en
Feedback
የጦር ሜዳ ውሎ 💪🏽

የጦር ሜዳ ውሎ 💪🏽

Open in Telegram

👉 የቻናሉ መከፈት ዋና አላማው ታሪክ የሚያጠፋውን ትውልድ በመቃወም ታሪክ የሚሰራ ትውልድ መገንባት ነው!! 🗣 Official Channel 👇🏽 📡 https://t.me/joinchat/AAAAAFUFiN1N7T13DEKhAQ Group Chanel 👥 @yetormida_welo 》》t.me/ @Tarikawi_fotowech 👉 ለአስተያየዎ @Eyoha_Bot ላይ ይፃፉልን

Show more
461
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
እውነት ነው

አውቶማቲክ ላይ አድርገው በቀኝ እጃቸው ጨብጠዋል፡፡ በጄኔራል ተሾመ ተሰብስበው የነበሩ የአብታዊ ሰራዊት አባላት ተደናግጠው ከተቀመጡበት ተነስተው ቆመው የጄኔራሉን የመጨረሻ ፍጻሜ ለማየት እየዘገነናቸው እንባ በእንባ ሆኑ፡፡ አንዳንዶቹ ደግሞ ህይወታቸውን ለማጥፋት የክላሽንኮቭና የሽጉጥ መጠበቂያ ከፍተው የጄኔራል ተሾመን ምሳሌነት ለመከተል ተዘጋጁ፡፡ ጄኔራል ተሾመ ከምጽዋ ወደብ በስተቀኝ ከሚገኘው ወታደራዊ ወደብና መደብር ላይ ሲደርሱም ለቀይ ባሕር መገደቢያ በተሰራ ግንብ ጠርዝ ላይ ጀርባቸውን ወደ ቀይ ባሕር ፊታቸውን ወደ ምፅዋ ከተማ ሰድርገው ቆሙ፡፡ ቀጥለውም በእጃቸው የነበረውን ክላሺንኮቭ ጠመንጃ ወደ ቀይ ባሕር ወረወሩት፡፡ ከዚያም በወገባቸው ታጥቀውት የነበረውን ኮልት ሽጉጥ አወጡና የሽጉጡን አፈሙዝ በአፋቸው ጎርሰው የካቲት 9 ቀን 1982 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡10 ሰዓት ሲሆን ቃታውን ሳቡት፡፡ የሽጉጥ ተኩስ እንደተሰማ ወደ ጀርባቸው በቀይ ባሕር ውሃ ላይ ወድቀው ሰጠሙ፡፡ በመቶዎች የሚቆጠሩ የአብዮታዊ ሠራዊት አባላት ተሸቀዳድመው ባሕር ጠረፉ ላይ ደርሰው የጄኔራሉን አስከሬን ሲመለከቱ ከጭንቅላታቸው የሚፈስ ደም በቀይ ባሕር ውሃ ላይ ቀልቶ ይታይ ጀመር፡፡ ወዲያውም ይህን የጄኔራል ተሾመን ሞት በምስክርነት ቆመው ካዩት መካከል ከ150 የማያንሱ የጦር መኮንኖችና ባለሌላ ማዕረግተኞች በሽጉጥ በእጅ ቦምብና በክላሽ ጠመንጃ ህይወታቸውን አጠፉ…….. የካቲት 9 ቀን 1982 ምፅዋ - ርዕሲ ምድሪ © ታደሰ ቴሌ ሳልቫኖ - አይ ምፅዋ @yetormida_welo

🔝 የመጣው ይምጣ ከሞት ውጪ የሚመጣ የለም ። ነገሩ ከአቅም በላይ ከሆነ ሻዕቢያ ዓይኔን ማየት ቀርቶ ሬሣዬንም አያገኛትም ። እድሜ ለቀይ ባህር ውሃ የቀይ ባህር ዓሳ ይቀብረኛል ። የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግስት ጣሉብኝ አደራ ከድንጋይ በላይ ይከብደኛል በመሆኑም ጠላት ከአቅም በላይ ከሆነ እንደ አጼ ቴዎድሮስ ሽጉጤን እጠጣለሁ፡፡ የካቲት 9 ቀን 1982 ዓም ምጽዋ ከተማ ለተከማቸው አብዮታዊ ሠራዊትና አመራሩ ክፉ ቀን ነበረች ሻዕቢያ ደግሞ እንደ ልደት ቀን ይቆጠረዋል ምክንያቱም የሻዕቢያ ተዋጊ የድል ባለቤት ሆኖ ለመጀመሪያ ጊዜ ምፅዋ ከተማን የረገጠው በዚች ዕለት ነውና ሻዕቢያ በ1970 ዓ.ም ከጀብሃ ተዋጊዎች ጋር በመሆን አብዛኛውን የኤርትራ ግዛት ተቆጣጥሮ ነበር፡፡ አሥመራ ባሬንቱ ምፅዋና ዓዲ ቀይህ ከተማ የነበሩትን የአብዮታዊ ሠራዊት አባላት ደምስሶ እነዚህን ከተሞች መቆጣጠር አልቻለም፡፡ በመሆኑም የሃያ ስምንት ዓመታት ምኞቱን ሻዕቢያ በምፅዋ እውን ያደረገበት ቀን የካቲት 9 ቀን 1982 ናት፡፡ ጄኔራል ተሾመ ተሰማ የካቲት 9 ቀን 1982 ዓ.ም ከጠዋቱ 1፡30 ሰዓት ላይ በምፅዋ ከተማ ርዕሰ ምድርዕ በተባለ አካባቢ በከባድ መሳሪያ በፈራረሱ ቤቶች ጥግ ሆነው የተወሰኑ የጦር መኮንኖችንና ባለሌላ ማዕረግተኞችን ሰብስበው ንግግር አደረጉ፡፡ ሻዕቢያ ያለ የሌለ ሃይሉን ተጠቅሞ በእጅ ቦምብና በክላሽ በአሁኑ ሰዓት የከተማ ውስጥ ውጊያ በማድረግ ላይ ነው፡፡ ሻዕቢያ የከባድ መሳሪያ ድብደባ አቁሞ በእግረኛ ብቻ ለመዋጋት አዲስ ተዋጊ ሃይሉን በመኪና እያመላለሰ ዕዳጋ ከተማ ላይ እያከማቸ ነው፡፡ በአዲስ ጉልበት ተዋግቶ ምፅዋን ለመያዝ ቆርጦ ስለመነሳቱ ጥርጥር የለውም፡፡ እኔ የሚፈለግብኝን አደራ ተወጥቻለሁ፡፡ ከጥር 30 ቀን 1982 እስከ ዛሬ የካቲት 9 ቀን 1982 የሞት ሽረት ትግል አድርጌያለሁ፡፡ የሻዕቢያን የጥፋት ዓላማ ለመግታት ያላደረኩት ጥረት የለም፡፡ ከዚህ በኋላ ግን የራስን ሕይወት በክብር ከማጥፋትና ለኢትዮጵያ ጀግኖችና ታሪክ ጸሃፊዎች ታላቅ ተምሳሌት ከመሆን ሌላ አማራጭ የለኝም፡፡ ጀግንነት ማለት በሁሉም መልክ ለጠላት ምቹ ሆኖ አለመገኘት ማለት ነው፡፡ በዚች የኢትዮጵያ ሕዝብ የባሕር በርና ዓለም ዓቀፍ ወደብ በሆነችው በምፅዋ ከተማና በቀይ ባህር ጠረፍ ላይ ቆሜ ሽጉጤን ለመጠጣት ዝግጁ ሆኜያለሁ፡፡ በዕውነት እኔ ዛሬ በሞት ብሸነፍም በታሪክና በመጭው የኢትዮጵያ ትውልድ ፊት አልሸነፍም፡፡ የአፄ ቴዎድሮስን ዕድል በማግኘቴም በጣም እኮራለሁ፡፡ እኔ አሁን የተዘጋጀሁለት ሞት ዘላለማዊ ክብርና ሕይወት ይሰጠኛል ፡፡ በሻዕቢያ ተማርኬ የሻዕቢያን መሪዎች ዓይን ማየት ግን የሞት ሞት ነው፡፡ አፄ ቴዎድሮስ በእንግሊዞች እጅ ወድቀው ከመዋረድ ሞትን መርጠው የራሳቸውን ህይወት መቅደላ ላይ አጠፉ፡፡ እኔ ደግሞ በተራዬ ከኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት የተሰጠኝን የጄኔራልነት ማዕረግ ሳላስደፍር ለመንግስትና ሕዝብ በገባሁት ቃል ኪዳን መሰረት አቅሜ የፈቀደውን ያህል ተዋግቼና አዋግቼ ሻዕቢያን አራግፌያለሁ፡፡ እንደ ጦር መሪም እንደ ተራ ተዋጊም ሆኜ ክላሺንኮቭ ጠመንጃ ይዤ ተፋልሜያለሁ፡፡ አሁን ግን ለመጨረሻዋ መስዋዕትነት ህይወቴን ለማጥፋት የቀሩኝ ጥቂት ደቂቃዎች ናቸው፡፡ ጎበዝ ስሙኝ ይህ የአደራ መልዕክቴ ነገ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ይደርስ ይሆናል፡፡ ምናልባት አምላክ ካለ ከእናንተ አንዱ መልዕክቴን ለኢትዮጵያ ሕዝብና መንግስት ያደርስ ይሆናል፡፡ ዛሬ ሻዕቢያ ምፅዋን ተቆጣጥሬያለሁ በማለት የዓለምን መገናኛ ብዙኃን እንደሚያጨናንቅ ጥርጥር የለውም፡፡ ይህ ደግሞ ለኢትዮጵያ ሀገሬና ሕዝቧ ትልቅ አደጋ ነው፡፡ በቀይ ባሕር በራችን በኩል ብዙውን ጊዜ ወረራ ፈጽመውብናል፡፡ በተደጋጋሚ ያሳፈርናቸውና ፊት ለፊት ያልቻሉን ምዕራባውያን ሀገሮችና ዓረቦች ዛሬ የሻዕቢያን ጊዜያዊ ድል ሰምተው ይፈነጥዛሉ፡፡ ምናልባትም የኢትዮጵያ የተፈጥሮ ድንበር የሆነውንና ለዘመናት በአባቶቻችን የደም ዋጋ ፀንቶ የቆየውን የባህር በራችንን ለመዝጋት እንዲሁም ቀይ ባሕር የኢትዮጵያ ባሕር አይደለም በማለት በምድር ተወስነን እንድንቆይ ይደረግ ይሆናል፡፡ይህ ደግሞ የሞት ሞት ነው፡፡ ይሁን ምንም ማድረግ አልችልም፡፡ ሁሉም ነገር ከቁጥጥሬ ውጪ ሆኗል፡፡ ከሙታን አለም መጥቼ ማረጋገጥ ባልችልም የፈለገ ጊዜ ይጠይቅ እንጂ ጀግናው የኢትዮጵያ ሕዝብ የባህር በር አልባ ሆና በኢምፔሪያሊስቶችና ጋሻጃግሬዎቻቸው ተሸንፎና እጁን አጣጥፎ አይቀመጥም፡፡ ይህ ከሆነማ የአፄ ዮሐንስ የቀይ ባህር ተጋድሎ እና የጀግናው ራስ አሉላ አባነጋ እንዲሁም የኔን ጨምሮ የአብዮታዊ ሠራዊት አባላት ደምና አጥንት የኢትዮጵያን ትውልድ ሁሉ እስከ ዘለዓለሙ ይፋረዳል፡፡ኢትዮጵያ ሀገሬ የጀግኖች መፍለቂያና ገናና ታሪክ ያላት ሀገር ናት፡፡ በመሆኑም ጀግናው ሕዝቧ ሕዝባዊ የባህር በሩ በሻዕቢያ ተይዞና የጠላቶቹ መፈንጫ ሆኖ አይቀርም፡፡ የፈለገ ጊዜ ይቆይ እንጂ ሻዕቢያ ምፅዋን እንደያዛት ለዘለዓለም አይኖርም ጊዜውን ጠብቆ የኢትዮጵያ ጀግና ጠላቱን ደምስሶ ምፅዋን ለኢትዮጵያ ሕዝብ እንደሚያስረክብ እምነቴ የጸና ነው፡፡ አሉና ትንሽም ፋታ ወሰዱ፡፡ የጄኔራል ተሾመ ዓይን የቆሰለ ነብር ዓይን መስሏል ከንፈራቸው በውሀ ጥም ደርቆ ቅርፊት ይዟል፡፡ ፊታቸው በደረቅ ላብ ዥንጉርጉር ሆኗል፡፡ ለረዥም ሰዓታት ከምግብ በመራቃቸው ሆዳቸው ከወገባቸው ተጣብቋል፡፡ በተሰበሰበው አባል ውስጥ በሰፈነው ጸጥታና ዝምታ መሃል እናንተ አብዮታዊ መኮንኖችና ባለሌላ ማዕረግተኞች! ስሙኝ አንድ ምሳሌ ልንገራችሁ፡፡ አሉ ጄኔራል ተሾመ ቆጣ ብለው፡፡ አንድ ሰው ቤት ሲሰራ የሚሰራው ቤት በርና መስኮት አሉት፡፡ አንድ ሰው ደግሞ ሞተ እንበል፡ መቃብሩ በርና መስኮት የለውም፡፡ በርና መስኮት የሕይወት ምልክቶች ናቸው፡፡ በመሆኑም ያለ ሀገር ነጻነትና ያለ ባሕር በር ብልጽግና ስለሌለ የኢትዮጵያ ሕዝብ የባሕር በር ተነጥቆ የሚኖር ሕዝብ አይደለም፡፡ ከሻዕቢያ ጀርባ ሆነው ቀይ ባሕር የኢትዮጵያ አይደለም የሚሉ ሀገሮችና ጋሻጃግሬዎቻቸው ሁሉ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ፍላጎታቸው የኢትዮጵያ ሞት ነው፡፡ ይህ ምሳሌ ከገባችሁ የባሕር በር የሌላት ሀገር ሞቶ ከተቀበረ ግለሰብ የምለየው በትንሹ ነው፡፡ ምክንያቱም የባሕር ሀብት ከማጣቷም በላይ ምርቷን ወደ ውጪ ለመላክ የግዴታ ወደብ ስለምትከራይ ለወደብ ክፍያ የምትከፍለው የገንዘብ ወጭ ዜጎቿን ያደኸያል፡፡ በአኳያው ጠላቶቿንና ባለወደቦቹን ያበለጽጋል፡፡ ይህ ዕድል ለኢትዮጵያ እንዳይደርሳት ቀይ ባሕርን የኢትዮጵያ ትውልድ ይፋረድ፡፡ ቀይ ባህር ለን ዘላለማዊ ቤቴ እንዲሆን ወስኛለሁ፡፡ ደስተኛና እድለኛ ጄኔራል ነኝ እን ብሞት ታሪኬ አይሞትም የእኔ ታሪክ በእንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ህሊና ውስጥ እንደሚኖር እገምታለሁ፡፡ ቻው! ቻው! ማንም ሰው ወደ እኔ እንዳይጠጋ አሉና ጄኔራል ተሾመ መኮንኖቹን ከሰበሰቡበት ቦታ ተፈናጥረው ወደ ቀይ ባሕር ጠረፍ አመሩ፡፡ የባሕሩ ጠረፍ ከስብሰባው ቦታ በግምት ከስልሳ ሜትር አይበልጥም በፍጥነት ወደዚህ ባሕር ጠረፍ ገሰገሱ፡፡ ክላሺንኮቭ ጠመንጃቸውን አቀባብለውና

