en
Feedback
AIRDROP ROOM

AIRDROP ROOM

Open in Telegram
2 485
Subscribers
No data24 hours
-157 days
-5230 days
Posts Archive
ኤርትራን በተመለከተ የዓብይ አህመድ ማብራሪያ በአማርኛ ቋንቋ በአሁኑ ወቅት የኤርትራ መንግሥት ኢትዮጵያ ከሌሎች አገሮች ጋር ያላትን አንዳንድ ችግሮች ለመፍታት የተለየ ድርሻ እየተጫወተ ነው። የኤርት
ኤርትራን በተመለከተ የዓብይ አህመድ ማብራሪያ በአማርኛ ቋንቋ በአሁኑ ወቅት የኤርትራ መንግሥት ኢትዮጵያ ከሌሎች አገሮች ጋር ያላትን አንዳንድ ችግሮች ለመፍታት የተለየ ድርሻ እየተጫወተ ነው። የኤርትራ መንግሥት ፍላጎት ኢትዮጵያ ከሌሎች ጋር ሰላም ሆና ከኤርትራም ጋር ያለው የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ሥራ ከፍ ብሎ በአንድነት እንጠቀማለን የሚል እንጂ፣ ውጊያን የኤርትራ ሕዝብና መንግሥት አይፈልግም። የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥትም አይፈልግም። የፌዴራል መንግሥት በትግራይ የሆነ ዕርምጃ እወስዳለሁ ካለ ራሱ ያደርገዋል። ይህን ማድረግ ምን ችግር ኖሮት ነው ሌሎችን እባካችሁ ኑ በጋራ ሆነን እንዲህ እናድርግ የምንለው? እውነት ለመናገር በዚህ ወቅት የኤርትራ መንግሥት የሰላም ኃይል መሆኑ፣ ኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን ዓለም ያወቀው ጉዳይ ነው። የትኛውም ዓለም ብትሄድ የኤርትራ መንግሥት ለሰላምና ለልማት ነው የሚሠራው እምነት ነው ያለው።” ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዓብይ አህመድ @ethiocheck

ፕሬዚዳንት ዶናልት ትራምፕ የአሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ እንዲራዘም ጠየቁ ፕሬዚዳንት ትራምፕ ምርጫው እንዲራዘም የጠየቁት፥ በፖስታ አማካኝነት የሚደረግ ምርጫ ለማጭበርበር አመቺ በመሆኑ እና ተአማኒ የ
ፕሬዚዳንት ዶናልት ትራምፕ የአሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ እንዲራዘም ጠየቁ ፕሬዚዳንት ትራምፕ ምርጫው እንዲራዘም የጠየቁት፥ በፖስታ አማካኝነት የሚደረግ ምርጫ ለማጭበርበር አመቺ በመሆኑ እና ተአማኒ የሆነ ውጤት ለማግኘት አስቸጋሪ ስለሚሆን ነው ብለዋል። የአሜሪካ ግዛቶች በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት የ2020 ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ በፖስታ የታገዘ እንዲሆን ጠይቀው እንደነበረ አይዘነጋም። ስድስት የአሜሪካ ግዛቶች በፖስታ መልእክት የታገዘ ምርጫን ለማድረግ እቅድ ይዘው የነበረ ሲሆን፥ እቅድ የያዙ ግዛቶችም ኡታህ፣ ሀዋይ፣ ኮለራዶ፣ ኦሬገን እና ዋሽንግተን ናቸው። በዚህም ግዛቶቹ የፖስታ ድምጽ መስጫዎችን ለመራጮች የሚልኩ ሲሆን፥ መራጮቹ የሰጡት ድምጽም በምርጫው ቀን ተመልሶ የሚላክ ይሆናል ነው የተባለው። @ethiocheck

