cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

አልፋ ና ዖሜጋ ነህ

ራዕይ 1:8 ያለውና የነበረው የሚመጣው ሁሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክ ፦ አልፋ ና ዖሜጋ እኔ ነኝ ይላል፡፡ ራዕይ 21:6 አልፋ ና ዖሜጋ መጀመሪያውና መጨረሻው እኔ ነኝ ለተጠማ ከሕይወት ውሃ ምንጭ እንዲያው እኔ እሰጠዋለሁ፡፡ ራዕይ 22፡13 አልፍ ና ዖሜጋ ፊተኛውና ከኃለኛው መጀመሪያው ና መጨረሻው እኔ ነኝ፡፡ @kalyewude

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
178Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
✨በማይመጥንህ ሰፈር አትገኝ አንድ አባት ከመሞቱ በፊት ለልጁ እንዲህ አለው "የሄን ሰአት አያትህ ነው የሰጠኝ በትንሹ 200 አመት ይሆነዋል አሁን ላንተ ከመስጠቴ በፊት "እዚ ሰፈር ያለው የሰአት መሸጫ ሱቅ ሂድና ስንት እንደሚያወጣ ጠይቀህ ና አለዉ" ልጁም ደርሶ መጣና ለአባቱ፡"አባዬ ሰአት ሻጩ ሰዉዬ አሮጌ ሰአት ነው አልገዛም አለኝ" አለው አባቱም አሁን ደግሞ ወደ ካፌ ብቻ ሰዎች ሰብሰብ ያሉበት ቦታ ሄደህ የገዙህ እንደሆን ጠይቅ አለው! ልጁም ደርሶ መጣና አባዬ አንድ ሰውዬ 100 ብር ልግዛህ አለኝ አሁን ደግሞ ሙዚየም ሄደህ ጠይቅ አለው ደርሶም መጣና 100,000 ብር እንግዛህ አሉኝ አለው፡፡ አባትየውም እንዲህ አለው "ያንተን ዋጋ የሚወስነው ትክክለኛ ቦታ ላይ ስትገኝ ብቻ እንደሆነ እንድታውቅ ነው እንዲህ ያረኩት፡፡ እራስህን ባልተገባ ቦታ ለማስገባት አትግፋው ትርፉ መናደድ እና መማረር ብቻ ነው። ዋጋህን የሚያዉቁት የሚያውቁህ ናቸውና አንተን በማይመጥንህ ሰፈር አትገኝ፡፡ ዋጋህ ውድ ነው የተገዛኸው በክርስቶስ ደም ነው ስለዚህ ዋጋህን በማይመጥን ሰፈር አትገኝ፡፡ ✝ @Excellent_youth ✝ ✝ @Excellent_youth
Show all...
. አመለጠች ነፍሴ ሳሙኤል ተ/ሚካኤል || NEW SONG 🕐-6:57Min-||-💾-30.3MB ▷THE GOSPEL IS CHRIST◁ Share 📲 Share 📲 Share ▷ @christ_progeny_tube ◁ ▷ @christ_progeny_tube ◁ △Join us△
Show all...
. አመለጠች ነፍሴ ሳሙኤል ተ/ሚካኤል || NEW SONG 🕐-6:58Min-||-💾-6.3MB ▷THE GOSPEL IS CHRIST◁ Share 📲 Share 📲 Share ▷ @christ_progeny_tube ◁ ▷ @christ_progeny_tube ◁ △Join us△
Show all...
እንካ ልቤን        ወዳጄ ኢየሱስ አንተ የልብ አምላክ ነህ። የልቤን በር በፍቅር ማንኳኳት ሳይሰለችህ በልቤ ደጃፍ ቆመሀል እኔ ግን በምቾት ሰንሰለት፣ በስንፍና ገመድ፣ በእንቅልፍ ቁልፍ በሬን ቀርቅሬ ደጅ አስጠናሁህ። አሁን እንኳ ምቾትን ልጠየፍ፣ ስንፍና ይሰልቸኝ፣ ከእንቅልፌም ልንቃ። እንካ የልቤን ቁልፍ፣ እንካ የሕይወቴን ቁልፍ።       ቁልፍ ለታማኝ እንጂ ለሌባ አይሰጥም፣ ቁልፍ ለጨዋ እንጂ የእጅ አመል ላለበት አይሰጥም፣ ቁልፍ እንደልብ ለሆነ ሰው እንጂ እንደ ልቡ ለሆነ ሰው አይሰጥም አንተ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ታማኝ ነህና እንኳ ቁልፌን ክፈተኝ፣ አስተካክለኝ።       ካንተ የምደብቀው ምስጢር የለኝምና የደስታዬን በር ተቆጣጠረው፣ የኅዘኔ መግቢያ ባንተ ብቻ ተከፍቶ ይዘጋ፣ የስኬቴና የውድቀቴ መስኮቶችም ባንተ ይዘወሩ፣ እኔ እንኳን የማላውቃቸው በሮቼ ሁሉ ባንተ ቁጥጥር ስር የዋሉ ይሁኑ።      ካንተ የምሸሽገው ጓዳ የለኝም ስለ ትዳሬ የምጨነቅበት ቁልፍ ይኸው፣ ይህ ደግሞ የልጆቼ ቁልፍ ነው፣ የሰርጌና ምላሹ ነገርም አንተ ካልከፈትከውና ካልዘጋኸው ባዶ ነው። ከማንም የምደብቀው የውስጥ ምሥጢሬ ቁልፍም ይኸው! እስከዛሬ እኔ ይዤው ሸክም ነው የኾነብኝ። አምላኬ ሆይ የኑሮዬን ቁልፍ ተቀበለኝና ሸክሜ ይቅለልልኝ።        እኔ ስከፍትና ስዘጋ ወና የነበረውን ሕይወቴን እስኪ ቁልፉን ያዝና አንተ ሙላው። ለብቻዬ ይዤው እኔ ምን ፈየድኩ? ካንተ ተነጥዬ ያፈራሁት በርና መዝጊያ ኹሉ ስንት ዝብርቅርቅን ፈጥሯል መሰለህ!? ጌታዬ ሆይ ይኸው ቁልፉ… እስኪ አንተ ግባና አስተካክለው፡፡           ይቀጥላል........................              ከተማርኩበት ✍አዶኒ @adonigospel @adonigospel
Show all...
Show comments
እ/ር ተስፋ አደርጋለሁኝ እሱም ይረዳኛል ❤️የዘማሪው የትላንት ታሪክ መዝሙር 27 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ እግዚአብሔር ብርሃኔና መድኃኒቴ ነው፤ የሚያስፈራኝ ማን ነው? እግዚአብሔር የሕይወቴ መታመኛዋ ነው፤ የሚያስደነግጠኝ ማን ነው? ² ክፉዎች፥ አስጨናቂዎቼ ጠላቶቼም፥ ሥጋዬን ይበሉ ዘንድ በቀረቡ ጊዜ፥ እነርሱ ተሰናከሉና ወደቁ። ³ ሠራዊትም ቢሰፍርብኝ ልቤ አይፈራም፤ ሰልፍም ቢነሣብኝ በዚህ እተማመናለሁ። ⁴ እግዚአብሔርን አንዲት ነገር ለመንሁት እርስዋንም እሻለሁ፤ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ በእግዚአብሔር ቤት እኖር ዘንድ፥ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘውንም አይ ዘንድ፥ መቅደሱንም እመለከት ዘንድ። ⁵ በመከራዬ ቀን በድንኳኑ ሰውሮኛልና፥ በድንኳኑም መሸሸጊያ ሸሽጎኛልና፥ በዓለት ላይ ከፍ ከፍ አድርጎኛልና። ⁶ እነሆ፥ አሁን በዙሪያ ባሉ በጠላቶቼ ላይ ራሴን ከፍ ከፍ አደረገ፤ በድንኳኑም የእልልታ መሥዋዕትን ሠዋሁ፥ ለእግዚአብሔር እቀኛለሁ እዘምርለትማለሁ። ♥አሁን ዘማሪው ህይወትተ መዝሙር 27 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁷ አቤቱ፥ ወደ አንተ የጮኽሁትን ቃሌን ስማኝ፤ ማረኝና አድምጠኝ። ⁸ አንተ ፊቴን እሹት ባልህ ጊዜ፦ አቤቱ፥ ፊትህን እሻለሁ ልቤ አንተን አለ። ⁹ ፊትህን ከእኔ አትሰውር፥ ተቈጥተህ ከባሪያህ ፈቀቅ አትበል፤ ረዳት ሁነኝ፥ አትጣለኝም፥ የመድኃኒቴም አምላክ ሆይ፥ አትተውኝ። ¹⁰ አባቴና እናቴ ትተውኛልና፥ እግዚአብሔር ግን ተቀበለኝ። ¹¹ አቤቱ፥ መንገድህን አስተምረኝ፥ ስለ ጠላቶቼም በቀና መንገድ ምራኝ። ¹² የሐሰት ምስክሮችና ዓመፀኞች ተነሥተውብኛልና ለጠላቶቼ ፈቃድ አትስጠኝ። ♥ግን ወደፊት በእኔ ዘመን መዝሙር 27 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹³ የእግዚአብሔርን ቸርነት በሕያዋን ምድር አይ ዘንድ አምናለሁ። ♥ስሙ ቅዱሳን ¹⁴ እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ፤ በርታ፥ ልብህም ይጽና፤ እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ። ከቃልኪዳን ንጋቱ @Kalyekal
Show all...
#የሕይወት ትርጉም ኢየሱስ ➥ ወንድሜ በሕይወትህ አንድ ቀን እደርስበታለው ብለህ ያሰብከው ህልምህ የደረስክበት ቀን ሕይወትህ ከዚያን ቀን በኋላ ትርጉም እንደሚሮረው የምታስብ ከሆነ እንግዲያውስ ልንገርህ አንተ ከሁሉም ሰው ይልቅ ሞኝ ነህ። መኖርህ ትርጉም ሊያገኝ የሚገባው ዛሬ ነው። አንተ እንድትኖር የተፈለገው ዛሬን ነው ። እርካታና ደስታ ከብዙ ጥረትና ስራ በኋላ የምትደርስባቸው እንደሆኑ አስበህ ሩቅ አታድርጋቸው። ወንድሜ ከሰሎሞን ተማር እንጂ ሕይወትህ ትርጉም የሚያገኘው በሰበሰብከው ገንዘብ፣ዕውቀት፣የሰዎች ፍቅር፣የእናንትህና የአባትህ አድናቆት አይደለም።ንጉስና ጠቢብ የነበረው ሰሎሞን አንተ በሕይወት ዘመንህ የምትመኛቸው ነገሮች በሙሉ እንዲያውም ከዚያ በላይ ነበረው ነገር ግን ለሰለሞን ሁሉ ከንቱ ነበረ። እነዚህ አሁን አንተ እየሰበሰብካቸው ያለሀቸው ነገሮች ያንተን ሕይወት ትርጉም ሊሰጧት በፍፁም አይችሉም። ሕይወትህን ትርጉም የሚሰጣት ነገር አጠገብህ ነው ያለው። ኢየሱስ ይባላል! ወንድሜ አይንህን ክፈት ደስታ አጠገብህ ነው ያለው። እርካታ አጠገብህ ነው ያለው። ምናልባት ይሄን የምታነቡ ፕሮቴስታንት ልጆች ለቀባሪው አረዳው በሚል አስተሳሰብ እያነበባቹት ሊሆን ይችላል ሚገርመው ግን መልዕክቱ ለናንተ ነው። የተቀበልከው ሐይማኖት አይደለም ሕይወት ነው። የዘለዓለም ደስታና ዕርካታ ያለበት ሕይወት። የሚያሳዝነው ግን አንተም ጌታን እንደማያውቅ ሰው ሕይወትህን በምትሰበስባቸው ነገሮች ትርጉም ልትሰጣት መሞከርህ ነው። “የእግዚአብሔር መንግሥት ጽድቅና ሰላም በመንፈስ ቅዱስም የሆነ ደስታ ናት እንጂ መብልና መጠጥ አይደለችምና።” — ሮሜ 14፥17 ➛ ብራዘር የመዳን ቀን ዛሬ ነው የሚለው ቃል ለጴንጤም የተፃፈ ነው። የደስታ ቀን ዛሬ ነው! የመርካት ቀን ዛሬ ነው! የተቀበልከው ፅድቅ የዛሬ ነው። በእግዚአብሔር አለም ነገ የሚባል ነገር የለም። ሁሉም ነገር አሁን ነው። አሁንና አሁን ነው። ጌታ አሁን ከወደደህ በላይ ነገ አይወድህም። ጌታ እንድትደሰት የሚፈልገው አሁን ነው። “ሕይወትም ተገለጠ አይተንማል እንመሰክርማለን፥ ከአብ ዘንድ የነበረውንም ለእኛም የተገለጠውን የዘላለምን ሕይወት እናወራላችኋለን፤” — 1ኛ ዮሐንስ 1፥2 ፀጋና ሰላም ይብዛላቹ። Share Share Share 👇👇👇👇👇👇👇 @Pure_Christianity @Pure_Christianity @Pure_Christianity
Show all...
