en
Feedback
AIRDROP ROOM

AIRDROP ROOM

Open in Telegram
2 485
Subscribers
No data24 hours
-157 days
-5230 days
Posts Archive
የትግራይ ክልል ተመድን ጨምሮ ለዓለም አቀፍ ተቋማት ጥሪ አቀረበ! ( በሪፓርተር ጋዜጣ የቀረበ ) ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በተለይ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) እና የአፍሪካ ኅብረት በኢትዮ
የትግራይ ክልል ተመድን ጨምሮ ለዓለም አቀፍ ተቋማት ጥሪ አቀረበ! ( በሪፓርተር ጋዜጣ የቀረበ ) ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በተለይ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) እና የአፍሪካ ኅብረት በኢትዮጵያ ላይ ያንዣበበውን አደጋ ለማስወገድ የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ፣ የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ጥሪ አቀረበ፡፡ በተመሳሳይ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ከአፍሪካ ኅብረት ጋር በመተባበር፣ ለአካባቢውም ሆነ ለዓለም ሰላምና ደኅንነት ሥጋት ሊሆን ይችላል ያለውን አደጋ ለመቀልበስ የበኩሉን እንዲወጣ ክልሉ በጻፈው ደብዳቤ ጥሪ አቅርቧል፡፡ ገዥው መንግሥት በያዘው አካሄድ መጓዙን የሚቀጥል ከሆነ አደጋው ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን የምሥራቅ አፍሪካ ቀጣናን ወደ ፖለቲካዊ፣ የደኅንነትና የሰብዓዊ ቀውስ ውስጥ ሊያሰምጥ ይችላል በማለት ክልሉ ማስጠንቀቂያ አዘል ጥሪውን ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ አቅርቧል፡ Readmore https://telegra.ph/Reporter-06-10

#UPDATE የኢትዮጵያ፣የሱዳንና ግብጽ የውሃ ሚኒስትሮች በትናንትናው እለት ያካሄዱት ስብሰባ “ውጤታማ ነው ብሎ መግለጽ በጣም አስቸጋሪ” መሆኑን የግብጽ ውሃ ሀብትና መስኖ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ
#UPDATE የኢትዮጵያ፣የሱዳንና ግብጽ የውሃ ሚኒስትሮች በትናንትናው እለት ያካሄዱት ስብሰባ “ውጤታማ ነው ብሎ መግለጽ በጣም አስቸጋሪ” መሆኑን የግብጽ ውሃ ሀብትና መስኖ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡ እንደ የግብጽ ውሃ ሀብትና መስኖ ሚኒስቴር መግለጫ ስብሰባው ትኩረት ያደረገው ስለውይይት ሂደት፤ ስለመወያያ ነጥቦችና ታዛቢዎች ስለሚኖራቸው ሚና ነበር፤ ስለዚህ ዉጤታማ ነው ማለት እንደማይቻል አብራርቷል፡፡ እንደመግለጫው ከሆነ ኢትዮጵያ በሁሉም ጉዳዮች ላይ ክርክር ከፍታለች፤ አዲስ ምክረ ሀሳብ አቅርባ እንዲታይላት መፈለጓና በዋሽንግተን ስምምነት ላይ የተደረሰባቸውን ጉዳዮች ላይም እየተከራከረች መሆኑን ገልጿል፡፡ ኢትዮጵያ በሀምሌ ወር ግድቡን ለመሙላት በያዘችው አቋም ላይም ጸንታለች ብሏል መግለጫው፡፡ ግብጽ፣ ኢትዮጵያ ድርድሩ ሳያልቅና ስምምነት ላይ ሳይደረስ መሙላት እንዳትጀምር ጠይቃለች። ኢትዮጵያም በበኩሏ ሶስቱ ሀገራት “የታዛቢዎቹ ሚና ምን ይሁን ” በሚለው ጉዳይ ስምምነት ላይ አለመድረሳቸውን የውኃ መስኖ ኢነርጂ ሚኒስቴት ባወጣው መግለጫ መግለጹ ይታወሳል፡፡ #AlAin

#UPDATE የሱዳን የመስኖ ሚኒስትር ያሲር አባስ የትላንቱ ውይይቱ ከተጠናቀቀ በኋላ “አዎንታዊ እና ፍሬያማ” ነበር ሲሉ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል። ሚኒስትሩ ድርድሩን በአፋጣኝ ለመቀጠል
#UPDATE የሱዳን የመስኖ ሚኒስትር ያሲር አባስ የትላንቱ ውይይቱ ከተጠናቀቀ በኋላ “አዎንታዊ እና ፍሬያማ” ነበር ሲሉ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል። ሚኒስትሩ ድርድሩን በአፋጣኝ ለመቀጠል የሚያስፈልጉ እርምጃዎች እና ሶስቱም አገራት በተናጠል ያነሷቸው ዋነኛ የልዩነት ነጥቦች ውይይት ተደርጎባቸዋል ብለዋል።  የሱዳን መስኖ ሚኒስትርን የጠቀሰው የግብጹ “አህራም” ድረ ገጽ፤ ኢትዮጵያ በዋሽንግተን ስምምነት በተደረሰባቸው ጉዳዮች ድርድር ለመቀጠል ፈቃደኛ ብትሆንም መሰረታዊ የልዩነት ነጥቦች እንዳሏት ይፋ አድርጋለች ሲል ዘግቧል።   ሶስቱ ሀገራት ከአርብ እና ከእሁድ በቀር የሶስትዮሽ ውይይቱን በየቀኑ ለመቀጠል መስማማታቸውን የሱዳን ዜና አገልግሎት ዘግቧል። የኢትዮጵያ መንግሥት “የሶስቱ ሀገራት ድርድር የግድቡ የመጀመሪያ ሙሌት እና ዓመታዊ አለቃቅ ላይ ብቻ የተወሰነ ይሆናል” ብሏል። እንደ ትናንትናው ሁሉ ዛሬም በቪዲዮ ኮንፍረንስ ይቀጥላል የተባለው ውይይት በመጪው ሰኞ አሊያም ማክሰኞ ይገመገማል። #EthiopiaInsider