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ለ1 ሺህ 441ኛው የኢድ አል አድሀ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ያስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ ሙሉ መልእክት እንደሚከተለው ቀርቧል፦ ለዒድ አል-አድሐ በዓል እንኳን አደረሳችሁ ለመላው ሙስሊም ወገኖቼና ለተቀረው ኢትዮጵያዊ ሁሉ፣ እንኳን ለ1 ሺህ 441 ኛው ዓመተ ሒጅራ፣ ለታላቁ የዒድ አል-አድሐ / የዐረፋ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን ለማለት እወዳለሁ። ዒድ ሙባረክ! የዘንድሮው የዐረፋ በዓል በተለያዩ ምክንያቶች ለእኛ ለኢትዮጵያውያን ለየት ያለ ትርጉም አለው፡፡ ከዓመታት ግንባታና የዲፕሎማቲክ ትግል በኋላ፣ የመጀመሪያውን የሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት ባሳካንበት ጊዜ የሚከበር በመሆኑ በዓሉን በከፍተኛ ሐሴት ውስጥ ሆነን ነው የምንቀበለው፡፡ ሙስሊሙ ወገናችን ከዓረቡ ዓለም ጋር ባለው የሃይማኖት፣ የባህልና የቋንቋ ትሥሥር ምክንያት ከመካከለኛው ምሥራቅና ከዓረብ ሀገራት ጋር በተያያዘ ሀገራችን ኢትዮጵያ ለሚገጥሟት ልዩ ልዩ የዲፕሎማሲ ትግሎች ወሳኝ ሚናዎችን ሲጫወት ቆይቷል፡፡ የሕዳሴ ግድባችን እውን እንዲሆንም ገንዘብ ከማዋጣትና ጠቃሚ ሐሳቦችን ከማበርከት ባለፈ በዲፕሎማሲያዊ ተጋድሎው ሂደት ግንባር ቀደም በመሆን የሁላችንም የሆነችው ሀገራችንን ለማኩራት በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ሙስሊሞች መሥዋዕትነት መክፈላችሁን እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በክብር ያየዋል፡፡ ላበረከታችሁት አስተዋጽዖ በኢፌዴሪ መንግሥትና በመላው ኢትዮጵያዊ ስም ሳላመሰግን አላልፍም፡፡ ዒድ አል አድሓ፣ በዓረብኛ “የመሥዋዕት በዓል” ማለት ሲሆን፣ ነቢዩ ኢብራሂም ለጌታው የነበረውን ፍጹም እምነት፣ በቆራጥነት ያሳየበት ልዩ ቀን ነው። ፈጣሪ አላህ፣ (ሱብሀነሁ ወተአላ) ልጅህን መሥዋዕት አቅርብልኝ ብሎ በጠየቀው ጊዜ ኢብራሂም አንድዬ ልጁን፣ እስማኤልን ወደ መሠዊያው ወስዶታል። ፈጣሪም የኢብራሂምን ፍጹም እምነት ተመልክቶ፣ ሙክት እንደሰጠውና በልጁ ምትክ ሙክቱ ስለተሰዋ የሚከበር በዓል ነው። የገዛ ልጁን ለመሠዋት ዝግጁ ከመሆን የበለጠ ቆራጥነት የለምና፣ ዒድ አል-አድሐ “የመሥዋዕት በዓል” እየተባለ ይጠራል። ከልጅ በላይ የቀረበና የሚወደድ ነገር እንደሌለ የወለደ ሰው ሁሉ ያውቀዋል፡፡ እንደ ኢብራሂም ያሉ መልካምና ቆራጥ ሰዎች፣ ለእምነታቸው ሲሉ አንድዬ ልጃቸውን መሥዋዕት ለማድረግ ይዘጋጃሉ። መልካም ሰዎች እንደ ኢብራሂም ናቸው፡፡ ለመልካም ዓላማ ሲሉ እጅግ ውድ የሆነ ሀብታቸውን፣ ልጃቸውን ሲሰጡ ቅር አይላቸውም፡፡ በተቃራኒው ክፉዎች ለእኩይ ዓላማቸው ወንድማቸው ላይ በትር ያነሳሉ፡፡ እህታቸው ላይ፣ ልጃቸው ላይ፣ እናትና አባታቸው ላይ ሲጨክኑ ዐይናቸውን አያሹም፡፡ ከእኛም መካከል አንዳንዶች ለተራ ቁሳዊ ሀብቶች፣ ለትንንሽ የፖለቲካ ድሎችና ለሥልጣን እኩይ ተግባራትን የሚፈጽሙ አሉ፡፡ ለሆዳቸው ሲሉ ቤተሰባቸውን፣ ለግል ጥቅማቸው ሲሉ ሀገርና ወገናቸውን ለመሸጥ ሲዘጋጁ እንደማየት የሚያሳዝን ነገር የለም፡፡ እንዲህ የሚያደርጉ አካላት ከክፉ ሥራቸው እንደሚለሱ ሕዝበ ሙስሊሙ በጥበብ እንዲያስተምራቸው አደራ ለማለት እወዳለሁ፡፡ የተከበራሁ ሙስሊም ወንድምና እህቶቼ፣እንደሚታወቀው የዒድ አል-አድሐ በዓል፣ ከአምስቱ የእስልምና መሠረቶች መካከል አንዱ የሆነውና ማንኛውም ሙስሊም የገንዘብና የጉልበት ዐቅሙ እስከፈቀደ ድረስ በሕይወት ዘመኑ ቢያንስ አንዴ ሊያከናውነው የሚገባው፣ የሐጅ ሥርዓት የሚፈጸምበትም ቅዱስ በዓል ነው። ያም ሆኖ የዘንድሮው የዐረፋ በዓል የሚከበረው ዓለምን እየፈተናት ያለውን የኮሮና ወረርሽኝ በምንዋጋበት ወቅት ነው፡፡ በዚህም ምክንያት በዓሉን ከዚህ ቀደም ካየናቸው በዓሎች ለየት ባለ መልኩ እንድናከብረው የሚገፋፉ ብዙ ምክንያቶች አሉ፡፡ ለወትሮው በዐረፋ በዓል ሕዝበ ሙስሊሙ በጋራ ሆኖ ለማክበር ዘመድ ወደ ዘመዱ፣ ልጆች ወደ ቤተሰቦቻቸውና ወደ ሀገር ቤት መሄድ የተለመደ ነበር፡፡ ከዚህም ከፍ ሲል በሚሊዮን የሚቆጠሩ የዓለም ሙስሊሞች የዐረፋ በዓልን ለማክበር ወደ ቅዱሱ ሥፍራ ወደ ሳዑዲ ይጎርፋሉ። ጥቁሩ፣ ነጩ፣ አፍሪካዊው፣ እስያዊው፣ አውሮፓዊውና ሌላውም ከያቅጣቸው ተሰባስቦ ዒድ አል-አድሐን በጋራ ሲያከብረው ኖሯል፡፡ ዘንድሮ ግን ነገሮች እንደቀድሞው ሊሆኑ አልቻሉም፡፡ መሰባሰብን የማይፈቅድ፣ አካላዊ መቀራራብን የሚከለክል ወረርሽኝ በማጋጠሙ ምክንያት በዓሉን በጥንቃቄ እንድናከብረው ግድ ብሏል፡፡ ሁላችንም እንደምናውቀው በአሁኑ ወቅት በኮሮና ቫይረስ የሚያዙ፣ የሚታመሙና የሚሞቱ ወገኖቻችን ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሻቀበ ነው። ይህ ጉዳይ የሁላችንም ጉዳይ መሆን አለበት። የትምህርታችንና የጸሎታችን ጉዳይ መሆን አለበት። ወረርሽኙን መከላከልን እንደ አንድ ሃይማኖታዊ ግዴታ ልንወስደው ይገባል። ወረርሽኙ የፈጠራቸውን ክፍተቶች ለመድፈን ሁሉም የበኩሉን አስተዋጽኦ ማበርከት ይኖርበታል፡፡ አቅማቸው ደከም ያሉ ወገኖቻችንን እንድንደግፍ፤ ማዕዳችንን እንድናጋራ፤ በዚህ ፈታኝ ወቅት ለተቸገሩ ወገኖቻችንን አልኝታቸው መሆናችንን እንድናሳያቸው ስል ጥሪዬን አስተላልፋለሁ፡፡ ዒድ አል-አድሐ የመሥዕዋትና የመዳን በዓል እንደመሆኑ መጠን ወደ ሐጅ የሚሄደው ሰው ብቻ ሳይሆን የማይሄደውም ጭምር ‹‹ኡድሒያ›› የማረድ ግዴታ እንዳለበት የእምነቱ አስተምሮ ያዛል፡፡ በዚህ አስተምህሮ መሰረት ለኡድሒያ ከሚታረደው አንድ ሦስተኛውን ለድኾችና ለተቸገሩ ወገኖቻችን በማካፈል በተለይም ይሄንን አስቸጋሪ ወቅት በስኬት እንደምንሻገረው አልጠራጠርም፡፡ በሌሎች አጋጣሚዎች እንደገለጽኩት፣ በዚህ ወቅት ማከናወን ከሚገቡን ሐገራዊ ተግባራት መካከል ሌላው ከሕዳሴ ግድብ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ በዚህ ወቅት ቀሪ የሕዳሴ ግድባችን ሥራዎች ላይ እንድንረባረብና የአረንጓዴ አሻራችንን በስኬት እንድንወጣ ከሁላችንም ይጠበቃል፡፡ አረንጓዴ አሻራችንን ከአሁኑ ማሳረፍ ካልቻልን የምንገነባው የሕዳሴ ግድብን ጨምሮ ሌሎች የልማት ሥራዎቻችን ሁሉ እድሜ አይኖራቸውም። ኢትዮጵያ አረንጓዴ ሀገር መሆን አለባት። ድርቅን የምትቋቋም፣ ምንጮቿ የማይነጥፉ፣ አራዊቷና አዕዋፏ የማይሰደዱ ሀገር መሆን አለባት። ይህ እንዲሆን ሕዝበ ሙስሊሙ ወሳኙን ሚና እንዲጫወት አደራ እላለሁ። በቀሪ የሕዳሴ ግድብ ግንባታና የዲፖሎማሲ ሥራዎች ላይ ርብርብ በማድረግ ቀጣዩ የዒድ አል-አድሐ በዓል ሲከበር ግድባችን እጅግ ከፍ ወዳለ ምእራፍ ተሸጋግሮ እንደሚሆን ቅንጣት አልጠራጠርም፡፡ በድጋሚ ለመላው ሕዝበ ሙስሊም፣ እንኳን ለዒድ አል-አድሐ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ለማለት እወዳለሁ! አመሰግናለሁ!!! ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራ፣ ተከብራና በልጽጋ ለዘላለም ትኑር! ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ! @ethiocheck

