en
Feedback
AIRDROP ROOM

AIRDROP ROOM

Open in Telegram
2 485
Subscribers
No data24 hours
-157 days
-5230 days
Posts Archive
በአዲስ አበባ በተደጋጋሚ ማስክ ሳያደርጉ የሚንቀሳቀሱ ሰዎችን በመለየት ፍርድ ቤት ማቅረብ ሊጀምር መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። ኮሚሽኑ ህብረተሰቡ ለኮቪድ 19 የሚያደርገው ጥንቃቄ ላይ መዘናጋት በመታየቱ ጠንከር ያለ ቁጥጥር ጀምሪያለሁ ብሏል፡፡ የኮሮና ቫይረስ መከላከያ ተብለው የተቀመጡትን በተለይ ማስክ አድረገው የማይንቀሳቀሱ ሰዎችን በመመዝገብ ደጋጋሚ የሆኑትን በመከታተል በአስቸኳይ አዋጁ የተቀመጠውን ቅጣት እንደሚጣልባቸውም ነው ዋና ኢንስፔክተሩ የተናገሩት፡፡ ከዚህ ቀደም ማስክ ሳያደርጉ የሚንቃቀሱ ሰዎችን ወደ ፖሊስ ጣቢያ ተወስደው እንዲታሰሩ ይደረግ የነበረ ቢሆንም አሁን ባለው ሁኔታ ሰዎችን ማሰር ስለማይቻል የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች እየተሰሩ አዋጁን በተደጋጋሚ በሚጥሱት ላይ ግን እርምጃ ለመወስድ አሰራሩ መዘርጋቱን ተናግረዋል፡፡ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የተደነገጉ የመብት እገዳዎችን፣ እርምጃዎችን፣ የተሰጠ መመሪያ ወይም ትዕዛዝን ሆን ብሎ የጣሰ ማንኛውም ሰው እስከ ሦስት ዓመት በሚደርስ ቀላል እስራት ወይም ከአንድ ሺህ ብር እስከ ሁለት መቶ ሺህ ብር የሚደርስ የገንዘብ መቀጮ ሊቀጣ እንደሚችል በአዋጁ መቀመጡ አይዘነጋም። @ethiocheck

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ (OMN) የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋዜጠኛ መለሰ ድሪብሳ እና ሌሎች 2 ሰራተኞች በሶስት ሺህ ብር ዋስትና ከእስር እንዲፈቱ ትዕዛዝ መስጠቱን ጠበቃቸው አቶ ከዲር ቡሎ ለ"ኢትዮጵያ ኢንሳይደር" አስታወቁ። በተመሳሳይ የጊዜ ቀጠሮ መዝገብ የተካተተው ኬንያዊው ጋዜጠኛ ያሲን ጂማ (በፖስፖርት ስሙ ኮሊንስ ኦሴሞ) እና በ“አቶ ጃዋር መሐመድ ቤት የሚኖሩ ናቸው” የተባሉት አቶ ሀሰን ጅማም በ3 ሺህ ብር ዋስትና እንዲፈቱ ፍርድ ቤቱ ማዘዙን ጠበቃው ተናግረዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) @ethiocheck

በ ቤሩት በተከሰተው ፍንዳታ ክፉኛ አዝኛለሁ። ጸሎቴ እና ሀሳቤ ከሊባኖስ ነዋሪዎች ጋር ነው። በሊባኖስ የምትኖሩ ኢትዮጵያውያን ከቆንስላችን ጋር ግንኙነት እንድትፈጥሩ በእጅጉ አበረታታለሁ። እንደዚህ
በ ቤሩት በተከሰተው ፍንዳታ ክፉኛ አዝኛለሁ። ጸሎቴ እና ሀሳቤ ከሊባኖስ ነዋሪዎች ጋር ነው። በሊባኖስ የምትኖሩ ኢትዮጵያውያን ከቆንስላችን ጋር ግንኙነት እንድትፈጥሩ በእጅጉ አበረታታለሁ። እንደዚህ ባለው አስከፊ ጊዜ መተጋገዝ አስፈላጊ ነው። I am Deeply saddened by the tragic explosion in Beirut. My thoughts and prayers with the people of Lebanon. I encourage Ethiopians living in Beirut to get in touch with the Consulate as you help one another amidst such an ordeal. @ethiocheck

በሊባኖስ ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን በሙሉ! (የኢትዮጵያ ቆንስላ ጄ/ፅ/ቤት ቤይሩት - ሊባኖስ) በቤይሩት ወደብ ዛሬ የተከሰተው ፍንዳታ ጋር ተያይዞ እስከ አሁን ወደ 10 የሚጠጉ ሰዎች መሞታቸው የተዘገ
በሊባኖስ ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን በሙሉ! (የኢትዮጵያ ቆንስላ ጄ/ፅ/ቤት ቤይሩት - ሊባኖስ) በቤይሩት ወደብ ዛሬ የተከሰተው ፍንዳታ ጋር ተያይዞ እስከ አሁን ወደ 10 የሚጠጉ ሰዎች መሞታቸው የተዘገበ ሲሆን ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ሰዎች ደግሞ እንደቆሰሉ ሪፖርት እየተደረገ ይገኛል፡፡ ፍንዳታው በተከሰተበት አካባቢ መንገዶች እና ህንጻዎች የፈራረሱ ሲሆን ከፍንዳታው እስከ በ10 ኪሎሜትር ርቀት ደግሞ ብዙ ህንጻዎች መስኮቶች ተሰባብረዋል፡፡ በመሆኑም ሁኔታዎች እስኪረጋጉ ዜጎች በተቻለ መጠን በቤታችሁ እንድትቆዩ ይመከራል ፤ ከቤት መውጣት የግድ ከሆነም ከቤት ከመውጣታችሁ በፊት መረጃዎችን እንድታጣሩና ጥንቃቄ እንድታደርጉ፤ እንዲሁም በሚከተሉት መልኩ ራሳችሁን እንድትጠብቁ ቆንስላ ጽ/ቤቱ ያሳስባል ፡- 1. ፍንዳታው ከተከሰተበት አካባቢ ራሳችሁን እንድትጠብቁና እንድትርቁ፣ 2. የአገሪቱን የዜና አውታሮች እንድትከታተሉ፣ መረጃዎችን እንድትለዋወጡ፤ 3. ከሊባኖስ መንግስት የሚሰጡ መግለጫዎችን እንድትከታተሉና እንድትተገብሩ፤ 4. በተቻለ መጠን ከመኖሪያ ቤታችሁ አካባቢ እንድትቆዩ ወይም ብዙ እንዳትርቁ፤ 5. ከቤት ስትወጡ የሞባይል ስልኮቻችሁን ቻርጅ እንድታደርጉ ይመክራል፤ ከዚህ ጋር ለተያያዙ ለድንገተኛ እና አስቸኳይ ጉዳዮች ብቻ በስልክ ቁጥሮች 71463074 ወይም 70696193 ወይም 81952182 ይደውሉ፡፡ @ethiocheck

