ኢትዮ Crypto
Open in Telegram
Hello. Bonus $1000 for registration. Casino🎰 BONUS promo code 1000$🎰 PROMO - 555 👇👇👇👇👇👇 https://Rbeto.com/auth/register?promo=555
Show more2 370
Subscribers
No data24 hours
-47 days
-4530 days
Posts Archive
2 370
#DillaUniversity
ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከ1 ሺህ 500 በላይ ተማሪዎችን ቅዳሜ ሰኔ 25/2014 ዓ.ም ያስመርቃል።
ተመራቂዎቹ በተለያዩ የሙያ መስኮች በመደበኛ፣ በክረምት እንዲሁም በቅዳሜና እሁድ መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።
እጩ ተመራቂዎቹ ከመጀመሪያ እስከ ሦሥተኛ ዲግሪ ተማሪዎች መሆናቸው ተገልጿል።
ዲላ ዩኒቨርሲቲ ባለፉት 25 ዓመታት ከ76 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ማስመረቁ ተመላክቷል።
"የአፕላይድ ሳይንስ" ዩኒቨርሲቲ ተብሎ የተመደበው ተቋሙ፤ ከ28 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በተለያዩ የሙያ ዘርፎች በማስተማር ላይ ይገኛል።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#DireDawaUniversity
ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የ2014 ዓ.ም የተማሪዎች የምረቃ ስነ ስርዓት ሰኔ 25/2014 ዓ.ም ያከናውናል።
ተመራቂዎቹ በመደበኛ እና በተከታታይ መርሃ ግብር በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።
ተማሪዎቹን በድምቀት ለማስመረቅ ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#BahirdarUniversity
የባህርዳር ዮንቨርስቲ ተማሪዎች በወለጋ የተፈፀመውን ዘር ተኮር ጭፍጨፋ በመቃወም የምግብ አድማ አድርገዋል::
#wollegamassacre #AmharaGenocide #Ethiopia
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#DebreMarkosUniversity
በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት ፈቃዱ እንግዳ "ከደረቅ ቆሻሻ የጭስ አልባ ከሰል ምርት" በማቅረብ የንግድ ሥራ ሃሳብ አሸናፊ ሆነዋል፡፡
አቶ ፈቃዱ እንግዳ በዩኒቨርሲቲው የሲቪልና ውሃ ሃብት ምህንድስና ትምህርት ቤት መምህር ናቸው።
መምህር ፈቃዱ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ባዘጋጁት የዩኒቨርሲቲ-ኢንደስትሪ ትስስር የምርምር ውጤቶች የገንዘብ ድጋፍ ውድድር ላይ የንግድ ሥራ ሃሳባቸውን በማቅረብ አሸናፊ ሆነዋል፡፡
በውድድሩ ላይ ከ20 ዩኒቨርሲቲዎች የተወጣጡ 49 የተጠናቀቁ እና ወደ ገበያ ሊገቡ የሚችሉ የምርምርና የንግድ ሥራ ሃሳቦች ቀርበዋል።
ውድድሩ የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም (UNDP) እና የእንግሊዝ ተራድኦ ድርጅት (FCDO) የሚደገፍ ነው።
መምህሩ ያቀረቡት የንግድ ሥራ ሃሳብ "Smokeless Charcoal Production from Organic Wastes" የተባለ ሲሆን ወደ ገበያ ለማስገባት የሚያስችለውን የገንዘብና የቴክኒክ ድጋፍ አሸንፏል።
ለሥራው ማስቀጠያ የሚሆን የግማሽ ሚሊየን ብር ድጋፍ መገኘቱን የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የዩኒቨርሲቲ-ኢንዱስትሪ ትስስርና ቴክኖሎጅ ሽግግር ዳይሬክተር ይበልጣል ታረቀኝ (ረ/ፕ) ገልጸዋል፡፡
ለዚህም ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ፣ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና የትምህርት ሚኒስቴር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#BahirDarUniversity
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መንግስት የዜጎችን የመኖር መብት እንዲያስከብር ጥሪ አቅርበዋል።
ተማሪዎቹ ዛሬ ሰኔ 20/2014 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲው የተለያዩ ግቢዎች ባካሄዱት ሰላማዊ ሰልፍ ሰሞኑን በምዕራብ ወለጋ ዞን ጊምቢ ወረዳ ቶሌ ቀበሌ በሚኖሩ ንፁሃን የአማራ ተወላጆች ላይ የደረሰውን ማንነትን መሰረት ያደረገ አሰቃቂ ጅምላ ግድያ አውግዘዋል።
