en
Feedback
AIRDROP ROOM

AIRDROP ROOM

Open in Telegram
2 485
Subscribers
No data24 hours
-157 days
-5230 days
Posts Archive
አቶ ልደቱ አያሌው ፍርድ ቤት ቀረቡ! አቶ ልደቱ አያሌው በዛሬው ዕለት በኦሮሚያ ክልል ቢሾፍቱ ወረዳ ፍርድ ቤት ቀርበው ነበር፡፡ ፖሊስ በሰኔ 23 ቀን 2012 በቢሾፍቱ ከተማ ለወጣቶች ገንዘብ በመስ
አቶ ልደቱ አያሌው ፍርድ ቤት ቀረቡ! አቶ ልደቱ አያሌው በዛሬው ዕለት በኦሮሚያ ክልል ቢሾፍቱ ወረዳ ፍርድ ቤት ቀርበው ነበር፡፡ ፖሊስ በሰኔ 23 ቀን 2012 በቢሾፍቱ ከተማ ለወጣቶች ገንዘብ በመስጠት ለብጥብጥና አመፅ በማነሳሳት በሚል ወንጀል እንደጠረጠራቸው አስታውቋል። ባለፈው አርብ አራት ሰዓት ላይ በቁጥጥር ሾር እንዳዋላቸውና በዚህም ወቅት ሁለት ሽጉጦች ማግኘቱን አስታውቋል። የሰው እና የሰነድ ማስረጃ ለማቅረብም የ14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜንም የኦሮሚያ መርማሪ ፖሊስ ጠይቋል። አቶ ልደቱ በበኩላቸው ቋሚ አድራሻቸው አ/አ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፣ መታወቂያቸውም በዚያው መሆኑን በማንሳት በፌደራል ፍርድ ቤት ነው መቅረብ ያለብኝ በሚል መቃወሚያ አንስተዋል። በተጨማሪ በዋስ እንዲፈቱ የጠየቁ ሲሆን የዛሬ ዓመት የልብ ቀዶ ጥገና ወዳደረጉበት ሀገር ዛሬ 4 ሰዓት ላይ ለመጓዝ የተዘጋጁ መሆናቸውንና ትኬት ያላቸው ቢሆንም አሁን ታስረው እንደሚገኙና የአስም በሽተኛ መሆናቸውን ለፍርድ ቤቱ ገልፀዋል። የእስር አያያዙም ለኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) እንዳያጋልጠኝ ያሰጋኛል በማለት ይህ ታሳቢ ተደርጎ በዋስ ይፍታኝ ብለዋል። መርማሪ ፖሊስ á‹¨áŠĽáˆľáˆ­ አያያዛቸው ምቹ እና ጥንቃቄ ያለው መሆኑን እና ከእስር ቢፈቱ ማስረጃ እንደሚሸሽበት በማሳወቅ ዋስትናውን ተቃውማል። የሁለቱን ክርክር ያዳመጠው ፍርድ ቤቱ áŒ‰á‹łá‹Ťá‰¸á‹ በዚያው በቢሾፍቱ አይታይ በሚል áˆ‹á‰€áˆ¨á‰Ąá‰ľ ወንጀሉ የተፈፀመው በቢሾፍቱ በመሆኑና መኖሪያቸው በዚያው በመሆኑ ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን እዚያው የማየት ስልጣን እንዳለው አስረድቷል፤ የዋስትና ጥያቄውንም ውድቅ በማድረግ ለመርማሪ ፖሊስ ተጨማሪ 14 ቀን የምርመራ ጊዜ ፈቅዷል። ምንጭ፦ https://telegra.ph/fbc-07-27 @ethiocheck

