en
Feedback
AIRDROP ROOM

AIRDROP ROOM

Open in Telegram
2 485
Subscribers
No data24 hours
-157 days
-5230 days
Posts Archive
የአቶ ጃዋር መሐመድ የዋስትና ጥያቄ ውድቅ ተደረገ መርማሪ ፖሊስ በአቶ ጃዋር መሐመድ ላይ ሲያካሂድ የነበረውን ምርመራ ማጠናቀቁን በመግለጽ፤ ዐቃቤ ሕግ በተጠርጣሪው ላይ የቀዳሚ ምርመራ መዝገብ እንደ
የአቶ ጃዋር መሐመድ የዋስትና ጥያቄ ውድቅ ተደረገ መርማሪ ፖሊስ በአቶ ጃዋር መሐመድ ላይ ሲያካሂድ የነበረውን ምርመራ ማጠናቀቁን በመግለጽ፤ ዐቃቤ ሕግ በተጠርጣሪው ላይ የቀዳሚ ምርመራ መዝገብ እንደከፈተባቸው አስታውቋል። በመሆኑም የምርመራ መዝገቡ እንዲዘጋ ጠይቋል። የተጠርጣሪው ጠበቃ በበኩላቸው በደንበኛቸው ላይ ፖሊስ ባካሄደው የምርመራ ስራ ያገኘው ውጤት ዋስትና የማያስከለክል በመሆኑ የዋስ መብታቸው እንዲጠበቅ ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል። ጉዳዩን የመረመረው ፍርድ ቤቱ ተጠርጣሪው ወደ ፊት ክስ የሚመሰረትባቸው ከሆነ የተጠረጠሩበት መዝገብ የሰው ህይወት የጠፋበትና ከ15 ዓመታት በላይ ሊያስቀጣ የሚችል በመሆኑ የዋስትና ጥያቄውን ውድቅ አድርጎታል። ተጠርጣሪው ስልጣን ላለው ፍርድ ቤት መብታቸውን መጠየቅ እንደሚችሉ ትዕዛዝ በመስጠት መዝገቡን ተዘግቷል። @ethiocheck

በወላይታ 21 ሰዎች መገደላቸውን የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር ተናገሩ! (በዶይቸ ቨለ) በወላይታ ዞን በተቀሰቀሰው ተቃውሞ 21 ሰዎች መገደላቸውን እና ከ105 በላይ መቁሰላቸውን እንዳረጋገጡ የወላይታ ብሔ
በወላይታ 21 ሰዎች መገደላቸውን የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር ተናገሩ! (በዶይቸ ቨለ) በወላይታ ዞን በተቀሰቀሰው ተቃውሞ 21 ሰዎች መገደላቸውን እና ከ105 በላይ መቁሰላቸውን እንዳረጋገጡ የወላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አንዱዓለም ታደሰ ለዶይቼ ቬለ ገልጹ።የደቡብ ክልል የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አለማየሁ ባውዲ "አምስት ሰዎች ሕይወታቸው አልፏል፤ አስራ አምስት ጉዳት ደርሶባቸዋል" ብለዋል።በወላይታ ዞን በተቀሰቀሰው ተቃውሞ 21 ሰዎች መገደላቸውን እና ከ105 በላይ መቁሰላቸውን እንዳረጋገጡ የወላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አንዱዓለም ታደሰ ለዶይቼ ቬለ ገልጹ።የጸጥታ አስከባሪዎች በዞኑ ሰዎች በጅምላ ማሰር መጀመራቸውን የገለጹት አቶ አንዱዓለም በሶዶ እና በአካባቢው ወታደሮች በብዛት መሰማራታቸውን አክለዋል።እንደ አቶ አንዱዓለም ከሆነ "መንገዶች፣ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች" ተዘግተዋል። የዐይን እማኞች እንደሚሉት የዞኑ ባለሥልጣናትን ጨምሮ የወላይታ ክልል እንዲመሠረት ግፊት በማድረግ ላይ የሚገኙ የተለያዩ ማሕበረሰቦች ተወካዮች ባለፈው እሁድ መታሰራቸው ከተሰማ በኋላ በተለይ ሶዶ እና ቦዲቲ ከተሞች የበረታ ተቃውሞ ተቀስቅሶባቸዋል።ከአዲስ አበባ 295 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው የቦዲቲ ከተማ የጸጥታ ኃይሎች በትንሹ ስምንት ሰዎች ተኩሰው መግደላቸውን በከተማዋ የሚገኝ የጤና ማዕከል ከፍተኛ ባለሥልጣን የሆኑት ተመስገን ሕሊና ለሬውተርስ ተናግረዋል።ሟቾቹ “ጭንቅላታቸው፣ ሆዳቸው እና ደረታቸው ላይ በጥይት ተመተዋል" ያሉት ተመስገን “የመጀመሪያ ሕክምና የሰጠኋቸው እኔ ነኝ። ከዚያ ሞቱ" ሲሉ ተናግረዋል። እንደ አቶ ተመስገን ከሆነ ከሟቾች መካከል የ14 አመት አዳጊ ይገኝበታል። @ethiocheck

