en
Feedback
መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ (ዶክተር) Dr Rodas Tadese

መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ (ዶክተር) Dr Rodas Tadese

Open in Telegram

ትክክለኛው ቻናሌ ይሄ ብቻ ነው። በዚ ብቻ ትምህርተ ሃይማኖትንና የኢትዮጵያ ምስጢራትን ሳይንሳዊ ጉዳዮችን በጥልቀት እንዳስሳለን። ሌሎቹ ቻናሎች የእኔ አይደሉም

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ (ዶክተር) Dr Rodas Tadese

Channel መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ (ዶክተር) Dr Rodas Tadese (@rodas9) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 39 818 subscribers, ranking 1 591 in the Religion & Spirituality category and 825 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 39 818 subscribers.

According to the latest data from 03 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 205 over the last 30 days and by 25 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 10.25%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 082 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 97.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
ትክክለኛው ቻናሌ ይሄ ብቻ ነው። በዚ ብቻ ትምህርተ ሃይማኖትንና የኢትዮጵያ ምስጢራትን ሳይንሳዊ ጉዳዮችን በጥልቀት እንዳስሳለን። ሌሎቹ ቻናሎች የእኔ አይደሉም

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 04 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

39 818
Subscribers
+2524 hours
+447 days
+20530 days
Posts Archive