ኢየሱስ ዛሬም አማላጃችን ነው።❗️ “የሞተው፥ ይልቁንም ከሙታን የተነሣው፥ በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፥ ደግሞ ስለ እኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው።” — ሮሜ 8፥34 ➛ክርስቶስ ይማልዳል ማለት ያስታርቃል ማለት ነው። ሐጢያትን ያስተሰርያል ማለት ነው። አሁንም ቢሆን በክርስቶስ በኩል ወደ እግዚአብሔር ለሚመጡ ሰዎች ክርስቶስ መሀከለኛ ነው። ክርስቶስ የአለምን ሁሉ ሀጢያት የተሸከመ የእግዚአብሔር በግ ነው። ሰዎች ሁሉ ስለበደሉት በደል ማስተሰሪያ ይሆን ዘንድ እግዚአብሔር ራሱ ያቀረበው ንፁህ ፣ቅዱስና ያለ ነውር የሆነ መስዋዕት ነው።በክርስቶስ በኩል ሆነን ወደ አብ የመግባት ድፍረት አለን። አሜን! ➞ኢየሱስ ክርስቶስ ሀጢያሠታችንን በማስተሰረይ ከዘላለም ሞት የሚያድነን ፣ ወደ እግዚአብሔር የሚያቀርበን በእግዚአብሄርና በኛ መካከል መካከለኛ ሆኖ እኛን ከእግዚአብሔር ጋር ሊያስታርቅ ብቃት እና ውክልና አለው።ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የእርቅ ውላችንና ሠነዳችን ነው። ➫ በክርስቶስ ደም ምክንያት ከ እግዚአብሄር ጋር ሠላም አለን። በሀጢያት ወድቀን ብንገኝ እንደወደቅን እንዳንቀር ከ አብ ዘንድ ለድካማችን ጠበቃ አለን!!ሀሌሉያ ጠበቃ አለን።ጠበቃ ማለት እኛን ከተከሰስንበት ክስ ለማዳን የእኛ በሆነ ነገር ሁሉ ላይ ስለኛ ተወክሎ የሚቆም ማለት ነው። ክርስቶስ ጠበቃችን ነው። የክርስቶስ ክህነት ፍፁም እና ለዘላለም ነው።አሜን እንደዚህ አይነት ሊቀ ካህን ይገባናል ➛ኢየሱስ ክርስቶስ በቀራኒዮ መስቀል ላይ የከፈለዉ የደሙ ዋጋ ለዘላለም ቤዛ ሁኖ፣ ለዘላለም አስታራቂ ሁኖ ለዘላለም አማላጅ ሁኖ የሠው ልጆችን ሁሉ በራሱ በኩል ከእግዚአብሄር ጋር ማስታረቅ ይችላል። ➥የእግዚአብሔር እውነት አንድ ነው እርሱም ወደ ዘላለም ሒወት ለመግባት የሚወድ ቢኖር በክርስቶስ ኢየሱስ /በደሙ/ በኩል እንዲመጣ ነው!! 📖“ስለ እነርሱም ሊያማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራልና ስለዚህ ደግሞ በእርሱ ወደ እግዚአብሔር የሚመጡትን ፈጽሞ ሊያድናቸው ይችላል።” ዕብራውያን 7፥25 📖“አንድ እግዚአብሔር አለና፤ ደግሞም በእግዚአብሔርና በሰዎች መካከል አንድ አስታራቂ አለ፤ እርሱም ሰው የሆነው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤”— 1ኛ ጢሞቴዎስ 2፥5 (አዲሱ መ.ት) 📖“ልጆቼ ሆይ፤ ይህን የምጽፍላችሁ ኀጢአት እንዳትሠሩ ነው፤ ነገር ግን ማንም ኀጢአት ቢሠራ፣ በአብ ዘንድ ጠበቃ አለን፤ እርሱም ጻድቁ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።” — 1ኛ ዮሐንስ 2፥1 (አዲሱ መ.ት) 📖“እርሱ ግን ስለ ኃጢአት አንድን መሥዋዕት ለዘላለም አቅርቦ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀመጠ፥” — ዕብራውያን 10፥12 📖 የእግዚአብሔር ጠላቶች ሳለን በልጁ ሞት ከእርሱ ጋር ከታረቅን፣ ዕርቅን ካገኘን በኋላ፣ በሕይወቱማ መዳናችን እንዴት የላቀ አይሆንም! ይህ ብቻ አይደለም። ነገር ግን አሁን ዕርቅን ባገኘንበት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በእግዚአብሔር ደግሞ ሐሤት እናደርጋለን። ሮሜ 5 ፥10-11(አዲሱ መ.ት) 📖“በመስቀሉ ላይ በፈሰሰው ደሙ ሰላምን በማድረግ በምድርም ሆነ በሰማይ ያለውን ነገር ሁሉ በእርሱ በኩል ከራሱ ጋር አስታረቀ።” — ቆላስይስ 1፥20 (አዲሱ መ.ት) ➫ ኢየሱስ ክርስቶስ አድኖአችኋል ማለት ከነበረባቹ የሀጢያት ህመም ወይንም በሽታ ተፈውሳችሁ ፃዲቅ ሆናችኋል ማለት ነው። ➙ ኢየሱስ ክርስቶስ የሞተበት ዋነኛ አላማውም ይሄ ነው። ❗️ ➙ በረከቶች ሀዲስ ኪዳን ስለ ፅድቅ ብቻ ነው የሚያስረዳን ፣ ፅድቅ እንዴት ሰዎች ጋር እንደሚደርስና ሰዎች እንዴት በእግዚአብሔር ፊት ተመልሰው መቆም እንደሚችሉ ነው የሚያወራው። ሀዲስ ኪዳን ይዞ የመጣው ትልቁ የምስራች ፅድቅ ነው። ፅድቅ ደግሞ በእግዚአብሔር ፊት መቆም የሚቻልበት ድፍረት ወይንም አቅም ነው። 〰️ አንተ በራስህ አቅም ስለማይቻል ይህን ችሎታ ከእግዚአብሔር ለመቀበል በመሀል ፀጋ የሚባል ነገር አስፈላጊ ሆነ። ፀጋ ማለት ፅድቅ የተቀበልክበት መንገድ ነው። አንተ ፃዲቅ የምትሆነው በፀጋ ነው። ማለትም ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሰርቶ በጨረሰው ስራ በኩል ነው። አለቀ! ➙ማንም ሁኑ፣የትም ሁኑ ፣ምንም ሁኑ እንዴትም ሁኑ ወዴትም ጌታ ይወዳቹሀል❗️🥰 ከዛሬ ጀምሮ ህይወቴን ለዚ ጌታ ሰጥቼ ከዚ ጌታ ጋር በፍቅሩ መኖር እፈልጋለሁ የምትሉ ይህንን መልዕክት የምታነቡ ሠዎች። ይህንን ፀሎት ባላቹበት ቦታ ሁናቹ ፀልዩ። ጌታ ኢየሱስ ሆይ በመስቀል ላይ ስለ እኔ ሀጢያት እንደሞትክ በሶስተኛው ቀን ለዘላለም ከአንተ ጋር በሕይወት እንድኖር ከሞት እንደተነሳህ በልቤ አምናለሁ በአፌም እመሰክራለሁ። አንተ ጌታዬ ነህ። አለምን ፣ሀጢያትን፣ዲያቢሎስን ክጃለሁ። ነብሴን ለአንተ አደራ እሰጣለሁ ተቀበለኝ። ስለተቀበልከኝ አመሰግንሀለሁ። አሜን! ፀጋና ሠላም ይብዛላቹ። 🙏ይሄንን መልዕክት አንብባቹ የጨረሳቹ ሼር ሳታደርጉ እንዳታልፉ❗️ 👇👇👇👇👇👇👇 ቻናሉን ለማግኘት @Pure_Christianity @Pure_Christianity @Pure_Christianity @Pure_Christianity
Show all...
ወደ ክብር አገልግሎት እንዴት ልግባ🔥🔥 1⃣.ልብህን አንፃ ⛳️በፍቅር፣በትህትና፣በምህረት የተሞላ ሰው ሁን። 📖ልበ ንጹሖች ብፁዓን ናቸው፥ እግዚአብሔርን ያዩታልና። 2⃣.ፀልይ ⛳️አንተ እግዚአብሔርን ስትፈልግ ብቻ ሳይሆን እርሱ ሲፈልግህ ተገኝለት ⛳️ጥያቄ ማቅረብ ብቻ ሳይሆን ድምፁን መስማት ተለማመድ 3⃣.ህይወትህ በአምልኮ የተሞላ ይሁን፤ 📖ንጹሕ የሆነ ነውርም የሌለበት አምልኮ በዓለምም ከሚገኝ እድፍ ሰውነቱን መጠበቅ ነው። 4⃣.በፍፁም ልብህ እግዚአብሔርን ታመን ⛳️ጥርጣሬ፣አለማመን፣ገደብን ከህይወትህ አስወግድ እርሱ ባሰበልህ ልክ ተጓዝ ፤ ለአሰራሩ ገደብ አታበጅ፤ 📖የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት ቢኖራችሁ ይህን ሾላ፦ ተነቅለህ ወደ ባሕር ተተከል ብትሉት ይታዘዝላችሁ ነበር። 5⃣.ከቅዱሳን ጋር በእውነትና በአንድ መንፈስ ህብረት አድርግ ⛳️አጠገብህ ካለው ሠው ጋር ፀጋን ተካፈል 📖የእግዚአብሔርም ክብር ይገለጣል፥ ሥጋ ለባሹም ሁሉ በአንድነት ያየዋል፥ የእግዚአብሔር አፍ ይህን ተናግሮአልና። 🗞ማቴ 5:8 ዮሐ 10:27 ያዕ 1:27 ሉቃ 17:6 ኢሳ 40:5 @jesusministry
Show all...