ሩሲያ ከዓለም የመጀመሪያ ያለችውን የኮሮናቫይረስ ክትባት ይፋ አደረገች ሩሲያ ከዓለም የመጀመሪያ ያለችውን የኮሮናቫይረስ ክትባት ይፋ ማድረጓን አስታወቀች የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የሞስኮ
ሩሲያ ከዓለም የመጀመሪያ ያለችውን የኮሮናቫይረስ ክትባት ይፋ አደረገች ሩሲያ ከዓለም የመጀመሪያ ያለችውን የኮሮናቫይረስ ክትባት ይፋ ማድረጓን አስታወቀች የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የሞስኮ ጋማሊያ ኢኒስቲትዩት ከዓለም የመጀመሪያውን የኮሮናቫይረስ ክትባት ጥቅም ላይ ይፋ አድርጓል ብለዋል፡፡ ክትባቱ ለሁለት ወር ያህል በሰው ላይ በሙከራ ደረጃ እንዲሰጥ በማድረግ የሩሲያ የጤና ሚኒስቴር አስፈላጊውን ክትልልና ቁጥጥር በማከናወን ጥቅም ላይ እንዲውል ፈቃድ ሰጥቷል ብለዋል ፕሬዝዳንት ፑቲን፡፡ ክትባቱ በሙከራ ሂደት አስተማማኝ የመከላከል አቅም በማሳየቱ የመጀመሪያው የኮሮናቫይረስ የክትባት መድኃኒት ሆኖ ሩሲያ ጥቅም ላይ እንዲውል መወሰኗን የአገሪቱ ፕሬዝዳንት በቴሌቪዥን ማስታወቃቸውን ዶቼ ቬሌ የእንግሊዝኛው አውታር ዘግቧል፡፡ ይሁንእንጂ በዓለምአቀፍ ደረጃ የኮሮናቫይረስ ክትባቱ ተቀባይነት እንዲኖረው ካስፈለገ የዓለምጤና ድርጅት ይሁንታን ማግኘት ይኖርበታል፡፡ እንደዓለም ጤና ድርጅት መረጃ በአሁኑ ጊዜ ሶስት የሙከራ ሂደትን ያለፉ ተስፋ አዘል የኮሮናቫይረስ ክትባት መድኃኒቶች የምርምር ፕሮጀክቶች 6 ብቻ ናቸው፡፡ @ethiocheck

ከሰሞኑ በወላይታ ዞን የተፈጠረውን አለመረጋጋት ተከትሎ የደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ርስቱ ይርዳው መገለጫ ሰጥተዋል ርዕሰ መስተዳደሩ በመግለጫቸዉ መንግስት ከክልል አደረጃጀት ጋር በተ
ከሰሞኑ በወላይታ ዞን የተፈጠረውን አለመረጋጋት ተከትሎ የደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ርስቱ ይርዳው መገለጫ ሰጥተዋል ርዕሰ መስተዳደሩ በመግለጫቸዉ መንግስት ከክልል አደረጃጀት ጋር በተያያዘ ህግና ስርዓት በሚፈቅደው አግባብ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ቢሆንም በወላይታ አንዳንድ አመራሮች ግን ይህንን ህጋዊ አካሄድ በሚጣረስ መልኩ የሄዱበት ያለው መንገድ በአካባቢው ግጭት እንዲፈጠር ምክንያት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ አመራሮቹ ሀገር የማፍረስ አላማ ካላቸው አካላት ጋር ተቀናጀተው ተልዕኮ በመቀበል እየሰሩ እንደነበርም አመልክተዋል፡፡ መንግስት በአካባቢው የተፈጠረውን ሁኔታ በህግ አግባብ ብቻ የሚፈታው እንደሆነ የገለፁ ሲሆን የአካባቢው ማህበረሰብም ከፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር ሰላምና ደህንነቱን ሊጠበቅ ይገባል ብለዋል በሰጡት መግለጫ፡፡

እነ አቶ ጃዋር መሀመድ ዳኛው ይነሳልን ሲሉ አቤቱታ አቀረቡ! በእነ ጃዋር መሀመድ መዝገብ ላይ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ የቅድመ ምርመራ ምስክሮችን ማሰማት ጀምሮ የነበረ ቢሆንም እነ አቶ ጃዋር ዳኛው ከመዝገባችን ይነሳልን ሲሉ አቤቱታ አቅርበዋል፡፡ችሎቱ በፌደራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት በልደታ አዳራሽ መስማት ተጀምሮ ነበር።ይሁን እንጅ እነ አቶ ጃዋር ዳኛው ከመዝገባችን ላይ ይነሳልን ሲሉ አቤቱታ አቅርበዋል፡፡ ፍርድ ቤቱም አቤቱታውን ተመልክቶ ዳኛው መዝገቡ እንዲመረመርና በመዝገቡ ላይ ትዕዛዝ እስከሚሰጥበት ድረስ ተጠርጣሪዎቹ በማረሚያ ቤት ሆነው እንዲቆዩ እና መጥሪያ ሲደርሳቸው የሚመጡ ይሆናል በማለት ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡መዝገቡም ወደ መዝገብ ቤት እንዲመለስ አዟል፡፡ከዚህ በፊት የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ በዚህ መዝገብ ላይ በአጠቃላይ በተጠርጣሪዎች ላይ የሚመሰክሩ 5 ምስክሮች ከመጋረጃ በስተጀርባ የምስክርነት ቃላቸውን እንዲሰጡ ሲል አቤቱታ ማቅረቡ ይታወሳል።ፍርድ ቤቱም አምስቱ የዐቃቤ ህግ ምስክሮች ከመጋረጃ በስተጀርባ ቃላቸውን እንዲሰጡ ብይን መስጠቱ የሚታወስ ነው። Via FBC @ethiocheck

ቲክቶክ ኩባንያ በኢትዮጵያ ለኮቪድ – 19 ምርመራ የሚውሉ 100 ሺህ ኪቶችን አበረከተ ድጋፉን በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ሚስተር ታን ጅያን ለጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ አስረክበዋል። ዶክተ
ቲክቶክ ኩባንያ በኢትዮጵያ ለኮቪድ – 19 ምርመራ የሚውሉ 100 ሺህ ኪቶችን አበረከተ ድጋፉን በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ሚስተር ታን ጅያን ለጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ አስረክበዋል። ዶክተር ሊያ በተረከቡበት ወቅት እንደገለጹት ድጋፉ አገሪቱ የመመርመር አቅሟን ለመጨመር የምታደርገውን ጥረት የሚያግዝ ነው። በተለይ በነሃሴ ወር ለተጀመረው ማህበረሰብ አቀፍ የምርመራ የንቅናቄ የዛሬው ድጋፍ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለውም ዶክተር ሊያ ተናግረዋል። የቻይና መንግስትና ህዝብ የኮሮናቫይረስ ከተከሰተ ጀምሮ ለኢትዮጵያ እያደረጉት ላለው ድጋፍና አጋርነት ምስጋናቸውን አቅርበዋል። @ethiocheck

