en
Feedback
አትራኮሰ-ጥበብ/ATRACOSE-TEBEBE

አትራኮሰ-ጥበብ/ATRACOSE-TEBEBE

Open in Telegram

አትራኮሰ-ጥበብ/ATRACOSE-TEBEBE ስለ ጥበብ በጥበብ እናወራለን ከኛ ጋራ ሁኑ! ግጥም፣ ወግና መጣጥፍ፤ ታሪክና ታሪካዊ ንግሮች፤ ምርጥ ምርጥ እባባልና ምስሎች፤ ሰበርና ወሳኝ መረጃዎች፤ የድምጸ መልካሞች ሙዚቃ፤ . . በሥነ-ኪን አቅም የተሻለ ነገን እንፈጥራለን! . . . . አትራኮሰ-ጥበብ!!!

Show more
790
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-430 days
Posts Archive
ጋዜጠኛ ደረጀ ኃይሌ የመኖሪያ ቤት ስጦታ ተበረከተለት በትናንትናው እለት የ60ኛ ዓመት የልደት በዓሉን እያከበረ የሚገኘው አንጋፋው ጋዜጠኛ ደረጀ ኃይሌ ከጃምቦ ሪልስቴት የመኖሪያ ቤት ስጦታ ተበርክቶ
+2
ጋዜጠኛ ደረጀ ኃይሌ የመኖሪያ ቤት ስጦታ ተበረከተለት በትናንትናው እለት የ60ኛ ዓመት የልደት በዓሉን እያከበረ የሚገኘው አንጋፋው ጋዜጠኛ ደረጀ ኃይሌ ከጃምቦ ሪልስቴት የመኖሪያ ቤት ስጦታ ተበርክቶለታል። በተጨማሪም ጋዜጠኛ ደረጀ ኃይሌ የጃምቦ ሪልስቴት የብራንድ አምባሳደር መሆኑ ይፋ ሆኗል። የአንጋፋው ጋዜጠኛ ደረጀ ኃይሌ የሙያ ባልደረቦቹና ወዳጆቹ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት የልደት በዓሉ ተከብሯል። Via dagu

ወገን እየተጠነቀቅን ቁጥሩ እየጨመረ ነው! ስለ ኤም ፖክስ (Mpox) በሽታ ከጤና ሚኒስቴር የተሰጠ ወቅታዊ ማብራሪያ #Ethiopia | በበሽታው የተያዙ ታማሚዎች ቁጥር 18 መድረሱ ሲረጋገጥ በበሽታ
+2
ወገን እየተጠነቀቅን ቁጥሩ እየጨመረ ነው! ስለ ኤም ፖክስ (Mpox) በሽታ  ከጤና ሚኒስቴር የተሰጠ  ወቅታዊ ማብራሪያ #Ethiopia  | በበሽታው የተያዙ ታማሚዎች ቁጥር 18 መድረሱ ሲረጋገጥ በበሽታው ከተያዙት ታማሚዎች መካከል የአንድ ወር ሕጻን ሕይወት አልፏል። በሌላ በኩል 5 ታካሚዎች ከቫይረሱ አገግመዋል። ለዚህ በሽታ አጋላጭ ሁኔታዎች ተብለው ከተለዩት መንገዶች  1.ለበሽታው ተጋላጭ የሆኑና በበሽታው እንደተያዘ ከተጠረጠረ ሰው ጋር የሚኖረንን ንክኪ (የግብረ ሰጋ ግንኙነት 2. የሰውነት ንክኪ 3.መሳሳም 4.መጨባበጥ) ማስቀረት እና ጥንቃቄ ማድረግ                  ምልክቶቹ 1.ከፍተኛ ትኩሳት 2.ራስ ምታት 3.የጀርባና የጡንቻ ህመም 4.እጢዎች ማበጥ 5.ለመተንፈስ መቸገር እና የቆዳ ላይ ሽፍታ ሲያሳዩ ወዲያዉኑ ራስን ከሌሎች ሰዎች መለየት እና ወደ ጤና ተቋም በመሄድ የሕክምና እርዳታ ማግኘት፣ የበሽታው ምልክቶች የታየበት ሰው ካጋጠመዎት ማስክ ማድረግ ወይም ርቀትን መጠበቅ እና ወደ ጤና ተቋም ቶሎ እንዲሄዱ ማገዝ፤ በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ንክኪ ከተፈጠረ እጅን በአግባቡ መታጠብ ከበሽታው ታማሚዎች ወይም ከሰውነት/ቁስል ፈሳሽ ጋር የተነካኩ ቦታዎችንና ቁሶችን በአግባቡ ማፅዳት፣ ከዚህም በተጨማሪም የዉጭ ሃገር የጉዞ ታሪክ ያለዉ እና ከላይ የተጠቀሱትን ምልክቶች የሚያሳይ ማንኛዉም ሰዉ በሚመለከቱበት ግዜ በአቅራቢያ በሚገኝ የጤና ተቋም ሪፖርት ማድረግ ወይም በ 8335 እና 952 ነፃ የስልክ መስመሮች ጥቆማ እንዲሰጡ እናሳዉቃለን። ዶ/ር መቅደስ ዳባ Via:- የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር

ቤት አፋልጉን እስቲ? ለተከታታይ ድራማ ሙሉ ጊቢ ያለው የድሮ ቤት ለመከራየት ፈልገናል። ከሦስት ወር እስከ ስድስት ወር ለሚሆን ጊዜ እንከራይና ከወደድነው ልንቀጥል እንችላለን! በቴሌግራም https:
ቤት አፋልጉን እስቲ? ለተከታታይ ድራማ ሙሉ ጊቢ ያለው የድሮ ቤት ለመከራየት ፈልገናል። ከሦስት ወር እስከ ስድስት ወር ለሚሆን ጊዜ እንከራይና ከወደድነው ልንቀጥል እንችላለን! በቴሌግራም https://t.me/BATRACOSE አድራሻችን የቤቱን ፎቶ በመላክና በመጠቆም ተባበሩን🙏 አትራኮሰ-ጥበብ! 👇👇👇 https://t.me/ATRACOSE 👆👆👆

ለእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1446ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በአል ቀን አደረሳችሁ ዒድ ሙባረክ !
ለእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1446ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በአል ቀን አደረሳችሁ ዒድ ሙባረክ !

ፌስታል መያዝ የሚያስቀጣውን ትላንት የጸደቀውን አዋጅ ግን ሰምታችኋል? ዜናው እንዲህ ይላል፦ "ለእንጀራ፣ ለዳቦ እና ለተለያዩ የሸቀጥ እቃዎች መጠቅለያነት የሚውለውን የአንድ ብሩን ፕላስቲክ ይዞ መገኘት ከ2000 እስከ 5000 ብር የሚያስቀጣው አዋጅ ጸደቀ፡፡ ማንኛውም ሰው አንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውል የፕላስቲክ ከረጢት ይዞ ከተገኘ ከ2000 እስከ 5000 ብር የሚያስቀጣው አዋጅ፤ ዜጎችን በማያውቁት ጉዳይ ለቅጣት የሚዳርግ ነው የሚል ትችት ከምክር ቤት አባላት ቀርቦበታል፡፡ የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ትላንት የጸደቀው #የደረቅ_ቆሻሻ_አያያዝ_እና_አወጋገድ_አዋጅ ፤ ማንኛውም ሰው አንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውል የፕላስቲክ ከረጢት ይዞ ከተገኝ ከ2000 እስከ 5000 ብር እንዲቀጣ ይደነግጋል፡፡ ያመረተ ወይም ወደ ሀገር ውስጥ ያስገባ፣ ለገበያ ያቀረበ ወይም የሸጠ፣ ለንግድ ዓላማ ያከማቸ ወይም ይዞ የተገኘ ከ50,000 ብር በማያንስና ከ200,000 ብር በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ እና ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት  እንዲቀጣ አዋጁ ያዝዛል፡፡ አዋጁ ይዞ የተገኝ እንዲቀጣ ይደነግጋል ህዝባችን የዚህ ግንዛቤ ይኖረዋል ወይ? የትኛው ፕላስቲክ እንደሆነ የመለየት ግንዛቤስ አለው ወይ? ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ ሌላ አንድ የምክር ቤት አባል በበኩላቸው ማንኛውም ሰው #ፕላስቲክ ይዞ ከተገኘ ከሁለት እስከ አምስት ሺህ ብር እንዲቀጣ ይደነግጋል፤ ይህ ከእኛ ነባራዊ ሁኔታ ጋር  እንዴት ታየ? በተለይ ዝቅተኛ ገቢ ያለው የማህበረሰብ ክፍል ሊጠቀመው ስለሚችል ጫና አይፈጥርም ወይ? ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ ለምሳሌ «አንዲት አሮጊት ወይም ሽማግሌ የሁለት ብር ዳቦ ወይም የአስር ብር ስኳር ገዝተው ሲሄዱ 5 ሺህ ብር ክፍሉ ቢባሉ ላይኖራቸው ስለሚችል ቅጣቱ ከ5 ሺህ ወደ 2 ሺህ ዝቅ እንዲል ተደርጓል ይህም የህብረተሰቡን የመክፈልም አቅም ከግንዛቤ ያስገባ ነው ሲሉ አስረድተዋል፡፡ የፕላስቲክ ከረጢቶች ከቅጣቱ በላይ ሀገርን የሚጎዱ ናቸው እስከ መቶ ዓመት ድረስም አይበሰብሱም ያሉት ምክትል ሰብሳቢው፤ ከዚህ አንጻር ቅጣቱ ሃያም ሰላሰም ሺህ ቢሆን ሀገርን ለማትረፍ ነው ብለዋል፡፡ ለህዝቡ ግንዛቤ ለመስጠትም ከመጪው ሃሙስ ጀምሮ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ይካሄዳል ሲሉ አወቀ አምዛዬ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡ አዋጁ የፕላስቲክ ጫማዎችን፣ የውሃ ኮዳዎችን እና ወፍራም የፕላስቲክ ውጤቶችን አይጨምርም መባሉን ሰምተናል፡፡ አዋጁ ማንኛውም ሰው ከመኖሪያ ቤቱ ድንበር አንስቶ ከሃያ ሜትር በላይ አካባቢውን የማጽዳት ግዴታን ያስቀምጣል፡፡ አዋጁ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከሚወጣበት ቀን ጀምሮ በመላ ሀገሪቱ ተፈጻሚ ይሆናል፡፡" የመረጃው ምንጭ፦ ሸገር ኤፍ ኤም ነው።

ብሔራዊና ሀይማኖታዊ በዓላት!
ብሔራዊና ሀይማኖታዊ በዓላት!

Repost from N/a
የአፋልጉኝ ማስታወቅያ! ቢቻል ሸራ ላይ ካልሆነም ወረቀት ላይም ሰዓሊነትን ስራዬ ብለው የያዙ ሴት ሰዓልያን ወዳጅ ያስፈልገኛልና እስቲ አለን በሉኝ🙏 "ለምን ሴት ሆነ? ለሚስትነት ነው ወይ የፈለካት
የአፋልጉኝ ማስታወቅያ! ቢቻል ሸራ ላይ ካልሆነም ወረቀት ላይም ሰዓሊነትን ስራዬ ብለው የያዙ ሴት ሰዓልያን ወዳጅ ያስፈልገኛልና እስቲ አለን በሉኝ🙏 "ለምን ሴት ሆነ? ለሚስትነት ነው ወይ የፈለካት፣ ወንድ ሰዓሊ አይሆንም ወይ? ደግሞ ሴቶች ያልከው የሴት ሰዓልያን ማህበር ልታቋቁም ነው ወይ?" የሚል ነገር ፈላጊ ጠያቂ ካለ በውስጥ ያናግረኝና ምቀኛ የሚል ቆንጆ ዘለፋ እመልስለታለሁ😄😜 ለማንኛውም ሴቶቹ ከሰዓሊነት ጎን ለጎን በተለይ ሥነ-ጽሑፍ አካባቢ ካሉ፣ ካላችሁ፣ ካለሽ  ደግሞ በስመአብ ብትተዋወቂኝ ወይም ብታስተዋውቁኝ ወይም ብተዋወቃት "የስራዬ ቃና ለውጥ" ይጀምራልና እስቲ አግዙኝ። ለማግኘት የቴሌግራም አድራሻዬን ተጠቀሙ፦https://t.me/BATRACOSE በቀጥታ አለሁ ከምትለኝ ሰዓሊት ባሻገር ደግሞ ከሰዓሊዋ ጋ ለሚያስተዋውቀኝ ሰው ወሮታውን እከፍላለሁ😜👍