በሊባኖስ የኢትዮጵያ ቆንሲላ ስራ ማቆሙን አስታወቀ!! በሊባኖስ የኢትዮጵያ ቆንሲላ ዲፕሎማትና የኮሚኒኬሽን ሀላፊ የሆኑት በፍርዴ ዳንግላ ካለፈው ሳምንት አንስቶ ቆንስላው ለምን በሩን ዘግቶ ስራውን እንዳቆመ ተጠይቀው በሰጡት መልስ ለዲፕሎማቶቹ ደህንነት ታስቦ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ ሲናገሩም ‹‹አንዳንዶቹ ሴቶች ባለፈው ሳምንት ተሰልፈው በመምጣት ሊያጠቁን ሞክረው ነበር፡፡ አሁንም እያስፈራሩን ቢሆንም ከእነሱ ጋር ግጭት ውስጥ መግባት አልፈለግንም›› በማለት አስረድተዋል፡፡ በስፍራው የወደቀችው ቤቲ የተባለችው ኢትዮጵያዊት ግን ይህንን አስተባብላለች፡፡ ለጋዜጣው ስትናገር ‹‹እኛ ምንም አላደረግናቸውም፡፡ በየቀኑ መኪናቸውን አስነስተው ሲገቡና ሲወጡ እናያቸዋለን፡፡ እኔ አሁን ለምሳሌ የሶስት ወር ደመወዝ ሳይከፈለኝ ጎዳና ላይ ወድቄያለሁ፡፡ የእነሱ ስራ እኛን መርዳት ቢሆንም እያደረጉ ያሉት በቻሉት መጠን እኛን ከአካባቢው ማጥፋት ነው›› ብላለች፡፡ አሶሺየትድ ፕሬስ በቅርቡ ባሰራጨው ቪዲዮ አንዲት ኢትዮጵያዊት ወደ ቆንሲላው ልትገባ ስትል በሊባኖስ የፀጥታ ሰራተኛ ስትገፈተር አሳይቷል፡፡ ይህንን በተመለከተ የተጠየቁት የቆንሲላው ኮሚኒኬሽን ሀላፊ አቶ በፍርዴ ኮሮናን ለመከላከል የተደረገ እርምጃ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ጨምረውም ‹‹እነዚህ ሴቶች የወረርሽኙን ምርመራ አላደረጉም፡፡ እነሱን አስገብተን የቆንስላውን ሰራተኞች አደጋ ውስጥ መክተት አልፈለግንም፡፡ በተደጋጋሚ የሊባኖስ ባለስልጣናትን ጣልቃ እንዲገቡና አሰሪዎቹ ያልከፈሏቸውን ደመወዝ እንዲሰጧቸው ጠይቀናል፡፡ ያንን ለማድረግ ግን ዘግይተዋል›› ብለዋል፡፡ በሊባኖስ ሰራተኛ ሚኒስቴር የማውንት ሌባኖን ሀላፊዋ ኢማን ካሃዛል ግን ሴቶቹ አሁን ላሉበት ሁኔታ የኢትዮጵያን መንግስት ተጠያቂ አድርገዋል፡፡ ለጋዜጣው ሲናገሩ ‹‹አሁን የሊባኖስ ኢኮኖሚ ወድቋል፡፡ እኛ እነዚህ ሴቶች ዶክመንት ስለሌላቸው በተለመደው አሰራር መቀጣት የነበረባቸው ቢሆንም ቅጣቱን ትተንላቸዋል፡፡ ነገር ግን ዜጎቹን አልወስድ ያለው የኢትዮጵያ መንግስት ነው›› በማለት አስታውቀዋል፡፡ ጋዜጣው እንዳለው እነዚህን ሴቶች ወደ አገራቸው ለመውሰድ ብቸኛው አማራጭ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ነው፡፡ ቢሆንም ለእነዚህ በወር 150 ዶላር ተቀጥረው ለነበሩ ሴቶች አየር መንገዱ ለአንድ ጊዜ ጉዞ ከፍተኛ ክፍያ መጠየቁን የገለፀው ጋዜጣው ስለሁኔታው የሊባኖስ ባለስልጣኗ ያሉትንም አካቷል፡፡ የሊባኖስ ሰራተኛ ሚኒስትር ባለስልጣኗ ኢማን ካሃዛል ለጋዜጣው ሲናገሩ ‹‹እንዴት በሊባኖስ ያሉት እነዚህ ሴቶች ይህንን ያህል ገንዘብ ከፍለው ትኬት ይገዙናል ብለው ያስባሉ? በሌላ ኤምባሲ እንደዚህ አይነት ችግር አልገጠመንም፡፡ በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ግንኙነት የማከብር ቢሆንም የኢትዮጵያ መንግስት እንዲህ አይነት ነገር በማድረጉ ግን ግራ ተጋብቻለሁ›› በማለት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ @ethiocheck

የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ጃዋር መሀመድን አስጠነቀቀ . የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ጃዋር መሀመድ የክልሉን ሰላም እና መረጋጋት ለማደፍረስ በተለያዩ የማህበራዊ ድህረ-ገፆች ከሚለጥፋቸው የተዛቡ መረጃዎች እንዲታቀብ በማስጠንቀቅ እስከአሁንም በለቀቃቸው ከእውነታ የራቁ መረጃዎች በህግ የሚጠየቅ መሆኑን አስታውቋል፡፡ ፖሊስ ኮሚሽኑ በትናንትናው እለት ሰኔ2/2012 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው "የኦሮሚያ ፖሊስ ወንጀልን ከመከላከል፣ የክልልሉን ሰላም እና ፀጥታ ከማስከበር እንዲሁም ህግ እና ስርዓትን ከማስከበር የዘለለ ተግባር የለውም፡፡ በዚህም መሠረት ከመቼውም ጊዜ በላቀ ሁኔታ ልዩ ኃይሉን በማደራጀት የሕዝቡን ሰላም እና የክልልሉን ፀጥታ በማስጠበቅ ላይ ይገኛል፡፡ ይሁን እንጂ ይህንን የክልልሉን ሰላም እና መረጋጋት የማይሹ አንዳንድ ግለሰቦች እና ቡድኖች የህዝብ መከታ የሆነውን ኃይል ሥም በማጠልሸት የፖለቲካ መጠቀሚያ በማድረግ ላይ እንደሚገኙ ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡ በዚህም መሰረት ከአሁን በኋላ ማንኛውም ግለሰብ ወይንም ቡድን የኦሮሚያ ልዩ ኃይልን መልካም ስም እና ዝና ዝና እንዲያጎድፍ እንዲሁም ለፖለቲካ ትርፍ እንዲጠቀምበት አንፈቅድም፡፡ ከዲንሾ ጋር ተያይዞ የሚሰራጨው ተራ አሉባልታም ሊገታ ይገባዋል፡፡ መነሻው የግለሰቦች ፀብ ሲሆን ጉዳዩ በህግ ተይዞ በመጣራት ላይ ይገኛል፡፡ ቢሆንም ግን እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ አንዳንድ ግለሰቦች በተለይም ጃዋር መሀመድ በፌስ ቡክ ገፁ ላይ የተዛባ መረጃን በመለጠፍ ብዙዎችን የማሳሳት ተግባሩን የቀጠለ ሲሆን በእንግሊዘኛ የለጠፈውን እንዲሁም ሌሎች ተጨባጭ መረጃዎችን በማያያዝ በህግ አግባብ የምንጠይቅ መሆኑን እንገልፃለን" ማለቱን ከፖሊስ ኮሚሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ ምንጭ፦ አዲስ ማለዳ @ethiocheck

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድሩ ትላንት ተካሄዷል! የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን የሙሌት እና ዓመታዊ የውሃ አለቃቅ በተመለከተ በኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ መካከል የሚደረገው
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድሩ ትላንት ተካሄዷል! የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን የሙሌት እና ዓመታዊ የውሃ አለቃቅ በተመለከተ በኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ መካከል የሚደረገው የሶስትዮሽ ድርድር ትላንት በበይነ-መረብ የቪዲዮ ኮንፈረንስ ታዛቢዎች በተገኙበት በውሃ ጉዳይ ሚኒስትሮች ደረጃ ተካሂዷል። በዚህ ድርድር ላይም ደቡብ አፍሪካ፣ የአውሮፓ ህብረት እና አሜሪካ ታዛቢ ሆነው ቀርበዋል፡፡ ሀገራቱ የድርድር ስነ-ስርዓትን/procedure፣ ታዛቢዎችን፣ ስለ ድርድሩ አካሄድ እና ዋናዋና የድርድር ያልተቋጩ ጉዳዮችን በተመለከተ መወያየታቸውን የኢትዮጵያ የውኃ፣ የመስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ገልጿል፡፡ እያንዳንዱ ሀገር ዋናዋና የድርድር ጉዳዮች ናቸው ያሏቸውን ሃሳቦች በዝርዝር ያቀረቡ ሲሆን በዚህም መሰረት በቀጣይ ቀናት ተከታታይ ውይይቶችን ለማድረግ መግባባት ላይ ተደርሷል ተብሏል። ይሁን እነጂ የታዛቢዎቹ ሚና ምን ይሁን የሚለውን በተመለከተ በሀገራቱ መካከል መግባባት ላይ ያልተደረሰ ሲሆን ስብሰባው በዛሬው ዕለትም የሚቀጥል ይሆናል። የሶስቱ ሀገራት ድርድር የግድቡ የመጀመሪያ ሙሌት እና ዓመታዊ አለቃቅ ላይ ብቻ የተወሰነ ይሆናል ሲል ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ገልጿል። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በተመለከተ ልዩነቶችን በድርድር ለመፍታት ኢትዮጵያ እንደ ትናንቱ ሁሉ ዛሬም ዝግጁ መሆኗን ገልጻለች።

