Tabor Education Center Director
Open in Telegram
999
Subscribers
No data24 hours
-67 days
-1230 days
Posts Archive
2017_E_C_2nd_Semester_Midterm_&_Model_Exam_Schedule_for_Grade_9.docx0.22 KB
2017_E_C_2nd_Semester_Midterm_&_Model_Exam_Schedule_for_Grade_9.docx0.18 KB
ቀን፡ 04/01/2017 ዓ.ም
ለታቦር ትምህርት ማዕከል ተማሪዎች በሙሉ;
የ2017 ዓ.ም ት/ዘመን መደበኛ ትምህርት የሚጀምረዉ መስከረም 13 ቀን 2017 ዓ.ም ስለሆነ በዕለቱ አስፈላጊዉን የትምህርት ቁሳቁስ በመያዝ 1፡50 ሰዓት በትምህርት ቤቱ ቅጥር ግቢ ዉስጥ እንድትገኙ ከወዲሁ እናስታዉቃለን፡፡
ታቦር ትምህርት ማዕከል!
ቀን፡ 24/11/2016 ዓ.ም
ለታቦር ትምህርት ማዕከል ነባሪ ተማሪዎች በሙሉ፤
የ2017 ዓ.ም ትምህርት ዘመን የመደበኛ ትምህርት ምዝገባ ከሐምሌ 25 ቀን 2016 ዓ.ም እስከ ነሐሴ 10 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ስለሆነ የመስከረም 2017 ዓ.ም ወራዊ የትምህርት ክፍያ ብር 1250 (አንድ ሺህ ሁለት መቶ ሃምሳ ብር) እና ብር 300 የመመዝገቢያ በድምሩ ብር 1550 (አንድ ሺህ አምስት መቶ ሃምሳ ብር) በአዋሽ ባንክ ታቦር ወንጌላዊት ኮሌጅ ሒሳብ ቁጥር 01308903421000 በመክፍል ስሊፑን እና ከክፍል ወደ ክፍል የተዛወራችሁበትን ካርድ ይዛችሁ ከወላጆቻችሁ ጋር በአካል በመቅረብ ደረሰኝ እያስቆረጣችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን ከወዲሁ እናስታዉቃለን፡፡
ማሳሰቢያ፡-
1ኛ፣ ማንኛዉም ክፍያ በባንኩ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን፤
2ኛ፣ እስከ 10/12/2016 ዓ.ም ድረስ ላልተመዘገባችሁ ተማሪዎች ት/ቤቱ ቦታ የማይኖር መሆኑን፤
2ኛ፣ በዲስፕሊን ምክንያት የተሰናበታችሁ ተማሪዎች መመዝገብ የማትችሉ መሆኑን እናሳስባለን፡፡
ቀን፡ 13/11/2016 ዓ.ም
ማስታወቂያ
ለታቦር ት/ት ማዕከል ነባሪና አዲስ ገቢ ተማሪዎች በሙሉ፤
የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ባወጣዉ መርሃ-ግብር መሠረት የ2017 ዓ.ም ትምህርት ዘመን መደበኛ ምዝገባ የሚካሄደዉ ከሐምሌ 25 ቀን 2016 ዓ.ም እስከ ነሐሴ 10 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ብቻ ስለሆነ ነባሪ ተማሪዎች ከሀምሌ 25 ቀን 2016 ዓ.ም እስከ ነሐሴ 3 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ብቻ በአካል እየቀርባችሁ እንድትመዘገቡ እየገለጽን አዲስ ገቢ ተማሪዎች ከሐምሌ 22-24 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ለመግቢያ ፈተና እንድትመዘገቡ እያስታወቅን የመግቢያ ፈተና የሚሰጠዉ ሐምሌ25 ቀን 2016 ዓ.ም ከጧቱ 3፡00 ሰዓት መሆኑን ከወዲሁ እናስታዉቃለን፡፡
ታቦር ትምህርት ማዕከል (ኢቫን ትምህርት ቤት)!
ማሳሰቢያ፡- 1. አዲስ ገቢ ተማሪዎች ለመግቢያ ፈተና ብር 300፤
2. ለነባሪ ተማሪዎች መመዝገቢያ ብር 300 እና ወራዊ የትምህርት ክፍያ ብር 1250፤
3. ከክፍል ወደ ክፍል ያለፋችሁበትን ካርድ በመያዝ ከወላጆቻችሁ ጋር መምጣት ይጠበቅባችኋል፤
4. የመግቢያ ፈተና የሚታልፉ አዲስ ገቢ ተማሪዎች 3X4 በቁጥር 2 ጉርድ ፎቶግራፊ የተማሪዉ/ዋ
እና 1 የወላጅ እንዲሁም 1 ዶስ ይዛችሁ መምጣት ይኖርባችኋል፡፡
Tabor Education Center General Secondary & Preparatory School Celebrates Parents' Day or School Closing Day on this Saturday, 13 July 2024.
ቀን፡ 01/11/2016 ዓ.ም
ማስታወቂያ
ለታቦር ትምህርት ማዕከል [EVAN] ተማሪ-ወላጆች በሙሉ፤
እንኳን ለ2016 ዓ.ም ትምህርት ዘመን የተማሪ ወላጆች በዓል ቀን በሰላም አደረሳችሁ!
የታቦር ትምህርት ማዕከል አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት የ2016 ዓ.ም ትምህርት ዘመን የዉጤት መግለጫ ካርድ የሚሰጠዉ ሐምሌ 6 ቀን 2016 ዓ.ም ከጧቱ 2፡30-4፡30 ሰዓት ድረስ ብቻ ስለሆነ ከልጆቻችሁ ጋር ተገንታችሁ በዓሉን እንድታከብሩ በአክብሮት እየጠራናችሁ የዉጤት መግለጫ ካርድ የሚሰጠዉ ለወላጅ ብቻ መሆኑን ጭምር ከወዲሁ እናስታዉቃለን፡፡
ከታቦር ትምህርት ማዕከል!
ማሳሰቢያ፡- ወራዊ የትምህርት ክፍያ አጠናቅቆ ያልከፈለ የዉጤት መግለጫ ካርድ የማይሰጥ መሆኑን እየገለጽን በወሩ ያልተፈጸመ ክፍያ በየወሩ ብር 100 ቅጣት የሚጣል መሆኑን ጭምር እናስታዉቃለን፡፡