መንግስት የዜጎችን የመኖር መብት እንዲያስጠብቅ በተለይም በአማራ ተወላጆች ላይ በተደጋጋሚ እየደረሰ ያለውን ማንነትን መሰረት ያደረገ ጥቃት በአስቸኳይ እንዲያስቆም ጠይቀዋል።
ምንጭ፦ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ከ6 ሺህ በላይ ተማሪዎችን
ሐምሌ 09/2014 ዓ.ም ያስመርቃል።
ተመራቂዎቹ በመደበኛ እና በተከታታይ መርሃ ግብር በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ እና በዶክትሬት ዲግሪ ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።
በ1999 ዓ.ም የተቋቋመው ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ፤
ከ38 ሺህ የሚበልጡ ተማሪዎችን አስመርቋል።
በአሁን ወቅት ከ40 ሺህ የሚበልጡ ተማሪዎችን በሰባት ኮሌጆች እና በሦሥት ትምህርት ቤቶች እያስተማረ ይገኛል።
“የአፕላይድ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲ” የሆነው ተቋሙ፤ በ2022 ዓ.ም "ቴክኖሎጂ መር የግብርናና የጤና ልህቀት ማዕከል"ለመሆን እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በሂሳብ ትምህርት አዲስ የ2ኛ ዲግሪ ፕሮግራም ለመክፈት ዝግጅት ላይ ነው።
ፕሮግራሙን ለማስጀመር በውጭ ባለድርሻ አካላት የካሪኩለም ግምገማ ማካሄዱን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
በቀጣይ ፕሮግራሙን ለዩኒቨርሲቲው ሴኔት አቅርቦ በማጸደቅ ትምህርቱን ለመጀመር እንደሚሰራ ገልጿል፡፡
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#ማሳሰቢያ📣
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የፀጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ መግለጫ ሰጥቷል።
ግብረ ኃይሉ ሽብርተኛ ተብሎ የተፈረጀው ህውሃት ቡድን ፋይናንስ ያደርጋቸዋል ያላቸው ሚዲያዎች የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት ለማደናቀፍ ተማሪዎች በብሄርና በሀይማኖት በመከፋፈል ግጭት እንዲፈጠር ለማነሳሳት ሌት ተቀን እሰሩ እንደሆነ ደርሼበታለሁ ብሏል።
እነዚሁ ሚዲያዎች ሰሞኑን «በአማራ ክልል ዩኒቨርስቲዎች የሚማሩ የኦሮሞ እና የሌሎች ብሄር ተማሪዎችን ለማጥቃት የተደራጀ የደህንነት ቡድን ወደ አማራ ክልል ተልኳል» የሚል በዩኒቨርሲቲዎች ግጭት ለማስነሳት መልዕክት አስተላልፈዋል ብሏል።
የዩኒቨርሲቲዎችን ሰላም ለማናጋት እና ተማሪዎች በሰላም እንዳይማሩ የሚያደርጉ አካላትን ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ያሳሰበው ግብረኃይሉ ይህን ተላልፈው በሚገኙት ላይ ጥብቅ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወድ አስጠንቅቋል።
ዩኒቨርሲቲዎች፣ ተማሪዎችና ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላት ሆን ተብሎ ግጭት ለማስነሳት እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን በመገንዘብ እራሳቸውን በመጠብቅ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የፀጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይሉ አሳስቧል።
(የግብረ ኃይሉ ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
ፈተና አላሰራከኝም በሚል ምክንያት ድብደባ የፈጸሙት ሎካል ተማሪዎች
ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተለያዩ የሀገራችን ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ላይ እየተለመዱ የመጡ ነውረኛ ድርጊቶች ተበራክተዋል። በብዙ ዩንቨርሲቲዎቻችን ላይ ሎካል በመባል የሚታወቁ ዩንቨርሲቲው በሚገኝበት አካባቢ ነዋሪ የሆኑ ተማሪዎች በሌሎች ተማሪዎች ላይ አለፍ ሲልም በግቢው ሰራተኞች ላይ መምህራንንም ጨምሮ ጫና ሲያሳድሩ ይስተዋላል። ሎካል የሚባሉት ስብስቦች ያደርሷቸዋል ከሚባሉት ጫናዎች መካከል በብዛት የሚደርሱን ጥቆማዎች በፈተና ወቅት የሚፈፀሙ ተገቢ ያልሆኑ ድርጊቶች ናቸው።