✨ በሙሽራዋ ዕርገት የሙሽሪት ቤተ ክርስቲያን ደስታ 📖 በመጋቤ ሐዲስ ዶ/ር ሮዳስ ታደሰ 📚 ነገረ ክርስቶስ መጽሐፌ ገጽ 209-212 ☁️ ቅዱስ ሉቃስ እንደጻፈው ጌታችን በሚያርግበት ጊዜ ሐዋርያት ወደ ሰማይ በናፍቆት ሽቅብ ሽቅብ ትኲር ብለው ሲመለከቱ ነጫጭ ልብስ ለብሰው መላእክት ተገልጠውላቸዋል። 📖 የሐዋ ፩፥፲ 🤍 ነጫጭ ልብስ ለብሰው መታየታቸው በትንሣኤው እንደተገለጡት “ወርኀ ፍሥሐ፣ ወርኀ ተድላ” ነው ሲሉ ነው። 🕊️ ከዚያም፦ “የገሊላ ሰዎች ሆይ ወደ ሰማይ እየተመለከታችኊ ስለ ምን ቆማችኋል? ይኽ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲኼድ እንዳያችኹት እንዲኹ ይመጣል” ብለው በናፍቆት ሲያዩት ለነበሩት ለሐዋርያት ጉባኤ ዳግመኛ ለፍርድ ተመልሶ የመምጣቱን ነገር ነግረዋቸዋል፡፡ ⛪ በጌታችን ዕርገት የተደረገው የመላእክትና የሐዋርያት ጉባኤ፣ የቤተ ክርስቲያን አንድነት፣ የሰጠውን ፍጹም ደስታና ሐሴት ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ የቤተ ክርስቲያንን የምእመናንን አንደበቷን አንደበት አድርጎ አምልቶና አስፍቶ እንዲኽ ይተነትነዋል፦ ☞ “የገነነው ሙሽራ በአባቱ ቤት ይመሰገናል፤ የብርሃን ልጆች ጉባኤም በርሱ መኼድ ተቀሰቀሱ፤ ሙሽሪት፣ የሐዋርያት ጉባኤ፣ ቤተ ክርስቲያን፣ ሙሽራዋ በታላቅ ክብር ሲያርግ ተመለከተች፤ መከራ ሲቀበል አይታ አጐንብሶ የነበረውን ራሷን ቀና አደረገች፤ በኀይል ተነሥቶ ወደ አባቱ ያረገውን ተመለከተች፤ እናም በሞቱ የተነሣ በሐዘን ተቀስፎ የነበረ ልቧ ተጽናና 📖 ዮሐ ፲፬፥፳፰-፳፱። 💒 የሙሽሪት ናፍቆት ☁️ በአየር ላይ ሲኼድ ስታይ በስቅለቱ ጊዜ የደረሰበትን ስድብና ውርጅብኝን ተወች፤ ከርሱ ፊት የሚጋልቡትን ደመናዎችና ጒምን ተመለከተች፤ እናም ርሱን ተከትላ የብርሃን ልጅ እንደመኾኗ ለመኼድ ተመኘች። ❤️ “ወደምትኼድበት ከአንተ ጋር ውሰደኝ፤ የአንተ ኾኜያለኹና፤ ወደ አባትኽ ካንተ ጋር ላርግ ፈቃድኽ ይኹን” አለችው። ✝️ በፍቅርኽ ፈለግኸኝ፤ በመከራኽ ዐጨኸኝ፤ በጦር ተወግተኽ ነጻ አወጣኸኝ፤ እነሆ ገንነኻል፤ አንተን ተከትዬ ወደ አባትኽ ቤት ልሩጥ። 🌹 ወደ ሸንጎው ውስጥ የአንተን መከራ ለማየት ገባኊ፤ በአንተ የተነሣ ከአይሁድ ኀፍረትን ተቀብዬያለኊ፤ በመስቀል ላይ ሲዘባበቱብኽም እሞት ይኾን ብዬ ፈርቼ ነበር፤ በኀጢአተኞች ስትደበደብ ሸሽቼ ተደብቄ ነበር። 📖 መሓ ፭፥፯ 🪦 በወንበዴዎች መኻከልም ሲሰቅሉኽ ከአንተ ጋር ተዘባብተውብኝ ነበር፤ እንደገናም እንደ ሙታን በመቃብር ውስጥ ሲያኖሩኽ አሞኝ ነበር፤ ዕጹብ ድንቅ በኾንኸው ባንተ የተነሣ ተጽናንቼ ሐዘኔን ረሳኹት። 🕊️ በአንተ የተነሣ መሳደድ ደርሶብኛልና ከአንተ ጋር ልኺድ፤ ስምኽ ለእኔ የሚያስደስተኝ የከርቤ ዘይት ይኹንልኝ። 📖 መሓ ፩፥፫ 🍷 ምሕረትኽ ከወይን የተሻለ ነውና በአንተ ልጽናና፤ ከአንተ ከሙሽራው ከምወድድኽ ጋር ወደ ቦታኽ ልኺድ፤ ጠፍቼ እንዳልቀር በአንተ እሰበሰብ ዘንድ በመንጋኽ ውስጥ ዐስበኝ። 