en
Feedback
AIRDROP ROOM

AIRDROP ROOM

Open in Telegram
2 485
Subscribers
No data24 hours
-157 days
-5230 days
Posts Archive
የወላይታ ህዝብ እራሱን በራሱ የማስተዳደር ህገ-መንግስታዊ በክልል የመደራጀት የመብት ጥያቄ በምክር ቤቱ ተገቢው ምላሽ ባለመሰጠቱ በደ/ብ/ብ/ህ/ ክልል ም/ቤት የወላይታ ህዝብ ተመራጮች እራሳቸውን ከ
የወላይታ ህዝብ እራሱን በራሱ የማስተዳደር ህገ-መንግስታዊ በክልል የመደራጀት የመብት ጥያቄ በምክር ቤቱ ተገቢው ምላሽ ባለመሰጠቱ በደ/ብ/ብ/ህ/ ክልል ም/ቤት የወላይታ ህዝብ ተመራጮች እራሳቸውን ከምክር ቤት አባልነት ማግለላቸውን የወላይታ ዞን ምክር ቤት አስታወቀ፡፡ ምክር ቤቱ በዛሬው ቀን በጉዳዩ ዙሪያ መግለጫ ሰጥቷል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የጅቡቲ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ተመለሱ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ እና የልዑካን ቡድናቸው በሶማሊያ እና በሶማሌላንድ ግንኙነት ዙሪያ በሚደረገው የምክክር መድረክ
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የጅቡቲ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ተመለሱ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ እና የልዑካን ቡድናቸው በሶማሊያ እና በሶማሌላንድ ግንኙነት ዙሪያ በሚደረገው የምክክር መድረክ ላይ የነበረውን ተሳትፎ አጠናቆ ዛሬ ተመልሷል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትናንት ነበር ለውይይቱ ጅቡቲ የገቡት በሶማሊያ እና በሶማሌላንድ ግንኙነት ዙሪያ በጅቡቲ የተካሄደው የምክክር ጉባኤው በየካቲት 2012 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ አዘጋጅነት በአዲስ አበባ የተደረገው ውይይት ተከታይ ክፍል ነው። በምክክር መድረኩ ላይም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የጅቡቱ ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌ፣ የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሞሃመድ አብዱላሂ ፋርማጆ እና የሶማሌላንድ ፕሬዚዳንት ሙሳ ቢሂ አብዲ እና የኢዳግ ዋና ፀሃፊ ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ ተገኝተዋል። #FBC

"ሙሶሎኒ በኢትዮጵያ የመርዝ ጋዝ አልተጠቀመም" ያለው ጋዜጠኛ ሐውልት እንዲፈርስ ተጠየቀ! ኤርትራዊቷን በባርነት ገዝቶ የኖረው እና "ሙሶሎኒ በኢትዮጵያ የመርዝ ጋዝ አልተጠቀመም" ያለው የጋዜጠኛ ኢን
"ሙሶሎኒ በኢትዮጵያ የመርዝ ጋዝ አልተጠቀመም" ያለው ጋዜጠኛ ሐውልት እንዲፈርስ ተጠየቀ! ኤርትራዊቷን በባርነት ገዝቶ የኖረው እና "ሙሶሎኒ በኢትዮጵያ የመርዝ ጋዝ አልተጠቀመም" ያለው የጋዜጠኛ ኢንድሮ ሞንታኔሊ ሐውልት እንዲፈርስ ለተቃውሞ በወጡ ሰልፈኞች ተጠይቋል፡፡ በ1930ዎቹ(እ.አ.አ) በውትድርና አገልግሎት ላይ ሳለ አንዲት የ12 ዓመት ኤርትራዊትን በገንዘብ ገዝቶ እና በኋላም አግብቷት ይኖር እንደነበር አምኗል። ታዲያ ሰሞኑን ለተቃውሞ የወጡ ሰልፈኞች የቆመለትን ሀውልት በቀለም አበላሽተውታል፡፡ በአሜሪካና በአውሮፓ ጸረ ባርነትና ጸረ ዘረኝነት ተቃውሞዎች መስፋፋታቸውን ተከትሎ በጣሊያንም ተቃዋሚዎች የዚህን ሰው ሐውልት በአስቸኳይ አፍርሱልንም እያሉ ነው። በጣሊያን አገር ሬተስቱደንቲሚሊኖ የሚባሉ የመብት ተቆርቋሪ ቡድኖች ይህንን ሞንታኔሊ የተባለ ሰው "እጅግ ነውረኛና ዘረኛ የነበረ፣ የቅኝ ግዛት ደጋፊና የባርነት አቃፊ›› ሲሉ ይነቅፉታል። "ለዚህ ነውረኛ ሰው ሐውልት ማቆም ነውር ነው" ሲሉ ቅዋሚያቸውን አስተጋብተዋል። የሚላን ከንቲባ በበኩላቸው "ሞንታኔሊ ሐውልቱ የቆመለት በነበረው የጋዜጠኝነት ጀብዱ ነው" ሲሉ ተከላክለውታል። ይህ ሐውልት ቆሞ የሚገኘው በጣሊያን ሚላን ፓርክ ውስጥ ነው። ሞንታኔሊ የሞተው እንደ አውሮፓዊያኑ በ2001 ነበር።

