en
Feedback
AIRDROP ROOM

AIRDROP ROOM

Open in Telegram
2 485
Subscribers
No data24 hours
-157 days
-5230 days
Posts Archive
10ኛው የኢትዮጵያ ክልል! (በኢትዮጵያ ኢንሳይደር) በዛሬው የሲዳማ የስልጣን ርክክብ ስነ ስርዓት የታደሙ የሲዳማ ተወላጅ የዞን እና የፌደራል ባለስልጣናት ደስታቸውን በተለያዩ መልኩ ሲገልጹ እንደነበ
10ኛው የኢትዮጵያ ክልል! (በኢትዮጵያ ኢንሳይደር) በዛሬው የሲዳማ የስልጣን ርክክብ ስነ ስርዓት የታደሙ የሲዳማ ተወላጅ የዞን እና የፌደራል ባለስልጣናት ደስታቸውን በተለያዩ መልኩ ሲገልጹ እንደነበር ኢትዮጵያ ኢንሳይደር በፎቶ ዘገባው አሳይቷል። ባለስልጣናቱ እግዚያብሔርን ደጋግመው ሲያመሰግኑ መደመጣቸውንና፤ በይፋዊ ንግግራቸውም ሆነ በስልክ ቃለ ምልልሳቸው ይህንኑ ሲያስተጋቡ እንደነበር ተገልጿል። በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ደስታቸውን በመተቃቀፍ አሊያም በመጨባበጥ መግለጽ ያልቻሉት ባለስልጣናቱ፤ ክርኖቻቸውን በማጋጨት “የእንኳን ደስ አላችሁ” መልዕክት ሲለዋወጡ ታይተዋል። በዛሬው ስነ ስርዓት ላይ የቀድሞዎቹ የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድሮች ደሴ ዳልኬ እና ሚሊዮን ማቲዮስ፣ የቀድሞው እና የአሁኑ የሲዳማ ዞን አስተዳዳሪዎች ቃሬ ጫዊቻ እና ደስታ ሌዳሞ እንዲሁም የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ተገኝተዋል። #EthiopiaInsider

10ኛው የኢትዮጵያ ክልል 'ሲዳማ ክልል' ! የደቡብ ክልልና አዲሱ የሲዳማ ክልል በዛሬው ዕለት በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል ምክር ቤት ፊት ቀርበው የስልጣን ርክክብ አካሂደዋል። ይህን ተ
10ኛው የኢትዮጵያ ክልል 'ሲዳማ ክልል' ! የደቡብ ክልልና አዲሱ የሲዳማ ክልል በዛሬው ዕለት በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል ምክር ቤት ፊት ቀርበው የስልጣን ርክክብ አካሂደዋል። ይህን ተከትሎ ሲዳማ በሀገሪቱ 10ኛው ክልል የሚሆን ሲሆን ፥ የምክር ቤቱ አባላት ለሲዳማ ክልል ህዝብ 'እንኳን ደስ አላችሁ' ብለዋል።

"በሌላ ጉዳይ ላይ ለመነጋገር እንችላለን፤ በመብታችን ላይ በተለይ ደግሞ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብታችን ላይ በተመለከተ ግን መደራደር አንችልም፤ በፍፁም። ይህ ቀይ መስመር ነው። ከዚህ በታች
"በሌላ ጉዳይ ላይ ለመነጋገር እንችላለን፤ በመብታችን ላይ በተለይ ደግሞ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብታችን ላይ በተመለከተ ግን መደራደር አንችልም፤ በፍፁም። ይህ ቀይ መስመር ነው። ከዚህ በታች የሆኑ ብዙ ነገሮች ሊኖሩ ይችላሉ። “ይህን ኣምጣ ይህን ልሰጥህ” ልትል የምትችልበት። በዚህ ጉዳይ ላይ ግን ሰጥቶ መቀበል ብሎ ነገር የለም። ምርጫ መሰረታዊና ትልቅ ነገር ነው። ዋናው ነገር የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት ነው። ያለፈው የትግል ውጤት አስጠብቆ የመሄድና ቀጣዩን የማስተካከል ጉዳይ ነው። ምክንያቱም ያለፈውን አስጠብቀን ነው ቀጣዩን ማስተካከል የምንችለው። በትግራይ እጅግ በጣም የተደራረበ ብዙ ጫና ነው ያለው። እያልን ያለነው ግን ለምንም ጫና አንበገርም ነው። ምንም ዓይነት ጫና አይበግረንም። ግዜ ተጣበበብን ብለንም አንጨናነቅም። ሁላችንም ተጋግዘን ልንሻገረው እንችላለን። ምርጫችን በእጃችን ነው። መብታችንም በእጃችን ነው። የመመከቱ ነገርም እንደዚሁ በእጃችን ነው። ማሟላት ያለብንን ነገር ግን ማሟላት ኣለብን። ለዚህም ጎን ለጎንም ዝግጅት ማድረግም ጀምረናል።" (የድርጅቱ ሊቀ መንበር ጓድ ዶክተር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል)

