en
Feedback
AIRDROP ROOM

AIRDROP ROOM

Open in Telegram
2 485
Subscribers
No data24 hours
-157 days
-5230 days
Posts Archive
የአቶ ለማ ቀጣይ የፖለቲካ ጉዞ የተለያዩ መላምቶችን እያሰጠ ነው በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ምናልባትም ዘመን ተሻጋሪ አሻራን ስለማሳረፋቸው በርካቶች የሚመሰክሩላቸው የቀድሞ የመከላከያ ሚንስትር
የአቶ ለማ ቀጣይ የፖለቲካ ጉዞ የተለያዩ መላምቶችን እያሰጠ ነው በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ምናልባትም ዘመን ተሻጋሪ አሻራን  áˆľáˆˆáˆ›áˆłáˆ¨á‹á‰¸á‹ በርካቶች የሚመሰክሩላቸው የቀድሞ የመከላከያ ሚንስትር ለመባልም የበቁት አቶ ለማ መገርሳ አሁን ላይ የራሳቸውን መንገድ የለዩ መስለዋል፡፡ አስቀድሞም በመደመርና በብልጽግና አካሄድ አልተስማማሁም በሚል ለሚዲያ ወጥተው የተናገሩት አቶ ለማ ምናልባትም መርተው እዚህ ደረጃ ላይ በማድረስ የተሳተፉበትን የለውጥ ሂደት ትተው ለመውጣት የባቀቻው ገፊ ምክኒያት ምን ይሆን የሚል ጥያቄ ግን በበርካቶች አዕምሮ ዘንድ በቂ ምላሽን አላገኘም፡፡ የፓርቲ ተሳትፎአቸው መቋረጥ ከሳምንት በፊት ሲሰማ በመንግስታዊ ኃላፊነታቸው ይቀጥሉ ይሆናል የሚል ተስፋን ያላሟጠጠ ቢሆንም በትናንትናው እለት በእሳቸው የኃላፊነት ቦታ አዲስ የመከላከያ ሚንስትር የመሾሙ ዜና ይፋ መሆንን ተከትሎ የአቶ ለማ ቀጣይ የፖለቲካ ጉዞ የተለያዩ መላምቶችን እያሰጠ ነው፡፡ አስተያየታቸውን ለዶይቼ ቨሌ ያጋሩት የፖለቲካ፣ የጋዜየኝነት እና የህግ  á‰Łáˆˆáˆ™á‹Ťá‹Žá‰˝ አቶ ለማ መገርሳ ከመንግስታዊ ኃላፊነታቸውም ጭምር መለየታቸው አሁን እርግጥ ቢሆንም በኢትዮጵያ ፖለቲካ ያላቸው ሚና ግን አሁንም እንደማያበቃ ምልከታቸውን አስቀምጠዋል፡፡ @ethiocheck

ለህዳሴ ግድብ ግንባታ እስካሁን 13 ቢሊዮን 800 ሚሊዮን ብር ከሕዝብ ተሰብስቧል! የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የመጀመሪያው ዙር ውኃ ሙሌት ከተከናወነ በኋላ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ብቻ ለግንባታው
ለህዳሴ ግድብ ግንባታ እስካሁን 13 ቢሊዮን 800 ሚሊዮን ብር ከሕዝብ ተሰብስቧል! የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የመጀመሪያው ዙር ውኃ ሙሌት ከተከናወነ በኋላ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ብቻ ለግንባታው የሚውል ከ116 ሚሊዮን 473 ሺህ 348 ብር ገቢ ተገኝቷል። ባለፈው ሐምሌ ወር ብቻ ከ8100 “A” አጭር የጽሑፍ መልእክት ገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ-ገብር ከ11 ሚሊዮን 271 ሺህ ብር በላይ ገቢ መገኘቱን የግድቡ ግንባታ ሕዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽ/ቤት አስታውቋል። በዚሁ ወር ከቦንድ ግዢ እና ከስጦታ ደግሞ 105 ሚሊዮን 201 ሺህ 874 ብር መሰብሰቡን የጽ/ቤቱ የሚዲያ እና ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ኃይሉ አብርሃም ገልጸዋል። የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ከተጀመረ ጊዜ አንስቶ እስካሁን በአጠቃላይ 13 ቢሊዮን 800 ሚሊዮን ብር ከሕዝብ ተሰብስቧል። #ENA @ethiocheck