📖 መሓ ፩፥፯ 👑 በፍቅሩ የታመመች ሙሽሪት 🌸 የኢየሩሳሌም ቆነጃጅት ሆይ ንጉሡን ሙሽራ ወዴት አያችኹት? በጣም አብዝቼ ብፈልገውም ወደ ቦታው በማረጉ ፈጽሞ ላገኘው አልቻልኩም። 📖 መሓ ፫፥፪ 💘 እነሆ በሙሽራው ፍቅር ታምሜያለኊ ርሱንም እፈልገዋለኊ፤ ከኹሉም ውቦች በላይ ውብ የኾነውን እወድደዋለኊ፤ ሲናገር ከናፍሮቹ መውደድን ያዘንባሉ፤ ለሚመለከቱት ኹሉ ርሱ ከኹሉም በላይ ውብ ነው። 📖 መዝ ፵፬፥፪ 🌿 ልብሶቹም ልክ እንደ አሮን ጣፋጭ የዕጣን መዐዛን ይረጫሉ፤ ከርሱ የሚፈስሰውም ነጭና ቀይ፤ ውሃና ደም ነው። 📖 መሓ ፭፥፲፤ ዮሐ ፲፱፥፴፬ 🌺 ለሚመለከተው ጉንጮቹ የሽቱ ብልቃጥ ናቸው፤ አባቱ በርሱ ምክንያት ዓለምን በመታረቁ ሙሉ በሙሉ ሽቱ ነው። ☁️ ወደ ሰማይ ያረገው ሙሽራ 👣 በመንገድ ላይ አግኝቶኝ ነበር ባለማወቄ የተነሣ አላወቅኹትም ነበር። 📖 ሉቃ ፳፬፥፲፮ ☁️ ወደ ሰማያቱ ዐርጓል፤ ርሱን አየው ዘንድ ርሱ ወዳለበት ማን ያሳርገኛል? አለች። ⛰️ የሐዋርያት ጉባኤ በደብረ ዘይት ቆመዋል፤ ድንግል ሙሽሪት፣ ቤተ ክርስቲያን፣ ምእመን፣ ከምድር ያረገውን ሙሽራ አተኲራ ትመለከተዋለች። 📖 የሐዋ ፩፥፲ 🕊️ እነሆ ርሱ ትቷት በማረጉ የተነሣ ልታነባ ስትል መላእክት “እነሆ እንደገና ይመጣል” ብለው ሊያጽናኗት ቀረቧት። 📖 የሐዋ ፩፥፲፩ 👑 ንግሥቲቱ ሙሽሪት፣ ቤተ ክርስቲያንን፣ ምእመንን፣ የንጉሡ አገልጋዮች (መላእክት) ሲያጽናኗት ነበር። ✨ “ከቶ ማዘን የለብሽም ምክንያቱም ይኸው ሙሽራ ይመጣልና በርግጠኛነት ታይዋለሽ፤ የኼደው የከበሩ ነገሮችን ይዞልሽ ሊመለስ ነው፤ ፈጽሞ አይተውሽም፤ ወደ አንቺም ይመለሳል።” 🕊️ “የሚመጣውን ተመልከቺው፤ በአካሉ ተሸከመሽ እነሆ በርሱ የተቀደሰ ስፍራ ከርሱ ጋር ነሽ፤ መንፈሱን ሰጠሽ።” 📖 ዮሐ ፳፥፳፪ 💛 “እነሆ ርሱ እዚኹ ከአንቺ ስፍራ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ራስሽ በርሱ ተፈጠርሽ፤ ርሱ ግን ከአንቺ ጋር ነውና መቼም ብቻሽን አይተውሽም።” 📖 ዮሐ ፲፬፥፲፰ 🌍 ሰማይና ምድር በዕርገቱ ተጣመሩ 🤍 መላእክት ደቀ መዛሙርትን ከብበው አበረታቷቸው፤ “ጌታችኊ ይመጣል፤ ርሱ ምስጉን ነውና ፈጽሞ ዐትዘኑ፤ ወደ ሰማይ ሲኼድ እንዳያችኹት እንዲኹ ሲመጣም ታዩታላችኊ፤ ዳግመኛ በክበበ ትስብእት እያበራ ይመጣልና” አሏቸው። 🕊️ መላእክቱ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ለመደሰት መጡ፤ አንዳቸውን ጉባኤ ከሌላቸው ጋር በታላቅ ሰላም አጣመረ፤ ከደስታቸው የተነሣ መላእክት ራሳቸውን በነጭ ካባዎች አጐናጸፉ። ✨ ምክንያቱም በጠላትነት ከነበሩ ከሰው ዘሮች ጋር አስታርቋቸዋልና፤ በእግዚአብሔር ልጅ ሰማይና ምድር ርስ በርስ ተጣመሩ፤ በርሱ አማካይነት በሰው ዘርና በመላእክት መኻከል ሰላም ሰፈነ። 