በዘንድሮው የችግኝ ተከላ መርሐ-ግብር 4.1 ቢሊዮን ችግኞች ተተክለዋል ተባለ! በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ለመትከል ከተያዘው 5 ቢሊዮን ችግኞች ውስጥ እስካሁን 4.1 ቢሊዮን ችግኞች መተከላቸውን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።የግብርና ሚኒስትሩ አቶ ዑመር ሁሴን ዛሬ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ባቀረቡት ሪፖርት እስካሁን የተተከለው ችግኝ ከዕቅዱ ውስጥ 83 በመቶ መሆኑን ገልጸዋል።በዚህ መርሐ-ግብር የደቡብ ክልል እና የቤኒሻንጉል ክልል ከዕቅዳቸው በላይ ያሳኩ መሆኑን አቶ ዑመር ተናግረዋል። ምንጭ: ኢቲቪ @ethiocheck

አቶ ዳውድ ኢብሳ "ቁም እሥር ላይ ነኝ" አሉ! የኦሮሞ ነፃነት ግንባር /ኦነግ/ ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ በመንግሥት ፀጥታ ኃይል ከመኖሪያ ቤታቸው እንዳይወጡ ከተከለከሉ ከ10 ቀናት በላይ እንደሆናቸው ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል። ከኦነግ ደምብና ከእርሳቸው እውቅና ውጭ የሆነ ስብሰባም በጉለሌው ፅህፈት ቤታቸው መካሄዱን ገልፀዋል። ስብሰባውን የመሩት አቶ አራርሳ ቢቂላ ስብሰባው የአቶ ዳውድን ሊቀመንበርነት ለመቀማት አይደለም ብለዋል። አቶ ዳውድ ኢብሳ ለምን ቤት ውስጥ እንደታጎሩ ለመጠየቅ ወደ ፌዴራልና አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ተደጋጋሚ ሙከራ ብናደርግም አልተሳካም ብሏል የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ። #VoA @ethiocheck

የአቶ ጃዋር መሃመድ የፍርድ ቤት ውሎ! የፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት በአቶ ጃዋር መሐመድ ላይ ፖሊስ የጠየቀውን ተጨማሪ የ14 ቀን የምርመራ ጊዜ በማየት 12 ቀን ፈቅዶ ለነሐሴ 5 ቀን 2012 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱን ከኢብኮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል። ሁከት እና ብጥብጥ በተከሰተባቸው የኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የተሰማራው የምርመራ ቡድን በርካታ የሰው ሞት እና የንብረት ውድመት የተመለከተ መረጃ መላኩንም ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል። አቶ ጃዋር በበኩላቸው ተከሰተ የተባለው ወንጀል እሳቸውን እንደማይመለከትና ሚዲያዎች ችሎቱን እንዳይዘግቡ ፍርድ ቤቱን መጠየቃቸው የኢብኮ መረጃ ያሳያል። አቶ ጃዋር ያቆሟቸው 9 ጠበቆች የምርመራ ሥራው አዲስ አለመሆኑንና ፖሊስ የጠየቀው የጊዜ ቀጠሮ ውድቅ እንዲሆን ወይም ጥቂት ቀን እንዲሆንም ጠይቀዋል። ፍርድ ቤቱም ፖሊስ ቀደም ሲል በተሰጠው 13 ቀናት ውስጥ ምርመራውን በአግባቡ በማከናወኑ እና ቀሪ ሥራዎችን ለማጠናቀቅ የጠየቀውን ተጨማሪ የ14 ቀን የምርመራ ጊዜ አይቶ 12 ቀን በመፍቀድ ለነሐሴ 5 ቀን 2012 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። @ethiocheck

የህግ የበላይነት ማክበር፣ ማስከበር እና ፍትህን ማስፈን የህልውናችን መሰረት ነው ሲሉ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ህግ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ገለፁ። የህግ የበላይነት እና ፍትህ እንዲሰፍን ዘርፈ ብዙ ስራ እና
የህግ የበላይነት ማክበር፣ ማስከበር እና ፍትህን ማስፈን የህልውናችን መሰረት ነው ሲሉ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ህግ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ገለፁ። የህግ የበላይነት እና ፍትህ እንዲሰፍን ዘርፈ ብዙ ስራ እና ርብርብ ላይ እየተደረገ እንደሚገኝ በፌስቡክ ገፃቸው ላይ አስፍረዋል። በኢትዮጵያ ፍትህ እንዲሰፍን በሚደረገው ርብርብ ሁሉም ሰው በህግ ፊት እኩል እና ከህግ በታች መሆኑን ለማረጋገጥ በህግ የተጀመረው ስራ በህግ የሚጨረስ መሆኑን መረዳት ተገቢ ነው ብለዋል። የተለያዩ ሃላፊነት የጎደላቸው እና ከእውነት የራቁ እንቅስቃሴዎች፣ ንግግሮች፣ መግለጫዎች በራስ ወዳድነት፣ ለግላዊ ጥቅም፣ ለርካሽ ተወዳጅነት እና ለዝና የሚደረጉ ድርጊቶች ለብዙ ጥፋት እና ጉዳት እንደሚዳርጉ በአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ሞት ሳቢያ የተፈጠረው ጊዜያዊ ረብሻ ማሳያ ሆኗልም ነው ያሉት። ከአሁን በኋላም የህግ የበላይነትን የሚረጋገጠው እና ፍትህን ለማስፈን የሚተጋው እንደ አማራጭ ሳይሆን የሃገሪቱን እና የህዝቡን የህልውና ዋና መሰረት መሆኑን በመረዳት መሆኑን ጠቅላይ ዐቃቤ ህጓ ተናግረዋል ። @ethiocheck