⬆️ በቅርቡ ኢትዮጵያ ውስጥ ከባንክ ደጃፍ ላይ ተይዞ ለጅቡቲ የፀጥታ ሀይሎች ተላልፎ የተሰጠው የቀድሞው የጅቡቲ አየር ሀይል አብራሪ ሀገሩ ከተወሰደ በሁላ የደረሰበትን ድብደባ የሚያሳይ ቪድዮ በመውጣቱ ጅቡቲ ውስጥ የተቃውሞ ሰልፍ እየበረታ ነው! ሌ/ት ፉአድ ዩሱፍ አሊ ከጅቡቲ ጠፍቶ ኢትዮጵያ ውስጥ የገባው መጋቢት 2012ዓ/ም ነበር። እርሱ እንደሚለው ለመጥፋቱ ምክንያቱ የደሞዝ አለማግኘት ነበር። ከዛ ግን አዲስ አበባ ውስጥ ዳሀብሺል ከተባለ የሀዋላ አገልግሎት ገንዘብ ሊያወጣ ሲል በኢትዮጵያ የፀጥታ ሀይሎች ተይዞ ከዛም ለጅቡቲ የፀጥታ ሀይሎች ተላልፎ ተሰጥቷል። የጅቡቲ የፀጥታ ሀይሎችም በልዩ አውሮፕላን ወደ ጅቡቲ ወስደውት ነበር። ከዛ ግን ለብዙ ሳምንታት ደብዛው ከጠፋ በሁዋላ ሰሞኑን የደረሰበትን ድብደባ የሚያሳይ ቪድዮ ከእስር ቤት ሾልኮ ወጥቷል፣ ይህም ጅቡቲ ውስጥ ቁጣ ቀስቅሷል። "ይህ ቪድዮ ሾልኮ ወጥቶ ከታየ በህይወት አልተርፍም፣ መሞቴ ግን ብዙ አያስጨንቀኝም" የሚለው ሊ/ት ፉአድ ሰውነቱ ላይ በድብደባ የደረሰበትን ጉዳት እና የታሰረበትን ቆሻሻ ስፍራ በቪድዮው ላይ ያሳያል። የቪድዮው መውጣትን ተከትሎ በሺዎች የሚቆጠሩ የጅቡቲ ዜጎች ግለሰቡ ይፈታ ብለው ሰልፍ ወጥተዋል። ሰልፉ በተለይ በጅቡቲ ሁለተኛዋ ከተማ አሊ ሳቢህ ውስጥ ብሷል ተብሏል። የጅቡቲ መንግስት በበኩሉ ግለሰቡ የተያዘው "በሀገር መክዳት ወንጀል ነው" ያለ ሲሆን ሰልፍ የወጡት ሰዎችም ዝርፊያ እየፈፀሙ እንደሆነ ጠቅሶ ማስጠንቀቂያ አውጥቷል። በኢትዮጵያ ካሉት የጅቡቲ አምባሳደር እና ከሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ሞክሬ አልተሳካም፣ በኢትዮጵያ በኩልም ምንም አልተባለም። "ምናልባት ኢትዮጵያ ይህንን ፓይለት ለጅቡቲ አሳልፋ የሰጠችው ከ15 አመት በፊት በተመሳሳይ ከኢትዮጵያ ጠፍተው ጅቡቲ የገቡ የአየር ሀይል ፓይለቶችን ጅቡቲ ለኢትዮጵያ አሳልፋ ሰጥታ ስለነበር ሊሆን ይችላል" ያሉኝ አንድ የምስራቅ አፍሪካ ተንታኝ ናቸው። የደረሰኝ መረጃ እንደሚያመለክተው ሊ/ት ፉአድ 37 አመቱ ሲሆን የሰባት ልጆች አባት ነው። የጅቡቲ አየር ሀይልን የተቀላቀለው ከ14 አመት በፊት ሲሆን በሩስያ እና ደቡብ አፍሪካ ትምህርት ተከታትሏል። @ethiocheck

photo content

"የሴቶች እና የህጻናት ጥቃትን በተመለከተ 94 መዝገቦች በፖሊስ ምርመራ ላይ ናቸው" የሴቶች እና የህጻናት ጥቃትን በተመለከተ ዛሬ የጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን ግምገ
"የሴቶች እና የህጻናት ጥቃትን በተመለከተ 94 መዝገቦች በፖሊስ ምርመራ ላይ ናቸው" የሴቶች እና የህጻናት ጥቃትን በተመለከተ ዛሬ የጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን ግምገማ ማካሄዳቸውን ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በይፋዊ ፌስቡክ ገጻቸው ላይ ገልጸዋል። በዚህም 94 መዝገቦች በፖሊስ ምርመራ ላይ መሆናቸውን እና 23 ክሶች መመስረታቸውን እንዲሁም በዚሁ ጊዜ ውስጥ በ 4 መዝገቦች ላይ የፍርድ ውሳኔ መሰጠታቸዉን የጠቀሱት ጠቅላይ አቃቤ ሕጓ ፍርድ ቤቶችም የሴቶች እና ህጻናት ችሎቶችን በሙሉ አቅማችው እንዲሰሩ መከፈታቸውን ገምግመናል ብለዋል። የኮቪድ 19 መከላከል ስራ ጋር ተያይዞ በቤት መቆየት ምክንያት እና የፍትህ መስሪያ ቤቶች ተዘግተዋል በሚል ጥቃቶች መጨመራቸወን፣ ወደ ፍትህ አካላት መጠቆም መቀነሳችውን እና መረጃ አያያዝ ክፍተቶችን በዝርዝር በግምገማው ተነስተዋል ሲሉ አክለው ገልፀዋል።

