en
Feedback
FDRE Defense Force -የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት

FDRE Defense Force -የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት

Open in Telegram

FDRE Defence Force የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት # ቁልፍ_እሴቶች 1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣ 2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣ 3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣ 4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላቀ ውጤት። የፌስቡክ ገፃችንን ይከታተሉ https://www.facebook.com/fdredefense.official @FDRE_DEFENCE_FORCE

Show more
4 610
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ህዳር 2 ቀን 2015 ዓ.ም በፌዴራል መንግስት እና በህወሃት አመራሮች መካከል የሚደረገዉን የሰላም ዉይይት የአላማጣ የኮረም እና ጨርጨር ከተማ ነዋሪዎች አደነቁ። በፌዴራል መንግስት እና በህወሃት አ
+2
ህዳር 2 ቀን 2015 ዓ.ም በፌዴራል መንግስት እና በህወሃት አመራሮች መካከል የሚደረገዉን የሰላም ዉይይት የአላማጣ የኮረም እና ጨርጨር ከተማ ነዋሪዎች አደነቁ። በፌዴራል መንግስት እና በህወሃት አመራሮች መካከል እየተደረገ ያለዉን የሰላም ዉይይት ተከትሎ በሰፈነው አንፃራዊ ሰላም በተለያዩ ዕለታዊ ፍጆታዎች ላይ የዋጋ ቅናሽ እና መረጋጋት በመታየቱ መደሰታቸውን ነዉ የአላማጣ የኮረም እና ጨርጨር ከተማ ነዋሪዎች የተናገሩት። ነዋሪዎቹ እጅግ ባጠረ ጊዜ የመብራት እና የስልክ አገልግሎት ማግኘት መቻላቸውም ለዕለት ተዕለት ኑሯቸው እገዛ እንዳደረገላቸዉ ገልፀዋል። በግጭት ወቅት በተከሰተው የሠላም እጦት ምክንያት ሰላም እርቋቸዉ መረጋጋት ተስኗቸዉ ህይወታቸዉን አንድ ቦታ ላይ ሆነዉ መምራት ያልቻሉ መሆናቸዉን ያወሱት ነዋሪዎቹ ከጦርነት ኪሳራ እንጅ ትርፍ አይገኝም በማለት ትዝባታቸዉን ለመከላከያ ሚዲያ ገልፀዋል። አሁን ላይ መንግስት በእነኝህ አካባቢዎች እና የጦርነት ቀጠና በነበሩ አካባቢዎች አስፈላጊ ድጋፎችን ለህብረተሰቡ ከማደረስ ጀምሮ እንደቴሌ መብራት እና ዉሃ የመሰሰሉ መሰረታዊ እና ለሰዉ ልጅ አስፈላጊ መሰረተ ልማቶችን በፍጥነት እየገነባ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡ ስለሆነም ነዋሪዎቹ በፌዴራል መንግስት እና በህወሃት አመራሮች መካከል የሚደረገዉን የሰላም ዉይይት አድንቀዉ በህብረት የኢትዮጵን የዕደገት ግስጋሴ ለማፋጠን ዝግጁ መሆናቸዉን ተናግረዋል፡፡ የኃላሸት ሶረሳ ፎቶግራፍ በየኃላሸት ሶርሳ

ህዳር 2 ቀን 2015 ዓ.ም በፌዴራል መንግስት እና በህወሃት አመራሮች መካከል የሚደረገዉን የሰላም ዉይይት የአላማጣ የኮረም እና ጨርጨር ከተማ ነዋሪዎች አደነቁ። በፌዴራል መንግስት እና በህወሃት አመራሮች መካከል እየተደረገ ያለዉን የሰላም ዉይይት ተከትሎ በሰፈነው አንፃራዊ ሰላም በተለያዩ ዕለታዊ ፍጆታዎች ላይ የዋጋ ቅናሽ እና መረጋጋት በመታየቱ መደሰታቸውን ነዉ የአላማጣ የኮረም እና ጨርጨር ከተማ ነዋሪዎች የተናገሩት። ነዋሪዎቹ እጅግ ባጠረ ጊዜ የመብራት እና የስልክ አገልግሎት ማግኘት መቻላቸውም ለዕለት ተዕለት ኑሯቸው እገዛ እንዳደረገላቸዉ ገልፀዋል። በግጭት ወቅት በተከሰተው የሠላም እጦት ምክንያት ሰላም እርቋቸዉ መረጋጋት ተስኗቸዉ ህይወታቸዉን አንድ ቦታ ላይ ሆነዉ መምራት ያልቻሉ መሆናቸዉን ያወሱት ነዋሪዎቹ ከጦርነት ኪሳራ እንጅ ትርፍ አይገኝም በማለት ትዝባታቸዉን ለመከላከያ ሚዲያ ገልፀዋል። አሁን ላይ መንግስት በእነኝህ አካባቢዎች እና የጦርነት ቀጠና በነበሩ አካባቢዎች አስፈላጊ ድጋፎችን ለህብረተሰቡ ከማደረስ ጀምሮ እንደቴሌ መብራት እና ዉሃ የመሰሰሉ መሰረታዊ እና ለሰዉ ልጅ አስፈላጊ መሰረተ ልማቶችን በፍጥነት እየገነባ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡ ስለሆነም ነዋሪዎቹ በፌዴራል መንግስት እና በህወሃት አመራሮች መካከል የሚደረገዉን የሰላም ዉይይት አድንቀዉ በህብረት የኢትዮጵን የዕደገት ግስጋሴ ለማፋጠን ዝግጁ መሆናቸዉን ተናግረዋል፡፡ የኃላሸት ሶረሳ ፎቶግራፍ በየኃላሸት ሶርሳ