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ከፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ጋር እየተወያዩ ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከተለያዩ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ከፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ጋር እየተወያዩ ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከተለያዩ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ጋር እየተወያዩ ነው። ውይይቱ በመንግሥት እና በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል በወቅታዊ የአገሪቱ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው። በቀጣይም አገራዊ ምርጫን በሚመለከት ከዚህ በፊት ከተደረው ምክክር የቀጠለ ውይይት እንደሚደረግም ተገልጿል። በዚህም እስከ ሰባት በሚደርሱ አጀንዳዎች ላይ ምክክር ለማድረግ ስምምነት ተደርሷል፣ በቅድሚያ ግን ውይይት የሚደረግባቸው አራት አጀንዳዎችም ተለይተዋል። በቅድሚያ አገራዊ መግባባት ላይ ውይይት ለማድረግ የተስማሙ ሲሆን፣ በዚህም ጉዳይ ላይ ገለጻ ለማድረግ እና ለማወያየት ከተለያዩ ፖለቲካ ፓርቲዎች ሰዎች ተመርጠዋል። @ethiocheck

የመአዛ መንግስቴ ዘ ሻዶው ኪንግ የተሰኘው መፅሀፍ በዝነኛው ዘ ቡከርስ ፕራይዝ የ2013 እጩዎች ዝርዝር ተካተተ! በየአመቱ የሚወጣውና ለሀምሳ አመታት ያክል በብሪታንያና በአየርላንድ በእንግሊዘኛ የታ
የመአዛ መንግስቴ ዘ ሻዶው ኪንግ የተሰኘው መፅሀፍ በዝነኛው ዘ ቡከርስ ፕራይዝ የ2013 እጩዎች ዝርዝር ተካተተ! በየአመቱ የሚወጣውና ለሀምሳ አመታት ያክል በብሪታንያና በአየርላንድ በእንግሊዘኛ የታተሙ የልበ ወለድ መፅሀፎችን የመሸለም የሚታወቀው 'The Bookers Prize' በእንግሊዝ ለደራስያን ከሚሰጡ ሽልማቶች አንዱ ሲሆን፣ በመጪው ጥቅምት አሸናፊውን ለማሳወቅ በዝግጅት ላይ የሚገኙት የሽልማቱ አዘጋጆች በትላንትናው እለት የመአዛ መንግስቴን 'The Shadow King' የተሰኘ ልብ ወለድ መፅሀፍ በዘንድሮው ዘ ቡከርስ ፕራይዝ እጩዎች ዝርዝር ውስጥ መካተቱን ይፋ አድርገዋል። ይህ በልብ ወለድ ደራስያን ዘንድ ታላቅ ክብር የሚሰጠው ሽልማት ከእጩዎቹ መካከል ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ መአዛ መንግስቴ በመካተቷ የተሰማውን ኩራት በእንግሊዝ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲም በትዊተር ገፁ በትላንትናው እለት ባሰፈረው መልእክት ገልጿል። በዘ ቡከርስ ፕራይዝ ፋውንዴሽን የሚዘጋጀው ሽልማት በዘርፉ ልምድን ባካበቱ ዳኞች በመታገዝ ሽልማቱን የመጨረሻ እጩዎቹን በመጪው መስከረም 5 2013 ዓ.ም የሚያሳውቅ ሲሆን የዘንድሮ የቡከርስ ፕራይዝ አሸናፊን ደግሞ በጥቅምት 17 2013 ዓ.ም ይፋ እንደሚያደርግ ከመካነድሩ መረዳት ይቻላል። መአዛ መንግስቴ በተወዳጅ የልብ ወለድ ድርሰቶቿ ካካበተችው ታላቅ ሙገሳ በተጨማሪ በተለያዩ መፅሀፍቶቿ የኢትዪጵያን ታሪክ በማካተት አገሯን በተለያዩ መድረኮች ማስጠራት በመቻሏ ከብዙ ኢትዮጵያውያንም ሆነ ከቀሪው አለም ሙገሳን አግኝታለች።ለዚህም እንደማሳያነት ከላይ የተጠቀሰው ዘ ሻዶው ኪንግ በተሰኘው መፅሀፍ ደራሲዋ መቼቱን በጣልያን ወረራ ወቅት በማድረግ ለአንባቢው ታሪካዊ ዳራውን በጠበቀ መልኩ ማቅረቧን መግለፅ ይቻላል። @ethiocheck

ኢትዮጵያ ግብጽ እና ሱዳን በህዳሴዉ ግድብ ዙሪያ በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት የፊታችን ሰኞ ሊሰበሰቡ ነው፡፡‼️ የሱዳኑ የሙሃና መስኖ ሚንስቴር እንዳለዉ ህብረቱ ከቀጣይ ሰኞ ጀምሮ ሶስቱን ሀገራት
ኢትዮጵያ ግብጽ እና ሱዳን በህዳሴዉ ግድብ ዙሪያ በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት የፊታችን ሰኞ ሊሰበሰቡ ነው፡፡‼️ የሱዳኑ የሙሃና መስኖ ሚንስቴር እንዳለዉ ህብረቱ ከቀጣይ ሰኞ ጀምሮ ሶስቱን ሀገራት ማለትም ኢትዮጵያ፣ግብጽና ሱዳን በህዳሴዉ ግድብ ዙሪያ ለሶስት ቀናት እንዲወያዩ ይደረጋል ማለታቸውን የፈረንሳዩ አጃንስ ፍራንስ ዘግቧል፡፡ ዉይይቱ በአፍሪካ ህብረት ስር የሚካሄድ ሆኖ የደቡብ አፍሪካዉ ፕሬዝዳንት ስሪል ራማፎሳ ይመሩታል ተብሏል፡፡ ይሁንና ዉይይቱ በምን ጉዳዮች ላይ ትኩረቱን እንደሚያደርግ ዘገባዉ ያለዉ ነገር የለም፡፡ ሕብረቱ የሶስቱ አገራት መሪዎች በተገኙበት ባካሄደው ስብሰባ ላይ ኢትዮጵያ የህዳሴው ግድብ የመጀመሪያ የዉሃ ሙሌቱን መጠናቀቁን ለተሰብሳቢዎቹ በመግለጽ ሰርፕራይዝ ማድረጓ የሚታወስ ነዉ፡፡ የግብጽ መገናኛ ብዙሃን ደግሞ የግድቡ ውሃ ሙሌት መጠናቀቁ የግብጽን የውሃ ጥቅም እንዳልጎዳው በመዘገብ ላይ ናቸው። ሶስቱ አገራት በግድቡ በርካታ ጉዳዮች የተግብቡ ቢሆንም በድርቅ ወቅት ሊለቀቅ በሚገባው የውሃ መጠን ላይ ግብጽ ያልተገባ ፍላጎት በማሳየቷ ኢትዮጵያ ውድቅ ማድረጓም ተገልጽል። @ethiocheck