ኢ/ር ታከለ ኡማ የእውቅና ሽልማት ተበረከተላቸው! የአዲስአበባ ከተማ ምክር ቤት ኢ/ር ታከለ ኡማ ከመሀል ከተማ ነዋሪ ጀምሮ አዋሳኝ ቦታ ላይ የሚገኙ አርሶአደሮች ድረስ የባለቤትነት ስሜት በመፍጠር
ኢ/ር ታከለ ኡማ የእውቅና ሽልማት ተበረከተላቸው! የአዲስአበባ ከተማ ምክር ቤት ኢ/ር ታከለ ኡማ ከመሀል ከተማ ነዋሪ ጀምሮ አዋሳኝ ቦታ ላይ የሚገኙ አርሶአደሮች ድረስ የባለቤትነት ስሜት በመፍጠር የከተማዋ እድገት ሁሉንም ያካተተ እንዲሆን በማድረግ በኩል ባለፋት ሁለት ዓመታት ላደረጉት ስኬታማ ስራ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የእውቅና ሽልማት አበርክቶላቸዋል። አስታዋሽ አጥተው ለዘመናት የተዘነጉ የማህበረሰብ ክፍሎችን ማዕከል ያደረጉ ስራዎችን በመስራት፣ የከተማዋን ታሪካዊና የቱሪዝም መስህብነት የሚያጎሉ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ሚና ያላቸው ታላላቅ ፕሮጀክችን ማስጀመራቸው፣ በከተማዋ ለሚገኙ ተማሪዎች ምግብ፣ የትምህርት ቁሳቁስ እና ዩኒፎርም እንዲቀርብ አመራር መስጠታቸው ለሽልማቱ በምክንያትነት ተጠቅሷል። @ @ethiocheck

እናቶች በኮሮና ቫይረስ ቢያዙም ልጆቻቸውን ጡት ማጥባት አለባቸው-የዓለም የጤና ድርጅት አዲስ የተወለዱ ሕፃናትን ወይም ልጆችን ጡት ማጥባት የሚሰጠው ጥቅም የኮቪድ 19 በሽታ ከሚያመጣው ስጋት እጅግ የላቀ በመሆኑ እናቶች በኮሮና ቫይረስ ቢያዙም ልጆቻቸውን ጡት ማጥባት አለባቸው ሲል ዓለም አቀፉ የጤና ድርጅት ገልጿል። የዓለም አቀፉ የጤና ድርጅት ኃላፊ ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም ÷ምንም እንኳን እናቶች በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ቢያዙም ልጆቻቸውን ጡት ማጥባታቸው ለህጻናቱ የሚሰጠው ጥቅም በሽታው ከሚያስከትለው ጉዳት ከፍ ያለ መሆኑን ተናግረዋል። ሃላፊው ይህንን የተናገሩት በዓለም አቀፍ ደረጃ የጡት ማጥባት ግንዛቤ ማስጨበጫ ሳምንት በተከበረበት ወቅት ሲሆን ÷ በኮቪድ- 19 በሽታ የተጠረጠሩ ወይም መያዛቸው የተረጋገጠ እናቶች እንደሌሎች እናቶች ሁሉ ህጻናት ልጆቻቸውን ጡት ማጥባት እንዲቀጥሉ መበረታታት አለባቸውም ብለዋል። አዲስ ለተወለዱ ሕፃናት እና ልጆች ጡት ማጥባት የሚሰጠው ጥቅም በኮቪድ-19 ኢንፌክሽኖች ከሚመጣው ስጋት እጅግ የላቀ ነውም ነው ያሉት። ምንጭ፡-ሮይተርስ/ኤፍ.ቢ.ሲ @ethiocheck

