en
Feedback
AIRDROP ROOM

AIRDROP ROOM

Open in Telegram
2 485
Subscribers
No data24 hours
-157 days
-5230 days
Posts Archive
ፖሊስ ለ3 አመታት ቤት የተቆለፈበትን ግለሰብ ህይወት ታደገ ፖሊስ በናይጀሪያ ሰሜናዊ ካኖ ከተማ በወላጅ አባቱና በእንጀራ እናቱ ለሶስት አመታት ቤት የተቆለፈበትን ግለሰብ ህይወት ታደገ። የ30 አመቱ
ፖሊስ ለ3 አመታት ቤት የተቆለፈበትን ግለሰብ ህይወት ታደገ ፖሊስ በናይጀሪያ ሰሜናዊ ካኖ ከተማ በወላጅ አባቱና በእንጀራ እናቱ ለሶስት አመታት ቤት የተቆለፈበትን ግለሰብ ህይወት ታደገ። የ30 አመቱ አህመድ አሚኑ ሱስ ትጠቀማለህ በሚል ምክንያት በአንድ ክፍል ውስጥ ተቀልፎበት ሶስት አመታትን አሳፏል። ግለሰቡ የናይጀሪያ ፖሊስ በጎረቤቶቹና አንድ መንግስታዊ ባልሆነ ድርጅት በደረሰው ጥቆማ መሰረት በቤተሰቦቹ መኖሪያ ቤት ባደረገው ፍተሻ ነው ሊገኘው የቻለው። አሚኑ በደረሰበት ኢ-ሰባዊ ድርጊት ምክንያት መንቀሳቀስ እንደማይችልና በአሁኑ ሰዓትም በተሽከርካሪ ታግዞ ወደ ሆስፒታል ተወስዶ የህክምና እርዳታ እየተደረገለት እንደሚገኝ ተገልጿል። @ethiocheck

አሁን ላይ የህዳሴ ግድብ ከፍታ 565 ሜትር ላይ ይገኛል! ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከፍታ በሚቀጥለው ዓመት የበጋ ወራት በ30 ሜትር በማሳደግ 595 ሜትር ላይ የማድረስ ስራ እንደሚከናወን ተገል
አሁን ላይ የህዳሴ ግድብ ከፍታ 565 ሜትር ላይ ይገኛል! ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከፍታ በሚቀጥለው ዓመት የበጋ ወራት በ30 ሜትር በማሳደግ 595 ሜትር ላይ የማድረስ ስራ እንደሚከናወን ተገልጿል። የቴክኒክ ኮሚቴው ሰብሳቢ ኢንጂነር ጌድዮን አስፋው እንዳስረዱት አሁን ላይ የህዳሴ ግድብ ከፍታ 565 ሜትር ላይ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመት የበጋ ወራት የግድቡ መሃል ከፍታው 30 ሜትር እንዲጨምር ሲደረግ 595 ሜትር ላይ ይደርሳል ተብሏል። ከፍታው ሲጨምርም በሚቀጥለው ዓመት የክረምት ወቅት በእቅዱ መሰረት ግድቡ 18 ነጥብ 4 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ የመያዝ አቅም ላይ ይደርሳል። ግድቡ ከሶስት ዓመታት በኋላ ተጠናቆ ከፍታው 640 ሜትር ሲደርስ በሰው ሰራሽ ሃይቁ ውስጥ ከ70 በላይ ደሴቶችን ማግኘት ይቻላል። በደሴቶቹ ላይ ሪዞርቶች እና መዝናኛዎችን በመገንባት ግድቡን ከኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫነት ባለፈ ለቱሪዝም እና ለትራንስፖርት አገልግሎት መጠቀም ስለሚቻል ከወዲሁ ዝግጅት ማድረግ ይገባል ሲሉ ኢንጂነር ጌዲዮን ገልጸዋል። #EPA @ethiocheck

