en
Feedback
AIRDROP ROOM

AIRDROP ROOM

Open in Telegram
2 485
Subscribers
No data24 hours
-157 days
-5230 days
Posts Archive
የኢትዮጵያ፣ ግብፅ እና ሱዳን መሪዎች በቪድዮ ተገናኝተው በህዳሴ ግድብ ዙርያ መክረዋል! "የአፍሪካ ህብረት ዓባላት ቢሮ ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ ለታላቁ የሕዳሴ ግድብ ከአፍሪካ የመነጨ መፍትሔን
የኢትዮጵያ፣ ግብፅ እና ሱዳን መሪዎች በቪድዮ ተገናኝተው በህዳሴ ግድብ ዙርያ መክረዋል! "የአፍሪካ ህብረት ዓባላት ቢሮ ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ ለታላቁ የሕዳሴ ግድብ ከአፍሪካ የመነጨ መፍትሔን ማበጀት ላይ ያተኮረ ውጤታማ ውይይት አድርገናል" ብለዋል ጠ/ሚር አብይ አህመድ። አክለውም "ይህንን አህጉራዊ ጠቀሜታ ያለው የከፍተኛ አመራሮች ስብሰባ ላስተባበሩት የአፍሪካ ኅብረት ሰብሳቢ፣ ፕሬዚደንት ሲሪል ራማፎሳ ምስጋናዬን አቀርባለሁ። ለኅብረቱ ሊቀ መንበር ሙሳ ፋኪም ምስጋናዬ ይድረስ" ያሉ ሲሆን የፓን አፍሪካዊነት መንፈስ ያለው አህጉራዊ ተቋማችን ለአፍሪካ ከፍተኛ ጠቀሜታ ያላቸውን ውይይቶች ለማካሄድ ትክክለኛው ሥፍራ ነው ብለዋል። "ታላቁ የሕዳሴ ግድብ ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት የላቀ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት እና የጋራ ብልጽግና የሚያገኙበትን ዕድል ይዟል።" @eliasmeseret

"ምርጫ ማካሄድ የሚያስችል ሁኔታ እስኪረጋገጥ በየትኛውም የአገሪቱ ክልል ምርጫ አይካሄድም"- ምርጫ ቦርድ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ኛው አገራዊ ጠቅላላ ምርጫ የሚካሄድበት ጊዜ እንዲራዘም ምክ
"ምርጫ ማካሄድ የሚያስችል ሁኔታ እስኪረጋገጥ በየትኛውም የአገሪቱ ክልል ምርጫ አይካሄድም"- ምርጫ ቦርድ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ኛው አገራዊ ጠቅላላ ምርጫ የሚካሄድበት ጊዜ እንዲራዘም ምክንያት የሆነው የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ሁኔታ እንደገና ተገምግሞ ምርጫ ማካሄድ የሚያስችል ሁኔታ መፈጠሩ እስኪረጋገጥ ድረስ በየትኛውም የአገሪቱ ክልል ምርጫ እንደማያካሂድ ገለጸ። ቦርዱ ዛሬ ባወጣው መግለጫ እንደገለጸው የትግራይ ክልል ምክር ቤት "የኢፌዴሪ ህገ መንግስት በሚያዘው መሰረት ቦርዱ የክልል ምክር ቤት ምርጫ እንዲፈጸምለትና ምርጫውን ለማካሄድ  የሚያስፈልግ የሰው ሃይልና ሎጂስቲክስ ዝግጅት እንዲያደርግ" ሲል ቦርዱን መጠየቁን አስታውቋል። ለቀረበለት ጥያቄ ምላሽ የሰጠው ቦርዱ የትግራይ ክልል ምክር ቤት የኢፌዴሪ ህገ መንግስት በሚያዘው መሰረት በክልሉ ውስጥ 6ተኛውን ዙር የክልል ምክር ቤት ምርጫ እንዲካሄድ ውሳኔ ለመስጠት እንዲሁም ቦርዱ ይህንን ውሳኔውን ተቀብሎ ሊያስፈጽም ይገባል የሚልበት ህጋዊ መሠረት የለውም ሲል ገልጿል። ቦርዱ የትግራይ ክልል ምክር ቤት የክልል ምክር ቤት ምርጫን አስመልክቶ የሰጠውን ውሳኔ እንዲያውቅለትም ሆነ ምርጫ እንዲያስፈፅምለት ያቀረበውን ጥያቄም ያልተቀበለው መሆኑን ገልጾ የተጠየቀውን የሰው ሀይል፣ የሎጄስቲክስ እና የቁሳቁስ አቅርቦት የሚሰጥበት የህግ አግባብ አለመኖሩን አስታውቋል፡፡  ሙሉ መግለጫው 👉 https://telegra.ph/ETH-06-24 [የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ] @ethiocheck

