en
Feedback
Bahir Dar Academy Middle School Channel

Bahir Dar Academy Middle School Channel

Open in Telegram

educational

Show more
Ethiopia8 692The category is not specified
2 524
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ጥር 29 ቀን 2014 ዓ.ም የተላከ

ጉዳዩ፡- የባህርዳር አካዳሚ ዋናው ግቢ ተማሪዎችን ብቻ ይመለከታል፡፡ የተከበራችሁ የተማሪዎቻችን ወላጆች እንደምን አላችሁ፡፡ የባህርዳር አካዳሚ የዋናው ግቢ የተማሪ ወርሃዊ የትምህርት ክፍያ በዳሽን ባንክ ስኩል ፔይ ሲስተም (School Pay System) አማካኝነት ከየካቲት ወር 2014 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል፡፡ ስለዚህ በልጆቻችሁ በኩል ከ2 ሳምንት በፊት በተላከው የተማሪ መለያ ቁጥር (ID) መሰረት ብቻ እንድትከፍሉ እያሳወቅን ፤ የየወሩ ክፍያ የሚጀምርበትን (Active የሚሆንበት) ቀን በፈረንጆች አቆጣጠር ወሩ በገባ በ5 ሲሆን በዝርዝር ከዚህ በታች ተቀምጧል፡፡ 1. የየካቲት ወር ክፍያ - ጥር 28 ቀን 2014 ዓ.ም (February 05, 2022 G.C) 2. የመጋቢት ወር ክፍያ - የካቲት 26 ቀን 2014 ዓ.ም (March 05, 2022 G.C) 3. የሚያዚያ ወር ክፍያ - መጋቢት 27 ቀን 2014 ዓ.ም (April 05, 2022 G.C) 4. የግንቦት ወር ክፍያ - ሚያዚያ 27 ቀን 2014 ዓ.ም (May 05, 2022 G.C) 5. የሰኔ ወር ክፍያ - ግንቦት 28 ቀን 2014 ዓ.ም (June 05, 2022 G.C) ማስታወሻ፡- 1) ክፍያውን በአቅራቢያችሁ በሚገኝ የዳሽን ባንክ ቅርንጫፍ መክፈል ትችላላችሁ፣ 2) እስከ ጥር ወር 2014 ዓ.ም ያልተከፈለ ውዝፍ ክፍያ ካለ አዲሱ ስኩል ፔይ ሲስተም ከመጀመሩ በፊት በድሮው የአከፋፈል ስርዓት ክፍያው ተከፍሎ መጠናቀቅ አለበት፣ 3) አዲስ ሲስተም በመሆኑ ለሚያጋጥሙ ችግሮች በየጊዜው የመፍትሄ ማስተካከያዎችን የምናሳውቅ መሆኑን እንገልፃለን፡፡ እናመሰግናለን፡፡

ጥር 19 ቀን 2014 ዓ.ም የተላከ

የተከበራችሁ የተማሪዎቻችን ወላጆች እንደምን አላችሁ፡፡ የጥር ወር ወርሃዊ ክፍያን እንዲሁም ከጥር ወር በፊት ላሉት ወራት ውዝፍ ክፍያ ካለብዎ እስከ ጥር 12 ቀን 2014 ዓ.ም (ሐሙስ) ድረስ ብቻ እንድትከፍሉ በዚህ የቴሌግራም ቻናል ማሳወቃችን ይታወሳል፡፡ በዚህም መሠረት አብዛኞቹ ደንበኞቻችን ክፍያውን በተሰጠው የጊዜ ገደብ ከፍለዋል፡፡ ነገር ግን ጥቂት ደንበኞቻችን አሁንም ያለባቸውን ወርሃዊ ክፍያ ስላልከፈሉ በአሠራር ላይ ችግር እየፈጠረብን ይገኛል፡፡ ስለሆነም ያለብዎትን ወርሃዊ ክፍያ እስከ ጥር 14 ቀን 2014 ዓ.ም (ቅዳሜ) ድረስ ብቻ ከፍለው እንዲያጠናቅቁ ከአደራ ጋር እናሳስባለን፡፡ እናመሰግናለን፡፡

ጥር 13 ቀን 2014 ዓ.ም የተላከ

የተከበራችሁ ወላጆች እና የተወደዳችሁ ተማሪዎቻችን እንደምን አላችሁ፡፡ በ1ኛው ወሰነ ትምህርት የማጠቃለያ ፈተና ጊዜ ከጥር 13 - 20/2014 ዓ.ም ተማሪዎች ት/ቤት የሚቆዩት እስከ ቀኑ 6፡30 ስዓት ድረስ ብቻ መሆኑን እንገልፃለን፡፡ ስለሆነም ተማሪዎቻችን (ልጆቻችሁን) በስዓቱ እንድትረከቡልን እንዲሁም ከስዓት በኋላ ያለውን ጊዜያቸውን በጥናት እንዲያሳልፉ እንድታበረታቱልን ከአደራ ጋር እናሳውቃለን፡፡ እናመሰግናለን፡፡