የጠፋው ቅርስ በ50 ዓመቱ ተገኘ፡፡ በተለያዩ አጋጣሚዎች ቅርስ በእጃቸው ያለ ሰዎች ቅርሶችን በመመለስ የድርሻቸውን እንዲወጡም ጥሪ ቀርቧል፡፡ በደቡብ ጎንደር ዞን አንዳቤት ወረዳ ከደብረ ሰላም ወርቻሜ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በ1962 ዓ.ም ጠፍቶ የነበረው የስንክሳር መጽሐፍ ተገኝቷል፡፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ዋና ሼል አስኪያጅ መልአከ ፀሐይ ጸዳሉ ነጋሽ እንዳሉት ከጠፋ ከ50 ዓመታት በኋላ የተገኘው ስንክሳር ከመጋቢት እስከ ነሐሴ የሚነበበውን የመንፈቅ ምንባብ የያዘ ነው፡፡ ስንክሳሩ ከ20 ኪሎ ግራም በላይ ክብደት ያለው፡፡ ስንክሳር በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንም የቅዱሳንን እና የጻድቃንን ታሪክ የያዘ ትልቅ ዓመቱን መገልገያ ነው፡፡ በኢትዮጵያ አሉ ከሚባሉ የሚዳሰሱ ቅርሶች መካከልም ትልቅ ሀገራዊ ገጽታ እና ትልቅ ሃይማኖታዊ ግልጋሎት ያለው ነው፡፡ ቅርሱ ከጠፋ ጊዜ ጀምሮ የማፈላለግ ሼል ሲከናወን ቆይቶ ሐምሌ 4/2012 ዓ.ም በባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ደብረ-ገነት ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን በማዳበሪያ ተጠቅልሎ ጸሎት በሚያደርጉ እናቶች ተገኝቷል፡፡ ሕጋዊ ሂደቱን ተከትሎ ወደ ቦታው መመለሱንም ዋና ሼል አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡   መልአከ ፀሐይ ጸዳሉ እንዳሉት ዞኑ የበርካታ ታሪካዊ እና ሃይማኖታዊ ቅርሶች መገኛ ቢሆንም ተገቢ ጥበቃና እንክብካቤ ስለማይደረግላቸው ለጥፋት እየተዳረጉ ነው፡፡ ሀገረ ስብከቱም ከመንግሥት ጋር በመሆን በሰዎች እጅ የሚገኙ ቅርሶችን እያፈላለገ ነው፡፡ በዚህ ቅርሶች እየተገኙ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ በቅርቡም ሁለት ግለሰቦች ቅርስ ተገኝቶባቸው በሕግ ተጠያቂ ተደርገው በእስር ላይ መሆናቸውን አንስተዋል፡፡ ነገር ግን ቅርስ በሚዘርፉ እና በሚያጠፉት ላይ የሚወሰደው ርምጃ አስተማሪ አለመሆኑን አንስተዋል፡፡  ቅርሶችን ለመንከባከብ በርካታ ሥራዎች ቢሠሩም ቅርሶች እየተዘረፉ መሆኑን የዞኑ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ አስታውቋል፡፡ የሕዝቡ ተሳትፎ አናሳ መሆኑ፣ በአጥፊዎች ላይ የሚወሰደው ርምጃ ጠንካራ አለመሆኑ እና በርካታ ቅርሶች በሰዎች እጅ መገኘታቸው በምክንያትነት ተጠቅሰዋል፡፡ የመምሪያ ኃላፊ ኃላፊው ወይዘሮ ሰናይት አስራደው እንዳሉት መንግሥት በቅርሶች ላይ ቁጥጥርና ክትትል እንደሚያደርግ እና አዳዲስ ቅርሶችን እንደሚመዘግብ አስታውቋል፡፡ የተመዘገቡት በየዓመቱ ኦዲት ስለሚደረግባቸው የመጥፋት ዕድላቸው ዝቅተኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ማኅበረሰቡ ይሰረቅብናል በሚል በእጅ ያሉ ቅርሶችን ለማስመዝገብ ፈቃደኛ አለመሆን ግን ፈተና ሆኖ ቆይቷል፡፡ በሚፈለገው ደረጃ ባይሆንም ግንዛቤ በመፍጠር ብዙ ቅርሶች ከማኅበረሰቡ ተመልሰው ምዝገባ ተደርጎላቸዋል፡፡ ቀደም ብሎ የተዘረፉ ቅርሶችን የማፈላለግ ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም መምሪያ ኃላፊዋ አስታውቀዋል፡፡ የታወቁ ጥንታዊ ቅርሶች ባሉባቸው ቦታዎችም የደብር ሙዚዬም በማሠራት ተገቢው እንክብካቤ ለቅርሶች እንደሚደረጉ ተመላክቷል፡፡ ሥራው በመንግሥት ብቻ ውጤታማ ስለማይሆን ሕዝቡ ቅርሱን ጠንክሮ ሊጠብቅ እንደሚገባም ወይዘሮ ሰናይት መክረዋል፡፡ በተለያዩ አጋጣሚዎች በእጃቸው ያሉ ቅርሶችን ለመንግሥት እንዲያሳውቁም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ @ethiocheck

