Bahir Dar Academy Middle School Channel
Open in Telegram
2 524
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ለባህርዳር አካዳሚ አባይ ካምፓስ ወላጆች ብቻ
የተከበራችሁ ወላጆች እንደምን አላችሁ፡፡ ባህርዳር አካዳሚ አባይ ካምፓስ ለ2015 ዓ.ም የተማሪ ወርሃዊ ክፍያ ጭማሪ ላይ ከወላጆች ጋር ውይይት ግንቦት 28 ቀን 2014 ዓ.ም (እሁድ) ጥዋት 3፡00 ሰዓት ላይ በባህርዳር አካዳሚ አባይ ካምፓስ ግቢ ውስጥ ያካሂዳል፡፡ ይህ ውይይት የእያንዳንዳችሁን የተማሪ ወላጆች ንቁ ተሳትፎ ስለሚፈልግ ሁላችሁም ሰዓቱን አክብራችሁ እንድትገኙልን በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡
ለባህርዳር አካዳሚ ዋና ግቢ ወላጆች ብቻ
የተከበራችሁ ወላጆች እንደምን አላችሁ፡፡ ባህርዳር አካዳሚ ለ2015 ዓ.ም የተማሪ ወርሃዊ ክፍያ ጭማሪ ላይ ከወላጆች ጋር ውይይት ለማድረግ ባለፈው እሁድ ጠርቶ የነበረ ቢሆንም በዕለቱ ምልዓተ ጉባኤ ያልተሟላ በመሆኑ ለሚቀጥለው ሳምንት ግንቦት 21 ቀን 2014 ዓ.ም (እሁድ) ጥዋት 3፡00 ሰዓት ላይ ስለተቀጠረ እንዲሁም ይህ ውይይት ከዚህ በኋላ ለሌላ ጊዜ የማይራዘምና የመጨረሻ ስለሆነ በዕለቱ 3፡00 ሰዓት ላይ ሁላችሁም ወላጆች ባህርዳር አካዳሚ ዋናው ግቢ እንድትገኙ ከአደራ ጋር እናሳስባለን፡፡ የወላጅ ውይይት ቦታው እንዲቀየር በአንድ ተሳታፊ ሃሳብ የቀረበ ቢሆንም የት/ቤቱ አስተዳደር የውይይት ቦታው ባህርዳር አካዳሚ ዋናው ግቢ እንዲሆን ስለወሰነ የውይይት ቦታችን እንደተለመደው ልጆቻችን የሚማሩበት ግቢ ነው፡፡
ማሳሰቢያ፡- የባህርዳር አካዳሚ አባይ ካምፓስ ወላጆች ውይይት ከዋናው ግቢ ውይይት ቀጥሎ ባሉው ሳምንት ስለሚካሄድ በሌላ ጊዜ በዚህ የቴሌግራም ቻናል የውይይት ቀኑን የምናሳውቅ ይሆናል፡፡
Middle School 2nd Semester Final Exam Schedule.docx0.15 KB
ጉዳዩ፡- የ2014 ዓ.ም የ2ኛው ወሰነ ትምህርት ማጠቃለያ ፈተናን ይመለከታል፡፡
የተከበራችሁ ወላጆች እና የተወደዳችሁ ተማሪዎቻችን እንደምን አላችሁ፡፡
1. የ2ኛው ወሰነ ትምህርት የማጠቃለያ ፈተና ከሰኔ 17 - 23/2014 ዓ.ም ይሰጣል፡፡
2. የፈተና ወረቀታቸው ለተማሪዎች የሚመለስበት እና ውጤታቸው ከ100% የሚነገርበት ሰኔ 24 ቀን 2014 ዓ.ም ይሆናል፡፡
3. የማጠቃለያ ፈተና ፕሮግራም ከዚህ በታች አያይዘን ልከናል (Attach ተደርጓል)፡፡
4. ስለዚህ ተማሪዎች ከአሁኑ ጊዜያችሁን በአግባቡ በመጠቀም እንድታጠኑ እያሳሰብን ወላጆችም አስፈላጊ በሆነው ሁሉ እገዛችሁ እንዳይለያቸው አደራ እንላለን፡፡ እናመሰግናለን፡፡
ለባህርዳር አካዳሚ ዋና ግቢ ወላጆች ብቻ
የተከበራችሁ ወላጆች እንደምን አላችሁ፡፡ ባህርዳር አካዳሚ ለ2015 ዓ.ም የተማሪ ወርሃዊ ክፍያ ጭማሪ ላይ ከወላጆች ጋር ውይይት ግንቦት 14 ቀን 2014 ዓ.ም (እሁድ) ጥዋት 3፡00 ሰዓት ላይ በባህርዳር አካዳሚ ዋናው ግቢ ያካሂዳል፡፡ ይህ ውይይት የእያንዳንዳችሁን የተማሪ ወላጆች ንቁ ተሳትፎ ስለሚፈልግ ሁላችሁም እንድትገኙ በአክብሮት እየጠቅን ውይይቱ ከጥዋቱ 3፡00 ሰዓት የሚጀምር መሆኑን እንገልፃለን፡፡