የአሁኑን የደቡብ ክልል ለአራት ከፍሎ ለማዋቀር በቀረበ ሰነድ ላይ ዛሬ ውይይት ተካሂዷል! በአቶ አባዱላ ገመዳ በሚመራው የጥናት ቡድን የቀረበውና ለፌደሬሽን ምክር ቤት የተመራው ሰነድ የደቡብ ክልልን
የአሁኑን የደቡብ ክልል ለአራት ከፍሎ ለማዋቀር በቀረበ ሰነድ ላይ ዛሬ ውይይት ተካሂዷል! በአቶ አባዱላ ገመዳ በሚመራው የጥናት ቡድን የቀረበውና ለፌደሬሽን ምክር ቤት የተመራው ሰነድ የደቡብ ክልልን ለአራት የሚከፍል እንደሆነ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር አስነብቧል፡፡ በዚህም፡- - ሲዳማ ክልል ( ቀድሞ በህዝበ ውሳኔ ክልል መሆኑ የተረጋገጠ )፣ - በተለምዶ “ምዕራብ ዞን” ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ያሉ ሸካ፣ ቤንች፣ ማጂ፣ ከፋ እና ዳውሮ ዞኖች በአንድ ክልል ስር እንዲሆኑ በምክረ ኃሳብ ተቀምጧል፣ - በተለምዶ “ማዕከላዊ ዞን” በመባል በሚታወቀው አካባቢ ያሉት የጉራጌ፣ ስልጤ፣ ሀድያ፣ ከምባታ፣ ሀላባ ዞኖች እና የም ልዩ ወረዳ በጋራ ሆነው ሁለተኛ ክልል እንዲመሰርቱ በምክረ ሀሳብ ተቀምጧል፣ - ኦሞቲክ” በሚል መጠሪያ የሚታወቀውን የጋሞ፣ ጎፋ፣ ኮንሶ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ደራሼ፣ ቡርጂ፣ አማሮ እና ኮንሶ ዞኖች እና ልዩ ወረዳዎች በአንድ ክልል እንዲጠቃለሉ ሃሳብ ቀርቦ ከመግባባት ላይ ተደርሷል። በተጨማሪ፡- - ጌዲኦ በልዩ ዞን እንዲደራጅ ከስምምነት ላይ ቢደረስም “በየትኛው ክልል ይካተት?” የሚለው ግን ወደፊት ይወሰናል ተብሏል።  - የወላይታ ዞን 'ኦሞቲክ' የተሰኘው ውስጥ እንዲካተት ቢጠየቅም በስብሰባው ተሳታፊዎች ዘንድ ተቀባይነት ሳያገኝ በመቅረቱ ወደፊት ውሳኔ ይሰጥበታል ተብሏል፡፡ #EthiopiaInsider

አዲሱ ገበያ አካባቢ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የአንድ ሰው ህይወት አለፈ! አዲሱ ገበያ አካባቢ ከሱሉልታ ከተማ የከብቶች መኖ ጭኖ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ ተሸከርካሪ ተገልብጦ የአሽከርካሪው ህይ
አዲሱ ገበያ አካባቢ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የአንድ ሰው ህይወት አለፈ! አዲሱ ገበያ አካባቢ ከሱሉልታ ከተማ የከብቶች መኖ ጭኖ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ ተሸከርካሪ ተገልብጦ የአሽከርካሪው ህይወት ሲያልፍ ሁለት እግረኞች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡ የአሽከርካሪው ረዳት ከመኪናው ዘሎ በመውረድ ህይወቱን ከአደጋው መትረፉን በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የጉለሌ ፣የካ እና የአራዳ ክፍለ ከተሞች የቀጠና 2 የትራፊክ ቁጥጥር ም/ዳይሬክተር ኮማንደር ሙሉጌታ ልፀዋል፡፡

የቡሩንዲ ፕሬዘዳንት ፔይሬ ንኩሩንዚዛ አረፉ! የቡሩንዲው ፕሬዘዳንት ፔይሬ ንኩሩንዚዛ በልብ በሽታ ምክንያት በ55 አመታቸው መሞታቸውን ቢቢሲ በሰበር ዜናው ዘግቧል፡፡ በቡሩንዲ በዚህ አመት ምርጫ ተካ
የቡሩንዲ ፕሬዘዳንት ፔይሬ ንኩሩንዚዛ አረፉ! የቡሩንዲው ፕሬዘዳንት ፔይሬ ንኩሩንዚዛ በልብ በሽታ ምክንያት በ55 አመታቸው መሞታቸውን ቢቢሲ በሰበር ዜናው ዘግቧል፡፡ በቡሩንዲ በዚህ አመት ምርጫ ተካሂዶ የገዥው ፓርቲ እጩ ምርጫ ያሸነፉ ሲሆን የስልጣን ርክክብ እስከሚደረግ ድረስ ንኩሩንዚዛ በስልጣን ላይ እንደሚቆዩ ተገልጾ ነበር፡፡ #BBC #AlAin

ባለፉት 11 ወራት ከ19 ሺ በላይ መሳሪያዎች ወደ አዲስ አበባ ሊገቡ ሲሉ ተይዘዋል! ባለፉት አስራ አንድ ወራት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ባደረገው ክትትል
ባለፉት 11 ወራት ከ19 ሺ በላይ መሳሪያዎች ወደ አዲስ አበባ ሊገቡ ሲሉ ተይዘዋል! ባለፉት አስራ አንድ ወራት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ባደረገው ክትትል ከልዩ ልዩ የሀገሪቷ ክፍሎች በህገ-ወጦች አማካኝነት ወደ አዲስ አበባ የገቡ ከ19 ሺ በላይ የጦር መሣሪያዎች እና ከ 55 ሺ በላይ ጥይቶችን መያዙን አስታወቀ፡፡ 19 ሺ 119 የተለያዩ ሽጉጦች፣ 91 ክላሽንኮቭ ጠብመንጃ፣ 6 መትረየስ ፣ 15 ኋላቀር መሣሪያ እና 4 ፒ.ፒኤ.ች በአጠቃላይ 19 ሺ 235 የጦር በተጨማሪም 55 ሺ 361 የተለያዩ ጥይቶች ሊያዙ መያዙን ኮማንደር ግርማ ገልፀው ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ 106 ግለሠቦች ላይ ክስ ተመስርቶ ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፓሊስ አስታውቋል፡፡ በቅርቡ በወጣው የጦር መሳሪያ ቁጥጥር አዋጅ መሰረት 3 ተከሳሾች ከ 2 እስከ 3 አመት እስራት እንደተፈረደባቸው 18ቱ ደግሞ ዋስትና ተከልክለው በማረሚያ ቤት እንደሚገኙ እና ሌሎቹ ከ3 ሺ እሰከ አንድ መቶ ሺ ብር በሚደርስ የገንዘብ ዋስትና በፍርድ ቤት ተለቀው ጉዳያቸውን በውጪ ሆነው እንዲከታተሉ መደረጉን ነው የተገለጸው፡፡