በቻይና ከሚያዚያ ወዲህ በአንድ ቀን ከፍተኛ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ተመዘገበ የቻይና ባለሥልጣናት 57 አዲስ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች መመዝገባቸውን ያስታወቁ ሲሆን ይህም ከሚያዝያ ወር አጋማሽ
በቻይና ከሚያዚያ ወዲህ በአንድ ቀን ከፍተኛ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ተመዘገበ የቻይና ባለሥልጣናት 57 አዲስ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች መመዝገባቸውን ያስታወቁ ሲሆን ይህም ከሚያዝያ ወር አጋማሽ ወዲህ በአንድ ቀን ውስጥ የተመዘገበ ከፍተኛ ቁጥር ነው፡፡ የብሔራዊ ጤና ኮሚሽን 38ቱ ከማህበረሰቡ ውስጥ የተገኙ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ 36ቱ በቤጂንግ የተገኙ መሆናቸውን አስታውቋል፡፡ ከትናንት አንስቶ በቫይረሱ የተያዙ አዳዲስ ሰዎች መገኘታቸውን ተከትሎም በአንዳንድ አካባቢዎች ከቤት ያለመውጣት ገደብ እንደገና ተጥሏል፡፡ አብዛኞቹ ሰዎች በቫይረሱ የተያዙት ከገበያ ቦታዎች ጋር በተገናኘ ነው ተብሏል፡፡ በዚህም በአቅራቢያው ያሉ አስራ አንድ የመኖሪያ መንደሮች እንዲዘጉ ተደርገዋል፡፡ ነዋሪዎቹ መውጣት የሚፈቀድላቸው መሰረታዊ ግዥ ለመፈጸም ብቻ ነው፡፡ በቻይና ከ84ሺህ በላይ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠ ሲሆን 4 ሺህ 638 ሰዎች ደግሞ ሕይወታቸውን እንዳጡ የጆንስ ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ መረጃ ያሳያል፡፡ የአገሪቷ መንግሥት ኮሮናቫይረስን ድል መትተናል ብሎ ካወጀ በኋላ በአገሪቷ ተጥለው የነበሩ በርካታ ገደቦችን አላልታለች፡፡ ይሁን እንጅ በቅርቡ እየታየ ያለው በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር መጨመር ሁለተኛ ዙር ወረርሽኝ እንዳይከሰት ስጋት ፈጥሯል፡፡

በኮሮና የሟች ቤተሰቦች የጣሊያኑን ጠ/ሚኒስትር ሊከሱ እየተዘጋጁ ነው። በሰሜን ጣሊያን አቃቢ ሕግ ጠቅላይ ሚኒስትር ጆሴፔ ኮንቴን ዛሬ አርብ ለምርመራ ቀጥሯቸዋል። ምክንያቱ ደግሞ ዘመድ ወዳጆቻቸው በ
በኮሮና የሟች ቤተሰቦች የጣሊያኑን ጠ/ሚኒስትር ሊከሱ እየተዘጋጁ ነው። በሰሜን ጣሊያን አቃቢ ሕግ ጠቅላይ ሚኒስትር ጆሴፔ ኮንቴን ዛሬ አርብ ለምርመራ ቀጥሯቸዋል። ምክንያቱ ደግሞ ዘመድ ወዳጆቻቸው በኮሮና የሞቱባቸው ቤተሰቦች "መንግሥት ቶሎ እርምጃ አልወሰደም፤ ተዘናግቶ ነበር፣ ቤተሰቦቻችንን በሞት ያጣነው በመንግሥት እንዝላልነት ነው" የሚል ክስ በማቅረባቸው ነው።