የመጣው ይምጣ ከሞት ውጪ የሚመጣ የለም ። ነገሩ ከአቅም በላይ ከሆነ ሻዕቢያ ዓይኔን ማየት ቀርቶ ሬሣዬንም አያገኛትም ። እድሜ ለቀይ ባህር ውሃ የቀይ ባህር ዓሳ ይቀብረኛል ። 👇👇👇 @yetor
+1
የመጣው ይምጣ ከሞት ውጪ የሚመጣ የለም ። ነገሩ ከአቅም በላይ ከሆነ ሻዕቢያ ዓይኔን ማየት ቀርቶ ሬሣዬንም አያገኛትም ። እድሜ ለቀይ ባህር ውሃ የቀይ ባህር ዓሳ ይቀብረኛል ። 👇👇👇 @yetormida_welo

#የባረንቱ_ዘመቻ ክፍል ሁለት በአዲሱ አመት መጀመሪያ ላይ ማለትም በመስከረም ወር 1978 ዓ.ም ፕሬዚዳንት መንግስቱ ሀይለማርያም በዘመቻው ዝግጅት ላይ አዲስ ከተሾሙትና ከነባር አዛዥ ጀኔራሎቻቸው ጋር መከሩ። ብዙ ጊዜ እንደሚስማሙ ከጀኔራሎቻቸው በኩል የሚቀርቡትን ሀሳቦች ማጣጣል እንደሚያዘወትሩ የሚነገርላቸው መንግስቱ ምንም እንኳን በአጭር ጊዜ ውስጥ ብዙ መስዋዕትነትን ቢያስከፍልም በዘመቻ ቀይ ባህር በሻዕቢያ ላይ የተገኘው ድል ስላስደሰታቸው ከመቼውም ጊዜ በተለየ ሁኔታ ተለሳልሰው ከዚህ በፊት የታዩ አንዳንድ የአመራር ስህተቶች እንዳይፈፀሙ አጥብቀው በማሳሰብ ጀኔራሎቹ ለዘመቻው ዝግጅት እንዲያደርጉ ያዛሉ። ጀኔራሎቹ አስመራ በግል ጭውውትና በስራ ላይ ሆነው በአሁኑ ዘመቻ የአገሪቱ መሪ እንዳለፈው ጊዜ ጫና ማብዛት የለባቸውም ። እርሳቸው ሀገሪቱን እንደሚወዱ ሁሉ እኛም እንወዳለን። ሁልጊዜ እኛን ለምን አሳንሰው ያዩናል? የመምራት እድሉን ለምን አንዴ እንኳን ለእኛ አይሰጡንም? እያሉ የሚነጋገሩትን አስመራ የሚገኙትና በሁለተኛው አብዮታዊ ሰራዊት (ሁአሠ) ግንባር የወታደራዊ ደህንነት ጥበቃ መምሪያ የበላይ ሀላፊ የነበሩት ብ/ጀኔራል #አለማየሁ_ወልዱ ሰምተው ለመንግስቱ ይነግራሉ። ጀኔራሎቹ ይህ ስሞታቸው በቀጥታ ለፕሬዚዳንቱ እንዲደርስ በመፈለጋቸው ሆን ብለው ይህን መሰል ውይይቶችን ጀኔራል አለማየሁ ፊት ይነጋገራሉ። እባክዎ ጓድ ፕሬዚዳንት በዚህ ዘመቻ ዝግጅት ዕድሉን ይስጧቸው። በትጋት ዘመቻውን ለመምራት አቅደዋል። ሁልጊዜ እኛን ለምን አሳንሰው ያዩናል? እያሉ ነው ስለዚህ እነርሱ ያወጡትን የዘመቻ እቅድ ተመልክተው ማጠናከሪያ በማድረግ ያፅድቁላቸው በማለት በትህትናቸው የሚታወቁት ጀኔራል ዓለማየሁ ያስባሉ። ፕሬዚዳንቱ ጀኔራሎቻቸውን አሳንሶ የማየት የመዝለፍና የማዋረድ ባህሪ ጎልቶ ይታይባቸው እንደነበር ብዙ ሰወች በተለይም የቀድሞ መንግስት ከፍተኛ የሲቪል ባለስልጣናት ይናገሩ ነበር። ይህ የአገሪቱ መሪ ድርጊት ብዙዎችን ያሳዘነና ከጀኔራሎቻቸው ጋርም ከፍተኛ ቅራኔ ውስጥ የከተታቸው ከባድ ስህተታቸው እንደነበር እነዚህ ወገኖች በተጨማሪ ይገልፃሉ። የሆነው ሆኖ ከጀኔራሎቹ በኩል የቀረበው ስሞታ በመጀመሪያ ዙር የቀይ ባህር ኦፕሬሽን ውጤት የተደሰቱትን ፕሬዚዳንት ቅር የሚያሰኝ ሆነ። መንግስቱ እንደ እንቅፋት መቆጠራቸው ቢያሳዝናቸውም ከብዙ ማቅማማት በኋላ በጀኔራል አለማየሁ ሀሳብ ይስማማሉ። በዚህ አጋጣሚ በተፈጠረው ሁኔታ ግን የመንግስቱ አእምሮ እንደተለመደው በጀኔራሎቹ ላይ ቅሬታ ይመዘግባል። እኔን ጣልቃ አትግባ ካሉ ችግር ይፈጠርና አሳያቸዋለሁ!! የሚል ስሜት እንዲይዙም አደረጋቸው። ለዘመቻው የሚያስፈልገው የሰው ሀይል መሳሪያና በጀት ሁሉ በመንግስት ተመደበ። ፕሬዚዳንቱ የአየር ወለድ ጦር ተሳትፎ ታክሎበት የቀይ ባህር ኦፕሬሽን ተከታይ የነበረው #ዘመቻ_ባህረ_ነጋሽ_ፀደቀ እንደተለመደው ሻዕቢያ የመረጃ የበላይነቱን ይዞ የባረንቱ ውድቀቱን ገምግሞ መልሶ መቋቋም አድርጎ በባረንቱ ከባድ ውጊያ የተበታተነውንና የተመታውን ጦሩን በሌላ አዲስ ኋይል ቀይሮ በመጠናከር በጋሸና ስቲት አውራጃ ጦርነት ክንዱ የዛለውን አጥቂውን አብዮታዊ ጦር በተጠናከረ መከላከል መክቶ የመያዝ ስልቱን ነድፎ ይጠባበቃል። አብዮታዊ ሰራዊትም ከዘመቻ ቀይ ባህር ከፍተኛ ድካም ሳያገግምና አካሉን ሳያሳርፍ በሌላ ጦር ሙሉ በሙሉ ሳይቀየር በተሰውትና በቆሰሉት ምትክ ብቻ የሰው ሀይል ተሟልቶለት አሰልቺ የነበረውን የፖለቲካ ትምህርት እየተማረ ቆይቶ በጥድፊያ ለውጊያ ተዘጋጀ። ዘመቻው ተጀመረ በወገን የታሰበው ግብ ላይ ለመድረስ ከፍተኛ ርብርብ ቢካሄድም ሻዕቢያና ናቅፋ አሁንም አልተበገረም። በመጨረሻም የታቀደውና የተፈለገው ውጤት ሳይገኝ ዘመቻው ለመንግስት ከባድ ኪሳራ አስከትሎ ቆመ። ፕሬዚዳንቱ እና ጀኔራሎቹ በዘመቻ ባህረ ነጋሽ ውጤት የተነሳ ዱላ ቀረሽ ውዝግብና ቅራኔ ውስጥ ገቡ። ቀጣይ ጀኔራሎቹ ምን ይገጥማቸው ይሆን? ክፍል ሶስት ይቀጥላል @yetormida_welo @yetormida_welo