🎄 #የማለዳ_ስንቅ የመንፈስ ረሃብ የሚለቅ አምልኮ አድምጡልኝ! @nazrawi_tube @nazrawi_tube
Show all...
ተወለደልን ዘማሪት ቅድስት ካሳ 🎁 Marry Christmas 🎁 sʜᴀʀᴇ ◈JOIN◈ sʜᴀʀᴇ ▷◈ @ZELALEMAWI ◈◁ ── ❖ ── ✦ ── ❖ ──
Show all...
https://youtu.be/8-XPY-oXzaU ────────────── 👇ሰምታችሁ ተባረኩበት
Show all...
. ህፃን ተወልዷል ዘማሪ አብርሃም ሃላኬ 🎁 Merry Christmas 🎁 sʜᴀʀᴇ ◈JOIN◈ sʜᴀʀᴇ ▷◈ @ZELALEMAWI ◈◁ ── ❖ ── ✦ ── ❖ ──
Show all...
. የደስታ ሌት ኢያሱ ተ/ማሪያም 🎁 Merry Christmas 🎁 sʜᴀʀᴇ ◈JOIN◈ sʜᴀʀᴇ ▷◈ @ZELALEMAWI ◈◁ ── ❖ ── ✦ ── ❖ ──
Show all...
. ጌታ ሆይ ተነስ ሙዚቀኛ ክብረአብ ምትኩ NEW GOSPEL SONG sʜᴀʀᴇ ◈JOIN◈ sʜᴀʀᴇ ▷◈ @ZELALEMAWI ◈◁ ── ❖ ── ✦ ── ❖ ──
Show all...
. "የናዝሬቱ ኢየሱስ" ቃልኪዳን ጥላሁን From the Album #እዩልኝ sʜᴀʀᴇ ◈JOIN◈ sʜᴀʀᴇ ▷◈ @ZELALEMAWI ◈◁ ── ❖ ── ✦ ── ❖ ──
Show all...
YouTube ላይ ዝማሬዎችን ለማግኘት
. "እጓጓለሁ" ጋሽ ታደሰ Studio Live Worship sʜᴀʀᴇ ◈JOIN◈ sʜᴀʀᴇ ▷◈ @ZELALEMAWI ◈◁ ── ❖ ── ✦ ── ❖ ──
Show all...
. "እወድሃለሁ" ዘማሪ አንድነት ባይሳ Cover Live Worship sʜᴀʀᴇ ◈JOIN◈ sʜᴀʀᴇ ▷◈ @ZELALEMAWI ◈◁ ── ❖ ── ✦ ── ❖ ──
Show all...
🤔__ለምን ግን❕❔ በመጽሐፍ ቅዱሳች ዘሌዋውያን ላይ ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ◻️እግዚአብሔር ለሙሴ የተናገረው ሙሴም ለእስራኤል ሴቶች እንዲናገር የታዘዘው ቃል አለ፡፡ቃሉም እንዲህ ብሎ ይጀምራል፡፡እግዚአብሔርም ሙሴን እንዲህ ብሎ ተናገረው፦ለእስራኤል ልጆች እንዲህ ብለህ ንገራቸው፦ ሴት ብታረግዝ ወንድ ልጅም ብትወልድ፥ ሰባት ቀን ያህል የረከሰች ናት፤ እንደ ሕመምዋ መርገም ወራት ትረክሳለች፡፡ ◻️በስምንተኛውም ቀን ልጁ ከሥጋው ሸለፈት ይገረዝ።ከደምዋም እስክትነጻ ሠላሳ ሦስት ቀን ትቀመጥ የመንጻትዋ ቀንም እስኪፈጸም ድረስ የተቀደሰን ነገር አትንካ፥ ወደ መቅደስም አትግባ፡፡ዘሌ 12፥1-5 ወደ ቀጣዩ ቁጥር ከመግባቴ በፊት ይሄኛውን አብረን እንመልከት፡፡ሴት ልጅ ብታረግዝ ብሎ ይጀምራል፡፡ ◻️ስለዚህ በዛን ሰዕት ጉዳዩ የሚመለከታቸው ሴቶች ናቸው፡፡ቀጥሎ ወንድ ልጅም ብትወልድ፥ ሰባት ቀን ያህል የረከሰች ናት፡፡እስከ አሁን የሚወራው ስለምትወልደዋ ሴት እንጂ ስለሚወለደው ልጅ አይደለም፡፡ሰባት ቀን የምትረክሰው የምትወልደዋ ሴት ነች፡፡ስለዚህ ቀኑ ስለስዋ የተፃፈ ነው፡፡ሰባት ቀን! ያዙት እንዳትረሱት፡፡ልክ ይሄ ሰባት ቀን አልፎ ስምንተኛው ቀን ላይ ስለ ሚወለደው ልጅ ይናገራል፡፡ ◻️በብሉይ ኪዳን የኪዳን ምልክት ስለሆነው ስለ መገረዝ ወንድ ልጅ ሲወለድ በስምንተኛው ቀን ይገረዝ ስለሚለው የኪዳን ትዕዛዝ፡፡ወረድ ስትሉ ሰባት ቀን ስለምትረክሰው ሴት ደግሞ ይናገራል፡፡ከደምዋም እስክትነጻ ሠላሳ ሦስት ቀን ትቀመጥ ይላል፡፡ይሄ ሁላ በመውለድዋ ምክንያት ነው፡፡ወንድ በመውለድዋ፡፡ቅድም ሰባት ቀን እንደረከሰች ሲነግረን አሁን ደግሞ ሠላሳ ሦስት ቀን መውጣት መንካት፣ ቤተ-መቅደስ መግባት እንደማትችል ይናገራል፡፡ ◻️ሁለቱ ሲደመሩ 7+33=40 ቀን ይቺ ሴት ምንም ነገር ማድረግ እንደማትችል ይነግረናል፡፡ቀኑ ስለ ተወለደው ልጅ ሳይሆን ስለወለደቺው እናት የሚመለከት ነው፡፡ታድያ ለምንድነው አንዳንድ ሃይማኖቶች ይሄንን ቃል ወስደው ህጻናትን የሚያጠምቁበት? ወንድ ልጅ ቢወለድ በአርባ ቀኑ መጠመቅ አለበት ብለው ሲያስጠምቁ ይታያል፡፡እኔን ጨምሮ በአርባ ቀኔ አጥምቀውኝ ነበር፡፡ ይ ቀ ጥ ላ ል S h a r e ' ✳️✳️ @Yezelalemhiywet✳️✳️ ✳️✳️ @Yezelalemhiywet✳️✳️ ✳️✳️ @Yezelalemhiywet✳️✳️
Show all...
በክርስቶስ ኢየሱስ ያለህን ማንነት ጠንቅቀህ እወቅ፡፡ሰይጣን አንተን የሚያይበትና እግዚአብሔር አንተን የሚያይበት መንገድ ፍጹም የተለየ ነው፡፡ሰይጣን አንተን እንደ ኃጢአተኛ ሲመለከትህ እግዚአብሔር ግን በልጁ እንደጸደቅ ፃዲቅ እንደሆንክ ነው የሚመለከትህ፡፡ሰይጣን በባህሪው የእግዚአብሔርን ሐሳብ በተቀራኒ የሚቶረጉምና የሚመለከት የተወዛገበ ፍጥረት ነው፡፡እሱ የሚልህን አትስማ፡፡ስለ አንተ የመናገር ሆነ የመተንበይ ስልጣይ የለውም፡፡አንተ የእርሱ ስላይደለህ የእርሱን ነገር መስማት የለብህም፡፡ለአንተ ዋጋ የከፈለ የራሱ ያደረገህ የዘላለም ወዳጅ አለህ፡፡ኢየሱስ፡፡ማንነትህን ለማወቅ ከፈለክ ኢየሱስን እወቅ፡፡አዲሱ ማንነትህ ያለው በልጁ ውሰጥ ነው፡፡ብዙ ሰዎች በአሮጌው ማንነት እየኖሩ አዲሱን ማንነት ለመኖር ይጥራሉ፡፡ይሄ የሆነው ትክክለኛ ማንነታቸውን ካለማወቅ የተነሳ ነው፡፡አዳማዊ ማንነት ይዘህ አዲስ ኪዳንን ለመኖር መሞከር ሞኝነት ነው፡፡አንተና አዳም ፍጹም የተለያያችሁ ፍጥረት ናችሁ፡፡የምትለያዩት ደግሞ አንተ በሰለጠነ ዘመን በስጋ በመወለድህ ሳይሆን ዳግመኛ የተወለድክበት ዘር የተለየ ስለሆነ ነው፡፡አዳም እንዳንተ ከእግዚአብሔር አልተወለደም፡፡ተፈጠረ እንጂ፡፡ይገርምሃል! አንተ የመለኮት ባህሪይ ተካፍለህ ከእግዚአብሔር ከውሃና ከመንፈስ ዳግመኛ የተወለድክ ድንቅ ፍጥረት ነህ፡፡በአካል ምንም እንኳን አዳምን ብትመስል በውስጥህ ዳግመኛ የተወለደው ማንነትህ ግን ፍጹም ልዩ ነው፡፡እርሱ አዲሱ ማንነትህ ምንም እኳን በሚሞተው አዳምን በሚመስለው አካል ውስጥ ቢኖርም በመጨረሻው ጊዜ የራሱ የሆነ አካል ምድራዊ ያልሆነ ከአፈር ያልተበጀ አካል ይለብሳል፡፡ዘላለምም ከኢየሱስ ጋር ይኖራል፡፡Share it ⚗✳️ @Yezelalemhiywet ✳️⚗ ⚗✳️ @Yezelalemhiywet ✳️⚗ ⚗✳️ @Yezelalemhiywet ✳️⚗
Show all...
