en
Feedback
864
Subscribers
No data24 hours
+37 days
+530 days
Posts Archive
“የአገልግሎት አሰጣጥን በማሻሻል ብልሹ አሰራርን እንከላከል” ******************** ፌታይኮ የፍትህ ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮችና ሰራተኞች “የአገልግሎት አሰጣጥን በማሻሻል ብልሹ አሰራርን እንከላከል” በሚል መሪ ቃል የጋራ ንቅናቄ የውይይት መድረክ ተካሄደ፡፡ የውይይት መድረኩን በንግግር የከፈቱት በፍትህ ሚኒስቴር ተቋማዊ ሪፎርምና አቅም ግንባታ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ኤርሚያስ የማነብርሃን ዶ/ር፤ የመልካም አስተዳደርና የብልሹ አሰራር ችግሮችን ለማስወገድ መንግስት በሀገር አቀፍ ደረጃ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ባለበት ወቅት የፍትህ ዘርፉ አስፈጻሚ አካል እንደመሆኑ ከዚህ ተግባር ራስን በማራቅ ለዜጎች ፍትሃዊ አገልግሎት መስጠት ይገባል ብለዋል፡፡ አያይዘውም በፍትህ ዘርፉ ግልፀኝነትን፣ አካታችነትን፣ ተጠያቂነትንና ውጤታማነትን መርህ አድርጎ መስራት ይገባል ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው ያሉብንን የጥራት፣ ቅልጥፍና እና ብልሹ አሰራሮች ልንቀርፍ ይገባል ብለዋል፡፡ በፍትህ ዘርፍ አገልግሎት አሰጣጥና አሰራር ላይ የሚስተዋሉ ችግሮች ላይ የተዘጋጀውን የዳሰሳ ጥናት ያቀረቡት በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የስነ- ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ክፍል ሃላፊ ወ/ሮ ትዕግስት አቡዬ፤ ጠበቆች ያልተገባ ጥቅም መፈለግ፣ ፋይል እንዲጠፋ ማድረግ፣ ሰራተኞች ወደስራ ገበታቸው በሰዓት ያለመግባት፣ ባለጉዳይን ያለአግባብ ማጉላላት፣ የመንግስት ንብረትን በአግባቡ ያለመያዝ ከሚስተዋሉ ችግሮች ውስጥ የሚጠቀሱ መሆናቸውን ተናግረዋል። የውይይት መድረኩን የመሩት የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ ሙሉጌታ አያሌው፤ የፍትህ ተቋማት ድርብ ኃላፊነት ያለብን መሆኑን በመረዳት ሁሉም ተቋማት ወቅታዊና ጥራት ያለው ዘመናዊ አገልግሎት መስጠት እንደሚገባቸው ተናግረዋል፡፡ የውይይቱ ተሳታፊዎችም አገልግሎት አሰጣጡን ለማሻሻል ተጠያቂነት ያለው ስርአት በመገንባት የተጠናከረ የመልካም ስነምግባር ስርአት እንዲገነባ ለማድረግ የአመራር ቁርጠኝነት የሚጠይቅ ጉዳይ በመሆኑ በብልሹ አሰራርና ሙስና ተግባር ላይ ተሰማርቶ የሚገኝ አመራርም ሆነ ሰራተኛ ላይ የተጠያቂነት አሰራርን በማስፈን ተገቢና አስተማሪ የቅጣት እርምጃ መውሰድ ይገባል ብለዋል፡፡ በመጨረሻም የፍትህ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኡሞድ ኡጅሉ በሰጡት የማጠቃለያ ሀሳብ የተነሱ ሃሳቦች ግልፅና የፍትህ ስርዓቱን ወደፊት ሊያራምዱ የሚችሉ በመሆናቸው ለተግባራዊነቱ ሁሉም አመራርና ሰራተኛ እንዲረባረብ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን 17ኛው የብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀንን በስራ ላይ በመሆን በደማቁ አከበሩ ፡፡ ******************** ፌታይኮ ጥቅምት 04/2017 ዓ.