ችሎት! የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ [ኦፌኮ] አመራር አቶ ደጀኔ ጣፋ እና አቶ ኮርሳ ደቻሳ በኮሮና በሽታ ተይዘው በሆስፒታል ህክምና ላይ በመሆናቸው ፤ ዛሬ በነበራቸው የፍርድ ቤት ቀጠሮ ላይ ሳይገኙ
ችሎት! የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ [ኦፌኮ] አመራር አቶ ደጀኔ ጣፋ እና አቶ ኮርሳ ደቻሳ በኮሮና በሽታ ተይዘው በሆስፒታል ህክምና ላይ በመሆናቸው ፤ ዛሬ በነበራቸው የፍርድ ቤት ቀጠሮ ላይ ሳይገኙ መቅረታቸውን ጠበቆቻቸው ገለጹ። ፖሊስ አቶ ደጀኔን ጨምሮ በተመሳሳይ መዝገብ የተካቱቱ ሶስት ተጠርጣሪዎችን ፤ የድምጻዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያን ተከትሎ በአዲስ አበባ ፣ ቡራዮ እና በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች በተቀሰቀሰው ሁከት ፤ 'ተሳትፎ አላቸው' በሚል እንደጠረጠራቸው ለፍርድ ቤት አስታውቋል። የሶስቱን ተጠርጣሪዎች የጊዜ ቀጠሮ ጉዳይ እየተመለከተ የሚገኘው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት፤ የ8 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ለፖሊስ መፍቀዱን ጠበቃቸው ተናግረዋል። ከተጠርጣሪዎቹ መካከል በዛሬው ችሎት የቀረቡት አቶ ሚሻ አደም ብቻ ናቸው። @ethiocheck

ችሎት! የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) የብሔራዊ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል እና የሙያ ማኅበራት ተጠሪ ሂሩት ክፍሌ ዛሬ ሰኞ ሐምሌ 20 ቀን 2012 ዓ·ም ፍርድ ቤት ቀርበው ነበር
ችሎት! የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) የብሔራዊ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል እና የሙያ ማኅበራት ተጠሪ ሂሩት ክፍሌ ዛሬ ሰኞ ሐምሌ 20 ቀን 2012 ዓ·ም ፍርድ ቤት ቀርበው ነበር። ፖሊስ ተጨማሪ ምርመራዎች ለማድረግ 14 ቀን ጊዜ ቀጠሮ የጠየቀ ሲሆን፤ የሂሩት ክፍሌ ጠበቃ ፖሊስ ከዚህ ቀደም ምርመራ እንዲያደርግ በተሰጠው 10 ቀን በቂ ምርመራ ሳያደርግ ተጨማሪ ጊዜ መጠየቁ አግባብ ባለመሆኑ ፍርድ ቤቱ የጊዜ ቀጠሮ መዝገቡን ዘግቶ የደንበኛቸውን የዋስትና መብት እንዲያስከብር ጠይቀው ነበር። ፍርድ ቤቱ ክርክሩን አዳምጦ መዝገቡን ለመመርመር ተጨማሪ ጊዜ ወስዶ ካየ በኋላ ፖሊስ የምርመራ መዝገቡን አጠናቆ እንዲያቀርብ ተጨማሪ 8 ቀን ፈቅዷል። በሌላ መረጃ የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ (OMN) ባልደረባ የነበሩት አቶ ሸምሰዲን ጣሃ ዛሬ ሰኞ ሐምሌ 20/2012 የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ቀርበው እንደነበር ጠበቃቸው ተናግረዋል። ፖሊስ ተጨማሪ 8 የምርመራ ቀናት ተፈቅዶለታል። @ethiocheck

የችሎት ውሎ (4)፦ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ምክትል ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባ "ከህመምተኛ ልጃቸው ጋር እንዳይገናኙ በመከልከላቸው ለ3 ቀናት የረሃብ አድማ አድርገው እንደነበር" ፤
የችሎት ውሎ (4)፦ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ምክትል ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባ "ከህመምተኛ ልጃቸው ጋር እንዳይገናኙ በመከልከላቸው ለ3 ቀናት የረሃብ አድማ አድርገው እንደነበር" ፤ ዛሬ በነበራቸው የፍርድ ቤት ውሎ መናገራቸውን ጠበቃቸው አቶ ቱሊ ባይሳ ለ"ኢትዮጵያ ኢንሳይደር" ተናገሩ። የአቶ በቀለ ገርባን የጊዜ ቀጠሮ ጉዳይ በዛሬው ውሎው የተመለከተው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት፤ 8 ተጨማሪ የምርመራ ቀናት ለፖሊስ መፍቀዱን ጠበቃቸው ገልጸዋል። ፖሊስ ፍርድ ቤቱን የጠየቀው 14 ቀናትን እንደነበርም ጠቁመዋል። @ethiocheck