ሰበር ዜና! ነባሩ የደቡብ ክልል እና አዲሱ የሲዳማ ክልል የስልጣን ርክክብ አካሄዱ! የደቡብ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል ምክር ቤት 5ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 2ኛ አስቸኳይ ጉባኤ ላይ
ሰበር ዜና! ነባሩ የደቡብ ክልል እና አዲሱ የሲዳማ ክልል የስልጣን ርክክብ አካሄዱ! የደቡብ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል ምክር ቤት 5ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 2ኛ አስቸኳይ ጉባኤ ላይ ነባሩ የደቡብ ክልል እና አዲሱ የሲዳማ ክልል በምክር ቤቱ ፊት ቀርበው የስልጣን ርክክብ አካሂደዋል፡፡የስልጣን ርክክቡ ከመካሄዱ በፊት በደቡብ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግሥት በአዳዲስ መዋቅሮች ለመደራጀት የቀረበ ጥያቄ ምላሽና የውሳኔ ሀሳብ የያዘ ሰነድ ለምክርቤቱ ቀርቧል፡፡በቀረበው ሰነድ ላይ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች የደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር አቶ እርስቱ ይርዳ ምላሽ ሰጥተዋል ፡፡የሲዳማ ክልል እራሱን ችሎ በመውጣቱ በሌሎች ህዝቦች ላይ የሚፈጥረው ተጽዕኖ እንደማይኖር ተናግረዋል፡፡የህዝቦች አብሮነት ከዚህ ቀደምም ለረጅም አመታት ተጠናክሮ የቀጠለ ነው ያሉት አቶ እርስቱ ነባሩ ክልል እና አዲሱ ክልል በመደገፍ ለጋራ እድገት እንሰራለን ብለዋል፡፡የምክር ቤቱ አባላት ለሲዳማ ክልል ህዝብ እንኳን ደስ ያላችሁ ብለዋል፡፡ Via SNNPR Communication

የትግራይ ነፃነት ፓርቲ - በመቀሌ ትግራይ ክልልን ከኢትዮጵያ ገንጥሎ ሃገር ለማድረግ መስራት ዋና ዓላማና ግብ ያደረገ ፓርቲ የመሥራች ጉባኤውን አካሄደ። ራሱን የትግራይ ነፃነት ፓርቲ ብሎ የሰየመው
የትግራይ ነፃነት ፓርቲ - በመቀሌ ትግራይ ክልልን ከኢትዮጵያ ገንጥሎ ሃገር ለማድረግ መስራት ዋና ዓላማና ግብ ያደረገ ፓርቲ የመሥራች ጉባኤውን አካሄደ። ራሱን የትግራይ ነፃነት ፓርቲ ብሎ የሰየመው ይህ ፓርቲ በአለፈው ቅዳሜ እና እሁድ በመቀሌ ከተማ የመስራች ጉባኤውን በማካሄድ የፓርቲው ሕገ ደንብና ፕሮግራም በማፅደቅ መሪዎቹን መርጧል። #VOA

#GERD - የዋይት ሀውስ ብሄራዊ የፀጥታ ምክር ቤት በትናንትናው እለት በትዊተር ገጹ፥ “257 ሚሊየን የምስራቅ አፍሪካ ህዝቦች የኢትዮጵያ ጠንካራ አመራርን ለማየት ይሻሉ፤ ይህም ማለት ፍትሃዊ ስም
#GERD - የዋይት ሀውስ ብሄራዊ የፀጥታ ምክር ቤት በትናንትናው እለት በትዊተር ገጹ፥ “257 ሚሊየን የምስራቅ አፍሪካ ህዝቦች የኢትዮጵያ ጠንካራ አመራርን ለማየት ይሻሉ፤ ይህም ማለት ፍትሃዊ ስምምነትን የሚጠይቅ ነው፤ በህዳሴ ግድብ ዙሪያ ያሉ የቴክኒክ ጉዳዮች መፍትሄ አግኝተዋል፤ አሁን ደግሞ የህዳሴ ግድብ ውሃ ሙሌት ከመጀመሩ በፊት ስምምነት ላይ የሚደረስበት ጊዜ ሊሆን ይገባል” የሚል ፅሁፍ በማውጣቱ ብዙዎችን አስቆጥቷል። - "በህዳሴ ግድብ ምክንያት ችግር ይደርስብናል ካሉት ግብፅና ሱዳን ጋር ከ2004 ጀምሮ ያለው ድርድር ዋነኛ የቴክኒካል ጉዳዮች ላይ በትናንትናው እለት መፍትሄ አስቀምጠናል፡፡ የሙሊትና ውሃ አለቃቀቅ ደንብና መመሪያ ድርድሩ ያልተፈቱ የህግ ጉዳዮች አሉት። የሱዳኑ ውሃ ሚኒስትር ጠ/ሚኒስትራቸውን ማነጋገር ስለፈለጉ ድርድሩ በዛሬው እለት አይኖርም"--- የውሀ፣ ኢነርጂ እና መስኖ ልማት ሚኒስት ኢ/ር ስለሺ በቀለ - የሕዳሴ ግድብን አስመልክቶ ፕሬዝዳንት አል ሲሲ ለሚያሳልፉት ማንኛውም ውሳኔ የግብጽ የፓርላማ አባላት ድገፋቸውን ገልጸዋል፡፡ ለፕሬዝዳንት አል ሲሲ በህዳሴ ግድብ እና በሊቢያ ጉዳዮች ላይ አስፈላጊ ውሳኔዎችን እንዲወስኑ ሙሉ ውክልና መስጠታቸውንም የምክር ቤት አባላቱ አስታውቀዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና የሱዳን ሉዓላዊ ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢ ሌፍተናንት ጀነራል መሐመድ ሐምዳን ዳግሎ የአዳማ የኢንዱስትሪ ፓርክን እየጎበኙ ነው። የሱዳን ሉዓላዊ ምክር ቤት ምክትል
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና የሱዳን ሉዓላዊ ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢ ሌፍተናንት ጀነራል መሐመድ ሐምዳን ዳግሎ የአዳማ የኢንዱስትሪ ፓርክን እየጎበኙ ነው። የሱዳን ሉዓላዊ ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢ ሌፍተናንት ጀነራል መሐመድ ሐምዳን ዳግሎ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ለመምከር በትላንትናው ዕለት አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወሳል፡፡ #EBC