ህዳር 2 ቀን 2015 ዓ.ም በፌዴራል መንግስት እና በህወሃት አመራሮች መካከል የሚደረገዉን የሰላም ዉይይት የአላማጣ የኮረም እና ጨርጨር ከተማ ነዋሪዎች አደነቁ። በፌዴራል መንግስት እና በህወሃት አመራሮች መካከል እየተደረገ ያለዉን የሰላም ዉይይት ተከትሎ በሰፈነው አንፃራዊ ሰላም በተለያዩ ዕለታዊ ፍጆታዎች ላይ የዋጋ ቅናሽ እና መረጋጋት በመታየቱ መደሰታቸውን ነዉ የአላማጣ የኮረም እና ጨርጨር ከተማ ነዋሪዎች የተናገሩት። ነዋሪዎቹ እጅግ ባጠረ ጊዜ የመብራት እና የስልክ አገልግሎት ማግኘት መቻላቸውም ለዕለት ተዕለት ኑሯቸው እገዛ እንዳደረገላቸዉ ገልፀዋል። በግጭት ወቅት በተከሰተው የሠላም እጦት ምክንያት ሰላም እርቋቸዉ መረጋጋት ተስኗቸዉ ህይወታቸዉን አንድ ቦታ ላይ ሆነዉ መምራት ያልቻሉ መሆናቸዉን ያወሱት ነዋሪዎቹ ከጦርነት ኪሳራ እንጅ ትርፍ አይገኝም በማለት ትዝባታቸዉን ለመከላከያ ሚዲያ ገልፀዋል። አሁን ላይ መንግስት በእነኝህ አካባቢዎች እና የጦርነት ቀጠና በነበሩ አካባቢዎች አስፈላጊ ድጋፎችን ለህብረተሰቡ ከማደረስ ጀምሮ እንደቴሌ መብራት እና ዉሃ የመሰሰሉ መሰረታዊ እና ለሰዉ ልጅ አስፈላጊ መሰረተ ልማቶችን በፍጥነት እየገነባ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡ ስለሆነም ነዋሪዎቹ በፌዴራል መንግስት እና በህወሃት አመራሮች መካከል የሚደረገዉን የሰላም ዉይይት አድንቀዉ በህብረት የኢትዮጵን የዕደገት ግስጋሴ ለማፋጠን ዝግጁ መሆናቸዉን ተናግረዋል፡፡ የኃላሸት ሶረሳ ፎቶግራፍ በየኃላሸት ሶርሳ

ጥቅምት 16 ቀን 2015 ዓ.ም "ቆስለንም እየታከምን ነው።" ፦ እጃቸውን ለመከላከያ ሰራዊታችን የሠጡ የህወሓት ታጣቂዎች አሸባሪው ህወሓት በደረሰበት ምት መበታተኑን እጃቸውን ለመከላከያ ሰራዊት የሠ
ጥቅምት 16 ቀን 2015 ዓ.ም "ቆስለንም እየታከምን ነው።" ፦ እጃቸውን ለመከላከያ ሰራዊታችን የሠጡ የህወሓት ታጣቂዎች አሸባሪው ህወሓት በደረሰበት ምት መበታተኑን እጃቸውን ለመከላከያ ሰራዊት የሠጡ ታጣቂዎች አረጋግጠዋል። እጃቸውን ለመከላከያ ሰራዊታችን የሠጡ ታጣቂዎች እንደገለፁት በመከላከያ ሠራዊቱ የተደረገልን አቀባበል ከተነገረን በተቃራኒው ሆኖ አግኝተነዋል። መከላከያ ሠራዊቱ ሲማርከን እንደቤተሰቡ ነው የተቀበለን ያሉት መኮንን ጉድላክ እና ከማኢስ አመሀ እጅ በመስጠታችን እድለኞች ነን ቆስለንም እየታከምን ነው ብለዋል። ሽመልስ ሹምዬ ፎቶግራፍ ሽመልስ ሹምዬ ለተጨማሪ መረጃዎች ከታች ያሉትን ሊንኮች ይጠቀሙ:: ፌስቡክ https://www.facebook.com/fdredefense.official

መከላከያ ሠራዊት በወሰደው ርምጃ የሽብር ቡድኑ ታጣቂዎች በሁሉም ግንባር እጅ እየሰጡና እየተበተኑ ነው። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በወሰደው ከባድና ፈጣን ርምጃ የሕወሐት ታጣቂዎች ተበትነዋል፤ የታ
መከላከያ ሠራዊት በወሰደው ርምጃ የሽብር ቡድኑ ታጣቂዎች በሁሉም ግንባር እጅ እየሰጡና እየተበተኑ ነው። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በወሰደው ከባድና ፈጣን ርምጃ የሕወሐት ታጣቂዎች ተበትነዋል፤ የታደሉት እጅ ሰጥተዋል። ሌሎች ደግሞ በተሳሳተ መረጃ ተደናግረው ምን ማድረግ እንዳለባቸው ግራ እንደተጋቡ መረጃዎች አመልክተዋል። በቅርቡ ለመከላከያ እጅ የሰጡ የአሸባሪው ሕወሓት ታጣቂዎች የክፋት አዝማቾቻቸውን ሁኔታ በአንድ ጥሩ የትግርኛ ምሳሌያዊ አነጋገር ገልጸውታል። ማሽላውን ከአደጋ ለመከላከል የከበበው አጥር ለማሽላው እንጂ ራሱ አጥሩን አልጠቀመውም። ይሄም ጁንታው እንጂ ታጣቂዎቹ ከጦርነቱ ያተረፉት እልቂት ብቻ መሆኑን ያሳያል። በመሆኑም የተበተኑና ከጁንታው የጥፋት ወጥመድ ማምለጥ የሚፈልጉ የጁንታው ታጣቂዎች መከላከያ ወደ ተቆጣጠራቸው የትግራይ አካባቢዎችና ወደ አጎራባች ክልሎች በመሄድ እጃቸውን በሰላም እንዲሰጡ የመከላከያ ሠራዊት ጥሪ ያቀርባል። እጃቸውን ለሚሰጡ የጁንታው ታጣቂዎች አስፈላጊው ክብካቤ እንዲደረግ መመሪያ ተላልፏል። የአጎራባች ክልሎችና ከህወሓት የተላቀቁ የትግራይ አካባቢዎች ሕዝብ፣ እጅ የሚሰጡ የጁንታው ታጣቂዎችን በመቀበል፣ ተንከባክቦ ለመከላከያ ሠራዊቱ እንዲያስረክብ መከላከያ መልእክት ያስተላልፍላችኋል።