በጀርመን በኮሮና ምክንያት ት/ቤት ከተዘጋ በኋላ የመጀመርያዎቹ ተማሪዎች ትናንት ወደ መማርያ ክፍላቸው ገብተዋል፡፡ በጀርመን ት/ቤቶች መከፈት የጀመሩ ሲሆን በሰሜን ጀርመን ግዛት የሚገኙ ተማሪዎችም ከክረምት እረፍት በኋላ ወደ ሙሉ ሰአት ትምህርት ገበታቸው ሲመለሱ በሀገሪቱ የመጀመርያዎቹ ሆነዋል፡፡ የጀርመን ትምህርት ሚኒስትር አንጃ ካረሊሼክ በትምህርት ቅጥር ግቢ ውስጥ የፊት መሸፈኛ ማስክ ማድረግ አስገዳጅ እንዲሆን ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን በትምህርት ቤቶች ውስጥ መሟላት ስላለባቸው ቅድመ ሁኔታዎች የመጨረሻው ውሳኔ የሚሆነው ግን የክልል መንግስቱ ነው ብለዋል ፡፡ ትምህርት ቤቶች የተወሰኑ ክፍሎችን ሲሰጡ የነበረ ቢሆንም፣ ጥቂቶች ደግሞ በከፊል የተወሰኑ ሰአቶች ለማስተማር ሲሞክሩ የነበረ ቢሆንም በመደበኝነት ሙሉ በሙሉ ሲጀመር ግን ትናንት የመጀመርያው ነው፡፡ አስራ ስድስቱም የጀርመን ክልሎች ሙሉ ሰአት ትምህርት ለመጀመር ተስማምተው ነበር፡፡ በሀምቡርግ ከነገ በስትያ ትምህርት የሚጀመር ሲሆን በበርሊን ደግሞ በሚቀጥለው ሳምንት ይጀመራል ተብሏል፡፡ ላይፕዚሽ ዩኒቨርሲቲ ትምህርት ቤቶች የኮሮና ወረርሽኝ ምንጭ አይሆኑም ሲል ባጠናው መሰረት ነው ጀርመን ት/ቤቶቿን ሙሉ ለሙሉ ለመክፈት የወሰነችው፡፡ በ 2 ሺህ 6 መቶ በሳክሶኒ በሚገኙ ተማሪዎችና መምህራን ላይ በግንቦትና በሰኔ የተደረገው ምርመራ የሚያሳየውም በማንም ላይ ቫይረሱ አለመኖሩን ነው፡፡ በጀርመን የኮሮና ተጠቂዎች 211 ሺህ መድረሳቸውን ቢቢሲ ዘግቧል። @ethiocheck

ሥራ አጥ ወጣቶች ባለ ሦስት እግር ተሽከርካሪዎችን በብድር የሚያገኙበት ዕድል እንዳመቻቹ ኩባንያዎች አስታወቁ በተለምዶ ባጃጅ እየተባሉ የሚጠሩትን ባለሦስት እግር ተሽከርካሪዎችን ለሥራ አጥ ወጣቶች በ
ሥራ አጥ ወጣቶች ባለ ሦስት እግር ተሽከርካሪዎችን በብድር የሚያገኙበት ዕድል እንዳመቻቹ ኩባንያዎች አስታወቁ በተለምዶ ባጃጅ እየተባሉ የሚጠሩትን ባለሦስት እግር ተሽከርካሪዎችን ለሥራ አጥ ወጣቶች በብድር ለማቅረብ መዘጋጀታቸውን ቫዮ አውቶሞቲቭ ማኑፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበርና ቡና ኢንተርናሽናል ባንክ አስታወቁ፡፡ ሁለቱ ተቋማት ሐምሌ 22 ቀን 2012 ዓ.ም. በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት የብድር አገልግሎት ለማቅረብ ቡና ባንክ በመስማማቱ፣ በአገር ውስጥ ተሽከርካሪዎችን የሚገጣጥመው ቫዮ አውቶሞቢል ባለሦስት እግር ተሸከርካሪዎችን ለሥራ አጥ ወጣቶች ለማቅረብ ተስማምተዋል፡፡ በሁለቱ ኩባንያዎች ስምምነት መሠረት 75,000 ብር ቅድመ ክፍያው በብድር ለተሽከርካሪ አምራቹ ከተፈጸመ በኋላ፣ ቀሪው በ24 ወራት ውስጥ ይከፈላል ያሉት የቫዮ አውቶሞቢል የንግድና ግብይት ኃላፊ ወ/ሪት ሊዲያ ኪዳኔ ናቸው፡፡ ወ/ሪት ሊዲያ እንዳሉት ለባ ለሦስት እግር ተሽከርካሪው የሚፈጸመው አጠቃላይ ክፍያ 175,000 ብር ሲሆን፣ በየወሩ 4,956 ብር እየከፈሉ የተሽከርካሪ ባለቤት መሆን እንዲችሉ ለወጣቶች ዕድሉ ተመቻችቶላቸዋል ብለዋል፡፡ቫዮ አውቶሞቲቭ አዲስ አበባና ዙሪያዋን ጨምሮ፣ በጎንደር፣ በባህር ዳር፣ በድሬዳዋ፣ በጂማ፣ በአምቦና በሌሎችም ከተሞች በሚገኙ ወኪሎቹና በቡና ባንክ ቅርንጫፎች አማካይነት በተመቻቸው የብድር አገልግሎት መሠረት ወጣቶች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ሥራ አስኪያጇ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ #ሪፖርተር @ethiocheck

