ኢትዮ Crypto
Open in Telegram
Hello. Bonus $1000 for registration. Casino🎰 BONUS promo code 1000$🎰 PROMO - 555 👇👇👇👇👇👇 https://Rbeto.com/auth/register?promo=555
Show more2 370
Subscribers
No data24 hours
-47 days
-4530 days
Posts Archive
2 370
አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ (AASTU) እንዲሁም አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ (ASTU) በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማሯቸውን ተማሪዎች ነገ ሰኔ 25/2014 ዓ.ም ያስመርቃሉ።
በተመሳሳይ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ (ECSU) በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ነገ ሰኔ 25/2014 ዓ.ም ያስመርቃል።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#ArbaMichUniversity
አርባ ምንጭ የኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 2 ሺህ 540 ተማሪዎች ያስመርቃል።
ተመራቂዎቹ ከመጀመሪያ እስከ 3ኛ ዲግሪ በመደበኛ፣ በክረምት፣ በማታ፣ በሳምንት መጨረሻ እና በተከታታይ መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።
ከዩኒቨርሲቲው 35ኛ ዙር ተመራቂዎቹ መካከል 657ቱ ሴቶች መሆናቸው ተገልጿል፡፡
የተማሪዎች የምረቃ ስነ ስርዓት ነገ ሰኔ 25/2014 ዓ.ም እና እሁድ ሰኔ 26/2014 ዓ.ም ይከናወናል።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
ሠመራ ዩኒቨርሲቲ እና የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት በትብብር ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።
ስምምነቱ ሁለቱ ተቋማት በጥናትና ምርምር፣ በፖሊሲ ቀረጻ፣ በባለሙያና ልምድ ልውውጥ፣ በስልጠናና የአቅም ግንባታ ሥራዎች እና ሌሎችም ጉዳዮች በጋራ ለመስራት ያስችላቸዋል ተብሏል።
የሠመራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት መሃመድ ኡስማን (ዶ/ር) እና የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ደሳለኝ አምባው (ዶ/ር) ስምምነቱን ፈርመዋል።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#WachemoUniversity
ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን 1 ሺህ 445 ተማሪዎች ነገ ያስመርቃል።
ተመራቂዎቹ በመጀመሪያ እና በ2ኛ ዲግሪ ፕሮግራም ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።
ዩኒቨርሲቲው ከ26 ሺህ በላይ ምሩቃንን በተለያዩ የሙያ መስኮች አሰልጥኖ አስመርቋል።
"የአጠቃላይ ወይም ኮምፕሪሄንስቪ" ዩኒቨርሲቲ ተብሎ የተመደበው ተቋሙ፤ በአሁን ወቅት ከ27 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በማስተማር ላይ ይገኛል።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#Mattu_University
መቱ ዩኒቨርሲቲ ሲጠቀምበት የቆየውን የተቋሙን አርማ/ሎጎ ቀይሯል።
አዲሱ አርማ የተቋሙን ተልዕኮ እና ራዕይ መሰረት ባደረገ እንዲሁም የአካባቢውን እሴት፣ ባህል እና የተፈጥሮ ሃብትን ባማከለ መልኩ መዘጋጀቱን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።
አዲሱ አርማ በአፋን ኦሮሞ የዩኒቨርሲቲውን ስያሜ ተጨማሪ አድርጎ አካቷል። ይህም ተቋሙ የሚገኝበት የአካባቢውን ቋንቋ በአርማው ላይ ለማካተት በማሰብ የተደረሰ እንደሚሆን ይገመታል።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#BuleHoraUniversity
የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የሥራ አመራር ቦርድ የዩኒቨርሲቲውን ፕሬዝዳንት እና ሁለት ምክትል ፕሬዝዳንቶች ከኃላፊነታቸው አንስቷል፡፡