ፕሬዝደንት አብዱልፈታህ አል-ሲሲ በህዳሴ ግድብ ዙርያ የሀገራቸውን ህዝብ ለጦርነት ለማነሳሳት መሞከር ተገቢ እንዳልሆነ ጠቅሰዋል! በትናንትናው እለት የሩቢኪ የኢንደስትሪ ከተማን የመረቁት ፕሬዝደንቱ
ፕሬዝደንት አብዱልፈታህ አል-ሲሲ በህዳሴ ግድብ ዙርያ የሀገራቸውን ህዝብ ለጦርነት ለማነሳሳት መሞከር ተገቢ እንዳልሆነ ጠቅሰዋል! በትናንትናው እለት የሩቢኪ የኢንደስትሪ ከተማን የመረቁት ፕሬዝደንቱ ለሀገራቸው ሚድያዎች የተላለፈ በሚመስለው መልእክታቸው "ግብፅ ውስጥ ያለውን የህዝብ አስተያየት ከወታደራዊ እርምጃ ጋር ማያያዝ አያስፈልግም" ብለዋል። ፕሬዝደንቱ አክለውም "ሁሉም ተጠቃሚ በሚሆንበት ጉዳይ ዙርያ እየተወያየን ነው፣ ጉዳት ማንም ላይ እንዲደርስ አንፈልግም" ብለዋል። @ethiocheck

አንዳንድ ‘ሳኒታይዘሮች’ ለጤና እክል ያጋልጣሉ ተባለ የአሜሪካ የምግብና መድኃኒት ቁጥጥር ተቋም (ኤፍዲኤ) አንዳንድ እጅ ማጽጃዎች (ሳኒታይዘር) ለጤና እክል እንደሚያጋልጡ አሳሰበ። ከአልኮል የተሠሩ
አንዳንድ ‘ሳኒታይዘሮች’ ለጤና እክል ያጋልጣሉ ተባለ የአሜሪካ የምግብና መድኃኒት ቁጥጥር ተቋም (ኤፍዲኤ) አንዳንድ እጅ ማጽጃዎች (ሳኒታይዘር) ለጤና እክል እንደሚያጋልጡ አሳሰበ። ከአልኮል የተሠሩና በከፍተኛ ደረጃ ሜታኖል የተባለው ኬሚካል ያላቸው ሳኒታይዘሮች ጥቅም ላይ ሲውሉ ጥንቃቄ መወሰድ እንዳለበት ተቋሙ አስጠንቅቋል። እሳት በማስነሳት የሚታወቀው ሜታኖል ቆዳ ላይ ጉዳት ያስከትላል። ሰውነት ውስጥ ከገባ ደግሞ ሕይወት ሊቀጥፍም ይችላል። መሰል ጉዳት ያላቸው ሳኒታይዘሮች ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ ማስጠንቂያ ማውጣቱን ተቋሙ ገልጿል። ገበያ ላይ ያሉት ሳኒታይዘሮች ለሸማቾች እንዳይሸጡም እንቅስቃሴ ጀምሯል። ተቋሙ ውሳኔውን ያስተላለፈው፤ በርካታ ሰዎች የልብ ህመም እንደገጠማቸው፣ ማየት እንደተሳናቸው እንዲሁም የሞቱ ሰዎች እንዳሉም ሪፖርት ከተደረገ በኋላ ነው። @ethiocheck

#Update : በኖርዌይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለጠ/ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ ያላቸውን ድጋፍ ለመግለጽ ለኖቤል የሰላም ሽልማት ኮሚቴ ደብዳቤ አስገቡ በኖርዌይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያ
#Update : በኖርዌይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለጠ/ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ ያላቸውን ድጋፍ ለመግለጽ ለኖቤል የሰላም ሽልማት ኮሚቴ ደብዳቤ አስገቡ በኖርዌይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ያላቸውን ድጋፍ ለመግለጽ ለኖቤል የሰላም ሽልማት ኮሚቴ ደብዳቤ አስገቡ። መቀመጫቸውን ኖርዌይ ያደረጉት እና በተለያዩ ተቋማት ውስጥ በማገልገል ላይ የሚገኙት ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያኑ አሁናዊውን የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ሁኔታ አስመልክተው ነው ደብዳቤውን ያስገቡት። በደብዳቤያቸውም የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳን ድግያ ተከትሎ የተፈጸመውን ድርጊት በማውገዝ የመንግስትን የሰላም ጥረት ለማደናቀፍ የተደረገ ሴራ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያኑ ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የሃገሪቱን እድገት እና ብልጽግና ለማረጋገጥ ሌት ተቀን እየሰሩ ይገኛሉ በማለትም ለኮሚቴው በደብዳቤያቸው አስታውቀዋል። በዚህም ኮሚቴው የኢትዮጵያ መንግስት እያደረገ ያለውን ጥረት እንዲገነዘብ አሳስበዋል። በተጨማሪም ኮሚቴው ለጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ያበረከተው የሰላም ሽልማት የሚገባቸው መሆኑን ምሁራኑ ጠቅሰዋል። @ethiocheck

ፍትሕ እና ዋስትና እፈልጋለሁ - ኃይሌ ገብረሥላሴ በሻሸመኔና በባቱ ከተሞች ውስጥ በተፈጸመው ጥቃት በንብረት ላይ የደረሰው ውድመት ከፍተኛ መሆኑን የከተማዋ ነዋሪዎችና ባለንብረቶች እማኝነታቸውን ሰጥ
ፍትሕ እና ዋስትና እፈልጋለሁ - ኃይሌ ገብረሥላሴ በሻሸመኔና በባቱ ከተሞች ውስጥ በተፈጸመው ጥቃት በንብረት ላይ የደረሰው ውድመት ከፍተኛ መሆኑን የከተማዋ ነዋሪዎችና ባለንብረቶች እማኝነታቸውን ሰጥተዋል። በእነዚህ ከተሞች ከወደሙ ንብረቶች መካከል በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በዓለማችን የሩጫ ታሪክ ውስጥ ስማቸው ከሚጠቀሱ ጥቂት ብርቅዬ አትሌቶች መካከል አንዱ የሆነው የኃይሌ ገብረሥላሴ ሁለት ትልልቅ ሆቴሎች ይገኙበታል። ኃይሌ ገብረሥላሴ በከተሞቹ ውስጥ የአገር ውስጥም ሆነ የውጪ እንግዶችን ከሚያስተናግዱ ደረጃቸውን የጠበቁ ጥቂት ሆቴሎች መካከል ቀዳሚ በሆናቸው በሁለቱ ሆቴሎቹ የደረሰው ውድመት በገንዘብ ቢሰላ ከሁለት መቶ ሚሊዮን ብር ሊበለጥ እንደሚችል ግምቱን ገልጿል። ትክክለኛ ቁጥሩን አላወቅንም፤ እስከ 290 ሚሊዮን [ሊደርስ ይችላል]። እንዲሁ ከሁለት መቶ ሚሊዮን ብር በላይ ብለን ነው የያዝነው" የሚለው ኃይሌ ስሌቱ ሲሰራ የወደሙ ወይንም የጠፉ ዕቀዎችን ለመመልሰ ቢሞከር ዛሬ ገበያው ላይ ባላቸው ዋጋ መሰረት መሆኑን ይገልፃል። "አገሬ ነች፣ ኢትዮጵያ ነች፣ የትም አልሄድም። ሞትም ቢመጣ እዚሁ ነው የምጋፈጠው:: @ethiocheck