የቀጠለ_በእውኑ ግን ይሄ ቃል ስለጥምቀት ያወራልን! እግዚአብሔር ለሙሴ ተናገር ብሎ የነገረው ስለ ህጻናት ጥምቀት ነው? ለምትወልደው ሴት የተፃፈውን ቀን ወስዶ ለሚወለደው ልጅ ማድረግስ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነው? አይገባኝም፡፡ቃሉ ሲጀመር ከላይ እስከ ታች ስለ ጥምቀት አያወራም፡፡ስለመርከስ እንጂ፡፡ታድያ በምን ሒሳብ ይሄ ሊሆን የቻለው!? ◻️ሁለተኛው ደግሞ እንዲህ ይላል፡ ሴት ብታረግዝና ሴት ልጅም ብትወልድ እንደ መርገምዋ ወራት ሁለት ሳምንት ያህል የረከሰች ናት፤ ከደምዋም እስክትነጻ ድረስ ስድሳ ስድስት ቀን ትቀመጥ።ይሄ ደግሞ ወንድ ልጅ ከምትወልደው ቀን በሁሉም በለጥ ይላል፡፡ከወለድ በኃላ በመርከስ በአንድ ሳምንት ይሄኛው ይበልጣል፡፡ከቤት ባለመውጣትና ቤተ መቅደስ ባለመግባትም ወንድ ልጅ ከወለደቺው ሁለት እጥፍ ቀን ይበልጣል፡፡ ◻️ሴት ልጅ ብትወልድ ሁለት ሳምንት ትቀመጥ ማን? የወለደቺው ሴት፡፡ቀኑን ያዙት፡፡ከደምዋም እስክትነጻ ስድሳ ስድስት ቀን ትቀመጥ ይላል፡፡ሁለት ሳምንት 14 ቀን ነው፡፡14+66=80 ቀን፡፡እንግዲህ ይሄንን ቀን ሴት ልጅ ስትወለድ በሰማንያ ቀንዋ መጠመቅ አለባት የሚል አንድምታ አለውን? ስለ ውሃ ጥምቀትስ ያወራልን? አያወራም፡፡እንኳን ስለ ጥምቀት ስለሚወለዱት ህጻን እራሱ አያወራም፡፡ስለምትወልደው እንጂ፡፡በብሉይ ኪዳን ያለ ቃል ነው፡፡ ◻️እሺ አይቻልም ግን እንደምንም ልክ አንዳንድ ሃይማኖቶች እንዳደረጉት ቀኑን ለልጆቹ ሰጥተን የሌለውን ያልተፃፈውን በዛን ቀን ነው በውሃ መጠመቅ ያለባቸው ብንል፡፡አዲስ ኪዳን ላይ ያለውን ቃል እናፈርሳለን፡፡ያመነ የተጠመቀ ይድናል፡፡ማቴ 16፥16 እምነት ከመጠመቅ ቀዳሚ ነው፡፡ሰው ሳያምን ቢጠመቅ ጥምቀቱ በዛው ውሃ ይበለዋል እንጂ ትርጉም የለውም፡፡ያመነ ካለ ለመጠመቅ ማመን ግድ ነው፡፡ተጠምቆ ማመን አይቻልም፡፡ ◻️ምን አምነህ ትጠመቃለህ! ለመጠመቅ ማመን ከቀደመ ለማመንስ ምን ይቀድማል? ሮሜ 10፥17 እምነት ከመስማት ነው፥ መስማትም ከእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡ለማመን ቃሉን ምስማትና ማንበብ ወንጌልን መስማት ያስፈልጋል፡፡በአጭሩ ስለ አዳኙ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል መስማት ነው፡፡ ◻️ታድያ ፈጣሪ አላየንም ብለን ለወለደቺው ሴት የተፃፈውን ቀን አዙረን ለተወለዱት ብንሰጥና ብናጠምቅ ስለምን ሳያምኑ ይጠመቃሉ? ከመጠመቅ በፊት እኮ ማመን ይቀድማል፡፡ህጻናቱ በዛን ሰዕት ወንጌል ሰምተው ነውን? በነዛ ቀናት ኢየሱስ አዳኝ ነው ብለው አምነው ነውን? አይደለም፡፡ስለዚህ የቃሉን እውነት ወደ ተፃፈለት ቦታ ብንመልሰው ይሻላል፡፡ S h a r e ' ✳️✳️ @Yezelalemhiywet✳️✳️ ✳️✳️ @Yezelalemhiywet✳️✳️ ✳️✳️ @Yezelalemhiywet✳️✳️
Show all...
🪨 ከንቱ❕ ◽️እግዚአብሔር ከፈጠራቸው ፍጥረቶች ከሰው ልጅ በስተቀር ሌሎቹ ሁሉ ጊዜአዊና ጠፊ ናቸው፡፡አሁን የምናየው ሰማይና ምድር እራሱ ጊዜአዊ የሆነ የሚወገድ ነው፡፡ግን የሰው ልጅ ጊዜአዊ በሆነው አለም እየኖረ ለከንቱ ነገር ሲታክት እናየዋለን፡፡ከንቱ በሆነው አለም ውስጥ እየኖረ ለከንቱ ኑሮ እጎመጀ እድሜውን በከንቱ የሚጨርስ ሰው! ◽️በዚህ ምድር የሚኖረው ቆይታ ጥቂት እንደሆነ እያወቀ ነፍሱን በከንቱና በሚጠፋ ነገር ለማስደሰት ደፋ ቀና የሚል፤ ለነፍሱ የሚያስፈልጋት የሰማዩ ጌታ የሕይወት ምንጭ የሆነው ኢየሱስ ሁኖ ሳለ ነገር ግን ሕይወት ለማይሆናት ለደቂቃ የሚያስደስታት ነገር ብቻ ጊዜውን በከንቱ ያሳልፋል፡፡ለምን ነፍስን ከንቱ በሆነ ነገር ታጓጓታለህ? የሚያስፈልጋት አንድ ሁኖ ሳለ፡፡ ◽️አንድ ታሞ የሞተ ሰው በዛን ሰዕት ምን የሚያስፈልገው ይመስልሃል? ገንዘብ፣ እውቀት፣ ሐብት፣ የተመቻቸ ኑሮ፣ ዝና፣ ተፈላጊነት፣ ሐብታም ቤተሰብ፣ መኪና ምድነው የሚያስፈልገው? ይገርምሃል ለሞተ ሰው ይሄ ሁላ ከንቱ ነገር አያስፈልገውም፡፡እርሱ በዛን ሰዕት የሚፈልገው አንድ ነገር ብቻ ነው ለሞተው ማንነቱ ሕይወት የሚሰጠው፡፡እነዚህ ሁሉ ሕይወት ሊሰጡት አይችሉም፡፡ ◽️ደስታ ሊሰጡት አይችሉም፡፡ምክንያቱም ሰውየው ሙት ስለሆነ፡፡በሞተ ማንነት እነዚህ ነገሮች ቢኖሩህ ምን ይጠቅምሃል! ሕይወት ሊሆኑህ አይችሉም፡፡ይልቁንስ ሞትህን ያፈጥኑት ይሆናል፡፡“ከፀሐይ በታች የተሠራውን ሥራ ሁሉ አየሁ፤ እነሆም፥ ሁሉ ከንቱ ነው፥ ነፋስንም እንደ መከተል ነው።መክ 1፥14 ሁሌ የሚደንቀኝ ቃል ነው፡፡እስኪ ንገረኝ በዚህ አለም ላይ ከንቱ ያልሆነ ነገር!? ጌታን ከመከተል ውጪ፡፡በጌታ ከመሆን ውጪ፡፡ ◽️በእርሱ ከማመን ውጪ፡፡ገንዘብ አገኘህ ሐብታም ሆንክ መኪና ገዛህ ቤትም ገዛህ! እሺ ከዛስ ብልህ! ከዛማ ጥሩ ትዳር እመሰርታለሁ! እሺ ከዛስ? ያውው ልጆች እንወልዳለን! ከዛስ? ከዛማ ሁሉም እንደሚያረጀው እናረጃለን፡፡ከዛስ? ቀናችን ሲደርስ እንሞታለን! ትለኛለህ፡፡አየህ ያሁላ ነገር ከጊዜ በኃላ ከንቱ ነው፡፡በዛን ሰዕት አንተም ስላለህ ዘላለም አብሮህ የሚቆይ ይመስልሃል፡፡ ◽️ነገር ግን ከንቱ ነገር ነውና አብሮህ ዘላለም አይኖርም፡፡ለነፍስ የሚያስፈልጋት ከሞትክ በኃላ ስላለው ከዛስ ለሚለው ጥያቄ መልስ የሚሆን ሕይወት የሚሆነው ጌታ ብቻ ነው፡፡እርሱ ሕይወት ይሆናታል፡፡በስጋ ብትሞት እንኳን ሕይወት የሚሆናት ኢየሱስ ነው፡፡መኖርዋንም በእርሱ የሕይወት ምንጭ ዘላለም ከሕይወትዋ ጋር ትኖራለች፡፡የኢየሱስ ሕይወትነት ማንም ሰው ከሚተነፍሰው እስትንፋስ የሚበልጥ የተለየ ነው፡፡ ◽️በምድር የምተነፍሰው እማ ለሁሉም ሰው የተሰጠ ነጻ ስጦታ ነው፡፡ሰው የተባለ ፍጥረት ሁሉ ያመነም ያላመነም እኩል ይተነፍሳል፡፡ነገር ግን የእርሱ ሕይወትነቱ ዘላለማዊ መጨረሻ የሌለው መኖር የሚያኖር መሆኑ ነው፡፡ኢየሱስ ሕይወት ለሆናቸው ሁሉ ዘላለም የሚኖሩት በኦክስጂን ሳይሆን በእርሱ ነው፡፡በምድር ሰው ያለ ኦክስጂን መኖር እንደማይችል ሁሉ፤ በሚመጣው አለም ላይም ሰው ያለ ኢየሱስ ዘላለም መኖር አይቻልም፡፡ S h a r e ' ✳️✳️ @Yezelalemhiywet✳️✳️ ✳️✳️ @Yezelalemhiywet✳️✳️ ✳️✳️ @Yezelalemhiywet✳️✳️
Show all...
' ኢየሱስ ክርሰቶስን እናስብ "በወንጌል እንደምሰብከው፣ ከሙታን የተነሣውን፣ ከዳዊት ዘርም የሆነውን፣ ኢየሱስ ክርስቶስን እስብ።" (ጢሞ 2:8-13) ጸሐፊው ጳውሎስ በማይመች ጊዜና ሁኔታ ውስጥ፣ ከእስር ቤት ሆኖ፣ ኢየሱስ ክርስቶስን አሰበ። ያሠረውና ያሣሠረው ወገን ክርስቶስን ለማስረሣት ተጠባብቆ ሊሆን ይችላል። ጳውሎስ እንኳንስ ለራሱ ሊረሣው፣ ጢሞቴዎስን ያሳስበዋል። ለራሱ ጸንቶ፣ ለጢሞቴዎስ የሚያጸና ቃል ይጽፍለታል። በምዕራፉ ጅማሬ ላይ "...በርታ" ብሎታል። እዚህ ጋ ደግሞ "አስብ" (አስታውስ) ይለዋል። ብዙ ነገራችን የሚጀምረው ከማሰብ ነው። ኢየሱስ ክርስቶስንም ለማገልገል የሚቻለው አስቀድሞ በማሰብ ነው። ስለዚህ ማሰብም፣ ማሳሰብም አስፈላጊ ነው። ዛሬ ይህን የማድረግ ኃላፊነት የእኛ ነው። እያሰብን እናሳስብ ዘንድ። ይህ የወንጌሉን ምስክርነት በጽናት ለመቀጠል ያግዛል። ኢየሱስ ክርስቶስን ስናስብ (2 ጢሞ:8) 1. በወንጌል የተሰበከውን - ከሐዋርያቱ ዘመን ጀምሮ የወንጌል ዋና ርዕስ ሆኖ የኖረውንና የሚኖረውን፣ 2.ከዳዊት ዘር የሆነውን - በብሉይ መጻሕፍት የተመሰከረለትን መሢሕ፣ ሰው በመሆንም መከራ የተቀበለውን፣ 3.ከሙታን የተነሣውን - ከዘላለም እስከ ለዘላለም በሕይወት የሚኖረውን -ጌታና አምላክ የሆነውን፣ 4.የዘላለም ሕይወትና ክብር የሚያስገኘውን (10) 5.የማይለወጥ ማንነት ያለውን - የታመነ ሆኖ የሚኖረውን እናስባለን(13)። ይህን ጌታ በዚህ መንገድ ብናስበው መልካም ይሆናል። ኢየሱስ ክርስቶስን ማሰብ ጸንቶ ለመቆምም፣ በሕይወት ለምልሞ ለማገልገልም ይጠቅማል። በመሆኑም፣ በመከራ የጸናውን፣ መከራና ሞትን ድል በመንሣት በሰማያት በእግዚአብሔር አብ ቀኝ በክብር የተቀመጠውን፣ ኢየሱስ ክርስቶስን ልናስብ ይገባናል(ቆላ 3:1። ዕብ 12:3)። የሰይጣን ምኞቱ መከራን በመጠቀም የአማኝን እምነት ማዳከም፣ ክርስቶስን ማስረሣት፣ ተስፋ ማስቆረጥ፣ የወንጌሉንም አገልግሎት ማሰናከል ወይም "ማሠር" መሆኑን አንዘንጋ። "የእግዚአብሔር ቃል ግን አይታሠርም"(9)። ኢየሱስ ክርስቶስን እናስብ። በሕይወትም እንኑር። ሞትና ትንሣኤውን በመንገር፣ በሞት ጥላ ውስጥ ላሉትም የምሥራቹን ቃል እናሰማ። በዚህ ቃል፣ በክርስቶስ ወንጌል፣ ከሞት የሚያመልጡ ገና ብዙዎች አሉ (የሐዋ 18:10) ። ኢየሱስ ክርስቶስ የሃሳባችን ማዕከልና የወንጌላችን ዋና ርዕስ ይሁን፤ በመሆንም ይቀጥል። ምክንያቱም፣ በኃጢአት ለወደቀውና ለተጨነቀው የዓለም ሕዝብ የሚሆን መድኃኒት ከኢየሱስ ክርስቶስ ውጭ ሌላ ማንም የለም ። "እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ" የተባለለትም እርሱ ብቻ ነው(ዮሐ 1:29)። "መዳንም በሌላ በማንም የለም፣ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና" (የሐዋ 4:12)። ኢየሱስ ከኃጢአትም ከሞትም ያድናል። የመስቀል ደሙ ከእግዚአብሔርም ከሰውም ያስታርቃል። ይቅርታን ያስገኛል። ፍቅርን ይመልሳል። እውነተኛውን ሰላም እውን ያደርጋል(ኤፌ 2፡ 13-17)። የሰላምን አለቃ ክርስቶስን አምኖ የሚቀበል ይህን ሊያረጋግጥ ይችላል። እኛስ ምን እናድርግ? በጊዜውም አለጊዜውም፣ ኢየሱስ ክርስቶስን በትጋት የምናስብ እንሁን። እንመስክር። ማሰቡ ወደ ማገልገል ያድርሰን። ይህን ለማድረግ የሚያበረታን የኃይል መንፈስ፣ መንፈስ ቅዱስ፣ ዘወትር ይርዳን። አሜንፓስተር ተስፋዬ ጋብሶ ለወዳጆ ያጋሩ @NAZRAWI_TUBE
Show all...