#AtoLidetuAyalew በምስራቅ ሸዋ ዞን የቢሾፍቱ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት አቶ ልደቱ አያሌው በህክምና ምክንያት ያቀረቡትን የዋስትና ጥያቄ ውድቅ አድርጓል፤ ለመርማሪ ፖሊስ ለመጨረሻ ጊዜ ምርመራውን አጠናቆ እንዲቀርብ የሰባት ቀን ጊዜ ፈቅዷል። via: fbc @ethiocheck

በወላይታ የዞኑን ከፍተኛ አመራሮች ጨምሮ 26 ግለሰቦች ታሰሩ የወላይታ ዞን ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ ቁጥራቸው 26 የሚሆኑ ግለሰቦች ዛሬ እሁድ ነሐሴ 3፤ 2012 በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የደቡብ ክልል አስታወቀ። የግለሰቦቹን በቁጥጥር ስር መዋል ተከትሎ የዞኑ አስተዳደር መቀመጫ በሆነችው ሶዶ ከተማ ወጣቶች ተቃውማቸውን ሲያሰሙ ማምሸታቸውን እና የጥይት ተኩስም ይሰማ እንደነበር ነዋሪዎች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። የደቡብ ክልል ቴሌቪዥን ጣቢያ የክልሉን ፖሊስ ኮሚሽን እና ጸጥታ ቢሮን ጠቅሶ ምሽቱን ባቀረበው የዜና እወጃ፤ የዞኑ ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ 26 ግለሰቦች ዛሬ ከሰዓት መያዛቸንው ዘግቧል። ጣቢያው የአመራሮቹን ማንነት ግን በዝርዝር አላሳወቀም። በወላይታ በተቃዋሚ ፓርቲነት የሚንቀሳቀሰው የዎላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ (ዎብን) የፓርቲው የአደረጃጀት ጉዳይ ኃላፊ እና የወላይታ ዞን ከፍተኛ አመራሮች መታሰራቸውን ምሽቱን ባወጣው መግለጫ አረጋግጧል። ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ይህን (ሊንክ) ማገናኛ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2020/1532/ @ethiocheck

አቶ ለማ መገርሳ ፣ ዶ/ር ሚልኬሳና ሚደጋ እና ወ/ሮ ጠይባ ሀሰን ከብልፅግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ታገዱ የኦሮሚያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቃል አቀባይ አቶ ታዬ ደንደአ ይህኑ በይፋዊ የፌስቡክ ገጻቸው ላይ አስፍረዋል። ፓርቲው ሰሞኑን በክልሉ የተፈጠረውን ቀውስ በመገምገም ላይ መሆኑ ይታወቃል። @ethiocheck

ሥልጣን የሚለቁ የፓርቲ አባል ያልሆኑ ተሿሚዎች ቁጥር እየጨመረ ነው! (በሪፖርተር የቀረበ) የጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) አስተዳደር የመንግሥት ሥልጣን ከያዘ ጀምሮ በርካታ የፓርቲ አባል ያልሆኑ ኃላፊዎች ቢሾሙም፣ በየጊዜው ከኃላፈነታቸው በመልቀቅ ላይ ይገኛሉ፡፡ከጥቂት ሳምንታት በፊት የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽነር የነበሩት አቶ አበበ አበባየሁ፣ ከኃላፊነታቸው በገዛ ፈቃዳቸው እንደለቀቁ አስታውቀው ነበር፡፡ ይሁንና ከሰሞኑ የሥራ ዕድል ፈጠራ ኮሚሽንን ከጥንስሱ ጀምረው በመሥራች ኃላፊነት የመሩትና በሕክምና ሙያ የሠለጠኑት ኤፍሬም ተክሌ (ዶ/ር) ኃላፊነታቸውን ከለቀቁ ጎራ ተቀላቅለዋል፡፡ላለፉት ሁለት ዓመታት ገደማ ኮሚሽኑን ሲመሩ የቆዩት ኤፍሬም (ዶ/ር)፣ በግል ጉዳይ ምክንያት ለመልቀቅ መገደዳቸውን ይፋ ያደረጉት ሐሙስ ሐምሌ 30 ቀን 2012 ዓ.ም. በትዊተር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት ደብዳቤ ነበር፡፡ ‹‹ውድ የሥራ አጋሮቼና ወዳጆቼ የሥራ ፈጠራ ኮሚሽን ኮሚሽነርነቴን በመተው መልቀቂያ የማስገባቴን ዜና የማካፍላችሁ በተደባለቀ ስሜት ነው፡፡የምለቀውም ሙሉ በሙሉ በግሌ ምክንያት ነው፤›› በማለት ከኃላፊነታቸው መልቀቃቸውን አስታውቀዋል፡፡በሥራ ዕድል ፈጠራ ኮሚሽን ኃላፊነታቸው ወቅትና ከዚያም በፊት በነበረው የመንግሥት አገልግሎት በጠቅላላው ከአሥር ዓመታት ያላነሰ ጊዜ ማሳለፋቸውን ያስታወሱት ኤፍሬም (ዶ/ር)፣ በዚህ ወቅት ቤተሰባቸው ላይ ጫና ማሳደሩን፣ በሥራ ምክንያት ለረዥም ጊዜ ከቤተሰብ ጋር የሚያሳልፉበት ወቅት እምብዛም መሆኑን ጠቃቅሰዋል።ከእሳቸው በፊት የኃላፊነት ቦታቸውን የለቀቁትም ተመሳሳይ ምክንያቶችን አቅርበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽነር የነበሩት አቶ አበበም ተመሳሳይ ይዘት ያለው ሐሳብ ማካፈላቸው ይታወሳል፡፡በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ቅርብ በሆነ ኃላፊነት ቦታ ይሠሩ የነበሩት አቶ አበበ፣ ወደ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን እንዲመጡ የተደረገው የቀድሞው ባልደረባቸው የነበሩት በላቸው መኩሪያ (ዶ/ር) በተመሳሳይ ከኃላፊነት መልቀቃቸውን ማስታወቀቸው ተከትሎ ነበር፡፡በአሁኑ ወቅት ከኃላፊነታቸው ለመልቀቅ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ደብዳቤ ማስገባታቸው ከሚነገርላቸው መካከል፣ የስትራቴጂ ጉዳዮች ኢንስቲዩት ኃላፊ አቶ ሃሌሉያ ሉሌ እንደሚገኙበት የሪፖርተር ምንጮች ገልጸዋል፡፡እንደ ምንጮች ማብራሪያ ከሆነ አቶ ሃሌሉያ መልቀቂያ ካስገቡ ሁለት ወራት አስቆጥረዋል፡፡ ይሁን እንጂ ጥያቄያቸው እንደ ሌሎቹ ወዲያውኑ ተቀባይነት እንዳላገኘ ይነገራል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ለሥራ የማያመቹ ሁኔታዎች እየተፈጠሩ እንደመጡ፣ አንዳንዶችም መስቀል አደባባይ አካባቢ የሚገኘው ጽሕፈት ቤታቸው ብዙ ዕድሳት ተካሂዶበት ለሥራ በሚያመች መንገድ ታድሶ በተዘጋጀበት ወቅት ከመስቀል አደባባይ እስከ ማዘጋጃ ቤት ለሚዘረጋው ፕሮጀክት በጽሕፈት ቤትነት የተወሰደበትን አጋጣሚ በማጣቀስ፣ ለመልቀቃቸው አንዱ ምክንያት ያደርጉታል፡፡ እንዲህ ያሉ ጉዳዮችን በማንሳት ለአቶ ሃሌሉያም ሆነ ለኤፍሬም (ዶ/ር) ጥያቄ ለማቅረብና ምላሾቻቸውን ለማካተት የተረደገው ጥረት አልተሳካም፡፡ሁለቱም ኃላፊዎች በስልክም በአጭር ጽሑፍ መልዕክትም ተጠይቀው ምላሽ አልሰጡም፡፡ከጊዜ ወደ ጊዜ ቁጥራቸው እየተመናመነ የመጡትና የፖለቲካ ፓርቲ አባላት ያልሆኑ የመንግሥት ሹማምንት የስንብት ጉዳይ ጥያቄ እያስነሳ ነው፡፡አንዳንዶቹ ኃላፊዎች የፓርቲ አባል ባለመሆናቸው ምክንያት፣ የፓርቲ አባል በሆኑት ዘንድ የሚነሳባቸው ጥያቄ አለ፡፡ ቢሮክራሲውን ለታማኝ የፖለቲካ ሹማምንት ከማስጠበቅ ባሻገር ከጥቅማ ጥቅምና ከክፍያ ጋር በተያያዘ በፓርቲ አባላት ዘንድ ቅሬታና ስሞታ እንደሚቀርብ የሚገልጹ ወገኖች፣ እየለቀቁ ለሚገኙ ሹመኞች መነሳት አንዱ መንስዔ እንደሆነ ያቀርባሉ፡፡ በሌላ በኩል ከፓርቲና ከፖለቲካ ውጪ የተሾሙ ኃላፊዎች የመንግሥትን መዋቅር ለማጎልበትና ቢሮክራሲውን ለማጠናከር ሲባል በተመድና በሌሎችም ተቋማት የሚፈከላቸው ደመወዝና ሌሎችም ጥቅማ ጥቅሞች ለረዥም ጊዜ በቦታቸው የማያቆያቸው እንደሆነ፣ ለአጭር ጊዜ በተመደቡበት ቦታ ሠርተው የሚፈልገለውን ውጤት አስገኝተው እንዲሄዱ ስለሚፈለግ መልቀቃቸው ብዙ እንደማያስገርም የሚያነሱም አልታጡም፡፡በዚህም ተባለ በዚያ እየለቀቁ ያሉት ኃላፊዎች ለመንግሥት የቢሮክራሲ መዋቅር አመኔታን ለማትረፍና ግልጽነትን ለማስፈን ብዙ አስተዋጽኦ ሊያደርጉበት የሚችሉበት ዕድል እንደነበር፣ መንግሥት የሥራ ኃላፊነቶችን የሚሰጠው ለፖለቲካ ታማኞች ብቻ ሳይሆን በዕውቀት፣ በክህሎትና በትምህርታቸው ብሎም በሚመደቡበት ቦታ ውጤታማ ሥራ መሥራት እንደሚችሉ ለሚታመንባቸው በተለይም ደግሞ ወጣቶች ለሆኑት መሆኑ ትልቅ ትርጉም እንደነበረው የሚጠቁሙ አስተያየት ሰጪዎች፣ ይህ አሠራር እየደበዘዘ እንዳይመጣ ሥጋታቸውን ይገልጻሉ፡፡ ቢሮክራሲው በፖለቲከኞችና በፓርቲ አባልነታቸው ብቻ በሚሾሙ ኃላፊዎች ከተሞላ ነባሩ አዙሪት ተመልሶ ሊመጣ እንደሚችል ያሳስባሉ፡፡ @ethiocheck