"በትግራይ ያለውን የወጣቶች እንቅስቃሴ ህዝቡ የእኔ ነው ብሎ መደገፍ ይኖርበታል” ዶክተር አብርሃም በላይ፣የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ************************ (ኢፕድ) አዲስ አበባ ፦ በትግራይ እያታየ ያለው የወጣቶች እንቅስቃሴ ህዝባዊ ዓላማ እስከአለው ድረስ ህዝቡ የእኔ ነው ብሎ መደገፍና ሥርዓት ይዘው እንዲንቀሳቀሱ ማድረግ ይኖርበታል ሲሉ የትግራይ ብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር እና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶክተር አብርሃም በላይ አስታወቁ። የህውሀት ጥገኛ ቡድን እንቅስቃሴ የኢትዮጵያን ህዝብ ፍላጎት በተለይደግሞ የትግራይን ህዝብ የማይመጥን እንደሆነም አመለከቱ። ህዝቡ የወጣቶቹን እንቅስቃሴ ሊቀበልና ሊደግፍ እንደሚገባ ዶክተር አብርሃም ጠቅሰው፣ በትግራይ ያለው አፋኝ መንግስት ወይም ፓርቲ ወጣቶችን እንዳያሰቃያቸው ከለላ መሆን ያለበትም ህዝቡ መሆኑን አስገንዝበዋል። ለህዝብ ጥያቄ የተንቀሳቀሰ ወጣት ሲገደል እንዲሁም ለምን ተናገርክ ተብሎ ሲጨፈጨፍና ሲታሰር ካየ፤ ለህዝብ ብሎ እየተጨፈጨፈ ላለው ለእዚህ ወጣት ህዝቡ ራሱ ከለላ መሆን መጀመር መቻል አለበት ብለዋል። በዚህ ረገድ የወጣቶች እንቅስቃሴ ብቻ ሳይሆን የፓርቲ እንቅስቃሴም የሚያደርጉ አካላት አባሎቻቸው እየታሰሩ እና እየተሰቃዩ መሆናቸውን በየጊዜው እየገለጹ መሆናቸው ዶክተር አብርሃም ጠቅሰው፣ ያልሆኑ ሃሳቦችና ንግግሮች በእነሱ ተቃኝተው ወጣቱ እንዲገለጹላቸውና እንዲናገራቸው ይደረጋሉ ዕምቢ ካለ ደግሞ ይታሰራል፤ ይደበደባል፤ ይሰቃያል። ትግራይ ውስጥ ያለው ይሄ ነው። ሰዎች እስከ መገደል የደረሱበት ሁኔታም እየታየ ነው ሲሉ ተናግረዋል። ዶክተር አብርሃም ይሄንን በማድረግም የፓርቲ እና የወጣቶች እንቅስቃሴን የሚከለክልና የሚያፍን፤ ዴሞክራሲያዊ ሁኔታ እንዳይፈጠር የሚያደርግ፣ ብዙ ሃሳብና እውቀት በሞላበት ክልል ውስጥ የሃሳብ ፍጭት እንዳይኖርና ሃሳብ እንዳይንሸራሸር የሚያደርግን አካል ተው ብሎ ማስተው፤ ካልተወም በግፊት እንዲተው ማስገደድ ያስፈልጋል ብዬ አምናለሁ፤ ይህ ደግሞ የህዝቡ ሃላፊነት ጭምር ነው ብለዋል። አንድ በትክክል መገንዘብ ያለብን ነገር ህውሃት ፓርቲ መሆኑን ነው ያሉት ዶክተር አብርሃም፣ ፓርቲ ደግሞ ጠቅላላውን ህዝብ እንደማይወክል ተናግረዋል። ‹‹አለመታደል ሆኖ ምንጩ ከትግራይ ሆኖ በአገራችንም እንደ አጠቃላይ፤ ከአገራችንም በተለየ ደግሞ በትግራይ ውስጥ ከፍተኛ የክፋት እንቅስቃሴዎች እና የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች፤ ሰው የማሰር፣ የመግረፍ፣ የማሰቃየት፣ ብሎም በኔትዎርክ የጥቅመኝነት እንቅስቃሴ እና ተደራጅቶ አገርን የመረበሽ እንቅስቃሴ እያደረገ ያለ ቡድን አለ ሲሉ ያብራራሉ። በአጠቃላይ ህወሓት በሚል ባይገለጽም በጣም ጥሩ መሆኑን ተናግረው፣ ህወሓት ውስጥ ሆነው የትግራይን ህዝብ ፍላጎት፣ በትግራይ ውስጥ ዴሞክራሲ እንዲኖር፤ የሚፈለገው ልማት እንዲመጣ፣ ሰላም እንዲሰፍን የሚሰሩ፣ በሌብነት የማይንቀሳቀሱ፣ በኔትወርክ ጥቅም ያልተሳሰሩ፣ ለህዝብ ብለው የሚኖሩ ብዙ አባላት እንዳሉም ዶክተር አብርሃም አብራርተዋል። እንደ ዶክተር አብርሃም ገለጻ፤ የህወሓት ከላይ ያለው ቡድን የሚናገረውና የሚያደርገው ይለያያል። ሴራዎቹ ሌሎች ናቸው፤ ፊት ለፊት መልካም የሚመስሉ ነገሮች ሊናገር ይችላል፤ ተደብቆ የሚሰራቸው ደግሞ ያው ይፋ እየተደረጉ እየታዩ ናቸው። ፓርቲው የወያኔን እንቅስቃሴ ይዞ የተነሳና ከህዝብ ጋር ያለው ቁርኝት ጠበቅ ያለ ስለነበር፤ ፓርቲው ፊት ለፊት የሚናገራቸውን መልካም ነገሮች እያየ፤ ከፓርቲው ጋር ተሳስረው የቆዩ፣ እውነታውን በትክክል ያላወቁ አንዳንድ አባላት የተደበቁበትም ነው። እንደ ህወሃትም ሁሉንም በአንድ አይን ማየት በጣም ትክክል አይደለም ያሉት ዶክተር አብርሃም፣ እዚህ ሆነው በዋናነት ችግር እየፈጠሩ ያሉት፤ ህዝብን ከህዝብ ለማጋጨት የሚሰሩት፤ ሰላም ትግራይ ውስጥ እንዳይኖር የሚያደርጉት፤ ፍትህ እንዳያገኝ፣ የአፈና ስራው ከላይ እስከታች እንዲዘረጋ እያደረጉ ያሉት እዚህ ከፍተኛ ጉዳት ሲፈጽሙ የነበሩ፤ ለትግራይ ህዝብ ምንም ሳያደርጉለት እዚህ የራሳቸውን ኔትዎርክ ሲያስተካክሉ፣ ሀብት ሲዘርፉ፣ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ሲፈጽሙ የነበሩ ቡድኖች እንዳለ ተሰብስበው ከነሃጢያታቸው ወደ ህዝባችን ሄደው ተለጥፈዋል ሲሉ አብራርተዋል። “ከዚህ በኋላ ትግራይን ለማልማት ነው የተመለስነው” በሚል የማዘናጊያ ቋንቋ ወደ ህዝባችን ገብተዋል ሲሉ ጠቅሰው፣ ህዝባችን ደግሞ የዋህ ነው ልጆቹን አይጥልም። ህዝቡም ትግራይን ያለማሉ ብሎ አምኖ ነው የተቀበላቸው ብለዋል። እነርሱ ግን እዚህ ሲፈጽሙት የነበረን ሴራ በሙሉ ትግራይ ውስጥ ለመድገም እየተንቀሳቀሱ መሆናቸውን ዶክተር አብርሃም አስታውቀዋል። ከሚታወቁት የኢኮኖሚ ሴራዎችና የሰብዓዊ ጥሰቶች አልፈው፤ ትግራይ ውስጥ ሌላ አገርን የማበጣበጥና አገርን የመበተን ፍላጎቶች ይዘው እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። የእነሱን ጥፋት የሚሸፍን ወይም ደግሞ ሸፍኖ የሚያቆይና እድሜ የሚሰጥ እስከ ሆነ ድረስ እነዚህ ሰዎች የማያደርጉት እንደሌለም አስታውቀው፣ እነዚህ ሰዎች ወይም ቡድኖች (ህወሓት በሚል በሙሉ መጥራት አልችልም) እዚህም እዛም የፈጸሙት ጥፋት ሰፊ መሆኑን ገልጸዋል። ሰላም ከሆነና ለውጥ ከመጣ ተጠያቂ ነን ብለው እንደሚያምኑን ተናግረው፣ እነዚህ ሰዎች በሰላም ጊዜ እነሱ በማይመሩበት ምህዳር ላይ እድሜ አይኖራቸውም። ጥፋታቸው በጣም ከባድ ስለሆነ ይሄን ያውቁታል ብለዋል። አዲስ ዘመን ሐምሌ 27/2012 @ethiocheck