ም. የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን 17ኛው የብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀንን “ሰንደቅ ዓላማችን ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ከፍታ!” በሚል መሪ ቃል በስራ ላይ በመሆን በደማቁ አከበሩ፡፡ የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ጥቅምት በገባ በመጀመሪያ ሳምንት ሰኞ የሚከበረውን 17ኛው የብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀንን የኮሚሽኑ ፕሬዚዳንት ፣ ዳኞች ፣ አመራሮች እና መላው ሰራተኞች በተገኙበት በስራ ላይ በመሆን የተለያዩ የእለቱን መልዕክቶችን በማስተላለፍ በደማቁ አከበሩ፡፡ የኮሚሽኑ ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ ሙሉጌታ አያሌው፤ ሰንደቅ አላማችን ለእኛ ኢትዮጵያዊያን ከአለም ጫፍ እስከ ጫፍ ባለንበት ቦታ ሁሉ አብሮን የሚኖር የማንነታችን መገለጫ ፣ የነጻነታችንና የሉዓላዊነታችን ህያው ምስክር በመሆኑ እሱም በጀግና ልጆቿ መስዋዕትነትና ድል አድራጊነት ከልጅ ወደ ልጅ የሚተላለፍ ረቂቅ ሚስጥር ነው ብለዋል፡፡ የኮሚሽኑ ዳኞች ለሰንደቅ ዓለማ ክብር እና ጥቅም የተከፈለውን መስዋዕትነት በማስታወስ በችሎት ስራቸው ላይ እንዳሉ በመቆም ነፃና ገለልተኛ በመሆን ለማገልገል ቃል የገቡ ሲሆን በተጨማሪም ከዚህ ቀደም እንደሚያደርጉት የእረፍት ጊዜያቸውን ለስራ በመስጠት መዝገቦችን በተያዘላቸው ጊዜ ቀጠሮ ለማጠናቀቅ ቃል ገብተዋል፡፡ በተጨማሪም እንደሀገር 1 ትሪሊዬን ብር ለመሰብሰብ የታቀደውን ከግብ ለማድረስ በህግና በመመሪያው መሰረት ነፃና ገለልተኛ በመሆን ተጨማሪ ሰዓት በመስራትና አጠር ያለ ቀጠሮ በመስጠት ፍትሀዊ ውሳኔዎችን ለማውጣት ቃል ገብተዋል፡፡ ሰንደቅ ዓላማችን የሕብረብሔራዊነታችን የአብሮነታችን ማሳያ የአንድነታችን የጋራ ዓርማ መሆኑን በመገንዘብ ወደ ኮሚሽናችን አገልግሎት ፈልገው ለሚመጡ ተገልጋዮች ስነ-ምግባርን በመላበስ ፍትሀዊ እና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ሁሉም የኮሚሽኑ አመራሮች እና ሰራተኞች በሰንደቅ አላማ ፊት ቃል ገብተዋል፡፡ ነፃና ገለልተኝነት ለፍትሐዊ የታክስ ሥርዓት የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን

“ሰንደቅ ዓላማችን ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ከፍታ!”
“ሰንደቅ ዓላማችን ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ከፍታ!”

