en
Feedback
AIRDROP ROOM

AIRDROP ROOM

Open in Telegram
2 485
Subscribers
No data24 hours
-157 days
-5230 days
Posts Archive
የፌደሬሽን ምክር ቤት... ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም በጠሩት የምክር ቤቱ መደበኛ ሰብሰባ ዋዜማ የመልቀቂያ ውሳኔ መስጠታቸው ተገቢነት የሌለውና የብሔር ብሔረሰቦችን ሃላፊነትን ከግምት ያላስገባ መሆኑን የ
የፌደሬሽን ምክር ቤት... ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም በጠሩት የምክር ቤቱ መደበኛ ሰብሰባ ዋዜማ የመልቀቂያ ውሳኔ መስጠታቸው ተገቢነት የሌለውና የብሔር ብሔረሰቦችን ሃላፊነትን ከግምት ያላስገባ መሆኑን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አስታወቀ። አፈ-ጉባዔዋ ዛሬ በመገናኛ ብዙሃን ልዩነታቸውን ቢናገሩም ምክር ቤቱ ምንም አይነት የጽሁፍም ሆነ የሃሳብ ልዩነት እንዳልነበራቸው ገልጿል። ጉባዔ ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም ከሃላፊነት መልቀቃቸውን ይፋ ማድረጋቸውን ተከትሎ የምክር ቤቱ ምክትል አፈ-ጉባኤን ጨምሮ የምክር ቤቱ የስራ ሃላፊዎች በጉዳዩ ላይ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። ምክትል አፈ ጉባኤው አቶ መሃመድ ረሽድ ሀጂ እንዳሉት አንድ የምክር ቤት አባል መልቀቂያ ሲያስገባ የራሱ የሆነ ደንብና ስርዓት ቢኖረውም የአፈ-ጉባዔዋ ውሳኔ ግን ከዚህ ያፈነገጠ እንደሆነ ገልጸዋል። እስካለፈው ሐሙስ ድረስ የምክር ቤቱን መደበኛ ስብሰባ ተገኝተዋል፤ በመጪው ሰኔ 3 ቀን 2012 ዓም ደግሞ ራሳቸው በደብዴቤ ስብሰባ መጥራታቸውንና በቀረቡ አጃንዳዎች ላይ ምንም ልዩነት እንዳልነበራቸው ገልጸዋል። አፈጉባኤዋ ጥያቄዎቸ ቢኖረቸው እንኳን ለምክር ቤቱ ማቅረብ እንደነበረባቸው ገልጸው፤ የምክር ቤቱን መደበኛ ስብሰባ ለማድረግ አስተባባሪ ኮሚቴው ሳያውቅ በሚዲያ መናገራቸው ትክክለኛ ውሳኔ አይደለም ብለዋል። በአፈጉባኤዋ መልቀቅም በቀጣይ በምክር ቤቱ አጀንዳዎችና መደበኛ ስራውን የሚያስተጓጉል ሂደት እንደሌለ ገልጸው ሁሉም ጉዳዮች በቂ ቅድመ ዝግጅት ስለተደረገባቸው ይካሄዳሉ ብለዋል። ወይዘሮ ኬሪያ ራሳቸው በጠሩት ስብሰባ ዋዜማ መልቀቃቸው፣ የፓርቲ ወገንተኝነታቸውን ከብሄር ብሄረሰብ ተወካይነታቸውን ያሳነሰ ተገቢነት የሌለው ውሳኔ ነው ሲሉም ተናግረዋል። #ኢዜአ