ከ80 ዓመት በኀላ ኢትዮጵያ ከፍተኛ የህዝብ ቁጥር ከሚገኝባቸው ሀገራት አንዷ ትሆናለች! "ዘ ላንሰት" የተባለው የሳይንስ ጥናቶችን የሚያወጣ መፅሄት ከ80 አመት በሁዋላ ኢትዮጵያ በአለም ላይ ከፍተኛ
ከ80 ዓመት በኀላ ኢትዮጵያ ከፍተኛ የህዝብ ቁጥር ከሚገኝባቸው ሀገራት አንዷ ትሆናለች! "ዘ ላንሰት" የተባለው የሳይንስ ጥናቶችን የሚያወጣ መፅሄት ከ80 አመት በሁዋላ ኢትዮጵያ በአለም ላይ ከፍተኛ የህዝብ ቁጥር ከሚገኝባቸው 8 ሀገራት አንዷ እንደምትሆን ጠቁሟል! በመፅሄቱ ዘገባ መሰረት ህንድ፣ ናይጄርያ፣ ቻይና፣ አሜሪካ፣ ፓኪስታን፣ ዴሞክራቲክ ኮንጎ፣ ኢንዶኔዥያ እና ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2100 ከፍተኛ የህዝብ ቁጥር ያላቸው ስምንት የአለማችን ሀገራት ይሆናሉ። በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ የህዝብ ብዛት ከሰማንያ አመት በሁዋላ 223.5 ሚልዮን ይደርሳል ተብሎ ተገምቷል። አሁን ላይ የኢትዮጵያ የህዝብ ቁጥር ከ115 ሚሊዮን በላይ ( #worldometer ) ይሆናል ተብሎ ይገመታል፡፡ @ethiocheck

#NewsUpdate ትላንትና ዛሬ በአወዳይ ከተማ አለመረጋጋት መኖሩን በዚህም ህይወታቸው ያለፉ ሰዎች መኖራቸውን ቢቢሲ የአከባቢውን ነዋሪዎች ጠይቆ ዘግቧል። ቢቢሲ ያናገረው የአወዳይ ከተማ ነዋሪ ትላ
#NewsUpdate ትላንትና ዛሬ በአወዳይ ከተማ አለመረጋጋት መኖሩን በዚህም ህይወታቸው ያለፉ ሰዎች መኖራቸውን ቢቢሲ የአከባቢውን ነዋሪዎች ጠይቆ ዘግቧል። ቢቢሲ ያናገረው የአወዳይ ከተማ ነዋሪ ትላንት 6:00 ሰዓት አከባቢ አቶ ጃዋር መሐመድ መታመሙን ሲሰማ 'መታከም አለበት መለቀቅ አለበት' ብለው መፈክር ይዘው መውጣት ሲጀመሩ የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ፓሊስ እና የመከላከያ ሰራዊት ሰዎችን ማስቆም መጀመራቸውን ይናገራል። ከዚያም ተኩስ ተከፍቶ ወደ 10 ሰዎች በጥይት መመታታቸውን የተናገረው ነዋሪው 'እኔ በዓይኔ ያየውት ሁለት ሰዎች ተገለዋል ዛሬ ደግሞ 4 ሰዓት ተኩስ ነበር አንድ ሰውም ሞቷል። አሁን ላይ እንቅስቃሴዎች ቆመዋል' ሲል አስተያየቱን ሰጥቷል። የጭሮ ሆስፒታል ተጠባባቂ ዳይሬክተር ዶ/ር ሳዳም አሉዋን በበኩላቸው ወደ ሆስፒታሉ የመጡ ሰዎች ወደ 24 እንደሚጠጉ ለቢቢሲ ገልጸዋል። ከእነዚህም መካከል ሁለት ሰዎች ህይወታቸው ማለፉንም ነው የገለጹት። ከሞቱት ሰዎች መካከል አንዷ እድሜያቸው በአርባዎቹ የሚገኝ ሲሆን አንዱ ደግሞ የ20 ዓመት ወጣት ነው ሲሉ ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። ሁለቱም ጀርባቸውን መመታታቸውን ጭምር ነው የገለጹት። የአሮሚያ ክልል መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ አቶ ጌታቸው ባልቻ በበኩላቸው በአወዳይ፣ በአሳሳና ዶዶላ አከባቢዎች የተወሰኑ እንቅስቃሴዎች መደረጋቸውን የጠቀሱ ሲሆን ድርጊቱ ከሙከራ ያለፈ አይደለም መንገድም ክፍት ነው ሲሉ ገልጸዋል። አክለውም ሁሉም ሰው በህግ ፊት እኩል ነው። በህግ መጠየቅ ያለበት በህግ ይጠየቃል ሰዎች ድምጻቸውን ማሰማት የሚፈልጉ ከሆነ ህጋዊ ስርዓቱን ተከትለው ለሚመለከተው አካል ስለ ሰላማዊ ሰልፉ አሳውቀው ማሰማት ይችላሉ ከዚህ ውጪ በዘፈቀደ የሚኖርባት ሀገር አይደለችም ብለዋል። #BBC @ethiocheck