"አቤቱ፥ አንተ ለትውልድ ሁሉ መጠጊያ ሆንህልን። ተራሮች ሳይወለዱ፥ ምድርም ዓለምም ሳይሠሩ፥ ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ አንተ ነህ።" (መዝ. 90:1-2) እግዚአብሔር ትላንትናን፣ ዛሬንና ነገን በአንድ ጊዜ በእጁ የያዘ አምላክ ነው! እርሱ በመገረምም ሆነ በድንጋጤ አይያዝም፤ ያለፈውን በጸጸትና በቁጭት፣ የወደፊቱንም በሥጋት ወይም በተስፋ አይጠብቅም! እርሱ የፍጥረት መገኛና ዘላለማዊ ነው። በሰማይንና በምድር ሁሉ ላይ ሉዓላዊ ነው፤ ክብር ጎድሎበት፣ ፍጥረትን ክብር አይለምንም፤ በማንም አይደገፍም፤ ለሥራውና ውሳኔው ትክክለኛነት ማንንም አያስፈቅድም፤ ማስተዋሉ ፍጹም፣ ምክርም ማንንም አይጠይቅም፤ እውቀት አይጨመርለትም፤ አልገባኝም አሰርዱኝ አይልም - ነገሮች ሳይጀመሩ ፍጻሜያቸውን ያውቃልና! አውጉስጢን እንዳለው፡ “እግዚአብሔር እንተ ዘላለማዊና የማትለወጥ ነኽ፤ የእኛ “ዛሬ” ያልቃል፤ “የአንተ ዛሬ” ግን ዘላለማዊ ነው። በአንተ “ዛሬ” ውስጥ ሁሉ ተከናውኗል። በአንተ “ዛሬ" ውስጥ፣ የእኛ ትላትናን፣ ነገን እና ከነገ በኋላ ያለው ሁሉ በአንድ ጊዜ ተይዟል። (St. Augustine of Hippo, Confessions: 1.6.10) በዚህ ተለዋዋጭ ዓለም፤ የሚታመኑበትና የማይለወጥ እርሱ ብቻ ነው። ያለፈውን 2013 ዓመት ዞር ብለን ስናስብ፤ ለካስ የተጨነቅንባቸው፣ ስጋት ላይ የጣሉንና ለጊዜው መልስ ያጣንባቸው የሕይወት ኹነቶች በሙሉ በእርሱ ሉዓላዊ ማዕቀፍ ውስጥ ነበር የተያዙት። በርግጥም "ያልጠፋነው ከእግዚአብሔር ታላቅ ምሕረት የተነሣ ነው፤ ርኅራኄው አያልቅምና።" (ሰቆቃወ 3:22)። ክብር ለስሙ ይሁን! እግዚአብሔር አገራችንን ይባርክ፤ በሰላሙም ይጠብቅ። መልካም ዐዲስ ዓመት! . ግርማ በቀለ (ዶ/ር) @nazrawi_tube
Show all...
"መልከ ፀዴቅ"New Ethiopian Gospel Song 2021 Ebba Daniel,Beruk Asefa,Abenezer Dejene,Abraham Halake ---- ድንቅ ዝማሬ ተጋበዙልኝ😊 @nazrawi_tube
Show all...
#ኃይላችን_ለቤት_ሥራችን ቤተክርስቲያን በዚህ በአሁነኛው ዘመን እንደ ስሕተት ትምህርት እየተገዳደራት ያለ ሌላ ነገር ያለ አይመስለኝም፡፡ የስልጡኑ ዓለም ስይጥንና ጫና ውስጥ ስለከተታት ሁሉን አለዝቦ ማየትን ልማዴ ብላለች፡፡ ከጊዜ ወደ ጊዜ የርዕቱ አስተምህሮ ጉዳይ ግድ የማይሰጣቸው አገልጋዮች (መጋቢዎች እና መሪዎች) ጤናማ በምንላቸው አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ እየበዙ ነው፡፡ ፕሮግራሞች እንዴት ባለ ሁኔታ ይድመቁ እንጂ፣ እንዴት ያለ ይዘት ያለው ነገር ይቅረብባበቸው የሚለው ለብዙዎች አሳሳቢ እየሆነ አይደለም፡፡ እንዲህ አይነቱ ለዘብተኝነት ከቀን ወደ ቀን እየባሰበት ይታያል፡፡ መጽሐፉ ስለ ርዕቱ አስተምህሮ የሚሰጠውን ዋጋ ያህል በመሪዎች አካባቢ እየተሰጠ አይደለም፡፡ ፕሮግራም መር የሆነው የቤተክርስቲያን መርሐ ግብር መልኩ የተመሳቀለ ኾኗል፡፡ ትኩረት ለፕሮግራሞች ድምቀት ብቻ እየተሰጠ ስለሆነ፤ በእውነተኛው የክርስትና ሕይወት ስር የመስደድ ጉዳይ ያለፈበት ጉዳይ መስሏል፡፡ በቤተክርስቲያን ቀድሞ በነበረ ልማድ፣ አገልጋዮች ከሌላ ስፍራ ለመጋበዝ “ማነው? ምን ያምናል? የት አጥቢያ ያገለግላል? ሕይወቱ ምን ይመስላል…” የሚሉ ቅድመ ጥያቄዎች ነበሩ፤ በነኝህ መስፈሪያዎች ሚዛን የማይደፋ አገልጋይ፣ አገልጋይ ለመሰኘት የሚበቃም አልነበረም፡፡ በዚህኛው ጊዜ ግን ማንን ብንጠራ ሰው ይሰበሰባል? የሚለው ከንቱ ሰው ተኮር እሳቤ ሚዛን ደፍቶ ይታያል፡፡ ስለዚህም አየሩን ሞልቶ ያሉ ዘመነኞች እዚም እዛም ሲራወጡ ይስተዋላል፡፡ በዚህም ቤተክርስቲያን መለኮታዊ አደራዋን ሰከን ብላ ከመፈጸም ይልቅ በድግስ እየባተለች አለች፡፡ ምእመናንም ቃርሚያ ፍለጋ ከዚህ ወደ እዛ የሚንከራረቱ ስለሆኑ ቤተክርስቲያን የጋራ ምእመን እንጂ እውነተኛ ደቀመዛሙርት የሏትም፡፡ ነገሩ ለሕዝባችን ምን ያስፈልጋል ከሚለው መሰረታዊ አስፈልጎት ተንሸራትቶ፤ አገልግሎት ገበያ ተኮር ሸቀጥ ኾኗል፡፡ ይህም ደግሞ ቤተክርስቲያንን ከቀን ወደ ቀን እየናጣት ያለ ወቅታዊ ተግዳሮት እንደሆነ እያየን ነው፡፡ እና ምን ይሻላል? የተባለ እንደሁ እንደ እኔ ከሁሉ ቅድሚያ ቤተክርስቲያን ወደ ተልእኮዋ ማተኮር አለባት ብዬ አስባለሁ፡፡ ቤተክርስቲያን ቀዳሚ ሥራዋ ወቅታዊ ድግሶችን ማጧጧፍ አይደለም፡፡ ዘመን አይሽሬ (የማይዘምንም፣ ዘመን የማያልፍበትም) ተልእኮ አላት፡፡ እርሱ ተልእኮ የሰዎች ጊዜያዊ ደስታ ላይ ያረፈ አስረሽ ምቺው አይደለም፤ ይልቁን ቅዱሳንን ለክብር ቀን የመሞሸር ትልቅ መለኮታዊ አደራ ነው፡፡ ይህም ደግሞ ደቀ መዝሙራዊ አገልግሎትን አድምቶ በመሥራት፤ በዚህ ድካም የሚገኝ ነው፡፡ እርግጥ ይህ ወቅታዊ ድግሶችን እየደገሱ ሕዝብ እንደመሰብሰብ ቀላል አይደለም፡፡ ቢሆንም ቤተክርስቲያን በምድር ያለችው ከዚህ ላነሰ ጉዳይ አይደለም፡፡ በመሆኑም ሙሉ ኃይሏን ለወንጌል አገልግሎት እና ደቀመዝሙር ለማድረግ ልታውለው ይገባታል፡፡ መጋቢ ስንታየሁ በቀለ @nazrawi_tube
Show all...