ከኃላፊነታቸዉ በተነሱት አመራሮች ምትክ አዲስ አመራሮች በቦርዱ ተመድበዋል።
በዚህም ታምሩ አኖሌ (ዶ/ር) የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ሆነው ተመድበዋል። አቶ ዳራራ ሰናይ የቢዝነስ እና ተቋማዊ ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት እንዲሁም ትንሳዔ ታምራት (ዶ/ር) የምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት በመሆን መመደባቸውን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
አዲስ የተመደቡት አመራሮች የሥራ ርክክብ ማድረጋቸውም ተመላክቷል፡፡
የሥራ አመራር ቦርዱ ያካሄደውን የሥራ ግምገማ ተከትሎ አስተዳደራዊ እርምጃው መወሰዱን ቢገልጽም፤ አመራሮች ከኃላፊነታቸው የተነሱበትን ምክንያት በግልፅ አላስቀመጠም። (ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ)
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#HawassaUniversity
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከመጀመሪያ እስከ ሦሥተኛ ዲግሪ ያስተማራቸውን 6 ሺህ 24 ተማሪዎች ነገ ያስመርቃል።
ተመራቂዎቹ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በመደበኛ እና በተከታታይ መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።
ከተመራቂዎቹ መካከል 18 በPhD፣ 46 በስፔሻሊቲ እና 1,604 በ2ኛ ዲግሪ መሆናቸውን የዩኒቨርሲቲው የሬጅስትራርና አልሙናይ ዳይሬክተር ዘሪሁን ክፍሌ (ዶ/ር) ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ገልጸዋል።
ከ2014 ዓ.ም ጠቅላላ ተመራቂዎች ውስጥ 1 ሺህ 421ዱ (24 በመቶ) ሴት ተማሪዎች መሆናቸውን ጠቁመዋል።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#Mettu_University
መቱ ዩኒቨርሲቲ ከ1 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ቅዳሜ ሰኔ 25/2014 ዓ.ም ያስመርቃል።
ተመራቂዎቹ በመደበኛ እና በተከታታይ መርሃ ግብር በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#AmboUniversity
አምቦ ዩኒቨርሲቲ ከ4 ሺህ 400 በላይ ተማሪዎችን ቅዳሜ ሰኔ 25/2014 ዓ.ም ያስመርቃል።
ተመራቂዎቹ በተለያዩ የሙያ መስኮች በመደበኛ፣ በክረምት እንዲሁም በቅዳሜና እሁድ መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።
ከተመራቂዎቹ መካከል ሁለቱ በ 'PhD' ሲሆኑ 23ቱ ደግሞ የሜዲሲን ተማሪዎች መሆናቸውን ሰምተናል።
በትግራይ ክልል ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች በጊዚያዊነት በአምቦ ዩኒቨርሲቲ ተመድበው ትምህርታቸውን የተከታተሉ 448 ተማሪዎች በዕለቱ ይመረቃሉ።
አንጋፋው አምቦ ዩኒቨርሲቲ የተመሰረተበትን 75ኛ ዓመት በቅርቡ ማክበር እንደሚጀምር የዩኒቨርሲቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ መንግስቱ ባላቻ (ዶ/ር) ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ተናግረዋል።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#WolkiteUniversity
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሴኔት በ2014 ዓ.ም የሚመረቁ ተማሪዎችን አጽድቋል።
ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 1 ሺህ 53 ተማሪዎች ቅዳሜ ሰኔ 25/2014 ዓ.ም ያስመርቃል።
ከተመራቂዎቹ 64ቱ በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።
የዩኒቨርሲቲው ሴኔት የሦሥት መምህራን የሥራ አፈጻጸም በመገምገም የማዕረግ እድገትም ሰጥቷል።
1. ብርሀኑ አራጌ (ዶ/ር) ~ ከፊዚክስ ት/ት ክፍል ከረዳት ፕሮፌሰርነት ወደ ተባባሪ ፕሮፌሰርነት
2. ሳሙኤል ደሱ ~ ከኅብረተሰብ ጤና ት/ት ክፍል የረዳት ፕሮፌሰርነት ማዕረግ የተሰጣቸው