አምነስቲ ኢንተርናሽል ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ ላይ ያወጣው ዘገባ ስህተት መሆኑን ገልጾ ይቅርታ ጠየቀ፡፡ አምነስቲ ኢንተርናሽናል የተሰኘው ድርጅት ግንቦት 2012 ዓመተ ምህረት በኢትዮጵያ በተለይም በ
አምነስቲ ኢንተርናሽል ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ ላይ ያወጣው ዘገባ ስህተት መሆኑን ገልጾ ይቅርታ ጠየቀ፡፡ አምነስቲ ኢንተርናሽናል የተሰኘው ድርጅት ግንቦት 2012 ዓመተ ምህረት በኢትዮጵያ በተለይም በኦሮሚያና አማራ ክልሎች ስላለው የሰብዓዊ መብት አያያዝ ሪፖርት ማውጣቱ የሚታወስ ነው፡፡ ይህን ተከትሎ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ የማጣራት ተግባር በማከናወን የአምነስቲ ኢንተርናሽናል ሪፖርት መንግስት ሕግ ለማስከበር የሚወስደውን እርምጃዎች ሁሉ የሰብዓዊ መብት ጥሰት አድርጎ የማጠልሸት ዝንባሌ የሚስተዋልበት መሆኑን የሚገልፅ መግለጫ አውጥቶ ነበር፡፡ የኢፌዴሪ ጠቅላይ አቃቤ ህግ በዚህ መግለጫውም የአምነስቲ ኢንተርናሽናል ሪፖርት በአብዛኛው ገለልተኘነት የጎደለው፣ የማስረጃ ምዘና ችግር ያለበት፣ የሃገሪቱን ነባራዊ ሁኔታ እና ዐውድ ያላገናዘበ እና ሌሎችም መሰርታዊ ግድፈቶች ያሉበት እንደሆነ በመግለጽ ድርጅቱ ካወጣቸው ሪፖርቶችና በከፊል ተዐማኒነት ካላቸው ጉዳዮች መካከልም ቢሆን በርካቶቹ ጉዳያቸው በአምነስቲ ሪፖርቱ ከመውጣቱም በፊት በመንግስት ታውቀው የምርመራ ስራ ሲከናወንባቸው እንደነበር በመግለጽ በሪፖርት አዘጋጆቹ ዘንድ የፖለቲካ ወገንተኛነት እንደሚታይ አስታውቆም ነበር። በመሆኑም አምነስቲ ኢንተርናሽናል ትላንት በቲውተር ገጹ ባሰፈረው ጽሁፍ ሪፖርቱ አሉታዊ ተፅኖ የነበረው ከስህተት ጋር የወጣ ነው በማለት ይቅርታ ጠይቋል፡፡ ይህንንም ተከትሎ የኢፌዴሪ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ባወጣው መግለጫ እንደ አምነስቲ ኢንተርናሽል አይነት ትልቅ ድርጅት የአንድ ሀገርን ገጽታ ሊያበላሽ የሚችል ስህተት መስራትና ማሰራጨት ከድርጅቱ የማይጠበቅ መሆኑን ጠቅሷል በመሆኑም ለወደፊቱ ተዓማኒነት የሌላቸው መረጃዎችን ከማሰራጨቱ በፊት ስለመረጃው ትክክለገኛነት ከሚመለከተው አካል ማጣራት ተገቢ መሆኑን ነው ያመለከተው @ethiocheck

አዲስ አበባ 32ተኛ ከንቲባ ዛሬ ተሹሞላታል! ኢህአዴግ አገሪቱን ከተቆጣጠረ በኋላ እንደ አርከበ ዕቁባይ (ዶ/ር) እና እንደ ታከለ ኡማ (ኢንጂነር) የተወደደም፣ የተቸም የለም። ዶ/ር አርከበ አፍርሶ
አዲስ አበባ 32ተኛ ከንቲባ ዛሬ ተሹሞላታል! ኢህአዴግ አገሪቱን ከተቆጣጠረ በኋላ እንደ አርከበ ዕቁባይ (ዶ/ር) እና እንደ ታከለ ኡማ (ኢንጂነር) የተወደደም፣ የተቸም የለም። ዶ/ር አርከበ አፍርሶ በመገንባት ኢ/ር ታከለ ደግሞ በማህበራዊ ተሳትፎአቸው ተወዳጆች ነበሩ። በመጨረሻ ኢ/ር ታከለ እንዲነሱ ሲወሰን ሶስት ሠዎች እንዲተኳቸው ታጭተው ነበር: አለሙ ስሜ (ዶ/ር) አቶ አሰግድ ጌታቸው እና አቶ ረሻድ ከማል። ሦስቱም ፍላጎት ባለማሳየታቸው አዲስ አበባን የመምራት ኃላፊነት ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ላይ ወድቋል። Via Wudineh Zenebe @ethiocheck