ስብሀት ነጋ ከተለቀቀ ምህረት ከተደረገ አንድ ያደረገን መንግስቱ ሀይለማሪያም ለምንድነው ይቅርታ ማይደረግለት እውነት መንግስቱ ከህወሀት የባሰ ነው? ሁላችሁም ሀሳብ ስጡበት #የቀድሞው_ጦር

🔝 የሰው ልጅ እንደ ቅጠል የረገፈበት #የባረንቱ_ዘመቻ መንግስቱ ሀይለማርያም በዚህ ዝግጅት ላይ እንዳሉ በ1977 ዓ.ም ሰኔ ወር መጨረሻ ላይ ሳይጠበቅ ሻዕቢያ በጋሸና ስቲት አውራጃ በተሰማራው የወገን ጦር ይዞታ ላይ ከፍተኛ ማጥቃት ሰንዝሮ የባንንቱን ከተማ ይቆጣጠራል። በጥቃቱ ማግስት እንደተለመደው በሌ/ጀኔራል ተስፋየ ገብረ ኪዳን የተመራ የሰራዊቱ ከፍተኛ አመራር አካላት ያቀፈ አንድ ቡድን አስመራ ገብቶ ቀዳሚ መምሪያውን አቋቋመ በውጭ ሀገር በትምህርት ላይ የሚገኙ አዛዦችና መስመራዊ መኮንኖች አብዛኛወቹ ትምህርታቸውን አቋርጠው ወደ ሀገር ቤት እንዲመለሱ ታዘዘ። በሆለታና በሁርሶ ጦር ት/ቤቶች በስልጠና ላይ ከሚገኙ እጩ መኮንኖች መካከል የተወሰኑት እንድሁም በልዩ ልዩ ማሰልጠኛ ማዕከል ስልጠና ላይ ይገኙ የነበሩ በርካታ ወታደሮች በተመሳሳይ ስልጠናቸውን አቋርጠውና ሌሊት በጨረቃ ብርሐን ተመርቀው በቀናት እድሜ ውስጥ ገስግሰው ኤርትራ ባሬንቱ ግንባር ደረሱ። ከዚህ በኋላ አብዮታዊው ሰራዊት ወድያውኑ በዘመቻ ቀይ ባህር እየተመራ በሻዕቢያ ላይ ከባድ መልሶ ማጥቃት ሰነዘረ። የወገን ጦር የተነጠቀ ይዞታውን ለማስመለስ በከፍተኛ ተጋድሎ ከጠላቱ ጋር ጉሮሮ ለጉሮሮ ተናንቆ ለቀናት ያህል ያለማቋረጥ ተዋጋ። ሻዕቢያ አስቀድሞ በያዘው አመቺ ስፍራ ላይ ሆኖ ባረንቱን ላለመልቀቅ ባደረገው ጠንካራ መከላከል በወገን ጦር ላይ ጉዳት ያደረሰ ቢሆንም የአብዮታዊ ሰራዊትን ያልተቋረጠ ተከታታይ የማጥቃት ጫና ፈፅሞ መቋቋም ስለተሳነው ይዞታውን እስከመጨረሻ ድረስ ጠብቆ ማቆየት አልቻለም። ነሀሴ 18/1977 ዓ.ም ጠላት ባጋጠመው ከባድ ሽንፈት የተነሳ የባረንቱ ከተማን ለቆ እግሬ አውጪኝ ብሎ በመሸሹ አብዮታዊ ሰራዊት ማሳደዱን በሜካናይዝድ ጦር እና በተዋጊ ሄሊኮፕተሮች ታግዞ በመቀጠል የሻዕቢያ ዋና ግምጃ ቤት የሚገኝበትን ሳዋ ፎርቶ የተባለውን ጠንካሬ ይዞታውን ከነሙሉ ድርጅቱ ተቆጣጠረ። በዚህ ወቅትም በርካታ የጠላት ወታደሮች የተማረኩ ሲሆን ለሱዳን ጠረፍ የምትቀርበዋ የተሰነይ ከተማም በዘመቻ ቀይ ባህር አብዮታዊ ሰራዊት ከፍተኛ ተጋድሎ ነፃ ልትወጣ ችላለች። የጠላት ጠንካራ መከላከል እንዳለ ሆኖ በወገን የበላይ አመራር አካላት በኩል በተደጋጋሚ በተከሰተው የተለመደው የአሰራርና የቅንጅት ጉድለት የተነሳ በአብዮታዊ ጦር ላይ ብዙ ጉዳት ቢደርስም ሻዕቢያ በአረፈበት ከባድ ምት ከፍተኛ ተስፋ መቁረጥ አጋጥሞት በመበታተን ነሐሴ 19/1977 ዓ.ም የጋሸናን ስቲት አውራጃን ሙሉ ለሙሉ ለቆ ወደ ትግራይ ሱዳን እና የተፈጥሮ ምሽጉ ወደሚገኝበት ናቅፋ ድረስ አፈገፈገ። በወቅቱ በወገን በኩል የተከፈለው መስዋዕትነት እና የተገኘው ውጤት አይመጣጠንም በማለት በሰራዊቱ ውስጥ ከተለያየ አቅጣጫ ብዙ ቅሬታወች ቀርቦ የነበረ ቢሆንም ዘመቻውንን በበላይነት የመሩትና ያስተባበሩት ጓዶች ግን ምንም ይሁን ምን ሽንፈታቸውን በቆራጡ ተጋድሏችን በድል ተጠናቋል በማለት የተፈጠረውን ቅሬታ ለማለዘብ ሞክረዋል። ከዚህ በኋላ መንግስት በጠላት ላይ የተገኘው ድል ስላረካው የወገን ጦር ሳያገግምና እረፍት ሳያደርግ ከጋሸና ስቲት ወደ ሳህል አውራጃ ናቅፋ ተበታትኖ የሸሸውን ጠላት በፍጥነት ለመደምሰስ የሚያስችል የተጣደፈ የማጥቃት ዕቅድ ነደፈ። በአዲሱ አመት መጀመሪያ ላይ ማለትም በመስከረም ወር 1978 ዓ.ም ፕሬዚዳንት መንግስቱ ሀይለማርያም በዘመቻው ዝግጅት ላይ አዲስ ከተሾሙትና ከነባር አዛዥ ጀኔራሎቻቸው ጋር መከሩ። ፕሬዚዳንቱ የመከሩት ነገር ምን ይሆን ቀጣይ የምናየው ይሆናል.. ይቀጥላል @yetormida_welo

የሰው ልጅ እንደ ቅጠል የረገፈበት #የባረንቱ_ዘመቻ 👇👇 @yetormida_welo
የሰው ልጅ እንደ ቅጠል የረገፈበት #የባረንቱ_ዘመቻ 👇👇 @yetormida_welo

የቃኘው ሻለቃ የቃኘው ሻለቃ ኮርያ ላይ ሄዶ ጠላት ሲያጠቃ ... በኮርያ ጦርነት ወቅት በተባበሩት መንግስታት የ collective security መርህ ጥላ ስር ከክቡር ዘበኛ የጦር ክፍል ተውጣጥቶ ወ
+3
የቃኘው ሻለቃ የቃኘው ሻለቃ ኮርያ ላይ ሄዶ ጠላት ሲያጠቃ ... በኮርያ ጦርነት ወቅት በተባበሩት መንግስታት የ collective security መርህ ጥላ ስር ከክቡር ዘበኛ የጦር ክፍል ተውጣጥቶ ወደ ልሳነ ምድሩ የዘመተው የኩራት የነበረው የአናብስት ስብስቡ #ቃኘው_ሻለቃ *እንኳን በህይወት ያለውን ቀርቶ በጦርነቱ የተሰው አባሎቹን ከከሌሎች ሀገራት በብቸኝነት ያላስማረከ በአውደ ውጊያ ወታደራዊ ብቃቱና ዲሲፕሊኑ በአግራሞትና አድናቆት የሰለጠነውን አለም ያስደመመ *በልእለ ኃያሏ የወቅቱ መሪ ፕሬዝደንት ዱዋይት አይዘናወር ታላቅ አድናቆትና ምስጋና የተቸረው *እሱ በተሰለፈበት ግንባር የነበረውን የኮሚኒስት ቻይናን ጦር ክፋኛ ጎድቶ የደመሠሠው *ከ3500 አጠቃላይ አባላቱ 121 ተሠውተውበት፣ 536 ቆስለውበት ፣ በ0 ምርኮ ወደ ሀገሩ በኩራት የተመለሰው * ...ጀግናው #የቃኘው_ሻለቃ ጦር በፎቶ ሲታወስ... በነገራችን ላይ የ3ኛ ክቡር ዘበኛ የመኮንኖች ማሰልጠኛ ተመራቂ የነበረው የያኔው ወጣት መ/አለቃ የበኃላው የሁአሰ ዋና አዛዥና የአየር ወለድ መስራች መሀንዲስ #ደምሴ_ቡልቶ {ሜ/ጀኔራል} የአናብስቱ ስብስብ የነበረው #የቃኘው_ሻለቃ አባል ነበር ። በተጨማሪም የሜክሲኮ ኦሎምፒክ የማራቶን ሻምፒዮኑ ጀግናው ሻምበል ማሞ ወልዴ ፣ የክራሩ ንጉስ ካሳ ተሰማ እና አርቲስት ተስፋዬ ሳህሉ [አባባ ተስፋዬም] የቃኘው ሻለቃ አባላት ነበሩ ። @Tarikawi_fotowech @Tarikawi_fotowech