የኮሮና ቫይረስን እጅን በመሳም አጠፋለዉ ያለዉ ህንዳዊዉ የሀይማኖት መሪ በኮሮና ቫይረስ ህይወቱ አለፈ በፓርዲያሽ ግዛት ራትላም በተባለች አዉራጃ ነዋሪ የሆነዉ የመንፈሳዊ መሪ አስላም ባባ ለተከታዮቹ
የኮሮና ቫይረስን እጅን በመሳም አጠፋለዉ ያለዉ ህንዳዊዉ የሀይማኖት መሪ በኮሮና ቫይረስ ህይወቱ አለፈ በፓርዲያሽ ግዛት ራትላም በተባለች አዉራጃ ነዋሪ የሆነዉ የመንፈሳዊ መሪ አስላም ባባ ለተከታዮቹ በተለይም ለሴቶች እጆቻቸዉን በመሳም ብቻ የኮሮና ቫይረስን እንደሚፈዉስ ይናገራል፡፡ ይህንን የሰሙ 40 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ላለመያዝ በሚል እጃቸዉ እንዲሳምላቸዉ ወደ ስፍረዉ ያቀናሉ፡፡ እጃቸዉ በባባ አስላም ከተሳመላቸዉ 40 ሰዎች መካከል 20 ያህሉ በቫይረሱ መያዛቸዉሲረጋገጥ ሰባቱ የመንፈሳዊዉ መሪ አስላም ባባ ቤተሰቦች መሆናቸዉ ታዉቋል፡፡ የቫይረሱ ተጠቂ የሆኑ ሰዎች በቅርበት ሲያገኝ የነበረው ባባ አስላም እርሱ በቫይረሱ ይያዛል፡፡ህክምና ቢያገኝም ማገገም ሳይችል ህይወቱ ማለፉን የህንድ ሚንስቴር ይፋ አድርጓል፡፡ ልክ እንደ አስላም ሁሉ ከወራቶች በፊት የጤናናይጄሪያዊዉ ፓስተር የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ቻይና ሄጆ አጠፋዋለሁ በማለት ወደ ቻይና በመጓዝ ቫይረሱን አጠፋዋለሁ ቢልም በቫይረሱ ህይወቱ አልፎ ስርዓቱ ቀብሩ በቻይና ተፈጽሟል፡፡