32 የኦነግ ሸኔ አባላት ለሰላማዊ ትግል እጃቸውን ሰጡ በምዕራብ ጉጂ ዞን ገላና ወረዳ በትጥቅ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 32 የኦነግ ሸኔ አባላት ሰላማዊ ትግል በመምረጥ እጃቸውን ሰጡ፡፡ የምዕራብ ጉጂ ዞን ዋና አሰተዳደር አቶ ተፈሪ ወንድይፍራው ለዋልታ በደረሰው መረጃ ከዚህን በፊት ዞኑ በጸጥታ ችግር ውሰጥ እንደቆየ ሲሆን ዛሬ ላይ ግን ከህዝብ ጋር በተሰራ ስራ 32 የኦነግ ሸኔ አባላት እጃቸውን መስጠታቸውን ተናግረዋል፡፡ አባላቱ የተሰጠን ተልዕኮ አሁን በሀገር ደረጃ እየታየ ያለውን ለውጥ ማደናቀፍና የህዳሴውን ግድብ ጨምሮ ሌሎች መሰረተ ልማቶችንና ንጹሐን ዜጎችን ማጥቃት ነበር ብለዋል፡፡ የምዕራብ ጉጂ ዞን አሰተዳደር በበኩሉ የተጀመረውን የጸረሠላም ሀይል ማጥራት ዘመቻ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል፡፡ ከአባላቶቹ መካካል አቶ ገልማ ቦሩ ወይም የትግል ሰሙ ዲና ራሳ የተባለው ካተሰጠው ስም አወጣጥ ጀምሮ ህዝቡን እንዲገድል እና ጥፋት እንዲያደረስ ተልዕኮ እደተሰጠው ገልጾ፣ መሰረተ ልማቶችንና ንጹሐዋን ዜጎችን ለማጥቃት ይተጉ እንደነበር ተናግሯል፡፡ ሌላው የኦነግ ሸኔ አባል የሆነው አበበ ጂሎ ወይም አብዲ ሰባ እንደሚለው እኔ አረሶ አደር ነበረኩ እነሱ በውሸት ሰብከው ወደነሱ ገብቼ ሰልጠናን በመውሰድ መቀላቀሉን ገልጾ፣ ተግባራቸው አሰነዋሪ በመሆኑን እይቶ እጅ መሰጠቱን አስረድቷል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ አጋ አረቦ ወይም ቄራንሶ ሰባ እሱም እንደ ጓደኞቹ በትግል ዘመኑ ሁሉ ከኦነግ ሸኔ የቀሰመው ነገር ቢኖር መግደልና መዝረፍ መሆኑን ተናግሮ፣ የኦሮሞን ኩሩ ህዝብ ንብረቱን በማውደም በዕኩይ ተግባራት የተሰማሩ በመሆኑ ይህን ሀይል በቶሎ ማክሰም ተገቢ እንደሆነ ተናግሯል፡፡ •ዘገባውን ያደረሰን የገላና ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ነው። @ethiocheck

#BREAKING ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስር ሹመቶችን ዛሬ ሰጡ:- - ዶ/ር ቀንዓ ያደታ የመከላከያ ሚኒስትር - ዶ/ር ጌድዮን ጢሞቴዎስ፤ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ - ዶ/ር ሳሙኤል ሁርካቶ፤ የሳይ
#BREAKING ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስር ሹመቶችን ዛሬ ሰጡ:- - ዶ/ር ቀንዓ ያደታ የመከላከያ ሚኒስትር - ዶ/ር ጌድዮን ጢሞቴዎስ፤ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ - ዶ/ር ሳሙኤል ሁርካቶ፤ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር - ታከለ ኡማ፤ የማዐድንና ነዳጅ ሚኒስትር - ተስፋዬ ዳባ፤ ምክትል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ - ዮሐንስ ቧያለው፤ የኢትዮጵያ የውጭ ግነኙነት ስትራቴጂክ ጥናት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር - ንጉሡ ጥላሁን፤ የሥራ ዕድል ፈጠራ ኮሚሽን ኮሚሽነር - እንደአወቅ አብቴ፤ የብረታ ብረት ኢንጅኔሪንግ ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ዳይሬክተር - ፍቃዱ ጸጋ፤ ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ - ፕሮፌሰር ኂሩት ወልደ ማርያም፤ በሚኒስትር ማዕረግ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማኅበራዊ ዘርፍ አማካሪ ምንጭ፦ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት @ethiocheck

ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ከባንክ ውጭ ግለሰቦች ወይም ኩባንያዎች ማስቀመጥ ተከለከለ! የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገዥ ዶክተር ይናገር ደሴ በዛሬው እለት መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸው በኢትዮጵ
ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ከባንክ ውጭ ግለሰቦች ወይም ኩባንያዎች ማስቀመጥ ተከለከለ! የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገዥ ዶክተር ይናገር ደሴ በዛሬው እለት መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸው በኢትዮጵያ ግለሰቦች ወይንም ኩባንያዎች ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ከባንክ ውጭ ማስቀመጥ መከልከሉን ይፋ አድርገዋል። የመንግስትም ሆኑ የግል ባንኮች ከውጭ አበዳሪ ተቋማት በዶላር መበደር ይችላሉም ተብሏል። ይህ አሰራር ደግሞ በአገሪቱ የሚስተዋለውን የውጭ ምንዛሬ እጥረት ለማቃለል ይረዳል ብለዋል። የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ወደ ባንክነት ማደግ የሚችሉበት መመሪያ መውጣቱን ዶክተር ይናገር ይፋ አድርገዋል #ENA @ethiocheck