የግብጽ ጠቅላይ ሚኒስትር ካርቱም ገብተዋል! የግብጽ ጠቅላይ ሚኒስትር ሙስጠፋ ከማል ማድቡሊ ለአንድ ቀን ስራ ጉብኝት ሱዳን ካርቱም ገቡ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ካርቱም አየር ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ ሚኒ
የግብጽ ጠቅላይ ሚኒስትር ካርቱም ገብተዋል! የግብጽ ጠቅላይ ሚኒስትር ሙስጠፋ ከማል ማድቡሊ ለአንድ ቀን ስራ ጉብኝት ሱዳን ካርቱም ገቡ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ካርቱም አየር ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሃምዶክን ጨምሮ ከፍተኛ የሃገሪቱ ባለስልጣናት አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡ ሃምዶክ የማድቡሊ ጉብኝት የሃገራቱን ግንኙነት ከማሳደግም በላይ የጋራ ፍላጎቶቻቸውን ለማሳካት እንደሚያግዝ በይፋዊ የትዊተር ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡ “ይህ ጉብኝት የሕዝቦቻችንን ጥቅምና ብልጽግና የሚደግፍ እና በሁለቱ አገራት መካከል ጠንካራ ትስስር የሚያሰምር ውጤትን ያስገኛል ብለን ተስፋ እናደርጋለን” ሲሉም ነው ያሰፈሩት፡፡ ማድቡሊ በካርቱም በሚኖራቸው ቆይታ ከሃምዶክ እና ከሚኒስትሮቻቸው ጋር እንዲሁም ከሉዓላዊ የሽግግር ምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት ጄነራል አብደል ፋታህ አልቡርሃንና ሌሎች የምክር ቤቱ ወታደራዊ አመራሮች ጋር እንደሚመከሩም ይጠበቃል። #AlAin @ethiocheck

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የገንዘብ ሚኒስቴር የቢሮ እድሳት የደረሰበትን ደረጃ ጎበኙ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ባደረጉት ድንገተኛ ጉብኝት የገንዝብ ሚኒስትር የቢሮ እድሳት የደረሰበትን ደረጃ ጎበኙ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የገንዘብ ሚኒስቴር የቢሮ እድሳት የደረሰበትን ደረጃ ጎበኙ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ባደረጉት ድንገተኛ ጉብኝት የገንዝብ ሚኒስትር የቢሮ እድሳት የደረሰበትን ደረጃ ጎበኙ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የቢሮ እድሳቱ የደረሰበት ደረጃ አስደሳች ነው ብለዋል በፌስቡክ ገፃቸው ላይ:: በፐብሊክ ሰርቪስ ዘርፍ ምቹ የሥራ ሁኔታ መፍጠር ለተሻሻለ የአገልግሎት አሰጣጥ ቁልፍ ሚና ይጫወታልም ነው ያሉት፡፡ በእጁ የሚለካውን ያልሠራ በኅሊናው የሚለካውን አያሳካምና በማለት በፌስቡክ ገፃቸው ላይ ያሰፈሩት። Via fbc @ethiocheck

ሩሲያ የኮቪድ-19 ክትባት ማምረት ጀመረች የሩሲያ ጤና ሚኒስትር መሥሪያ ቤት ለኮሮናቫይረስ የተዘጋጀውን ክትባት ማምረት መጀመራቸውን አስታወቀ። ሚኒስቴሩ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ በብዛት የሚመረተ
ሩሲያ የኮቪድ-19 ክትባት ማምረት ጀመረች የሩሲያ ጤና ሚኒስትር መሥሪያ ቤት ለኮሮናቫይረስ የተዘጋጀውን ክትባት ማምረት መጀመራቸውን አስታወቀ። ሚኒስቴሩ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ በብዛት የሚመረተው ክትባት በያዝነው ወር መጨረሻ ላይ መከፋፈል እንደሚጀምር ገልጿል። ቢሆንም ግን በርካታ የዘርፉ ተመራማሪዎች ሩሲያ በችኮላ ያመረተችው ክትባት ሌላ መዘዝ ይዞ እንዳይመጣ ስጋታቸውን እየገለጹ መሆኑን ቢቢሲ ዝግቧል። @ethiocheck

#FakeNewsAlert በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የተላከ "የትግራይ ክልል ምርጫ መራዘሙን ስለማሳወቅ"' የሚል በፎቶ ሾፕ የተቀነባበረ ሀሰተኛ ደብዳቤ እየተዘዋወረ ይገኛል
#FakeNewsAlert በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የተላከ "የትግራይ ክልል ምርጫ መራዘሙን ስለማሳወቅ"' የሚል በፎቶ ሾፕ የተቀነባበረ ሀሰተኛ ደብዳቤ እየተዘዋወረ ይገኛል። ይህን ደብዳቤ ዋቢ እያደረጉ እጅግ በርካታ ተከታይ ያላቸው ሚዲያዎች ሳይቀሩ ሳያጣሩ እና ለማጣራትም ሳይሞክሩ እያሰራጩት ነው። ዛሬ ምሽት የትግራይ ክልል ምርጫ ኮሚሽን 6ኛው ክልላዊ ምርጫ ጳጉሜ 4/2012 ዓ/ም እንደሚደረግ ማስታወቁ ይታወቃል። @ethiocheck