🔥 የወልድ መገለጥ እና የሰማያውያን ድንቅ 👼 የሰማያዊ ፍጥረታት ነገዶች ርሱን ሊያዩ ፈለጉ፤ ምክንያቱም ወደ እኛ መጥቶ ሥጋን ለብሶ በመኻከላችን እስኪኖር ድረስ አላዩትም ነበር። ☀️ ከአባቱ ጋር እንደነበረና ከርሱም ጋር ኅቡዕ እንደኾነ ያውቁታል፤ ነገር ግን ሰማያዊ ነገዶች ርሱን በባሕርዩ ለማየት ችሎታ አልነበራቸውም። ✝️ ለሰው ልጅ ባለው ፍቅር ሥጋን ተውሕዶ በምድር ላይ ሲገለጽ፤ ርሱ ከመገለጹ የተነሣ እነሆ የሰማይ ጭፍሮች ሊያዩት ፈለጉ፤ ኀይላት ሥልጣናት በየነገዳቸው ተደነቁ። 🌟 ምክንያቱም ስዉር የኾነው ርሱ በፈቃዱ ይመለከቱት ዘንድ ተገልጧልና፤ ወደ ሰማያት ሲያርግ ሥልጣናት ሊያዩት ተሰበሰቡ፤ ምክንያቱም ይዞት በመጣው የምሥራች ተነሳሥተው እና ተቀስቅሰው ለርሱ ምስጋናን አቀረቡለት። 🕯️ ርሱ ራሱ እንዲገለጽ የወደደው ዐዲስ ተአምር፣ ምስጢር ያውም የወልድን መገለጥ በቅንነት ለማየት ፈለጉ፤ በሥጋ ተገለጸ፤ በክብርም ዐረገ፤ ሲያርግም በሰዎችና በመላእክት ታየ። 📖 ፩ኛ ጢሞ ፫፥፲፮ 📚 ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ በእንተ ዕርገተ እግዚእ በመጋቤ ሐዲስ ዶ/ር ሮዳስ ታደሰ 📚 ነገረ ክርስቶስ መጽሐፌ ገጽ 209-212 [ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ በዕርገትኽ ዕርገታችንን የገለጽክልን እንወድኻለን]

🖤👑 ጥቊሯ እመቤት ማርያም (ለልደቷ መታሰቢያ ጻፍኩ) 📖 በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ 📚 መልክአ ሥዕል ንባቡና ትርጓሜው ገጽ 261–264 ✨ በዐዲስ አበባ በማኅደረ ስብሐት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያንና የ3000 ዓመት ታሪክ ባላት በብርብር ማርያም ቤተ ክርስቲያን የሥዕሏ ቅጂ የሚገኙና በተአምር አድራጊነቷ የምትታወቀው ጥቁሯ እመቤት (The Black Madonna) ወይም ጥቁሯ ማርያም በመባል በመላው ዓለም የምትታወቀው የእመቤታችን ሥዕል ናት። 🎨 ይኽቺን ሥዕለ ማርያም እመቤታችን በናዝሬት ቤቷ ሳለች ከዕንጨት በተሠራ ሰሌዳ ላይ ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊ ሥሏታል፡፡ 🌸 ቅድስት ድንግል ማርያም ራሷ ለሥዕሉ እንደተቀመጠችለት ይነገራል፤ በመጨረሻም ቅዱስ ሉቃስ ሥዕሏን ሥሎ ሲፈጽም አይታ፦ “ጸጋዬና ከእኔ የተወለደ የርሱም ጸጋ ከዚኽ ሥዕል ጋር ለዘላለም ይኹን።” ብላ ባርካዋለች፡፡ 📏 የመዠመሪያዋ ሥዕል 122 