#ድምፃችን_ለግድባችን አ.አ ፒያሳ አከባቢ @ethiocheck
#ድምፃችን_ለግድባችን አ.አ ፒያሳ አከባቢ @ethiocheck

💥በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ከተገኘባቸው ሰዎች ውስጥ 70 በመቶው የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ናቸው።"-የጤና ሚኒስቴር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ሰብሳቢነት ሥራውን የሚከውነው እና ቫይረሱን የመከላከል ሥራዎችን የሚያስተባብረው የሚኒስቴሮች ኮሚቴ፣ በወቅታዊው ሁኔታ ላይ ተወያይቷል። የጤና ሚኒስቴር እና የትምሕርት ሚኒስቴር ወረርሽኙ በዓለም አቀፍ እና በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለውን አካሄድ በተመለከተ ገለጻ አቅርበዋል። ጤና ሚኒስቴር ባቀረበው ሪፖርት መሠረት፣ እስከ አሁን ድረስ በኢትዮጵያ,17,500 በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች የተገኙ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ 70 በመቶው የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ናቸው። በቫይረሱ ከተያዙት ሰዎች መካከል፣ 84 በመቶው ዕድሜያቸው ከ50 ዓመት በላይ ሲሆን፣ ከመመርመራቸው በፊት በቫይረሱ የመያዝ ምልክቶች አልታዩባቸውም። ይህም ምልክት ሳይታይባቸው ቫይረሱን የሚያስተላልፉ ብዙ ሰዎች መኖራቸውን ያመላክታል ተብሏል ። የትምሕርት ሚኒስቴር የመጀመሪያ፣ የሁለተኛ እና የሦስተኛ ደረጃ ትምሕርት ሁኔታዎችን መረጃ አጠቃልሎ አቅርቧል። በዚህም መሠረት፣ ትምሕርት ቤቶች ተመልሰው ከመከፈታቸው በፊት ሊተኮርባቸው የሚገቡ ቅድመ ሁኔታዎችን አመላክተዋል። ከእነዚህም ውስጥ የቫይረሱ የስርጭት መጠን መቀነስ ዋነኛው መሆኑ መገለፁን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አስታውቋል ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የምርመራ መጠንን ከፍ ማድረግ የወረርሽኙን አካሄድ ለመረዳት ወሳኝ ተግባር መሆኑን በአጽንዖት ተናግረዋል። ለአንድ ወር የሚቆይ ሀገር አቀፍ የምርመራ ዘመቻ እንዲካሄድም አቅጣጫ ሰጥተዋል። አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ @ethiocheck

ሕንድ በቀን 57 ሺህ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን ገለጸች ============================== የሕንድ ባላስልጣናት አገሪቱ ባለፉት 24 ሰዓታት ብቻ 57 ሺህ አዲስ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች
ሕንድ በቀን 57 ሺህ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን ገለጸች ============================== የሕንድ ባላስልጣናት አገሪቱ ባለፉት 24 ሰዓታት ብቻ 57 ሺህ አዲስ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን እንዳገኙ አስታውቀዋል። በአንድ ቀን ከተመዘገበው ይህ ከፍተኛው ነው ተብሏል። ሕንድ ከ50 ሺህ ሰው በላይ በቀን ስታስመዝብ ይህ ለሦስተኛ ተከታታይ ቀን ሲሆን የቫይረሱ ስርጭት በእጅጉ እየጨመረ እንደሆነ ማሳያ ነው ተብሏል። @ethiocheck