ጥቅምት 16 ቀን 2015 ዓ.ም “የጥንካሬያችን ምንጭ ሕዝባችን ነው!!” በሚል መሪ ቃል የመከላከያ ሠራዊት ቀንን በአትሚስ የሚገኘው የኢትዮጵያ 7ኛ ሞተራይዝድ ሻለቃ የሠራዊት አባላት በፓናል ውይይት
+2
ጥቅምት 16 ቀን 2015 ዓ.ም “የጥንካሬያችን ምንጭ ሕዝባችን ነው!!” በሚል መሪ ቃል የመከላከያ ሠራዊት ቀንን በአትሚስ የሚገኘው የኢትዮጵያ 7ኛ ሞተራይዝድ ሻለቃ የሠራዊት አባላት በፓናል ውይይት አከበሩ። የ7ኛ ሞተራይዝድ ሻለቃ ዋና አዛዥ ኮ/ል ወዳጅ ቦጋለ በፓናል ውይይቱ ላይ ተገኝተው እንደተናገሩት ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የራሷን ሠራዊት በሚኒስቴር መስሪያ ቤት ያቋቋመችበትን ቀን ጥቅምት 15/1900 ዓ.ም የሠራዊት ቀን ሆኖ መከበሩ ለሠራዊቱ ከፍተኛ አስተዋፆ አለው። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በሁሉም አካባቢ እና ቀጠና የተሰጠውን ግዳጅ በአመሪቂ ድል ሲፈፅም ጠንካራው ህዝባችን ከጎናችን አልተለየም ይህንንም በዓል ስናከበር ህዝባችንንም እያወደስን እና እያመሰገንን መሆን አለበት ሲሉ ተናግረዋል። ከፍተኛ መኮንኑ አክለውም የአለም መንግስታት በሶማሊያ የሰጡንን ትልቅ ኃላፊነት እና አደራ በብቃት እና በጥራት በመወጣት ላይ እንገኛለን ይህንንም ተግባር አጠናክረን ለመቀጠል ይህ በዓል ከፍተኛ አበርክቶ አለው ብለዋል። በፓናል ውይይቱ ላይ ተሳታፊ ከነበሩት የሠራዊት አባላት መካከል ሻ/ል ዘመኑ አበራ እና አስር አለቃ ደመላሽ ጌትነት በሰጡት አስተያዬት የመከላከያ ሠራዊት ቀንን በአትሚስ ተልዕኮ ላይ ሆነን ስናከብር ለምንፈፅመው ግዳጅ ትልቅ አስተዋፆ አለው ብለዋል። ፍፁም ከተማ ፎቶግራፍ አማላይ ገደፋው

ነሐሴ 1 ቀን 2014 ዓ.ም ✍ የወጣቱ ተጋድሎ በደጎሎ ሀገራችን ኢትዮጵያ በተለያዩ ጊዜያት የውጪም ሆነ የውስጥ ጠላቶች ሲያጋጥሟት ዜጎቿም በአንድ አይነት አስተሳሰብ እና በአንድ አይነት ዓላማ በደም እና በህይወታቸው ቤዛነት የማያልፍ ታሪክ ሰርተው ህዝብና ሀገርን አፅንተዋል። ህዝቦቿ የሀገርን ሉዓላዊነትን ለመዳፈር ለሚሞክሩ ማንኛውም ፀረ ሠላም ሃይሎች በተባበረ ክንዳቸው "ዶጋመድ" እንደሚያደርጉት ለማወቅ የታሪክ ድርሳናትን ማገላበጥ አይጠበቅብንም። ምክንያቱም በቅርቡ እንኳን አሸባሪው እና ወራሪው የህውሃት ቡድን ኢትዮጵያን አፈርሳለሁ ብሎ ሲቋምጥ የሀገራችን ህዝቦች ከሊቅ እስከ ደቂቅ ከህፃን እስከ አዛውንት ግንባር መዝመታቸው ብቻ ሁነኛ ምስክር መሆን ስለሚችል። ሀገራችን ኢትዮጵያ በገጠማት ፈተናዎች ሁሉ ቆራጥ ጀግና እና ሀሞተ ኮስታራ ጀግኖች በየዘመኑ ነበሩ አሁንም አሉ ወደ ፊትም ይኖራሉ። አሸባሪው እና ወራሪው የህውሃት ቡድን ወረራ ባደረገባቸው አንዳንድ የአማራ ክልል ወረዳዎች እንዲሁም በአፋር የተወሰኑ አካባቢዎች ለማመን የሚከብዱ አፀያፊ ተግባራትን መፈፀሙ የአደባባይ ሚስጥር ሆኖ በጥቁር አሳፋሪ መዝገብ ተከትቧል። በደቡብ ወሎ ዞን በጃማ ደጎሎ ወረዳ አንድ ወጣት ስለሰራው አስገራሚ ጀብዱ ልነግራችሁ ወደድኩ። ወጣት ቴዎድሮስ ታደሰ ይባላል ውልደቱም እድገቱም ጃማ ዶጎሎ ነው። ለቤተሰብ ደግሞ የበኩር ልጅ ነው ይህ ወጣት አሸባሪው እና ወራሪው የህውሀት ቡድን በጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት ድባቅ ተመትቶ ከመሸሹ በፊት በወረራ ይዞት በነበረው ጃማ ዶጎሎ ውስጥ በርካታ ጥፋትን ሲያደርስ እንደነበረ ያነሳል። ለወጣት ቴዎድሮስ ታደሰ የመጀመሪያ ጥያቄዬን ጠየኩት ጥያቄው ደግሞ ከአሸባሪው የህውሃት ቡድን አባላት ጋር እንዴት ተገናኛችሁ የሚል ነበር? በሰፈራችን ሁለት የእነሱ ታጣቂዎች መጡ አንደኛው ክላሽ ይዟል ሌላኛው ደግሞ ዱላ ነበር የያዘው እኔ ደግሞ እቤቴ ደጃፍ ቁጭ ብዬ ነበር እዚህ ጠላት ወይም አብዮታዊ አሉ አለኝ "መከላከያ ሠራዊቱን ማለታቸው ነው"። አረ የለም አልኳቸው በመቀጠል ሁለቱ በትግረኛ አውርተው ወደ እኛ ቤት ለመግባት ተስማሙ። በመቀጠል አንደኛው መሳሪያ የያዘው በረንዳ ላይ ቁጭ አለ አንደኛው ደግሞ ሳሎን ቤት ገብቶ በመበርበር የእህቴን የአንገት ወርቅ እና የጆሮ ጌጥ እንዲሁም 5ሺህ ብር ይዞ ወጣ እና ለጓደኛው የፈለግነውን አግኘተናል አለው። መሳሪያ የያዘው ሌላ ነገር ምን አላችሁ? አለኝ ይላል ወጣት ቴዎድሮስ እኔም በማስከተል ተጨማሪ ጥያቄ ጠየኩት ምን አልካቸው? በጓሮ የሚሸጡ በጎች ነበሩን እና ድምፅ ስለሰሙ ከዋሸሁ እንዳይገሉኝ የሚሸጡ በጎች አሉ አልኩት ፍጠን አምጣ አለኝ "ወዲ ዘኸድጊ" እያለ እኔም ከሚሸጡት በጎች መካከል አንዱን አመጣሁ እና ሰጠሁት። ስንት ብር ነው የሚሸጠው አለኝ 1500 ብር አልኩት እየሳቀ ለመከላከያ ቢሆን ኖሮ በነፃ ነበር የምትሰጠው ብሎ ተፋብኝ እኔም ዝም ብዬ በውስጤ አንድ ሃሳብ እያሰብኩ ነበር። ክላሽ የያዘው ጓደኛውን ጠርቶ በጉን ያዝ እንሂድ አለው እሱም እሺ አለው እና በጉን ተሸክሞ ወጣ አንደኛው ደግሞ ክላሽ አንግቶ ሊወጣ ሲል መሳሪያውን ከትከሻው ላይ በፍጥነት ቀማሁት በዚህ ጊዜ ሁለቱም እግሬ አውጪኝ ብለው ፈረጠጡ። ክላሹን ከተቀበልክ በኋላ ምን አደረክ የእኔ ጥያቄ ነበር? ክላሹ በእጄ ሲገባ አንደኛው በጉን ጥሎ ወደ ግራ ታጠፈ አንደኛው ደግሞ ወደ ቀኝ ታጠፈ እኔም ክላሹን ወደ ቀኝ ወደታጠፈው እየተካስኩ ተከተልኩት ነገር ግን አለገኘሁትም። ከእነሱ የወሰድኩትን መሳሪያ ይዤ ወደ ጫካ ገባሁ ከዛ በኋላ እነሱን አግኝቻቸው አላውቅም ብሎ ሃሳቡን ያጠቃልላል። አሸባሪውን እና ወራሪው የህውሃት ቡድን በወረራቸው አካባቢዎች የሚገኙ ነዋሪዎች ይህንን የሽብር ቡድን የታጠቃቸውን መሳሪያዎች የዘረፋቸዉን የህዝብ እና የመንግስት ንብረት ይዞ እንዳይወጣ መማረክ እና መደምሰስ እንደሚያስፈልግ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ዕዝ በተሰጠው አቅጣጫ መሠረት ጀግናው ወጣት ቴዎድሮስ ታደሰ ከአሸባሪው የህውሃት ቡድን የማረከውን መሳሪያ ለሌሎችም ሀገር ወዳድ የአካባቢዉ ወጣቶች ጥሩ አብነት ይሆናል። ጀግናዉ ቴዎድሮስ ታደሰ በአሁን ሰዓት ከጁንታዉ የማረከዉን ክላሽ ታጥቆት የአካባቢውን ሠላም እያስጠበቀበት ይገኛል። ለሀገር እና ለህዝብ ክብር መቆም ይሉሃል ይህ ነው። ኢትዮጵያ አሸንፋለች። ፍፁም ከተማ ፎቶግራፍ አከለ አባተ ለተጨማሪ መረጃዎች ከታች ያሉትን ሊንኮች ይጠቀሙ። ፌስቡክ 👇 https://www.facebook.com/fdredefense.officia