የትግራይ ምርጫ ጳጉሜ 4/2012 ዓ.ም ይካሄዳል! የትግራይ ክልል የሚያካሂደው 6ኛ ክልላዊ ምርጫ ጳጉሜ 4/2012 ዓ.ም እንደሚካሄድ እና ለተፎካካሪ ፓርቲዎች የተፈቀደው የባጀት ድልድል ከነገ ጀምሮ
የትግራይ ምርጫ ጳጉሜ 4/2012 ዓ.ም ይካሄዳል! የትግራይ ክልል የሚያካሂደው 6ኛ ክልላዊ ምርጫ ጳጉሜ 4/2012 ዓ.ም እንደሚካሄድ እና ለተፎካካሪ ፓርቲዎች የተፈቀደው የባጀት ድልድል ከነገ ጀምሮ እንደሚለቀቅላቸው የትግራይ ክለልል የምርጫ ከሚሽን አስታውቋል፡፡ ምንጭ :-የምርጫ ከሚሽን ድህረ ገፅ @ethiocheck

"አቶ ለማ መገርሳ በፌዴሬሽን ምክር ቤት አባልነታቸዉ ይቀጥላሉ" - የጨፌ ኦሮሚያ ጽ/ቤት ሪፖርተር ጋዜጣ አቶ ለማ መገርሳ፣ ወ/ሮ ጠይባ ሀሰን እና ዶ/ር ሚልኬሳ ሚደጋ ከፌዴሬሽን ምክር ቤት አባልነ
"አቶ ለማ መገርሳ በፌዴሬሽን ምክር ቤት አባልነታቸዉ ይቀጥላሉ" - የጨፌ ኦሮሚያ ጽ/ቤት ሪፖርተር ጋዜጣ አቶ ለማ መገርሳ፣ ወ/ሮ ጠይባ ሀሰን እና ዶ/ር ሚልኬሳ ሚደጋ ከፌዴሬሽን ምክር ቤት አባልነታቸዉ ታግደዋል በማለት ይዞት የወጣዉ ዜና ሀሰት ነዉ ሲል የኦሮሚያ ክልል ኮሚውኒኬሽን ቢሮ አስታውቋል፡፡ አቶ ለማ መገርሳ በፌዴሬሽን ምክር ቤት አባልነታቸዉ ይቀጥላሉ ያለው ቢሮው ወ/ሮ ጠይባ ሀሰን እና ዶ/ር ሚልኬሳ ሚደጋ አስቀድሞኑ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት አይደሉም ሲልም ገልጿል፡፡ቢሮው በተለያዩ ምክንያት በተጓደሉ የፌዴሬሽን ምክርቤት አባላት ቦታ መተካካት መኖሩንም አንስቷል፡፡ በዚህም አቶ ፈቃዱ ተሰማ፣ አቶ ሳዳት ነሻ እና አቶ አብዱልሀኪም ሙሉ የፌዴሬሽን ምክርቤት አባላት በነበሩት አምባሳደር እሼቱ ደሴ (በአምባሳደርነት አየርላንድ ተመድበዉ በማገልገል ላይ ያሉ)፣ አቶ በከር ሻሌ (ኮሪያ ሀገር ትምህርት ላይ ያሉ) አቶ ሙክታር ከድር (ኮሪያ ሀገር ትምህርት ላይ ያሉ) የተተኩም ናቸው ብሏል፡፡ @ethiocheck

የኦነግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የግንባሩ ሊቀ-መንበር አቶ ዳውድ ኢብሳን በጊዜያዊነት ከኃላፊነት ማገዱን አስታወቀ፡፡ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር(ኦነግ) ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ባለፉት ሦስት ሳምንታት በግንባሩ
የኦነግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የግንባሩ ሊቀ-መንበር አቶ ዳውድ ኢብሳን በጊዜያዊነት ከኃላፊነት ማገዱን አስታወቀ፡፡ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር(ኦነግ) ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ባለፉት ሦስት ሳምንታት በግንባሩ ውስጥ የተፈጠሩትን አለመግባባቶች ለማረቅ ከተወያየ በኋላ ሊቀ-መንበሩ አቶ ዳውድ ኢብሳ ከኃላፊነታቸው እንዲታገዱ መወሰኑን የግንባሩ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ቀጀላ መርዳሳ አረጋግጠዋል፡፡ ከጥቂት ሳምንታት በፊት ሊቀ-መንበሩ አቶ ዳውድ ኢብሳ ለደህንነታቸው ሲባል ከቤታቸው እንዳይወጡ መከልከላቸውና በፀጥታ ኃይሎች ጥበቃ እየተደረገላቸው መሆኑ ከተሰማ በኋላ በግንባሩ ውስጥ አለመግባባቶች ስለማየላቸው ሲነገር ቆይቷል፡፡ ግንባሩ ሊቀ-መንበሩ በሌሉበት መግለጫዎችን ሲሠጥ እንደነበረም አይዘነጋም፡፡ አቶ ዳውድ ግንባሩ የሚሰጣቸው መግለጫዎችና የሚያደርጋቸው ስብሰባዎች ከእሳቸው እውቅና ውጭ መሆኑንም በተደጋጋሚ ሲናገሩ ተደምጠዋል፡፡ ይሁንና የግንባሩ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ ቀጀላ መርዳሳ እንዳረጋገጡት አቶ ዳውድ ኢብሳ ለጊዜው ከኃላፊነታቸው ታግደዋል፤ የሊቀ-መንበሩን ቦታም ምክትላቸው ተክቶ ይሰራል፡፡ የግንባሩ ሊቀ-መንበር በምን ምክንያት ታገዱ የሚለውን ጥያቄ ለአቶ ቀጀላ ቢያቀርብም ይህንን ለመናገር አሁን ጊዜው አይደለም የሚል ምላሽ አግኝቷል፡፡ @ethiocheck