የሰኔ 14ቱ ግርዶሽ- የትና መቼ በኢትዮጵያ ? በአብዛኛው የኢትዮጵያ ክፍል ፀሐይ ከ60 - 80 ፐርሰነት ተሸፍና ከፊል ግርዶሽ ይታያል፡፡ ከ80 ፐርሰነት በላይ ያለውን ዋናውን ግርዶሽ ግን ከምዕራብ
የሰኔ 14ቱ ግርዶሽ- የትና መቼ በኢትዮጵያ ? በአብዛኛው የኢትዮጵያ ክፍል ፀሐይ ከ60 - 80 ፐርሰነት ተሸፍና ከፊል ግርዶሽ ይታያል፡፡ ከ80 ፐርሰነት በላይ ያለውን ዋናውን ግርዶሽ ግን ከምዕራብ ኢትዮጵያ አንሥቶ እስከ ሰሜን ምሥራቅ ኢትዮጵያ በሚገኝ ስፍራ ጎልቶ ይታያል፡፡ ክስተቱ ወለጋ አካባቢ ጀምሮ ከፊል ጎጃምን ፣ ከፊል ጎንደርን አልፎ ወደ ወሎ ላሊበላን አቋርጦ ይሄዳል፡፡ በእነዚህ ቦታዎች ፀሐይ እስክ 99 ፐርሰንት ተሸፍና ቀለበታዊውን ግርዶሽ ማየት ይቻላል፡፡ ቀለበታዊ ግርዶሽ ማየት ከሚችሉ አነስተኛ ከተሞች/ቦታዎች ቤጊ ፣ ሜቲ፣ መንዲ ፣ ጫልቱ ፣ ቡሬ ፣ አገው ግምጃቤት ፣ እንጅባራ ፣ ግሽ አባይ፣ ሞጣ ፣ ዳሞት ፣ ጋይንት ፣ ንፋስ መውጫ ፣ ጋሸና ፣ ሙጃ ፣ ዋጃ ፣ ቆቦ ፣ ኮረም፣ አላማጣ ፣ ጊራራ እና ላሊበላ ይገኙበታል፡፡ በአዲስ አበባ ፤ ሐዋሳ ፤ ድሬደዋ ፤ መቐለ ፤ ደሴ ፤ አዳማ ፤ በመሳሰሉት ከተሞች ቀለበታዊ ግረዶሽ ባይኖርም ከፊል የፀሐይ ግርዶሽ ግን ይኖራቸዋል - #ESSS

በዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ ከዚህ ቀደም የነበረውና ትላንት ለኮሮና ፅኑ ህሙማን ይሆናል የተባለው ዴክሳሜታሶን በተባለው መድኃኒት ላይ የተደረገው ሙከራና ያስገኘውን ውጤት መልካም ዜና መሆኑን የዓለም
በዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ ከዚህ ቀደም የነበረውና ትላንት ለኮሮና ፅኑ ህሙማን ይሆናል የተባለው ዴክሳሜታሶን በተባለው መድኃኒት ላይ የተደረገው ሙከራና ያስገኘውን ውጤት መልካም ዜና መሆኑን የዓለም ጤና ድርጅት አስታወቀ። በሙከራው ይህ መድኃኒት በኮሮናቫይረስ በጽኑ የታመሙ ሰዎች ብቻ ሕይወት በ1/3ኛ መታደግ እንደሚችል እና በወረርሽኙ ሰበብ ኦክስጂን በሚያስፈልጋቸው ሰዎች ላይ የሚያጋጥምን ሞት በአንድ አምስተኛ ሊቀንስ እንደሚችል ለድርጅቱ የቀረበው የመጀመሪያ ደረጃ ግኝት አመልክቷል። የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድኃኖም እንዳሉት "ይህ ኦክስጂንና የመተንፈሻ መርጃ መሳሪያ ለሚያስፈልጋቸው የኮሮናቫይረስ ህሙማን ላይ የሚያጋጥምን ሞት የሚቀንስ የመጀመሪያው መድኃኒት ነው" ብለዋል። ዋና ዳይሬክተሩ ይህም ታላቅ ዜና መሆኑን ጠቅሰው የዩናይትድ ኪንግደም መንግሥትንና ይህንን ህይወትን የሚታደግ የመጀመሪያ ግኝት ላይ በመሳተፍ አስተዋጽኦ ላበረከቱት ለኦክስፎርድ ዩኒቨርስቲ፣ ለሆስፒታሎችና ለህሙማን የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

አዲስ አበባ - ሴት ልጆቿን ለጨረታ የምታቀርብ ከተማ ( በአዲስ ማለዳ የቀረበ ) አዲስ ማለዳ ጋዜጣ ሰኔ 6 ይዞት በወጣው ዕትሙ በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች ስላሉ የራቁት ጭፈራ ቤቶች፣ ሴቶች
አዲስ አበባ - ሴት ልጆቿን ለጨረታ የምታቀርብ ከተማ ( በአዲስ ማለዳ የቀረበ ) አዲስ ማለዳ ጋዜጣ ሰኔ 6 ይዞት በወጣው ዕትሙ በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች ስላሉ የራቁት ጭፈራ ቤቶች፣ ሴቶች እንደ እቃ ለጨረታ የሚቀርቡበትና የሚሸጡበት፣ በእድሜ የገፉ ሰዎች ለመዳራት ንቁ የሚሆኑበትና ከዛም አልፎ ግልጽ ወሲባዊ መዳራቶችን ስለሚፈጸሙበት ሥፍራዎች የምርመራ ዘገባ ሰርቷል፡፡ ድርጊቱ በተለይም ሴት ልጆች ላይ የሚደርሱ በደሎችና ጥቃቶች፣ እናቱን በሴት አንቀጽ የሚጠራ ለሞላባት፣ ለእናት የተዘፈነ እልፍ ሙዚቃ በሚንቆረቆርባት አገር፣ የሚፈጸም ድርጊት ነውን ብሎ ለመጠየቅ ያስደፍራል፡፡ ደግሞም በዚህ ተግባር ላሉ ደላሎች የኮቪድ 19 ወረርሽኝ መከሰት ስጋት አይደለም፣ ይልቁንም ወጣትና አዳጊ እድሜ ክልል ላይ የሆኑ ሴቶች በቀላሉ እንዲገኙ ያስቻለ መልካም አጋጣሚ ፈጥሮላቸዋል ሲል ይገልጻል፡፡ ሙሉ ዘገባውን በዚህ ያንብቡ https://addismaleda.com/archives/12358