ለሁለት ሳምንታት ያህል ከቤታቸው ሳይወጡና የሰልክ ግንኙነት ለማድረግ ሳይችሉ እንደቆዩ የሚናገሩት በአቶ ዳውድ ኢብሳ ከትናንት አርብ ጀምሮ ከቤታቸው መውጣት እንደቻሉ #ለቢቢሲ ተናግረዋል።‼️ አቶ ዳውድ ተጥሎባቸው ስለነበረው የእንቅስቃሴ እቀባና እርሳቸው በሌሉበት በፓርቲያቸው ከፍተኛ አመራር አባላት ስለተካሄደው ስብሰባ ከቢቢሲ ጋር ባደረጉት አጭር ቆይታ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ©BBC @ethiocheck

የ2012 የዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎች ለ2 ወራት ተምረው እንዲመረቁ አቅጣጫ ተቀመጠ! በኮሮና ቫይረስ (COVID-19) ወረርሽኝ ምክንያት ትምህርት አቋርጠው በቤታቸው የሚገኙ የመጀመሪያ ዲግሪ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመራቂ ተማሪዎችን ያቋረጡትን ትምህርት ከ45 ቀን እስከ 2 ወር በሆነ ጊዜ ውስጥ ተምረው በማጠናቀቅ እንዲመረቁ አቅጣጫ መቀመጡን 'አዲስ ማለዳ ጋዜጣ' በዛሬው ዕትሙ መረጃውን ይዞ ወጥቷል። የኢፌዴሪ ሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር እንደገለፀው ከተመራቂ ተማሪዎች በተጨማሪ ሌሎች በየደረጃው ያሉ ተማሪዎች በተቀመጠው ጊዜ ያለፋቸውን ትምህርት አጠናቀው ወደ 2013 የትምህርት ዘመን እንዲሸጋገሩ ውሳኔ ላይ መደረሱን ለማወቅ ተችሏል። በሀገር አቀፍ ደረጃ የተቀመጠው አቅጣጫ ተማሪዎቹ መቼ ወደ ዩኒቨርሲቲዎች እንደሚመለሱ ቀን እንዳልተቆረጠለት ተመላክቷል። ይህ የሆነበት ምክንያት ተማሪዎቹ መቼ ወደ ዩኒቨርሲቲ መመለስ እንዳለባቸው ኮቪድ-19 ያለበትን ደረጃ ያገናዘበ የመንግስትን ውሳኔ የሚፈልግ ጉዳይ በመሆኑ ነው ተብሏል #AddisMaleda @ethiocheck

የትግራይ ክልል መንግስት ምርጫ ለማካሄድ የጀመረውን ኢ-ህገ መንግስታዊ እንቅስቃሴ በአፋጣኝ እንዲያቆም ሲል የፌዴሬሽን ምክር ቤት አሳሰበ፡፡ ምክር ቤቱ ለትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት በላከው ደብዳቤ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ምክንያት ስድስተኛውን ሀገራዊ ምርጫ ማካሄድ እንደማይችል ያቀረበውን ሪፖርት መነሻ በማድረግ የሕገ መንግስት ትርጉም እንደተሰጠበት አስታውሷል፡፡ በዚህም የኢፌዴሪ ሕገ መንግስት ምርጫን በወቅቱ ለማካሄድ ከአቅም በላይ የሆነ እክል ሲያጋጥም ምን መደረግ እንዳለበት በግልጽ ባለመደንገጉ እና ህገ መንግስቱ በሚፈቅደው መሰረት ክፍተቱን በህገ መንግስት ትርጉም መሙላት ተገቢ መሆኑን በማመን ስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ እንዲራዘም መወሰኑንም አስታውሷል፡፡ ይሁንና የትግራይ ክልል መንግስት ይህን ውሳኔ ወደጎን በመተው በክልሉ ምርጫ ለማካሄድ ወስኖ እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑን አረጋግጠናል ያለው ምክር ቤቱ በህገ መንግስቱ አንደቀጽ 102 መሰረት በፌዴራልና በክልል ነጻና ትክክለኛ ምርጫ በገለልተኛነት ማካሄድ የሚችለው የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ብቻ እንደሆነና በክልል ደረጃ የሚቋቋም ምርጫ ቦርድ አለመኖሩን ጠቅሷል፡፡ በመሆኑም የትግራይ ክልል ምርጫን በሚመለከት የወሰነው ውሳኔና የራሱን የምርጫ ኮሚሽን በማቋቋም ጭምር እያካሄደ ያለው እንቅስቃሴ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ስድስተኛውን ሀገራዊ ምርጫ በተመለከተ ሰኔ 3 ቀን 2012 ዓመተ ምህረት ያሳለፈውን ውሳኔ ያላከበረ ከመሆም ባሻገር ግልጽ የሆነ የህገ መንግስት ጥሰት ነው ብሏል ምክር በቱ በደብዳቤው፡፡ በተጨማሪም በሀገ መንግስቱ አንቀጽ 62 (9) መነሻ በማድረግ ማንኛም ክልል ህገ መንግስቱን በመጣስ ህገ መንግስዊ ስርዓቱን አደጋ ላይ የጣለ እንደሆነ የፌደራሉ መንግስት ጣልቃ የሚገባበትን ስርዓት ለመደንገግ በወጣው አዋጅ ቁጥር 359/1995 አንቀጽ 12 መሰረት በአንድ የክልል መንግስት ተሳትፎ ወይም እውቅና ህገ መንግስቱን ወይም ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን ባለማክበር የሚደረግ እንቅስቃሴ ወይም ድርጊት ህገ መንግስታዊ ሰርዓቱን አደጋ ላይ የጣለ እንቅስቃሴ ወይም ድርጊት እንደሆነ በግልጽ መደንገጉን ጠቅሷል፡፡ በመሆኑም የትግራይ ክልል ምርጫን ለማካሄድ የጀመረው እንቅስቃሴ ህገ መንገስቱን የሚቃረን፡ ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን አደጋ ላይ የሚጥልና የኢዮጵያን የፌዴራል ስርዓት የሚጎዳ አካሄድ ነው ብሎታል፡፡ በተጨማሪም በህገ መንግስቱ አንቀጽ 50 (8) መሰረት ለፌደራል መንግስት የተሰጠው ስልጣን በክልሎች መከበር ያለበት መሆኑና የህገ መንግስት የበላይነት በሚደነግገው የህገ መንግስቱ አንቀጽ 9 (1) መሰረት፡ ማንኛውም ህግ ወይም የመንግስት አካል ውሳኔ ከህገ መንግስቱ ጋር የሚቃረን ከሆነ ተፈጻሚነት እንደማይኖረው ታውቆ የክልሉ መንግስት ህገ መንግስቱንና የፌዴሬሽን ምክር ቤትን ውሳኔ እንዲያከብርና የጀመረውን ኢ-ህገ መንግስታዊ እንቅስቃሴ በአፋጣኝ እንዲያቆም ሲል ምክር ቤቱ አሳስቧል፡፡ @ethiocheck