ታህሳስ 2 ቀን 2014 በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የተመራው ዘመቻ ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት፣ ዋናውን የወልድያ መቀሌ ጎዳና ቆርጦታል፡፡ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመሩት የጸጥታ ኃይሎች ጥምረት፣ በአሸባሪው ወራሪ ላይ በሰነዘሩት ክንደ ብርቱ ማጥቃት፣ በምሥራቅ ግንባር ስትራቴጂያዊ የሆኑትንና ወራሪው በፍጻሜ ዋዜማ ላይ መሆኑን የሚያሳዩትን የዞብል ሠንሠለታማ ተራሮችን ጨምሮ ከፍተኛ ወታደራዊ ጠቀሜታ ያላቸውን የአርጆ፣ ፎኪሳ እና ቦረን ከተሞችን ተቆጣጥሯል፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ የጉራ ወርቄ አካባቢዎችን በመቆጣጠር የወልድያ መቀሌ ዋናውን አውራ ጎዳና በመቁረጥ ጠላት መውጫ አጥቶ ነፍስ ውጪ ነፍስ ግቢ ውስጥ እንዲገባ አድርጎታል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በዚሁ ግንባር የድሬ ሮቃና የሶዶማ ከፍተኛ ወታደራዊ ጠቀሜታ ያላቸውን ከተሞችና ተራሮች በመቆጣጠር ጥምር ጦሩ ወደ ሐራ ከተማ እየገሠገሠ ይገኛል፡፡ በውጫሌ ግንባር ደግሞ የአምባሰል ከፍተኛ ሠንሠለታማ ተራሮችን ጨምሮ የሮቢትና የጎልቦን፣ በወረባቦ ወረዳ የሚሌ ኮትቻን፣ በሐብሩ ወረዳ የኮልቦን፣ የመርካታና የፋጂን አካባቢዎችን በመቆጣጣር ወደ መርሳ ከተማ እየገሠገሠ ነው፡፡ በእነዚህ ግንባሮች በተደረገው ኦፐሬሽን በአሸባሪው የጠላት ኃይል ላይ በተሠነዘረበት ማጥቃት ጠላት ሙት፣ ቁስለኛና ምርኮኛ ሆኗል፡፡ የወገን የመካናይዝድ ኃይልና ንሥሮቹ የአየር ኃይሉ በጥምረት ባካሄዱት ኦፐሬሽን የጠላት ኃይል ምንም ዓይነት ተሸከርካሪ እና ከባድ መሣሪያዎችን ይዞ እንዳይንቀሳቀስ ስላደረጉት፣ ጠላት በየአቅጣጫው ጥሎ ለመፈርጥጥ ተገድዷል፡፡ ለበርካታ ቀናት ያከማቻቸውን ቁስለኞችንም ጥሎ ፈርጥጧል፡፡ የዘረፈውን ንብረትም በየቦታው እያዝረከረከ እግሬ አውጪኝ በማለት ላይ ይገኛል፡፡ ጠላት ዋናው የቆቦ ወልድያ መንገድ ስለተዘጋበት በድንብርብር በጋሸና ላሊበላ በኩል ለማምለጥ ከፍተኛ ትንቅንቅ ቢያደርግም በወገን ጥምር ጦር እንደ ቅጠል ከመርገፍ አልተረፈም፡፡ በወረራ ውስጥ የቆየው ኅብረተሰብ በከፍተኛ ወኔና ጀግንነት በመነሣሣት ከወገን ጦር ጋር ተባብሮ በመሰለፍ አኩሪ ተጋድሎ ፈጽሟል፡፡ አሁንም ክንደ ብርቱውን የወገን ጥምር ጦር መቋቋም አቅቶት በየጢሻው የተበተነውን የአሸባሪውን ጀሌ፣ የየአካባቢው ሕዝብ በመማረክ፣ እምቢ ያለውንም በመደምሰስ የጀግንነት ተግባሩን እንዲፈጽም መንግሥት ጥሪ ያቀርባል፡፡ ነጻነታችንን የምናረጋግጠው በተባበረ ክንዳችን ነው! የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