⬆️ #EthioCheck Exclusive በኤልያስ መሰረት (Ethiopia Check) "አንድ በኤርትራ የትጥቅ ትግል ወቅት ትልቅ ስፍራ የነበረው ግለሰብ ወንድሜ ኮ/ል በዛብህ በህይወት እንዳለ እና በአይኑ እንዳየው ከአራት ወይም አምስት አመት በፊት ገደማ ነግሮኛል። በማይታወቁ ሰዎች ከሚፃፍ ፅሁፍ ይልቅ የአይን እማኝ ባምን እመርጣለሁ"--- ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ "ገፁ ከኤርትራ መንግስት ጋር የተያያዘ ስላልሆነ ሌሎች በፃፉት ዙርያ አስተያየት ለመስጠት እቸገራለሁ"--- አንድ ከፍተኛ የኤርትራ ባለስልጣን "Eritrean Press" የተባለ የፌስቡክ ገፅ ትናንት ይዞት የወጣ አንድ ፅሁፍ ላይ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት መጀመርያ አካባቢ ተዋጊ ጀት ሲያበሩ ጀታቸው ተመትቶ የጦር ምርኮኛ ሆነው የነበሩት ኮ/ል በዛብህ ጴጥሮስ ከአመታት በፊት ህይወታቸው እንዳለፈ ፅፎ ነበር። ይህንን ተከትሎ የኮ/ል በዛብህ ወንድም የሆኑትን ፕ/ር በየነ ጴጥሮስን ለቤተሰብ የደረሰ መረጃ ይኖር ይሆን ብዬ ማምሻውን አናግሬያቸው ነበር። ፕ/ር በየነ በጉዳዩ ዙርያ በተደጋጋሚ ከኤርትራ የሚወጡ የሀሰት መረጃዎች እንዳሉ ጠቁመው "ይህ የተለመደ ነው። በየስድስት ወሩ ግዜ እየጠበቁ ስለ ወንድሜ ኮ/ል በዛብህ ጴጥሮስ የሚነዙት ወሬ ቤተሰብን ከማሸበር ያለፈ ጥቅም የለውም" ብለዋል። አክለውም "ይህ አሁን ተፃፈ የተባለው የአይን እማኞች ከነገሩኝ የተለየ ነው። እንደውም አንድ በሀገሪቱ የትጥቅ ትግል ወቅት ትልቅ ስፍራ የነበረው ግለሰብ ወንድሜ ኮ/ል በዛብህ በህይወት እንዳለ እና በአይኑ እንዳየው ከአራት ወይም አምስት አመት በፊት ገደማ ነግሮኛል። በማይታወቁ ሰዎች ከሚፃፍ ፅሁፍ ይልቅ የአይን እማኝ ባምን እመርጣለሁ" ብለዋል። ለፕ/ር በየነ ጉዳዩ በመንግስት ደረጃ በቅርቡ ተነስቶ ይሆን ብዬ ላቀረብኩላቸው ጥያቄ ሲመልሱ "በመሪ ደረጃ መነሳቱን እንጃ፣ ታች ባሉ ባለስልጣናት በኩል ግን ተነስቶ ነበር። የሰማሁት በጉዳዩ ላይ መነጋገር እንደማይፈልጉ ነው። ጠበቅ ተደርገው ሲጠየቁ የኮ/ል በዛብህ ጉዳይ የባለስልጣናት ጉዳይ ሳይሆን የኤርትራ ህዝብ ጉዳይ ነው እንደሚሉ ሰምቻለሁ" ብለዋል። "ይህ በየግዜው የሚመጣ ወሬ ሰላም እየነሳን ነው፣ ቤተሰብም እያሸበረ ነው" ብለዋል ፕ/ር በየነ። በጉዳዩ ዙርያ አንድ ከፍተኛ የኤርትራ ባለስልጣንን መረጃ ጠይቄ "ያልከውን ፅሁፍ አላየሁትም። ቢሆንም ገፁ ከኤርትራ መንግስት ጋር የተያያዘ ስላልሆነ ሌሎች በፃፉት ዙርያ አስተያየት ለመስጠት እቸገራለሁ" ብለው መልስ ሰጥተውኛል። @Ethiocheck