⬆️ የሔመቲ የኢትዮጵያ ጉብኝት እና ያስከተለው ሴራ ትንተና! ሌ/ጀ መሐመድ ሐምዳን ዳግሎ (ብዙዎች 'ሔመቲ' በሚለው ቅፅል ስሙ ይጠሩታል) ሱዳን ውስጥ እጅግ አወዛጋቢ ግለሰብ ነው። ከግመል ነጋዴነት ተነስቶ አሁን ሱዳን ውስጥ ከፍተኛ ሀይል በእጁ የያዘ ግለሰብ የሆነው ሔመቲ ሚሊሺያዎችን በቀላሉ ማንቀሳቀስ የሚችል፣ በፊት ከግመል፣ አሁን ደግሞ ከወርቅ ንግድ ሚሊዮኖችን ያፈሰ እንዲሁም የሱዳን ወታደራዊ ሽግግር ምክር ቤት ምክትል ሀላፊ ነው። ፈጣን ድጋፍ ሰጪ ሀይል (RSF) የተባለውን ጦርም የሚመራ ሲሆን በበርካታ ግድያዎች እና የመብት ጥሰቶች ይጠረጠራል። "አሁን ላይ ሱዳን ጠ/ሚር እና የሽግግር ምክር ቤቱ ዋና ሀላፊ ቢኖራትም ሔመቲ በእጁ ከፍተኛ ሀይል ያለው ግለሰብ ነው" ይላሉ የቀጠናው ተንታኞች። ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብፅ በህዳሴ ግድብ ዙርያ ሲያካሂዱት የነበረው ውይይት ካለ ስምምነት መጠናቀቁን ተከትሎ ይህ የሱዳን ባለስልጣን ባሳለፍነው ሳምንት አዲስ አበባ ተገኝቶ ነበር። "በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ" ውይይት እንደተደረገ የተገለፀ ሲሆን ዝርዝሩ ግን አልታወቀም። ይህ ጉብኝት ሱዳን እና ግብፅ ውስጥ ያሉ አንዳንዶችን ያሳሰበ ይመስላል። ሔመቲ በቅፅበት በሚወስናቸው ውሳኔዎቹ የሚታወቅ ስለሆነ "ምን ብሎ ይሆን? ምን ተስማምቶ ይሆን?" የሚሉት ጥያቄዎች ብዙዎች ጆሮዎች ላይ እንዳቃጨሉ ከዲፕሎማቶች ሰምቻለሁ። በተለይ በግብፅ በኩል ትኩረት ተደርጎበታል ይላሉ እነዚህ ዲፕሎማቶች። አክለውም "ግብፅ ልክ እንደ ሳውዲ አረቢያ እና ኤምሬቶች ሔመቲን ትደግፋለች፣ ቢሆንም የውይይቱ ምክንያት እና ውጤት አሳስቧቸዋል" ይላሉ። ይህ በእንዲህ እያለ አንዳንድ ሚድያዎች "ይህ የሱዳን ባለስልጣን ወደ ኢትዮጵያ የሄደው የሱዳን መንግስት ሳያውቅ በግሉ ነው" የሚል ዘገባ ይዘው ወጥተው ነበር፣ ሗላ ላይ የሽግግር ምክር ቤቱ ቢያስተባብለውም። "ሔመቲ ከባድ ሰው ነው። በጣም ጠጋ ማድረግም፣ ማራቅም ችግር አለው ብዬ አስባለሁ። በዚህ ወቅት ኢትዮጵያ መምጣቱ ግን በምንም ምዘና ለኢትዮጵያ ጥሩ ነገር ነበር ተብሎ መናገር ይቻላል" ብለው ያጫወቱኝ ሌላኛው ዲፕሎማት ናቸው። በቅርቡ አንድ የAP ዜና እዚህ ላይ ይኖራል። @ethiocheck