#የአልጌና_አንድ_ማስታወሻ ሚያዚያ ወር 1973 ዓመተ ምህረት፡ 90ኛሚሊሺያብርጌድ፡ በፎቶው ላይ የምንመለከታቸው: ከቀኝ ወደግራ… ኮሎኔል ብጹዓን ኪዳኔ የብርጌዱ አዛዥ፣ ሁለተኛው ,የብርጌዱ የፖለቲካ
#የአልጌና_አንድ_ማስታወሻ ሚያዚያ ወር 1973 ዓመተ ምህረት፡ 90ኛሚሊሺያብርጌድ፡ በፎቶው ላይ የምንመለከታቸው: ከቀኝ ወደግራ… ኮሎኔል ብጹዓን ኪዳኔ የብርጌዱ አዛዥ፣ ሁለተኛው ,የብርጌዱ የፖለቲካ ኮሚሣር፣ ሦስተኛው ,የብርጌዱ ዘመቻ መኮንን ሻለቃ ይታገሱ፣ አራተኛ ,የመቶ አለቃ ስዩም ጎርፉ የብርጌዱ መገናኛ መኮንን፡፡ ቀጣዮቹ ሁለቱ የብርጌዱ የሕክምና ክፍል ባልደረቦች ሲሆኑ አንደኛው ሲቪል ነበር፡፡ ከበስተኋላ ቆመው የሚታዩት የብርጌዱ መመሪያ አባላትና የ90ኛው ሚሊሺያ የሚኒቴሪ ፖሊስ ባልደረቦች ናቸው፡፡ኮሎኔል ብጹዓን ኪዳኔ በጦር ሜዳ መሰዋቱን አንዳንድ የተጨበጡ…መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ ምናልባትም ከብርጌዱ መምሪያ አባላት መካከል እንደአዛዣቸው ለኢትዮጵያ ክብር ሲባል በአልጌና በረሃ… በሳህል አውራጃ አንዱ ሰርጥ ውስጥ ወድቀው የቀሩ ይኖሩበታል፡፡ የታሪክ እና የዕጣ-ፈንታ ጉዳይ ሆኖ ግን…የያኔው የፖለቲካ ኮሚሳር ዛሬ በሕይወት አለ፡፡ አንድ ቀን ስላለፈው ታሪክ በአደባባይ ይመሰክር ይሆናል…ሞልቶ ከተረፈው ጤና እና ዕድሜ እግዚአብሔር ጨምሮ ያድለው እንጂ… @Tarikawi_fotowech

#የአልጌና_አንድ_ማስታወሻ ሚያዚያ ወር 1973 ዓመተ ምህረት፡ 90ኛሚሊሺያብርጌድ፡ በፎቶውላይየምንመለከታቸው: ከቀኝ ወደግራ… ኮሎኔል ብጹዓን ኪዳኔ የብርጌዱ አዛዥ፣ ሁለተኛው ,የብርጌዱ የፖለቲካ ኮ
#የአልጌና_አንድ_ማስታወሻ ሚያዚያ ወር 1973 ዓመተ ምህረት፡ 90ኛሚሊሺያብርጌድ፡ በፎቶውላይየምንመለከታቸው: ከቀኝ ወደግራ… ኮሎኔል ብጹዓን ኪዳኔ የብርጌዱ አዛዥ፣ ሁለተኛው ,የብርጌዱ የፖለቲካ ኮሚሣር፣ ሦስተኛው ,የብርጌዱ ዘመቻ መኮንን ሻለቃ ይታገሱ፣ አራተኛ ,የመቶ አለቃ ስዩም ጎርፉ የብርጌዱ መገናኛ መኮንን፡፡ ቀጣዮቹ ሁለቱ የብርጌዱ የሕክምና ክፍል ባልደረቦች ሲሆኑ አንደኛው ሲቪል ነበር፡፡ ከበስተኋላ ቆመው የሚታዩት የብርጌዱ መመሪያ አባላትና የ90ኛው ሚሊሺያ የሚኒቴሪ ፖሊስ ባልደረቦች ናቸው፡፡ኮሎኔል ብጹዓን ኪዳኔ በጦር ሜዳ መሰዋቱን አንዳንድ የተጨበጡ…መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ ምናልባትም ከብርጌዱ መምሪያ አባላት መካከል እንደአዛዣቸው ለኢትዮጵያ ክብር ሲባል በአልጌና በረሃ… በሳህል አውራጃ አንዱ ሰርጥ ውስጥ ወድቀው የቀሩ ይኖሩበታል፡፡ የታሪክ እና የዕጣ-ፈንታ ጉዳይ ሆኖ ግን…የያኔው የፖለቲካ ኮሚሳር ዛሬ በሕይወት አለ፡፡ አንድ ቀን ስላለፈው ታሪክ በአደባባይ ይመሰክር ይሆናል…ሞልቶ ከተረፈው ጤና እና ዕድሜ እግዚአብሔር ጨምሮ ያድለው እንጂ… @Tarikawi_fotowech

የምድር ጦር ጥገና ማሰልጠኛ ሻለቃ የቴክኒክ ተማሪዎች የምረቃ በዓል ሆለታ ገነት የካቲት 1979 ዓ.ም @Tarikawi_fotowech
የምድር ጦር ጥገና ማሰልጠኛ ሻለቃ የቴክኒክ ተማሪዎች የምረቃ በዓል ሆለታ ገነት የካቲት 1979 ዓ.ም @Tarikawi_fotowech

19 ነኛው ተራራ ክፍለጦር አባላት @Tarikawi_fotowech
+2
19 ነኛው ተራራ ክፍለጦር አባላት @Tarikawi_fotowech

#የአልጌናው_ከባድ_የቃኚ_ወታደሮች_ግዳጅ_ክፍል_ስምንት (የመጨረሻው) ለነብስ አድኑ እርዳታ የተንቀሳቀሰው ቡድን አዛዥ መኮንን ከአነጋገሩ ለመረዳት እንደሚቻለው የተፈጠረውን ሁሉ በመስማት አዝኖ ይህንን በሞትና በህይወት መካከል የሚገኝ የቃኚ ጦር ለመታደግ ምንም የሚያግደው ኃይል ያለ አይመስልም። ከለሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ላይ የመቶ አለቃ አይናቸውን ገልጠው ተንጋለው በነበረበት ወቅት ነበር አንድ ከወደ ደቡባዊ አቅጣጫ የሚሰማ ድምፅ እንዳለ የተገነዘቡት ድምፁም የተንቀሳቃሽ ሞተር ድምፅ ለመሆኑ ባይጠራጠሩም ወደ ቀይ ባህር በመጠጋታቸው በባህር ይጓዝ የነበረ መርከብ ድምፅ አንዳንዴ በንፋስ አቅጣጫ ግፊት ወደ በረሀው ይሰማ ስለነበር እሱ ሊሆን ይችላል በሚል ተጠራጠሩ። ብዙም ሳይቆይ ንፋሱ እየገፋውና መቃረብ ሲጀምር የመኪና ለመሆኑ አልተጠራጠሩም። በመገናኛው ሬዲዮ ግንኙነት በማድረግ ሲያረጋግጡ ለእርዳታ የመጣው ጦር በመሆኑ አቅጣጫቸውን ለማመላከት አብሪ ጥይት ወደ ሰማይ ተኮሱ። ከረዳቱ ጦር ለመልስ የሚሆን አብሪ ጥይት ሲተኮስ የሞተር ድምፁ የቀረበ ቢመስልም አብሪው ጥይቱ ትንሽ ራቅ እንዳሉ አረጋገጠላቸው ቢሆንም እርዳታው በአጭር ጊዜ ውስጥ ይደርሳል። ነገር ግን የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀለት ጦር ትእግስትን በማጣት ወደ ተሽከርካሪው አቅጣጫ እየተውተረተረ መንቀሳቀስ ጀመረ። ከዚያ በኃላ በተለይ ከቀዳሚው የእግረኛ ጦር ጋራ የባትሪ ምልክትን እየተለዋወጡ በመጓዝ ተጨባበጡ። አስር አለቃ #አብዲሳ ረዳቱን ጦር እየመራ ስለመጣ በጓዶቹ ወገብና አንገት ላይ በመጠምጠም እንኳን ለዚህ አበቃን እያለ ደስታውን ይገልፅ ነበር። ረዳቱ ጦር በፍጥነት የታደገውን በውሃ ጥምና በጉዞ የተጎሳቆለ ጦር ትጥቅ በመፍታት በቀጭኑ የተበጠበጠ በሶ ማደል ጀመረ። የተሰጣቸውን በሶ ለመጠጣት በመጓጓት ወደ ጉሮሮዋቸው ለማውረድ ቢሞክሩም በአጠቃላይ ማለት ይቻላል በቁስል ላይ አልኮል የፈሰሰበት ያክል አይነት ጎሮሮዋቸው በመቃጠሉ ህመሙን በመቋቋም ለመጠጣት ተሳናቸው። አብዛኛዎቹ በሶውን በመተው ውሃ እንዲሰጣቸው በመጠየቅ ውሃውን ሲጠጡት እንደበሶው አይነት ስቃይ ስላልነበረው እሱን መረጡ። ትንሽ ከተረጋጉ በኃላ ነበር ይሙቱ ይኑሩ ወደማይታወቀው የተቀሩት አባላት ለመንቀሳቀስ ዝግጅት የተጀመረው። ነገር ግን አንድ ችግር ተፈጠረ ወደ ኃላ በተሽከርካሪ መጓዝ አደጋ ስላለው ከረዳቱ ጦር ጋር አቅጣጫውን የሚጠቁም አንድ ሰው አብሮ መጓዝ ይጠበቅበታል የትኛው ጠንካራ ወታደር ነው አቅም ኖሮት በመጓዝ ጓዶቹን የሚታደገው? ይህ የማይታሰብ በመሆኑ ለእርዳታ የመጣው ጦር ጠንካራ ወታደሮችን መርጦ አቅጣጫ ተጠቁመው ጉዞ ጀመሩ። ተንቀሳቃሹ ጓድ ከመቶ አለቃ ጋር ቀጥተኛ የሆነ የሬዲዮ ግንኙነትን በማድረግ ሲጓዝ አድሮ ረፋዱ ላይ ቦታው ላይ ደርሶ ወታደሮቹን እያፈላለገ መሆኑን የሬዲዮ መልእክት አደረገ። አሁን ጥያቄው በህይወት ያገኟቸው ይሆን?! ጭንቁ እሱ ሆነ በድጋሚ ሌላ የደስታ መልዕክት መጣ ሁለት ወታደሮች ተገኝተዋል የቀሩትስ? በውሃ ጥም ሞቱ ቀጣዩን መጠበቁ አስጨናቂ ሆነ ሲጠበቅ የነበረው መልእክት በድጋሚ መጣ ወታደሮቹ አፍና ጎሮሮዋቸው ቆስሎ በጣር ላይ ይገኙ ነበር። በመልሱ ጉዞ ሁሉንም በህይወት ይዞ መግባት ሳይቻል ቀርቶ አንድ ተጨማሪ ወታደር ህይወቱ አልፎ አስከሬኑን እንኳን ቢሆን ተሸክመው ተርፈው በጉጉት ይጠብቁ ከነበሩት አባላት ጋር በመሆን ለመቆበር በማሰብ ጉዞ ቢጀምሩር ከአየሩ ፀባይ አንፃር አካሉን ተሸክመው በማይጓዙት መልኩ እየተቀየረ በመምጣቱ ሊቀብሩት ተገደዱ። የቡድኑ መሪ የያኔው ም/መ አለቃ(ሻለቃ) #ማሞ_ለማ ዛሬም በህይወት ይገኛሉ። በቀጣይ ስለ ጀግናው ሻለቃ ማሞ ታሪክ እንመለስበታለን!! ስለ አንዲት እናት ሀገር ኢትዮጵያ የተሰዋችሁ እናንተ ጀግና የሰራዊታችን አባላት ስለከፈላችሁት መስዋእትነት እናመሰግናለን!! @yetormida_welo