የሕዳሴ ግድብ የፕሮጀክት አፈጻጸም 74 በመቶ ደርሷል! የገድቡ ሥራ አስኪያጁ ኢንጅነር ክፍሌ ሆሮ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት ፣ ፕሮጀክቱ በሙሉ አቅም በሁሉም አቅጣጫ በሶስት ሽፍት እየ
የሕዳሴ ግድብ የፕሮጀክት አፈጻጸም 74 በመቶ ደርሷል! የገድቡ ሥራ አስኪያጁ ኢንጅነር ክፍሌ ሆሮ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት ፣ ፕሮጀክቱ በሙሉ አቅም በሁሉም አቅጣጫ በሶስት ሽፍት እየተሰራ ነው ። የግድቡ የሲቪል ኢንጅነሪንግ ሥራው 87 በመቶ ፣የብረታ ብረት ሥራዎቹ ደግሞ ከ 31 በመቶ በላይ ፤ የኤሌክትሮ ሜካኒካል የተርባይንና የጀነሬተር ሥራዎች አፈጻጸምም 45 በመቶ ፤ አጠቃላይ የፕሮጀክቱን አፈጻጸም ደግሞ 74 በመቶ ደርሷል ብለዋል። ለሁለቱ ቅድመ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የሚሆን የብረታ ብረት ሥራዎች ተከናውነው ኮንክሪት እየተሞሉ መሆኑን የጠቆሙትሥራ አስኪያጁ በቀጣይም የጀነሬተር ተርባይን ተከላ እንደሚጀመር ገልጸዋል። በኤሌክትሮ ሜካኒካሉም፣ በሲቪሉም፣ በብረታ ብረት ሥራውም በሶስት ሽፍት ያለ እረፍት እየተሰራ ነው፤ ይህም በጣም አስደሳችና እስከ ዛሬ ያልተሰራበት አካሄድ ነውም ሲሉ ነው ያስረዱት፡፡ ‹‹በዚህ ዓመት ውሃ ሙሌቱ ይጀመራል ስላልን ብቻ ሳይሆን አሁን ላይ ያለው የግድቡ ሥራ አፈጻጸም በራሱ የውሃ ሙሌት እንዲጀመር አስገዳጅ ነው›› ያሉት ሥራ አስኪያጁ፣ ‹‹የመካከለኛውን የግድቡን ክፍል ከ 525 ወደ 560 ሜትር ከፍ እያደረግን ስለምንሄድ ውሃ ሙሌቱ ያስፈልጋል፤ በዚህም 4 ነጥብ 9 ቢሊዮን ሜትር ኩዩብ ውሃ እንይዛለን። በሚቀጥለው ዓመት ደግሞ ሁሉም ነገር ተስተካክሎልን ከሰራን ወደ 590 ሜትር ስለምናደርሰው ውሃ የመያዝ አቅማችን 16 ነጥብ 5 ሜትር ኩዩብ ይሆናል›› ብለዋል። #አዲስዘመን

ማምሻውን የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰን ዛሬ በስፋት ስለተነገረለት ዴክሳሜታሶን ስለተባለው መድሀኒት ጠይቄያቸው ነበር! በሰጡኝ መልስ "የክሊኒካል አማካሪ ቡድናችን በዚህ መድሀኒት ዙርያ የወጣውን
ማምሻውን የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰን ዛሬ በስፋት ስለተነገረለት ዴክሳሜታሶን ስለተባለው መድሀኒት ጠይቄያቸው ነበር! በሰጡኝ መልስ "የክሊኒካል አማካሪ ቡድናችን በዚህ መድሀኒት ዙርያ የወጣውን ጆርናል እየገመገመው ነው፣ ነገ አንድ ድምዳሜ ላይ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል። በመድሀኒቱ ዙርያ የቀረበው ማስረጃ ላይ ስምምነት ላይ ከተደረሰ ዴክሳሜታሶን በሀገራችን በስፋት ስለሚገኝ ችግር አይሆንም" ብለዋል። አሁንም በድጋሜ ለማስታወስ: መድሀኒቱ ቬንትሌተር እና ኦክስጅን የሚጠቀሙ ፅኑ ህሙማን ላይ ከፍ ያለ ውጤት አሳይቷል ተብሎ ተገልጿል። ነገር ግን ሙሉ ለሙሉ ቫይረሱ ያለባቸውን ሰዎች የመፈወስ አቅም እንደሌለው ይፋ የተደረገው ምርምር ያሳያል። በመድሀኒቱ ውጤት ተስፋ እያረግን ጥንቃቄያችንን እንቀጥል!