photo content

ከዩኒቨርሲቲ ሲመለሱ የታገቱ ተማሪዎችን አስመልክቶ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ! የደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለምክር ቤቱ በሰጡት ማብራሪያ ጠለፋውን
ከዩኒቨርሲቲ ሲመለሱ የታገቱ ተማሪዎችን አስመልክቶ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ! የደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለምክር ቤቱ በሰጡት ማብራሪያ ጠለፋውን ያቀነባበሩ፣ ያስተባበሩ እና ያሳለጡ በርካታ ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተማሪዎቹ እገታ “ተራ እገታ” ነው ለማለት ያስቸግራል ያሉ ሲሆን መጀመሪያ ታግቼ ነበር ብላ የተፈታችው ልጅን ጨምሮ የሌሎች ተማሪዎችንም ዶክመት የያዘ ግለሰብ በአሰሳ መገኘቱንም ጠቁመዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ “የመከላከያ ሰራዊት እና የፌዴራል ፖሊስ አባላት በአካባቢው ሁሉም ቀበሌዎች ከፍተኛ አሰሳ አድርገዋል፤ ተማሪዎቹ አሉ በተባሉበት ሁሉ በተደረገ አሰሳ ተማሪዎቹን በአካል ለማግኘት አልተቻለም፤ የሞተ ሰውም አንድም ሪፖርት የለም፤ ኃላፊነት የወሰደ አንድም አካልም የለም” ብለዋል። “በቴክኒክ መረጃ የተማሪዎች ስልክ አማራ ክልል ሲገኝ፣ ጠፍቶ ደግሞ ቤኒሻንጉል ክልል ይገኛል፣ ቤኒሻንጉል ክልል ሲፈለግ ደግሞ ጠፍቶ ኦሮሚያ ክልል ይገኛል፤ ይህም እንቅስቃሴ መኖሩን ያሳያል” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። የትኛውም ኃይል በጠለፋው ላይ ኃላፊነትን አልወሰደም፡፡ ነገር ግን፣ በምርመራው ሂደት ከክስተቱ ጋር ተያያዥነት ኖሯቸው የተገኙ ሰዎች ተይዘዋል፡፡ ተማሪዎቹን ለማስመለስ የሚደረገው ጥረት እንደ ቀጠለ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የፌደራል መንግሥት ይህንን ጉዳይ ለመፍታት አስፈላጊውን ሁሉ ከማድረግ ወደ ኋላ አለማለቱንም ጨምረው ገልፀዋል፡፡ -#EBC

የትግራይ ክልል ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዕ/ቤት ከደቂቃዎች በፊት እንደገለፀው የፌዴሬሽን ም/ቤት አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም ከስራቸው በፍቃዳቸው ለቀዋል! ሙሉ መግለጫው ⬇️ ወ/ሮ ከይርያ ኢብራሂም
የትግራይ ክልል ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዕ/ቤት ከደቂቃዎች በፊት እንደገለፀው የፌዴሬሽን ም/ቤት አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም ከስራቸው በፍቃዳቸው ለቀዋል! ሙሉ መግለጫው ⬇️ ወ/ሮ ከይርያ ኢብራሂም ብፍቓደን ካብ ኣፈ ጉባኤነት ቤት ምኽሪ ፌደሬሸን ለቒቐን። ወ/ሮ ከይርያ ኢብራሂም ሰልጣነን በገዛ ፍቓደን ዝለቐቓ ሕገ መንግሰቲ ምሰ ዝጥሕስን ውልቀ ምልክነት ምሰ ዘሰጉም ጉጅለ ሓቢረን ንምሰራሕ ፍቓደኛ ብዘይ ምኳነን ገሊፀን ሙሉእ መግለፂ ድሕሪ ሒደት ሰዓት ክነቕረብ እዩ። ቢሮ ርክብ ህዝብን መንግስትን ክልል ትግራይ መቐለ፡ 01 ሰነ 2012 ዓ/ም ፍልፍል፡ ቴሌቪዥን ትግራይ