አለመጸለይን እንዴት እናሸንፈው? በጸሎት ዙሪያ ድንቅ መጽሐፍ የጻፉና ብዙ ግሩም መጣጥፎች ያሏቸው Timothy Keller (መጽሐፉን ፈልጉና አንብቡት)፣ “ጸሎት ነገር መለኮትን ወደ ልምምድ ይቀይራል (Prayer turns theology into experience)" ብለው ተናግረዋል፡፡ Soren Kierkegaard ደግሞ “ጸሎት የሚጸልየውን ሰው ይለውጣል (Prayer changes the one who prays)” ብሏል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስም በተለያዩ ስፍራዎች እንደሚያስተምረን፣ ጸሎት እጅግ ብዙ ጥቅሞች አሉት፡፡ ታዲያ ጸሎት በዘላቂነት ይጠቅመን ዘንድ፣ ተዘውታሪነቱ እየጨመረና መጠኑ (its intensity) እየጠለቀ መሄድ ይኖርበታል፡፡ ቢሆንም ፍሬያማ የሆነ ጸሎት መጸለይ አንደ ቀላል ተግባር መታየት የለበትም፡፡ ትግል አለው፡፡ ተግዳሮቶች አሉት፡፡ ትንቅንቅ አለው፡፡ አንዳንዴ ግብ ግቡ ገሃድ ነው፡፡ አንዳንዴ ደግሞ ስውር ነው፡፡ ያለውን ውስጣዊም ሆነ ውጫዊ ተጽእኖ ተቋቁሞ ለመጸለይ የጸሎትን ትሩፋት በሚገባ ማወቅን ይጠይቃል፡፡ ያለ ጌታ ምንም ማድረግ እንደማንችልም አጥብቆ መረዳትንም የሚሻ ጉዳይ ነው። እኛ ሰዎች፣ by default ቅኝታችን አለመጸለይ ነው፡፡ ማለትም በቀላሉ ያንን መንፈስ ቶሎ አናገኘውም፡፡ በሌላ አገላለጽ ቶሎ ለጸሎት የመነሣሣት ችግር አለብን፡፡ ለመሆኑ ቲቪውንና ሞባይላችንን ወዲያ ብሎ መጸለይ ቀላል ነውን? በፍጹም! በዚያ ላይ ‘አጅሬው’ ቀልባችንን እያካለበ ለጸሎት ጉልበታችንን ሳናጥፍ እንድንውልና እንድናድር የሚያደርገን ጊዜ ብዙ ነው፡፡ ይኼ መቼም የብዙዎቻችን ድካም ነው፡፡ ታዲያ እንዴት ነው ውጤታማ (ውስጣዊ ለውጥ የሚያመጣ) ጸሎት መጸለይ የሚቻለው (ተግዳሮቶቹን አሸንፎ)? ከላይ የጠቃቀስኳቸውን ችግሮች ማሸነፊያው መንገድ አንድ ነገር ብቻ ነው˗˗ዲሲፕሊን/ "ስለ ንዝነዛው ተነሥቶ የሚፈልገውን ሁሉ ይሰጠዋል።” (ሉቃ.11፥8) እንዲል ቅዱስ ቃሉ፡፡ “Action---->Habit---->Character” የሚለውን በውጤት ሂደት የተሰናሰለ መርሕ እንደ ወረደ መተግበር አለብን፡፡ ማለትም ቢጥመንም ባይጥመንም፣ ቢሰማንም ባይሰማንም፣ በቁርጠኝነት በእግዚአብሔር ፊት መሆን ይኖርብናል—አዘውትረን፡፡ ያንን ጨክነን ደጋግመን ከተገበርነው፣ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ፣ እየተለመደና እየጣፈጠ ስለሚሄድ፣ ውሎ አድሮ ትግል መሆኑ ይቀራል፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ “ከማመስገን ጋር በጸሎት እየነቃችሁ ለእርሱ ትጉ።” እንዲሁም “በጸሎትና በልመናም ሁሉ ዘወትር በመንፈስ ጸልዩ፤ በዚህም አሳብ ስለ ቅዱሳን ሁሉ እየለመናችሁ በመጽናት ሁሉ ትጉ፡፡” (ቈላ.4፥2፤ ኤፌ.6፥18) ብሎ የሚመክረው ተግዳሮቶቹን ሁሉ አስቦ እንደ ሆነ አምናለሁ፡፡ የማሸነፊያውም መንገድ በግልጽ ቋንቋ˗˗“በመጽናት ሁሉ ትጉ” የሚለው መጽሐፍ ቅዱሳዊ መርሕ ነው! ሌላ ምንም አቋራጭ መንገድ የለውም! ጸሎት:-ጌታ ሆይ በዚህ ክፉ ዘመን ወደ አንተ የበለጠ እንድንጠጋ ጸጋህን አብዛልን! መልካም ቆይታ ተባረኩልኝ! በቀለ በላቸው @nazrawi_tube @nazrawi_tube
Show all...
#መንፈስ_ቅዱስ_ይፀልይልናል!! 😊 "እንዲሁም ደግሞ መንፈስ ድካማችንን ያግዛል፤ እንዴት እንድንጸልይ እንደሚገባን አናውቅምና፥ ነገር ግን መንፈስ ራሱ በማይነገር መቃተት ይማልድልናል፤" (ሮሜ 8: 26) 1. "መንፈስ ድካማችንን ያግዛል!" - የሚለው ከሥጋ ዝለትና ስንፍና የሆነ መጸላይ ያለመቻል ድካም አይደለም:: ይልቁን "እንዴት እንድንጸልይ እንደሚገባ አናውቅምና" ከሚለው እውነት ጋር የተሳሰረ እንጂ:: "እንዴት መጸለይ እንዳለብን ያለማወቅ ድካምስ ምንድነው!?" ይህ ክፍል ከቁጥር 18-39 ካለው አውድ ጋር ተሳስሮ ነው መነበብና መፈታት ያለበት:: ሐዋሪያው ጳውሎስ አጽናፈ-ዓለሙ ከእኩይና መከራየተነሳ በሥቃይ ሲቃ እና መቃተት ውስጥ እንደሆነ ይነግረናል:: በመሆኑም ፍጥረት በሙሉ ይቃትታል (ቁ. 22) ይላል:: ቀጥሎም እኛ አማኞች እንቃትታለን (ቁ. 23) ይላል:: በዚህ ሂደት ውስጥ ፍጥረት በሙሉ የሚቃትትበትን እና አማኞች የሚቃትቱበትን ተመሳሳይ ሥቃይ መንፈስ ቅዱስ አማኞች ውስጥ ሆኖ ይቃትታል (ቁ. 26) ይላል:: "በእንባ የራሴን ሲሞታ: ላኩኝ ደብዳቤ ለጌታ" እንዲል ዘማሪ ዶ/ር ደረጀ ከበደ አንዳንዴ መከራና ሥቃዮ እጅግ ከብዶን ከእንባ በቀር የምንገልጥበት ቃላት እናጣለን:: የፍፁም ቤዛዎት ተስፋ እየደበዘዘ ሕይወት ትርጉም ዐልባ ቅዥት ይሆንብናል:: አዕምሯችን ማሰብ አቁሞ አንደበታችን ዲዳ በመሆን ስሜታችን ደንዝዞ ማድረግ የምችለው እንባ ማፍሰስ ብቻ ይሆናል:: ይህም የመከራና ሥቃዮን ምንጭና ትርጉም ካለማወቅ "ለምን ይህ ሁሉ ደረሰብኝ?" ለሚል ጥያቄ ትርጉም ያለው ምላሽ ከማጣት የሚመጣ ነው:: እናም የእኩይና ሥቃይ ምስጢር በአዕምሯችን መረዳትና በቃላት ማስረዳት የማንችል ይሆንና የሕመሙን ክብደት ለእግዚአብሔር የሚናቀርብበት ቋንቋ እናጣለን:: እናም እንዴት መጸለይ እንዳለብን ግራ ይገባናል:: መንፈስ የሚያግዘው ድካማችን ይህ ሰው የመሆንና የሥቃዮን ምስጢርና የሲቃውን ክብደት መግለጽ ያለመቻል ውስንነታችንን ነው:: በመከራና ሥቃይ ውስጥ ያለውን የእግዚአብሔርን መግቦታዊ አሰራርና ፈቃድ አናውቅም:: እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ግን ያውቃል:: በመሆኑም መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን ሆኖ ይቃትታል:: ወደ እግዚአብሔር ይጸልይልናል ይማልድልናል:: ያ የመንፈስ ቅዱስ ጸሎት እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የሆነ ጸሎት ነው:: በመሆኑም እግዚአብሔር ሰምቶ በመከራና ሥቃያችን እገዛና መጽናናትን ይሰጣል!! 2. "የማይነገር መቃተት" ብዙ ሰዎች መንፈስ ቅዱስ በአማኞች ውስጥ ሆኖ በመከራና ሥቃያቸው ወቅት ወደ እግዚአብሔር ለመጸለይ ቋንቋ ባጡበት ጉዳይ ወደ እግዚአብሔር የሚደርገውን ጸሎት "ከአማኞች በልሳን መጸለይ" ጋር ወይንም ጳውሎስ ወደ ሰማይ ተነጥቆ የማይነገር መገለጥ ካየው ክስተት ጋር ያዛምዳሉ:: ጳውሎስ ሁለቱንም እያለ አይደለም:: ለዚህም ነው ምሁሩ ፍራንክ ቴልማን "የማይነገር መቃተት ልሳንን ወይንም ወደ ሰማይ ተነጥቆ በሰው ቋንቋ መግለጥ የማይቻል መገለጥ ማየትን አያመለክትም" የሚሉት:: በሌላ መልኩ ደግሞ ቴልማን እንደሚለውና ዳግላስ ሞ እና ጎርደን ፊ እንደሚስማሙት "የመንፈስ በማይነገር መቃተት መማለድ አማኞች በመከራና ሥቃያቸው ወቅት መጸለይ እንዲችሉ መንፈስ ቅዱስ ይገፋፋቸዋል" ማለትም አይደለም!! ጳውሎስ እያለን ያለው "መንፈስ ቅዱስ ራሱ በማይነገር መቃትተ ወደ እግዚአብሔር ይማልድልናል" ነው:: ይህም ከመከራና ሥቃዮ ክብደትና ምስጢርነት የተነሳ ከእንባ በቀር በቃላት የማይገለጥ ሲቃ ውስጥ ሆነን ስንቃትት ቋንቋ ባጣንለት ጉዳይ - እኛ ቃላት ቢኖረን ኖሮ ለእግዚአብሔር መግለጥ በምንችልበት ልክ ራሱ መንፈስ ቅዱስ በእኛ ፋንታ ሆኖ ለእግዚአብሔር ጸሎታችንን ያደርሳል ማለት ነው:: ልብንም የሚመረምረው እና የመንፈስ አሳብ ምን እንደሆነ የሚያውቀው እግዚአብሔር የመንፈስ ቅዱስን በመቃተት ሲቃ የተደረገ ጸሎት ሰምቶ ይረዳናል: ያግዘናልም:: በመሆኑም ነው ተሃድሶአዊው ምሁር ጆን ሙሬይ "አማኞች ሁለት የመለኮት አማላጆች አሏቸው:: ኢየሱስ ክርስቶስ በሰማይ በመለኮት ሸንጎ ሲያማልድላቸው መንፈስ ቅዱስ በልባቸ ውስጥ ባለ ፍርሃትና ስጋት ላይ ያማልድላቸዋል" ያለል። #Alex_zetse'at @nazrawi_tube @nazrawi_tube
Show all...