በዩናይትድ ኪንግደም በድመት ላይ ኮሮናቫይረስ ተገኘ ================= በዩናይትድ ኪንግደም ድመት ላይ ኮቪድ-19 መገኘቱን የአገሪቷ የእንስሳት ጤና ባለሙያ አስታወቁ። በአገሪቷ ቫይረሱ በእ
በዩናይትድ ኪንግደም በድመት ላይ ኮሮናቫይረስ ተገኘ ================= በዩናይትድ ኪንግደም ድመት ላይ ኮቪድ-19 መገኘቱን የአገሪቷ የእንስሳት ጤና ባለሙያ አስታወቁ። በአገሪቷ ቫይረሱ በእንስሳት ላይ ሲገኝ ይህ የመጀመሪያው ነው ተብሏል። ውጤቱ ይህንን ቢያሳይም መንግሥት ግን እንስሳዋ በሽታውን ለአሳዳሪዋ ወይም ለሌሎች የቤት እንስሳት ለማስተላለፏ እንዲሁም ቫይረሱን ወደ ሰው ማስተላለፍ እንደምትችል የሚያሳይ ምንም አይነት ማስረጃ አለመኖሩን ተናግሯል። የምርመራ ውጤቱ የተረጋገጠው ረቡዕ ዕለት ሲሆን፤ የተካሄደውም በዌይብሪጅ ቤተ ሙከራ ነበር። ይህንንም ተከትሎ የኢንግላንድ የሕብረተሰብ ጤና ተቋም ሰዎች ከእንስሳት ጋር ከመነካካታቸው በፊት እና በኋላ እጃቸውን እንዲታጠቡ መክሯል። @ethiocheck

#ችሎት ከሰኔ 15ቱ የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ግድያ ወንጀል በተከሰሱ በእነ ሻምበል ማማር ጌትነት መዝገብ የሚገኙ 49 ተከሳሾች በአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ክስ ቀርቦ የኮቪድ 19 ወረርሽ
#ችሎት ከሰኔ 15ቱ የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ግድያ ወንጀል በተከሰሱ በእነ ሻምበል ማማር ጌትነት መዝገብ የሚገኙ 49 ተከሳሾች በአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ክስ ቀርቦ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ በሽታ ምክኒያት ከሰኔ 22 ቀን 2012ዓ.ም ጀምሮ አስከ ሐምሌ 17 ቀን 2012ዓ.ም በተለያዩ የስራ ቀናት በመነጣጠል ተከሳሾች የእምነት ክህደት ቃላቸውን ሲሰጡ ቆይተዋል፡፡ ሃምሌ 17 ቀን 2012ዓ.ም በዋለው ችሎት የምስክር አሰማምን በተመለከተ የትኛው ምስክር በየትኛው ተከሳሽ ላይ እንደሚመሰክር በመለየት ለፍርድ ቤቱ ለሐምሌ 24 ቀን 2012ዓ.ም እንዲቀርብ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡ በእነ ሻምበል ማማር ጌትነት መዝገብ የሚገኙ አጠቃላይ ተከሳሾች 55 ሲሆኑ ከስድስቱ ተከሳሾች ወስጥ አራቱ ተከሳሾች ላይ የጋዜጣ ጥሪ መደረጉን የክልሉ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታውቋል፡፡ https://telegra.ph/ANRSAG-07-25 @ethiocheck