3. ሂርፓሳ ተሬሳ ~ ከባዮሎጂ ትምህርት ክፍል
የረዳት ፕሮፌሰርነት ማዕረግ የተሰጣቸው
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
👆👆
ehen mereja groupoch lay share argut, letaserut temariwochu/wendmochachn dimts linhon yigebal
2 370
#EthiopianHumanRightsCouncil
መንግስት በእስር ላይ የሚገኙ ሰልፈኛ ተማሪዎችን እንዲፈታ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) ጠይቋል።
በኦሮሚያ እና ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ታጣቂዎች ሰኔ 11/2014 ዓ.ም የፈጸሟቸውን ጥቃቶች ለማውገዝ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሰኔ 18/2014 ዓ.ም እንዲሁም በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጥበብ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የሕክምናና ጤና ሳይንስ
ተማሪዎች ሰኔ 20/2014 ዓ.ም ሰላማዊ ሰልፎች ማድረጋቸውን ኢሰመጉ አስታውሷል።
የጸጥታ ኃይሎች አስለቃሽ ጭስና ኃይል በመጠቀም ሰልፎቹ እንዲበተኑ ማድረጋቸውን ጉባዔው ጠቁሟል።
በሁለቱም ዩኒቨርሲቲዎች በነበሩ ሰልፎች የተደበደቡ እና የታሰሩ ተማሪዎች እንደሚገኙ ከሰበሰባቸው መረጃዎች መረዳቱን ኢሰመጉ ገልጿል።
መንግስት የዜጎችን ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብት እንዲያከብር የጠየቀው ጉባዔው፤ ሰላማዊ ሰልፍ ሲያደርጉ በነበሩ ተማሪዎች ላይ ድብደባ እና እንግልት የፈጸሙ አካላትን ለህግ በማቅረብ ተጠያቂ እንዲያደርግ አሳስቧል።
(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል።)
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#AddisAbaba
71 ሺ 832 ተማሪዎች የሚፈተኑበት የዘንድሮው የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ሰኔ 27 ይጀምራል።
የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ከሰኔ 27 እስከ 29 እንደሚሰጥ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ምክትል ሃላፊ አቶ ዳኘው ገብሩ በፈተናው አሰጣጥ ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫው የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና በከተማዋ በ 792 ትምህርት ቤቶች እንደሚሰጥ ተነግሯል።
ለዚህም 179 የመፈተኛ ጣቢያዎች ተዘጋጅተዋል ብለዋል ።
አቶ ዳኘው አክለውም አጠቃላይ በከተማዋ 71 ሺህ 832 ተማሪዎች እንደሚፈተኑ ነው የተናገሩት።
ኮማንድ ፖስት ተቋቁሞ እስካሁን ያለውን የፈተናው ዝግጅት ሂደት የገመገመ ሲሆን ፈተናው ወደ መፈተኛ ጣቢያዎች ለማጓጓዝ ሂደት ላይ ነውም ተብሏል።
ሰኔ 24 ቀንም ለሁሉም ፈተናውን ለሚመለከት የትምህርት ማህበረሰብ ኦረንቴሽን እንደሚሰጥም ተገልጿል፡፡
(አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ)
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#Update
የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ከሰኔ 27 እስከ 29 እንደሚሰጥ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ምክትል ሃላፊ አቶ ዳኘው ገብሩ በፈተናው አሰጣጥ ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫው የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና በከተማዋ በ 792 ትምህርት ቤቶች እንደሚሰጥ ተነግሯል።
ለዚህም 179 የመፈተኛ ጣቢያዎች ተዘጋጅተዋል ብለዋል ።
አቶ ዳኘው አክለውም አጠቃላይ በከተማዋ 71 ሺህ 832 ተማሪዎች እንደሚፈተኑ ነው የተናገሩት።
ኮማንድ ፖስት ተቋቁሞ እስካሁን ያለውን የፈተናው ዝግጅት ሂደት የገመገመ ሲሆን ፈተናው ወደ መፈተኛ ጣቢያዎች ለማጓጓዝ ሂደት ላይ ነውም ተብሏል።