photo content

"ኢትዮጵያ: የአፍሪካ ራስ ምታት" ይላል አህራም ኦንላይን ከደቂቃዎች በፊት ይዞት የወጣው ነገር! የተስፋ መቁረጥ፣ የመሰላቸት ወይም የንዴት አባባል ይመስላል። የፀጥታው ምክር ቤት ግብፅ እንዳሰበችው
"ኢትዮጵያ: የአፍሪካ ራስ ምታት" ይላል አህራም ኦንላይን ከደቂቃዎች በፊት ይዞት የወጣው ነገር! የተስፋ መቁረጥ፣ የመሰላቸት ወይም የንዴት አባባል ይመስላል። የፀጥታው ምክር ቤት ግብፅ እንዳሰበችው ስብሰባ አለመጥራቱ፣ ጥቁር የአሜሪካ ኮንግረስ አባላት ያወጡት መግለጫ፣ እነ ሶማልያ እና ጅቡቲ አረብ ሊግ ላይ የግብፅን አቋም አለመደገፋቸው፣ የሱዳኑ ሔመቲ ኢትዮጵያ ብቅ ማለታቸው እንዲሁም የግድቡ ሙሌት እውን መሆን ግልፅ እየሆነ ሲመጣ ግራ ሊገባ ይችላል። ዋናው ነገር እውነትን ይዞ ለተፈጥሮአዊ መብት በደንብ መሞገት ነው፣ ሌላው ግዜውን ጠብቆ ለሁሉም ግልፅ ይሆናል። @ethiocheck

"መቀመጫቸዉን ግብጽ ያደረጉ የሳይበር ወንጀለኞች በኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ጫና ለመፍጠር የሰነዘሩት የሳይበር ጥቃቶችን መከላከል ተችሏል"--- ኢመደኤ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ
"መቀመጫቸዉን ግብጽ ያደረጉ የሳይበር ወንጀለኞች በኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ጫና ለመፍጠር የሰነዘሩት የሳይበር ጥቃቶችን መከላከል ተችሏል"--- ኢመደኤ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ (ኢመደኤ) ሰኔ 10፣ 12፣ 13 እና 14 መቀመጫቸዉን ግብጽ ያደረጉ የሳይበር ወንጀለኞች በኢትዮጵያ የኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ጫና ለመፍጠር የተቃጡ የሳይበር ጥቃቶችን ማክሸፉን አስታውቋል። የሳይበር ጥቃት ሙከራው የተቃጣው ሳይበር ሆሩስ ግሩፕ (Cyber Horus Group)፣ አኑቢስ ዶት ሃከር (AnuBis.Hacker) እና ሴኪዩሪቲ ባይ ፓስ (Security_By_Passed) በተባሉ የሳይበር አጥቂዎች አማካይነት መሆኑን ኤጀንሲው ገልጿል፡፡ ወንጀለኞቹ ለረጅም ጊዜ ሲዘጋጁ የቆዩ እና ኤጀንሲው ሲከታተላችው የነበሩ እንደሆኑ የተገለፀ ሲሆን በይበልጥ ሰኔ 12 እና ሰኔ 13 ከፍተኛ የሚባል የሳይበር ጥቃት ሙከራዎች ማድረጋቸውን የገለጸው ኤጀንሲው በዚህ ጊዜ ዉስጥ የ13 የመንግስት፣ 4 መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትን የድረ-ገጽን የማስተጓጎል ሙከራ ማድረጋቸውን አስታውቋል፡፡ የሳይበር ጥቃት ሙከራው በሀገሪቱ የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት፤ የደህንነት መስሪያ ቤቶች እና የግል ድርጅቶች ድረ-ገጽ ላይ ያነጣጠረ ነበር፡፡ ሳይበር ሆሩስ ግሩፕ፣ አኑቢስ ዶት ሃከር እና ሴኪዩሪቲ ባይ ፓስ የሳይበር ጥቃት አድራሽ ቡድኖች ሃላፊነቱን የወሰዱ ሲሆን ዋና አላማቸዉም ከህዳሴው ግድብ ዙሪያ በተለይ በውሃ አሞላል ጋር በተያያዘ ሁሉን አቀፍ ተጽእኖ በሀገሪቱ ላይ ለመፍጠር በማሰብ