259 ኢትዮጵያዊያን ዜጎቻችን ከኩዌት ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል! 259 ኢትዮጵያዊያን ዜጎች ከኩዌት ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚነስትር ዴኤታ
259 ኢትዮጵያዊያን ዜጎቻችን ከኩዌት ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል! 259 ኢትዮጵያዊያን ዜጎች ከኩዌት ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚነስትር ዴኤታ ወ/ሮ ጽዮን ተክሉ፣ የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት አየለች እሸቴ፣ የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ ፍሬዓለም ሽባባው፣ የዳያስፖራ ኤጄንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ መሀምድ ሰኢድ እንዲሁም ሌለች ከፍተኛ የመንግስት ተወካዮች ተገኝተው አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ሰሞነኛ ኩነቶች ባሳለፍነው ሳምንት የታንዛንያው መሪ ከውጪ የሚገቡ የጎረና መከላከያ ቁሳቁሶች ላይ ምርመራ በማድረግና እንሰሳት ላይ በመሞከር የኮረና ቫይረስ እንዳገኘባቸው መወያያ ሆኖ ሰንብቷል። ከዚህ ጋር በተያያዘ አንዳንድ የአፍሪካ ሀገራት ኮሮና ቫይረስ ጠፍቷል ውጡ እያለ ህዝቡን ሲገፋፉ የሰነበቱ ሲሆን በሀገሪቱ የፖለቲካ ተቃዋሚዎችና ግለሰቦች ዘንድም ህዝብን ለአደጋ እያጋለጡ ነው በማለት ሲወቀሱ ሰንብተዋል። እንደ ኤርትራ ያሉ ሀገራት ደግሞ ምንም አይነት ከውጪ የሚላኩ ቁሳቁሶችን አንቀበልም በማለት ወጥ አቋማቸውን የገለፁ ሲሆን እስካሁንም ኤርትራ ከ40 ያለዘዘለለ የቫይረሱ ተጠቂ ያስተናገደች ሲሆን ሙሉ በመሉም በቫይረሱ የተጠቁት አገግመው ወተዋል አሁን ባለው መረጃም ምንም የቫይረሱ ተጠቂ የለባትም። በዚህም መሰረት ወደ ማሕበረሰቡ ገብታ እየመረመረች ሲሆን አስመራ ከተማ በተደረገ ጠቅላላ ምርመራም አንድ ሰው ብቻ በቫይረሱ የተጠቃ ተገኝቷል። በቀጣይም በሌሎች ከተሞች ምርመራው እንደሚቀጥል ተናግረዋል። ወደ ሀገራችን ስንመለስ ደግሞ ኢትዮጵያ በቫይረሱ የተጠቁ ዜጎች በፍጥነት እየጨመረ በመምጣቱ ከአፍሪካ 18 ተኛ ደረጃን ይዛለች። በአማካኝም በቀን ከ80 እስከ 150 ሰው ቫይረሱ ያለበት ሰው እየተገኘ ሲሆን ይህም 3500- 5000 እና ስድስት ሺህ ምርመራ ውጤት ነው። የኮሮና ቫይረስ መድሀኒትን ለማግኝት ብዙ ሀገራት እየሞከሩ እንደሆነ ቢነገርም እንዳውም አያሌ ሀገራት መከላከያ ክትባትና መድኃኒቱን አገኘን ሲሉ እንጂ ተግባራዊ ሲደረግ አልታየም ኢትዮጵያ ሀገራችንም መድኃኒቱን ለማግኘት እየመኮረች እንደሆነና ውጤታማ ሊሆን እንደሚችል በጤና ሚኒስቴር ከተገለፀ በኋላ የተገለፀ ሌላ ነገር ባለመኖሩ እስካሁን ምንም አይነት የታወቀ ነገር የለም ሆኖም ግን እነ አሜሪካንና ቻይና የመሳሰሉ ሀገራት ክትባቱን ለመጀመር ያኮበኮቡ እንዲሁም የጀመሩ ሲሆን ነገር ግን ከፍተኛ ቅሬታ አስነስቷል ሁል ጊዜም ቢሆን ለእውነትና ለሕዝብ የቆመች ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት የሞልዶቫን ቤተክርሰቲያን ይህን ክትባት ከሳምንት በፊት በነበራት የምልዕተ ጉባኤ የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ውሳኔ ላይ በይፋ አውግዛለች። የሞልዶቫን ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ክትባት ተብሎ ለሕዝቡ የቀረበው የማይክሮ ቺፕ ሰይጣናዊ ተልዕኮ ነው ስትል በቅዱስ ሲኖዶሷ ጉባኤ ኮንናዋለች በዚህም መሰረት ክትባቱን የጀመሩ ሀገራትና የአለማችን ባለ ፀጋ የሆነውን ቢልጌትን ከዚህ እኩይ ተግባራቸው እንዲመለሱ አሳስባ የውግዘት መልዕክቷን በይፋ ገልፃለች። ምሥራቅ አውሮፓዊቷ ሀገር ሞልዶቫ ሩማንያውያን ዮክሬናውያን፣ የጋጋውዝ እና ሩስያውያን እንዲሁም ቡልጋርያውያን ተሰብስበው ከታላቋ ሶቬት ኅብረት መፍረስ በኀላ ነፃ ያወጧት ሀገር ናት፡፡ በሞልዶቫ የምትገኘው የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ይፋ እንዳደረገችው በCOVID-19 ላይ ክትባት የማዘጋጀት አቅም ያለው ማይክሮሶፍት የተሰኘው ተቋም በሰዎች ክንድ የሚቀበር ማይክሮቺፕ አብሮ ማዘጋጀቱን ፤ክትባቱን የወሰዱ ሰዎችን ጤና ለመከታተል በሚል ምክንያት ሽፋን የተደረገ መሆኑን በመግለጽ ድርጊቱን እንደምታወግዝ አስታውቃለች፡፡የማይክሮሶፍት ባለቤት እና የአለማችን ባዕለጸጋ ሰው ቢል ጌት በቢል እና መሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን በኩል በ18 ወራት ኮሮና ቫይረስን የሚከላከል ክትባት ለማምረት በሥራ ላይ መሆኑን የዓለም የጤና ድርጅት ዳይሬክተር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድኃኖም ማስታወቃቸው ይታወቃል፡፡ የሞልዶቫ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ድርጊቱ የሰዎችን እንቅስቃሴ ለመሰለል እና የሰዎችን እቅድ ለመረዳት የማይክሮቺፕ ወይም ሌሎች ይህን መሰል መሣሪያዎችን በሰው አካል ውስጥ ያስተዋውቃል በማለት ነው የማይክሮሶፍት ድርጅትን ያወገዘችው ቤተክርስቲያኗ በዓለም ዙሪያ ካሉ ከሌሎች ዋና ዋና የኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ጋር ሙሉ ትብብር ያላት ቤተክርስቲያን ስትሆን በምዕራብ አውሮፓ እንደ መብት የሚታየውን የግብረ ሰዶማውያን እንቅስቃሴ በማውገዝ የሃይማኖት መሪዎቿ ምእመናንን በማስተባበር ከዚህ የከፋ ደዌ እና ኃጢአት ትውልዱን ለመጠበቅ በምሥራቅ አውሮፓ ከፍተኛ ሕዝባዊ ንቅናቄ በማድረግ የምትታወቅ ቤተክርስቲያን ናት፡፡ አንድ የቤተክርስቲያኒቱ ካህን በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ “ዓለም አቀፍ ፀረ-ክርስቲያናዊ ሥርዓት በ 5G ቴክኖሎጂ አማካይነት ሰዎችን ለመቆጣጠር የሚያስችል ቴክኖሎጂ በሰዎች አካል ውስጥ ማይክሮቺብስ ለመቅበር ይፈልጋል ይህንንም በማስተዋወቅ ላይ ይገኛል ቤተክርስቲያናችን ይህ ዓይነቱን ፀረ ክርስቲያን ተግባር አትታገሰውም” ብለዋል ፡፡ በማኅበረሰቡ አንዳንድ የቤተክርስቲያን አባላትም የማይክሮሶፍት ድርጅት በዋነኝነት ማይክሮባኪንግ ቴክኖሎጂን የመፍጠር ሀሳቡን ለማሳካት ሰዎችን በ COVID ክትባት አማካይነት በቁጥጥር ሥር ለማዋል እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡ ክትባቱ በ 5G ቴክኖሎጂ አማካኝነት በሰዎች አካል ውስጥ የሚቀበረው ማይክሮቺፕ በሚሰጠው መረጃ ሰዎችን በርቀት እንዲቆጣጠር የሚፈቅድ ግዑዝ አካልን ወደ ሰውነት ያስገባል በማለት ቤተክርስቲያኗ እቅዱን አውግዛለች፡፡ የ5G ቴክኖሎጂ ከ(COVID-19) ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ አሉታዊ ተፅእኖ አለው የሚለው ሐሳብ በአውሮፓ እና በአሜሪካ እንዲሁም በአውሮፓ ህብረት አባል ባልሆኑ ወግ አጥባቂ ቡድኖች እና ሚዲያዎች ከተስፋፋ በኀላ ወሬው የሩሲያ ሚዲያ ሊስፋፋ ችሏል፡፡ በዚህም በአውሮፓ አንዳንድ ሀገሮች የ5 ጂ ኔትወርክ ማማዎች ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡ በአገሪቱ ውስጥ ትልቁ የእምነት ተቋም የሆነው የሞልዶቫ ሜትሮፖሊታን ቤተክርስትያን በሩስያ ኦርቶዶክስ ቀኖና ስር ያለ የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ነው፡ኦፊሴላዊ መረጃ እንደሚያሳየው በሞልዶቫ ወደ 97 ከመቶ የሚሆነው ሕዝብ በይፋ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ናቸው ዘገባው ዘጳጳስ ፖስት (The Pappas Post) እና አልጀዚራ (Al Jazeera) ነው፡፡ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንም ሆነ ከሌሎች ቤተ እምነቶችስ ምን ይጠበቃል? በቀጣይ እንወያይበታለን። @ethiocheck

