የጭፍን ተከታይነት ምርኮኛ አትሁን፡፡ እርሱ የደደቦች ማስረጃ ፣ የአመጸኞች ምርኩዝ ነው፡፡” (በህሩል ሙሒጥ አስሰጃጅ ፊ ሸርህ ሶሂህ አልኢማም ሙስሊም ብን አልሀጃጅ ፡16/677) ሙሐመድ ሰዒድና ኸድር የተናጋሪውን ንግግር ያውቁ ነበር ፤ መሰረታዊም ይሁን ቅርንጫፋዊ በሆኑ ጉዳዮች ተግባራዊ ያደርጉትም ነበር፡፡ እርሱም የሚከተለው ንግግር ነው፡-   وليس كل خلاف ؏اإ معتبرا إلا خلافاله حظ من النظر                      ልዩነቱ ሁሉ አይሰጠው ግምት        ድርሻ ያለው ሲቀር ፣ ልዩ የሆነ ጥናት - ኢማም አልባኒ I የተተነተነ ትችትን ከውዳሴ ማስቀደምን ለሚቃወሙ ሰዎች የሚከተለውን ተናግረዋል፡- “የዚህን ትልቅ እውቀት ህግና መርሆ  ማለትም ከዑለሞች ዘንድ በታወቀው መስፈርት ትችትን ከውዳሴ ማስቀደም የሚለውን መርሆ - በመተውና ጠማማ የሆነ አካሄድ በመከተል የዝንባሌ ባለቤቶች የፈለጉትን ሀዲስ ትክክለኛ የፈለጉትን ደግሞ ደካማ ማድረግ ይችላሉ፡፡” አድዶዒፋ : 9/125-130) - ሙመይዓው ኸድር ከሚሴ ፣ ሙሐመድ ብን ሰዒድ እና ሌሎችም- “የተተነተነ ትችት ከውዳሴ ማስቀደም” ኡለሞች የተወዛገቡበትና በእርሱም ላይ ተንተርሰን ውዴታና ጥላቻ የምንመሰርትበት አይደለም!!!” የሚል አመለካከት ስላላቸው ይህ አካሄድ ከእነርሱ ዘንድ የተጣመመ ፣ እንዲሁም ለቢድዓ ፣ ለሽርክ እና ለጥመት ባለቤቶች በር የሚከፍት አይደለም፡፡ ከብዥታ ነጻ ካለመሆን በአላህ እንጠበቃለን፡፡ ይህ መዋዥቅ ከሀዲስ፣ ከሱና ባለቤቶችና ቀደምት ደጋግ ባሮች ከነበሩበት ጎዳና የማፈንገጥ ዋጋ ነው፡፡ ✍🏼 ፀሀፊ የተከበሩ ሼኽ ሁሴን ሙሀመድ አስልጢ  (ዶ/ር) ✍🏼 ተርጓሚ ኡዝታዝ ዩሱፍ አህመድ

Fozu
1 005
🟢 በእናንተ ሙገታ ከሄድንማ ኢኽዋንም የዳቦ ስም ነው ኧረ ሱፍያውም ያው ነው የአህባሹም እዛው ነው እንደው ምን አለፋህ ድፍን ሀበሻዊ ሱንይ ሰለፍይ ነው። የሆነ ነገራቸው የሚመሳሰልብኝ እኔን ብቻ
🟢 በእናንተ ሙገታ ከሄድንማ ኢኽዋንም የዳቦ ስም ነው ኧረ ሱፍያውም ያው ነው የአህባሹም እዛው ነው እንደው ምን አለፋህ ድፍን ሀበሻዊ ሱንይ ሰለፍይ ነው።
የሆነ ነገራቸው የሚመሳሰልብኝ እኔን ብቻ ነው?
https://t.me/abunehla

Fozu
1 005
‏قال شيخ الإسلام ابن تيمية رحمه الله: تظهر الشياطين، في المواضع التي يختفي فيها، أثر التوحيد . 📙 كتاب النبوات 1019/2