የቀድሞ ኤታማዦር ሹም ጀነራል ሰሞራ የኑስ ከአውሎ ሚዲያ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ያነሳቸው አንኳር ነጥቦች ። 1) #በጡረታ የተገለልኩት ድጋሚ ለመመለስ እንዳልሆነ እኔም መንግስትም እናውቃለን። ለኢትዮጵያ ህዝብና መንግስት ይጠቅማል ብዬ የማስበውን ሃሳብ ከተጠየኩ ሃሳብ እሰጣለሁ። የተማርኩት በአገሪቱ ግብር ከፋይ ህዝብ ገንዘብ መሆኑ መታወቅ አለበት 2) #ኢህአዴግ ገዢ መደብ ሆኖ ነበር። በ2007 ጥልቅ ተሃድሶ አድርገናል መንግስት መሆን አለብን ሲሉ ምንም እንኳም ወታደር በመሆኔ በፓለቲካ ጉዳይ መግባት ባይኖርብኝም ለአገር ካለኝ ተቆርቋሪነት አንፃር የሚያስፈልጋችሁ ተአድሶ አይደለም እጅግ ስለበሰበሳችሁ degeneration አድርጋችሁ ድጋሚ መፈጠር ነው ያለባችሁ ብያቸው ነበር። በወቅቱ ደሃውን ህዝብ ረስተው ስለነበር። 3) #በለውጡ ወቅት የተወሰኑ ቡድኖች መፈንቅለ መንግስት ማድረግ የፈለጉ ነበሩ። ሰራዊቱ ግን ሊሆን እንደማይችል ነግሯቸው ነው ያስቆማቸው 4) #ፓለቲከኞች ህዝቦችን እርስ በርሳቸው እንዳይተማመኑ የማድረግ ስራ ይሰሩ ነበር 5) #መሪዎችና ፓለቲከኞች በተለዋወጡ ቁጥር አገር መታኮስ የለባትም። ኢትዮጵያ መታኮስ ይብቃት 6) #ደርግን ያሸነፈው ወያኔ ሳይሆን የኢትዮጵያ ህዝብ ነው 7) #ዶክተር አብይ ሰራዊቱ ጋር በነበረ ግዜ ለትምህርት ደቡብ አፍሪካ ልኬው ጨርሶ ሲመለስ በተማረው መሰረት ኢንሳን የማዋቀር አዲስ ፕሮፖዛል ይዞ በመምጣቱ መንግስት አድንቆት ሃሳቡ ተግባር ላይ እንዲውል ተዱርጓል። 8) #ሙስና ሙሉ ለሙሉ አልነበረም አይባልም። ሆኖም የሙስና መጠኑን ለማወቅና ለማረጋገጥ በህግ የተቋቋመው ፀረ ሙስና ኮሚሽን የሁሉንም ሃብት አንዴ ከመዝገበ በኃላ በየአመቱ ያለውን የሃብት ለውጥን መመዝገብ ነበረበት። ለምሳሌ እኔ ጡረታ ስወጣ ኮሙሽኑ መጥቶ ቀድሞ ካስመዘገኩት ጋር ስለቅ የነበረኝ የሃብት መጠን መጥቶ ማጣራት ነበረበት! @ethiocheck

የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ክለቦች በኮሮናቫይረስ ምክንያት ከ2019/20 ገቢያቸው 1 ቢሊየን ፓውንድ እንደሚያጡ ‘ዴሎይት’ የተባለው ድርጅት አስታውቋል። በሊጉ የሚሳተፉ 20 ክለቦች ባሳለፍነው የውድድ
የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ክለቦች በኮሮናቫይረስ ምክንያት ከ2019/20 ገቢያቸው 1 ቢሊየን ፓውንድ እንደሚያጡ ‘ዴሎይት’ የተባለው ድርጅት አስታውቋል። በሊጉ የሚሳተፉ 20 ክለቦች ባሳለፍነው የውድድር ዘመን 5 ቢሊየን ፓውንድ ገቢ ሰብስበው ነበር። ነገር ግን የዘንድሮው የውድድር መርሀግብር ከመጋቢት ወር ጀምሮ የተቋረጠ ሲሆን ቀሪ 92 ጨዋታዎች ደግሞ ያለ ደጋፊ በዝግ ስታዲየሞች