ልክ በዛሬዋ ቀን በሚያዝያ 27 ቀን 1928 ዓ.ም የፋሺስትን ግፈኛ ማርሻል ባዶሊዮ አረንጓዴ-ቢጫ-ቀዩን የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ አስወርዶ፣ ቀይ-ነጫና-አረንጓዴውን ባንዲራ የሰቀለበት ቀን ነበር፡፡
+2
ልክ በዛሬዋ ቀን በሚያዝያ 27 ቀን 1928 ዓ.ም የፋሺስትን ግፈኛ ማርሻል ባዶሊዮ አረንጓዴ-ቢጫ-ቀዩን የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ አስወርዶ፣ ቀይ-ነጫና-አረንጓዴውን ባንዲራ የሰቀለበት ቀን ነበር፡፡ ልክ በአምስት ዓመቱ፤ ሚያዝያ 27 ቀን 1933 ዓ.ም ደግሞ ንጉሠ ነገሥቱ በከፍተኛ አጀብ እኩለ ቀን ላይ ከታላቁ የዳግማዊ ምኒልክ ቤተመንግሥት ላይ አረንጓዴ-ቢጫ-ቀዩን ሰንደቅ ዓላማችንን መልሰው የሰቀሉበት ቀን ነበር፡፡ መልካም የድል በዓል ቀን! 👇👇👇 https://t.me/ATRACOSE 👆👆👆

ልክ በዛሬዋ ቀን በሚያዝያ 27 ቀን 1928 ዓ.ም የፋሺስትን ግፈኛ ማርሻል ባዶሊዮ አረንጓዴ-ቢጫ-ቀዩን የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ አስወርዶ፣ ቀይ-ነጫና-አረንጓዴውን ባንዲራ የሰቀለበት ቀን ነበር፡፡
+2
ልክ በዛሬዋ ቀን በሚያዝያ 27 ቀን 1928 ዓ.ም የፋሺስትን ግፈኛ ማርሻል ባዶሊዮ አረንጓዴ-ቢጫ-ቀዩን የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ አስወርዶ፣ ቀይ-ነጫና-አረንጓዴውን ባንዲራ የሰቀለበት ቀን ነበር፡፡ ልክ በአምስት ዓመቱ፤ ሚያዝያ 27 ቀን 1933 ዓ.ም ደግሞ ንጉሠ ነገሥቱ በከፍተኛ አጀብ እኩለ ቀን ላይ ከታላቁ የዳግማዊ ምኒልክ ቤተመንግሥት ላይ አረንጓዴ-ቢጫ-ቀዩን ሰንደቅ ዓላማችንን መልሰው የሰቀሉበት ቀን ነበር፡፡ መልካም የድል በዓል ቀን! 👇👇👇 https://t.me/ATRACOSE 👆👆👆

ትንቢተ ኢሳያስ (ባቢ) የጋሽ ጥላሁን ገሰሰን "ቆሜ ልመርቅሽ" ደግሞ እንዳቀነቀነው። 🎤🎤🎤 🎧🎧🎧🎧🎧🎧 https://t.me/ATRACOSE 🎧🎧🎧🎧🎧🎧