በኢትዮጵያ የሟቾች ቁጥር 32 ደርሷል! ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተገናኘ የ5 ኢትዮጵያውያን ህይወት አልፏል። በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ የተገኘባቸውና ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር ሰላሳ ሁለት (32
በኢትዮጵያ የሟቾች ቁጥር 32 ደርሷል! ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተገናኘ የ5 ኢትዮጵያውያን ህይወት አልፏል። በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ የተገኘባቸውና ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር ሰላሳ ሁለት (32) ደርሷል። ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ዝርዝር ሁኔታ ፦ 1. የ42 ዓመት ኢትዮጵያዊት የአዲስ አበባ ነዋሪ ፤ በህክምና ማዕከል ህክምና ላይ የነበረች። 2. የ40 ዓመት ኢትዮጵያዊ የአዲስ አበባ ነዋሪ፤በህክምና ማዕከል ህክምና ላይ የነበረች። 3. የ32 ዓመት ኢትዮጵያዊት የአዲስ አበባ ነዋሪ ፤ በአስክሬን ምርመራ ቫይረሱ የተገኘባት። 4. የ40 ዓመት ኢትዮጵያዊ የአዲስ አበባ ነዋሪ፤ በአስክሬን ምርመራ ቫይረሱ የተገኘበት። 5. የ85 ዓመት ኢትዮጵያዊት የአዲስ አበባ ነዋሪ፤ በጤና ተቋም በህክምና ላይ የነበሩ።