የፍትህ ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የዕቅድ ክንውን አፈፃፀም ገመገሙ ፡፡ ******************** ጥቅምት 01/2017 ዓ.ም. ፌታይኮ የፍትህ ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የዕቅድ ክንውን አፈፃፀም የፍትህ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) በተገኙበት ገመገሙ ፡፡ የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የዕቅድ ክንውን አፈፃፀም ሪፖርት ያቀረቡት የኮሚሽኑ ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ ሙሉጌታ አያሌው ካነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች መካከል፡- - ከ2016 በጀት ዓመት የዞሩ 326 መዛግብቶችን በመያዝ እና በ2017 በጀት ዓመት የተከፈቱ 280 በድምሩ 606 መዛግብቶች ለኮሚሽኑ የቀረቡ ሲሆን የያዙት የገንዘብ መጠን 4,064,092,920.00 ብር ነው፡፡ ከነዚህ ላይ 258ቱን መዛግብት አከራክሮ በ251 መዝገቦች ላይ ውሳኔውን አሳርፏል፡፡ ውሳኔዎቹም የያዘዙት የገንዘብ መጠን 1.646.849.611 ብር ነው ፣ - በመጀመሪያ ሩብ ዓመት በ160 መዝገቦች ላይ በከፍተኛ ፍ/ቤት ይግባኝ ተጠይቆባቸው 6ቱ ብቻ ተሽረው በድጋሚ እንዲመረመሩ የተመለሱ ሲሆን እነሱም በመታየት ሒደት ላይ ይገኛሉ ፣ - የኮሚሽኑ ውሳኔዎች ይግባኝ ተጠይቆባቸው በከፍተኛ ፍ/ቤት ተሽረው ከሚመለሱት ብዛት አንፃር ስንመለከት ውሳኔዎቹ ጥራታቸውን እና ሙሉ በሙሉ የኮሚሽኑን ነፃነት ፣ ገለልተኛነት እና ፍትሐዊ የታክስ ሥርዓትን እያረጋገጠ መሆኑን ማሳያ ናቸው፡፡ - በ1ኛ ሩብ ዓመት የራሱን ውሳኔ እንዲያስፈፅም ለኮሚሽኑ 72 መዝገቦች የቀረቡለት ሲሆነ 1 የተፈፀመ ፣ 3 ዕግድ እና 68ቱ በሂደት ላይ ናቸው ፣ - በሩብ ዓመቱ 56 አመልካቾች የይግባኝ ጊዜያቸው እንዲራዘምላቸው ጠይቀው ተራዝሟል ፣ - 7 ባለጉዳዮች የዘገየ ይግባኝ ጠይቀው 1ዱ ሲፈቀድ ፣ 4ቱ ያቀረቡት ማስረጃ አሳማኝ ባለመሆኑ ያልተፈቀደላቸው ሲሆን 2ቱ በሒደት ላይ ናቸው ፣ በታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ስር ሆነው ሥራቸውን የሚያከናውኑ ሦስቱ የአስተዳደር ችሎቶችን ስንመለከት የምርት ገበያ አስተዳደር ችሎት ምንም የቀረበ አቤቱታ አልነበረም ፣ የንግድ ውድድርና የሸማቾች ጥበቃ አስተዳደራዊ ችሎት ፣ ነጋዴው በሌላ ነጋዴ ከቀረቡ የክስ መዝገቦች 7,009,000 (ሰባት ሚሊዮን ዘጠኝ ሺህ ብር) ካለፈው በጀት ዓመት የዞሩ 2 መዝገቦች ግምቱ 3,000,000 (ሦስት ሚሊዮን) ፣ 1 አዲስ የተከፈተ መዝገብ በድምሩ የገንዘብ ግምታቸው 10,009,000 (አስር ሚሊዮን ዘጠኝ ሺህ) ብር የሆኑ 3 መዝገቦች በቀጠሮ ላይ የነበሩ ሲሆን በ2ቱ መዝገቦች ላይ ውሳኔውን አሳርፏል፡፡ 1 መዝገብ በቀጠሮ ላይ ይገኛል ፣ ከቀረቡት 3 መዝገቦች የዳኝነት 109,126 (መቶ ዘጠኝ ሺህ አንድ መቶ ሃያ ስድስት) ወደ ፍትሕ ሚኒስቴር የሒሳብ አካውንት ገቢ እንዲሆን ተደርጓል፡፡ የፌዴራል የንግድ ውድድርና የሸማቾች ጥበቃ አስተዳደራዊ ይግባኝ ሰሚ ፍ/ቤት - 2 መዝገቦች በስር የዳኝነት ችሎት የተሰጠው ውሳኔ ይሻርልን በማለት ቅሬታ አቅርበው የዳኝነትም ክፍያ በፍትህ ሚኒስቴር አካውንት 38,138.40 (ሠላሳ ስምንት ሺህ አንድ መቶ ሠላሳ ስምንት ከአርባ ሳንቲም) ገቢ አድርገው የተከፈቱ ሲሆን ቅሬታቸውን እንዲያሰሙም በቀጠሮ ሒደት ላይ ይገኛል፡፡ ተቋማዊ ተደራሽነት በተመለከተ - የአገልግሎት አሠጣጡን ተደራሽ እንዲሆን የዳታ ቤዝ ሲስተም በማልማት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ ሲስተሙን ከገቢዎች ሚኒስቴር እና ጉምሩክ ኮሚሽን ጋር ለማቀናጀት የፍላጎት ጥናት ቀርቦ ለኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እንዲሁም ቀደም ሲል ሲስተሙን ካለማው ድርጅት ጋር የጋራ ውል ስምምነት ለመፈራረም በሒደት ላይ ይገኛል ፣ - ከ(2011-2015) ጀምሮ በሀርድ ኮፒ የቀረቡ የቅሬታ መዛግብትን ዲጂታላይዝ ለማድረግ ታቅዶ በሩብ ዓመቱ (3950) መዛግብትን ዲጂታላይዝ በማድረግ ማደራጀት ተችሏል ፣ - ሴቶችን ወደ አመራርነት ለማብቃት የሚያስችል ሥርዓት በመቅረጽና የሴቶችን የአመራርነት ተሳትፎ ዕቅድ በተቋማችን ደረጃ 60% ደርሷል ፡፡ የኮሚሽኑ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች - መዛግብትን በተያዘላቸው የጊዜ ቀጠሮ መሠረት ውሳኔ የመስጠት አቅምን ማሳደግ፡፡ - ከገቢዎችና ጉምሩክ፣ ከኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ተቋማት እንዲሁም ከአልሚው ድርጅት ጋር በቅንጅት ለመሥራት የተጀመረው የማልማት ሥራው ከግብ ማድረስ፡፡ - በሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ዙሪያ የሠራተኛውን ግንዛቤ ለማዳበር የሥልጠናና የጥናት ቡድን ውይይቶችን አጠናክሮ መቀጠል፡፡ - ተቋማዊ አገልግሎት አሠጣጥን ለማሻሻል የተገልጋዮች የእርካታ ደረጃ ዳሰሳ ጥናት ማካሄድ፡፡ - የኮሚሽኑ ተሿሚ ዳኞች ያለምንም ጣልቃ ገብነት ሥራቸውን ማከናወናቸውን ማረጋገጥ፡፡ - የተጠናከረ የውስጥ ሱፐርቪዥንና የልምድ ልውውጥ ፕሮግራሞችን ማካሄድ የሥራ ክፍሎችን መደገፍ፡፡ - የአቅም ማሳደግ ሥልጠናዎችን ለዋና ሥራ ክፍሎች (ለዳኝነት ክፍሉ) ትኩረት ሰጥቶ መተግበር፡፡ በፍትህ ሚኒስቴር ሚኒስቴር ዲኤታ ክቡር ኤርሚያስ የማነብርሃን (ዶ/ር የተለያዩ ጥያቄዎች ቀርበው በተጠሪ ተቋማት አመራሮች ምላሽ ያገኙ ሲሆን በመጨረሻም በፍትህ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) ማጠቃለያ እና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ በመስጠት ተጠናቋል ፡፡ የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ነፃና ገለልተኛነት ፣ ለፍትሐዊ የታክስ ስርዓት