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ የአፍሪካ ከፍተኛውን የስፖርት ሽልማት አሸናፊ ሆኑ። የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አሕመድ የአፍሪካ ብሄራዊ የኦሎምፒክ ኮሚቴዎች ማኅበር /አኖካ/ ለኦሎምፒክ ስፖርት ዕድገት ድጋፍ ላደረጉ መሪዎች እና ታዋቂ ሰዎች የሚሰጠው ሽልማት አሸናፊ መሆናቸው ተገልጿል። ለኢትዮጵያ ስፖርት እና ለኦሎምፒክ ንቅናቄ ላበረከቱት አስተዋፅኦ ነው በአፍሪካ በስፖርት ዘርፍ ከፍተኛ የሆነው ሽልማት ተሸላሚ መሆናቸውን አኖካ ያስታወቀው። ማኅበሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ በቀጣይ በሚመረጥ ቦታና ጊዜ ሽልማቱ እንደሚበረከትላቸው አስታውቋል ሲል ፋብኮ ዘግቧል። ዘንድሮ ሊካሄድ የነበረውን የቶክዮ ኦሎምፒክን መሰረት በማድረግ ኢትዮጵያ የኮሮና ወረርሽኝ ከመከሰቱ ቀደም ብላ ባሉት ወራት ሰፊ ከማስ ስፖርት ጋር በማስተሳሰር ሀገር አቀፍ የኦሎምፒክ ስፖርት ንቅናቄ ስታደርግ መቆየቷ ይታወሳል። @ethiocheck

በአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ላይ ጥይት ተኩሶ በመግደል ወንጀል የተጠረጠረው ግለሰብ ወንጀሉን መፈፀሙን አመነ‼️ በአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ላይ ጥይት ተኩሶ በመግደል ወንጀል የተጠረጠረው አቶ ጥላሁን ያሚ የተባለው ግለሰብ ወንጀሉን ስለመፈፀሙ ለፖሊስ በሰጠው የእምነት ክህደት ቃል አረጋገጠ። ተጠርጣሪው “ይህንን ተልእኮ የሰጡኝ ሰዎች ድርጊቱን መፈፀምህን በሚስጥር የማትይዝ ከሆነ በቤተሰቦችህ ላይ ጉዳት እናደርሳለን” በማለት እንዳስጠነቀቁት ለፈደራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት፣ የአራዳ ምድብ፣ አንደኛ ወንጀል ችሎት ተናግሯል። በዚህም “ለቤተሰቦቼ በቂ ጥበቃ እንዲደረግላቸው እና የኔም ጉዳይ በፍጥነት እልባት እንዲያገኝ” በማለት ለፍርድ ቤቱ አመልክቷል። “የፀሀይ ብርሀን አግኝቼ አላውቅም፣ ካቴና ከእጄ አልወለቀም፣ ክስ እስከሚመሰረትብኝ እንኳን ከሌሎች ተጠርጣሪዎች ጋር እንድቀላቀል ይደረግልኝ” በማለት ለፍርድ ቤቱ አቤቱታ አቅርቧል። ተጠርጣሪው ባለፈው የጊዜ ቀጠሮ በዚሁ ችሎት ቀርቦ “እራሴን እንዳጠፋ ይፈቀድልኝ” ማለቱን ችሎቱ አስታውሷል። በዚያው ቀጠሮው መርማሪ ፖሊስ ካቴናው ከእጁ የማይወልቀው ተጠርጣሪው እራሱን እንዳያጠፋ ለመከላከል መሆኑንም ችሎቱ ገልጿል። መርማሪ ፖሊስ በዛሬው ቀጠሮው ተጠርጣሪው የካቴናውን ጉዳይ ዳግም በማንሳቱ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የሚመለከተው የስራ ሀላፊ በቀጣይ ቀጠሮው ስለሁኔታው ያስረዳ ብሏል ችሎቱ። ፖሊስ ባለፈው የተሰጠው የጊዜ ቀጠሮ ያከናወነውን የምርመራ ስራ ያደመጠው ፍርድ ቤቱ በቀጣይ በተለይም በቁጥጥር ስር ከሚገኙ ተጠርጣሪዎች ጀርባ ድርጊቱን ያቀነባበሩ አካላትን በቁጥጥር ስር ለማዋል እና ሌሎች የሰነድ ማስረጃዎችን ለማደራጀት ከጠየቀው 14 ቀን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ፍርድ ቤቱ 11 ቀን ፈቅዷል። ፍርድ ቤቱ ውጤቱን ለመጠባበቅም ለነሀሴ 12 ቀን 2012 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል @ethiocheck