ሴንቲሜትር × 82 ሴንቲሜትር ወይም 48 በ 32 ኢንች ነው፡፡ 🙏 በሥዕሉ ላይ ቅድስት ድንግል ማርያም ልክ እንደ “መራሒተ ፍኖት” መድኃኒት ወደኾነው ወደ ኢየሱስ ልጇ ቀኝ እጇን ታሳያለች፡፡ ጌታ ደግሞ በግራ እጁ ወንጌል እየያዘ፤ ቀኝ እጁን ወደ ተመልካቹ ዘርግቶ ይታያል፡፡ 📜 የቅዱሳት ሥዕላት ትውፊት እንደሚገልጸው፣ ሮማውያን የኢየሩሳሌምን ከተማዋን ለጥፋት ሲቆጣጠሩ በፔላ አቅራቢያ በሚገኝ ዋሻ ውስጥ ተሰውራ ነበር፡፡ ከብዙ መቶ ዓመታት በኋላ በ326 ዓ.ም. ቅድስት እሌኒ እውነተኛው የጌታን መስቀል እና ንዋያተ ቅድሳትን ስትፈልግ የተቀደሰችውን ሥዕል በኢየሩሳሌም አግኝታት ወደ ቁስጥንጥንያ በ፫፻፳፮ አምጥታዋለች። 🌍 ከስምንተኛው ክፍለ ዘመን ዠምሮ ሥዕሏ ጋሊሺያ፣ ባቫሪያ እና ሞራቪያን ጨምሮ ወደ ተለያዩ ቦታዎች ተጉዛለች። የልቮቭን ከተማ የመሠረተው ልዑል ሊዮ ሥዕሏን ወደ ሩሲያ አምጥቶ በቤልዝ ምሽግ ውስጥ ያስቀመጣት ሲኾን በተቀደሰ ሥዕሏ ፊት በጊዜው ብዙ ተአምራት ተፈጽመዋል፡፡ 🏹 ታታሮች ሩሲያን ወርረው ምሽጉን መክበብ ሲጀምሩ ልዑሉ ሥዕሏን በከተማው ግድግዳ ላይ እንዲያስቀምጧት አዘዘ። ያን ጊዜ በወረወሩት ቀስት የተመታበት የሥዕሏ ክፍል ላይ በተአምራት ደም መፍሰስ ዠመረ። ያዩትም ኹሉ እጅግ ፈሩ፤ ታታሮች ጥቁር ጭጋግ በሸፈናቸው ጊዜ ማፈግፈግ ዠመሩ፤ ብዙዎቹም ሞቱ። ⛪ ቭላዲስላቭም በ፲፫፻፹፪ በያስና ጎራ ገዳም ገንብቶ ሥዕሏን ለመነኮሳቱ ሰጥቷቸዋል፡፡ ⚔️ ከብዙ ዓመታት በኋላ የዮሐንስ ሁስ ተከታዮች ቸስቶቾዋን በማጥቃት ገዳሙን ዘረፉ። የቼስቶቾዋ ሥዕሏን በጋሪ ለማንሣት ሲሞክሩ ፈረሶቹ በማይታይ ኃይል ተይዘው ከቦታው ለመንቀሳቀስ ፈቃደኛ አልኾኑም፡፡ 💧 ከሁሲያውያን አንዱ ተቆጥቶ ሥዕሏን ወደ መሬት ላይ ሲወረወር፣ ሌላው ደግሞ የድንግልን ፊት በሰይፍ ወጋው። ያን ጊዜ ደም በተአምራዊ ኹኔታ ከሥዕሏ ጉንጮች ላይ ፈሰሰ። ይኽ የቁስሏ ምልክት እስከ ዛሬ በሥዕሎቿ ላይ ይታያሉ፡፡ ⚠️ ወዲያውኑ የመዠመሪያው ሰው ተቀስፎ ሲሞት የኹለተኛውም ሰው እጅ ደግሞ ደረቀ። በዚኽ ድፍረታቸው ሌሎቹ ወራሪዎችም ከእግዚአብሔር ቅጣት ደርሶባቸዋል። አንዳንዶቹ እዚያው ሲሞቱ ሌሎቹ ደግሞ ዐይናቸው ታውሯል። ምንም እንኳን ብዙዎቹ የገዳሙ ውድ ሀብቶች በሁሲውያን የተሰረቁ ቢኾንም አስደናቂው ተአምር አድራጊዋ የእመቤታችን ሥዕል ግን ለመውሰድ አልቻሉም። 👑 በተጨማሪም በአምላክ እናት በቅድስት ድንግል ማርያም የተቀደሰ ሥዕል በመማፀን ፖላንዳውያን ስዊድናውያንን በማሸነፍ ጦርነቱን በ፲፮፻፶፮ ማብቃት ቻሉ። ያንጊዜ ንጉሥ ጃን ካሲሚር የአምላክ እናት የፖላንድ ንግሥት እንደኾነችና ሀገሩም በርሷ ጥበቃ ሥር እንደኾነ በይፋ አወጀ። 