የተከበራችሁ ወላጆች እና የተወደዳችሁ ተማሪዎቻችን እንደምን አላችሁ፡፡ በ1ኛው ወሰነ ትምህርት የማጠቃለያ ፈተና ጊዜ ከጥር 13 - 20/2014 ዓ.ም ተማሪዎች ት/ቤት የሚቆዩት እስከ ቀኑ 6፡30 ስዓት ድረስ ብቻ መሆኑን እንገልፃለን፡፡ ስለሆነም ተማሪዎቻችን (ልጆቻችሁን) በስዓቱ እንድትረከቡልን እንዲሁም ከስዓት በኋላ ያለውን ጊዜያቸውን በጥናት እንዲሳልፉ እንድታበረታቱልን ከአደራ ጋር እናሳውቃለን፡፡ እናመሰግናለን፡፡

ጥር 12 ቀን 2014 ዓ.ም የተላከ

ጉዳዩ፡- የባህርዳር አካዳሚ ዋናው ግቢ ተማሪዎችን ብቻ ይመለከታል፡፡ የተከበራችሁ የተማሪዎቻችን ወላጆች እንደምን አላችሁ፡፡ የባህርዳር አካዳሚ የዋናው ግቢ የተማሪ ወርሃዊ የትምህርት ክፍያ በዳሽን ባንክ ስኩል ፔይ ሲስተም (School Pay System) የተማሪ መለያ ቁጥርን (ID) በመጠቀም ክፍያ እንድትፈፅሙ ጥር 04 ቀን 2014 ዓ.ም ማስታወቃችን ይታወሳል፡፡ ነገር ግን የተማሪዎች ዝርዝር እንዲሁም የክፍያ መረጃዎች በጥቅምት ወር ለዳሽን ባንክ ተልኮ ከታህሳስ ወር ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ የታሰበ ሲሆን፤ በልዩ ልዩ ምክንያቶች ዘግይቶ ጥር 04 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ መጠቀም እንደምንችል አሳውቆናል፡፡ ሆኖም ወላጆች ለክፍያ ወደ ባንክ ሲሄዱ የታህሳስን ወር ጨምሮ እንዲከፍሉ የባንኩ ሲስተም ስለጠየቃቸው ባንኩ መረጃውን እንደገና ማስተካከል አስፈልጎታል፡፡ ስለዚህ ከየካቲት ወር ጀምሮ ያለውን በስኩል ፔይ ሲስተም (School Pay System) የተማሪ መለያ ቁጥርን (ID) በመጠቀም ክፍያ የምትፈፅሙ ሲሆን የተለየ ሁኔታ ሲያጋጥም ለወደፊት በዚህ የቴሌግራም ቻናል የምናሳውቅ ይሆናል፡፡ ለአሁኑ ግን ከአሁን በፊት ስትከፍሉበት በነበረው መደበኛ የባንኩ የገንዘብ ማስገቢያ ስርዓት መሠረት ክፍያውን እንድትፈፅሙ እየገለፅን ለተፈጠረው የመረጃ አሰጣጥ ክፍተት በቅድሚያ ይቅርታ እንጠይቃለን፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ፡- 1. የጥር ወር 2014 ዓ.ም ወርሃዊ የትምህርት ክፍያን እንዲሁም፣ 2. ከጥር ወር 2014 ዓ.ም በፊት ላሉት ወራት ውዝፍ ክፍያ ካለብዎት እስከ ጥር 12 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ ብቻ ክፍለው እንዲያጠናቅቁ ከአደራ ጋር እናሳስባለን፡፡ እናመሰግናለን፡፡

ጥር 06 ቀን 2014 ዓ.ም የተላከ

+1
Middle School 1st Semester Final Exam Schedule for 2014 E.C.docx0.15 KB

የተከበራችሁ ወላጆች እና የተወደዳችሁ ተማሪዎቻችን እንደምን አላችሁ፡፡ 1. የመጀመሪያው ወሰነ ትምህርት የማጠቃለያ ፈተና ከጥር 13 - 19/2014 ዓ.ም ይሰጣል፡፡ 2. የማጠቃለያ ፈተና ፕሮግራም ከዚህ በታች አያይዘን ልከናል (Attach ተደርጓል)፡፡ 3. ጥር 20 ቀን 2014 ዓ.ም ለተማሪዎች የፈተና የመልስ ወረቀት ይሰጣል እንዲሁም ውጤት ከ100% ይነገራቸዋል፡፡ 4. ከጥር 21 - 29/2014 ዓ.ም 9 ቀናት ለተማሪዎች የእረፍት ጊዜ ይሆናል፡፡ በዚህ ወቅት መምህራን የተማሪዎችን የውጤት ሮስተር ይሰራሉ፡፡ 5. ጥር 30/2014 ዓ.ም የሁለተኛው ሴሚስተር ትምህርት ይጀመራል፡፡ በዕለቱ ሁሉም መምህራን ዕለታዊ የትምህርት ዕቅድ በማዘጋጀት መደበኛ የመማር ማስተማር ተግባር ያከናውናሉ፡፡ ስለዚህ ሁሉም ተማሪዎች ጥር 30 ት/ቤት መገኘት አለባቸው፡፡