እንኳን ለኢሬቻ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ! አደረሰን ! ኢሬቻ የኦሮሞ ሕዝብ ከዘመን ወደ ዘመን በሰላም ላሸጋገረው አምላክ ምስጋና የሚያቀርብበት በዓል ነው ፡፡ ******************** ኢሬቻ ማለት ዋቃ (ፈጣሪ) የፈጠረውን ማመስገን ማለት ሲሆን ማኅበራዊ ደረጃ እና የእድሜ ልዩነት ሳይፈጠር የኦሮሞ ሕዝብ የኢሬቻ በዓልን ለዘመናት በጋራ ሲያከብር ቆይቷል ። የኢሬቻ በዓል ከገዳ ሥርዓት ጋር ጥብቅ ቁርኝት ያለው በመሆኑ በኦሮሞ ማኅበረሰብ ዘንድ ለዘመናት ሲከበር የቆየ በአዲስ አበባ ሆራ ፊንፊኔ ፣ በቢሾፍቱ ሆራ ሃር-ሰዲ ከመስቀል በዓል በኋላ ባሉት ቅዳሜ እና እሁድ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሕዝብ በታደመበት በዓሉ በደማቁ ይከበራል ። ኢሬቻ የዘመን መለወጫ በዓልም ነው። የኦሮሞ ሕዝብ ክረምቱ በማለፉ በኢሬቻ ቀን ምስጋናውን ለፈጣሪ ያቀርባል። በክረምት ወራት ተራርቆ ሳይገናኝ የቆየ ዘመድ አዝማድ መስከረም ላይ ይገናኛል። ሕዝቡም ክረምቱን በፈጣሪ ፍቃድ የሞላው ውሃ ጎድሎ ከዘመድ አዝማድ በመገናኘቱ እና ከጨለማ ወደ ብርሃን በመሸጋገሩ ለአምላኩ ምስጋና ያቀርባል ። የኢሬቻ በዓልን ለማክበር የሚወጣ ታዳሚ "ፈጠሪያችን ሆይ አንተ ያጸደቅከው ነው አብቦ ፍሬ ያፈራው ለዚህም እናመስግንሃለን" በማለት እንደ ሳር ወይም አበባ ያለ እርጥብ ነገር በእጅ ተይዞ ይወጣል ። በኢሬቻ በዓል ላይ የኦሮሞ ሕዝብ ለመላው የሰው ልጆች ሰላምና ደኅንነት ፈጣሪውን ዋቃን ይለምናል ፣ያመሰግናል ። መልካም የኢሬቻ በዓል ! ፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ነፃና ገለልተኝነት፤ ለፍትሐዊ የታክስ ስርዓት ! ስለ ፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛ አድራሻችንን ይጠቀሙ ፡- ፌስ ቡክ 👇 https://www.facebook.com/ftacofficial ቴሌግራም 👇 https://t.me/ftac_official ትዊተር 👇 https://twitter.com/federal_appeal ድረ ገፅ 👇 http://ftac.gov.et/en-us/ ዩ ቱብ 👇 https://www.youtube.com/channel/UCzpuuuXybdHh7BlgWXMVIGw አድራሻችንን follow, join, subscribe, like, comment, and share በማድረግ ህብረተሰቡ ስለ ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ትክክለኛ መረጃ እንዲያገኝ የድርሻዎን ይወጡ ፡፡

ተለዋጭ ቀጠሮ ስለማሳወቅ መስከረም 24/2017 ዓ.ም ተቀጥረው የነበሩ ወደ ጥቅምት 05/2017 ዓ.ም የተዛወሩ መሆናቸውን እንገልፃለን ፡፡ ነፃና ገለልተኝነት ለፍትሐዊ የታክስ ስርዓት ! ስለ ፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛ አድራሻችንን ይጠቀሙ ፡- ፌስ ቡክ 👇 https://www.facebook.com/ftacofficial ቴሌግራም 👇 https://t.me/ftac_official ትዊተር 👇 https://twitter.com/federal_appeal ድረ ገፅ 👇 http://ftac.gov.et/en-us/ ዩ ቱብ 👇 https://www.youtube.com/channel/UCzpuuuXybdHh7BlgWXMVIGw አድራሻችንን follow, join, subscribe, like, comment, and share በማድረግ ህብረተሰቡ ስለ ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ትክክለኛ መረጃ እንዲያገኝ የድርሻዎን ይወጡ