የኬንያ ፖሊስ አንዲትን ሴት ከሞተር ሳይክል ጀርባ አስሮ መንገድ ላይ መጎተቱ ቁጣን ቀሰቀሰ --------------------------------------------- ---------------------
የኬንያ ፖሊስ አንዲትን ሴት ከሞተር ሳይክል ጀርባ አስሮ መንገድ ላይ መጎተቱ ቁጣን ቀሰቀሰ --------------------------------------------- ------------------------------------------ ኬንያዊው ፖሊስ አንዲትን ሴት ከሞተር ሳይክል ጀርባ አስሮ በመንገድ ላይ ሲጎትትና ሲገርፋት የሚያሳይ ቪዲዮ መውጣቱን ተከትሎ ቁጣን ቀስቅሷል፤ ፖሊሱም በምርመራ ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል። ግለሰቧ ሜሪ ቼሮኖ የምትባል ስትሆን ናኩሩ በምትባለው የኬንያ ከተማ ነዋሪ ናት። ፖሊሱ በከተማው በተፈጠረ ዝርፊያ ጠርጥሬያታለሁ በሚል ነው መንገድ ለመንገድ የጎተታት ግለሰቧ በእጇና እግሯ ላይ ከፍተኛ ጉዳት በመድረሱ ሆስፒታል ህክምና ላይ እንደምትገኝ ተገልጿል። ሜሪ ቼርኖ ፖሊሱን እንደምታውቀው ለሲትዝን ቴሌቪዥን ተናግራለች። ፖሊሶችን በተመለከተ ማጣራት የሚያደርገው ነፃ ድርጅት ግለሰቡ ላይ የሚያስፈልገው እርምጃ እንደሚወሰድበት ገልጿል። ባለፈው ይኸው ድርጅት ባወጣው መግለጫ የኮሮናቫይረስን መዛመት ለመግታት የወጡ ህጎችን አስከብራለሁ በሚል የአስራ አምስት ኬንያውያን ህይወት መጥፋቱን እንዲሁም 31 መቁሰላቸውን አጋልጧል። የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብት ቢሮ ከሰሞኑ ባወጣው ሪፖርትፖሊስ ጭካኔ የተሞላበት ጥሰት ማድረሱን ያሳወቀ ሲሆን፤ ድርጅቱም መደፈር፣ ድብደባና ንብረቶችን በማውደም ፖሊስን ወንጅሎታል።

የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች እና ታዋቂ ሰዎች የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጎበኙ የኪነ-ጥበብና የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች እና ታዋቂ ሰዎች ዛሬ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጎብኝተዋል። አየር መንገዱ ባዘጋ
የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች እና ታዋቂ ሰዎች የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጎበኙ የኪነ-ጥበብና የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች እና ታዋቂ ሰዎች ዛሬ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጎብኝተዋል። አየር መንገዱ ባዘጋጀው ጉብኝት ላይ የተሳተፉት ታዋቂ ሰዎች በሰጡት አስተያየት አየር መንገዱ ብሔራዊ ኩራት በመሆኑ በስኬቱም ሆነ በጉድለቱ አብረው መሆናቸውን ገልጸዋል። የአየር መንገዱን ሥራዎች በመመልከቱ ደስተኛ መሆኑንና ባየው እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ኩራት ተሰምቶኛል ሲል አርቲስትና የማስታወቂያ ባለሙያ ሠራዊት ፍቅሬ ተናግሯል። አየር መንገዱ አገርንም አህጉሩንም የሚያኮራና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርገው ተግባር እያከናወነ መሆኑን ተመልክተናል ያለው ሌላው ጋዜጠኛ በፍቃዱ አባይ ነው። ''አየር መንገዱ ውስጥ እየተደረጉ ያሉት ለውጦች በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚያኮሩ ናቸው'' ያሉት ደግሞ ሌላው ታዋቂ ሰው ኢንስፔክተር አሰፋ መዝገቡ ናቸው። ሁሉም ተቋማት እንደ አየር መንገዱ ሥራቸውን በትጋት ሊስሩ ይገባል በማለትም ምክራቸውን ለግሰዋል ። የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካውያንም ኩራት ስለሆነ በጥንቃቄ ልንይዘው ይገባል በማለት አትሌት ኃይሌ ገብረ ሥላሴ አሳስቧል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገብረ ማርያም የጉብኝቱን ተሳታፊዎች አመስግነው፤ጉብኝቱ በአየር መንገዱ ያለውን እውነታ ለማወቅ እንዳስቻላቸው እምነታቸውን ገልጸዋል። አየር መንገዱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርገውን ዘመናዊ መሠረተ ልማት ማስፋፊያ ሥራዎች እያከናወነ መሆኑ በዚህ ወቅት ተመልክቷል።