🌟 በዚኽቺ የተቀደሰች ሥዕል እጅግ ብዙ ተአምራት የተሠሩ ሲኾን የሥዕሏ ቅጂ በብዙ የዓለማችን ሀገራት ይገኛል፡፡ 🌸✨ እንኳን ለእመቤታችን ልደቷ በሰላም አደረሳችኹ። 🙏⛪ የነዚኽን ኹሉ ቅዱሳት ሥዕላት ታሪክን የያዘው መልክአ ሥዕል ንባቡና ትርጓሜው መጽሐፍና ታላላቅ ተአምራትን በማድረግ ከሚታወቁት የእመቤታችን ሥዕላት ውስጥ፦ 🚪✨ “አቃቢተ ኆኅት” (ደጃፍን የምትጠብቅ) በመባል በመላው ዓለም የምትታወቀው 💧 ከጉንጯ ደም የሚፈስስት ሥዕለ ማርያም 📖 ከታሪኳ ጋር፣ 🖤👑 “ጥቁሯ እመቤት” በመባል የምትታወቀው 🌟 አስደናቂዋ ሥዕለ ማርያምና ታሪኳ 🏡🙏 ለራሳችኹ፣ ⛪ ለጸሎት ቤታችኹ፣ 🎁 እንዲሁም የእመቤታችንን ልደት ምክንያት በማድረግ ስጦታ መስጠት ለምትፈልጉ፣ 🏢 4 ኪሎ ቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርስቲ ሕንጻ 📖 ብርሃኑ መጻሕፍት መደብር 📞 0902327081 📞 ወይም በስልክ ቁጥር 0937488144 ደውላችኹ 🖼️ እያንዳንዱን በ100 ብር መውሰድ ትችላላችኹ። 🌹✨ የእመቤታችን የልደቷ በረከትና ጸጋ ከኹላችን ጋር ይሁን።

🌸✨ እንኳን ለእመቤታችን ልደቷ በሰላም አደረሳችሁ ✨🌸 🙏⛪ ታላላቅ ተአምራትን በማድረግ ከሚታወቁት የእመቤታችን ሥዕላት ውስጥ፦ 🚪✨ “አቃቢተ ኆኅት” (ደጃፍን የምትጠብቅ) በመባል በመላው ዓለም የምትታወቀው 💧 ከጉንጯ ደም የሚፈስስት ሥዕለ ማርያም 📖 ከታሪኳ ጋር፣ 🖤👑 “ጥቁሯ እመቤት” በመባል የምትታወቀው 🌟 አስደናቂዋ ሥዕለ ማርያምና ታሪኳ 🏡🙏 ለራሳችሁ፣ ⛪ ለጸሎት ቤታችሁ፣ 🎁 እንዲሁም የእመቤታችንን ልደት ምክንያት በማድረግ ስጦታ መስጠት ለምትፈልጉ፣ 📞 በስልክ ቁጥር 0937488144 ደውላችሁ 🖼️ እያንዳንዱን በ100 ብር መውሰድ ትችላላችሁ። 🌹✨ የእመቤታችን በረከትና ጸጋ ከሁላችን ጋር ይሁን።

በልደቴ ማግስት የሚያዝያ ወር ሙሉ ጨረቃ ሚያዝያ 23 የእናንተን ፎቶ አጋሩኝ በዚ ሊንክ https://t.me/+xN518gdGKvswNzE0

✨ የቅዱስ ጊዮርጊስ ሥዕል ኃይልና ምሳሌ 📖 በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ (መልክአ ሥዕል ንባቡና ትርጓሜው መጽሐፍ ገጽ 40) 🛡️ ቅዱስ ጊዮርጊስን ጨምሮ በዘመነ ሰማዕታት ዘመን የነበሩ ክርስቲያን ወታደሮች “ጣዖት አናመልክም ክርስቶስን አንክድም” በማለት ታማኝነታቸውን ከምድራዊ ንጉሥ፤ ወደ ሰማያዊ ንጉሥ ወደ ክርስቶስ በማድረጋቸው የሰማዕትነትን አክሊል ተቀዳጅተዋል፡፡ 🎖️ በዚኽ ምክንያት ከ10ኛው ክፍለ ዘመን አስቀድመው በተሣሉ የቅዱስ ጊዮርጊስ ሥዕላትና የሌሎች ሰማዕታት ሥዕል በቆመ ወታደር አምሳል ይሣሉ ነበረ፡፡ 👤 የቅዱስ ጊዮርጊስም ሥዕል