የግድቡ የመጀመሪያው ዙር የውሃ ሙሌት የአባይ ወንዝ ባለቤትነታችን በዓለም ሁሉ ታውቆና ጸንቶ እንዲኖር አድርጓል — አቡነ ማቲያስ -------------------------------------------
የግድቡ የመጀመሪያው ዙር የውሃ ሙሌት የአባይ ወንዝ ባለቤትነታችን በዓለም ሁሉ ታውቆና ጸንቶ እንዲኖር አድርጓል — አቡነ ማቲያስ ---------------------------------------------------------- ”የህልውናችንና የማንነታችን ልዩ ጸጋ የሆነው የህዳሴ ግድብ የመጀመሪያው ዙር የውሃ ሙሌት በድል መጠናቀቃችን የአባይ ወንዝ ባለቤትነታችንን በዓለም ሁሉ ታውቆና ጸንቶ እንዲኖር አድርገናል” ሲሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን ፓትርያርክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ገለጹ፡፡ ፓትርያርኩ የግድቡ የመጀመሪያው ዙር የውሃ ሙሌት መጠናቀቁን አስመልክተው ዛሬ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ ፓትርያርኩ በመግለጫቸው የሰው ልጅ በስነ ፍጥረት ራሱን እየጠቀመ የፈጣሪውን ክብር በማድነቅና እያመሰገነ እንዲኖር ስልጣን ተሰጥቶታል ብለዋል፡፡ ሆኖም ኢትዮጵያውያን የታሪክና የተፈጥሮ ስጦታቸው በሆነው በአባይ ወንዝ ለረጅም ጊዜያት ሳይጠቀሙበት መቆታቸውን ተናግረዋል፡፡ ይሁን እንጂ ይህ የኢትዮጵያውያን ሃብት የሆነው ወንዝ ላይ የሚሰራው ግድብ ከዘጠኝ ዓመታት በፊት ግንባታው ተጀምሮ አሁን የመጀመሪያው ዙር የውሃ ሙሌት በመጠናቀቁ መደሰታቸውን ገልጸዋል፡፡ ቤተ-ክርስቲያን ለግድቡ ግንባታ አስተዋጽኦ ስታደርግ መቆየቷን የገለጹት ፓትርያርኩ፣ ይህን ድጋፍ ለወደፊትም አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጠዋል፡፡ የግድቡን ግንባታ እዚህ ደረጃ ላይ ያደረሱ አካላት የኢትዮጵያ ባለውለታ በመሆናቸው ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል፡፡ @ethiocheck

በበይነ መረብ የሚካሄድ ኑዛዜ ተቀባይነት አገኘ ኮሮናቫይረስ በርካታ ሥራዎች በበይነ መረብ እንዲከናወኑ ምክንያት ከሆነ ሰነባብቷል። ስብሰባና ትምህርት የሚካሄደው፣ ወዳጅ ዘመድ የሚጠያየቀውም እንደ ዙምና ፌስታይም ባሉ መተግበሪያዎች አማካይነት ነው። አሁን ደግሞ የዩናይትድ ኪንግደሞቹ እንግሊዝ እና ዌልስ በበይነ መረብ ለሚደረግ ኑዛዜ ሕጋዊ እውቅና ሰጥተዋል። ከበሽታው ራስን ለመከላከል አካላዊ ርቀትን መጠበቅ የግድ በመሆኑ ሰዎች ኑዛዜ እያካሄዱ ያሉት በበይነ መረብ ነው። ይህ የኑዛዜ ማስተላለፊያ መንገድ እስከ ጎርጎሮሳውያኑ 2022 ድረስ ተቀባይነት እንዳለው ተገልጿል። @ethiocheck

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹን እያስመረቀ ነው! አንጋፋው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በፊት ለፊት እና በኦንላይን ያስተማራቸውን ከ,5600 በላይ ተማሪዎችን ለመጀመሪያ ጊዜ #በvirtual እያስመረ
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹን እያስመረቀ ነው! አንጋፋው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በፊት ለፊት እና በኦንላይን ያስተማራቸውን ከ,5600 በላይ ተማሪዎችን ለመጀመሪያ ጊዜ #በvirtual እያስመረቀ ይገኛል። የምርቃት ስነ ስርዓቱ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን /etv/ በቀጥታ እየተላለፈ ነው። @ethiocheck

የፍርድ ቤት ውሎ! የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ተረኛ ችሎት የአቶ ጃዋር መሐመድና በ9 ግለሰቦች እንዲሁም የአቶ በቀለ ገርባና የአቶ እስክንድር ነጋ አራት የምርመራ መዝገቦችን
የፍርድ ቤት ውሎ! የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ተረኛ ችሎት የአቶ ጃዋር መሐመድና በ9 ግለሰቦች እንዲሁም የአቶ በቀለ ገርባና የአቶ እስክንድር ነጋ አራት የምርመራ መዝገቦችን ተመልክቷል፡፡ በዚህም በአቶ ጃዋር መዝገብ ፖሊስ የጠየቀውን 14 ቀን ሲፈቅድ በ9ኙ ተጠርጣሪዎች ላይ የ12 ቀን የምርመራ ጊዜ ፈቅዷል፡፡ ፍርድ ቤቱ በተጨማሪም በአቶ በቀለ ገርባ ላይ 11 ቀን፣ እንዲሁም በአቶ እስክንድር ነጋ ላይ 13 ቀን ተጨማሪ ምርመራ ጊዜ ፈቅዷል። @ethiocheck