ኅዳር 30 ቀን 2014 የመከላከያ የሰራዊት ግንባታ ስራዎች ዋና አስተባባሪ ሌ/ጄ ባጫ ደበሌ ፣ የልዩ ዘመቻዎች ሀይል ፣ የሪፐብሊክ ጥበቃ ሀይል እና የአየር ወለድ አባላት በጭንቅ ላይ ያለች አገርን
ኅዳር 30 ቀን 2014 የመከላከያ የሰራዊት ግንባታ ስራዎች ዋና አስተባባሪ ሌ/ጄ ባጫ ደበሌ ፣ የልዩ ዘመቻዎች ሀይል ፣ የሪፐብሊክ ጥበቃ ሀይል እና የአየር ወለድ አባላት በጭንቅ ላይ ያለች አገርን ችግር የፈቱ የጭንቅ ቀን ደራሾች መሆናቸውን አስታወቁ። ሌ/ጄ ባጫ ደበሌ ይህንን የተናገሩት ፣ የመጀመሪያውን ምዕራፍ የሽብር ቡድኑን የመደምሰስ ግዳጅ በድል መገባደድ እና ለቀጣይ ወሳኝ ተልዕኮ መነቃቃትን ለመፍጠር በሚያስችል መልኩ በግንባር በተካሄደ መድረክ ላይ ተገኝተው ነው ። ቀይ መለዮ ለባሾቹ በወሳኝ ወቅት አስቸጋሪና ፈታኝ ግዳጆችን በድል በመወጣት በደማቅ ቀለም የተፃፈ ታሪክ መስራታቸውን ተናግረዋል። ጀግኖቹ ከሰሞኑ በጣርማበርና ዙሪያገባዎቹ የፈፀሙት አንፀባራቂ ድል የጠላትን ቅስም የሰበረ ነው ያሉት ሌ/ጄ ባጫ ደበሌ ፣ አሁንም የደም የመስዋዕትነት እና የድል አድራጊነት ምልክት የሆነውን ቀይ መለዮአቸውን አጥልቀው ለዳግም ድል መትጋት እንዳለባቸው አሳስበዋል። የልዩ ዘመቻዎች ፣ የሪፐብሊኩ ሀይልና አየር ወለዶች የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች እና የምድር ላይ ድሮን መሆናቸውን እንዳስመሰከሩ ሁሉ ፣ የህልውናችን ጠንቅ ሆኖ በምዕራባውያን የሚጋለበውን የህወሀት ሽብር ቡድን እስከ መጨረሻው በመቅበር ታላቁን የድል ዜና መቀሌ ላይ ሆነን እናበስራለን ብለዋል። መላክ በቃሉ (ከግዳጅ ቀጣና) ፎቶግራፍ እፀገነት ዴቢሳ

ኅዳር 30 ቀን 2014 የሃገርን ደህንነት ለማስጠበቅ የሚያስችልና ከውስጥና ከውጭ የሚመጡ ችግሮችን የሚመክት ዘመናዊ የሆነ ባህር ሃይል መገንባት ማደራጀትና ማሰልጠን አስፈላጊ መሆኑን የመከላከያ ባህ
+4
ኅዳር 30 ቀን 2014 የሃገርን ደህንነት ለማስጠበቅ የሚያስችልና ከውስጥና ከውጭ የሚመጡ ችግሮችን የሚመክት ዘመናዊ የሆነ ባህር ሃይል መገንባት ማደራጀትና ማሰልጠን አስፈላጊ መሆኑን የመከላከያ ባህር ሃይል የሰው ሃብት ልማት ዳይሬክተር ካፒቴን ተዘራ በቀለ ተናገሩ ፡፡ ካፒቴን ተዘራ ፣ ቢሾፍቱ ባቦጋያ የሚገኙትን የባህር ሃይል መሠረታዊ ባህርተኞች ፣ በውሃ ዋና የሚሰጡ ግዳጆችን ለመወጣት የሚያስችል ስልጠና ላይ ተገኝተው እንደተናገሩት ፣ የውጭ ሀገራት የእጩ መኮንን ስልጠናዎችና ባህር ዳር ማሪታይም አካዳሚ በኤሌክትርካልና መካኒካል የኢኒጂነሪግ መስክ ሥልጠናዎችን ማከናወን መቻሉን አስረድተዋል ፡፡ አሁን እየሰለጠናችሁ ያላችሁት በመርከብ ላይ ሊደረጉ የሚገቡ የጥንቃቄና የአደጋ መከላከል ደንቦች ጠቀሜታው የጎላ በመሆኑ ያገኘነውን የስልጠና አቅም የኢትዮጵያን ባህር ሃይል በፍጥነት ለግዳጅ ዝግጁ ከማድረግ አንፃር ጠቀሜታው ስትራተጂካዊ ነው ብለዋል፡፡ ካሣሁን ኪዳኔ ፎቶግራፍ ካሣሁን ኪዳኔ ‼️ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት፦ የፌስቡክ ገፃችንን ይከታተሉ https://www.facebook.com/fdredefense.official የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ https://t.me/FDRE_DEFENCE_FORCE በቲዉተር ለመከታተል https://twitter.com/Fdre_defence