ከሳምንታት በፊት የዱባይን የሰልፍ ክልከላ ህግ ጥሰው አደባባይ በመውጣት ዳውን ዳውን ሲሉ የተያዙት 3ሺ ድርሃም እንዲቀጡ በመቀጠል ዳውን ዳውን ብለው ወዳጣጣሏት ኢትዮጵያ እስከ ኦገስት 10 ዲፖርት
ከሳምንታት በፊት የዱባይን የሰልፍ ክልከላ ህግ ጥሰው አደባባይ በመውጣት ዳውን ዳውን ሲሉ የተያዙት 3ሺ ድርሃም እንዲቀጡ በመቀጠል ዳውን ዳውን ብለው ወዳጣጣሏት ኢትዮጵያ እስከ ኦገስት 10 ዲፖርት እንዲደረጉና ዳግመኛ ወደ ዱባይ እንዳይመለሱ አሻራ እንዲሰጡ የዱባይ ፍርድ ቤት በትላንትናው ዕለት ወስኗል።‼️ ዶ/ ር አብይ አህመድ ግን ይህን ጉዳይ ቢያጤኑት መልካም ነው ! ምንም ቢሆን እነዚህ ከድንቁርናቸው ብዛት እንጂ እነሱም ኢትዮጵያን ናቸው ! እንዲህ አይነት መረር ያለ እርምጃ በኢትዮጵያን ላይ ሲወሰድ ዝም ማለት የለባቸውም ነገሩን በዲፕሎማሲ መፍታት አለባቸው ከእነሱ አልፎ ቤተሰባቸውን ሀገርን ይጎዳል ! ዞሮ ዞሮ መተው የሀገር ሸክም ነው የሚሆኑት እዛው ሆነው ራሳቸውን ቤተሰባቸውን ሀገራቸውን ቢደግፋ ለሀገር ይጠቅማል ብለን እናሰባለን :: @ethiocheck

ሼይኽ መሐመድ ሁሴን አሊ አል አሙዲ ለኡዱሂያ 105 በሬዎችን አበርክተዋል! "የኢድ አል አድሃ አረፋ በዓልን ሚስኪኖች በዓሉን ተደስተው ያሳልፉ ዘንድ ኢትዮጵያዊው ባለሃብት ሼይኽ መሐመድ አሊ አል አ
ሼይኽ መሐመድ ሁሴን አሊ አል አሙዲ ለኡዱሂያ 105 በሬዎችን አበርክተዋል! "የኢድ አል አድሃ አረፋ በዓልን ሚስኪኖች በዓሉን ተደስተው ያሳልፉ ዘንድ ኢትዮጵያዊው ባለሃብት ሼይኽ መሐመድ አሊ አል አሙዲን በድርጅታቸው ዋና ስራ አስኪያጅ በጀማል አህመድ በኩል 105 በሬዎችን ለኡዱሂያ አበርክተዋል። በሬዎቹም ታርደው ስጋው ለአቅመ ደካሞች እና ለሚስኪኖች በዓሉን በደስታ እንዲያሳልፉት ይከፋፈላል። ሼይኽ መሐመድ ለሃገራቸው እና ለድሆች ዘወትር ድጋፍ እያደረጉ ይገኛሉ።" Via Ustaz Abubeker Ahmed @ethiocheck