#Dexamethasone 'ዴክሳሜታሰን' የተባለው መድሃኒት በኮሮና ቫይረስ በሽታ በፅኑ የታመሙትን ሰዎች ህይወት ለመታገድ እንደሚረዳ የብሪታንያ ተመራማሪዎች ገለፁ። ሳይንቲስቶቹ በህክምና ላይ ያሉና
#Dexamethasone 'ዴክሳሜታሰን' የተባለው መድሃኒት በኮሮና ቫይረስ በሽታ በፅኑ የታመሙትን ሰዎች ህይወት ለመታገድ እንደሚረዳ የብሪታንያ ተመራማሪዎች ገለፁ። ሳይንቲስቶቹ በህክምና ላይ ያሉና በቬንትሌተር የሚተነፍሱት ታማሚዎችን የመሞት እድል በአንድ ሶስተኛ እንደሚቀንስ የገለጹ ሲሆን በኦክስጅን ውስጥ ያሉትን የመሞት ዕድላቸውን በአንድ አምስተኛ እንደሚቀንስ ተናግረዋል፡፡ ይህ መድሃኒት የኮቪድ-19 ለማከም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከተደረጉ ትልልቅ ሙከራዎች አንዱ መሆኑንም ነው የቢቢሲ ዘገባ የሚያመለክተው፡፡ ተመራማሪዎቹ የኮሮና ቫይረስ ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ይህ መድሃኒት ጥቅም ላይ ውሎ ቢሆን ኖሮ የአምስት ሺ ሰዎችን ሕይወት ማትረፍ ይቻል እንደነበርም አስታውቀዋል፡፡ ይህ መድሃኒት (ዴክሳሜታሶን) ዋጋው በጣም አነስተኛ እና ለድሃ ሀገራትም ጭምር በቀላሉ ሊገዙት የሚችሉት መሆኑ ተገልጿል፡፡ ምንጭ፦ ቢቢሲ ፣ አል ዓይን

"ተወካዮቹ ራሳቸውን ማግለላቸው የስልጣን ርክክቡን አያደናቅፈውም"- የወላይታ ዞን አ/ር በትናንትናው ዕለት የደቡብ ክልል ምክር ቤት የወላይታ ሕዝብ ተወካዮች ራሳቸውን ከምክር ቤቱ አባልነት ማግለላቸ
"ተወካዮቹ ራሳቸውን ማግለላቸው የስልጣን ርክክቡን አያደናቅፈውም"- የወላይታ ዞን አ/ር በትናንትናው ዕለት የደቡብ ክልል ምክር ቤት የወላይታ ሕዝብ ተወካዮች ራሳቸውን ከምክር ቤቱ አባልነት ማግለላቸው በፍጹም በሕገመንግስቱ መሠረት በሕዝበ ውሳኔ ያለቀለትን የሲዳማ ሕዝብ የሥልጣን ርክብክብ ሊያደናቅፈውም ሆነ ተጽዕኖ ሊያሳድርበት አይችልም ሲል የወላይታ ዞን አስተዳደር ገልጿል፡፡ ህዝቡ ያነሳውን የክልልነት ጥያቄ የክልሉ ምክር ቤት ተገቢ ትኩረት ሳይሰጥ ጉዳዩ ወደ ፌዴሬሽን ምክርቤት በአቤቱታ መልክ በተላከበት ወቅት ምክርቤቱ ከዚህ በኃላ በህጉ መሠረት የህዝቡን ጥያቄ የሚመለስበት ህጋዊ አግባብ ባለመኖሩ የምክር ቤቱ የወላይታ ተመራጮች ከምክር ቤቱ አባልነት መልቀቃቸውን በወቅቱ በፊርማቸው አረጋግጠዋል፡፡ በትላንትናው ዕለት የተሰጠው መግለጫም ከሰሞኑ ምክር ቤቱ የስብሰባ ጥሪ በማቅረቡ የተሰጠ እንጂ የሲዳማን ህዝብ ህገመንግስታዊ የመብት ጥያቄ ድል ለማደናቀፍ አይደለም፤ ሊሆንም አይችልም ብሏል። የወላይታ ህዝብ ህገመንግስታዊ መብት ጥያቄውን በበሰለ አካሄድ ሲያካሄድ እንደነበር በመግለጫው ጠቅሶ አንዳንድ ከአጎራባች ህዝቦች ጋር ያለው ህዝብ ግንኙነት እንዲሻክር እየጣሩ የሚገኙ ግለሰቦች በዎላይታ አከባቢ መንገድ ለመዝጋት ዝግጅት እየተረገ ነው በሚል የሚናፈሰው የውሸት ወሬ ትክክል አለመሆኑንም ጭምር ገልጿል፡፡