#የአልጌናው_ከባድ_የቃኚ_ወታደሮች_ግዳጅ_ክፍል_ሰባት ከብርጌድ አንድ አስቸኳይ መልዕክት መጣና ለመቆም ተገደዱ። መልዕክቱም ሁኔታውን በቅርብ ይከታተል የነበረው ብርጌድ ከፍተኛ ስጋት ስለገጠመው አሁን የሚገኙበት መልክዓ ምድር ምቹ ስለሆነ ሊታደጋቸው የሚችል አንድ በብረት ለበስ የተጠናከረ ኃይል ስላነቃነቀ በካርታ ቦታችሁን አሳውቁንና የት ድረስ መጥቶ እንደሚቀበላችሁ እናመቻቻለን ነበር። በተጠየቀው መሰረት መረጃውን ስጡ ደርሶ ይጠብቃችኋል የተባለበትን ቦታ በካርታ ሲመለከቱ አሁን ከሚገኙበት ቢያንስ የአንድ ቀን መንገድ ይሆናል ሁኔታው ተስፋ ሰጪ ቢሆንም ከነበረው የውሃ ችግር አንፃር እንዴት ነው በዚህ በረሃ የተዳከመው ጦር የሚጓዘውና እራሱን በማዳን ቀሪዎቹን የሚታደገው?! ይህ እውነታ ቢኖርም መጓዙ የግድ ነበር። ተስፋን ሰንቀው ቢጓዙም ፊታቸው ገርጥቶ ከሰውነታቸው የሚመነጨው ላብ ጨውነትና አሸዋው ተዳምሮ ነጭ አመድ ለብሰዋል። ያፍ መድረቅ ብቻ ሳይሆን ላንቃና ምላሳቸው ተጣብቆ መቁሰልን ስለጀመረ መናገር እራሱ ህመም ስላለው የግድ ካልሆነ መናገር የሚፈልግ አልነበረም። የሚነኩትም ሆነ የሚረግጡት አሸዋ ሸክ ሸክ ሲልና ትጥቅና መሳሪያ ሲንገጫገጭ እየሰሙ በማለክለክ ነበር የሚጓዙት። አያድርገውና በዚህ አይነት ከጠላት ጋር ቢገጣጠሙ እንዴት አድርገው ሊዋጉ እንደሚችሉ መገመቱ ይከብዳል። ደግነቱ ለጊዜው ትግሉ ከተፈጥሮ ጋራ ብቻ ነበር መጪው ግን አይታወቅም?! ለማረፍ መሞከሩ በበረሀ መበላትን ስለሚያስከትል ያለው ብቸኛ አማራጭ የነበረውን ተስፋ ሰንቆ መጓዝ ብቻ ነበር። የደከሙት ወታደሮች ላለመውደቅ ጥረትን ቢያደርጉም ሞተሩ እንደነከሰ መኪና ትንሽ ጠንከር ባሉ ጓዶቻቸው ሲጎተቱ ማየቱ እንዴት ተስፋ ያስቆርጣል። የቃኚው ቡድን መሪ የሚመሩትን ጓድ ተስፋ ላለማስቆረጥ የበረቱ ቢመስሉም ሁኔታውን በቅርብ ለተከታተለ ከአቅማቸው በላይ መሆኑን ለመረዳት አያዳግትም ነበር። ይህን የተረዳው የመቶ ሃምሳ አለቃው(አስር አለቃ አብዲሳ)በድንገት ወደ አጠገባቸው ቀረብ ብሎ "ጌታዬ ትጥቅዎን ልርዳዎ" አላቸው። ይህን ሲል በድርቀት የተጣበቁ ከንፈሮቹን ለማላቀቅ ሲቸገር ይስተዋል ነበር። የመቶ አለቃ ታወቀብኝ ብለው "ምነው እሱም ይወድቃል ብለህ ፈራህ እንዴ" ብለው በለሁሳስ ጥያቄን ሲያቀርቡ በውስጣቸው" ይገርማል በዚህ አይነት ሁኔታም ውስጥ ጉልበት ኖሮት ለማገዝ ጥያቄን ያቀረበ ጓድ በመኖሩ እየተገረሙ ነበር"! ይህን የሰማ አንድ ወታደር ቀረብ ብሎ መሳሪያቸውን ለመቀበል እጁን ሲዘረጋ"ደህና በጣም የደከመውን ስለምትረዳ ተወው" ብለው ደህና እንደሆኑ ለማስመሰል ከሞከሩ በኅላ በዚህ መልኩ መጓዝ ስለማይቻላቸው ቦታን መርጠው ትንሽ ማረፍ እንደሚገባቸው በማሰብ ላይ በነበሩበት ሰዓት ነበር የተኩስ ድምፅ የተሰማው። የባሰ አታምጣ ምን ተፈጠረ ደግሞ?! አንድ ተስፋ የቆረጠ ወታደር ነበር ምንም ምልክት ሳያሳይ ቆም ብሎ እራሱን በአሰቃቂ ሁኔታ የሰዋው። የመቶ አለቃን ወታደሩ የወሰደው እርምጃ ሌሎቹንም ተስፋ አስቆርጦ ወደ ተመሳሳይ ሁኔታ ውስጥ እንዳይከታቸው ሀሳብ ውስጥ ገቡ። ሁኔታው በቡድኑ ተስፋ ላይ ጥላውን አጠላበት። በጊዜያዊነት ካረፉበት ቦታ ሆነው አመቺ ጉብታን መርጠው ለእርዳታ መጣ ከተባለው ኃይል ጋር የሬድዮ ግንኙነት ለማድረግ ሙከራ ቢያደርጉም አልተሳካም። እራሱን የሰዋውን ወታደር በካርታ ነጥበው በመቅበር ከብርጌዱ ጋር ግንኙነት በማድረግ ሊታደጋቸው የመጣው ጦር ወደ እነርሱ እየተጓዘ መሆኑን አረጋገጡ። በተደረገላቸውም የካርታ ጥቆማ መሰረት ወደ ምስራቅ እያሰፋ እንደሆነ የሚጓዘውን ለመገንዘብ ቻሉ። የመቶ አለቃ ጠንካራውን የመቶ ሃምሳ አለቃ አብዲሳን ከሌላ ጠንካራ ጓድ ጋር አጋዡ እየመጣ ነው ወደ ተባለበት አቅጣጫ በመላክ የተላኩት መልዕክተኞች ችግር ካልገጠማቸው ተገናኝተው ሲጨባበጡ የሬዲዮ መልዕክት ስለሚደርሳቸው ይህንኑ በጉጉት መጠባበቅ ጀመሩ። ሰአቱ የቆመ ቢመስልም ከረጅም ጥበቃ በኅላ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የሬዲዮ መልዕክት መጣ መልዕክተኛው ጓድ ተመስገን ተጨባብጧል። ለእርዳታ የተነቃነቀው ጦር አዛዥ "አንበሶቼ እናንተ ብቻ በርቱልኝ እንጂ መልዕክት ይዘው የመጡት ጓዶች እየመሩኝ እናንተው ድረስ እመጣለሁ"አለ! በቅርብ በሚደርስላቸው እርዳታ እነርሱ ለመትረፋቸው ተስፋ ሰጪው ብርሃን ፈነጠቀ። ይህ የተስፋ ብርሃን እውነት ይሆን? አሁን ጥያቄው ደግሞ በጠባቂ ጥለዋቸው የመጡት የታመሙ ጓዶች በህይወት ይቆይዋቸው ይሆን? ክፍል ስምንት ይቀጥላል ..... #ክብር_ለተሰዉ_አብዮታውያን_ጓዶች!! @yetormida_welo @yetormida_welo

እንኳን አደረሳችሁ። መልካም የገና በዓል! Ethiopian Army band back in 1988 G.C @Tarikawi_fotowech @Tarikawi_fotowech