ጥር 05 ቀን 2014 ዓ.ም የተላከ

ጉዳዩ፡- የባህርዳር አካዳሚ ዋናው ግቢ ተማሪዎችን ብቻ ይመለከታል፡፡ የተከበራችሁ የተማሪዎቻችን ወላጆች እንደምን አላችሁ፡፡ የባህርዳር አካዳሚ የዋናው ግቢ የተማሪ ወርሃዊ የትምህርት ክፍያ በዳሽን ባንክ ስኩል ፔይ ስስተም (School Pay System) አማካኝነት ከዛሬ ጥር 04 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ ሆኗል፡፡ ስለዚህ በልጆቻችሁ በኩል ዛሬ በሚደርሳችሁ የተማሪ መለያ ቁጥር (ID) መሰረት ብቻ እንድትከፍሉ እያሳወቅን፡- 1. በአቅራቢያችሁ በሚገኝ የዳሽን ባንክ ቅርንጫፍ መክፈል ትችላላችሁ፣ 2. በተሰጣችሁ ID መሰረት ብቻ እንድትከፍሉ፣ 3. ወሩ በገባ ከ10 የስራ ቀናት በኋላ የባንኩ ሲስተም ቅጣት የሚጨምር በመሆኑ በወቅቱ ክፍያ እንድትፈፅሙ፣ 4. አዲስ ሲስተም በመሆኑ ለሚያጋጥሙ ችግሮች በየጊዜው የመፍትሄ ማስተካከያዎችን የምናሳውቅ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

ጥር 04 ቀን 2014 ዓ.ም የተላከ

የተከበራችሁ ወላጆች እንዲሁም የተወደዳችሁ ተማሪዎቻችን እንደምን አላችሁ፡፡ የአንደኛው ወሰነ ትምህርት ማጠቃለያ ፈተና ከጥር 13 - 19/2014 ዓ.ም ይሰጣል፡፡ ስለዚህ ተማሪዎች ከአሁኑ ጊዜያችሁን በአግባቡ በመጠቀም እንድታጠኑ እያሳሰብን ወላጆችም አስፈላጊ በሆነው ሁሉ እገዛችሁ እንዳይለያቸው አደራ እንላለን፡፡ የፈተና ፕሮግራሙን በቅርቡ በዚሁ ቴሌግራም ቻናል የምናሳውቅ ይሆናል፡፡

ታህሳስ 25 ቀን 2014 ዓ.ም የተላከ

በባህር ዳር አካዳሚ ስም የተለያዩ የ facebook ገጾች በማኅበራዊ መገናኛዎች ተከፍተዋል፡፡ ነገር ግን ትክክለኛዉ የባህር ዳር አካዳሚ የ facebook ገጽ የት/ቤቱ አርማ ያለበት እና ከዚህ በታች ሊንኩን ተጭነዉ የሚያገኙት ነዉ፡፡ በመሆኑም የት/ቤቱ ተማሪዎችም ሆናችሁ የተማሪዎች ወላጆችች ሊንኩን በመጫን እና Follow ወይም Like በማድረግ ስለት/ቤቱ ትክክለኛ መረጃ ማግኘት የምትችሉ መሆኑን በአክብሮት እንገልጻለን፡፡ የ facebook ገጹን ሊንክ እንደሚከተለዉ ነዉ፡፡ https://www.facebook.com/Bahir-Dar-Academy-110684694782938 ይጫኑት እና ይከተሉት፡፡እናመሰግናለን፡፡ This is the link to Bahir Dar Academy facebook page. You all are invited to open and follow the page. here is the link to the page https://www.facebook.com/Bahir-Dar-Academy-110684694782938 Facebook Log in or sign up to view See posts, photos and more on Facebook.

ታህሳስ 15 ቀን 2014 ዓ.ም የተላከ

የተከበራችሁ የተማሪዎቻችን ወላጆች የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ትም/መምሪያ ህዳር 24 ቀን 2014 ዓ.ም ሁሉም የት/ቤቱ መምህራንና ሠራተኞች እንዲሁም ከ7ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች አገራችን እያደረገችው ያለውን የህልውና ዘመቻ በተመለከተ የድጋፍ ሰላማዊ ሰልፍ ከጥዋቱ 1፡00 ጀምሮ እንዲደረግ አስታውቆናል፡፡ ባህርዳር አካዳሚም በዚህ የድጋፍ ሰልፍ ላይ በንቃት ይሳተፋል፡፡ ስለዚህ፡- 1. ከኬጂ እስከ 6ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች ነገ (አርብ) መምህራኖቻቸው የድጋፍ ሰልፉ ላይ ስለሆኑ ት/ቤት አይመጡም፡፡ 2. ከ7ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች ሁሉም የድጋፍ ሰላማዊ ሰልፉ ላይ እንዲገኙ ጥዋት 1፡00 ስዓት ላይ ት/ቤቱ ቅጥር ግቢ እንድታደርሱልንና ፕሮግራሙ እንዳለቀ ወዲያውኑ የት/ቤቱ ኃላፊዎች በሚቀጥሯችሁ ቦታ እንድትረከቡን እናሳውቃለን፡፡