#UPDATE በኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤና በሀገር ሽማግሌዎች የተጀመረው ይህ የእርቅና የሸምግልና ሀሳብ አንድ ደረጃ አድጎ አሳታፊ ድርድር በሁሉም ወገን እንዲደረግ ሀገራዊ መድረክ መከፈት እ
#UPDATE በኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤና በሀገር ሽማግሌዎች የተጀመረው ይህ የእርቅና የሸምግልና ሀሳብ አንድ ደረጃ አድጎ አሳታፊ ድርድር በሁሉም ወገን እንዲደረግ ሀገራዊ መድረክ መከፈት እንዳለበትም ስምምነት ላይ ተደርሷል ተብሏል። አትሌት ሺ አለቃ ሀይሌ ገብረ ስላሴ ለአውሎ ሚዲያ እንደተናገረው ውይይቱ ስኬት የተገኘበት ሲሆን ሀገር አቀፍና አሳታፊ ለማድረግ ይህ የሀገር ሽማግሌዎች መማክርት ጉባኤ ቀጣይ የቤት ስራ በመያዝ ወደ ተሻለ እና በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ድርድርና ውይይት የሚያካሒድበትን መድረክ ያዘጋጃል ብሏል። በትግራይና በፌዴራል መንግስት ብቻ ሳይሆን በመላ ሀገሪቱ የፖለቲካ ውጥረት በመኖሩ ውይይቱና ድርድሩ ሀገር አቀፍና አጀንዳ ተኮር እንዲሆን ለማድረግ ታቅዷል ነው ያለው አትሌት ሺ አለቃ ሀይሌ ገብረስላሴ። የሀገር ሽማግሌዎችና የሀይማኖት ተቋማት መሪዎችን ያካተተው 52 አባላት ያሉት ይህ የእርቅና የሰላም ቡድን ውይይቱን አጠናቆ አሁን ምሽት አዲስ አበባ ገብቷል። #አዉሎሚዲያ

"ሁሉም የፖለቲካዊ ድርጅቶች፣ የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች የሚሳተፉበት አገራዊ መድረክ መዘጋጀት አለበት” - ዶ/ር ደብረፅዮን የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የበላይ ጠባቂ አባቶች እና የአገር
"ሁሉም የፖለቲካዊ ድርጅቶች፣ የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች የሚሳተፉበት አገራዊ መድረክ መዘጋጀት አለበት” - ዶ/ር ደብረፅዮን የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የበላይ ጠባቂ አባቶች እና የአገር ሽማግሌዎች መማክርት በአገራችን ውስጥ በተፈጠረው ፖለቲካዊ ውጥረት መሰረት በማድረግ በመቐለ ከተማ ተገኝተው ከትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ከፍተኛ አመራሮች ጋር የውይይት መደረክ አካሂደዋል፡፡  ተቋማቱ ለውይይቱ መነሻ ይሆናል ያሉት ሀሳብ በፅሑፍ ያቀረቡ ሲሆን "የትግራይ ክልል አመራር ከፌደራል መንግስት አመራር ጋር በክብ ጠረጴዛ በሰከነ ዴሞክራሲያዊ መንገድ ስለአጠቃላይ አገራዊ መግባባት ፣ አለምአቀፍና አገር ወለድ ተግዳሮቶችን በጋራ ለመፍታት በአስቸኳይ ግንኙነት እንዲያደርጉ ያሳስባል" በውይይቱ የትግራይ ብሄራዊ ክልልላዊ መንግስት ምክትል ርእስ መስተዳድር ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል የውውይት መድረክ መፈጠር ካለበት፣ ሁሉም የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ድርጅቶች፣ የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች የሚሳተፉበት አገራዊ መድረክ መዘጋጀት አለበት ብለዋል፡፡ ውይይቱ በመጨረሻ ሰአት የተጀመረ ቢሆንም መሞከሩ ግን ጥሩ ነው ያሉት ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ይህን መሰል መድረክ ሲዘጋጅ መፍትሔ ለማምጣት ተፈልጎ ከሆነ ቢያንስ ትግራይ ውስጥ የሚገኙ ፖለቲካዊ ድርጅቶች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ሌሎች የሚመለከታቸው የህብረተሰብ ክፍሎች መሳተፍ ነበረባቸው ሲሉ አክለው ገልጸዋል። Readmore https://telegra.ph/TPLF-06-16 #TPLF