ታክሲዎች በሙሉ ወንበር እንዲጭኑ ጥያቄ ቀረበ‼️ በአዲስ አበባ ከተማ የሚታየውን የትራንስፖርት እጥረት ለመቅረፍ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ያወጣው ሕግ እንዲያሻሻል ጥያቄ ማቅረቡን የአዲስ አበባ ትራንስ
ታክሲዎች በሙሉ ወንበር እንዲጭኑ ጥያቄ ቀረበ‼️ በአዲስ አበባ ከተማ የሚታየውን የትራንስፖርት እጥረት ለመቅረፍ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ያወጣው ሕግ እንዲያሻሻል ጥያቄ ማቅረቡን የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ባለሥልጣን አስታውቋል። ይህም የሕዝብ የትራንስፖርት ሰጪ ተሽከርካሪዎች በሙሉ ጭነው ታሪፉ ወደነበረበት እንዲመለስ የሚጠይቅ መሆኑን አዲስማለዳ ዘግቧል፡፡ ኅብረተሰቡ ከቤት መውጣት እንዲቀንስ፣ አካላዊ ርቀቱን እንዲጠብቅ ለማድረግ እና በየቤቱ ሆኖ የመሥራት ሁኔታው እንዲጨምር ታስቦ የነበር ቢሆንም አሁን በመላ ከተማው የሚስተዋለው ወደ ቀድሞ እንቅስቃሴ የመመለሱ ነገር መሆኑን እና ውሳኔው ላይ ለውጥ ማድረግ እንደሚያስፈልግ የባለሥልጣን መሥርያ ቤቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ በድሉ ሌሊሳ ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል። ባለሥልጣን መሥርያ ቤቱ በሠራው ዳሰሳ እና በታዘበው መሠርት የዋና ዋና ትራንስፖርት ስምሪት ኬላዎች ላይ የሕዝብ ሰልፍ መብዛት፤ ሰልፉ ደግሞ እንደ ከዚህ ቀደሙ ለአጭር ጊዜ የሚቆይ ሳይሆን ዘለግ ላለ ጊዜ የሚቆይ መሆኑ መታየቱን አንስተው በዚህም ተደጋጋሚ ቅሬታ ከኅብረተሰቡ እንደሚመጣላቸው አውስተዋል። @ethiocheck

ትላንት ጠሚ አብይ ከፋና የትግርኛ ክፍል ጋዜጠኛ ጋር ባተደረገ ቃለመጠይቅ Via Wonde Birhanu kabew " ወልዲያ መንገድ ተዘግቶ ነበር አሁንም የትዕምት ላይ መዝጋት አለ ለሚለው ጥያቄ • "መጀመሪያ ደረጃ የትግራይ መንግስት የፌደራሉን መንግስት ሌባ ነው አናቀውም ይላል። ታዲያ ለምንድን ምትፈለገው ስትለው ለበጀትና ለኢኮኖሚ ብቻ ይልሀል። • ትዕምት የአገሪቱን በማውደም (ችግር በመፍጠር) በኩል የተዋጣላቸው ነበሩ። አሁንም የትዕምት ተቋማት ከኢኮኖሚው በተጨማሪ ፖለቲካም በጆንያ ቋጥረው የሚዞሩ ናቸው። ከፈለጉ ፖለቲካውን ትተው ንግዳቸውን ብቻ ይስሩ። እኛ የትግራይን ህዝብ የመጉዳት መብቱም ፍላጎቱም የለንም። ከምርጫ ጋር በተያያዘ ለተጠየቀው ጥያቄ • "የፌደራልን ስልጣን በየትኛውም ክልል ይሁን ሳንሸራርፍ የመተግበር ግዴታ አለብን። የክልሎችንም ስልጣን አንነካም።"(የምርጫ ጉዳይ ደግሞ የፌደራል መንግስት ስልጣን ብቻ ነው) • "ህውሀት ለምርጫ ከሚያወጣው ብዙ ሚሊዮኖች ውስጥ ከቻለ ሁለት ጉድጓዶችን ጭሮ ለአክሱምን የውሃ ችግር ቢቀርፍበት ካልሆነም አንድ ጥሩ ሆስፒታል ቢገነባ ለትግራይ ይጠቅማል። ምርጫውን አንድ አመት ብቻ ታግሶ ይወዳደር። • ሁሉንም ሀሳቦች አፍነህ ምርጫ አደርጋለሁ ማለት ህውሀትን መልሼ በግድ ካላመጣሁ የሚል ነው የሚሆነው። • ትግራይን የፌደራል መንግስት ይወጋል ተዘጋጅቷል የሚሉት እንኳን የእብዶች ወሬ ነው። ጦርነት ቢያስፈልገን ባለፉት ሁለት አመታት ብዙ ጦርነት የሚያስከፍቱን ነገሮች ሰርተዋል።" • የፌደራል መንግስት ውጊያ ሳይሆን የሚፈልገው ትግራይም ውስጥ ህግ ማስከበር ነው። ህግ ማስከበር ግዴታ ግን አለብን። ይሄ ጦርነት አይባልም በጦርነትም የሚደረግ ስርአት አይደለም" • ከኤርትራ ጋር ሆኖ መንግስት እንዴት ኑና አገሬን እንውጋት ልንል እንችላለን። • ቆይ እኛ የትግራይ መንግስት ጋር እርምጃ መውሰድ ከፈለገ ምን ከልክሎት ነው ኤርትራን ሚጠይቀው? ይሄ ሌላ የውጭ አካል አያስፈልገውምኮ። ትግራይ ውስጥ ህውሀት እንዲወድቅ ቡድኖችን ታደራጃላችሁ ለሚለው ጥያቄ "ይህ የህውሀት ባህሪ ሆኖ እንጂ የትግራይ ህዝብ የህውሀት ሀሳብ ብቻ ተሸካሚ አይደለም። ትግራይ ሰፊ ነው ብዙ ሀሳቦች አሉት። ሁሉም የተደራጁም ያልተደራጁም ሀሳባቸውን በነጻነት የመግለጽ መብት አላቸው። ይህንን ህውሀት ማክበር ግዴታ አለበት።" "የትግራይ ህዝብ እንደ ደጺ አይነቶቹን ቢያግዝ ሌሎቹ ጦር የሚጎስሙትን እረፉ ቢል ሰላም ይመጣል ብየ አስባለሁ" @ethiocheck