#GERD : ኢትዮጵያ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድርድር ሰበብ በዓባይ ወንዝ ላይ የሚኖራትን ቀጣይ የመልማት መብት የሚገድብ ስምምነት እንደማትቀበል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገዱ አንዳርጋቸው አረጋ
#GERD : ኢትዮጵያ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድርድር ሰበብ በዓባይ ወንዝ ላይ የሚኖራትን ቀጣይ የመልማት መብት የሚገድብ ስምምነት እንደማትቀበል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገዱ አንዳርጋቸው አረጋገጡ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት በግድቡና ወቅታዊ ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ከኢዜአ ጋር በነበራው ቆይታ ነው። ግብፅ በግድቡ ላይ የሚደረገውን ድርድር በማስታከክ ኢትዮጵያ በግድቡ ላይ የሚኖራትን መብት ለመገደብ እየሞከረች መሆኗንም አስረድተዋል። የግድቡ ጉዳይ የዓባይ ወንዝ ፍትሃዊ ተጠቃሚነት አንድ ነጠላ አካል ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ የዓባይ ወይም የናይል ወንዝ ተጠቃሚነት መታየት ያለበት ሁሉም የተፋሰሱ አገሮች በተደራደሩበት የትብብር ስምምነት መሠረት ነው ብለዋል። ስምምነቱን ከተደራደሩት 10 አገሮች ስድስቱ የፈረሙ ሲሆን፤ ከነዚህም ኢትየጵያን ጨምሮ አራት አገሮች ስምምነቱን በፓርላማቸው አፅድቀው የሕጋቸው አካል አድርገውታል። ግብፅ ከአሁኑ የሦስትዮሽ ድርድር አፈንግጣ መውጣቷን የገለፁት አቶ ገዱ፣ኢትዮጵያ የዓባይን ወንዝ ተጠቃሚነት በተመለከተው የናይል ተፋሰስ ስምምነት መሠረት ወንዙን በፍትሃዊነት መጠቀም ትችላለች ብለዋል ሚኒስትሩ።

የአብዱል ፈታህ አል ሲ ሲ የጦር ነጋሪት ሞጎሰም ተቀባይነት የለውም‼️ በተባበሩት መንግስታታት ድርጅት እውቅና ያለው የሊቢያ መንግስት የግብፁ ፕሬዚዳንት አብዱል ፈታህ አል ሲ ሲ ያስተላለፉት የጦርነ
የአብዱል ፈታህ አል ሲ ሲ የጦር ነጋሪት ሞጎሰም ተቀባይነት የለውም‼️ በተባበሩት መንግስታታት ድርጅት እውቅና ያለው የሊቢያ መንግስት የግብፁ ፕሬዚዳንት አብዱል ፈታህ አል ሲ ሲ ያስተላለፉት የጦርነት ጉሰማ ተቀባይነት የለውም አለ። አል ሲ ሲ በተባበሩት መንግስታታት ድርጅት እውቅና ያለው የሊቢያ መንግስት የግብፅ እና የጄኔራል ካሊፍ ሃፍታር ጦር ቀይ መስመርን እንዳያልፍ ሲሉ በትናትናው ዕለት ማስጠንቀቂያ አዘል መልዕክት አስተላልፈው ነበር። ቅዳሜ ዕለት በሊቢያ አቅራቢያ በሚገኘው የግብፅ አየር ሀይል ጣቢያ በተገኘቡት ወቅት እንደተናገሩት አስፈላጊ ከሆነ ተጨማሪ ጦር ወደ ሊቢያ ሀገራቸው እንደምትልክ ገልፀዋል። ይህንን ተከትሎ በተባበሩት መንግስታታት ድርጅት እውቅና ያለው የሊቢያ መንግስት የምክር ቤት አባል የሆኑት አብዱርሃማን ሻተር ሊቢያ ያልተቀበለችው የግብፅ ወታደራዊ ጣልቃ ገብነት በሊቢያ ዲሞክራሲን አደጋ ላይ ጥሏል ማለታቸውን አልጀዚራ ዘግቧል። አብዱርሃማን ሻተር ከእኛ ላይ እጃችሁን አንሱ በየመን የፈፀማችሁትን አሰቃቂ ድርጊት እንዳትደግሙት ሲሉ ነው በትዊተር ገፃቸው ላይ ያሰፈሩት። ©አልጀዚራ