ለሀገር ውስጥ የፖለቲካ ፍጆታ ሲባል የሚፈፀሙ አሳዛኝ ድርጊቶች! የግብፅ ሚድያዎች የሚያራግቡትን ፕሮፖጋንዳ እዚህ አምጥቶ እና ተርጉሞ ማራገፍ የተለመደ ሆኗል። ግድቡ ስራው ቆሟል እንዲሁም ከደቡብ ሱ
ለሀገር ውስጥ የፖለቲካ ፍጆታ ሲባል የሚፈፀሙ አሳዛኝ ድርጊቶች! የግብፅ ሚድያዎች የሚያራግቡትን ፕሮፖጋንዳ እዚህ አምጥቶ እና ተርጉሞ ማራገፍ የተለመደ ሆኗል። ግድቡ ስራው ቆሟል እንዲሁም ከደቡብ ሱዳን በኩል በግብፅ ጥቃት ሊሰነዘርበት ነው ተብሎ ሰሞኑን ያልሆነ ወሬ ሲነዛ በራሱ ካልኩሌተር ስሌት አስልቶ ወሬውን የሚያሰራጭ የሀገር ሰው ሞልቷል። ግብፅ ብንሄድ ተቃዋሚውም፣ ደጋፊውም፣ ወታደሩም፣ ሲቪሉም በአንድነት ቆሞ ይሞግታል። ግድቡ ከፖለቲካ በላይ ነው! ኧረ እንደው ገመናችንን ለራሳችን እናስቀረው! ለሚያልፍ የፖለቲካ ትኩሳት የአለም ህዝብ መጠቋቆሚያ አንሁን!

ጅቡቲ ሶማልያን እና ሶማሌላንድን ለመሸምገል ዝግጅት ጨርሳለች! ዛሬ ጠዋት የሶማሌላንድ ፕሬዝደንት ሙሴ ቢሂ በኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ተሳፍረው ወደ ጅቡቲ ያቀኑ ሲሆን የሶማልያው መሪ መሀመ
ጅቡቲ ሶማልያን እና ሶማሌላንድን ለመሸምገል ዝግጅት ጨርሳለች! ዛሬ ጠዋት የሶማሌላንድ ፕሬዝደንት ሙሴ ቢሂ በኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ተሳፍረው ወደ ጅቡቲ ያቀኑ ሲሆን የሶማልያው መሪ መሀመድ ፎርማጆም ይከተሏቸዋል ተብሎ ይጠበቃል። ሁለቱ ተቀናቃኝ መሪዎች ለመጀመርያ ግዜ ፊት ለፊት የተገናኙት አዲስ አበባ በአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ወቅት እንደነበር ተገልፆ ነበር። ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ እና የልዑካን ቡድናቸውም በሶማሊያ እና በሶማሌላንድ ግንኙነት ዙሪያ በሚደረገው የምክክር መድረክ ላይ ለመሳተፍ ጅቡቲ ደርሰዋል ፡፡ 3.5 ሚልዮን ገደማ ህዝብ ያላት ሶማሌላንድ ከሶማልያ በራሷ ፈቃድ የተገነጠለችው የዛሬ 29 አመት ገደማ ነበር። ይሁንና ሶማሌላንድ በአለም አቀፉ ማህበረሰብ እንደ ሀገር እውቅና ያልተሰጣት ቢሆንም በአንፃራዊ ከሶማልያ የተሻለ መረጋጋት፣ ሰላም እና የንግድ እንቅስቃሴ አላት።