''12፣12፣12'' በሚል ስያሜ የተጠራው ሰልፍ ሕገ-ወጥ ነው - የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ************* "12፣12፣12" በሚል ስም ለገ ነሐሴ 12 ቀን 2012 ዓ.ም የተጠራው ሰልፍ ሕገ-ወ
''12፣12፣12'' በሚል ስያሜ የተጠራው ሰልፍ ሕገ-ወጥ ነው - የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ************* "12፣12፣12" በሚል ስም ለገ ነሐሴ 12 ቀን 2012 ዓ.ም የተጠራው ሰልፍ ሕገ-ወጥ እና የጥሪው ዓላማም ፀረ-ሰላም በመሆኑ ኅብረተሰቡ ለዚህ ስልፍ ተባባሪ እንዳይሆን የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አሳሰበ። በሌላ በኩል "አቶ ጀዋር መሐመድ ታሟል፤ ችግር ደርሶበታል" ተብሎ በተለያዩ የሚዲያ አውታሮች የሚወራው ሐሰተኛ መረጃ መሆኑን እና ግለሰቡ በተሟላ ጤንነት ላይ የሚገኝ መሆኑን ፖሊስ ኮሚሽኑ ገልጿል። በመሆኑም በዚህ ሰበብ ሰውን እያወናበዱ በሐሰተኛ ወሬ የፍርድ ሂደቱን ለማዛባት የሚደረገው ጥረት በማንኛውም ሁኔታ ተቀባይነት የሌለው ተግባር መሆኑን ኅበረተሰቡ ተገንዝቦ ለሕ-ገወጥ ጥሪዎች እና ቅስቀሳዎች ተባባሪ እንዳይሆን አሳስቧል። ኅብረተሰቡ ሰላምና ፀጥታ በማስከበር ተግባር ላይ ከተሰማሩ የፀጥታ ኃይሎች ጎን ተሰልፎ ሰላሙን እንዲጠብቅ ጥሪውን አስተላልፏል። @ethiocheck

አቶ ጃዋር መሀመድን ጨምሮ 8 ተጠርጣሪዎች ላይ የዐቃቤ ህግ የቅድመ ምርመራ ምስክሮችን ለመስማት ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠ አቶ ጃዋር መሀመድን ጨምሮ 8 ተጠርጣሪዎች ላይ የዐቃቤ ህግ የቅድመ ምርመራ ምስክ
አቶ ጃዋር መሀመድን ጨምሮ 8 ተጠርጣሪዎች ላይ የዐቃቤ ህግ የቅድመ ምርመራ ምስክሮችን ለመስማት ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠ አቶ ጃዋር መሀመድን ጨምሮ 8 ተጠርጣሪዎች ላይ የዐቃቤ ህግ የቅድመ ምርመራ ምስክሮችን ለመስማት ዛሬ ቀጠሮ የያዘ ቢሆንም አቶ ጃዋር መሀመድ አሞኛል ብለው በችሎት በተደጋጋሚ መውጣት እና መግባት የምስክር ሂደቱን ስለሚያስተጓጉል በሚል ፍርድ ቤቱ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ @ethiocheck

በእነ ጃዋር መሐመድ መዝገብ የቅድመ ምርመራ ጉዳያቸው እየታየ ካሉ 14 ተጠርጣሪዎች መካከል 5ቱ በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው በምርመራ መረጋገጡን የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ለፌደራል የመጀመ
በእነ ጃዋር መሐመድ መዝገብ የቅድመ ምርመራ ጉዳያቸው እየታየ ካሉ 14 ተጠርጣሪዎች መካከል 5ቱ በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው በምርመራ መረጋገጡን የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ለፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ገለጸ። Via Ethiopia Insider @ethiocheck

የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት በአቶ ልደቱ አያሌው እጅ የተገኘው አንደኛውን ሽጉጥ እንዳላስታጠቃቸው እና ሽጉጡ ኢሳያስ ወልደጊዮርጊስ በተባለ ሰው ስም የተመዘገበ ነው ሲል ምላሽ መስጠቱን መር
የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት በአቶ ልደቱ አያሌው እጅ የተገኘው አንደኛውን ሽጉጥ እንዳላስታጠቃቸው እና ሽጉጡ ኢሳያስ ወልደጊዮርጊስ በተባለ ሰው ስም የተመዘገበ ነው ሲል ምላሽ መስጠቱን መርማሪ ፖሊስ ገለፀ። ዛሬ ለሶስተኛ ጊዜ በቢሾፍቱ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት የቀረቡት አቶ ልደቱ አያሌው አቶ ኢሳያስ በወቅቱ የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ምክትል ሀላፊ እንደነበሩ ጠቅሰዋል። ይሁንና እሳቸው ኃላፊነታቸውን ተጠቅመው የሰጧቸው መሆኑን ያብራሩ ቢሆንም መርማሪ ፖሊስ ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ያቀረበው ማስረጃ ግን ተቋሙ ያስታጠቃቸው እንዳልሆነ ተመልክቷል። ፍርድ ቤቱ በባለፈው ቀጠሮ በሀገር ውስጥ የልብ ህክምና እንዲያገኙ አዞ የነበረ ሲሆን፥ አቶ ልደቱ ላንድ ማርክ ሆስፒታል ክትትል ማድረጋቸውን እና የልብ እና የአስም ህመምተኛ መሆናቸውን የህክምና ማስረጃ በፅሁፍ አያይዘው አቅርበዋል። ፍርድ ቤቱም ይህን ተረድቶ ወደውጭ ሀገር ተጉዘው እንዲታከሙ እንዲፈቅድላቸው፥ እንዲሁም የታሰሩበት እስር ቤት ለበሽታ ተጋላጭ እንደሚያደርጋቸው እና የጤናቸው ሁኔታ አደጋ ውስጥ እንደሆነ በመጥቀስ በዋስ እንዲፈቱ ጠይቀዋል። አቶ ልደቱ ከዚህ በፊት በቀረቡበት ጊዜ ጥብቅና የሚቆምላቸው ሰው ማጣታቸውን መግለፃቸውን ተከትሎ ፍርድ ቤቱ ህገመንግስታዊ መብታቸው እንዲከበር በማሰብ የመንግስት ተከላካይ ጠበቃ አቁሞላቸዋል። መርማሪ ፖሊስ ባቀረቡት የዋስትና ጥያቄ ላይ በርካታ ምርመራ እየሰራ መሆኑን ገልፆ በእጃቸው ላይ የተገኘ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ፎረንሲክ ምርመራ መላኩን እና ውጤት እየተጠባበቀ መሆኑን በመግለፅ የጀመረውን የምርመራ ስራ አጠናቆ እንዲቀርብ ተጨማሪ የ14 ቀን ይሰጠኝ ሲል ፍርድ ቤቱን ጠይቋል ። @ethiocheck

ስራ ያቆመው LTV ሰራተኞቹን አሰናበተ! በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚሰራጩ የግል የቴሌቪዥን ጣቢያዎች አንዱ የሆነው Ltv ባጋጠመው ኪሳራ ምክንያት መዘጋቱን ሠራተኞች አስታወቁ።ሠራተኞች እንደሚናገሩት ሰኞ
ስራ ያቆመው LTV ሰራተኞቹን አሰናበተ! በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚሰራጩ የግል የቴሌቪዥን ጣቢያዎች አንዱ የሆነው Ltv ባጋጠመው ኪሳራ ምክንያት መዘጋቱን ሠራተኞች አስታወቁ።ሠራተኞች እንደሚናገሩት ሰኞ ሐምሌ 28/2012 በኪሳራ ምክንያት ስለመዘጋቱ የሚገልጽ ደብዳቤ እንደተሰጣቸው ለአዲስ ማለዳ አስታውቀዋል።ቅድመ ማስጠንቀቂያ እና መዘጋጃ እንዳልተነገራቸው የገለፁት ሠራተኞቹ ድንገት ሥራውን መቀጠል እንደማይችል እና የሦስት ወር ደሞዝ (ሥራ የማፈላለጊያ) እና የሥራ ልምድ በመስጠት ግንኙነታችን እንደተቋረጠ ነው የተነገረን ሲሉ አስታውቀዋል። @ethiocheck

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ለእስራኤልና ለተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፉ። እስራኤልና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ባሳለፍነው ሀሙስ መደበኛ የዲፕሎማሲ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ለእስራኤልና ለተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፉ። እስራኤልና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ባሳለፍነው ሀሙስ መደበኛ የዲፕሎማሲ ግንኙነት ለመመስረት ከስምምነት መድረሳቸው ይታወሳል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድም ይህንን ተከትሎ ነው በዛሬው እለት በኢፌዴሪ መንግስት እና በራሳቸው ስም ለሁለቱም ሀገራት የደስታ መግለጫ መልእክት ያስተላለፉት። በፌስቡክ ገፃቸው ባስተላለፉት መልእክታቸውም ሀገራቱ ሰላማዊ ግንኙነትን በድጋሚ ለማስጀመር የወሰዱት እርምጃ በዓለም ዙሪያ ሰላምና መረጋጋትን ለማስጠበቅ ለሚደረጉ ጥረቶች ወሳኝ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ በመልእክታቸው አክለውም፤ “ወንድሜ ልዑል መሀመድ ቢን ዘይድ አል-ናህያን ለሚሰጡት አመራር አመሰግናቸዋለሁ፤ በመካከለኛው ምስራቅ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን የተጀመረው ጉዞ እንደሚሳካ እምነታቸው መሆኑንም ጠቅሰዋል። እስራኤልና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መደበኛ የዲፕሎማሲ ግንኙነት ለመመስረት ባሳለፍነው ሀሙስ ነበር ከስምምነት የደረሱት። እስራኤል እና የተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች የደረሱት ስምምነት እስራኤል ነፃነቷን በ1948 ካወጀች በኋላ 3ኛው የእስራኤል አረብ የሰላም ስምምነት መሆኑ ታውቋል። @ethiocheck

የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ስብሰባውን ማካሄድ ጀመረ። የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ በየክልሉ ሥራ አስፈጻሚዎች የቀረቡትን ሪፖርቶች ለመገምገምና በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለመወያየት
የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ስብሰባውን ማካሄድ ጀመረ። የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ በየክልሉ ሥራ አስፈጻሚዎች የቀረቡትን ሪፖርቶች ለመገምገምና በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለመወያየት ሰብሰባ መጀመሩን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አስታወቁ። የፓርቲው ሊቀመንበርና የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አህመድ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው እንደገለጹት ፓርቲው በሚቀርቡት ሪፖርቶችና በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ በመምከር የተለያዩ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል። @ethiocheck

ከስድስት መቶ በላይ ሰዎችን በቁጥጥር ስር መዋላቸዋን የሻሸመኔ ከተማ ከንቲባ ገለፁ! በቅርቡ የድምጻዊ ሀጫሉ ሁንዴሳን ህልፈተ ህይወት ተከትሎ የሻሸመኔን ከተማ ጨምሮ በአንዳንድ የኦሮሚያ የክልል ከተ
ከስድስት መቶ በላይ ሰዎችን በቁጥጥር ስር መዋላቸዋን የሻሸመኔ ከተማ ከንቲባ ገለፁ! በቅርቡ የድምጻዊ ሀጫሉ ሁንዴሳን ህልፈተ ህይወት ተከትሎ የሻሸመኔን ከተማ ጨምሮ በአንዳንድ የኦሮሚያ የክልል ከተሞች የሰው ህይወት መጥፋቱ ፤ ንብረት መውደሙ እንዲሁም ብዙዎች ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸው ይታወሳል፡፡ የሻሸመኔ ከተማ ከንቲባ አቶ ጉታ ላቹሬ ለአሀዱ እንደተናገሩት በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ በዚህ ወንጀል የተጠረጠሩ እና ተሳትፈዋለል የተባሉ ከ ስድስት መቶ በላይ ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልፀዋል፡፡ ወንጀለኞችን ለመያዝ እና ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ ለማድረግ አጣሪ ኮሚቴ ተቋቁሞ እየሰራ ነው ብለዋል። @ethiocheck

በመቂ ከተማ አንድ ወጣት ለእናቱ ያስገነባውን መኖሪያ ቤት የአረጋዊያን ማእከል አድርጓል! ወጣት ያሬድ ኢሳያሥ ተወልዶ ያደገው በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን መቂ ከተማ ነው፡፡ ያሬድ በመቂ ከተማ
በመቂ ከተማ አንድ ወጣት ለእናቱ ያስገነባውን መኖሪያ ቤት የአረጋዊያን ማእከል አድርጓል! ወጣት ያሬድ ኢሳያሥ ተወልዶ ያደገው በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን መቂ ከተማ ነው፡፡ ያሬድ በመቂ ከተማ ያስገነባው ባለ አንድ ፎቅ ህንፃ እና 12 ክፍሎች ያሉትን ሰርቪስ ቤት ያሰራው የእናቱ መኖሪያ ቤት እንዲሆን ነበር። ሆኖም በብዙ ውጣ ውረድ ያሳዳገችኝ እናቴ በመጦሪያ እድሜዋ እንድትኖርበት ያስገነባሁት ቢሆንም አልተሳካም ይላል ያሬድ። የያሬድ እናትም ልጃቸው ወዳስገነባላቸው አዲስ ቤት ሳይገቡ ሞት ቀደማቸውና ወደ ዘላቂ ማረፊያቸው አመሩ። "አጋጣሚው ሀዘኔን መሪር አድርጎታል" የሚለው ያሬድ "የእናቴን መልካምነት ሁሌም ለማስታወስ ስል ቤቱን የአረጋዊያን ማእከል ለማድረግ ወስኛለሁ" ይላል። ማእከሉንም በእናቱ ስም እንዲጠራ በማድረግ "እልፍነሽ ሆርሳ የአረጋዊያን መኖሪያ ማዕከል" ብሎ መሰየሙን ገልጿል። Via ኢዜአ @ethiocheck