#NewsAlert ግብጽ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ጉዳይ በድርድር ሂደት ላይ እያለ ጉዳዩን ወደ ተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት መውሰዷን እንደማትቀበል ሱዳን ገለፀች። የሱዳን
#NewsAlert ግብጽ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ጉዳይ በድርድር ሂደት ላይ እያለ ጉዳዩን ወደ ተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት መውሰዷን እንደማትቀበል ሱዳን ገለፀች። የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዴኤታ ኡመር ቀመረዲን ከቢቢሲ አረብኛ ጋር በነበራቸው ቆይታ ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብን የመጀመሪያ የውሃ ሙሌት ብትጀምር ሱዳን ከኢትዮጽያ ጋር ወደ ግጭት እንደማትገባ ግልፅ አድርገዋል። ሀገራቸው ችግሩ በዲፕሎማሲ መንገድ ብቻ እንዲፈታ እንደምትሰራም ነው የተናገሩት። የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባለፈው አርብ ሀገራቸው ጉዳዩን ወደ ፀጥታው ምክር ቤት መውሰዷን መግለፃቸው ታወሳል። ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብን የመጀመሪያ የውሃ ሙሌትን በሚቀጥለው ወር ለመጀመር የማንም ፈቃድ እንደማያስፈልጋት አስታውቃለች። በዚህ ክረምት የውሃ ሙሌቱን ለማስጀምር በሚያስችላት ዝግጅት ላይም ትገኛለች ። ሰሞኑን ሶስቱ ሀገራት በግድቡ የመጀመሪያ የውሃ ሙሌት ላይ አንዳች ስምምነት ላይ ለመድረስ በቪዲዮ ኮንፍረንስ ለበርካታ ቀናት ሲደራደሩ የቆዩ ሲሆን፥ በመሰረታው የቴክኒክ ጉዳዮች ላይ ከስምምነት የደረሱ ሲሆን፥ ህግ ሆኖ ለመውጣት በሚያስችሉ የህግ ጉዳዮች ላይ ግን እንደሚቀራቸው ነበር የተገለፀው ። በእስካሁኑ የድርድር ሂደት ላይ ሱዳን ተጨማሪ ምክር እንደምትፈለግ መግለጿን ተከትሎ ድርድሩ ከዚያ በኋላ እንደሚቀጥል በመስማማት ነበር የተለያዩት - #FBC

"ኢትዮጵያ በህዳሴው ግድብ ድርድር ሰበብ የዓባይ ወንዝ ተጠቃሚነቷን የሚገድብ ስምምነት አትቀበልም"- አቶ ገዱ አንዳርጋቸው (በኢትዮጵያ ዜና አገለግሎት የቀረበ ) - ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የምታደር
"ኢትዮጵያ በህዳሴው ግድብ ድርድር ሰበብ የዓባይ ወንዝ ተጠቃሚነቷን የሚገድብ ስምምነት አትቀበልም"- አቶ ገዱ አንዳርጋቸው  (በኢትዮጵያ ዜና አገለግሎት የቀረበ ) - ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የምታደርገው ድርድር ግድቡን በሚመለከቱ ጉዳዮች እንጂ በቀጣይ የዓባይን ወንዝ ተጠቅማ የመልማት መብቷን እንደማያካትት አቶ ገዱ ከ #ኢዜአ በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል። - ግብፅ ከአሁኑ የሦስትዮሽ ድርድር አፈንግጣ መውጣቷን ገልጸዋል። - ሦስቱ አገሮች የሚያደርጉት ድርድር ግድቡን ብቻ እንደሚመለከትና ይህም ኢትዮጵያ በቀጣይ ሌላ ግድብ የመገንባትም ይሁን ፍትሃዊ በሆነ መንገድ ወንዙን የመጠቀም መብቷን የሚያስጠብቅ መሆን እንዳለበት አመልክተዋል። - ኢትዮጵያን ምንም ዓይነት ውጫዊም ይሁን ውስጣዊ ችግር ግድቡን ውሃ ከመሙላት እንደማያግዳት ተናግረዋል። Readmore https://telegra.ph/ENA-06-21