ህወሓት ወደ አዲስ አበባ ሽማግሌ ልኳል ? ከሰሞኑን በአንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በፌደራል መንግስቱና በትግራይ ክልል መንግስት መካከል ያለውን አለመግባባት ለመፍታት ህወሓት ለሽምግልና በዶ/ር
ህወሓት ወደ አዲስ አበባ ሽማግሌ ልኳል ? ከሰሞኑን በአንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በፌደራል መንግስቱና በትግራይ ክልል መንግስት መካከል ያለውን አለመግባባት ለመፍታት ህወሓት ለሽምግልና በዶ/ር አዲስአለም ባሌማ የተመራ ቡድን ወደ አዲስ አበባ ልኳል ተብሎ ሲነገር ነበር። በዚህ ጉዳይ የቀድሞ የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የነበሩት የህወሓት ከፍተኛ አመራር ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም '#አባይ' ከተባለ ሚዲያ ስለጉዳዩ እውነትነት ጥያቄ ቀርቦላቸው 'ሲናፈስ የነበረው ነጭ ውሸት ነው፣ ህወሓት ሽማግሌ አላከም፣ ሊልክም አይችልም' ሲሉ መልስ ሰጥተዋል። በሌላ በኩል ወ/ሮ ኪሪያ ኢብራሂም ህወሓት አሁንም ለውይይት ዝግጁ መሆኑን ነገር ግን አሁን ያለው ችግር ሀገራዊ ስለሆነ ጉዳዩን የህወሓት እና የብልፅግና ፓርቲ ብቻ አድርጎ መወሰድ እንደሌለበት ፤ ሁሉንም ወገን ያካተት፣ ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚሳተፉበት የውይይት መድረክ ከተዘጋጀ ፓርቲው እንደማንኛው ፓርቲ ለመሳተፍ ዝግጁ እንደሆነ አሳውቀዋል። ወ/ሮ ኪሪያ 'በህወሓት እና በብልፅግና ፓርቲ መካከል ብቻ የሚደረግ የውይይት መድረክ ሊሆን አይችልም ፤ ከዚህ ቀደም ወደ መቐለ መጥተው ለነበሩት የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች የተሰጠው ሀሳብም ይኸው ነው ፤ አሁንም የያዝነው አቋም ይህ ነው' ብለዋል። @ethiocheck

በአፋር ክልል የአዋሽ ወንዝ ባስከተለው የጎርፍ አደጋ 49 ሺህ 65 ሰዎች መጠቃታቸውን የአፋር ክልል አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ፕሮግራም ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት አስታወቀ፡፡ የፅህፈት ቤቱ ምክ
በአፋር ክልል የአዋሽ ወንዝ ባስከተለው የጎርፍ አደጋ 49 ሺህ 65 ሰዎች መጠቃታቸውን የአፋር ክልል አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ፕሮግራም ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት አስታወቀ፡፡ የፅህፈት ቤቱ ምክትል ሃላፊ ወይዘሮ ኩልሱማ ቡርሃባ አሊ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደተናገሩት በማዕከላዊና ታችኛው አዋሽ በስጋት ቀጠናነት ከተለዩት 17 ወረዳዎች መካከል 10ሩ በጎርፍ አደጋ ተጠቅተዋል፡፡ በዚህ ሳቢያም 19 ሺህ 656 ሰዎች መፈናቀላቸውን ጠቅሰው ከተፈናቀሉት በተጨማሪም በእንስሳት እና ንብረት ላይ ጉዳት መድረሱንም ነው የተናገሩት፡፡ ከዚህ ባለፈም በጎርፉ ሳቢያ 51 ሺህ 659 ሰዎች ስጋት ውስጥ ይገኛሉም ነው ያሉት፡፡ አሁን ላይ ከጎርፍ አደጋው ጋር በተያያዘ በ5 ወረዳዎች ምላሽ ተሰጥቷል ያሉት ምክትል ሃላፊዋ ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች ድጋፍ የማድረግና ከመከላከያ ጋር በመተባበር በሄሊኮፕተር የነብስ አድን ስራ እየተሰራ እንደሚገኝም አስረድተዋል፡፡ በዋናነትም በክልሉ ምላሽ ሰጭ ግብረ ሃይል ተቋቁሞ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው ከፌደራል መንግስት እና ከበጎ አድራጎት ድርጅቶች ጋር በመተባበር ምግብ እና ምግብ ነክ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑም ገልጸዋል፡፡ እየወጡ ያሉ የአየር ትንበያ መረጃዎች በቀጣይ የጎርፍ አደጋ ሊከሰት እንደሚችል አመላካች መሆናቸውን ተከትሎም ነዋሪዎችን ወደ ከፍተኛ ቦታዎች የማዘዋወር እና ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ እየተሰራ ነውም ብለዋል፡፡ ባለፈው አመት በአዋሽ ወንዝ ላይ አቅጣጫ የማስቀየር ስራ ቢሰራም በሃገር ውስጥና በጎረቤት ሃገራት ከፍተኛ ዝናብ መዝነቡን ተከትሎ የጎርፍ አደጋው መከሰቱንም አውስተዋል፡፡፡ @ethiocheck

የአቶ እስክንድር ነጋ የዋስትና ጥያቄን ፍርድ ቤቱ ውድቅ አደረገ ************** የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ አንደኛ የወንጀል ችሎት የአቶ እስክንድር ነጋን የዋስትና ጥያቄ ውድቅ አደረገ። የፖሊስ ምርመራ ቡድን ፍርድ ቤቱ በሰጠው የምርመራ ጊዜ ያገኘውን የምርመራ ሥራ ለፍርድ ቤቱ አብራርቶ ለቀሪ የምርመራ ሥራዎችም የ14 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ጠይቋል። በምርመራ ቡድኑ አፈፃፀም እና ቀጣይ ጥያቄ ዙሪያ የተጠርጣሪ ጠበቆች እና የምርመራ ቡድኑ ያደረጉትን ክርክር የመረመረው ችሎቱ፣ የፖሊስን የተጨማሪ ምርመራ ጊዜ ጥያቄ አልተቀልኩም ብሏል። ጠበቆችም አቶ እስክድር ነጋ የዋስትና መብቱ እንዲጠበቅ የጠየቁ ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱ የዋስትና ጥያቄውን ውድቅ አድርጓል። ምክንያቱ ደግሞ መርማሪ ቡድኑ አቶ እስክንድር የጠረጠረበት ወንጀል ሞት ያስከተለ በመሆኑ ጥፋተኛ ሆኖ ከተገኘ ከ15 ዓመት በላይ ሊያስቀጣቸው ስለሚችል ነው ብሏል። በሌላ በኩል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ በአቶ እስክንድር ላይ የቀዳሚ ምርመራ ፋይል እንዲከፈት የወሰንኩ በመሆኑ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ይስጠኝ በማለት አመልክቷል። በዚህም ችሎቱ በሰጠው ትዕዛዝ ዐቃቤ ሕግ ለቀዳሚ ምርመራ ችሎት የሚያቀርበው አቤቱታ እስከነምስክሮች ዝርዝር እንዲያቀርብ ትዕዛዝ በመስጠት ለነሐሴ 5 ቀን 2012 ዓ.ም ዐቃቤ ሕግ በሚያቀርበው አቤቱታ የጠበቆች መቃወሚያ ካለም እሰማለሁ ብሏል። ይህ እስከሚሆን ድረስ ግን ተጠርጣሪው አቶ እስክንድር ነጋ በፖሊስ ማረፊያ ቤት እንዲቆይ አዝዟል። ከዐቃቤ ሕግ ባገኘነው መረጃ መሠረት ከአቶ እስክንድር ጋር ስንታየሁ ቸኮል እና ቀለብ ስዩም የተባሉ ተጠርጣሪዎች በዚሁ የቀዳሚ ምርመራ ፋይል ውስጥ የሚካተቱ ይሆናል። (EBC) @ethiocheck