በጌዲዮ ዞን ገደብ ወረዳ የዘጠኝ አመት ህጻን ልጁን የደፈረው ግለሰብ በ #በሃያ_አንድ(21) ዓመት ጽኑ እስራት መቀጣቱን #STV ዘግቧል። በህፃናት ላይ በተደጋጋሚ እየደረሰ ያለው የአስገድዶ መድፈር ጥቃት እንዳሳሰባቸው ጭምር የጌዲኦ ዞን ነዋሪዎች ተናግረዋል። #STV

በባሌ ዞን ዲንሾ ከተማ የተቃውሞ ሰልፍ ተደረገ! ተቃዋሚዎቹ መንገዶችን የዘጉ ሲሆን፣ ፖሊስ አስለቃሽ ጭስ ተኩሷል። ባሳለፍነው ሰኞ ሳዲቅ ሃጂ ኢብሮን የተባሉ የጭነት መኪና አሽከርካሪ በአካባቢው መገ
በባሌ ዞን ዲንሾ ከተማ የተቃውሞ ሰልፍ ተደረገ! ተቃዋሚዎቹ መንገዶችን የዘጉ ሲሆን፣ ፖሊስ አስለቃሽ ጭስ ተኩሷል። ባሳለፍነው ሰኞ ሳዲቅ ሃጂ ኢብሮን የተባሉ የጭነት መኪና አሽከርካሪ በአካባቢው መገደላቸውን ተከትሎ ቅሬታ ተፈጥሯል። በአሽከርካሪው ግድያ የተጠረጠሩ 2ፖሊሶች እና 10 የዲንሾ ፓርክ የጥበቃ አባላት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የባሌ ዞን አስተዳደር ከቀናት በፊት መግለጹ ይታወሳል።

"በኢትዮጵያ 280 ሴቶችና ህፃናት ጥቃት ተፈፅሞባቸዋል" ጥናት በኢትዮጵያ ሦስት ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ 280 ሴቶችና ህፃናት ጥቃት እንደተፈጸመባቸው አንድ ጥናት አመለከተ። የሴቶች ህፃናትና ወጣቶች
"በኢትዮጵያ 280 ሴቶችና ህፃናት ጥቃት ተፈፅሞባቸዋል" ጥናት በኢትዮጵያ ሦስት ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ 280 ሴቶችና ህፃናት ጥቃት እንደተፈጸመባቸው አንድ ጥናት አመለከተ። የሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ሚኒስቴር በሴቶችና ህፃናት ላይ የሚደርሰውን ጥቃት መከላከልና ጥቃቱ ሲፈጸም ምን አይነት ምላሽ መስጠት ይገባል በሚሉ ጉዳዮች ላይ በሴቶች ጉዳይ ከሚሰሩ ሲቪክ ማህበራትና ፌዴሬሽኖች ጋር ዛሬ እየተወያየ ነው። በውይይቱ ላይ ከመጋቢት 1 ቀን 2012 እስከ ግንቦት 20 ቀን 2012 ዓ.ም ባሉት ጊዜያት በሴቶችና ህፃናት ላይ የደረሰውን ጥቃት የሚያብራራ ጥናት ቀርቧል። ጥናቱ የሴቶች ህጻናትና ወጣቶች ሚኒስቴር፣ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግና የአዲስ አበባ ሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ቢሮ በጋራ ያስጠኑት ጥናት ነው። በጥናቱ መሰረት በኢትዮጵያ በሁለት ወር ከሃያ ቀን ብቻ 280 ሴቶችና ህፃናት ጥቃት ተፈጽሞባቸዋል፤ ከነዚህ ውስጥ 273ቱ ሴቶች ሲሆኑ ሰባቱ ወንዶች ናቸው ተብሏል። ጥቃት ከደረሰባቸው ሴቶችና ህፃናት መካከል 215ቱ በአዲስ አበባ በሚገኙ አስሩ ክፍለ ከተሞች ነዋሪ ሲሆኑ ቀሪዎቹ በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የሚኖሩ መሆናቸውን ጥናቱ አመላክቷል። በሴቶችና ህፃናት ላይ የተፈጸሙት ጥቃቶች አስገድዶ መድፈር፣ ግብረሰዶምና ያለዕድሜ ጋብቻ መሆናቸውም በጥናቱ ተገልጿል።