#የአልጌናው_ከባድ_የቃኚ_ወታደሮች_ግዳጅ_ክፍል_ስድስት አንድ ወታደር በውሃ ጥም ላንቃው ተጣብቆ ተዘርሯል። ውሃ ከየት ሊመጣ? ወታደሩ በውሃ ጥም ላንቃው ተጣብቆ ስቃዩን እያየ ቢገኝም በቅርብ የሚገኙት ጓዶች ትጥቁን በመፍታች የሸሚዙን ቁልፎች በመከፋፈት አየርን እንዲያገኝ እየረዱት ይገኛሉ። የመቶ አለቃ ኮዳቸው ውስጥ የቀረችውን ጭላጭ ውሃ በመክደኛው በማንቋረር ላንቃውን ለማራስ ሞከሩ ሆኖም እራሱን የሳተው ወታደር ከገባበት ሰመመን ሊነቃ ባለመቻሉ ግዜን ላለማጥፋት በማሰብ የጓዱ ወታደሮች ተራ በተራ እየተሸከሙት ለመጓዝ ተገደዱ። ከቆሙበት ጋር ሲታሰብ የሸክሙ ጉዞ ፍጥነታቸውንም ሆነ ግዜን ከመውሰዱ በተጨማሪ ከፍተኛ ድካምን ፈጠረ። ይህ ሁኔታ በሌሎችም ወታደሮች ላይ ተመሳሳይ አደጋን እንደሚፈጥር የተረዱት የመቶ አለቃ ለብርጌዳቸው ስለ ሁኔታው ሪፖርት አደረጉ። የሚጓዙበት አካባቢው ከትናንሽ ጉብታዎች በስተቀር ከለላ የሚሆን ነገር የለውም። ጎህ ቀዶ ፀሃይዋ ከመጠንከሯ በፊት የመዋያ ስፍራን በማፈላለግ አዘጋጁ። ሰመመን ውስጥ የነበረው ወታደር በመሀከል እየቃዠ እባካችሁ መሳሪያዬን ስጡኝ ወይም ጨርሱኝ ይል ነበር!አሁን ግን ካረፉ በኅላ ሙሉ ለሙሉ ለመንቃት ችሎ ጭላጭ ውሃ የነበራቸው ሁሉ አጠረቃቅመው ስኳር በመበጥበጥ ኃይልን እንዲያገኝ ጥረት ተደረገ በእውነት ፊቱን ሲመለከቱት የመገርጣት ምልክት ስለሚታይበት ይህ ወታደር እራሱን ችሎ በእግሩ ይሄዳል ብሎ ለመገመት ያዳግታል። ሁኔታውን በጥሞኖ ቆሞ ይከታተል የነበረው ቀልደኛው የጓዱ መሪ #የሐረሩ_ወታደር_አሊ ፈጣሪውን በመማፀን አይነት"እዚህ አለን በቂ ጣጣ አቦ አላህ ሌላ አታምጣ"ብሎ የተቀሩትን ጓዶች ፈገግ እንደማለት አሰኛቸው። ፀሃይዋ በስተምስራቅ ባለው ተራራ መጥለቅ ስትጀምር ለጎዞ በመሰናዳት የታመመው ወታደር በሁለት ሰው ተደግፎ እየተውተረተረ መራመድ ችሎ ጎዞዋቸውን ቀጥለው እስከ ለሊቱ ስምንት ሰአት በመጓዝ አብዛኛው ሰው ስለተዳከመ ለማረፍ ተገደዱ። ቀድመው ለብርጌዱ ባቀረቡት ሪፖርት መሰረት የተጨነቁት የብርጌድ ኃላፊዎች ስለሁኔታው ለመረዳት በተደጋጋሚ ጥያቄዎችን ያቀርባሉ። ሁኔታውም ይዘውት የነበረውን የመገናኛ ሬዲዮ ባትሪ ሊጨርሰው ስለሆነ በሰዓት በቀጠሮ ለመገናኘት ወስነው ሬዲዮናቸውን አጠፉ። ከትንሽ እረፍት በኅላ ዳግም ጉዞን ጀምረው ንጋት ላይ እንደተመካከረ ሁለት ወታደሮች እራሳቸውን ስተው ጠብ ጠብ አሉና ጎዞው ተገታ። ጉልበት ሰጪው መድሃኒት በሶና ስኳር ነበር እሱም ደግሞ ውሃን ይፈልጋል? ምን ይሻል ይሆን? ስኳሩን እንኳን አፋቸውን በመክፈት ለመጨመር የሚቻል ቢሆንም ምራቅ ከሌለ እንዴት ይሟሟል? አይ ፈተና!እንግዲህ ሶስት ሰው ተሸክሞ መጓዝ ስለማይቻል በጓድ መሪዎች በመከፋፈል እራሳቸውን የሳቱትን ወታደሮች ከታማሚው ጋር በጠባቂ አስቀምጦ መጓዝ ቢጀመርም ብዙም ሳይጓዙ ለመቆም ተገደዱና ሁሉም በያለበት አረፉ። መቶ አለቃ ለአስር ደቂቃ ያህል አረፍ ካሉበት ለመነሳት ሙከራ ሲያደርጉ ጉልበታቸውም ሆነ ቋንጃቸው ሰውነታቸውን መሸከም አቅቶት መውተርተር ሲጀምር አለቀልኝ እኔው እራሴ አራተኛው ሰው መሆኔ ነው ብለው ደነገጡ። በዚህ ሁኔታ ላይ እያሉ ነው "እባክህን ፈጣሪዬ በዚህ ሁላ ሰው ይሁንብህ ብርታቱን ስጠን" በማለት የፀለዩት! በዚህ አይነት መልኩ ተጉዞ የመትረፍም ሆነ ታመው ከበስተኅላ ጥለዋቸው የመጡትን አባላት መታደግ እንደማይችሉ ስለተረዱ በመሰባሰብ ጠንከር ያሉት አባላት በቅድሚያ ሌላው ደግሞ ከበስተኅላ በመጓዝ በቅርብ ከሚገኝ የወገን ጦር ጋር ለመቀላቀልና ለመሰባሰብ ወሰኑ። እየወደቁ እየተነሱ በዚህ አይነት ሁኔታ እየተጓዙ ነበር ይጥፋ ተብሎ የነበረው የመገናኛ ሬዲዮ ሳይጠፋ ተረስቶ ኖሯል ከብርጌድ አንድ አስቸኳይ መልዕክት መጣና ለመቆም ተገደዱ። ምን ይሆን የመጣው መልዕክት? ቀጣዩን እንመለከታለን፦ ክፍል ሰባት ይቀጥላል... #ክብር_በሰሜን_ተራሮች_መስዋዕት_ለሆኑ_አብዮታውያን_ጓዶች!!! @yetormida_welo @yetormida_welo

#የአልጌናው_ከባድ_የቃኚ_ወታደሮች_ግዳጅ_ክፍል_አምስት እነርሱ ወዳሉበት ከመምጣታቸው በፊት ወደ ታች ለመውረድ እንቅስቃሴ በማድረግ ለመገናኘት ቢችሉም ሁለት ብቻ ነበሩ አንዱስ የሚል ጥያቄን ሰነዘሩ ተሰውቷል የሚል ምላሽን አገኙ። በወቅቱም ስለተፈጠረው ሲያስረዱ አካላቸውም ሆነ መንፈሳቸው በጣም መጎዳቱን ለመደበቅ አልቻሉም። በተገኘው መረጃ መሰረት በጠላት ከበባ ውስጥ ሊወድቁ ስለሚችሉ በመሰበጣጠር ከፍተኛ ጥንቃቄን አድርገው ከጠላት ጋር ድብብቆሹን ያለ ምንም ስህተት መፈፀም ይገባቸዋል። በዚህ አነስተኛ የጠላት ቃኚ ኃይል ላይ አደጋ መጣል አመቺ ሁኔታ ላይ ቢገኙም ከጥቅሙ ግን ጉዳቱ ሊያመዝን ስለሚችል መሰወሩን መርጠው የቃኚውን ኃይል እንቅስቃሴ በጥንቃቄ መከታተል ጀመሩ። ለመረዳት እንደቻሉትም ኃይሉም በአካቢው እንዳሉ ላለመረዳቱ አመላካች ሁኔታዎች ነበሩ። ምክንያቱም ጉዞም ገዢ መሬቱን ይዞ እነርሱ ወዳሉበት አቅጣጫ በቀጥታ ይጓዙ ስለነበሩ ስለመኖራቸው ጥርጣሬ እንዳልነበረው ያረጋግጣል። አሁን እየሆነ ያለው የጠላት ቃኚ ጦር ወዳደፈጠው ጦራችን ደርሶ እስኪፋጠጥ የጭንቅ ሰአት ሆነ። በቅርበት አድፍጦ ወደ ነበረው ጓድ ሁለት የጠላት ቃኚዎች ቀረቡ አማራጭ ስለጠፋ መተኮስ ግድ ሆነና ያደፈጠው የጓድ ጦር ሁለቱን እጅ ወደ ላይ ብሎ ለመማረክ ቢሞክርም እንቅስቃሴን በማድረጋቸው ተመተው ወደቁ። በዚህ አይነት መልኩ መሸሸጉ ውጤት ስለማያመጣ የቦታ ለውጥን በፍጥነት እያደረጉ መታኮሱ የግድ ሆነ። ተኩሱ ተፋፋመ የጠላት ኃይል እየተበራከተ በመምጣቱ የመልስ ጉዞአቸውን አደገኛ ቢያረገውም ወደ ደቡባዊው አቅጣጫ እየተታኮሱ ማፈግፈግን ተያያዙት። ወደ ደቡባዊ አቅጣጫ ማፈግፈጋቸውን የተረዳው ጠላት መታኮሱን አቁሞ መውጫ ይሆናቸዋል ብሎ ያሰበውን ሙት መሬት እየዘጋው እንደሆነ ለመረዳት ቻሉ። ይህ የጠላት ውሳኔ ከመከበብ ቢያድናቸውም በቀጣይ ከባድ ፈተና ይዞ ነበር የመጣው። ያለመከበባቸውን ከተረዱ በኃላ ተሰባጥረው ካፈገፈጉበት ተራራ በመውረድ ለመጓዝ በመሰባሰብ ላይ በሚገኙበት ወቅት ከወገን አቅጣጫ ለመሆኑ እርግጠኝነቱ የማያጠራጥር አንድ የተኩስ ድምፅ ተሰማ መሳሪያ ባርቆ ካልሆነ ሌላ ምን ሊሆን ይችላል? ይህ ደግሞ አደገኛ ነው! እንዴትስ ሊፈጠር ቻለ በሚል የመቶ አለቃ እያሰላሰሉ በሚገኝበት ወቅት አንድ የቃኚው ጦር አባል ሁኔታውን ለማጣራት ወደ ስፍራው በማቅናት ትንሽ ቆይቶ በከፍተኛ የሀዘን ስሜት ተመለሰ። ምን ተፈጠረ? ቁስለኛው ወታደር ማቲዮስ እንደልብ ሊንቀሳቀስ ባለመቻሉ በእርሱ ምክንያት ጦሩ አደጋ ላይ እንዳይወድቅ በማሰብ እራሱን አጥፍቶ ነበር። የመቶ አለቃ ለጓዱ መሪ እንዴት ቁስለኛው መሳሪያ አግኝቶ እራሱን ሊያጠፋ ቻለ በሚል ቁጣን የተላበሰ ጥያቄ አቀረቡ ሁኔታውን ለመረዳት ሲሞክሩ ግን ጉዳዩ እንዲህ ነበር። ተሰባጥረው እየተታኮሱ በተሸሸጉበት ወቅት ቁስለኛው ከአንዱ ወታደር ጋር በመሆን ነበር የተሸሸገው ወታደሩም እየተከበቡ ስለመሰለው ጋብ ያለው ተኩሱ ከቀጠለ ቁስለኛውንም ሆነ እራሱን ለመከላከል ጊዜያዊ ምሽግ ለማዘጋጀት መሳሪያውን አስቀምጦ ተለቅ ያሉ ድንጋዮችን ከቅርብ እየሰበሰበ ከለላውን በሚያዘጋጅበት አጋጣሚ ነበር ወታደር ማቲዮስ መሳሪያውን ለቀም አድርጎ "እኔን ብላችሁ እናንተ ከአደጋ ላይ ከምትወድቁ በፍጥነት እንድትንቀሳቀሱ ይረዳችኅል" የሚለውን ተናግሮ እራሱን ያጠፋው። ወታደሩ እራሱ የገደለው እስኪመስል የፀፀትና የመረበሽ ምልክት ስለታየበት የመቶ አለቃ የሆነው ሆኗል ከአሁን ወዲህ እንዲህ አይነት ስህተት እንዳይፈፀም በሚል ማስጠንቀቂያን ሰጡ። በፍጥነት የወታደር ማቲዮስን አስከሬን ማስ ማስ በማድረግ አፈር አለበሱ። አጅማ አካባቢ የመጣው ወታደር ማቲዮስ የ28 ዓመት ወጣትና የሦሥት ልጆች አባትም ነበር። ቀደም ሲል ለተወሰነ ጊዜ ከባለቤቱ የሚመጣ ደብዳቤ ይደርሰው ነበር። ከጊዜ በኅላ ግን እሱ ሳያቋርጥ ቢፅፍም የቤተሰቡ የሚመጣ ምላሽ አልነበረም። ስለ ቤተሰቡ ሁኔታ መስማት ካቆመ አራት አመት ሆኖታል። እንዲህ አይነቱ ሁኔታ በሰራዊቱ ውስጥ የተለመደ ነገር ነበር። ለዚህም ዋነኛው ምክንያት ያልተቋረጠ ጦርነት ለረጅም አመታት በመካሄዱ ቤተሰብ በሁኔዛው ተስፋ ወደ መቁረጥ እየመጣ ነበር። ካሉበት ሆነው ደንገዝገዝ ስላለ ጨለማውን ተገን አድርገው ለመጓዝ ተዘጋጁ። ጉዟቸው ሊሆን የሚገባው አንድ አብሪ ጓድ አስቀድመው ሳይለያዩ እየተናበቡ የሚመጣውን ኃይል ለመፋለም ተነጋግረው ያለ ምንም አይነት ድምፅ በምልክት ብቻ እየተግባቡ መጓዝ ጀመሩ። በጉዞውም ወቅት ከጠላት ጋር ተቀራርበው ስለሚገኙ አብሪዎቹ አካባቢውን እየቃኙ ምልክት እስከሚሰጡ ድረስ ከኅላ የሚገኘው ኃይል ለመጠበቅ ስለተገደደ ሁኔታው የጉዞአቸውን ፍጥነት ገታው። በዚህ መልኩ እስከ ንጋት ከተጓዙ በኅላ ጎህ ከመቅደዱ በፊት ወደ ሜዳማው ክፍል መቃረባቸውን ስላረጋገጡ በቅርብ ወደ ሚገኙ ጉብታዎች ለሁለት በመከፈል እረፍት አደረጉ። ከነበሩበት ቦታ ለፀሃይ ከለላ የሚሆን ነገር ባለመኖሩ ሙቀቱ አሁንም አሁንም ውሃ አምጡ ስለሚል በአጠቃላይ ማለት ይቻላል የነበራቸው የኮዳ ውሃ ተገባዷል። ከዚህ በኅላ የሚደረገው ጉዞ ጠላት ላይኖርበት ይችላል ብለው በመገመት የመረጡት ሜዳማና አሸዋማውን ክፍል ስለሆነ ውሃ ለማግኘት አይቻልም። የሆነው ሆኖ መጓዝ ስለሚገባቸው ማምሻውን ጉዞ ጀምረው እስከ እኩለ ለሊት በመጓዝ እጅግ አስቸጋሪ በሆነው ከሸማማ መሬት ላይ በሚገኝበት ወቅት ነበር አንድ መልዕክት ከበስተኅላ የመጣው ሁሉም መልዕክቱ ምን እንደሆነ ለመረዳት ቆም ካሉ በኅላ የመቶ አለቃ ወደ ቦታው በመቅረብ ሁኔታውን ለማረጋገጥ ሞከሩ። አንድ ወታደር በውሃ ጥም ላንቃው ተጣብቆ ተዘርሯል። የተዘረረው ወታደር ይተርፍ ይሆን? የተቀሩትስ ምን ይገጥማቸዋል ለሚለው መግቢያው ላይ ወታደር አሊን"እዚህ አለን በቂ ጣጣ........."ያሰኘው መራር ጉዞ እንመለከታለን፦ ክፍል ስድስት ይቀጥላል .... ዘላለማዊ ክብር በሰሜን ተራሮች ለመደቁ የሰራዊታችን አባላት!! አፍ አውጽእ ተዛረብ ጉና ተራራ ጉና ተራራ !! @yetormida_welo @yetormida_welo