#TIGRAY በትግራይ ክልል በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው የተረጋገጠ ሰዎች ቁጥር ሰባ ዘጠኝ (79) ደርሷል። ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ የተደረገው 207 የላብራቶሪ ምርመራ ሲሆን ከነዚህ መካከል ነው ሰባ
#TIGRAY በትግራይ ክልል በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው የተረጋገጠ ሰዎች ቁጥር ሰባ ዘጠኝ (79) ደርሷል። ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ የተደረገው 207 የላብራቶሪ ምርመራ ሲሆን ከነዚህ መካከል ነው ሰባት (7) ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠው። ከሰባቱ (7) መካከል ሁለቱ (2) የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ ያላቸው ፣ ሶስቱ (3) ሰዎች በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር የታወቀ ግንኙነት (ንክኪ) ያላቸው እንዲሁም የተቀሩት ሁለቱ (2) የውጭ ሀገር ጉዞ ታሪክና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት የሌላቸው ናቸው።

#Oromiyaa ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ የተከናወነው የላብራቶሪ ምርመራ 519 ሲሆን ከእነዚህ መካከል ነው ዘጠኝ (9) ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው የተረጋገጠው። የታማሚዎች ዝርዝር ሁኔታ ፦ ታማ
#Oromiyaa ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ የተከናወነው የላብራቶሪ ምርመራ 519 ሲሆን ከእነዚህ መካከል ነው ዘጠኝ (9) ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው የተረጋገጠው። የታማሚዎች ዝርዝር ሁኔታ ፦ ታማሚ 1 - የ60 ዓመት ኢትዮጵያዊት የምስራቅ ሀረርጌ ነዋሪ ፤ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ #የሌላቸው፤ በለይቶ ማቆያ የሚገኙ። ታማሚ 2 - የ10 ዓመት ኢትዮጵያዊት የምስራቅ ሀረርጌ ነዋሪ ፤ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ #የላትም፤ በለይቶ ማቆያ የምትገኝ። ታማሚ 3 - የ25 ዓመት ኢትዮጵያዊት የምስራቅ ሀረርጌ ነዋሪ ፤ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ #የላትም፤ በለይቶ ማቆያ የምትገኝ። ታማሚ 4 - የ12 ዓመት ኢትዮጵያዊት የምስራቅ ሀረርጌ ነዋሪ ፤ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ #የላትም፤ በለይቶ ማቆያ የምትገኝ። ታማሚ 5 - የ42 ዓመት ኢትዮጵያዊ የሰንዳፋ ቤኬ ነዋሪ ፤ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ #የለውም ፤ በለይቶ ማቆያ የሚገኝ። ታማሚ 6 - የ3 ዓመት ህፃን ኢትዮጵያዊ የጉጂ ነዋሪ ፤ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ #የለውም፤ በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት ያለው። ታማሚ 7 - የ14 ዓመት ኢትዮጵያዊት የጉጂ ነዋሪ ፤ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ #የላትም፤ በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት ያላት። ታማሚ 8 - የ25 ዓመት ኢትዮጵያዊ የምዕራብ ወለጋ ነዋሪ ፤ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ #የለውም፤ ከማህበረሰቡ የተገኘ። ታማሚ 9 - የ48 ዓመት ኢትዮጵያዊ የአዲስ አበባ ነዋሪ፤ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ ያለው ድንበር ተሻጋሪ መኪና አሽከርካሪ (ምርመራው የተደረገው ነቀምቴ ላብራቶሪ ነው)

በኢትዮጵያ ተጨማሪ 136 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ! ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 4,775 የላብራቶሪ ምርመራ 136 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይ
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 136 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ! ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 4,775 የላብራቶሪ ምርመራ 136 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 2,156 ደርሷል። ቫይረሱ የተገኘባቸው 85 ወንድ እና 51 ሴት ሲሆኑ የዕድሜ ክልላቸው ከ1 እስከ 97 ዓመት ውስጥ ይገኛል። በዜግነት 124 ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ 12 የውጭ ዜጎች ናቸው። ቫይረሱ የተገኘባቸው 115 ሰዎች ከአዲስ አበባ፣ 9 ሰዎች ከኦሮሚያ ክልል፣ 7 ሰዎች ከትግራይ ክልል፣ 2 ሰዎች ከሐረሪ ክልል፣ 2 ሰዎች ከሶማሌ ክልል እና 1 ሰው ከደቡብ ክልል ናቸው። ተጨማሪ መረጃ ፦ በትላንትናው ዕለት አስራ ሰባት (17) ሰዎች (8 ከአዲስ አበባ፣ 5 ከአማራ ክልል፣ 2 ከአፋር ክልል እና 2 ከቢኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል) ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 361 ደርሷል።