Fozu
1 005
⚠️በሐበሻ ምድር ሙመይዓዎች እነማን ናቸው❓ ✅ ክፍል አምስት  (5⃣) ሙብተዲዕ ለማለት የዑለሞች ስምምነት መስፈርት ነው” የሚለው የሙሐመድ ብን ሰዒድ የንግግሩ ጭብጥ ሐሳብ ነው፡፡ - በሐበሻ ምድር የሙመይዓ ሰንደቅ አላማ ተሸካሚ የሆነው ኸድር ከሚሴ የሚከተለውን አመለካከት አረጋግጧል ፡ - “ከጀርህና ተዕዲል መካከል ኢጅቲሐድይ የሆነ አለ፡፡ ከእርሱ መካከል ኢጅቲሐድይ ያልሆነም አለ፡፡” በዚህ አነጋገሩ እርስ በርሱ የሚጋጭና ልክ እንደተለመደው የቢድዓ ባለቤቶች ባህሪ አስገራሚ መዋዥቅ አለው፡፡ የንግግሩ ጭብጥ ሐሳብ፡ ዑለሞች በተተቸና በተወደሰ ግለሰብ ላይ የተወዛገቡ ጊዜ ጉዳዩ ኢጅቲሐዲይ ይሆናል ፤ በመሆኑም በእርሱ ዙሪያ ማስገደድ የለም፡፡ ለዚህም ምሳሌ የጠቀሰው የሻፍዕይ ሸይኽ የሆነውን ኢብራሒም ብን አቢ የህያ ነው፡፡ ሻፍዕይ ታማኝነቱን ሲገልጹ የጀርህና የተዕዲል ዑለሞች ደግሞ ፈተና የተባለ ሁሉ ከእርሱ ላይ ተሰብስቧል በማለት ትችት አቀረቡ፡፡ ትችቱን እንዲቀበሉ ሻፍዕይን አላስገደዱም፡፡ ኸድር ከሚሴ የሚከተለውን ተናገረ፡ “የተተነተነ ትችት ከውዳሴ መቀደሙ ዑለሞች የተወዛገቡበት ነው በመሆኑም በእርሱ ላይ ውዴታና ጥላቻ የሚመሰረትበት ጉዳይ አይደለም፡፡” ከኸድር ከሚሴ ዘንድ ያለው ጭብጥ ሐሳብ፡ “አንድን ሰው ሙብተዲዕ ለማለት የዑለሞች ስምምነት የግድ ነው፡፡ የተተነተነ ትችት ከውዳሴ መቀደሙ ከዑለሞች ዘንድ ውዝግብ ያለበት ጉዳይ በመሆኑ ሰዎችን በእርሱ ላይ አታስገድዱ !!!” የሚለው ነው፡፡ ሙሐመድ ሰዒድ እና ኸድር ከሚሴ፡ ሸይኽ ሙሐመድ ብን አደም አልኢትዮጵይ በጀርህና ተዕዲል ተቃርኖ ዙሪያ ዑለሞች የተናገሯቸውን ንግግሮች እንዳወሱ ጠቅሰዋል፡፡ “ይህ ፣ የተተነተነ ትችት ከውዳሴ መቀደሙ ውዝግብ ያለበት መሆኑ ማስረጃ ነው፡፡” በማለት ሁለቱ ሙመይዖች ተናገሩ፡፡ እኔም አልኩ፡ ሁለቱ በጀርህና በተዕዲል እንዲሁም በዲኑ ጥልቅ አዋቂ ከሆኑት ዓሊሞች ዘንድ ባለው ህግና መርሆ የእውቀት ችግር እንዳለባቸው ይጠቁማል፡፡ በዚሁ ኪታብ ሸይኽ ሙሐመድ I ራሳቸው የሚከተለውን ተናግረዋል፡-“ጀርህና ተዕዲል በተቃረነ ጊዜ ዋጋ ሊሰጠው የሚገባው መሰረት 'የተተነተነ ትችት ከውዳሴ መቀደሙ' ነው፡፡” (ኢዷህ አስሰቢል ፡ ገጽ 41) “ዋጋ ሊሰጠው የሚገባው መሰረት” የሚለውን ንግግራቸውን አስተውል፡፡ ይህ ማለት ከእርሱ ውጭ ያለው ዋጋ የሚሰጠው አይደለም ማለት ነው፡፡ ከሙመይዓ ዘንድ እንዲህ አይነቱ ጭብጥ ሐሳብ ፊት የሚሰጠው አይደለም፡፡ ከእነርሱ ዘንድ አንገብጋቢው ጉዳይ ልዩነት ከተከሰተ እርሱን ማጽደቅ ብቻ ነው!!! ተናጋሪው ማን እንደሆነ በማይታወቀው ዑለሞች በሚገልጹት (ቂለ) ወይም “ተባለ” የሚል ቃል ላይ ይደገፋሉ? የተተነተነን ትችት ከውዳሴ ማስቀደም ግዴታ መሆኑን ከሚገልጹ የሀዲስ ባለቤቶች በዋናነት ከቡኻሪና ሙስሊም መንሐጅ (ጎዳና) አፈነገጡ፡፡ ሸይኽ ሙሐመድ ብን ዓልይ አደም የተተነተነን ትችት ከውዳሴ ይቀደማል ከሚለው የሀዲስ ባለቤቶች ጎዳና ያፈነገጠውን ይቃወማሉ፡፡ ✍🏼 ፀሀፊ የተከበሩ ሼኽ ሁሴን ሙሀመድ አስልጢ  (ዶ/ር) ✍🏼 ተርጓሚ ኡዝታዝ ዩሱፍ አህመድ