አንዳንድ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ላይ ግልፅ በሆነ መልኩ ሎካል ለሚባሉት ተማሪዎች የፈተና ጥያቄዎች ቀድመው እንደሚወጡ በተለያዩ ጊዜያት ከሚደርሱን ጥቆማዎች ለመረዳት ችለናል።
አዲሱ የትምህርት ፍኖተ ካርታ ተግባራዊ መደረግ ከጀመረ ወዲህ በብዛት የሚፈለጉ የትምህርት መስኮችን ለመቀላቀል በሚደረገው ውድድር ላይም የሎካሎች ተጽዕኖ ቀላል እንዳልሆነ በርካታ ተማሪዎች በምሬት ጭምር ነግረውናል።
ሎካል የሚባሉ ተማሪዎችን የተለያዩ ፀያፍ ድርጊቶች በሌላ ሰፊ ዳሰሳ የምንመለስበት ይሆናል።
ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን የምትመለከቱት የተንቀሳቃሽ ምስል በትላንትናው ዕለት ያካፈሉን መረጃ ሲሆን ድርጊቱ የተፈፀመው በወልቂጤ ዩንቨርሲቲ ሎካል ተማሪዎች መሆኑን አረጋግጠናል።
የተማሪውን ጉዳይ በቅርበት እየተከታተልን ሲሆን ዩንቨርሲቲው በተማሪዎቹ ላይ የሚወስደውን እርምጃ እንዲሁም የተማሪውን የደህንነት ጉዳይ ተከታትለን እናሳውቃቹሃለን።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
የባህርዳር ዩንቨርስቲ ተማሪዎች በወለጋ ለተጨፈጨፉ ዜጎች ድምፅ ለመሆን በዛሬው እለት ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተዋል።
በዛሬው እለት የዩንቨርስቲው ተማሪዎች በኦሮሚያ ክልል በወለጋ የተፈጸመውን ግድያ ለማውገዝ እና ለተጎዱ ዜጎች ድምፅ ለመሆን ሰላማዊ ሰልፍ እያደረጉ ይገኛል።
በሰልፉ ላይ ተማሪዎቹ በማንነት ላይ ያነጣጠረ ጥቃት እና ግድያን በግልፅ መቃወማቸውን ከባህርዳር የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
ወለጋ ዩኒቨርሲቲ በተማሪች የቀረቡ የፈጠራ ሥራ ንድፈ ሃሳቦችን ገምግሟል።
የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ቴክኖሎጂ ማዕከል የፈጠራ ሃሳብ ያላቸው ተማሪዎች ንድፈ ሃሳባቸውን እንዲያስገቡ ጋብዞ ነበር።
የተለያዩ የፈጠራ ሥራ ያላቸው ተማሪዎች የንድፈ ሃሳባቸውን ፕሮቶ ታይፕ አቅርበዋል።
የፀሃይ ኃይል መሰብሰቢያ ማሺን ከቀረቡ የፈጠራ ሥራ ንድፈ ሃሳቦች መካከል ይጠቀሳል።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
ፎቶ / ቪድዮ ፦ በኦሮሚያ ክልል ፤ ምዕራብ ወለጋ ጊምቢ ወረዳ ፤ ቶሌ ቀበሌ ላት ባለፈው ሰኔ 11 /2014 የተፈፀመውን የንፁሃን ግድያ በማውገዝ ሰልፍ የወጡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ፀጥታ ኃይሎች እንደበተኗቸው ለማወቅ ተችሏል።
ተማሪዎቹ " ሞት ይብቃን፣ አትግደሉን...ያልሞትነው ተራችን ገና ስለሆነ ነው ፣ ዛፉ ከሰው ልጅ ያንሳል እንጂ አይበልጥም ፣ አባይን የምንገድበው ለሰው ፣ ለድሃ እንጂ ለዛፍ ማጠጫ አይደለም እና ሌሎች መስል መልዕክቶችን እያሰሙ ከዩኒቨርሲቲው ተነስተው ወደ 4 ኪሎ ቤተ መንግስት አቅጣጫ እየተጓዙ ነበር።
የፀጥታ ኃይሎች በሰልፈኞች ላይ የማባረር እና የመደብደብ ድርጊት መፈፀማቸውን በተሰራጩ ቪድዮዎች ለማየት ተችላሏል።
ከዩኒቨርሲቲው አልያም ከፌዴራል ፖሊስ የሚገኝ ማብራሪያ ካለ ተከታትለን እናሳውቃለን።
ፎቶ/ ቪድዮ ፦ ባንተይሁን (Tikvah Family) & ሶሻል ሚዲያ
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#UniversityOfGondar
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በምዕራብ ወለጋ ዞን ጊምቢ ወረዳ ቶሌ ቀበሌ በሚኖሩ ንፁሃን የአማራ ተወላጆች ላይ የደረሰውን ዘር ተኮር አሰቃቂ ግድያ በሰላማዊ ሰልፍ አውግዘዋል።
ተማሪዎቹ ዛሬ ጠዋት በተቋሙ ግቢ ውስጥ ባካሄዱት ሰልፍ "መንግስት ህግ ያስከብር"፣ "ዘር ተኮር ጥቃት ይቁም"፣ "ሰላም እንፈልጋለን" እና መሰል መልዕክቶችን አሰምተው ወደ መደበኛ ትምህርታቸው መመለሳቸውን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።
"የሁሉም ብሔር ልጆች የሆኑት ተማሪዎች ድርጊቱን ያለልዩነት በሰለጠነ መንገድ ማውገዛቸውን" ዩኒቨርሲቲው ጠቁሟል። #ጎንደር_ዩኒቨርሲቲ
በምዕራብ ወለጋ ቶሌ ቀበሌ ሰኔ 11/2014 ዓ.ም በተፈጸመው ጥቃት ከ700 የሚልቁ ንጹሀን ሰዎች መገደላቸውን የዐይን እማኞች ተናግረዋል።
መንግስት እስካሁን የሟቾቹን ቁጥር ይፋ ያላደረገ ሲሆን ‘ሸኔ’ በመባል የሚታወቀውን ታጣቂ ኃይል ተጠያቂ አድርጓል።