DrAbiyAhmed "ጨረቃ ላይ ለመድረስ ብታልም፣ ቢያንስ ከዋክብት ላይ ማረፍህ አይቀርም" እንደሚባለው፣ ዛሬ ለቀጣይ ሦስት ፕሮጀክቶች ማስጀመሪያ ገቢ ለማሰባሰብ 'ገበታ ለሀገር'ን በይፋ አስጀምረና
DrAbiyAhmed "ጨረቃ ላይ ለመድረስ ብታልም፣ ቢያንስ ከዋክብት ላይ ማረፍህ አይቀርም" እንደሚባለው፣ ዛሬ ለቀጣይ ሦስት ፕሮጀክቶች ማስጀመሪያ ገቢ ለማሰባሰብ 'ገበታ ለሀገር'ን በይፋ አስጀምረናል። የልማት ፕሮጀክቶቹ ከአማራ ክልል በጎርጎራ፣ ከኦሮሚያ ክልል በወንጪ እንዲሁም ከደቡብ ክልል በኮይሻ የሚከወኑ ሲሆን፣ የብልጽግና ጉዞን በክልሎች የሚያስቀጥሉ ናቸው። በመላው አዲስ አበባ ለሚካሄዱት ፕሮጀክቶች 'ገበታ ለሸገር' ብለን ካዘጋጀነው የግንቦት 2019 መርሐ ግብር ተሞክሮ በመቅሰም፣ በዚህኛው የ'ገበታ ለሀገር' መርሐ ግብር በቀጣይ ሁለት ወራት የ3 ቢሊየን ብር ገቢ ለማሰባሰብ አቅደናል። የድጋፍ ማሰባሰቡን ሥራ የሚከውነው ኮሚቴ በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻዎችን በማሳተፍ ሥራውን ይጀምራል። መቻላችንን በተግባር አሳይተናል! የሚቀጥለውን ዙር ሕልማችንን እውን ለማድረግ እንትጋ!" @ethiocheck

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የገበታ ለሀገር ፕሮጀክትን ይፋ አደረጉ። የገበታ ለሀገር ፕሮጀክት ቀደም ሲል በባለሀብቶች እና ተቋማት በተሰበሰበ ገንዘብ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የገበታ ለሀገር ፕሮጀክትን ይፋ አደረጉ። የገበታ ለሀገር ፕሮጀክት ቀደም ሲል በባለሀብቶች እና ተቋማት በተሰበሰበ ገንዘብ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች የተሠሩ የሸገር ፕሮጀክቶችን ወደ ክልሎች ለማስፋት ያለመ ነው። ፕሮጀክቶችን በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች እና የቱሪዝም መዳረሻዎች ለማስፋት ጥናት መደረጉም ተገልጿል። በዚህም ጥናት መሠረት በመጀመሪያ ዙር በሦስት ቦታዎች ላይ ተግባራዊ ለማድረግ ቦታዎች መመረጣቸው ታውቋል። እነዚህም በአማራ ክልል፣ ጣና ሐይቅ ምዕራባዊ ዳርቻ የሚገኘው ጎርጎራ፣ በአሮሚያ ክልል፣ ደቡብ ምዕራብ ሸዋ የሚገኘው ወንጪ ሐይቅ እና በደቡብ ክልል፣ ኮንታ የሚገኘው ኮንሻ ናቸው ተብሏል። ፕሮጀክቶቹ በቀጣይ አክሱም እና ላሊበላን ጨምሮ በርካታ ቦታዎች ላይ የሚከናወኑ መሆኑ ተገልጿል። ፕሮጀክቶቹ የግል ባለሀብቶችን ጨምሮ በአገር ውስጥ እና በውጭ የሚኖሩ ሁሉም ኢትዮጵያውያን የሚሳተፉባቸው እንደሚሆኑ ተገልጿል። ለዚህም ተሳትፎ የተለያዩ ፓኬጆች የተዘጋጁ ሲሆን፣ ለግል ባለሀብቱ ባለ 10 ሚሊዮን የከበረ ልዩ እራት (VVIP) እና ባለ አምስት ሚሊዮን ልዩ እራት (VIP) መዘጋጀቱ ተጠቁሟል። ሁሉንም ዜጋ ለማሳተፍ ደግሞ በኢትዮ-ቴሌኮም በኩል በአጭር ጽሑፍ መልእክት ባለ 5 እና ባለ 10 ብር ድጋፍ ፓኬጅ ተዘጋጅቷል። በተጨማሪም በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የሚሳተፉባቸው ፓኬጆች መኖራቸውም ተጠቁሟል። ከዚህ ባለፈ የተለያዩ የልማት አጋሮች፣ ዲፕሎማቶች እና ድርጅቶች የሚሳተፉባቸው ፓኬጆች እንደሚኖሩ ታውቋል። @ethioceck