ጃዋር መሐመድ እና በቀለ ገርባ የታሳሪዎችና የቤተሰቦቻቸው የባንክ አካውንት መታገዱ ተሰማ! የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያን ተከትሎ በቁጥጥር ሥር የዋሉ ሰዎች እና የቤተሰብ አባላት የባንክ አካውንት እንዲታገድ በመደረጉ የቤተሰብ አባሎቻቸው ገንዘብ ማንቀሳቀስ ባለመቻላቸው ለችግር መጋለጣቸውን ለቢቢሲ ተናገሩ።የተጠርጣሪዎች ጠበቃ በበኩላቸው የባንክ አካውንቶቹ እንዳይንቀሳቀሱ የተደረገው ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ነው በሚል ቅሬታ አሰምተዋል።የባንክ አካውንታቸው እንዳይንቀሳቀስ ከተደረገባቸው ሰዎች መካከል የአቶ ጃዋር መሐመድና ቤተሰባቸው፣ የአቶ በቀለ ገርባ እና የቤተሰባቸው እንዲሁም የጋዜጠኛ መለሰ ዲሪብሳ እና ባለቤቱ እንደሚገኙበት ተገልጿል። የአቶ ጃዋር መሐመድ እህት የሆነችው ራዲያ ሲራጅ፤ የእሷን ጨምሮ የአምስተ ወንድሞቿ የባንክ አካውንቶች እንዳይንቀሳቀስ መደረጉን ለቢቢሲ ተናግራለች።"አጠቃላይ የስድስት ሰዎች አካውንትን ነው የተዘጋው። የእኔንም አካውንት ዘግቷል። የአዋሽ እና የኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ አካውንቶች ናቸው የተዘጉት። ለምን እንደተዘጋ ስንጠይቃቸው እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ ስልክ ተደውሎ ነው ዝጉ የተባልነው አሉን።የሚያደርጉትን ያድርጉት ብለን ትተነዋል" ብላለች። በተመሳሳይ የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትዎርክ ጋዜጠኛ መለሰ ዲሪብሳ ባለቤት የሆነችው ታደለች መርጋ፤ የእርሷ እና የባለቤቷ የቁጠባ ሂሳብ እንዳይንቀሳቀስ መደረጉን ለቢቢሲ ተናግራለች።ታደለች በትናንትናው እለት የቤት ኪራይ ለመክፈል በማሰብ ገንዘብ ለማውጣት ወደ ባንክ መሄዷን ጠቅሳ ማውጣት እንደማትችል ከባንኩ ሠራተኞች ሲነገራት ለምን እንደሆነ መጠየቋን ገልጻለች። Via BBC Amharic @ethiocheck

“አቶ ሽመልስና ብልፅግና ፓርቲያቸው የህዝብ ጥያቄ መመለስ ሲያቅታቸው ህወሓትን እየወነጀሉ ነው-“ ©አቶ ጌታቸው ረዳ‼️ አቶ ሽመልስ አብዲሳ እና ፓርቲያቸው ብልፅግና የህዝብ ጥያቄ መመለስና ሰላም ማ
“አቶ ሽመልስና ብልፅግና ፓርቲያቸው የህዝብ ጥያቄ መመለስ ሲያቅታቸው ህወሓትን እየወነጀሉ ነው-“ ©አቶ ጌታቸው ረዳ‼️ አቶ ሽመልስ አብዲሳ እና ፓርቲያቸው ብልፅግና የህዝብ ጥያቄ መመለስና ሰላም ማስፈን ሲያቅታቸው ህወሓትን እየወነጀሉ መቀጠልን መርጠዋል ብሏል የህወሓት ስራ አስፈፃሚ አባል ጌታቸው ረዳ። አቶ ጌታቸው ረዳ ከአቶ ሽመልስ አብዲሳ ለተነሳው ውንጀላ ትናንት በሰጠው ምላሽ፤ በጨፌ ኦሮሚያ ባደረጉት ንግግር በአሁኑ ወቅት በኦሮሚያ ውስጥ እየተፈጠሩ ላሉት ችግሮችና በህዝቡ ለሚነሱ ጥያቄዎች ሁሉ ህወሓትና ኦነግ-ሸኔን ተጠያቂ ናቸው ሲል መወንጀሉን ጠቅሷል። አያይዞም “ከዚህ ቀደም ከተጠያቂነት ለማምለጥ ‘የህወሓት ተላላኪ ነበርን’ ሲሉ የነበሩት አቶ ሽመልስ አብዲሳ አሁንም ደግሞ “ህወሓት ኦሮሚያ ውስጥ በመለመላቸው ፈረሶች የሚፈጥረው ችግር እንደቀጠለ ነው የሚል አዲስ ለቅሶ ጀምሯል” ሲል ተናግሯል።አቶ ሽመልስ አብዲሳ እና ፓርቲያቸው ብልፅግና የህዝብ ጥያቄ መመለስና ሰላም ማስፈን ሲያቅታቸው ህወሓትን እየወነጀሉ መቀጠልን መርጠዋል ብለዋል። “የኦሮሚያ ፈረስ ጋልበው የሚጠቀሙ ሰዎች ከነበሩ ከአሁን በፊት የመጀመሪያ ተጠያቂ ፈረስ ሆኖ ያገለገለው ሰው ነው ካለ በኋላ ለምሳሌ አቶ ሽመልስ የሚመሩት መንግስት ከአሁን በፊት እንደሚሉት ህወሓት ጋልቦ ከሆነ እነ ሽመልስ ነበሩ ፈረሶቹ ማለት ነው፤ ብለዋል።“ስለዚህ የራሳቸው ጉዳይ ነው!” ያሉት አቶ ጌታቸው ኦሮሚያን የሚያስተዳድሩት እነሱ ናቸው፤ ራሱ ሲያስተዳድር ኖሮ ሲሳሳት ‘አይ እገሌ ብሎኝ ነው’ ካለ ያኔ ጥፋት ነው፣ አሁንም ኦሮሚያ ውስጥ ለሚፈጠር ማንኛውም እንቅስቃሴ የኦሮሚያ ክልል መንግስት የኦሮሚያን ህዝብ ጥያቄ መልሶ ሰላምና መረጋጋት የመፍጠር ኃላፊነት የኦሮሚያ መንግስት መሆኑን መታወቅ አለበት ብሏል። @ethiocheck

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች “እንኳን ለኢድ አል አድሃ አረፋ በዓል በሰላም አደረሳችሁ” በዓሉ የመረዳዳትና የመተሳሰብ ባህላችሁን ከፍ አድርጋችሁ የምታሳዩበት፤ ወገናችሁን የምታስቡበት እንደሚ
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች “እንኳን ለኢድ አል አድሃ አረፋ በዓል በሰላም አደረሳችሁ” በዓሉ የመረዳዳትና የመተሳሰብ ባህላችሁን ከፍ አድርጋችሁ የምታሳዩበት፤ ወገናችሁን የምታስቡበት እንደሚሆን እናምናለን። መልካም በዓል @ethiocheck