“ከ300 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንቦጭን ለመከላከል የሚረዳ ማሽን ከአውሮፓ ለመግዛት በመደራደር ላይ ነው”፡- ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እንቦጭን በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲያብራሩ አረሙን ለማ
“ከ300 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንቦጭን ለመከላከል የሚረዳ ማሽን ከአውሮፓ ለመግዛት በመደራደር ላይ ነው”፡- ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እንቦጭን በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲያብራሩ አረሙን ለማጥፋት ከአጭር ጊዜ መፍትሄ ይልቅ በረጅም ጊዜ እና በዘላቂ መፍትሄ ላይ ማተኮር እንደሚገባ ገልፀዋል። - የፌደራል መንግስት እንቦጭን ለመከላከል የሚረዳ፣ ከ300 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚጠይቅ የተሻለ ማሽን ከአውሮፓ ለመግዛት በመደራደር ላይ መሆኑንም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታውቀዋል። - በማሽን እና በሰው ሀይል የሚደረግ እንቦጭን የመከላከል ሂደት ጊዜያዊ መፍትሄ ብቻ የሚያመጣ በመሆኑ በዘላቂነት የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች ላይ በማተኮር መፍትሄ ማምጣት ይቻላል። - ዘንድሮ የሚተከሉት 5 ቢሊዮን ችግኞች እንቦጭን በዘላቂነት ለማጥፋት ዋነኛ መፍትሄ መሆኑንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልፀዋል። - የአጭር ጊዜ የመከላከያ መንገዱ በሰው ሀይል እና በማሽን በመታገዝ ለማሶገድ መሞከር ነው፤ ነገር ግን ይህኛው መንገድ ዘላቂ መፍትሄ አያመጣም። የረጅም ጊዜ የመከላከያ መንገዱ ደግሞ የአካባቢ ጥበቃ ስራ መስራት ነው። - የጉና ተራራ ጣናን እና ተከዜን የሚመግቡ ወንዞች መነሻ ነው፤ በተራራው ዙሪያ የሚገኙ አርሶ አደሮች፣ ተራራው የነበረውን ደን እያጣ በመምጣቱ ምክንያት በተለይ በፎገራ አካባቢ ያሉ አርሶ አደሮች በጎርፍ ይጠቃሉ፣ ለም መሬታቸው እና የተጠቀሙት ማዳበሪያ ታጥቦ ተወስዶ ለጣና ሀይቅ እንቦጭ ምግብ ይሆናል። -የክልሉ መንግስት ችግሩን አስመልክቶ በማሽኖች እና በሰው ሀይል እንቦጭን ለመከላከል ከሚያደርገው ጥረት ባሻገር በጉዳዩ ላይ እየመከረም ይገኛል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። #EBC