ኅዳር 30 ቀን 2014 የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ለመከላከያ ሰራዊታችን 20 ሚሊየን የጥሬ ገንዘብ እና 7 ነጥብ 9 ሚሊየን ብር የአይነት ድጋፍ አደረገ፡፡ የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ ፣
+1
ኅዳር 30 ቀን 2014 የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ለመከላከያ ሰራዊታችን 20 ሚሊየን የጥሬ ገንዘብ እና 7 ነጥብ 9 ሚሊየን ብር የአይነት ድጋፍ አደረገ፡፡ የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ ፣ ኢትዮጵያን በቀደመው የነፃነት ክብሯ ለማስቀጠል በግንባር ላይ እየተዋደቀ ያለ ምንም ስስት ነፍሱን ለሚሰጠው ጀግናው መከላከያ ሰራዊታችን የድጋፍ ክንዳችን ዛሬ ብቻ ሳይሆን በየትኛውም ጊዜ እና ወቅት ይዘረጋል ብለዋል፡፡ የመከላከያ ፋይናንስ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ማርታ ሉዊጂ ፣ ያለምንም መታከት ስላለው ሳይሆን ሃገር ከሁሉም ትቀድማለች ብሎ በማሰብ ካለው ላይ እየቀነሰ ለጀግኖቻችን የሚያደርገው ያልተቋረጠ ድጋፍ ታላቅ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ ብርሃን እንዳየሁ ፎቶግራፍ እፀገነት ዴቢሳ

ኅዳር 30 ቀን 2014 የአሮሚያ ክልል ዛሬም ለመከላከያ ሰራዊታችን 100 ሰንጋዎችን ጨምሮ ከ12 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አደረገ፡፡ የክልሉ የድጋፍ ሃብት አሰባሳቢ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ብርሃኑ ፈይሳ
+1
ኅዳር 30 ቀን 2014 የአሮሚያ ክልል ዛሬም ለመከላከያ ሰራዊታችን 100 ሰንጋዎችን ጨምሮ ከ12 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አደረገ፡፡ የክልሉ የድጋፍ ሃብት አሰባሳቢ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ብርሃኑ ፈይሳ ፣ ክልሉ ዛሬ ለአምስተኛ ዙር ከክልሉ ሴቶች አደረጃጀት ጋር በመተባበር ድጋፍ ያደረገ መሆኑን ተናግረዋል ፡፡ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ፅ/ቤት ኮሙኒኬሽን ባለሙያ አቶ አስቻለው ታደሰ ፣ በዚሁ የአምስተኛ ዙር ድጋፍ ሰራዊታችን ግዳጁን ሲፈፅምባቸው በነበሩ በአፋር እና በሸዋሮቢት ግንባር ድረስ በመሄድ 1ሺ 296 ኩንታል ብርቱካን ፣ 8 ሺ 592 እሽግ ውሃ ፣ አምስት ሮቶ ውሃ ከነተሳቢው በመስጠት ሁለቱ ሮቶ ጦርነቱ እስኪጠናቀቅ ድረስ በቋሚነት እዛው እንዲሰራ አድርገናል ብለዋል፡፡ የአሮሚያ ክልል ሴቶች አደረጃጀት በ3ኛ ዙር ድጋፋቸው 477 ደረቅ ምግቦችን የደገፉ ሲሆን በሶ ፣ ቆሎ እና ዳቦቆሎ በድጋፉ ውስጥ መካተታቸው ተገልጿል፡፡ የተደረገው ድጋፍ በብር ሲቀየርም ከ6 ሚሊየን ብር በላይ ነው ተብሏል፡፡ የክልሉ ሴቶች ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ወ/ሮ አስካለ ለማ ፣ ሴቶች ለሃገራቸው ሰላም የራሳቸውን ሚና መጫወት አለባቸው ብለን ስለምናምን ለጀግኖቻችን ያለንን አጋርነት በድጋፋችን አረጋጠናል ብለዋል፡፡ መከላከያ ሚኒስቴርን በመወከል ርክክቡን የፈፀሙት በፌደራል ደረጃ የክልሎች የድጋፍ ሃብት አሰባሳቢ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶክተር ተመስገን ቡርቃ ፣ የኢትዮጵያ ህዝቦች ከዳር-ዳር ተጠራርተው ለጋራ አላማ በጋራ የቁሙበት ድንቅ ወቅት ላይ መሆናችንን ያረጋገጥንበት እለት በመሆኑ ድጋፍ ለሚያደርጉ አካላት ሁሉ ታላቅ ምስጋና አለኝ ብለዋል፡፡ ብርሃን እንዳየሁ ፎቶግራፍ እፀገነት ዴቢሳ

ኅዳር 30 ቀን 2014 «አሸባሪው ቡድንን እና ባንዳን መንቀል ያለብን ሰርገው ካሉበት ቦታ ብቻ ሳይሆን ከምንጩ ነው » ሜ/ጄ አህመድ ሀምዛ የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ዳይሬክተር
+2
ኅዳር 30 ቀን 2014 «አሸባሪው ቡድንን እና ባንዳን መንቀል ያለብን ሰርገው ካሉበት ቦታ ብቻ ሳይሆን ከምንጩ ነው » ሜ/ጄ አህመድ ሀምዛ የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ዳይሬክተር ፡፡ ኮርፖሬሽኑ በአለም ለ18ኛ በኢትዮጵያ ለ17ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን ባከበረበት ወቅት ሜ/ጄ አህመድ ሀምዛ እንደተናገሩት ፣ ሽብርተኛው በሙስናና በራስ ወዳድነት መኖሩ ሳያንስ ሀገር ለማፍረስ ቢዘጋጅም በመላው ኢትዮጵያዊ ጥረት እየከሸፈ ሲሆን ፣ አሸባሪውን ቡድን እና ባንዳን ከምንጩ ማጥፋት አለብን ብለዋል፡፡፡ በዝግጅቱ ላይ የፌደራል ስነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽንን መልዕክት ያስተላለፉት ወ/ሪት ሳምራዊት ተሾመ ፣ ሙስና እና ብልሹ አሰራር ካለ ሠላምና መረጋጋት አይኖርም ፡፡ ሙስና ጠንካራ የሥራ ባህል እንዳይኖር ያደርጋል ፡፡ ሀገራችን በውስጥና በውጭ የተጋረጠባትን የህልውና አደጋ በፅናት ተቋቁማ ወደ ዕድገት የምታደርገው ጉዞ በሙስናና ብልሹ አሰራር ሊደናቀፍ አይገባም ፡፡ በተለይ አመራሩ ጠንክሮ ሊሠራ ይገባል ብለዋል፡፡ ያነጋገርናቸው የኮርፖሬሽኑ ሠራተኞችም ፣ ከቀድሞው ይልቅ አሁን ያለው ሀገራዊ አንድነታችን ከፍተኛ ነው ፡፡ አሸባሪውን የህወሃት ቡድንን ለማጥፋት በጋራ እንደተነሳን ሁሉ ሙስናና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል ብሎም ለማጥፋት አንድነታችንን አጠናክረን ልንሠራ ይገባል ብለዋል፡፡ «በሥነ-ምግባር የታነፀ አመራር ከሙስና ለፀዳች ኢትዮጵያ» በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው መድረክ ዕለቱን የተመለከተና ሀገራዊ አንድነትን የሚያጠናክር ጥናታዊ ጽሑፍ ፣ ግጥም ፣ መነባነብ ፣ ድራማና ሙዚቃዎች ለታዳሚያን ቀርቧል፡፡ ቃለእግዚአብሔር ፍቃዱ ፎቶግራፍ ብርቱካን ረጋሳ