ቤዛዬ ነው ስልህ! በይሁዳ ቤተልሔም በአናጢው ዮሴፍ ቤት ተወልዶ ያደገው ያ ብላቴና ፥ እንደ እብራዊያንም የመንጻት ልማድ በስምንተኛው ቀን ሲገረዝ የበግ ጠቦትን መሰዋት ካልቻለ ይልቁኑ የእርግብ ጫጩቶችን ካቀረበ ጉስቁል ቤተሰብ መሃል የኖረ እሱ የአለማቱ ጌታ፥የመላለሙ ፈጣሪ ፥ የፍጥረቱ ሁሉ ገዢ ነው እያልኩህ ነው። ወንድን ከማታውቅ ታዳጊ ወጣት፤ ትውልድ ሁሉ ብጽእት ከሚላት ድንግል የተወለደ እሱ በህይወት ለመሰንበት የእናቱ ጡቶች ላይ ጥገኛ ሆኖ ቢገኝም ህያዋን ሁሉ የሚደገፉበት የህይወት ሁሉ ራስ ነው እያልኩህ ነው። ሽንት ጨረቁን እናቱ የቀየረችለት ያ ኢየሱስ ከዋክብትን በስም የሚጠራ፣ ነጎድጓድ የሚታዘዝለት ሃያል ነው። ከፈለገህ ነሆለል ነህ በለኝ አሊያም ወፈፌ። ጌታዬ ብዬ ግን ምሰግደው ለእሱ ነው! በእድሜው ማለዳ የንጉስ ድንፋታን ሸሽቶ ወደ ግብጽ በስደት የወረደ እሱ የነገስታትን ልብ እንደ ፈሳሶች ወደ ፈለገበት የሚያቀና ነው። በመጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ በዮርዳዮስ የተጠመቀ እሱ ባህር አይታ የሸሸችው፣ ዮርዳኖስም ወደ ኋላ የሚሸሽለት ራሱ ነው። "የሰማይ ወፎች ጎጆ፣ ቀበሮዎችም ጉድጓድ አላቸው እኔ ግን መጠለያ እንኳ የለኝም" ያለው ያ ከገሊላ አውራጃ የሆነው ረቢ ሰማያትን እንደ መጋረጃ የዘረጋ፣ ውሆችንም በእፍኙ የሰፈር ነው። ከፈለክ የአይምሮ ጤና መቃወስ አለብህ ብለህ ክሰሰኝ አሊያም ጨርቁን የጣለ ንቅል በለኝ ። ቤዛዬ ብዬ ማወራህ ስለ እሱ ነው! 'የቀራጮች ወዳጅ፣ የአመንዝሮች ጓደኛ' ተብሎ የተከሰሰው እሱ በህያዋንና በሙታን ላይ ሊፈርድ በዙፋን ሚሰየም ነው። በጌተሰማኒ ፍርሃት አቆራምዶት ነፍሱ እስከ ሞት የተከዘችበት እሱ የሞትን መውርወሪያ የሰበረ የሲኦልም ደጅ የገለበጠ ነው። ራስ ቅሉን በእሾኽ ተበስቶ፣ ጎኑን በጦር ተወግቶ፣ በግራፋት ብዛት ጀርባው ተልጦ፣ ደም ግባት አጥቶ በእንጨት ላይ ተንጠልጥሎ ያየኸው እሱ ሰማያትን በክብሩ የሸፈነ፣ ምድርንም በሞገሱ የሞላ፣ የውበት መደምደሚያም ነው። መስቀል መሸከም ከብዶት ሲንገዳገድ ያየኸው፤ በወንበዴዎች መሃል የዋለው እሱ አለማትን በሃያል ቃሉ የደገፈ ነው። ቤዛዬ ነው ምልህ እሱን ነው! የነፍሴ ቤዛ!!! በኢብሳ ቡርቃ
Show all...
የክርስቲያናዊ ሕይወት የዕለት ተዕለት ግብ ክርስቶስን ለመምሰል በመለወጥ እግዚአብሔርን ማክበር ነው። ይህም ከሥጋ ፈቃድ፣ ከዓለምና ከገዢዋ ጋር በመጋደል በክርስቶስ ለእግዚአብሔር ክብር ለመኖር ራስን ሙሉ ለሙሉ መስጠት ማለት ነው። ንጽጽሩ በአሮጌው ሰውና በአዲሱ ሰው መካከል ነው። አማኞች ክርስቶስን መድኅንና ጌታ አድርገው ሲቀበሉ፣ ለአሮጌው ሰውነታቸው ሞተው ለአዲሱ ሰው ይኖራሉ። ይህ በጣም ሥር ነቀል የሆነ ለውጥ ነው። በተመሳሳይ መልኩ፣ ሐዋርያው ጳውሎስ ለኤፌሶን ቅዱሳን እንዲህ በማለት ያሳስባል፦ “እውነተኛ በሆነው ጽድቅ እንዲሁም ቅድስና እግዚአብሔርን እንዲመስል የተፈጠረውን አዲሱን ሰው እንድትለብሱ ነው። “ (ኤፌ. 3:24) ይህ ሕይወት፡- 1) ምድራዊ ምኞትን - ዓለማዊነትን (worldlines) መግደል - (Mortify) የሥጋችንን ፈቃድ “እምቢ” ማለት ነው። ይህ ራስን በማስጨነቅ ሳይሆን - “የምንሮረው ለክርስቶስ ክብር ነው” በሚል ዕሳቤ በደስታ ለክርስቶስ ክብር ራስን ማስገዛት ማለት ነው። ፍቅሩ ግድ ስለሚለን፣ ከኀጢአት እንሸሻለን። የኀጢአት ግዛት የእግዚአብሔር ፍርድና ቁጣ የተገለጠበት ነው። ይህ የቀድሞ ሕይወታችን ነበር፤ አሁን ግን በሚታይ የጽድቅ ፍሬያማነት ለክርስቶስ እንኖራለን! ሕይወትን በሙሉ፣ በሥራና በአንደበት (action and word) ለእግዚአብሔር ክብር ማዋል ማለት ነው፤ አሮጌውን ሰው ከሥራው ጋር አውልቀን ጥለናልና! “ በአእምሮአችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ” (ሮሜ 12:2)። በክርስቶስ አካል - በቤተ ክርስቲያን ውስጥ - የእርስ በእርስ መስተጋብር በዚህ የጽድቅ ሕይወት የተቃኝ ሲሆን ነው፣ በእርግጥ ለጨለማው ዓለም ብርሃንና ጨው፣ እንዲሁም በተራራ ላይ ያለች ልትሰውር የማትችል ከተማ መሆን የምንችለው። 2) ክርስቶስ ሁሉም ነው፤ በሁሉም ነው - አዲሱ ሰው፣ አዲስ የተባለበት ምክንያት ክርስቶስን ስለለበሰ ነው። ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው አልፏልና! በክርስቶስ የቀድሞ ጠላቶች ሁሉ ታርቀዋል፤ የክፍፍል ግድግዳ ፈርሷል። በክርስቶስ አካል ውስጥ ግሪክ ወይም ይሁዲ፣ የተገረዘ ወይም ያልተገረዘ፣ አረማዊ ወይም እስኩቴስ፣ ባሪያ ወይም ጌታ፣ ወንድ ወይም ሴት የሚል ክፍፍል የለም። ከመስቀሉ ሥራ የተነሣ የክርስቶስ ማኅበረሰብ መታወቂያውም ሆነ ውቅሩ ዘር፣ ቋንቋ፣ ባህል፣ መደብ ወይም ፖለቲካዊ ርእዮተ ዓለም አይደለም። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በእግዚአብሔርና በሰው፣ በሰውና በሰው እንዲሁም በሰውና በተፈጥሮ መካከል ያለውን የጥል ግድግዳ ለአንዴና ለዘላላም በማፈረስ አንድ አዲስ ሰው ፈጥሯል። “. . . ሁለቱን አንድ ያደረገ፣ የሚለያየውንም የጥል [ἔχθραν (ኤክትራን - የማይታረቅ ጠላትነት-irreconcilable hostility] ግድግዳ [በአይሁድና አሕዛብ መካከል (በቤተ መቀደሱ - Temple-partition) እንዲሁም በአይሁድ፣ በአሕዛብና በእግዚአብሔር መካከል (የቅደስት ቅዱሳን መጋረጃ - veil of the Temple] ያፈረሰ ሰላማችን [εἰρήνη - የሰላም ልዑል] እርሱ ራሱ ነውና” (ኤፌ. 2÷14-15)። አይሁድ፣ አሕዛብ፣ ወንድና ሴት፣ ባርያና ጨዋ አንድ ሆነዋል። 3) ልዩነት የለም - በምድር ላይ ካሉ ማኅበረሰቦች ሁሉ፣ የክርስቶስን ማኅበረሰብ ልዩ የሚያደርገው ይኸው በመስቀሉ ሥራ ብቻ የተገኘው ማንነት፣ ሰላምና አንድነት ነው። ዘላለማዊ የእግዚአብሔር ቤተሰብ ሆኗል! “ከቅዱሳን [ἁγίων (ሃጊዮን፣ ለእግዚአብሔር የተለየ) ጋር የአንድ አገር ዜጋ፣ የእግዚአብሔርም ቤተሰብ አባል” (ኤፌ 2÷19) የሆነው በክርስቶስ መስቀል ቤዛዊ ሥራ ነው። ይህ እግዚአብሔራዊ ቤተሰብነት፣ በየትኛውም ፖለቲካዊና ማኅበራዊ ዐውድ የማይገረሰስ ነው። በበዓለ አምሳ ቀን ከልዩ ልዩ ባህል፣ ነገድና ቋንቋ፣ የተሰበሰበውን ሕዝብ አንድ ያደረገው የሮም ፓለቲካዊ ርእዮተ ዓለም ወይም ይሁዲነትን ጨምሮ በወቅቱ የነበሩ ሃይማኖቶች አልነበሩም። መንፈስ ቅዱስ ነበር። ከክርስቶስ ዋጆአዊ ሥራ የተነሣ፣ የአዲሱ ማኅበረሰብ መታወቂያውም ሆነ ውቅሩ ዘር፣ ቋንቋ፣ ባህል፣ መደብ ወይም ፖለቲካዊ ርእዮተ ዓለም አይደለም። እነዚህ ማንነቶች ሁሉ አንጻራዊ ሆነዋል። ስለዚህ የክርስቶስ ማኅበረሰብ ውበቱ ልዩነቱ ነው። ለእግዚአብሔር ለራሱ የተለየ ሕዝብ [ἔθνος ἅγιον - ዘረ-ቅዱስ] በሆነበት መጠን ያህል ብቻ ነው ለሌላው ሕዝብ የዕርቅና ሰላም አማራጭ የሚሆነው። በርግጥ ልዩ የእግዚአብሔር ሕዝብ ከሆንን፣ የሚገዛንም ዋናው ፋይዳ ደግሞ ከሕዝብ፣ ከነገድና ከቋንቋ የተዋጀንበት ማንነት ከሆነ፣ እርስ በእርስም ሆነ ሌሎችን በብሔርተኝነት መነጽር ልንመለከት አንችልም (ራእ 5፥ 8-10)። አቤቱ አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ፤ ይህ እውነት ለእኛ፣ ለቤተ ክርስቲያንና ለአገራችን በርግጥ ይሁን። አሜን! Dr. Girma bekele @nazrawi_tube
Show all...