የፀሐይ ግርዶሽ እና ጥንቃቄ! የፀሐይ ግርዶሽን በዓይን በቀጥታ መመልከት ቋሚ ጉዳት በዓይን ላይ ያደርሳል። ግርዶሹን ለመመልከት ፦ 1. ደረጃውን የጠበቀ የግርዶሽ መነፅር መጠቀም 2. ፒን ሆል ካሜራ
የፀሐይ ግርዶሽ እና ጥንቃቄ! የፀሐይ ግርዶሽን በዓይን በቀጥታ መመልከት ቋሚ ጉዳት በዓይን ላይ ያደርሳል። ግርዶሹን ለመመልከት ፦ 1. ደረጃውን የጠበቀ የግርዶሽ መነፅር መጠቀም 2. ፒን ሆል ካሜራ ወይም በአነስተኛ ቀዳዳ ወደ ድፍን ካርቶን የሚገባውን ብርሃን የሚስለውን ስእል ጀርባ ለፀሐይ በማዞር መመልከት 3. ጨለማ ክፍል ውስጥ በቀዳዳ የሚገባውን የፀሐይ ብርሃን መሬት ወይም ግድግዳ ላይ የሚሰራውን ስእል መመልከት 4. በዛፎች ቅጠል አልፎ መሬት ላይ የሚያርፈውን የፀሐይ ስእል መመልከት 5. ለቴሌስኮፕም ሆነ ባይነኩላር የፀሐይ ብርሃን መጣኝ ደረጃውን የጠበቀ ፊልተር ግጥሞ መመልከት 6. ግርዶሹን የሚያሳዩ የቀጥታ ስርጭቶችን መመልከት የፀሐይ መነፅር ፣ ፍሎፒ ዲስክ ፣ የፎቶ ፊልም ፣የራጅ ፊልም እና የመሳሰሉት ቁሶች መጠቀም በዓይን ላይ ጉዳት ያደርሳል - #ESSS

ሜጀር ጄነራል ከፍያለው አምደ ተሰማ በተመድ ዋና ጸሀፊ ሹመት ተሰጣቸው ኢትዮጵያዊው ሜጀር ጄነራል ከፍያለው አምደ ተሰማ በደቡብ ሱዳን እና ሱዳን በሚወዛገቡባት አብዬ ግዛት በተባበሩት መንግስታት ድር
ሜጀር ጄነራል ከፍያለው አምደ ተሰማ በተመድ ዋና ጸሀፊ ሹመት ተሰጣቸው ኢትዮጵያዊው ሜጀር ጄነራል ከፍያለው አምደ ተሰማ በደቡብ ሱዳን እና ሱዳን በሚወዛገቡባት አብዬ ግዛት በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ስር ለሚንቀሳቀሰው ሰላም አስከባሪ ሀይል አዛዥ ሆነው በአንቶኒዮ ጉተሬዝ ሹመት ተሰጣቸው ። ሜጀር ጄነራል ከፍያለው ሌላውን የሀገራቸው ልጅ ሜጀር ጄነራል መሃሪ ዘውዴ ገብረማርያምን በመተካት ነው የተሾሙት። ሜጀር ጄነራል መሃሪ ዘውዴ ግዳጃቸውን ሀምሌ 2020 እንደሚያጠናቅቁም ይጠበቃል። ሹመት የተሰጣቸው ሜጀር ጄነራል ከፍያከው ከ30 ዓመት በላይ ልምድ እንዳላቸው የተገለጸ ሲሆን የኢትዮጵያ መከላከያ ምክር ቤት አባልም ነበሩ ተብሏል። በሩሲያና በአሜሪካ መማራቸውንም የመንግስታቱ ድርጅት ድረ ገጽ አስታውቋል። #AlAin

በኢትዮጵያ ተጨማሪ 176 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል! ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 5,636 የላብራቶሪ ምርመራ 176 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራ
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 176 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል! ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 5,636 የላብራቶሪ ምርመራ 176 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 3,521 ደርሷል። ቫይረሱ የተገኘባቸው 116 ወንድ እና 60 ሴት ሲሆኑ የዕድሜ ክልላቸው ከ5 እስከ 90 ዓመት ውስጥ ይገኛል። በዜግነት 175 ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ 1 ሰው የውጭ ሀገር ዜጋ ነው። ቫይረሱ የተገኘባቸው 98 ሰዎች ከአዲስ አበባ፣ 33 ሰዎች ከአማራ ክልል፣ 31 ሰዎች ከትግራይ ክልል፣ 7 ሰዎች ከሱማሌ ክልል፣ 3 ሰዎች ከኦሮሚያ ክልል፣ 2 ሰዎች ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እና 2 ሰዎች ከአፋር ክልል ናቸው። ተጨማሪ መረጃ ፦ በትላንትናው ዕለት ሰባ አምስት (75) ሰዎች (31 ከአዲስ አበባ፣ 28 ከሱማሌ ክልል፣ 10 ከኦሮሚያ ክልል፣ 5 ከአማራ ክልል እና 1 ከአፋር ክልል) ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 620 ደርሷል።