ሰኔ 24 ቀንም ለሁሉም ፈተናውን ለሚመለከት የትምህርት ማህበረሰብ ኦረንቴሽን እንደሚሰጥም ተገልጿል፡፡
(አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ)
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር በተለያዩ መስኮች በትብብር ለመስራት የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል።
ስምምነቱ ዩኒቨርሲቲው የሚያከናውናቸውን የመማር ማስማር፥ ምርምር፥ ማህበረሰብ አገልግሎት እንዲሁም የቴክኖሎጂ ሽግግርና ሌሎች ሥራዎችን በኢቢሲ የሚዲያ አማራጮች ለማቅረብ ያስችለዋል።
ለቀጣይ አምስት ዓመታት ገቢራዊ የሚሆነው ስምምነቱ፤ በርካታ የትብብር ጉዳዮች የተካተቱበት መሆኑ ታውቋል።
ስምምነቱ በዩኒቨርሲቲው የሚዘጋጁ መልዕክቶችን በኢቢሲ ሬዲዮ፣ ቴሌቪዥን እና ዲጂታል ሚዲያ ለህብረተሰቡ ለማስተላለፍ ያስችላል። የዩኒቨርሲቲው የጋዜጠኝነትና ኮሙዩኒኬሽን ተማሪዎች በኢንተርንሽፕ በኢቢሲ የሚሳተፉም ይሆናል።
የዩኒቨርሲቲውን አገልግሎቶች በኢቢሲ ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ጣቢያዎች ለማሰራትና ለማስተዋወቅ፤ ፕሮግራሞችን በአጋርነት ለማዘጋጀት፣ የጋራ ጥናትና ምርምር ለማካሄድ እና የጋራ ሴሚናሮችን ለማዘጋጀት
ሁለቱ ተቋማት መስማማታቸው ተገልጿል።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#AddisAbabaEducationBureau
የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ በሰርተፍኬት ሲያስተምሩ የነበሩ 4 ሺህ የቅድመ አንደኛ ደረጃ መምህራንን በዲፕሎማ ሊያሠለጥን መሆኑን አስታውቋል፡፡
የቅድመ አንደኛ ደረጃ (ሙዓለ ህፃናት) መምህራኑ ከሐምሌ 01/2014 ዓ.ም ጀምሮ ለቀጣይ ሦሥት ዓመታት በዲፕሎማ እንደሚሠለጥኑ ተገልጿል፡፡
ከግልና ከመንግሥት ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ 2 ሺህ 500 መምህራንን በደብረ ብርሃን መምህራን ኮሌጅ እንዲሁም 1 ሺህ 500 መምህራን በአሰላ መምህራን ኮሌጅ የሚማሩ ይሆናል፡፡
ቢሮው ከደብረ ብርሃን መምህራን ኮሌጅ እና ከአሰላ መምህራን ኮሌጅ ጋር ለቀጣይ ሦሥት ዓመታት አብሮ ለመስራት ሰኔ 20/2014 ዓ.ም ስምምነት አድርጓል።
ለስልጠናው ከተመዘገቡ ከ5 ሺህ 600 በላይ መምህራን ኮሌጆቹ ያስቀመጡትን የመግቢያ ነጥብ ያሟሉት 4 ሺህ ብቻ በመሆናቸው ትምህርት ቢሮው ሁሉንም መምህራን ወደ ኮሌጆቹ ለማስገባት መወሰኑ ታውቋል፡፡
ትምህርቱ በክረምት እና በቅዳሜና እሁድ ለሦሦት ዓመታት የሚሰጥ ሲሆን ለዚህም ቢሮው ከ80 እስከ 90 ሚሊዮን ብር መመደቡ ተገልጿል። #ሪፖርተር
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በዩኒቨርስቲዎች ዉስጥ እንደሚሰጥ ተገለፀ።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በሆሳዕና ፣ በወራቤና በወልቂጤ ከተሞች የሚገኙ ሁለተኛ ደረጃና ሞዴል ትምህርት ቤቶችን ጎብኝተዋል።
በጉብኚታቸዉ ወቅት ከተማሪዎችና ከትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ ጋር ባደረጉት ቆይታ የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና በትምህርት ቤቶች ሳይሆን በዩኒቨርስቲ ውስጥ እንደሚሰጥ ገልጸዋል።
እንደሚኒስትሩ ገለጻ የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና በኤሌክትሮኒክስ /online/ መስጠት እስከሚጀመር ድረስ በዩኒቨርስቲዎች መሰጠቱ ይቀጥላል።
የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና በዩኒቨርስቲ እንዲሰጥ የተወሰነው የፈተና ሰርቆትና ማጭበርበርን ለማስቀረት ታስቦ በመሆኑ ተማሪዎች ትምህርት በስራና በታታሪነት የሚገኝ መሆኑን አውቀው በርትተው መማር ፣ማጥናትና ማወቅ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር የትምህርትን ጥራትን ለማሻሻል በአጠቃላይና ከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፎች ሌሎችንም የተለያዩ እርምጃዎች በመውሰድ ላይ መሆኑንም ፕሮፌሰር ብርሀኑ ጠቁመዋል።
