Akaki kaliti Education Office
Open in Telegram
8 729
Subscribers
No data24 hours
-97 days
-2730 days
Posts Archive
እናስታውስዎ
በግንቦት 23/2017ዓ.ም በሚሰጠው የመምህራንና የትምህርት አመራር የሙያ ብቃት ምዘና ላይ የሚሳተፉ አካላት በሙሉ፡-
🟩🟦🟩🟦🟩🟦🟩🟦🟩🟦🟩🟦🟩
1️⃣ በምዘናው ወቅት ተመዛኞች መያዝ ያለባቸው ነገሮች፡-
1.1 እስክሪፕቶ
1.2 አድሚሽን ካርድ
2️⃣ በምዘና ወቅት የተከለከሉ ጉዳዮች፡-
❌ማንኛውም ተመዛኝ እና መዛኝ ሞባይል እና ሌሎች ኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ይዞ መግባት አይቻልም፡፡
❌ ማንኛውም ተመዛኝ ምዘናው ከተጀመረ ከ30 ደቂቃ በኋላ ወደ መፈተኛ ክፍል መግባት አይቻልም።
❌ማንኛውም አካል ተጨማሪ ወረቀት ይዞ ወደ መፈተኛ ክፍል መግባት አይቻልም። ተጨማሪ ወረቀት ካስፈለገ የባለስልጣኑ ሎጎ ያለበት በሱፐርቫይዘር በኩል በመጠየቅ ይሰጣል።
❌በምዘና ጣቢያ በተቀመጠው ሰዓት ጠዋት እስከ 1:30 ድረስ ያልተገኙ አስተባባሪ፣ ሱፐርቫይዘር፣ መዛኝ ወደ ስራ ተግባር/ ምደባ መግባት አይችሉም።
❌ማንኛውንም መምህርና የት/አመራር ቀደም ብሎ ስሙ ለምዘና ካልተላለፈ እና የምዘና ክፍል ድልድል ካልተሰጠው የምዘና ጣቢያ መግባትም ሆነ መመዘን አይቻልም።
▶️ተመዛኞች እና ማንኛውም በምዘናው የሚሳተፍ አካል የምዘና ጣቢያ መግቢያ በር ላይ በፀጥታ ሀይል የመፈተሽ ግዴታ አለበት።
▶️ማንኛውንም አካል በፈተናው ላይ የተቀመጡ ጥያቄዎች ላይ እርማት መስጠት አይችልም።
▶️ማንኛውንም መዛኝ፣ ሱፐርቫይዘር፣ አስተባባሪ በቅርንጫፉ ባለስልጣን የሚሰጠውን ባጅ የማድረግ እና በምዘናው መጨረሻ ላይ ባጁን ለሰጠው አካል የመመለስ ሀላፊነት አለበት፡፡
▶️የዲሲፕሊን ጥሰት የሚያሳዩ ሀላፊነታቸውን በአግባቡ የማይወጡ አካላት ከምዘና ታግዶ ለሚመለከተው አካል ሪፓርት በማድረግ በመመሪያ መሰረት እርምጃ ይወሰዳል።
👉በአቃቂ ቃሊቲ ቅ/ጽ/ቤት ስር የሚመዘኑ የምዘና ቦታው በፊታ/አባይነህ አንደኛ እና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በመሆኑ ተመዛኞች የምዘና ክፍል ድልድል በቴሌግራም ከተለቀቀው በመመልከት ወይንም በእለቱ በመፈተኛ ቦታው ከማስታወቂያ ላይ በመመልከት በየመፈተኛ ክፍላችሁ 30 ደቂቃ ቀደም ብላችሁ እንድትገኙ እናሳስባለን።
👍👍መልካም ጊዜ👍👍