በቀጣዮቹ የክረምት ወራት መደበኛና ከመደበኛ በላይ ዝናብ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለፀ በቀጣዮቹ የክረምት ወራት ነሀሴና መስከረም መደበኛና ከመደበኛ በላይ ዝናብ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የብሔራዊ ሚቲዮ
በቀጣዮቹ የክረምት ወራት መደበኛና ከመደበኛ በላይ ዝናብ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለፀ በቀጣዮቹ የክረምት ወራት ነሀሴና መስከረም መደበኛና ከመደበኛ በላይ ዝናብ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የብሔራዊ ሚቲዮሮሎጂ ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡ በዚህም የሰሜን ምዕራብና የምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች በአብዛኛው መደበኛና ከመደበኛ በላይ የዝናብ መጠን እንደሚኖራቸው ኤጀንሲ በሰጠው መግለጫ አመልክቷል። አብዛኛው የደቡብ ምዕራብ፣ የመካከለኛው፣ የምስራቅና የደቡብ ደጋማ እንዲሁም የሰሜን ምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎችም ከመደበኛ በላይ የሆነ ዝናብ እንደሚያገኙ ተገልጿል፡፡ ኤጀንሲው ከሚጠበቀው ከፍተኛ እርጥበት ጋር ተያይዞ በሰብሎች ማሳ ላይ የውሀ መተኛት ሊከሰት ስለሚችል የዘርፉ ባለሙያዎችና አርሶ አደሮች ቦይ በማውጣትና የውሀ ማጠንፈፍ ስራ በማካሄድ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል፡፡ በተጨማሪም ከሚፈጠረው ነጎድጓድ አዘልና በረዶ የቀላቀለ ከባድ ዝናብ ጋር ተያይዞ በአንዳንድ ቦታዎች ላይ የወንዞች ከመጠን በላይ መሙላት እንዲሁም ቅጽበታዊ ጎርፍ በረባዳማ ቦታዎችና ጎርፍ በሚያጠቃቸው አካባቢዎች ላይ ሊከሰት ስለሚችል የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ አስፈላጊውን ቅድመ ጥንቃቄ እንዲያደርጉም አሳስቧል፡፡ @ethiocheck

በመቀለ 'ሕገወጥ ሰልፍ ሊያካሂዱ ሲሉ ተይዘዋል' የተባሉ ዘጠኝ ወጣቶች ላይ ክስ ሊመሰረት ነው! በመቀለ 'ሕገወጥ ሰልፍ ሊያካሂዱ ሲሉ ተይዘዋል' የተባሉ ዘጠኝ ወጣቶች ላይ የትግራይ ፓሊስ ምርመራውን
በመቀለ 'ሕገወጥ ሰልፍ ሊያካሂዱ ሲሉ ተይዘዋል' የተባሉ ዘጠኝ ወጣቶች ላይ ክስ ሊመሰረት ነው! በመቀለ 'ሕገወጥ ሰልፍ ሊያካሂዱ ሲሉ ተይዘዋል' የተባሉ ዘጠኝ ወጣቶች ላይ የትግራይ ፓሊስ ምርመራውን በመጨረሱ ፋይላቸውን ክስ እንዲመሰረት ወደ ዐቃቤ ሕግ ማስተላለፉን ገልጿል። ከዚህ ቀደምም ሦስት ጊዜ ፍርድ ቤት መቅረባቸውንና ከሰባት ቀን በኋላ ክስ እንደሚመሰረትባቸው ነው ቢቢሲ የዘገበው። እንደ ቢቢሲ ዘገባ ወጣቶቹ ከ46 ቀናት በፊት፣ ሐምሌ ወር መጀመሪያ ላይ በመቀለ የሮማነት አደባባይ ላይ መንግሥትን በኃይል ለመጣል የሚያነሳሳ መፈክር ይዘው መገኘታቸውን እንዲሁም ያልተፈቀደ ሠልፍ ለማካሄድ ሲወጡ ፖሊስ በቁጥጥር ስር እንዳዋላቸው ገልጾ ነበር። ዘጠኙ ወጣቶች በሐምሌ ወር መጀመሪያ አካባቢ ላይ የክልሉን መንግሥት በመቃወም ሕገወጥ የተቃወሞ ሰልፍ ሊያካሂዱ ነበር በሚል በፖሊስ በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኀላ በወቅቱ በ48 ሰዓት ውስጥ ፍርድ ቤት ቢቀርቡም ፖሊስ በተደጋጋሚ የምርመራ ጊዜ ቀጠሮ በመጠየቅ ከ46 ቀናት በላይ በእስር ላይ ቆይተዋል። @ethiocheck