በኢትዮጵያ ተጨማሪ 190 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ! ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 4,599 የላብራቶሪ ምርመራ 190 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራች
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 190 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ! ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 4,599 የላብራቶሪ ምርመራ 190 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 2,336 ደርሷል። ቫይረሱ የተገኘባቸው 135 ወንድ እና 55 ሴት ሲሆኑ የዕድሜ ክልላቸው ከ1 እስከ 89 ዓመት ውስጥ ይገኛል። በዜግነት ሁሉ። ኢትዮጵያውያን ናቸው። ቫይረሱ የተገኘባቸው 153 ሰዎች ከአዲስ አበባ፣ 16 ሰዎች ከኦሮሚያ ክልል፣ 10 ሰዎች ከአማራ ክልል፣ 3 ሰዎች ከሐረሪ ክልል፣ 3 ሰዎች ከሶማሌ ክልል፣ 3 ሰዎች ከደቡብ ክልል እንዲሁም 2 ሰዎች ከትግራይ ክልል ናቸው። ተጨማሪ መረጃ ፦ በትላንትናው ዕለት አስራ ስምንት (18) ሰዎች (11 ከአዲስ አበባ፣ 5 ከአማራ ክልል፣ 2 ከሱማሌ ክልል) ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 379 ደርሷል።

"በኢትዮጵያ ተጨማሪ 190 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል፤ የ5 ሰዎች ህይወት አልፏል።" - ዶክተር ሊያ ታደሰ @ethiocheck

ጆርጅ ፍሎይድን አንገቱን በጉልበቱ ለዘጠኝ ደቂቃ ተጭኖ የገደለው ፖሊስ ፍርድ ቤት ቀረበ! ጆርጅ ፍሎይድን አንገቱን በጉልበቱ ለዘጠኝ ደቂቃ ተጭኖ የገደለው ፖሊስ ዴሪክ ቾቪን የሰው ህይወት በማጥፋት
ጆርጅ ፍሎይድን አንገቱን በጉልበቱ ለዘጠኝ ደቂቃ ተጭኖ የገደለው ፖሊስ ፍርድ ቤት ቀረበ! ጆርጅ ፍሎይድን አንገቱን በጉልበቱ ለዘጠኝ ደቂቃ ተጭኖ የገደለው ፖሊስ ዴሪክ ቾቪን የሰው ህይወት በማጥፋት ወንጀል ፍርድ ቤት ቀርቧል። በትላንትናው ዕለት በኢንተርኔት አማካኝነት በተደረገና አስራ አምስት ደቂቃ በፈጀው የፍርድ ሂደት ላይ አንድም ቃል ያልተነፈሰ ሲሆን እጁ በሰንሰለት ታስሮ ብርቱካናማ የመለዮ ልብስ አጥልቆ አነስ ባለች ጠረጴዛ ትይዩ ተቀምጦ ነበር። ዳኛዋ ጂኒስ ኤም የጆርጅ ፍሎይድን ቤተሰቦች በምንም መንገድ እንዳያገኝ፣ የጦር መሳሪያውን እንዲያስረክብና የፍርድ ሂደቱም እስኪጠናቀቅ ከፀጥታ ኃይል አባልነቱ እንዲሰናበት የሚሉ ቅድመ ሁኔታዎችን በማስቀመጥ 1.25 ሚሊዮን ዶላር የገንዘብ ዋስ እንዲያቀርብ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል። ጠበቃውም የገንዘብ ዋሱን አልተቃወሙም። ፖሊሱ ሶስት ክሶች የቀረቡበት ሲሆን እነዚህም ያልታሰበበት ሁለተኛ ደረጃ ነፍስ ማጥፋት፣ ሦስተኛ ደረጃ ነፍስ ማጥፋት እንዲሁም ለግድያ ማድረስ የሚሉ ሲሆን፤ በእነዚህም ወንጀሎች ጥፋተኛ ሆኖ ከተገኘ በያንዳንዳንዳቸው 40፣ 25ና አስር ዓመት የተቀመጠው ከፍተኛ ቅጣት ተፈፃሚ ይሆንበታል። ፍርድ ቤቱም ለሰኔ 22/2012 ቀነ ቀጠሮ ሰጥቷል። #BBC

ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ በህዳሴው ግድብ ላይ የጀመሩትን የሶስትዮሽ ውይይት ሊቀጥሉ ነው በሱዳን ጋባዥነት ዛሬ በኢንተርኔት የቪዲዮ ኮንፈረንስ አማካኝነት እንዲካሄድ ቀጠሮ በተያዘለት በዚህ ውይይት
ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ በህዳሴው ግድብ ላይ የጀመሩትን የሶስትዮሽ ውይይት ሊቀጥሉ ነው በሱዳን ጋባዥነት ዛሬ በኢንተርኔት የቪዲዮ ኮንፈረንስ  አማካኝነት እንዲካሄድ ቀጠሮ በተያዘለት በዚህ ውይይት የአሜሪካ፣ የደቡብ አፍሪካ እና የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ታዛቢዎች ይሳተፋሉ ተብሏል።  በውይይቱ ላይ በህዳሴው ግድብ ድርድር እስካሁንም እልባት ያልተደረሰባቸው ጉዳዮች በአጀንዳነት እንደሚቀርቡ የሱዳን ዜና አገልግሎት (ሱና) ምሽቱን ዘግቧል። ሶስቱ ሀገራት ከታዛቢዎች ሚና ጋር በተያያዙ የአካሄድ ጉዳዩችም ላይ ይወያያሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የዜና ወኪሉ በዘገባው ጠቅሷል።  #EthiopiaInsider