en
Feedback
SOS HGS Grade 12, 2018 E.C

SOS HGS Grade 12, 2018 E.C

Open in Telegram
404
Subscribers
No data24 hours
+17 days
-430 days
Posts Archive
ማስታወቂያ የትምህርት ቤት ክፍያ በተሰጠው የጊዜ ገደብ ላላጠናቀቃችሁ ወላጆች በሙሉ ፡ በ2018 የትምህርት ዘመን የትምህርት ክፍያ መክፈያ ጊዜን በተማሪዎች በኩል በደብዳቤ ያሳወቅን መሆኑ ይታወቃል፡
ማስታወቂያ የትምህርት ቤት ክፍያ በተሰጠው የጊዜ ገደብ ላላጠናቀቃችሁ ወላጆች በሙሉ ፡ በ2018  የትምህርት ዘመን የትምህርት ክፍያ  መክፈያ ጊዜን በተማሪዎች በኩል በደብዳቤ ያሳወቅን መሆኑ ይታወቃል፡፡ በተላለፈው መልዕክት መሰረት አብዛኛው ወላጅ በተሰጠው ጊዜ የሚጠበቀውን ክፍያ በመክፈል የወላጅነት ሃላፊነትን በአግባቡ እየተወጣ ስለሚገኝ ት/ቤቱ ከፍ ያለ ምስጋና ያቀርባል። ነገር ግን የተወሰኑ ወላጆች በወቅቱ ባለመክፈል በስራ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ በማድረሳችሁ ምክንያት ይህን መልዕክት ለማስተላለፍ ተገደናል።  ስለሆነም ይህ የሚመለከታችሁ ወላጆች ቀሪ የትምህርት ክፍያ እስከ የካቲት 20 ቀን 2018 ዓ. ም በማጠናቀቅ ክፍያ የፈጸማችሁበትን የባንክ ሰነድ ፋይናንስ ክፍል እንድታቀርቡ በአክብሮት እየጠየቅን በወቅቱ ባለመክፈል ለሚፈጠረው መስተጓጎል ትምህርት ቤቱ ኃላፊነት የማይወስድ መሆኑን እንገልፃለን ፡፡ ማሳሰቢያ: ከዓርብ የካቲት 20 ቀን 2018 ዓ. ም ጀምሮ ክፍያ ያላጠናቀቀ ተማሪ ክፍል የማይገባ መሆኑን በጥብቅ እናሳሰባለን:: ከሰላምታ ጋር የት/ቤቱ አስተዳደር

Updated Weekly Timetable Grade 9-12
Updated Weekly Timetable Grade 9-12

+4
2018 grade 12 physics model exam REV.pdf3.76 KB

Module III.pptx4.50 MB

ውድ ተማሪዎችና ወላጆች ከጥር 10 እስከ ጥር 12 ቀን 2018 ዓም ድረስ በከተራና በጥምቀት በዓል ምክንያት የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር በ 8 አቅጣጫ ያሉ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ እንደሚሆኑ የሀረሪ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል። ስለዚህ በተጠቀሱት ቀናት በተማሪዎቻችን ላይ የሚፈጠረውን የትራንስፖርት ችግርና መጨናነቅ ለመቀነስ ጥር 11 እና ጥር 12 /2018 ዓም ት/ቤቱ ዝግ መሆኑን እየገለፅን ፣ ረቡዕ ጥር 13 ቀን ሁሉም ተማሪዎች በተሟላ ሁኔታ በትምህርት ገበታቸው ላይ እንዲገኙ እያሳሰብን ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች መልካም በዓል እንዲሆንላችሁ እንመኛለን። የት/ቤቱ አስተዳደር

All students are expected to fill this form for Education Management Information System.

Module III.pptx4.50 MB

+8
Physics Grade 12 UEE.pdf7.40 KB

What is Bootstrap 5.docx0.50 KB

SAT English

+2
Entrance 2015, All Natural Subjects.pdf11.76 MB

#Update የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ይዘቶች ይፋ ሆኑ፡፡ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ፤ ተማሪዎች፣ የተማሪ ቤተሰቦች፣ መምህራንና የትምህርት አመራር ለፈተና ዝግጅት በሚያደርጉበት ወቅት ፈተና የሚሸፍናቸው የይዘት አካባቢዎች ይፋ አድርጓል። የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ከፍል ፈተና ዝግጅትና አስተዳደር የሚከተሉትን ያካትታል፡፡  1. የትምህርት ዓይነቶችን በተመለከተ ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ፦ - እንግሊዘኛ፣ - ሒሳብ፣ - እስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ - ኬሚስትሪ፣ - ፊዝክስና ባዮሎጂ ለማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ፦ - እንግሊዘኛ፣ - ሒሳብ፣ - እስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ - ታሪክ፣ - ጂኦግራፊና ኢኮኖሚክስ ናቸው። 2. ፈተናው ከ9ኛ እስከ 12ኛ ከፍል ደረጃዎችን እና በተማሪው መጽሐፍ ላይ ያሉትን ሁሉንም ምዕራፎች ይሸፍናል፡፡ 3. ከ10ኛ – 12ኛ ክፍል ሁሉም የትምህርት ዓይነት ፈተና በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሠረት እየተዘጋጀ ያለ ሲሆን የ9ኛ ክፍል ደግሞ የሁሉም የትምህርት ዓይነቶች ፈተናዎች ከቀድሞውና ከአዲሱ ሥርዓተ ትምህርቶች የጋራ ይዘቶችን ብቻ አካቶ እየተዘጋጀ ይገኛል፡፡ 4. ፈተናው ማንኛውም ተፈታኝ ተማሪ ከተማረው ሥርዓተ ትምህርትና ከተማሪው መጽሐፍ ላይ ብቻ ተመስርቶ እየተዘጋጀ ይገኛል፡፡ 5. የፈተናው አስተዳደር በበይነ መረብና በወረቀት ጎን ለጎን የሚሰጥ ሲሆን አብዛኛው ተፈታኝ በበይነ መረብ እንዲፈተን እየተሠራ ያለ በመሆኑ ተፈታኞች እራሳቸውን በበይነ መረብ ለመፈተን ሊያዘጋጁ ይገባል፡፡ #EAES

#National_ID የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ላይ ለመቀመጥ ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ቅድመ ሁኔታ ተደረገ። የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት " ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ለፈተና ለመቀመጥ ቅድመ ሁኔታ ነው " ብሏል። " ማንኛውም የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኝ ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ከፈተና ምዝገባ ቀድሞ ማውጣትና በእጁ መያዝ ይገባዋል " ሲል አሳውቋል። " ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) የሌለው ተማሪ ለፈተና መመዝገብ ሆነ በማንኛውም ሁኔታ መፈተን አይችልም " ሲል አስገንዝቧል። ተማሪዎች የብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ይዘው እንዲገኙ ፦ - የተማሪ ቤተሰብ - መምህራን - የትምህርት አመራሮች - የሚዲያ አካላት ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል። #National_ID