*ሚያዚያ 27 ቀን 1933 ዓ.ም* የአርበኞች ድል ቀን መታሰቢያ በዓል ጣሊያን በአድዋ የደረሰበትን ሽንፈት ለመበቀል እና ኢትዮጵያን ቀኝ ግዛት ለመያዝ 40 ዓመታትን ስትዘጋጅ ከርማ በ1928ዓ/ም ለመላው የጥቁር ሕዝብ እንደ ነጻነት ምልክት ተደርጋ የምትታየውን ኢትዮጵያን ወረረች፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብም በአንድነት የጣሊያንን ወረራ ለመከላከል ጨርቄን ማቄን ሳይል ተነሳ፡፡ በሰሜን እና በምስራቅ በተካሄዱ ጦርነቶች ግን ኢትዮጵያዊያን እንደ አድዋው ድል አልቀናቸውም፡፡ ንጉሠ ነገሥቱ በተሳተፉበት የማይጨው ጦርነትም ድል ባለመገኘቱ ኢትዮጵያዊያን የአርበኝነት ተጋድሎ እንዲጀምሩ አደረገ፡፡ ከጣሊያን መድፍ እና የአውሮፕላን መርዝ የተረፉ ቆራጥ አርበኞች ዱር ቤቴ አሉ፡፡ እንደ እጃቸው መዳፍ ጠንቅቀው የሚያውቁትን የአገራቸውን መልክዓ-ምድር መመኪያ አድርገው ጣሊያንን ይፋለሙ ጀመር፡፡ ከመኳንንቱ እና ከመሳፍንቱ በተጨማሪ ብዙ አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን የአርበኝነት ትግሉን ተቀላቀሉ፡፡ በበጌምድርና አካባቢው ራስ ውብነህ ተሰማና ቢትውደድ አዳነ፤ በጎጃም ቢትወደድ መንገሻ ጀምበሬ፣ በላይ ዘለቀ(አባ ኮስትር)፣ ደጃዝማች ኃይለየሱስ ፍላቴ እና ራስ ኃይሉ በለው፤ በሸዋ ራስ አበበ አረጋይ፣ መስፍን ስለሺ ፀሐይ ዕንቁሥላሴ፤ የበሼ ቤተሰቦች ደጃች ተሾመና አበበ ሽንቁጥ፤ በወሎ እነ ኃይሉ ከበደ፣ ወሰን ኃይሉ እና በሌሎች የአገራችን ክፍሎች የሚገኙ አርበኞች ሕዝቡን በማስተባበር ጣሊያንን ለአምስት ዓመት የረገጣት የኢትዮጵያ ምድር ረመጥ እንድትሆንበት አደረጉ፡፡ ከአምስት ዓመት ተጋድሎ በኋላም ጣሊያን ድጋሜ የሽንፈትን ጽዋ ተጎነጨ፡፡ አርበኞች በዱር በገደሉ፣ የውስጥ አርበኞች በከተማ እና ንጉሠ ነገሥቱ በውጭ ባካሄዱት የዲፕሎማሲ ትግል ወድቃ የነበረችው የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ተነሳች፡፡ ሚያዚያ 27/1933 ዓ/ም ድጋሜ በኢትዮጵያ ሰማይ በነጻነት ለመውለብለብ በቃች፡፡ ክብር ለኢትዮጵያ አርበኞች እንኳን ለአርበኞች ድል መታሰቢያ በዓል አደረሳችሁ!!!

የአዲስ ዓመት ሙዚቃ ቢሆንም የአትራኮስ ቴሌግራም "ግሩፕ" ውስጥ ዛሬ የተለቀቀ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት መግለጫ ነውና እነሆ አጋራናችሁ! በድጋሚ መልካም የትንሳኤ በዓል!

ሚሻሚሾ (ሙዚቃ) ትንቢተ ኢሳያስ (ባቢ) 🎤🎤🎤 https://t.me/ATRACOSE 🎤🎤🎤

"እንደተናገረ ተነስቷል!"
"እንደተናገረ ተነስቷል!"

ይህ ድምጸ መልካማችን በነበረችው ፀደይ ገ/ጻዲቅ ከዓመታት በፊት ተደርሶ የተዜመ ዝማሬ ነው! 🎤🎤🎤 https://t.me/ATRACOSE 🎤🎤🎤

ቸርነትህ ነው (ዝማሬ) አማኑኤል ዓለማየሁ 🎤🎤🎤 https://t.me/ATRACOSE 🎤🎤🎤

ማረኝ ኢየሱስ (ዝማሬ) ጸጋዬ አየለ 🎤🎤🎤 https://t.me/ATRACOSE 🎤🎤🎤