" ግብጽ አሁን የያዘችው መንገድ ለሀገሪቱ ብዙ ጠላት የሚያፈራባት ነው፤ ጠላትነት በጨመረ ቁጥር ጭራሹንም ውሃው ሙሉ በሙሉ የእኔ ነው ወደሚል የእልህ መንገድ ይወስዳል:: መቼም ቢሆን የግብጽ ሠራዊት
" ግብጽ አሁን የያዘችው መንገድ ለሀገሪቱ ብዙ ጠላት የሚያፈራባት ነው፤ ጠላትነት በጨመረ ቁጥር ጭራሹንም ውሃው ሙሉ በሙሉ የእኔ ነው ወደሚል የእልህ መንገድ ይወስዳል:: መቼም ቢሆን የግብጽ ሠራዊት ኢትዮጵያ ገብቶ ምሽግ ሠርቶ የዓባይን ገባር ወንዞች አይጠብቅም፤ የኢትዮጵያን ምድርንም አይረግጥም፤ እነዚህ ወንዞቻችን ከጦርነትም በላይ ታላቅ አቅምና ጉልበት አላቸው" | የጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኤታ ማዦር ሹም ጀነራል ብርሃኑ ጁላ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከታገሩት የተወሰደ Readmore https://telegra.ph/EPA-06-12

ፈረንሳይ ባዘጋጀችው 1000 የአፍሪካ ስራ ፈጣሪዎች ውድድር 11 ኢትዮጵያውያን አሸነፉ! ውድድሩ በአፍሪካ-ፈረንሳይ ጉባዔ 2020 ዋና ጸሃፊ እና ዲጂታል አፍሪካ ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን በመጠጥ ውሃ
ፈረንሳይ ባዘጋጀችው 1000 የአፍሪካ ስራ ፈጣሪዎች ውድድር 11 ኢትዮጵያውያን አሸነፉ! ውድድሩ በአፍሪካ-ፈረንሳይ ጉባዔ 2020 ዋና ጸሃፊ እና ዲጂታል አፍሪካ ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን በመጠጥ ውሃ እና ሳኒቴሽን፣በኢነርጂ ልማት እና በሌሎችም ዘርፎች የተሰማሩ በርካታ አፍሪካዊ ስራ ፈጣሪ ወጣቶች ተሳትፈውበታል፡፡ ስራ ፈጣሪዎቹ ከአህጉሪቱ 53 ሃገራት የተውጣጡ ሲሆኑ ውድድሩን ካሸነፉ 1 ሺ ስራ ፈጣሪዎች መካከል 11ዱ ኢትዮጵያውያን መሆናቸውንም የፈረንሳይ ኤምባሲ የውድድሩን አዘጋጆች ጠቅሶ አስታውቋል፡፡ አሸናፊዎቹ ገንዘብን ጨምሮ የተለያዩ የሙያና የስልጠና ድጋፎችን ያገኛሉ እንደ አዘጋጆቹ ገለጻ፡፡ 28ኛው የአፍሪካ-ፈረንሳይ ጉባዔ ባሳለፍነው ሳምንት በፈረንሳይ ቦርዶ ከተማ ሊዘጋጅ እቅድ ተይዞለት የውድድሩ አሸናፊዎች ጉባዔውን እንዲታደሙ ግብዣ ተደርጎላቸውም ነበር፡፡ ሆኖም በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ሳይሳካ ቀርቷል፡፡ #AlAin