ማሳሰቢያ፡- የባህርዳር አካዳሚ አባይ ካምፓስ ወላጆች ውይይት ከዋናው ግቢ ውይይት ቀጥሎ ባሉት ቀናት ውስጥ ስለሚካሄድ በሌላ ጊዜ በዚህ የቴሌግራም ቻናል የውይይት ቀኑን የምናሳውቅ ይሆናል፡፡
የተከበራችሁ የተማሪዎቻችን ወላጆች እንዲሁም የተወደዳችሁ ተማሪዎቻችን እንደምን አላችሁ፡፡ የ2ኛው ወሰነ ትምህርት አጋማሽ ፈተና (Mid-term Exam) ሚያዚያ 03 - 05 ቀን 2014 ዓ.ም (ከሰኞ - ረቡዕ) የሚሰጥ ሲሆን ተማሪዎችም ት/ቤት የሚቆዩት እስከ 6፡00 ስዓት ነው፡፡ ስለዚህ እግረኛ ተማሪዎችን ልክ 6፡00 ስዓት ላይ ት/ቤት መጥታችሁ እንድትረከቡ እንዲሁም በትራንስፖርት የሚሄዱ ተማሪዎችንም በስዓቱ እንድትቀበሉ እናሳውቃለን፡፡
የተማሪዎች የፈተና ፕሮግራም ከዚህ በፊት (መጋቢት 10/2014 ዓ.ም) በዚህ የቴሌግራም ቻናል የተገለፀ ስለሆነ በፕሮግራሙ መሰረት እንዲዘጋጁ ድጋፍ እንዲደረግላቸው እናሳስባለን፡፡ ስለሚደረግላቸው ድጋፍ በቅድሚያ እናመሰግናለን፡፡
ማሳሰቢያ፡-
ከሚያዚያ 06 ቀን 2014 ዓ.ም (ሐሙስ) ጀምሮ ሙሉ ቀን (እስከ 9፡00 ስዓት) ትምህርት የሚሰጥ ይሆናል፡፡
የ2014 ዓ.ም የ2ኛው ወሰነ ትምህርት አጋማሽ ፈተና (Mid-term Exam) ከሚያዚያ 03 እስከ 05 ባሉት ቀናት ይሰጣል፡፡ የፈተና ፕሮግራሙ ከዚህ በታች ተያይዟል (attach ተደርጓል)፡፡
ውድ ተማሪዎቻችን እንደምን አላችሁ፡፡ የ2014 ዓ.ም የ2ኛው ወሰነ ትምህርት አጋማሽ ፈተና (Mid-term exam) ከሚያዚያ 03 - 05/2014 ዓ.ም ይሰጣል፡፡ ስለዚህ የተሻለ ውጤት ለማግኘት ከአሁኑ በርትታችሁ እንድታነቡ እያሳወቅን የፈተና ፕሮግራሙን በቅርቡ በዚህ የቴሌግራም ቻናል የምናሳውቅ ይሆናል፡፡
ጉዳዩ፡- ከየካቲት ወር 2014 ዓ.ም ጀምሮ የተማሪ ወርሃዊ ክፍያ የተማሪ መለያ ቁጥር (ID) በመጠቀም ብቻ መከፈል ያለበት መሆኑን በድጋሜ ስለማሳወቅ፡፡
የተከበራችሁ የተማሪዎቻችን ወላጆች እንደምን አላችሁ፡፡ የባህርዳር አካዳሚ የተማሪ ወርሃዊ የትምህርት ክፍያ ከየካቲት ወር 2014 ዓ.ም ጀምሮ የዋናው ግቢ በዳሽን ባንክ እንዲሁም የአባይ ካምፓስ በብርሃን ባንክ ስኩል ፔይ ሲስተም (School Pay System) አማካኝነት የተማሪ መለያ ቁጥር (ID) በመጠቀም መከፈል እንዳለበት ከ1 ወር በፊት በዚህ የቴሌግራም ቻናል እና በወረቀትም በተማሪዎች በኩል ማሳወቃችን ይታወሳል፡፡
• በዚህም መሠረት አብዛኞች ደንበኞቻችን የተማሪን መለያ ቁጥር (ID) በመጠቀም ከፍለዋል፡፡
• ይሁን እንጂ ጥቂት ደንበኞች ክፍያ ባንክ ሲከፍሉ የተማሪን መለያ ቁጥር (ID) ስለማይጠቀሙ በት/ቤቱ የሂሳብ ክትትል ላይ ችግር እየፈጠረ ፤ በሂሳብ ክትትሉ ላይ የሚፈጥረው ችግርም በእናንተ በደንበኞቻችን ላይም መጉላላትን እያስከተለ ይገኛል፡፡
• ስለዚህ ከየካቲት ወር 2014 ዓ.ም ጀምሮ ያለውን የተማሪ ወርሃዊ ክፍያ የተማሪ መለያ ቁጥርን (ID) ሳይጠቀሙ መክፈል የማይፈቀድ መሆኑን በድጋሜ እናሳውቃለን፡፡ እናመሰግናለን፡፡
የተከበራችሁ ወላጆች እንዲሁም የተወደዳችሁ ተማሪዎቻችን እንደምን አላችሁ፡፡
1. የ2ኛው ወሰነ ትምህርት ጥር 30 ቀን 2014 ዓ.ም (ሰኞ) ይጀምራል፡፡
2. በዕለቱም መደበኛ መማር ማስተማር (ትምህርት) ሙሉ ቀን ይሰጣል፡፡
3. ስለዚህ ተማሪዎች ት/ቤት የሚቆዩት እስከ 9፡00 ሰዓት ነው፡፡ እናመሰግናለን፡፡