#COVID19 የአሜሪካ ኩባንያ ያመረተው የኮቪድ- 19 ክትባት የመጨረሻ የሙከራ ደረጃ ላይ መድረሱን #BBC ዘገበ። የአሜሪካ የባዮቴክኖሎጂ ኩባንያ ሞደርና ፤ የኮቪድ-19 ክትባት በሰዎች ላይ ለመሞ
#COVID19 የአሜሪካ ኩባንያ ያመረተው የኮቪድ- 19 ክትባት የመጨረሻ የሙከራ ደረጃ ላይ መድረሱን #BBC ዘገበ። የአሜሪካ የባዮቴክኖሎጂ ኩባንያ ሞደርና ፤ የኮቪድ-19 ክትባት በሰዎች ላይ ለመሞከር ወደ ሚያስችለው የመጨረሻ ደረጃ የሙከራ ሂደት በሐምሌ ወር መጨረሻ ላይ እንደሚገባ አስታውቋል። ኩባንያው በሙከራው 30 ሺህ ሰዎችን ለማሳተፍ እንዳለመም ገልጿል። @ethiocheck

#MinistryOfPeace የሰላም ሚኒስቴር የኢትዮጵያ የቅድመ ማስጠንቀቂያ እና ፈጣን ምላሽ ስርዓት አካል የሆነው የቅድመ ማስጠንቀቂያ ፕሮጀክት በይፋ ወደ ስራ ሊገባ እንደሆነ አብስሯል። የሰላም ሚ
#MinistryOfPeace የሰላም ሚኒስቴር የኢትዮጵያ የቅድመ ማስጠንቀቂያ እና ፈጣን ምላሽ ስርዓት አካል የሆነው የቅድመ ማስጠንቀቂያ ፕሮጀክት በይፋ ወደ ስራ ሊገባ እንደሆነ አብስሯል። የሰላም ሚኒስትሯ ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል የቅድመ ማስጠንቀቂያው ስርዓት ማህበረሰቡን ከተለያዩ ተፈጥሮአዊም ሆነ ሰው ሰራሽ አደጋዎች በመጠበቅ ረገድ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል ብለዋል። ስርዓቱ የሙከራ ጊዜዉን በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናቶች ውስጥ አገባዶ ሙሉ በሙሉ ወደ ስራ ይገባል። @ethiocheck

አርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ህይወቱ አለፈ ዝነኛ የኦሮምኛ ሙዚቃ ዘፋኝ የሆነው አርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ዛሬ ሰኔ 22፤ 2012 ለጊዜው ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች በጥይት ተመትቶ ህይወቱ ማለፉን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ከታማኝ ምንጮቼ አረጋጫለው ሲል ዘግቧል። በርከት ያሉ ምንጮች የአርቲስቱ ህይወት ማለፉን ቢገልፁም እስካሁን ከፖሊስ ማረጋገጥ አልተቻለም። ሃጫሉ አመሻሹ ላይ ገላን አካባቢ በጥይት መመታቱን ያረጋገጡት በኦሮሚያ ክልል ያሉ አንድ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣን ናቸው ሲል ኢትዮጵያዊ ኢንሳይደረ ዘግቧል። @ethiocheck

#BreakingNews ኢራን በአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ላይ የእስር ማዘዣ አወጣች። ኢራን ከወራት በፊት በፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ የተገደለባትን የጦር መሪ ቃሲም ሱለማኒ ተገድሎ
#BreakingNews ኢራን በአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ላይ የእስር ማዘዣ አወጣች። ኢራን ከወራት በፊት በፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ የተገደለባትን የጦር መሪ ቃሲም ሱለማኒ ተገድሎብኛል ብላለች። በመሆኑን በዚህ የግድያ ወንጀል በቀጥታ እጁ አለበት ያለችውን የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ወደ ኢራን ተይዘው እንዲመጡላት ማዘዣ ማውጣቷን አልጀዚራ ዘግቧል። ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕን ዓለም አቀፉ የፖሊስ ተቋም ኢንተርፖል እንዲተባበራትም ጠይቃለች። @ethiocheck