ኅዳር 30 ቀን 2014 "ሸኔ የወያኔ ጫማ ነው።" የባቲ ከተማ ነዋሪዎች ፡፡ ኢትዮጵያን ለማፍረስ የሽብር ጋብቻ የፈፀሙት ህወሀት ወያኔ እና ኦነግ ሸኔ በባቲ እና አካባቢው የተለያዩ ግፍና በደሎችን
+2
ኅዳር 30 ቀን 2014 "ሸኔ የወያኔ ጫማ ነው።" የባቲ ከተማ ነዋሪዎች ፡፡ ኢትዮጵያን ለማፍረስ የሽብር ጋብቻ የፈፀሙት ህወሀት ወያኔ እና ኦነግ ሸኔ በባቲ እና አካባቢው የተለያዩ ግፍና በደሎችን መፈፀማቸውን ነዋሪዎች አጋለጡ። ሁለቱ ፀረኢትዮጵያ ሀይሎች በባቲና አካባቢው በቆዩባቸው ቀናት የአማራ እና የኦሮሞ ተወላጆችን እንዲሁም የክርስትና እና የእስልምና እምነት ተከታዮችን የዘመናት አብሮነታዊ ባህል ፍፁም በሚቃረን መልኩ አሰቃቂ ግድያ እና አስገድዶ መድፈር መፈፀማቸውን ተናግረዋል። "የትግራይ ህዝብ ነፃ አውጪ ነኝ" የሚለው ወያኔ በባቲ ከተማ በህዝብ የተመረጡ የመንግስት መዋቅሮችን በማፍረስ ለሽብር አላማቸው የሚጋልቧቸውን የኦነግ ሸኔ አባላት በመሾም ዘር የለየ ዝርፊያ አካላዊና ስነልቦናዊ ጥቃት ከመፈፀም ባለፈ የመንግስትና የግል ተቋማትን አውድመዋል ብለዋል። ኦነግ ሸኔ ከአገር አፍራሽ ጋር ያበረ የህወሃት የሽብር ጫማ ነው የሚሉት የባቲ ከተማ ነዋሪዎች ፣ ከአንዳንድ የከተማዋ አመራሮች ጀምሮ አብረዋቸው በኖሩት ተከድተው ለከፍተኛ ስቃይና ችግር ቢዳረጉም የመከላከያ ሰራዊቱ በከፈለላቸው መስዋዕትነት አማካኝነት የነፃነት አየር ለመተንፈስና እንደልብ ለመንቀሳቀስ በመብቃታቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል። መላክ በቃሉ (ከግዳጅ ቀጣና) ፎቶግራፍ ተሰማ ኡርጌሳ

ኅዳር 29 ቀን 2014 በአሸባሪው ሕወሐት ተወርረው የነበሩት ቀሪ ከተሞች፣ የኢትዮጵያ የጸጥታ ኃይሎች ጥምረት፣ በዘመቻ ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት በወሰዱት ማጥቃት ነጻ እየወጡ ነው። ጀግኖቹ የጸጥታ
ኅዳር 29 ቀን 2014 በአሸባሪው ሕወሐት ተወርረው የነበሩት ቀሪ ከተሞች፣ የኢትዮጵያ የጸጥታ ኃይሎች ጥምረት፣ በዘመቻ ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት በወሰዱት ማጥቃት ነጻ እየወጡ ነው። ጀግኖቹ የጸጥታ ኃይሎች ጥምረት ባደረጉት ማጥቃት በደሴ ግንባር ሐይቅ፣ ቢስቲማ፣ ባሶሚሌ እና ውጫሌ ከተሞች ነጻ ወጥተዋል። ሠራዊቱም ወደ መርሳ እየገሠገሠ ነው። በተንታ ግንባር በተካሄደው ማጥቃት ዓለም አምባ፣ መቅደላና ጎሽሜዳ ከአሸባሪው የሕወሐት ወራሪ ነጻ ወጥተዋል። በሁሉም ግንባሮች የጸጥታ ኃይሎች ጥምረት ወደውስጥ ዘልቀው በመግባት የተበታተነውን አሸባሪ ኃይል ቀለበት ውስጥ አስገብተው በመደምሰስ ፣ ወራሪው ኃይል የዘረፈውን ንብረት እንዲሁም የያዘውን መሣሪያና ትጥቅ ይዞ እንዳይወጣ እያደረጉት ይገኛሉ። የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት። ‼️ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት፦ የፌስቡክ ገፃችንን ይከታተሉ https://www.facebook.com/fdredefense.official የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ https://t.me/FDRE_DEFENCE_FORCE በቲዉተር ለመከታተል https://twitter.com/Fdre_defence

ኅዳር 29 ቀን 2014 በምስራቅ ኢትዮጵያ የህወሃትና የሸኔን ተላላኪዎች በቁጥጥር ስር በማዋል የቀጣናውን ሰላምና ደህንነት ለማረጋገጥ የሚያስችል ዝግጁነት እንዳለው የምስራቅ ዕዝ ደጀን ሃይል አስታወ
+1
ኅዳር 29 ቀን 2014 በምስራቅ ኢትዮጵያ የህወሃትና የሸኔን ተላላኪዎች በቁጥጥር ስር በማዋል የቀጣናውን ሰላምና ደህንነት ለማረጋገጥ የሚያስችል ዝግጁነት እንዳለው የምስራቅ ዕዝ ደጀን ሃይል አስታወቀ፡፡ 16ኛውን የብሄር ብሄረሰቦች ቀንን አስቦ ለመዋል በተዘጋጀው ዝግጅት ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የምስራቅ ዕዝ አዛዥ ፅ/ቤት ሃላፊና የደጀን ሃይል አስተባባሪ ኮ/ል ሲሳይ ታደሰ እንደተናገሩት ፣ የዘንድሮው የብሄር ብሄረሰቦች ቀን እየተከበረ ያለው የብሄር ብሄረሰቦች ጠላት የሆነው ህወሃት እየተቀበረ በሚገኝበት ወቅት በመሆኑ ድላችንን ድርብ ድርብርብ ያደርገዋል ብለዋል፡፡ ውስጣዊ አንድነታችንን በማጠናከር በቀጣናችን ተሰግስገው የሚገኙ የህወሃትና የሸኔ ተላላኪዎች ከሌሎች የፀጥታ ሃይሎች ጋር በመቀናጀት በቁጥጥር ስር እየዋሉ ሲሆን ፣ በቀጣይነትም አሸባሪው በግንባር ያጣውን ድል በሽብር ለማካካስ ሊሞክር ስለሚችል አስፈላጊው የክትትልና የቁጥጥር ስራዎችን በመስራት የቀጣናውን ሰላምና ደህንነት ለማረጋገጥ የሚያስችል ዝግጁነት ያስፈልጋል ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ዳንኤል አወል ፎቶግራፍ እታለም ሰበቦ ‼️ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት፦ የፌስቡክ ገፃችንን ይከታተሉ https://www.facebook.com/fdredefense.official የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ https://t.me/FDRE_DEFENCE_FORCE በቲዉተር ለመከታተል https://twitter.com/Fdre_defence