ኢንተርናሽናል ክራይስስ ግሩፕ በህወሓትና በፌደራል መንግሥቱ መካከል ያለው ፍጥጫ በንግግር ሊፈታ ይገባል ሲል መክሯል። ኢንተርናሽናል ክራይስስ ግሩፕ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታ፣ በተለይም የትግራይንና
ኢንተርናሽናል ክራይስስ ግሩፕ በህወሓትና በፌደራል መንግሥቱ መካከል ያለው ፍጥጫ በንግግር ሊፈታ ይገባል ሲል መክሯል። ኢንተርናሽናል ክራይስስ ግሩፕ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታ፣ በተለይም የትግራይንና የማዕከላዊውን መንግሥት ፍጥጫ ትኩረት ሰጥቶ በገመገመበት ባለ 14 ገጽ ሰነድ እንደጠቀሰው በኦሮሚያ ክልል የሰላም መደፍረስና የፌዴራል መንግሥት ከትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መስተዳደር ጋር የገባበት ፍጥጫ በንግግር ሊፈታ ይገባል ሲል መክሯል። ቡድኑ በሰነዱ እንደጠቀሰው ውጥረት ለማርገብ አስፈላጊ ከሆነም የአፍሪካ ሕብረት ወይም የአፍሪካ መሪዎች በማሸማገሉ በኩል ተሳትፎ ሊያደርጉ ይችላሉ ከማለት በተጨማሪ በተለይ የወቅቱ የአፍሪካ ሕብረት ሊቀ መንበር የሆኑት የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ ቁልፍ ሚና ሊጫወቱ ይችላሉ ብሏል። ሙሉ ዘገባውን ያንብቡ https://telegra.ph/BBC-08-14-2 @ethiocheck

የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ለማ መገርሳ ከትላንት ረቡዕ ነሐሴ 6፤ 2012 ጀምሮ በቤት እንዲቆዩ ትዕዛዝ መሰጠቱን የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ታማኝ ምንጮች ተናገሩ። አቶ ለማ በዚህ ሳምንት በስራ ቦታቸው
የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ለማ መገርሳ ከትላንት ረቡዕ ነሐሴ 6፤ 2012 ጀምሮ በቤት እንዲቆዩ ትዕዛዝ መሰጠቱን የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ታማኝ ምንጮች ተናገሩ። አቶ ለማ በዚህ ሳምንት በስራ ቦታቸው ላይ የታዩ ቢሆንም፤ ከትላንት ጀምሮ ግን ወደ ስራ ቦታ ጭምር እንዳይመጡ እንደተነገራቸው ምንጮች ገልጸዋል። የኢፌዲሪ የመከላከያ ሚኒስትር በመሆን ከሚያዝያ 2011 ጀምሮ እያገለገሉ ከሚገኙት ከአቶ ለማ በተጨማሪም ለጸሃፊያቸውም ተመሳሳይ ትዕዛዝ እንደተላለፈ ምንጮች አስረድተዋል። በትላንትናው ዕለት በአቶ ለማ ጽህፈት ቤት ላይ ብርበራ ስለመካሄዱ መረጃዎች ቢወጡም፤ የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ምንጮች ግን ይህንን አስተባብለዋል። ©Ethiopian insider