በእንግሊዝ ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት የማይልኩ ወላጆች ይቀጣሉ ተባለ ***************************************** ************** በመጪው መስከረም ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት የማይልኩ ወላጆች የገንዘብ ቅጣት እንደሚጠብቃቸው የእንግሊዝ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። ''በጣም አስገዳጅ ሁኔታ ካልተከሰተ በቀር ወላጆች ላይ ቅጣት እንጥላለን’’ ብለዋል ሚኒስትሩ ጋቪን ዊሊያምሰን። ነገር ግን የትምህርት ቤቶች ዳይሬክተሮች ወላጆችን መቅጣት ትክክለኛው መንገድ አይደለም በማለት ተከራክረው ነበር። የትምህርት ቤቶቹ ኃላፊዎች እንደሚሉት ከሆን ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ ለማድረግ በመጀመሪያ በወላጆችና በትምህርት ቤቶች መካከል እምነት ሊፈጠር ይገባል። @ethiocheck

“ህዝቡን ብዥታ ውስጥ የሚከቱ መረጃዎችን በማጋራት የግልም ሆነ የቡድን ጥቅምን ለማጋበስ መፈለግ በሀገር ክህደት ሊያስጠይቅ የሚገባ ተግባር ነው” ---------------------------------
“ህዝቡን ብዥታ ውስጥ የሚከቱ መረጃዎችን በማጋራት የግልም ሆነ የቡድን ጥቅምን ለማጋበስ መፈለግ በሀገር ክህደት ሊያስጠይቅ የሚገባ ተግባር ነው” ------------------------------------------------------------------- የግብጽ መገናኛ ብዙሀን የሚያሰራጯቸውን ዘገባዎች ተጠቅሞ ህዝቡን ብዥታ ውስጥ የሚከቱ መረጃዎችን በማጋራት የግልም ሆነ የቡድን ጥቅምን ለማጋበስ መፈለግ በሀገር ክህደት ሊያስጠይቅ የሚገባ ተግባር ነው ሲሉ ከዋልታ ጋር ቆይታ ያደረጉ የትግራይ ክልል ተወላጆች ተናገሩ፡፡ የተለያየ የፖለቲካ አጀንዳ ያነገቡ አካላት ይህንን መሰል አጋጣሚዎችን ህዝቡን ብዥታ ውስጥ ለመክተት እንዳይጠቀሙበት መንግስት መረጃዎችን በፍጥነት ተደራሽ ሊያደርግ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡ ኢትዮጵያውን ከእለት ጉርሳቸው ቀንሰው ከመቀነታቸው ፈተው ባዋጡት ብር እየተገነባ የሚገኘው የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብ የብርሀን ጭላንጭልን እና ዘርፈ ብዙ ጥቅምን ፈልገው በጉጉት ለሚጠብቁት የሀገሩ ልጆች የተስፋ ፍሬን ሊያፈራ የተቃረበ ይመስላል፡፡ የግንባታ ሂደቱ 73 በመቶ የተጠናቀቀው ህዳሴ ግድቡ ከ15 ቀናት በኋላ የውሀ ሙሌት ስራው ሊጀመርም ቀነቀጠሮ ተይዞለታል፡፡ ታዲያ የህዳሴው ግድብ ሀ ብሎ ሲጀመር ጀምሮ አይኗ ደም የለበሰው ግብጽም በህዳሴው ግድብ ዙሪያ የተደረጉ በርካታ ድርድሮችን አቋርጣ ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት አቤቱታ እስከማቅረብ ብትደርስም ክሷ ያሰበችውን ውጤት ሳያመጣላት ቀርቶ በአፍሪካ ህብረቱ የወቅቱ ሊቀመንበር ሴሪል ራማፎሳ አጋፋሪነት በተሰናዳው የቪዲዮ ኮንፈረንስ ላይ ከኢትዮጵያ እና ሱዳን ጋር ለመደራደር ፊቷን እንድትመልስ አስገድዷታል፡፡ @ethiocheck