#የአልጌናው_ከባድ_የቃኚ_ወታደሮች_ግዳጅ_ክፍል_አራት የፀሐዩ ሙቀት ሲያይል ደግሞ በዚህ አይነት መልኩ ፍለጋቸውን ማድረግ ስለማይችሉ የመቶ አለቃ ይህ ከመሆኑ በፊት አንድ የመጨረሻ ውሳኔ ወሰኑ በአካባቢው ከሚገኙ ተራሮች አረንጓዴ ቅጠል ምልክት በብዛት ወደ ሚታይበት ተራራ በማምራት ሸጡን ተከትሎ ድንጋይ ላይ ታቁሮ የቀረ ውሃን ለማግኘት አሰሳቸውን ጀመሩ። ወደ ተራራው በመጠጋት ሸጡን ተከትለው ሲሞክሩ የቦታው አቀማመጥ ገደል ስለሆነባቸው እንደምንም እየባጠጡ ወደ ተራራው ወገብ ለመድረስ ችለው በድንጋይ ንጣፍ የተሞላውን የውሃ መውረጃ ሲመለከቱ ትላልቅ ዛፎች እንደሚገኙ ለመመልከት ቻሉ። የዛፎቹም ጫፍ ልምላሜ ስለሚታይበት ተስፋ ሰጪ ስለሆነ እየባጠጡ ወደ ስፍራው በመቅረብ አካባቢውን መቃኘት በጀመሩ በጥቂት ቆይታ ውስጥ አንድ በውሃ መውረጃው የድንጋይ ንጣፍ ላይ ጥቂት የታቆረ ውሃን ለማግኘት ቻሉ። በዚህ አይነት ሌላም ተጨማሪ የታቆረ ውሃ ሊኖር ይችላል በሚል ግምት ጥቂት ፍለጋን ካካሄዱ በኃላ ከግዜውና ከነበረው አደጋ አንፃር ይህንኑ የተገኘ ውሃ በመታቆሩ በአረንጓዴ መሳይ ነገር ቢሸፈንም ሰፈፉን በመግፈፍ ውስጡ የደፈረሰን ውሃ ለመጠቀም ወሰኑ። ውሃው መደፍረስና መጥቆሩ ባልከፋ። ነገር ግን በትናንሽ የውሃ ትል የተሞላ ነበር። ውሃውን እየቀዱ ወደ ኮዳቸው በሽርጥ በማጥለል አንቆርቁረው በውሃ ጥም የደረቀ ጎሮሮዋቸውን በማራስ ለጉዞ የሚሆናቸውን እያጠለሉ ወደ ተቀሩት የቡድኑ አባላት መልዕክተኛ በመላክ ወደ እነርሱም መጥተው ኮዳቸውን እንዲሞሉ ለማድረግ ተሞከረ። ውሃው በቂ ስላልሆነ ከተሞሉት ኮዳዎች በማቀናነስ እንዲዳረስ ተደርጎ አንድ ሙሉ ኮዳ ለቁስለኛው እንዲሰጥ ተደረገ። በሌላ አቅጣጫ ውሃ ለመፈለግ የወጡት ጓዶች ደብዛቸው ጠፋ ምን ተፈጠረ ቦታ ስተው ይሆን? ወይስ በጠላት እጅ ወደቁ? የሚለው ጭንቀት በመቶ አለቃ አዕምሮ እየተመላለሰ ያቃጭል ጀመር። የመቶ አለቃ በጭንቀት በተደጋጋሚ የእጅ ሰአታቸውን ቢመለከቱም የተወሰነው ሰዓት አለፈ። የሬዲዮ ሰራተኛው ለብርጌዱ የተፈጠረውን ለማሳወቅ መልዕክት ልኮ መልስ ይጠባበቁ ጀመር። የመጣውም ምላሽ ተንቀሳቀሱ የሚል ነበር። እንዴት አድርገው ነው የጠፉትን ጓዶች መጨረሻ ሳያውቁ የሚንቀሳቀሱት? ትዕዛዙን በመጣስ ለአንድ ሰዓት ያክል ከቆዩ በኃላ በደቡባዊው ምዕራብ አቅጣጫ የተኩስ ድምፅ ተሰማ። ተኩስም ደመቅ እያለ ግጭት ለመሆኑ አመላካች እየሆነ መጣ። የተኩሱ አቅጣጫ እሩቅ በመሆኑ በዚህ ሰዓት ቦታን ካልሳቱ እዚያ ሊገኙ አይችሉም ነበር። ሁኔታውን በመከታተል ላይ እንዳሉ ጠፍተው ከነበሩት መካከል አንዱ የቃኚው ጦር አካል አጠገባቸው ደረሰ። በዚህ አይነት የተቀሩት ሶስት አባላት ነበሩ የሚታኮሱት ማለት ነው። ሲያስቡት ሶስት ሰው እንዴት ከእንዲህ አይነት ተኩስ መሀከል ይወጣል የሚለውን ካሰቡ ተስፋን ያስቆርጣል። ለመረዳት የቻሉት አንድ ነገር ቢኖር እነዚህ ልምያ ያላቸው የቃኚው ጦር አባላት ጠላትን እነርሱ ወዳሉበት ቦታ ላለመምራት ነበር ማለት ነው ወደ ሌላ አቅጣጫ ጠላትን አርቀው የወሰዱት። መጨረሻውን እስከሚያውቁ ለመቆየት ወሰኑ። ከብዙ የተኩስ ልውውጥ በኃላ ፀጥ እረጭ አለ። አካባቢውን በመቃኘት እነርሱም የቦታ ለውጥ ማድረግ እንደሚገባቸው ለመወሰን በተዘጋጁበት ወቅት በቅርብ እርቀት በሚገኝ ገዢ መሬት ላይ ከፍተኛ የሆነ የጠላት እንቅስቃሴ መታየት ጀመረ። ይህ የጠላት አሳሽ ጦር አሰሳውን ከጀመረ እንደ እንቅስቃሴው ከሆነ መመለሻቸው የነበረውን መንገድ ሊዘጋው ይችላል። የመቶ አለቃ በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ገብተው ምን ማድረግ እንደሚገባቸው በማሰላሰል የጦር ሜዳ መነፅራቸውን ከአይናቸው በማድረግ አካባባቢውን ሲቃኙ ከተራራው ስር ጠፍተው የነበሩትን ጓዶች ለመመልከት ቻሉ። እነርሱ ወዳሉበት ከመምጣታቸው በፊት ወደ ታች ለመውረድ እንቅስቃሴ በማድረግ ለመገናኘት ቢችሉም ሁለት ብቻ ነበሩ አንዱስ የሚል ጥያቄን ሰነዘሩ ተሰውቷል የሚል ምላሽን አገኙ። በወቅቱም ስለተፈጠረው ሲያስረዱ አካላቸውም ሆነ መንፈሳቸው በጣም መጎዳቱን ለመደበቅ አልቻሉም። በተገኘው መረጃ መሰረት በጠላት ከበባ ውስጥ ሊወድቁ ስለሚችሉ በመሰበጣጠር ከፍተኛ ጥንቃቄን አድርገው ከጠላት ጋር ድብብቆሹን ያለ ምንም ስህተት መፈፀም ይገባቸዋል። ይህም ሆኖ የጠላት ጦር የአየሩ ፀባይ ቀዝቀዝ ሲል አሰሳውን አጠናክሮ ከመቀጠሉ በፊት አንድ ውሳኔ መወሰን ይገባቸዋል። መንቀሳቀስ አለባቸው ጉዞ ለማድረግ በተዘጋጁበት ወቅት ቁጥሩ አነስተኛ የሆነ የጠላት ኃይል እነርሱ ወዳሉበት አቅጣጫ እየተጓዘ እንደሆነ በመረዳት መሸሸግ ጀመሩ። በቀጣይ ምን ይፈጠር ይሆን? ክፍል አምስት ይቀጥላል .... #ክብር_ለቀድሞው_የሰራዊት_አባላት! @yetormida_welo @yetormida_welo