የግብፁ ፕሬዝደንት አብደልፈታህ አል-ሲሲ ሀገራቸው በህዳሴ ግድብ ዙርያ ያለውን ውዝግብ በዲፕሎማሲ መፍታት እንደምትፈልግ አስታውቀዋል! "ወደ ፀጥታው ምክር ቤት የሄድንበት ምክንያት የዲፕሎማሲ እና የ
የግብፁ ፕሬዝደንት አብደልፈታህ አል-ሲሲ ሀገራቸው በህዳሴ ግድብ ዙርያ ያለውን ውዝግብ በዲፕሎማሲ መፍታት እንደምትፈልግ አስታውቀዋል! "ወደ ፀጥታው ምክር ቤት የሄድንበት ምክንያት የዲፕሎማሲ እና የፖለቲካ መንገዱን እስከመጨረሻው ለመጠቀም በማሰብ ነው፣ ስምምነቱ የሁሉንም ሀገራት ጥቅም ያማከለ እንዲሆን እንፈልጋለን" ያሉት ፕሬዝደንቱ ሀገራቸው ቶሎ መቋጫ ላይ የመድረስ ፍላጎት እንዳላት አብራርተዋል። ከዚህ የሬውተርስ ዜና ወስጄ የተረጎምኩት ነው: https://af.reuters.com/article/topNews/idAFKBN23S0AQ-OZAT

ግብጽ “የቅኝ ግዛት ስምምነቶች ተፈጻሚ ናቸው” ስትል ለጸጥታው ምክር ቤት አመለከተች! ( በኢትዮጵያ ኢንሳይደር የቀረበ ) - ግብጽ የህዳሴ ግድቡ ላይ በሚደረጉ ድርድሮች ወቅት “ ‘የቅኝ ግዛት ስም
ግብጽ “የቅኝ ግዛት ስምምነቶች ተፈጻሚ ናቸው” ስትል ለጸጥታው ምክር ቤት አመለከተች! ( በኢትዮጵያ ኢንሳይደር የቀረበ ) - ግብጽ የህዳሴ ግድቡ ላይ በሚደረጉ ድርድሮች ወቅት “ ‘የቅኝ ግዛት ስምምነቶች ተፈፃሚ አይሆኑም’ በሚል በኢትዮጵያ ዘንድ የሚነሳው ጥያቄ አግባብ አይደለም፤ ስምምነቶቹ አሁንም ተፈፃሚ ናቸው” ስትል ከትናንት በስቲያ አርብ፤ ሰኔ 12፤2012 በድጋሚ ለጸጥታው ምክር ቤት በላከችው አቤቱታ አመልክታለች።   - “ኢትዮጵያ በአባይ ላይ የሚደረግ እና የውሃውን ፍሰት ሊይዝ የሚችል ማንኛውንም አይነት ግንባታ ላለማካሄድም ወይም እንዲካሄድ ላለመፍቀድ፤ በ1894ቱ ስምምነት ላይ ቃል ብትገባም ይህንን መቃወሟን ቀጥላለች” ስትል ግብጽ ኢትዮጵያን ወንጅላለች። ግብጽ በአጼ ምኒልክ በኩል የተፈረመውን ይህንን ስምምነትም አባሪ አድርጋም ለምክር ቤቱ ልካለች። - ግብጽ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ያለ ስምምነት የሚሞላ ከሆነ ዓለማቀፍ ሰላም እና ደህንንነትን አደጋ ውስጥ ሊጥሉ የሚችሉ አጸፋዊ እርምጃዎች ልትወሰድ እንደምትችልም አስጠንቅቃለች። - ግብጽ የጸጥታው ምክር ቤት ጉዳዩን በአስቸኳይ “የአፍሪካ የሰላም እና ደህንነንት ጉዳይ” በሚመለከተው አጀንዳው ሾር እንዲመለከተው አሳስባለች። Readmore https://telegra.ph/EthiopiaInsider-06-21