#GERD - የአፍሪካ ህብረት ዓባላት ቢሮ፣ ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ ለታላቁ የሕዳሴ ግድብ ከአፍሪካ የመነጨ መፍትሔን ማበጀት ላይ ያተኮረ ውጤታማ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ የገ
#GERD - የአፍሪካ ህብረት ዓባላት ቢሮ፣ ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ ለታላቁ የሕዳሴ ግድብ ከአፍሪካ የመነጨ መፍትሔን ማበጀት ላይ ያተኮረ ውጤታማ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ የገለጹት ማምሻውን ነበር፡፡ - ከዚያም በኀላ እኩለ ሌሊት አከባቢ የግብጽ ሚዲያዎችና አለማቀፍ ሚዲያዎች ኢትዮጵያ ከስምምነት በፊት የውሃ ሙሌት ላለመጀመር ተስማምታለች እንዲሁም የኢትዮጵያ ፣ የሱዳን እና ግብፅ መሪዎች በሁለት (2) ሳምንት ውስጥ ከስምምነት ላይ ሳይደርስ የውሃ ሙሌቱ እንዳይጀመር ተስማምተዋል የሚሉ ዘገባዎችን አስነብበውናል፡፡ - የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር የሆኑት ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ በትዊተር ገፃቸው የታላቁ የህዳሴ ግድብ ስምምነት ኢትዮጵያ ፣ ግብጽና ሱዳን ከሁለት እስከ ሶስት ባሉ ሳምንታት ለማጠናቀቅ መግባባት ላይ መድረሳቸውን እንዲሁ ከነጋ አስታውቀዋል። - ዛሬ የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት ባወጣው መግለጫ ትላንት በመሪዎች መካከል በአፍሪካ ህብረት የወቅቱ ፕሬዝዳንት በሆኑት የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎዛ አመቻችነት በተካሄደው ስብሰባ በግድቡ ሙሌት እና አስተዳደር ላይ የሚደረገው ድርድር በሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት እንዲጠናቀቅ መስማማታቸውን አስታውቋል፡፡ - መግለጫው አክሎም ኢትዮጵያ በመጪዎቹ ሁለት ሳምንታት የግድቡን ቀሪ የግንባታ ሥራዎች በማጠናቀቅ ሙሌት እንደምትጀምር አስታውቋል፡፡ ኢትዮጵያ በመጪው ሀምሌ ወር የግድቡን ሙሌት እንደምታካሂድ በተደጋጋሚ ስትገልጽ ነበር፡፡ - ሦስቱ ሀገራት በቅርቡ ባካሄዱት ድርድር በመሰረታዊ የቴክኒክ ጉዳዮች ላይ ከስምምነት መድረሳቸውንና ህግ ሆኖ ለመውጣት በሚያስችሉ የህግ ጉዳዮች ላይ ግን እንደሚቀራቸው መገለጹ ይታወሳል፡፡ @ethiocheck

"ኢትዮጵያ በመጪዎቹ ሁለት ሳምንታት የግድቡን ቀሪ የግንባታ ስራዎች በማጠናቀቅ ሙሌት ትጀምራለች፣ በነዚህ ሁለት ሳምንታትም ሀገራቱ ከስምምነት ለመድረስ ወስነዋል"--- የጠ/ሚር ፅ/ቤት
"ኢትዮጵያ በመጪዎቹ ሁለት ሳምንታት የግድቡን ቀሪ የግንባታ ስራዎች በማጠናቀቅ ሙሌት ትጀምራለች፣ በነዚህ ሁለት ሳምንታትም ሀገራቱ ከስምምነት ለመድረስ ወስነዋል"--- የጠ/ሚር ፅ/ቤት