ኅዳር 29 ቀን 2014 አንጋፋ የኢትዮጵያ አትሌቶች ማህበር ለመከላከያ ሰራዊታችን ከ110ሺ ብር በላይ የዓይነት ድጋፍ አደረገ ፡፡ ማህበሩን በመወከል ንግግር ያደረጉት ኮማንደር ጌጤ ዋሚ ፣ እኛ በተ
+2
ኅዳር 29 ቀን 2014 አንጋፋ የኢትዮጵያ አትሌቶች ማህበር ለመከላከያ ሰራዊታችን ከ110ሺ ብር በላይ የዓይነት ድጋፍ አደረገ ፡፡ ማህበሩን በመወከል ንግግር ያደረጉት ኮማንደር ጌጤ ዋሚ ፣ እኛ በተለያየ ጊዜ እና ወቅት በስፖርቱ አለም የሃገራችን ሰንደቅ አላማ ከፍ ብሎ እንዲውለበለብ የኢትዮጵያ ክብር እና ዝና ጎልቶ እንዲወጣ ስናደርግ ቆይተናል፡፡ አሁንም ለኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ሲል እየቆሰለ እና እየደማ ለሚገኘው ሰራዊታችን አጋርነታችንን ለመግለፅ ድጋፍ አድርገናል ብለዋል፡፡ የመከላከያ ፋይናንስ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ማርታ ሉዊጂ በበኩላቸው ፣ ስፖርተኞች እና ወታደሮች ለሃገራቸው ክብር እና ፍቅር ሲሉ መስዋዕትነት የሚከፍሉ በመሆናቸው ያመሳስላቸዋል፤ ዛሬም በስፖርቱ ሜዳ የኢትዮጵያን ስም በአለም መድረክ ሲያስጠሩ የቆዩ አትሌቶቻችን ላደርጉት ድጋፍ ታላቅ ምስጋና እና አክብሮት አለኝ ብለዋል፡፡ ብርሃን እንዳየሁ ፎቶግራፍ እፀገነት ዴቢሳ ‼️ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት፦ የፌስቡክ ገፃችንን ይከታተሉ https://www.facebook.com/fdredefense.official የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ https://t.me/FDRE_DEFENCE_FORCE በቲዉተር ለመከታተል https://twitter.com/Fdre_defence

ኅዳር 29 ቀን 2014 ጀግናው የመከላከያ ሰራዊታችን በአማራ ብሄራዊ ክልል ኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ባቲ ከተማ ሲደርስ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። በሽብርተኛው ህዝቦችን የመነጣጠል ሴራ እና በኦ
+2
ኅዳር 29 ቀን 2014 ጀግናው የመከላከያ ሰራዊታችን በአማራ ብሄራዊ ክልል ኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ባቲ ከተማ ሲደርስ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። በሽብርተኛው ህዝቦችን የመነጣጠል ሴራ እና በኦነግ ሸኔ የፀረአንድነት አካሄድ ምክንያት የቅርብ ሩቅ ሆነው የነበሩት በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር እና የአፋር ክልል ህዝቦችም ከአመታት በኋላ በባቲ ከተማ በደስታ ለመተቃቀፍ በቅተዋል። መላክ በቃሉ (ከግዳጅ ቀጣና) ፎቶግራፍ ተሰማ ኡርጌሳ ‼️ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት፦ የፌስቡክ ገፃችንን ይከታተሉ https://www.facebook.com/fdredefense.official የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ https://t.me/FDRE_DEFENCE_FORCE በቲዉተር ለመከታተል https://twitter.com/Fdre_defence

ኅዳር 29 ቀን 2014 ስታር ቢዝነስ ግሩፕ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ለመከላከያ ሠራዊታችን የ395 ሺ ብር መድኃኒት ድጋፍ አደረገ ፡፡ የማህበሩ ሀላፊ አቶ ሸጋሰው ወርቁ ፣ በህይወት እኩይ
+1
ኅዳር 29 ቀን 2014 ስታር ቢዝነስ ግሩፕ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ለመከላከያ ሠራዊታችን የ395 ሺ ብር መድኃኒት ድጋፍ አደረገ ፡፡ የማህበሩ ሀላፊ አቶ ሸጋሰው ወርቁ ፣ በህይወት እኩይ ተግባር መስዋዕትነት እየከፈለ ላለው ጀግናው የመከላከያ ሰራዊታችን የሚያደርጉት ድጋፍ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡ ድጋፉን የተረከቡት የጦር ሀይሎች ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሜዲካል ሎጄስቲክ ዳይሬክተር ኮ/ል ዶ/ር ገነት ይማም ፣ በሽበርተኛው ህወሃት ሰራዊታችን ላይ ጥቃት ከተቃጣበት ጀምሮ ህዝባችን ያለውን ድጋፍ እያደረገ በመሆኑ ለሰራዊታችን የሞራል ስንቅ ነው ፡፡ ለተደረገው ድጋፍም አመሰግናለሁ ብለዋል፡፡ አሰራት ወልደኪዳን ፎቶግራፍ አብይ ግሩም ‼️ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት፦ የፌስቡክ ገፃችንን ይከታተሉ https://www.facebook.com/fdredefense.official የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ https://t.me/FDRE_DEFENCE_FORCE በቲዉተር ለመከታተል https://twitter.com/Fdre_defence