የተማሪዎች ነፃ ዝውውር ውሳኔ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ቤት ለመመለስ ያለመ መሆኑን የኢፌደሪ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ባሕር ዳር፡ ነሐሴ 7/2012 ዓ.ም (አብመድ) በትምህርት ሚኒስቴር የተላላፈው ከ8ኛና 12ኛ ክፍል ውጪ ያሉ ተማሪዋች ነፃ ዝውውር ተማሪዋች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመለሱ ለማበረታታት መሆኑን ሚኒስቴሩ አስታውቋል፡፡ የትምህርት ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ዶክተር ኢንጂነር) እንዳሉት ውሳኔው በኮሮና ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የትምህርት መርሃ ግብር ሲጀመር ተማሪዋች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመለሱ ለማበረታታት እና ወረርሽኙ የፈጠረውን ጫና ለመቀነስ የታሰበ ነው። በአሁን ሰዓት ትኩረት ሰጥተን እየሰራን ያለነው ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ቤት መመለስ ላይ ነው ያሉት ሚኒስትሩ በቀጣይም ተማሪዋች ወደ ትምህርት ቤት ከተመለሱ በኋላ የትምህርት ጥራቱ ላይ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል። የትምህርት ጥራቱን ችግር በዘላቂነት ለመፍታትም በ2014 ዓ.ም ወደ ተግባር የሚገባ አዲስ ስርዓተ ትምህርት እየተዘጋጀ መሆኑም አስታውቀዋል ። በነፃ ዝውውር የተዘዋወሩ ተማሪዋች የትምህርት ምዕራፉ ሲጀመር በተዘዋወሩበት የትምህርት ክፍል ባለፈው የትምህርት ምዕራፍ ላይ ማካካሻ ወስደው ቀጣዪን የትምህርት መርሃ ግብር የሚቀጥሉ ይሆናልም ነው ያሉት። በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ትምህርት ቤቶች በመዘጋታቸው ከ 26 ሚሊየን በላይ ተማሪዋች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸው ከትምህርት ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመላክታል ። የትምህርት ሚኒስቴር ከ 8ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዋች ውጪ የነፃ ዝውውር ውሳኔ ማሳለፉ የሚታወስ ነው። @ethiocheck

የግድቡ አጠቃላይ የሲቪል ሥራ 88 ነጥብ 5 %፤ አፈፃፀሙ ደግሞ 75% መድረሱ ተገለጸ! አዲስ አበባ፡- የግድቡን አጠቃላይ የሲቪል ሥራ 88 ነጥብ 5 በመቶ፤ አጠቃላይ የግንባታ ፕሮጀክቱን ሥራ ደግሞ
የግድቡ አጠቃላይ የሲቪል ሥራ 88 ነጥብ 5 %፤ አፈፃፀሙ ደግሞ 75% መድረሱ ተገለጸ! አዲስ አበባ፡- የግድቡን አጠቃላይ የሲቪል ሥራ 88 ነጥብ 5 በመቶ፤ አጠቃላይ የግንባታ ፕሮጀክቱን ሥራ ደግሞ 75 በመቶ ላይ እንዳደረሰው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጅነር ክፍሌ ሆሮ ገለጹ። የዋናው ግድብ ሥራ፣ የኮርቻ ግድብ፣ የጎርፍ ማስተንፈሻና የኃይል ማመንጫ ሥራዎችን የሚያጠ ቃልለው የግድቡ አጠቃላይ የሲቪል ሥራ 88 ነጥብ 5 በመቶ፤ የኤሌክትሮ መካኒካል ሥራዎች ወደ 46 በመቶ፣ የብረታ ብረት ሥራው ደግሞ ወደ 33 በመቶ ከፍ አድርጓል። ይህም አጠቃላይ የግድብ ግንባታ ፕሮጀክቱን 75 በመቶ እንዲደርስ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል ብለዋል። ከመጀመሪያው ዙር ውሃ ሙሌት በኋላ የግንባታ ሥራዎች የቀጠሉ መሆናቸውን፤ በዚህም ሁለት ተርባይኖችን በመጠቀም በቀጣዩ ዓመት ኃይል ለማመ ንጨት የግድቡ ቀኝና ግራ የብረታ ብረት ሥራዎችና የጀኔሬተር ተከላዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል። - #EPA @ethiocheck

የኢትዮጰያ ሰባዊ መብት ኮምሽን በወላይታ ዞን የቀጠለው ሁከት እና የፀጥታ ኃይሎች በሰልፈኞች ላይ የሚጠቀሙት ከመጠን ያለፈ ኃይል በእጅጉ እንዳሳሰበው ተናገረ፡፡ ኮሚሽኑ በዞኑ ሁከቱ ከተቀሰቀሰበት ነሐሴ 4 ጀምሮ፣ ረቡዕ ዕለት ለሞት የተዳረገ 1 ተጨማሪ ሰውን ጨምሮ፣ የሟቾች ሰዎች ቁጥር ወደ 17 ማሻቀቡን ጠቅሷል፡፡ ከሟቾቹ ውስጥ ሕጻናት እንደሚገኙበትም የኮሚሽኑ መግለጫ አመልክቷል፡፡ ሶዶ ውስጥ ጉዳት የደረሰባቸው 3 ሰዎች ሕይወታቸው አስጊ ሁኔታ እንደሚገኝ የጠቀሰው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የፀጥታ ኃይሎች በተቻላቸው መጠን ኃይል ከመጠቀም እንዲታቀቡ አሳስቧል፡፡ የፀጥታ ኃይሎች በሰላማዊ መንገድ ተቃውሟቸውን በሚገልፁ ሰልፈኞች ላይ ሕይወትን አደጋ ላይ የሚጥል ኃይል ከመጠቀም መቆጠብ አለባቸው፤እንዲህ ዓይነት ድርጊቶች እንዲሁም ውጥረት የመላበትን ሁኔታ ከማባባስ ውጪ ፋይዳ አይኖረውም ብሏል ኮሚሽኑ ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዳጋቶ ኩምቤን ጨምሮ ባለፈው እሑድ በፀጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ሥር የዋሉ የዞኑ ባለሥልጣናትና የማኅበረሰብ መሪዎች ትናንት ከሰዓት በኋላ ፍርድ ቤት መቅረባቸው ተሰምቷል። የባለሥልጣናቱን በቁጥጥር ስር መዋል ተከትሎ በዞኑ የተለያዩ ወረዳዎችና ከተሞች የተቀሰቀሰው ተቃውሞም ትናንት በቦዲቲ ከተማ መቀጠሉ ተሰምቷል፡፡ Via:- Sheger FM @ethiocheck