የኢትዮጵያ፣ ግብፅ እና ሱዳን መሪዎች ትናንት በህዳሴ ግድብ ዙርያ ባደረጉት ውይይት የግድቡ ውሀ ሙሌት ስምምነት ላይ ሳይደረስ እንዳይጀመር ተስማምተዋል ብለው የሱዳን እና ግብፅ ባለስልጣናት ገልፀዋል
የኢትዮጵያ፣ ግብፅ እና ሱዳን መሪዎች ትናንት በህዳሴ ግድብ ዙርያ ባደረጉት ውይይት የግድቡ ውሀ ሙሌት ስምምነት ላይ ሳይደረስ እንዳይጀመር ተስማምተዋል ብለው የሱዳን እና ግብፅ ባለስልጣናት ገልፀዋል! በዚህ ዜና ዙርያ ኢትዮጵያ እስካሁን ያለችው ነገር የለም፣ ምናልባት ዛሬ የሚገለፅ ሊኖር ይችላል። እነዚህ አራት ነጥቦች ግን ወሳኝ ናቸው: - ኢትዮጵያ የውሀ ሙሌቱን ካለስምምነት ለማከናወን ማሰቧን ማስቀረቷ - ግብፅ ለበርካታ አመታት ስትሸሸው ወደነበረው የአፍሪካ ህብረት ወደሚመራው ውይይት መመለሷ - የሱዳኑ ጠ/ሚር አብደላ ሀምዶክ በዚህ ዙርያ ያሉት "ሀገራቱ በቴክኒካል ደረጃ የሚካሄደው ውይይት በሁለት ሳምንት ውስጥ እንዲጠናቀቅ ተስማምተዋል" ብለዋል። ይህ ውይይት በተባለለት ግዜ ከተጠናቀቀ የግድቡ ሙሌት ምናልባትም በመጪው ሳምንታት ሊጀምር ይችላል ማለት ነው። እዚህ ጋር ሌላው ዋና ጉዳይ "ሁለት ሳምንት" የሚለው ብቻ ሳይሆን በዚህ ውይይት ላይ "ምን ሰጥተን ምን እንቀበላለን?" የሚለው ነው። - በመጨረሻም፣ ግብፅ ለፀጥታው ምክር ቤት ያስገባችውን አቤቱታን ተከትሎ ሰኞ አባላቱ ምክክር ያደርጋሉ። ግብፅ ይህን አካሄድ እንድታቆም እና ወደ አፍሪካ ህብረት ሙሉ ለሙሉ እንድትመለስ ስምምነት ላይ ተደርሶ ይሁን፣ አይሁን አልታወቀም ግን ሌላው ዋና ነጥብ ነው። @ethiocheck

የኢትዮጵያ፣ ግብፅ እና ሱዳን መሪዎች በቪድዮ ተገናኝተው በህዳሴ ግድብ ዙርያ መክረዋል! "የአፍሪካ ህብረት ዓባላት ቢሮ ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ ለታላቁ የሕዳሴ ግድብ ከአፍሪካ የመነጨ መፍትሔን
የኢትዮጵያ፣ ግብፅ እና ሱዳን መሪዎች በቪድዮ ተገናኝተው በህዳሴ ግድብ ዙርያ መክረዋል! "የአፍሪካ ህብረት ዓባላት ቢሮ ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ ለታላቁ የሕዳሴ ግድብ ከአፍሪካ የመነጨ መፍትሔን ማበጀት ላይ ያተኮረ ውጤታማ ውይይት አድርገናል" ብለዋል ጠ/ሚር አብይ አህመድ። አክለውም "ይህንን አህጉራዊ ጠቀሜታ ያለው የከፍተኛ አመራሮች ስብሰባ ላስተባበሩት የአፍሪካ ኅብረት ሰብሳቢ፣ ፕሬዚደንት ሲሪል ራማፎሳ ምስጋናዬን አቀርባለሁ። ለኅብረቱ ሊቀ መንበር ሙሳ ፋኪም ምስጋናዬ ይድረስ" ያሉ ሲሆን የፓን አፍሪካዊነት መንፈስ ያለው አህጉራዊ ተቋማችን ለአፍሪካ ከፍተኛ ጠቀሜታ ያላቸውን ውይይቶች ለማካሄድ ትክክለኛው ሥፍራ ነው ብለዋል። "ታላቁ የሕዳሴ ግድብ ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት የላቀ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት እና የጋራ ብልጽግና የሚያገኙበትን ዕድል ይዟል።" @ethiocheck