በትግራይ ክልል ምርጫ እንሳተፋለን ያሉ... በትግራይ ክልላዊ ምርጫ ላይ እንደሚሳተፉ እስካሁን ድረስ ካሳወቁ የፖለቲካ ድርጅቶች መካከል የክልሉ ገዢ ፓርቲ ህወሓት ፣ ሳልሳይ ወያኔ ትግራይ ፣ ባይቶና
በትግራይ ክልል ምርጫ እንሳተፋለን ያሉ... በትግራይ ክልላዊ ምርጫ ላይ እንደሚሳተፉ እስካሁን ድረስ ካሳወቁ የፖለቲካ ድርጅቶች መካከል የክልሉ ገዢ ፓርቲ ህወሓት ፣ ሳልሳይ ወያኔ ትግራይ ፣ ባይቶና ትግራይና ውድብ ናፅነት ትግራይ ይገኙበታል። ከዚህ በተቃራኒ ዓረና ትግራይ እና የትግራይ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ በክልሉ ሊካሄድ የታቀደው ምርጫ ላይ የተለያዩ ጥያቄዎችን በማንሳት በሂደቱ ላለመሳተፍ መወሰናቸውን የቢቢሲ መረጃ ያሳያል። @ethiocheck

ዓረና በትግራይ በሚደረገው ምርጫ አልሳተፍም አለ! ዓረና ትግራይ ለዴሞክራሲና ሉዓላዊነት (ዓረና) ሓምለ 17 ባወጣው መግለጫ ነፃ ፣ ፍትሓዊና ሕገ-መንግስታዊ ባልሆነ ምርጫ አልሳተፍም ሲል አስታውቋል
ዓረና በትግራይ በሚደረገው ምርጫ አልሳተፍም አለ! ዓረና ትግራይ ለዴሞክራሲና ሉዓላዊነት (ዓረና) ሓምለ 17 ባወጣው መግለጫ ነፃ ፣ ፍትሓዊና ሕገ-መንግስታዊ ባልሆነ ምርጫ አልሳተፍም ሲል አስታውቋል። ፓርቲዊው በዚህ ምርጫ ላለመሳተፍ የወሰንኩበት አንዱ ምክንያት ህወሓት ሕገ-መንግስቱን በግላጭ የሚፃረር የምርጫ አካሄድ በመምረጡ ነው ብሏል። በተጨማሪ ህወሓት አካሂደዋለሁ በሚለው ሕገ-ወጥ ምርጫ ከተቋቋመ 12 ዓመታትን ያስቆጠረውና በትግራይ ፖለቲካ ተፅዕኖ ያለውን ዓረናን አግልሎ ራሱ የመረጣቸው ፓርቲዎች አቅፎ ለመሄድ በመወሰኑ ነው ሲል ገልጿል። ዓረና ባወጣው መግለጫው የመፍትሄ ሃሳቦች ናቸው ያለውን ያቀረበ ሲሆን ከመፍትሄዎቹ የመጀመሪያው ነጥብ ህወሃት እየሄደበት ያለው የምርጫ እንቅስቃሴ ኢ-ሕገ መንግስታዊና ኢ-ሕጋዊ በመሆኑ ይህን ውሳኔውን በማጤን ሊቀለብሰው እንደሚገባና በዚህ ምትክም ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር በመሆን እና በተናጠል ከፌዴራሉ መንግስት ጋር የምር ድርድር እንዲያካሂድ የሚጠይቅ ነው። ፓርቲው 'ነፃ ፣ ፍትሓዊ እና ሕገ-መንግስታዊ ባልሆነ ምርጫ አልሳተፍም' በሚል ያወጣውን መግለጫ ሙሉ ሃሳብ በ : https://telegra.ph/TigrayElection-07-25 ገብታችሁ ማንበብ ትችላላችሁ። @ethiocheck

አቶ ዳውድ ኢብሳ ከኃላፊነታቸው ተነስተዋል ? የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ያለ ግንባሩ ሊቀመንበር ያካሄደው ስብሰባ ዛሬ መጠናቀቁን አስታውቋል። ስብሰባው ከሳምንት በፊት በድርጅቱ ማዕከላዊ ኮሚቴ
አቶ ዳውድ ኢብሳ ከኃላፊነታቸው ተነስተዋል ? የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ያለ ግንባሩ ሊቀመንበር ያካሄደው ስብሰባ ዛሬ መጠናቀቁን አስታውቋል። ስብሰባው ከሳምንት በፊት በድርጅቱ ማዕከላዊ ኮሚቴ የአባላቱ መታሰርና የግንባሩ የወደ ፊት ስራዎች ላይ ለመምከር የተጠራ መሆኑን የግንባሩ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ቀጄላ መርዳሳ ለጀርመን ድምፅ ሬድዮ ተናግረዋል። አቶ ቀጀላ የኦነግ ሊ/መንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ ከ10 ቀናት አንስቶ በመንግስት የፀጥታ አካላት ሲጠበቁ ስለነበር አስቀድሞም እንደማይሳተፉ የተገመተ በመሆኑ ስብሰባው በምክትል ሊቀመንበሩ መካሄዱን ገልጸዋል። ስብሰባው የተካሄደው ሊቀመንበሩን ከኃላፊነታቸው ለማንሳት ነው በሚል በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨውን መረጃ 'ከእውነት የራቀ' ሲሉ አስተባብለዋል። አቶ ቀጄላ አሁን የአመራር ለውጥ ለማድረግ ፓርቲው ምንም እቅድ እንደሌለውም ገልጸዋል። አቶ ዳውድ ያሉበትን ሁኔታ ማየት አልቻልንም ያሉት የግንባሩ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ስልካቸውም ከባለፈው አርብ ጀምሮ መዘጋቱን ለጀርመን ድምፅ ሬድዮ ጣቢያ አረጋግጠዋል። @ethiocheck