እየተካሄደ ባለው ድርድር ግብጽ አራት ቅድመ ሁኔታዎችን አስቀምጣለች ተባለ! ኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብጽ ከማክሰኞ ጀምሮ በታላቁ የሕዳሴ ግድብ ላይ ዳግም ከሥምምነት ለመድረስ አሜሪካን፣ የዓለም ባንክን
እየተካሄደ ባለው ድርድር ግብጽ አራት ቅድመ ሁኔታዎችን አስቀምጣለች ተባለ! ኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብጽ ከማክሰኞ ጀምሮ በታላቁ የሕዳሴ ግድብ ላይ ዳግም ከሥምምነት ለመድረስ አሜሪካን፣ የዓለም ባንክን እና ደቡብ አፍሪካን በታዛቢነት አስቀምጠው ድርድር እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ ዛሬ #AlharamOnline የግብጽ የመስኖ ሚኒስቴር ቃል አቀባይን ጠቅሶ እንደዘገበው በዚህ ድርድር ላይ ግብጽ አራት ቅድመ ሁኔታዎችን እንዳስቀመጠች ገልጸዋል፡፡ 1. በድርድሩ ስምምነት እስኪገኝ ድረስ ኢትዮጵያ በግሏ ውሳኔ የውኃ ሙሌቱ ላይ ምንም እንቅስቃሴ እንደማታደርግ ማረጋገጫ እንድሰጥ ግብጽ ትፈልጋለች፣ 2. ድርድሩ በተገደበ የገዜ ሰሌዳ እንዲጠናቀቅ ግብጽ ቅድመ ሁኔታ አስቀምጣለች፡፡ በዚህም ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 6 ድረስ በግድቡ የውሃ ሙሌት እና ዓመታዊ የውሃ አለቃቀቅ ላይ መስማማትን እንደ ሁለተኛ ቅድመ ሀኔታ አስቀምጣለች፣ 3. ውይይቱ በዋሽንግተኑ የውይይት ኃሳቦች ላይ መሰረት ያደረገ እንዲሆን ግብጽ ጽኑ ፍላጎቷን እየገለጸች ነው፡፡ ይህንንም እንደ ቅድመ ሁኔታ አስቀምጣለች፣ 4. በድርድሩ በታዛቢነት የተገኙት አካላት ሚናቸው ከታዛቢነት ወደ ከአደራዳሪነት ከፍ እንዲል ግብጽ ትሻለች፡፡ የኢትዮጵያ የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ ግብጽ የግድቡን ጉዳይ ለሁለተኛ ጊዜ ወደ ተባበሩት መንግስታት ድርጅት(ተመድ) የጸጥታው ምክርቤት በመውሰድ ውጫዊ የዲፕሎማሲ ጫና ለማሳደር እየሞከረች ነው ሲል ገልጿል። በድርድሩ ወቅትም ታዛቢዎችም ተሞክሮ እንዲያካፍሉ በ3ቱ ሀገራት ካልተጠየቁ በስተቀር፣ በታዛቢነት ብቻ እንዲወሰኑ ኢትዮጵያ መጠየቋ ተገልጿል፡፡

ኢትዮጵያ እየተካሄደ ባለው የህዳሴ ግድብ ውይይት ላይ ትናንት አቋሟን ግልፅ ማድረጓን የደረሰኝ መረጃ ያመለክታል! በዚህም መሰረት: - የታዛቢዎች ሚና ከታዛቢነት እና ጥሩ ተሞክሮዎችን በሶስቱ ሀገራት
ኢትዮጵያ እየተካሄደ ባለው የህዳሴ ግድብ ውይይት ላይ ትናንት አቋሟን ግልፅ ማድረጓን የደረሰኝ መረጃ ያመለክታል! በዚህም መሰረት: - የታዛቢዎች ሚና ከታዛቢነት እና ጥሩ ተሞክሮዎችን በሶስቱ ሀገራት የጋራ ፍቃድ ከማቅረብ ያልዘለለ መሆን እንዳለበት፣ - ውይይቱ ከማክሰኞ፣ አርብ እና እሁድ በስተቀር በሌሎች የሳምንት ቀናት ስምምነት ላይ እስኪደረስ እንዲቀጥል እንደምትፈልግ፣ እንዲሁም፣ - እ.አ.አ በ2015 በሶስቱ ሀገራት የተፈረመው Agreement on the Declaration of Principles (DoP) ሙሉ ለሙሉ እንዲከበር ጠይቃለች። ሙሉ መረጃውን ከተያያዘው ስክሪንሾት ማየት ይቻላል።

photo content

ድምፃዊ ሚኪያስ ከበደ (ሚኪ ጎንድርኛ) ትዳር መሰረተ ! @ethiocheck
ድምፃዊ ሚኪያስ ከበደ (ሚኪ ጎንድርኛ) ትዳር መሰረተ ! @ethiocheck