የኦነግ አመራሮች ውዝግብ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ሃምሌ 19 እና 20 ካካሄደው አስቸኳይ የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ በኋላ በአመራሮቹ መካከል የተነሳው ውዝግብ ያለ ሁነኛ መፍትሄ እንደቀጠለ ነው። በትና
የኦነግ አመራሮች ውዝግብ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ሃምሌ 19 እና 20 ካካሄደው አስቸኳይ የማዕከላዊ ኮሚቴ  áˆľá‰Ľáˆ°á‰Ł በኋላ በአመራሮቹ መካከል የተነሳው ውዝግብ ያለ ሁነኛ መፍትሄ እንደቀጠለ ነው። በትናንትናው እለት በሊቀመንበሩ አቶ ዳውድ ኢብሳ ይሁኝታ የወጣ ነው የተባለው መግለጫ ስድስት የግንባሩ አመራሮች ለጊዜው ከስራ መታገዳቸውን ጠቁሟል፡፡ ታግደዋል የተበሉ አመራሮችም የግንባሩ ምክትል ሊቀመንበርን ጨምሮ ያለ ሊቀመንበሩ ይሁኝታ በማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባው እና ሰኞ እለት በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ የተሳተፉት ናቸው፡፡ በማዕከላዊ ኮሚቴው ስብሰባ እና በሂልተኑ የድርጅቱ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የተሳተፉት የግንባሩ ቃል አቀባይ አቶ ቶሌራ አደባ እንደተናገሩት እሳቸውን ጨምሮ ሌሎች አምስት አመራሮች ላይ እግድ ያስተላለፈው መግለጫ፣ የሊቀመንበሩ አቶ ዳውድ ኢብሳ ይሁኝታ ያለው ነው ብለዋል። የኦነግ ሊቀ መንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ በበኩላቸው በፓርቲው አመራሮች መካከል የተፈጠረው ልዩነት በሕግና በቁጥጥር ኮሚቴ የተያዘ በመሆኑ ማብራሪያ ሊሰጡ እንደማይችሉ ተናግረዋል። @ethiocheck