የእግዚአብሔር ተስፋ ደረቅ ቼክ አይደለም              ዓለም የእድሜ ማስረዘሚያ መድኃኒት ትቀምም ይሆናል ሰው ግን በዓለም የላብራቶሪ ምርት ሳይሆን በተስፋ እድሜውን ያረዝማል። ተስፋ ነገን የመኖር ጉጉትና አቅም ነው። ተስፋ የሌለው ሰው በራሱ ላይ ህይወትን ሳይሆን ሞትን የሾመና ያነገሰ ስለሆነ ለመኖር አቅምም ፍላጎትም የለውም።  የኑሮ ትልቁ ጉልበት ተስፋ ነው። ተስፋ ካለህ ሸለቆ ወርደህ ተራራ ወጥተህ ካሰብከው ትደርሳለህ           አንድ ሰው ደረቅ ቼክ ሊፅፍልህ ይችላል። ቼኩ ላይ ያለው የገንዘብ መጠን የኔ ነው እያልክ ልብህን ደስ ደስ ሊለው ይችላል። ባንክ ስትሄድ ግን እጅህ ላይ ያለው ቼክ ከገንዘብነት ወደ ባዶ ወረቀትነት ይቀየራል። ሰው እንዲህ ነው ተስፋ እየሰጠህም ሊዋሽህ ይችላል። እግዚአብሔር የሰጠህ ማንኛውም ተስፋ እንደ ቼኩ ደረቅ አይደለም።          ሰው ሞቅ ሲለው ቃል ይገባልህና ተስፋ እንድታደርገው የአዕምሮህን ሆድ ይሞላዋል። አንተም ከዛሬ ነገ ተስፋዬን እውን አደረገው ስትል ያልኩህን ነገር ትቼዋለሁ ብሎ ያስተነፍስሀል። ወዳጄ እግዚአብሔር ሞቅ ብሎት የገባልህ ተስፋ የለም። አፉንም አዳልጦት የተናገረህ ተስፋ የለም። ሁሉንም ተስፋ በእቅድና በእውነት ተናግሮሀል።            እግዚአብሔር ፍቃደኛ ሳይሆንና ሊደግፋችሁ ወደማይችለው ነገር አይዟችሁ እኔ ከናንተ ጋር ነኝ ብሎ አይጠራችሁም። በእውነትም የሚያስመካና የማይክድ አጋር ስለሆነ ክንዴን ተንተራሱት ይላችኋል። ጥንካሬ እንደሌለን ስለሚያውቅ እኔ ኃይላችሁ ነኝ ይለናል። ትኩረታችንን ከራሳችን ላይ አንስተን በእግዚአብሔር ላይ ካደረግን ከእርሱ ጋር ሁሉ እንደሚቻል ያሳየናል።            እግዚአብሔር አንድያ ልጁን ሰጥቶን በሌላ ነገር አንጠረጥረውም። ትልቁን ስጦታ ተቀብለን በትንሿ ተስፋ ማጉረምረም የለብንም። ተስፋችሁ ይፈፀማል። ✍አዶኒ @adonigospel @adonigospel
Show all...
🌼🌼  🌼🌼 🌼🌼  🌼🌼 🌼🌼  🌼🌼 🌼🌼  🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼  🌼🌼 🌼🌼  🌼🌼 🌼🌼  🌼🌼 🌼🌼  🌼🌼   🌻 🌻🌻🌻   🌻🌻 🌻🌻  🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻   🌻🌻🌻🌻🌻🌻   🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻  🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌼🌼  🌼🌼 🌼🌼  🌼🌼 🌼🌼  🌼🌼 🌼🌼  🌼🌼 🌼🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼  🌼🌼 🌼🌼🌼   🌼🌼 🌼🌼🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻 🌻🌻  🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻🌻🌻 🌻🌻🌻🌻 🌻🌻🌻 🌻🌻🌻 🌻🌻  🌻🌻 🌻🌻  🌻🌻 🌻🌻  🌻🌻 🌻🌻  🌻🌻 🌻🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻 🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻   🌼 🌼🌼🌼   🌼🌼 🌼🌼  🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼   🌼🌼🌼🌼🌼🌼   🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼  🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
Show all...
A Biblical response to the 'Man is spirit, has a soul, lives in a body" heresy 📔ርዕስ፦ሰው ምንድር ነው? 👤ደራሲ፦ዘላለም መንግስቱ 💾መጠን፦1.7MB 📑የገጽ ብዛት፦83 ዳሰሳ፦ሰው ምንድር ነው? ለሚለው ጥያቄ ሰፊ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ምላሽን እንዲሁ ከሰው ማንነት ጋር ለሚነሳ ኑፋቄ መልስን ያገኛሉ። በተጨማሪ የሰው መንፈስ አስተምህሮ ጅማሬ ፣ አስተምህሮውን ተከትለው የሚመጡ መዘዞች......ወዘተ በግሩም ሁኔታ ተካተውበታል። @AmharicSpritualBooks @AmharicSpritualBooks
Show all...
አንብበው.... #ለመፍረድ_አትቸኩል ዶክተሩ ስልክ ይደወልለትና እየሮጠ ወደ ሆስፒታል ይሄዳል፡፡ ሆስፒታል ከደረሰ በሇላ ልብሱን በፍጥነት ቀያይሮ ወደ ኦፕራስዮን ክፍል እየተጣደፈ ሲሄድ መግብያ በሩ ላይ ቁሞ ይጠብቀው የነበረ የታማሚው ልጅ አባት "እንዴት እንደዚህ ለመድረስ ይህን ሁሉ ሰአት ይፈጅብሃል ዶክተር....? የሰው ህይወት ግድ አይሰጥህም? በጣም ዘገየህ" ሲለው ዶክተሩ በፈገግታ..... "ይቅርታ" ሆስፒታል ግቢ ውስጥ አልነበርኩም፡ ስልክ ከተደወለልኝ በሇላ ግን አቅሜ በፈቀደ መጠን በፍጥነት ለመድረስ ሞክሬያለሁ ተረጋጋ አለው፡፡ "ተረጋጋ ትለኛለህ? ታሞ ሊሞት እያጣጣረ ያለው እኮ የኔ ልጅ ነው፡ እንዴት ተረጋጋ ትለኛለህ ? ያንተ ልጅ በሆን እንደዚህ ትላለህ? አንተ በመዘገየትህ ልጄ ሊሞትብኝ ነው ትንሽ አታስብም?" ብሎ ሲጮህበት ዶክተሩ አሁንም ፈገግ እያለ.. "ዶክተር የሰውን ልጅ ህይወት ሊያረዝምም ሊያሳጥርም አይችልም፡ አፈር ነንና ወደ አፈር መመለሳችን አይቀርም ፡ አሁንም ተረጋጋ እኔም ስራዬን ልስራበት" ብሎ ወደ ሰርጀሪ ክፍል ገብቶ ለተወሰኑ የህፃኑ ቀዶ ጥገና ካከናወነ በሇላ ወደ ውጭ ወጥቶ በፈገግታ የልጁን አባት "እንኳን ደስ አለህ... ልጅህ ሰርጀሪ ከተደረገለት በሇላ በጥሩ ጤንነት ላይ ይገኛል፡ ከዚህ በሇላ የሚያስፈልገህ ነገር ካለ ነርሷ ትረዳሃለች" ብሎት እየሮጠ ከሆስፒታሉ ወጣ፡፡ ሰውዬው በሰማው መልካም ዜና ቢደሰትም የዶ/ሩ ሁኔታ ግራ ስለገባው ነርሷን ....ዶ/ሩ ምን ሆኖ ነው እንዲህ የተዋከበው? ብሎ ሲጠይቃት "ዶክተሩ ትላንትና ልጁ በመኪና አደጋ ሞቶበት ቀብር ላይ ነበር ፡ ያንተ ልጅ ህመም አደገኛ ስለነበር እንዲያክመው ደውለን ጠርተነው ነው፡፡ አሁን ያንተን ልጅ ካዳነ በሇላ የልጁ ቀብር ላይ ለመድረስ ነው እየሮጠ ያለው፡፡ ስትለው.... ሰውዬው ድርቅ ብሎ ቀረ .....!! #የሰውን_ልጅ_በ_ምን_አይነት_ሁኔታ_ውስጥ_እንደሆ ነ_ሳታውቁ_አትፍረዱ። ✅CHRISTIAN MINDSET ETH @CHRISTIAN_MINDSET_ETH @CHRISTIAN_MINDSET_ETH @CHRISTIAN_MINDSET_ETH
Show all...
. #አእምሮን_ማንቃት 👇 ➊. #አራት አይነት ሰዎችን አክብር 1➳ የእውቀት ባለቤቶችን 2➳ ቤተሰብህን 3➳ አዛዉንቶችን 4➳ ባለ ስልጣናትን ❷. #አራት ነገሮች ይኑሩህ 1➳ ኢየሱስ 2➳ ታማኝነት 3➳ እምነት 4➳ መልካም ስራ ❸. ራስህን ከ #አምስት ነገሮች አርቅ 1➳ ሰዎችን ከመናቅ 2➳ ከማጭበርበር 3➳ ከብድር 4➳ ከዝሙት 5➳ ጣኦትን ከማምለክ ❹. #ሶስት ነገሮችን ተቆጣጠር 1➳ ምላስህን 2➳ ቁጣህን 3➳ ስሜትህን ❺. ከ #አራት ነገሮች ራስህን ጠብቅ 1➳ ከመጥፎ ስራ 2➳ ሰዎችን ከማማት 3➳ ከምቀኝነት 4➳ እግዚአብሔር ከማሳዘን ❻. #አራት ነገሮችን ፈልግ 1➳ እዉቀትን 2➳ ጥሩ ስነምግባርን 3➳ ታዛዥነትን 4➳ እግዚአብሔርን ❼. #ሶስት ነገሮችን ንጹህ አድርግ 1➳ ሰዉነትህን 2➳ ልብስህን 3➳ ንግግርህን ❽. #ሶስት ነገሮችን አስታዉስ 1➳ ሞትን 2➳ ሰዎች የዋሉልህን ዉለታ 3➳ ሰዎች የሰጡህን ምክር ✅CHRISTIAN MINDSET ETH @CHRISTIAN_MINDSET_ETH @CHRISTIAN_MINDSET_ETH @CHRISTIAN_MINDSET_ETH
Show all...
ዘማሪ አዲሱ ወርቁ ━━━━━━━━━━━━ ➠ TITLE: "ትዝ ይለኛል" ➠ GENRE: amazing song ➠ Quality: mp3 ➠ SIZE: 4.1 MB ➠ TIME: 4:17 ➠ CHANNEL : @marsilchannel ━━━━━━━━━━ ➠share link:t.me//marsilchannel
Show all...
. ባለውለታዬ ዘማሪት ቤተልሔም ወልዴ Amazing Gospel Song ሼር በማድረግ ወዳጆ ያካፍሉ sʜᴀʀᴇ💯 sʜᴀʀᴇ 💯 sʜᴀʀᴇ💯 ✅ @adadisemezemur ✅ ✅ @adadisemezemur ✅ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 📲ሼር ማድረግዎን እዳይረሱ📲 👇Subscribe For More👇 https://youtu.be/9AZqw7YPerc
Show all...
. ተቀሰቀሰ በረከት ተስፋዬ | የፋሲካ ዝማሬ 🕑-5:42Min💾-5.3MB sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ◈sʜᴀʀᴇ ▷ @yedestaye_elilta ◁ ▷ @yedestaye_elilta△Join Us△
Show all...
. ኢየሱስ ብዬ ዘማሪ ይትባረክ ታምሩ New Amazing Gospel Song ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያካፍሉ sʜᴀʀᴇ💯 sʜᴀʀᴇ 💯 sʜᴀʀᴇ💯 ✅ @adadisemezemur ✅ ✅ @adadisemezemur ✅ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 📲ሼር ማድረግዎን እዳይረሱ📲 👇Subscribe For More👇 https://youtu.be/9AZqw7YPerc
Show all...
. ✟መስቀልህ ስር✟ ዘማሪ ዩሴፍ በቀለ Amazing Easter Song ሼር በማድረግ ወዳጆ ያካፍሉ sʜᴀʀᴇ💯 sʜᴀʀᴇ 💯 sʜᴀʀᴇ💯 ✅ @adadisemezemur ✅ ✅ @adadisemezemur ✅ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 📲ሼር ማድረግዎን እዳይረሱ📲 👇Subscribe For More👇 https://youtu.be/9AZqw7YPerc
Show all...