ወጣት፣ ጢም የሌለው፣ ዐጭር ጠጒር ያለው እና የሮማን ከፍተኛ መኮንን ልብስ ለብሶ ይሣል ነበር። ✝️ በተጨማሪም የሰማዕትነቱ ምልክት መስቀል ወይም የጦር ሥዕል ዐብሮ ተሥሎ ነበረ እንጂ የደራጎን ሥዕል እምብዛም ተሥሎ አይታይም ነበር፡፡ 🌍 እንደዚኽ ዓይነት ሥዕላት በሶርያ፣ ሊባኖስ፣ ቀጰዶቅያ፣ ቁስጥንጥንያ ይገኛሉ፡፡ 🐉 ከዚያ በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስን ጨምሮ አስቀድመው ወታደር የነበሩ ሌሎች ቅዱሳን ሰማዕታት ሥዕላት ላይ ደራጎንን በመጨመር በብዛት ተሥለዋል፡፡ 🔥 ደራጎን የሚወክለው ሰይጣንን፣ አረማዊነትን፣ አምባገነንነትን፣ ክፋትን ሲኾን ሰማዕታቱ እነዚኽን ድል መንሣታቸውን ያመለክታል፡፡ 🏜️ በሲና በረሓ በሚገኘው በቅድስት ካትሪና ገዳም በሚገኘው የዘጠነኛው ክፍለ ዘመን ሥዕል ቅዱስ ጊዮርጊስ በነጭ ፈረስ ተቀምጦ ከቅዱስ ቴዎዶር ጋር ዐብሮ ተሥሏል፡፡ 🐎 ይኸውም በዮሐንስ ራእይ ላይ ክርስቶስ በነጭ ፈረስ ላይ ኾኖ እንደተገለጠ፤ ቅዱስ ጊዮርጊስም የንጹሐ ባሕርይ የክርስቶስ አገልጋይ መኾኑን፤ ዳግመኛም ጽድቅ ከጨለማው ሰራዊት ጋር የሚያደርገው የውጊያ ምልክትና ድልን ይወክላል፡፡ 🇪🇹 በኢትዮጵያ በሚገኙ ሥዕላቱ ላይ በነጭ ፈረስ ተቀምጦ የሚሣል ሲኾን ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ ስትገለጽ፤ ቅዱስ ጊዮርጊስም በነጭ ፈረስ ላይ ተቀምጦ ይገለጥ እንደነበር ተአምሯ ያስረዳል፡፡ 📜 በስብሐተ ፍቁር ዘቅዱስ ጊዮርጊስ ላይም ደራሲው፡- “ነዓ ጊዮርጊስ እንዘ ትጼዓን በፈረስ ወነዓ ፍቁርየ ዘልዳ ንጉሥ” (ጊዮርጊስ ሆይ በፈረስ ተቀምጠኽ ና፤ የልዳ ንጉሥ ወዳጄ ጊዮርጊስ ሆይ ና) ይላል፡፡ ⚔️ በወታደራዊ ትጥቅ፣ ዘንዶውን የሚወጋበትን ጦር ይዞ ሲታይ ጦሩ ብዙውን ጊዜ ጫፉ ላይ ትንሽ መስቀል አለው፤ ይኸውም ክፉውን በእምነት እንጂ በጉልበት አለመግደሉን ያመለክታል፡፡ 🏰 ልዕልቷ (ቤሩታዊት) ወይም ከተማ ከበስተጀርባው ኾነው ተሥለዋል እነዚኽ ሥዕላቱ በጣም የሚታወቁት ናቸው፡፡ 👑 በ፲፩ኛው – ፲፪ኛው ክፍለ ዘመን በመስቀል ጦርነት ወቅት ቅዱስ ጊዮርጊስ የወታደሮች ጠባቂ ነው ተብሎ ይታመን ነበርና ቅዱስ ጊዮርጊስ በወጣት አምሳል ይሣላል፣ ይኽም ንጽሕናን፣ ጥንካሬን፣ መንፈሳዊ ድፍረትን ይወክላል፡፡ 🔴 ደሙን በክርስቶስ ስም ማፍሰሱን ለማመልከት የሰማዕትነት ምሳሌ የኾነ ደማቅ ቀይ ቆብ አድርጎ አክሊለ ብርሃን ከበላዩ ይታያል፤ ይኽም ቅድስናውን ያገኘውን ድል ይገልጻል፡፡ 🌍 እንደዚኽ ዓይነት ሥዕላቱ ቁስጥንጥንያ፣ ቆጵሮስ፣ አንጾኪያ፣ ጆርጂያ፣ ቡልጋሪያ፣ ሰርቢያ ውስጥ ይገኛሉ፡፡ 🙏✨ የቅዱስ ጊዮርጊስ በረከት አይለየን።