የአማራ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ለሁለት ቀን ያካሄደውን የከፍተኛ አመራሮች ውይይት መጠናቀቁንና በውይይቱ የተነሱ ጉዳዮች አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል። የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አገኘሁ ተሻገር በሰጡት መግለጫ ፓርቲው በሁለት ዓመት የለውጥ ጉዞ ፣ ብልፅግና ፓርቲ ከመምጣቱ በፊትና ከመጣ በኋላ ስለመጣው ለውጥ መወያየቱን ገልፀዋል። ለውጡ የሁሉም የሀገሪቱ ህዝቦች መሆኑን መገምገሙንና በቀጣይ ለውጡን ለማስቀጠልና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ከሌሎች ክልሎች ጋር በጋራ እንደሚሰራ ነው የተናገሩት። በክልሉ ህገወጥ አደረጃጀት በማፍረስ እና ህገ ወጦችን ለህግ በማቅረብ በኩል የተሰራው ስራ በመድረኩ በጥሩ መልኩ መነሳቱን ገልፀዋል። ክልሉ አሁን ላይ ሰላሙ የተረጋገጠ መሆኑንና በቀጣይ የቱሪዝም ልማት ለማከናወን በውይይቱ መነሳቱን አብራርተዋል። ሌላው የአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ግድያን ተከትሎ በኦነግ ሸኔና ህወሃት ሴራ በዜጎች ላይ የተፈፀመውን ግድያና የሀብት ውድመት ፓርቲው ማውገዙን አቶ አገኘሁ ገልፀዋል። የኦሮሚያ ክልል መንግስትን ህግ የማስከበር ስራ የአማራ ብልጽግና ፓርቲ ፅህፈት ቤት እንደሚያደንቅና እውቅና እንደሚሰጠው አቶ አገኘሁ ተናግረዋል። በፓርቲው አመራር በቅርቡ ተናግሯል ተብሎ በወጣው መረጃ ዙሪያ መረጃ ለምን አሁን ወጣ? የሚለው በጥንቃቄ ለመገምገም ተሞክሯል ብለዋል። ይሁንና በአመራሩ የተነሱት ሀሳቦች በይዘትም ስህተት መሆኑንና በፓርቲ ደረጃ በዝርዝር መገምገም እንዳለበት አይተናል ብለዋል። የአማራና የኦሮሞን ህዝቦች መልካም ግንኙነት ማንም አይበጥሰውም ያሉት አቶ አገኘሁ በየትኛውም መንገድ የማይወዛወዝ ወንድማማችነት ያላቸው ህዝቦች ናቸው ብለዋል። በተመሣሣይ ከትግራይ ወንድማማች ህዝቦች የአማራን ህዝብ ህወሃት ሊነጥለው እንደማይችልም ነው የተናገሩት። ከዚህ ባለፈ በአማራ ብልፅግና ፓርቲ አመራሮች መካከል ልዩነት ተፈጥሯል የሚለው መሰረተ ቢስ መሆን በመግለፅ የአመራሩን አንድነት ለመለያየት በማህበራዊ ሚዲያዎች የተከናወነ ነው ብለዋል። አመራሩ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ አንድ መሆኑንም አንስተዋል። በናትናኤል ጥጋቡ @ethiocheck

#የሀሰት_ዜና አቶ ለማ መገርሳ፣ ወ/ሮ ጠይባ ሀሰን እና ዶ/ር ሚልኬሳ ከፌዴሬሽን ምክር ቤት አባልነታቸዉ ታግደዋል ተብሎ ሪፖርተር ጋዜጣ ላይ የወጣዉ ዜና ሀሰት ነዉ፡፡ ኦቦ ለማ መገርሳ በፌዴሬሽን
#የሀሰት_ዜና አቶ ለማ መገርሳ፣ ወ/ሮ ጠይባ ሀሰን እና ዶ/ር ሚልኬሳ ከፌዴሬሽን ምክር ቤት አባልነታቸዉ ታግደዋል ተብሎ ሪፖርተር ጋዜጣ ላይ የወጣዉ ዜና ሀሰት ነዉ፡፡ ኦቦ ለማ መገርሳ በፌዴሬሽን ምክር ቤት አባልነታቸዉ ይቀጥላሉ፡፡ ወ/ሮ ጠይባ ሀሰን እና ዶ/ር ሚልኬሳ ሚደጋ ሲጀመር የፌዴሩሽን ምክር ቤት አባላት አልነበሩም፡፡ #የኦቦ ለማ መገርሳና ወ/ሮ ጠይባ ሀሰን የቁም እስር ላይ ናቸዉ፣ ቤታቸዉ ተከቧል ተብሎ የሚናፈሰዉ ወሬም ውሸት ነዉ። ኦቦ ለማ መገርሳ መደበኛ ስራቸዉ ላይ ናቸው። @ethiocheck

ኦቦ ለማ መገርሳ ለቪኦኤ ኦሮምኛ ክፍል የራዲዮ ፕሮግራም ስለ ብልጽግና ፓርቲ ምስርታና አቋማቸው በሰጡት ኢንተርቪው የኦሮሚያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርጫፍ ማዕከላዊ ኮሚቴን (ODP) አቶ ለማን ገምግ
ኦቦ ለማ መገርሳ ለቪኦኤ ኦሮምኛ ክፍል የራዲዮ ፕሮግራም ስለ ብልጽግና ፓርቲ ምስርታና አቋማቸው በሰጡት ኢንተርቪው የኦሮሚያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርጫፍ ማዕከላዊ ኮሚቴን (ODP) አቶ ለማን ገምግሟቸው ማዕከላዊ ኮሚቴውን ይቅርታ ጠይቀው እንደነበር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኚ የኦሮሚያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርጫፍ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልና የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ገልፀዋል :: ምክትል ርዕሰ መስተዳድሯ አቶ ለማ ከድርጅት ስብሰባዎች ላይ ካለመገኘት አልፎ የድርጅቱን ሚስጥ በማውጣትና ከጠላት ጋር አብረው በመቆም ሁለት ቦታ በመርገጥ ፓርቲው ገምግሞ ከማዕከላዊ ኮሚቴ ለግዜው እንዳገዳቸው ምክትል ርዕሰ መስተዳድሯ አክለው ገልጸዋል:: @ethiocheck