“የግብጽ ጦር ጠንካራ አቅም ካላቸው ሃያል የመካከለኛው ምስራቅ ጦሮች መካከል አንዱ ነው”- አብዱል ፈታህ አልሲሲ ፕሬዝዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ “የግብጽ ጦር ጠንካራ አቅም ካላቸው ሃያል የመካከለ
“የግብጽ ጦር ጠንካራ አቅም ካላቸው ሃያል የመካከለኛው ምስራቅ ጦሮች መካከል አንዱ ነው”- አብዱል ፈታህ አልሲሲ ፕሬዝዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ “የግብጽ ጦር ጠንካራ አቅም ካላቸው ሃያል የመካከለኛው ምስራቅ ጦሮች መካከል አንዱ ነው” ሲሉ ተናገሩ፡፡ “ራሱን የማያስነካ ሌሎችንም የማይነካ” ሲሉ ጦሩን ያሞካሹት ባለ ፊልድ ማርሻል ማዕረጉ አል ሲሲ በሃገር ውስጥም ሆነ ከሃገር ውጭ ያለን የግብጽን ብሄራዊ የደህንነት ፍላጎት ለማስጠበቅ ሚያስችል አቅም እንዳለውም ገልጸዋል፡፡ ፕሬዝዳንቱ በምዕራብ የሃገሪቱ ጦር የዕዝ ማዕከል ተገኝተው የጦሩ አየር ሃይል በምን ቁመና ላይ እንደሚገኝ ገምግመዋል፡፡ በጉብኝቱ ወቅት በሃገር ውስጥም ሆነ ከሃገር ውጭ ለሚያስፈልግ ግዳጅ ጦሩ ዝግጁ እንዲሆን ስለማዘዛቸውም አል አረቢያ የተሰኘው የሳዑዲ ቴሌቪዥን ጣቢያ ዘግቧል፡፡ የጦሩን ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የጦር መኮንንኖችም በጉብኝት ስነ ስርዓቱ ላይ ነበሩ እንደ ፕሬዝዳንቱ ጽህፈት ቤት ቃል አቀባይ ገለጻ፡፡ ምዕራብ ቀጣና ከሃገሪቱ አራት ወታደራዊ ቀጣናዎች አንዱ ሲሆን ከሊቢያ ድንበር አቅራቢያ ማርሳ ማትሩህ በተሰኘ የወደብ አካባቢ ይገኛል፡፡ #AlAin

ግብፅ የሀገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ስለ ታላቁ የህዳሴ ግድብ እንዳይዘግቡ እገዳ ጣለች! የግብፅ መገናኛ ብዙኃን ስለ ታላቁ የህዳሴ ግድብ፣ በሀገሪቱ ስላለው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ እና ከሊቢያ ጋር አገ
ግብፅ የሀገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ስለ ታላቁ የህዳሴ ግድብ እንዳይዘግቡ እገዳ ጣለች! የግብፅ መገናኛ ብዙኃን ስለ ታላቁ የህዳሴ ግድብ፣ በሀገሪቱ ስላለው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ እና ከሊቢያ ጋር አገሪቱ እያረገች ስላለው ጦርነት በተመለከተ ምንም ዓይነት ዘገባ እንዳይሰሩ የሀገሪቱ የመገናኛ ብዙኋን ካውንስል ማገዱን አስታውቋል። ካውንስሉ ባስተላለፈው እገዳ መሰረት የግብፅ መገናኛ ብዙኃን እና የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች መንግስት ከሚሰጠው መግለጫ ውጭ ስለ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ምንም ዓይነት ዘገባም ሆነ ውይይት አንዲሰሩ አይፈቀድላቸውም። በሀገሪቱ የህትመት ሚድያዎች ላይ የሚሰሩ መገናኛ ብዙኋን ይዘቶችን ከማሳተማቸው በፊት ለሚመለከተው የመንግስት አካል ማስገምገም እና በፅሁፍ ጥያቄ አቅርበው ፍቃድ ማግኘት እንዳለባቸውም ተገልጿል። ሀገሪቱ እርምጃውን የወሰደችው ብሄራዊ ጥቅሟን ለማስጠበቅ በሚል ሽፋን ነው ተብሏል፡፡ #EBC

በጤና ሚኒስቴር የህክምና ግልጋሎት ዋና ኃላፊ የሆኑት አቶ ያዕቆብ ሰማን ለቢቢሲ እንደተናገሩት በአንዳንድ ሰዎች ተጋንኖ እንደሚነገረው ሳይሆን የመድኃኒቱ ፋይዳ ከኮቪድ-19 ጋር በተያያዘ በፅኑ ሕክም
በጤና ሚኒስቴር የህክምና ግልጋሎት ዋና ኃላፊ የሆኑት አቶ ያዕቆብ ሰማን ለቢቢሲ እንደተናገሩት በአንዳንድ ሰዎች ተጋንኖ እንደሚነገረው ሳይሆን የመድኃኒቱ ፋይዳ ከኮቪድ-19 ጋር በተያያዘ በፅኑ ሕክምና ላይ የሚገኙ ህሙማንን የሞት መጠን መቀነስ እንደሆነ፣ ይህ አዎንታዊ ጠቀሜታውም በቁጥር ደረጃ ሲሰላ አነስተኛ ነው ብለዋል። ከበሽታው እራስን ከመጠበቅ አንጻርም "በማኅበረሰቡ ዘንድ መዘናጋትን እንዳይፈጠር አሁንም ዋነኛው መተኮር ያለበት መንገድ ባለሞያዎች የሚሰጡት የመከላከያ እርምጃዎች ተግባራዊ መድረግ ነው" ብለዋል አቶ ያዕቆብ ሰማን።