📸 ጎንደር ዩኒቨርሲቲ
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#ጥቆማ
ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ከኬሮድ ስፖርት ማህበር እና ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የ15 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ እሁድ ሰኔ 19/2014 ዓ.ም ይከናወናል።
ለ”ኢትዮጵያ ሰላም እንሩጥ” በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው ውድድሩ፤ መነሻውን ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በማድረግ በወልቂጤ ከተማ ይጠናቀቃል፡፡
ውድድሩ የዩኒቨርሲቲውን ገጽታ እና አካባቢውን ለማስተዋወቅ ያግዛል ተብሏል።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#DillaUniversity
ዲላ ዩኒቨርሲቲ ሀገር ዐቀፍ ዲጂታል መታወቂያ ለተማሪዎቹ የማዘጋጀት ሥራ ነገ ይጀምራል።
ከጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት የተመደቡ ባለሙያዎች ከነገ ሰኔ 18/2014 ዓ.ም ጀምሮ ዲጂታል መታወቂያ ለዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች እንደሚያዘጋጁ ተገልጿል።
የዩኒቨርሲቲው አራቱም ካምፓሶች የሚገኙ ተማሪዎች
ፎቶ በመነሳትና ቅፅ በመሙላት የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ያከናውናሉ ተብሏል።
መንግስት በ2014 ዓ.ም በተመረጡ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ለማካሄድ እቅድ መያዙ ይታወቃል።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#KabridaharUniversity
ቀብሪደሃር ዩኒቨርሲቲ የነዳጅ ምህንድስና የትምህርት ፕሮግራም በቀጣይ ዓመት ይጀምራል።
የፕሮግራሙ ስርዓተ ትምህርት ለዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ምክር ቤት ቀርቧል።
የፕሮግራሙ አዋጭነት እንዲሁም የፕሮግራሙ በቀብሪደሃር ዩኒቨርሲቲ መጀመር የሚፈጥረው ዕድል እና የሚገጥመው ፈተና ላይ ውይይት ተደርጓል።
ፕሮግራሙን በቀጣይ የትምህርት ዘመን ለመጀመር ዝግጅት በመጠናቀቅ ላይ መሆኑ ተገልጿል።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#UniversityOfGondar
ሦሦተኛ ዙር የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የቃልኪዳን ቤተሰብ ትስስር መርሃ ግብር ሰኔ 26/2014 ዓ.ም ይካሄዳል።
ዩኒቨርሲቲው ለአዲስ ገቢ ተማሪዎች ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ ከጎንደር ከተማ ሕዝብ ጋር የቃል ኪዳን ቤተሰብ ትስስር ሲፈጥር መቆየቱ ይታወሳል፡፡
ትስስሩ የኢትዮጵያን ታሪክ፣ የተለያዩ ባህሎች እና ቋንቋዎች ለማስተዋወቅ ያግዛል ተብሏል።
የቤተሰብ ምልመላ፣ የተማሪ-ቤተሰብ ግንኙነትን እንዲሁም ተማሪዎች ከተመረቁ በኋላ ከጎንደር ቤተሰብ ጋር የሚኖራቸውን ዘላቂ ግንኙነትና ውጤት የሚከታተል 'የጎንደር የቃልኪዳን ቤተሰብ ትስስር ጽ/ቤት' ተቋቁሞ እየሠራ እንደሚገኝ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት አስራት አፀደወይን (ዶ/ር) ተናግረዋል።
የጎንደር ከተማ ህዝብ አዲስ ቤተሰቡን ለመቀበል በመመዝገብ ላይ እንደሚገኝ የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፤ መስፈርቱን የሚያሟሉ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች በመርሃግብሩ በመገኘት እንዲሳተፉ ጋብዘዋል።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#ArbaMinchUniversity
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የ2014 ዓ.ም የተማሪዎች የምረቃ ስነ-ስርዓት ሰኔ 25/2014 ዓ.ም ያከናውናል።
ዩኒቨርሲቲው በመደበኛ እና በተከታታይ መርሃ ግብር ከመጀመሪያ እስከ ሦሥተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎችን በዕለቱ ያስመርቃል።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