"ንጋት" አዲስ የሙዚቃ አልበም በአውታር መተግበሪያ ገበያ ላይ ውሏል!! ይህ የአልበም ሥራ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ጥቃት ለመመከትና የሃገር ዝግጁነትን ለመደገፍ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ዘርፍ ማህበራት ህብረት በአዲስ አበባ የከንቲባ ቢሮ በኩል ለኢትዮጵያ ህዝብ ያበረከተው ስጦታ መሆኑን አውታር መልቲሚዲያ ጠቅሷል። አውታር መልቲሚዲያም ይሄን ስጦታ ለህዝብ ሲያቀርብ ከዚህ የሙዚቃ ስራ ምንም ዓይነት ትርፍ የማያገኝና የሚገኘውን ገቢ ሙሉ ለሙሉ ለአላማው እንዲውል የሚያደርግ ሲሆን፣ ይሄም የሙዚቃ ስራ ገበያ ላይ በአልበም 30 ብር፣ በነጠላ ሙዚቃ 5 ብር የኢትዮጵያ ብር የሚሸጥ ይሆናል። መላው የሙዚቃ አፍቃሪም እራሱንና እና በቅርብ ያሉትን ወዳጆቹን ከኮቪድ 19 በሽታ እየጠበቀ፣ ይሄን ለተከበረ ዓላማ የሚውለውን የሙዚቃ አልበም በመግዛት ከሙዚቃ ባለሙያዎቹ ጎን እንዲቆም አውታር መልቲሚዲያ ይጋብዛል። Via:- #AwtarMultimedia @ethiocheck

photo content

#FactCheck ማስተንፈሻ ያላቸው ማስኮች ጉዳይ! በጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት (Ethiopia Check) ሰሞኑን "ከፊታቸው ማስተንፈሻ ያላቸው ማስኮች ለባሹን የሚከላከሉ ሲሆን በዙርያው ያሉ ሰዎችን ግን ያጋልጣሉ" የሚሉ መልእክቶች በስፋት ሲሰራጩ ነበር። በጉዳዩ ዙርያ ለጤና ሚኒስቴር እና ለአንድ ባዮ-ሜዲካል ኢንጅነር ጥያቄ አቅርቤ ነበር። የሁለቱም ሀሳብ ሲጨመቅ ይህን ይመስላል: "ማስተንፈሻ ያላቸው ማስኮች ማስተንፈሻ ከሌላቸው ማስኮች ጋር ተመሳሳይ ሊባል የሚችል መከላከል ለተጠቃሚው (ለለባሹ) ይሰጣሉ። ማስተንፈሻው መኖሩ ደግሞ አተነፋፈስን ቀላል ያደርጋል። ነገር ግን እንዲህ አይነት ማስኮች ከትንፋሽ የሚወጣው አየር ሳይጣራ ወደ ውጪ እንዲወጣ ያደርጋሉ፣ ስለዚህ ለምሳሌ ያህል በኦፕሬሽን ግዜ እንዲደረጉ አይመከሩም። ከኮሮና ቫይረስ ጋር ይህን ስናያይዘው ደግሞ እነዚህ ማስተንፈሻ ያላቸው ማስኮች የሚመከሩት ናሙና የሚወስዱ ሰዎች እንዲጠቀሙት ነው። በአጭሩ ህዝብ እንዲጠቀመው አይመከርም።" ስለዚህ "የራስ ወዳዶች ጭምብል" ወይም "The selfish mask" መባሉ ትክክል ቢመስልም ብዙ ሰው ግን ጉዳዩ እንደዚህ መሆኑን አውቆ ያረገው አይመስለኝም። እውነታው ግን ይህን ይመስላል። @EthioCheck

photo content

በኢትዮጵያ ዘጠኙ ክልሎች እና በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች ያለው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት እንደሚከተለው ቀርቧል ፦ • አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር - 1,510 ሰዎች • ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር - 11 ሰዎች • አማራ ክልል - 119 ሰዎች • ኦሮሚያ ክልል - 116 ሰዎች • ሶማሌ ክልል - 113 ሰዎች • ትግራይ ክልል - 72 ሰዎች • አፋር ክልል - 34 ሰዎች • ደቡብ ክልል - 24 ሰዎች • ሐረሪ ክልል - 14 ሰዎች • ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል - 4 ሰዎች • ጋምቤላ ክልል - 1 ሰው @ethiocheck