ኢትዮጵያ የውሃ ሙሌቱን እንዳታደርግ የሚያግዳት ስምምነትም ሆነ ህግ የለም! "ኢትዮጵያ የውሃ ሙሌቱን እንዳታደርግ የሚያግዳት ስምምነትም ሆነ ህግ የለም። በመሆኑም በቀጣዩ ሐምሌ ወር ውሃውን እየሞላች
ኢትዮጵያ የውሃ ሙሌቱን እንዳታደርግ የሚያግዳት ስምምነትም ሆነ ህግ የለም! "ኢትዮጵያ የውሃ ሙሌቱን እንዳታደርግ የሚያግዳት ስምምነትም ሆነ ህግ የለም። በመሆኑም በቀጣዩ ሐምሌ ወር ውሃውን እየሞላች በቀሪ ጉዳዮች ላይ ውይይት ማካሄዷን ትቀጥላለች። በዚህ መሰረት በመጀመሪያ ዓመት 4 ነጥብ 9 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ይሞላል፤ በሁለተኛው ዓመት ደግሞ በአጠቃላይ 18 ነጥብ 4 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ይደርሳል። እንዲህ እንዲህ እያለች ኢትዮጵያ 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃውን እንደምትሞላ ግልጽ አድርጋለች። አሁን ላይ የሚደረጉ ውይይቶች በድርቅ ወቅት የውሃ አጠቃቀም ምን ይሁን በሚለው ጉዳይ ላይ ነው። በዚህ ረገድ ስለውሃ ሙሌቱ ስምምነት ሳይደረስ ኢትዮጵያ ውሃ መሙላት አትችልም የሚል ይዘት ያላቸው መረጃዎችን ግብጽም ሆነ አሜሪካ ማውጣታቸው የውይይቱን ይዘት የማይወክሉ እና የተሳሳቱ መሆናቸው መታወቅ አለበት።" [ ኢ/ር ጌዲዮን አስፋው የህዳሴ ግድብ የሦስትዮሽ ድርድር ኮሚቴ አባልና የህዳሴ ግድብ የብሔራዊ ኤክስፐርቶች ፓናል ሰብሳቢ ] #አዲስዘመን

#LiaTadesse "ለኮቪድ-19 ህሙማን የሚውለውን 'ዴክሳሜታዞን' የተባለውን መድሀኒት በተመለከተ በእንግሊዝ መንግስት የተካሄደውን ጥናት እና ሪፖርት በዝርዝር ተመልክተነዋል፡፡ የህክምና ጉዳዮች አ
#LiaTadesse "ለኮቪድ-19 ህሙማን የሚውለውን 'ዴክሳሜታዞን' የተባለውን መድሀኒት በተመለከተ በእንግሊዝ መንግስት የተካሄደውን ጥናት እና ሪፖርት በዝርዝር ተመልክተነዋል፡፡ የህክምና ጉዳዮች አማካሪ ቡድናችን እና የጤና ባለሙያዎች አማካሪ ምክር ቤት፣ የሰጠንን ምክረ ሀሳብ መሰረት በማድረግ፣ ኦክሲጅን ወይም የመተንፈሻ መሳሪያ እገዛ ለሚያስፈልጋቸው የኮቪድ-19 ህሙማን የህክምና ባለሙያዎች በሚያዙት መሰረት ዴክሳሜታዞን እንደ ድንገተኛ ህክምና ለመጠቀም ተወስኗል ። ህክምናውን አስመልክቶ ዝርዝር መመሪያ በቅርቡ ይወጣል።" - ዶ/ር ሊያ ታደሰ

photo content

photo content

photo content