#የአልጌናው_ከባድ_የቃኚ_ወታደሮች_ግዳጅ_ክፍል_ሦስት በወቅቱም የጠላት ተመልካች ጦር ቦታውን ይዞት የነበረ ሲሆን አሁን ወደ ተራራው አናት በመውጣት መተኮሱን ቀጠለ። ይህን ተከትሎ በስተምስዕራብ አቅጣጫ ያሉበት ራቅ ቢልም በርካታ የጠላት እንቅስቃሴ መታየት ጀመረ። ይህም ማለት ተመልካች የነበረው የጠላት ጦር በአካባቢው ስለመገኘታችን ሪፖርት አድርጎ ወደኛ መንቀሳቀስ ጀምረዋል ማለት ነው። ጠላት የዚህን ገዢ መሬት ወታደራዊ ጠቀሜታ ከግምት በማስገባት ነበር ተመልካች ጦር ያስቀመጠው። መጠኑ አንድ ሻምበል የሚሆን የጠላት ኃይል ወደ ቃኚው ጦር ሲተም መታየት ጀመረ። የመቶ አለቃ በዚህ አይነት በነፃው የጠላት መሬት በቅርብ እርቀት የሚገኝ ኃይል የተኩሱን ልውውጥ በመስማት ወደ አካባባው እንደሚመጣ ገመቱ። በጠላትና በቃኚው ጦር መካከል የነበረው መልካዓ ምድር ወጣ ገባ የበዛበት በመሆኑ ወደ እነርሱ ለመጠጋት ሰአታት እንደሚፈጅበት እርግጥ ነበር። ወደ ተራራው አናት በመውጣት ይተኩስ የነበረው ተመልካች የጠላት ሃይል ደብዛውን አጠፋ ተኩሱም ቆመ። ሁኔታውም የተሸሸገበትን መለየት ስላላስቻለ ከፍተኛ ጥንቃቄን ይጠይቅ ነበር። ከተሸሸጉበት ሆነው ቢተኩሱ ጥሩ ነበር ቦታቸውን ለመለየትና ጥንቃቄን ለመውሰድ ነገር ግን አልሆነም። የመጀመሪያው ግጭት የጠላት ተመልካች ጦር ቀዳሚ መሪ ሆኖ ይንቀሳቀስ የነበረውን የቃኚ ወታደር አጠገቡ እስኪደርስ አድፍጦ በመጠበቅ ነበር ተኩሶ ሊገለው የሞከረው የተተኮሰበት የቃኚ ወታደር ቢቆስልም ተታኩሶ ከጓዶቹ ጋር ለመቀላቀል የቻለው። የመቶ አለቃ ከተሸሸጉበት ቦታ ሆነው ስለተፈጠረውም ሆነ ምን ማድረግ እንደሚገባቸው ሲያሰላስሉ ከቆዩ በኃላ አካባቢውን በጥልቀት መመርመር ጀመሩ። ለመረዳት እንደቻሉትም በስተደቡባዊ ምዕራብ በርቀት ባሉ ተራሮች ላይ የጠላት ምሽግና ተመሳስለው የተሰሩ መጠለያዎች አሉ። በተጨማሪም ወደ ተራራው በስተጀርባ የሚወስዱ ቀጫጭን የእግር መንገዶች ስለሚታዩ በስፍራው ከፍተኛ የሆነ የጠላት ኃይል እንደሰፈረ ያመላክታል። ወታደራዊ ካርታቸውን ነጥበው ዝርዝር መረጃን ካጠናቀሩ በኃላ የጠላትን ሁኔታ ይበልጥ በመረዳት ከፍተኛ የሆነ ኃይል ይዞ ለማጥቃት የመጣ የወገን ጦር ነው ብሎ ጠላት እንዲያስብ ለማድረግ የቃኚው ጦር አባላት ይዘውት በነበረው መትረየስና አርፒጂ ባሻገር የነበረውን ተራራ መደብደብ ጀመሩ። ይህ ሲሆን ጠላት በስተምዕራብ የሚገኘውን ከፍተኛ ወታደራዊ መሬት የወገን ጦር ቀድሞ ይቆጣጠርብኛል በሚል በድሽቃ የፍተሻ ተኩስ በሚመስል መልኩ ከርቀት እያሻገረ ተራራውን ይመታው ጀመር። የቃኚው ጦር ለመረዳት የቻለው ነገር ቢኖር ጠላት የነበሩበትን ቦታ በውል እንዳልተረዳ ነበር። ይህንን የቃኚ ጦር ለማጥቃት እንደመጣ ከፍተኛ ኃይል እንጂ እውነታውን ቢረዱ ከበባን ለመፈፀም ነበር ጥረት የሚያደርጉት። በወቅቱም የቃኚው ጦር በአካባቢው የነበረውን መረጃ እየመዘገበ በሬዲዮ ለብርጌዱ ዘገባውን ያስተላልፍ ነበር። በዚህ ሁኔታ ከተሸሸጉበት ሳይንቀሳቀሱ ውለው አመሻሹ ላይ በመንቀሳቀስ ተሸሽገው አድረው ወደ ነበረበት ቦታ ትተውት ከመጡት ቀሪ የቃኚ ጦር ጋር ተቀላቀሉ። የዋሉበት ማደሩም ሆነ ጉዞ ማድረጉ በአካባቢው ስለመኖራቸው ያወቀው ጠላት ክትትልን ስለሚያደርግ የቦታ ለውጥ በማድረግ በአካባቢው ማደር ግድ ይላቸዋል። በሌላ በኩል ውሃ ያለማግኘታቸው ሁኔታዎችን ፈታኝ አደረገው። ከመሃከላቸው የሚገኘው ቁስለኛ የሌሊቱ አየር መቀዝቀዝ ሲጀምር ቁስሉ ስለጠዘጠዘው ማቃሰት ጀምሯል። በቁስለኛው የሰቀቀን ድምፅ ሸለብ አድርጓቸው ከነበረው እንቅልፍ የነቁት የመቶ አለቃ ሰአታቸውን ሲመለከቱ ከለሊቱ ዘጠኝ ሰአት እንደሆነ በመረዳት አካባቢውን ማዳመጥ ጀመሩ ፍፁም ፀጥታ ሰፍኗል። አስር ሰአት ላይ ለንቅናቄ ተዘጋጁ በዕለቱ ተግባራቸው የሚሆነውም በመጀመሪያ ውሃ ማግኘት ነበር። ከብርጌድ የሚሰጣቸውን ትዕዛዝ በመጠባበቅ ላይ ቢሆኑም ካቀረቡት ሪፖርት አንፃር እንኳን ወደ ኃላ ተመለሱ ቢባሉም ቁስለኛ አብሯቸው ስላለ ውሃ ካላገኙ አስቸጋሪ ነው የሚሆነው። በተለይ ተመለሱ የሚባል ትዕዛዝ ከመጣ ወደ ሜዳው ክፍል እየተጠጉ ስለሚሄዱ ውሃ የውሃ ሽታ ይሆንና በረሀው ሊበላቸው ይችላል። ንጋት ላይ አመቺ የሆነ ቦታን ይዘው አካባቢውን መቃኘት ጀመሩ። ለመገንዘብ የቻሉት አንድ ነገር ቢኖር ጠላት ትላንትና ግጭቱ በተካሄደበት ወቅት ተሸሽገው ወደ ነበረበት አቅጣጫም እንኳን ለመድረሱ አመላካች የሆነ ነገር አጡ። ወደ ሰሜናዊ አቅጣጫ በሚገኝ ተራራ ላይ በርካታ እንቅስቃሴዎች ከመታየታቸው ውጪ የሚገኙበት አካባቢ ነፃ መሆኑን ስለተረዱ በሶስት አካሎች የተከፈለ ምድብ በማዘጋጀት ሰአትን ወስነው በተለያየ አቅጣጫ ውሃ ለማግኘት ተሰማሩ። ሽጡንና የአረንጓዴ ቅጠል ምልክት የሚታይበትን ቦታ ሁሉ መማስ ቢጀምሩም የውሃ ጠብታ ምልክት እንኳን ለማግኘት አልቻሉም። የፀሐዩ ሙቀት ሲያይል ደግሞ በዚህ አይነት መልኩ ፍለጋቸውን ማድረግ ስለማይችሉ የመቶ አለቃ ይህ ከመሆኑ በፊት አንድ የመጨረሻ ውሳኔ ወሰኑ አካባቢው ከሚገኙ ተራሮች አረንጓዴ ቅጠል ምልክት በብዛት የሚታይበት ተራራ በማምራት ሸጡን ተከትሎ ድንጋይ ላይ ታቁሮ የቀረ ውሃን ለማግኘት አሰሳቸውን ጀመሩ። ተሳክቶላቸው ውሃ ያገኙ ይሆን? ውሃው ካልተገኘስ? ክፍል አራት ይቀጥላል.... #ክብር_ለቀድሞው_የሰራዊት_አባላት!! @yetormida_welo @yetormida_welo