photo content

በአዲስ አበባ ከተማ የመሰረት ድንጋይ ተቀምጦላቸው ግንባታቸው ያልተጀመሩ ሁለት (2) ዘመናዊ ሆስፒታሎች ግንባታቸው ሊጀመር እንደሆነ ተገልጿል፡፡ ሆስፒታሎቹ ተጠናቀው አገልግሎት መስጠት ሲጀመሩ አሁን
በአዲስ አበባ ከተማ የመሰረት ድንጋይ ተቀምጦላቸው ግንባታቸው ያልተጀመሩ ሁለት (2) ዘመናዊ ሆስፒታሎች ግንባታቸው ሊጀመር እንደሆነ ተገልጿል፡፡ ሆስፒታሎቹ ተጠናቀው አገልግሎት መስጠት ሲጀመሩ አሁን ያለውን የከተማዋ ሆስፒታሎች አቅም በእጥፍ እንደሚያሳድገው የከተማዋ የጤና ቢሮ ገለጿል @ethiocheck

⬆️ #FactCheck ገበያ ላይ የሚቸበቸቡት አንዳንድ N95, KN95 እና Surgical Mask የተባሉት የፊት መሸፈኛዎች አመጣጣቸው ከየት ይሆን? በጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት (via Ethiopia Check) N95, KN95 እና Surgical Mask የተባሉት የፊት መሸፈኛ ማስኮች በየመንገዱ ጭምር በብዛት ሲሸጡ እያየን እንገኛለን። ነገር ግን በጤና ተቋማት የእነዚህ ማስኮች እና ሌላ ተዛማጅ ቁሶች እጥረት እንዳለ እንሰማለን። ታድያ አመጣጣቸው ከየት ይሆን? በደረሰኝ ተከታታይ ጥቆማ መሰረት ከአንዳንድ የጤና ተቋማት (በተለይ ሆስፒታሎች) ውስጥ እነዚህ ማስኮች ሀላፊነት በጎደላቸው ሰዎች እየወጡ እየተሸጡ ይገኛሉ። አንድ ጉዳዩን የሚያውቅ ግለሰብ እንዳለው "ለምሳሌ ከማውቀው አንድ ሪፈራል ሆስፒታል ውስጥ N95, KN95, Surgical Mask የሚባሉትን የአፍና አፍንጫ መሸፈኛዎችን በድብቅ እያወጡ በርካሽ የሚሸጡ አሉ። ለምሳሌ ፋርማሲ ውስጥ Surgical Mask የሚሸጠው በ25 ብር ሲሆን ሰራተኞቹ በ15 ብር እያወጡ ይሸጣሉ። N95 እና KN95 ማስክ ደግሞ ገበያ ላይ ከ150 እስከ 200 ብር የሚሸጥ ሲሆን እነዚህ ሰራተኞች ግን ከ40 እስከ 50 ብር እየሸጡት ይገኛሉ" ብሏል። ሌላኛው በአንድ ሆስፒታል ውስጥ የሚሰራ ባለሙያ ደግሞ "ገበያ ላይ የምናያቸው እና ለጤና ባለሙያዎች ተብለው የሚሰሩ ማስኮች ምንጫቸው ሙሉ በሙሉ ከጤና ተቋማት ነው ብለን ደፍረን መናገር ባንችልም ሾልከው በብዛት እየወጡ እንዳሉ እርግጥ ነው። መንግስት ምንጫቸውን ማጣራት ሊያደርግ ይገባል" ብሏል። "ጉዳዩን ታውቁት ይሆን?" ብዬ የጠየቅኳቸው አንድ የክልል ከፍተኛ የጤና ሀላፊ "እኛ የምናውቀው የጤና ተቋማት የማስክ እና ተዛማጅ ቁሶች እጥረት አለብን ብለው ለኛ ሪፖርት ማድረጋቸውን ነው። እጥረት አለብን ብለው በሌላ በኩል ወጥቶ እንዲሸጥ የሚያደርጉ ከሆነ ግን አስተማሪ እርምጃ እንወስዳለን" ብለዋል። የጤና ሚኒስቴር በቅርቡ እንዳስታወቀው በመጪዎቹ አራት ወራት 131 ሚሊዮን የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ እንደሚያስፈልገው በቅርቡ ገልፆ ነበር። @Ethiocheck