የሪፐብሊኩ ጥበቃ ልዩ ኃይሎች ተመረቁ! በውጭ ሀገርና በሀገር ውስጥ የሰለጠኑ የሪፐብሊኩ ጥበቃ ልዩ ኃይሎች መመረቃቸው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ዘግቧል። በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የሪፐብሊኩ ጥበቃ ኃይል
የሪፐብሊኩ ጥበቃ ልዩ ኃይሎች ተመረቁ! በውጭ ሀገርና በሀገር ውስጥ የሰለጠኑ የሪፐብሊኩ ጥበቃ ልዩ ኃይሎች መመረቃቸው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ዘግቧል። በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የሪፐብሊኩ ጥበቃ ኃይል ዋና አዛዥ ሜ/ጀነራል ብርሃኑ በቀለ የጥበቃ ኃይሉ እንደማንኛውም የፀጥታ ተቋም ህገ መንግስቱንና ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን ማስጠበቅ አላማ ያነገበ ነው ብለዋል። ሜ/ጀነራል ብርሃኑ አሁን የተመረቁት የሪፐብሊኩ የጥበቃ ልዩ ኃይሎች በውጭ ሀገር ለስድስት (6) እና ሰባት (7) ወራት ስልጠና የወሰዱ ናቸው ሲሉ ተናግረዋል። በውጭ የወሰዱት ስልጠና በእዛው ሀገር ዶክትሪን፣ መልክአ ምድርና የአየር ፀባይ ሲሆን ወደፊት ከሚገጥማቸው ግዳጅ ሊዛመድ የሚችል በኢትዮጵያ ዶክትሪን ፣ መልክአ ምድርና የአየር ፀባይ ለሁለት ወር 'በወንዶ ጢቃ' የማዛመጃ ስልጠና እንደተሰጣቸው አስታውቀዋል። @ethiocheck

በትግራይ ክልል የምርጫ ቅስቀሳ ሊጀመር ነው! በትግራይ ክልል ለሚደረገው ስድስተኛው ክልላዊ ምርጫ የሚሳተፉ የተፎካካሪ ፓርቲዎች ከነሃሴ 5/2012 ዓ/ም ጀምሮ አጠቃላይ የምርጫ ቅስቀሳ እንደሚጀምሩ
በትግራይ ክልል የምርጫ ቅስቀሳ ሊጀመር ነው! በትግራይ ክልል ለሚደረገው ስድስተኛው ክልላዊ ምርጫ የሚሳተፉ የተፎካካሪ ፓርቲዎች ከነሃሴ 5/2012 ዓ/ም ጀምሮ አጠቃላይ የምርጫ ቅስቀሳ እንደሚጀምሩ ተገልጿል። በመገናኛ ብዙሃን አጠቃቀም፣ በበጀት ድልድል እና በሌሎች ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ዙሪያ በተፎካካሪ ፓርቲዎችና በምርጫ ኮሚሽን አመራሮች መካከል ለሁለት ቀን ውይይት ሲደረግ ቆይቶ ትላንት መጠናቀቁን ከትግራት ቲቪ ያገኘነው መረጃ ያሳያል። የትግራይ ክልል ምርጫ ኮሚሽን ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር የጋራ ስምምነት በማድረግ የምርጫው ጊዜ ገደብ ተላይቶ በቀጣይ የውይይት መድረክ ይፋ እንደሚደረግ ገልጿል። በትግራይ ክልል በሚደረገው ምርጫ 5 ተፎካካሪ ፓርቲዎች (ህወሓት፣ ባየቶና ፣ ሳልሳይ ወያነ ትግራይ ፣ ውድብ ናፅነት ትግራይ ፣ አሲምባ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት) እና 11 የግል እጩዎች ተወዳዳሪዎች መመዝገባቸው ይታወሳል። @ethiocheck

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የአባይ ግድብ ሙሌት እና አስተዳደርን አስመልክቶ እየተደረገ ባለው ድርድር፤ ኢትዮጵያ ከስምምነት ላይ ለመድረስ የቀራት ጊዜ እየተሟጠጠ መሆኑን ሰሞኑን “ብሎምበርግ” ለተባለው መገናኛ ብዙሃን አስታውቆ ነበር። ይህንን የአሜሪካን አቋም በተመለከተ የተጠየቁት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቃባይ ዲና ሙፍቲ “ብሔራዊ ጥቅማችንን በጫና አሳልፈን [አንሰጥም]” ብለዋል። “በድርድሩ ዙሪያም ሆነ በሌሎች ጉዳዮች ላይ የኢትዮጵያን በሔራዊ ጥቅም አሳልፎ የሚሰጥ ነገር ላይ አሁን ያለው አመራርም ሆነ ህዝባችን ለመደራደር ፍቃደኛ አይደለም። ወደዚያ የሚገፋንን ማንኛውም ነገር [እንጸየፋለን]” ሲሉ ቃለ አቃባዩ የሀገራቸውን አቋም ግልጽ አድርገዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር) @ethiocheck

በኮሮና የተያዘው ታዋቂው የአፋን ኦሮሞ ድምፃዊ ኢቲቃ (በቢቢሲ የአማርኛው አገልግሎት የተዘጋጀ) በአፋን ኦሮሞ የፖለቲካ ዘፈኖቹ የሚታወቀው ድምጻዊ ኢቲቃ ተፈሪ በኮሮናቫይረስ መያዙን ካወቀ ሳምንታት
በኮሮና የተያዘው ታዋቂው የአፋን ኦሮሞ ድምፃዊ ኢቲቃ (በቢቢሲ የአማርኛው አገልግሎት የተዘጋጀ) በአፋን ኦሮሞ የፖለቲካ ዘፈኖቹ የሚታወቀው ድምጻዊ ኢቲቃ ተፈሪ በኮሮናቫይረስ መያዙን ካወቀ ሳምንታት መቆጠሩን ለቢቢሲ ተናግሯል። ድምጻዊው "በሽታው እንዲህ አይነት ቦታ ያዘኝ ብዬ መናገር አልችልም" ካለ በኋላ የሚጠረጥረው ስፍራ እንዳለ ግን ገልጿል። ድምጻዊው ሃጫሉ ሁንዴሳ በተገደለበት እለት የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ሳያደርግ ከጓደኞቹ ጋር በሆስፒታል ውስጥ ከወዲያ ወዲህ ሲሯሯጡ እንደነበር ያስታውሳል። አምቦ በነበረው የሃጫሉ ቀብር ስነስርዓት ላይም አብዛኛው ሰው በሐዘን ስሜት ውስጥ ሆኖ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ አልተጠቀመም ነበር። ትልቁ ጥርጣሬው ይህ እንደሆነ የሚናገረው ድምጻዊ ሂቲቃ ፣ ከአምቦ ከተመለሰ በኋላ የሕመም ስሜት ተሰምቶት ወደ ግል ጤና ጣብያ ቢሄድም ሌላ በሽታ ነው ተብሎ መርፌና ኪኒን ታዘዘለት። ይሁን እንጂ በራሱ ላይ የተመለከታቸው የሕመም ስሜቶች የኮሮና ቫይረስ ነበሩ ይላል ድምጻዊ ሂቲቃ። 'ሰውነቴ በጣም ይደክማል ፤ ደረቅ ሳል ሳያቋርጥ ለሶስት ሰዓት ያስለኝ ነበር' በማለት ይናገራል። ከዚያ በኋላ ለጤና ቢሮ በመደወል ምርመራ እንደተደረገለት እና በኮሮና መያዙ ሲረጋገጥም ወደ ሚሊየም አዳራሽ የኮሮና የህክምና ማዕከል ተወስዶ ሕክምናና እንክብካቤ ሲደረግለት መቆየቱን ይገልፃል። @ethiocheck

💥ግብጽና ሱዳን የታላቁ የኅዳሴ ግድብ ድርድርን አቋረጡ! ግብጽ እና ሱዳን በታላቁ የኅዳሴ ግድብ ላይ የሚደረገውን ድርድር ማቋረጣቸውን አስታወቁ። ሁለቱ አገሮች በአፍሪካ ኅብረት አሸማጋይነት ከሚደረ
💥ግብጽና ሱዳን የታላቁ የኅዳሴ ግድብ ድርድርን አቋረጡ! ግብጽ እና ሱዳን በታላቁ የኅዳሴ ግድብ ላይ የሚደረገውን ድርድር ማቋረጣቸውን አስታወቁ። ሁለቱ አገሮች በአፍሪካ ኅብረት አሸማጋይነት ከሚደረገው ድርድር ያፈነገጡት ኢትዮጵያ ትናንት በተደረገው ድርድር የግድቡን ውኃ አሞላል የተመለከተ ረቂቅ ደንብ ካቀረበች በኋላ ነው። የሱዳኑ የመስኖ ምኒስትር ያሲር አባስ ኢትዮጵያ ያቀረበችው ረቂቅ ሙሉ ድርድሩን የሚያሰጋ ነው ሲሉ ተናግረዋል። አባስ እንዳሉት የኢትዮጵያ ሰነድ የግድቡን የወደፊት አስተዳደር በአባይ ውኃ ላይ ለሚደረስ አጠቃላይ ስምምነት የሚተው ነው። ግብጽም እንደ ሱዳን ሁሉ ኢትዮጵያ ለድርድር ያቀረበችው ሰነድ የግድቡን የወደ ፊት የሥራ ክንውን እና ሕጋዊ የቅራኔ አፈታትን ያላካተተ ነው ብላለች። ኢትዮጵያ ያቀረበችው የግድቡን ውኃ አሞላል የተመለከተ የሥምምነት ረቂቅ "የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ ጽህፈት ቤት ሐምሌ 17 ቀን 2012 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ መሠረት" መሆኑን የውኃ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር ትናንት ማምሻውን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። የውኃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ምኒስትሩ ስለሺ በቀለ "የመጀመሪያውን የውኃ አሞላል ሥምምነት በፍጥነት ለመፈረም እና በቀጣይ ጊዜያት አጠቃላይ ሥምምነት ላይ ለመድረስ ድርድር ለመቀጠል" ኢትዮጵያ ፍላጎት እንዳላት ገልጸዋል። በጀርመን ድምጽ ራዲዮ የቀረበ @ethiocheck