ሚኒስትሩ ሶስቱንም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የጎበኙ ሲሆን የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ ችግኝም ተክለዋል፡፡
ምንጭ፦ ትምህርት ሚኒስቴር
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#ArbaMinchUniversity
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የ2014 ዓ.ም የነባር የቅድመ እና ድኅረ ምረቃ የክረምት መርሃ ግብር ተማሪዎች ምዝገባ ሐምሌ 11 እና 12/2014 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።
ትምህርት ሐምሌ 13/2014 ዓ.ም እንደሚጀመር ተገልጿል።
ዩኒቨርሲቲው የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች ቲቶሪያል ከሐምሌ 04 እስከ 09/2014 ዓ.ም እንደሚሰጥ አሳስቧል፡፡
ከተጠቀሱት ቀናት በፊትም ሆነ በኋላ የሚመጡ ተማሪዎችን የማያስተናግድ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
" ወንጀል ላይ ተሳትፎ ያላቸውን አካላት በመለየት ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ለማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራን ነው " - FIS
የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ፥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አንዳንድ አካላት በአጭር ጊዜ ውስጥ ‘ትርፋማ እናደርጋለን‘ በሚል በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች በሚያደርጉት የቅስቀሳ ተግባር ከህብረተሰቡ በርካታ ገንዘቦችን በተለያዩ የክፍያ አማራጮች እየሰበሰቡ እንደሆነ ገልጿል።
እነዚሁ አካላት በተለይ ማህበራዊ ሚዲያውን በመጠቀም ህብረተሰቡ ያለበት የኢኮኖሚ ጫና ተገን በማድረግ ባዘጋጁት የገንዘብ መሰብሰቢያ አማራጮች ላይ ማንኛውም ግለሰብ ገንዘብ የሚያስገባ ከሆነ ካስገባው ገንዘብ የበለጠ ትርፋማ እንደሚሆን በሚያቀርቧቸው የማሳመኛ መንገዶች ከበርካታ ሰዎች በህገ-ወጥ መንገድ ገንዘብ እየሰበሰቡ እንደሆነ አሳውቋል።
ገንዘቡን በተለያዩ የክፍያ መነገዶችን በመጠቀም ሊሰበስቡ እንደቻሉ ነው የገለፀው።
ከእነዚሁ አካላት መካከል የበርካታ ግለሰቦችን ገንዘብ ከሰበሰቡ በኋላ አድራሻቸውን በማጥፋት #የተሰወሩ አካላት እንዳሉ ከህብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማ መረዳቱን አሳውቋል።
እነዚህ የማጭበርበር ወንጀል ላይ ተሳትፎ ያላቸውን አካላት በመለየት ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ለማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጿል።
ህብረተሰቡ ከእንደነዚህ አይነት የማጭበርበር ተግባራት ራሱን ሊጠብቅ ይገባልም ብሏል።
(አድራሻ፦ የኢትዮጵያ ፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት)
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
ጥራት ያለው ተማሪ የማያፈሩ፤ ማኅበረሰቡን የማይጠቅሙ ዩኒቨርስቲዎች ሊዘጉ እንደሚችሉ ተጠቆመ
ጥራት ያለው ተማሪ ማፍራት የማይችሉ፣ ደረጃውን የጠበቀ ምርምር የማያካሂዱና የአካባቢውን ማኅበረሰብ የማይጠቅሙ ዩኒቨርስቲዎች ሊዘጉ እንደሚችሉ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ጠቆሙ።
ሚኒስትሩ ከዋቸሞ ፣ ወራቤና ወልቂጤ ዩኒቨርስቲ ምሁራን ተመራማሪዎችና የትምህርት ክፍል ኃላፊዎች ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት ነው ይህንን የገለጹት።
ዩኒቨርስቲዎች ዓለም አቀፍ ውድድሩን ለመሸከም የሚያስችል ዕውቀት የሚፈራባቸው ቦታዎች መሆናቸውን የጠቆሙት ፕ/ር ብርሃኑ ይሁን እንጂ አሁን ባለንበት ሁኔታ ዩኒቨርስቲዎች ጥሩ ዕውቀት ያላቸው ተማሪዎች ማፍራት ብቻ ሳይሆን ጥሩ ዜጎች እንኳን ማፍራት አልቻሉም ብለዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) በበኩላቸዉ የውይይቱ ዓላማ በትምህርት ዘርፉ ያሉ ችግሮችን ምንነት በመለየት ችግሮችን ለመፍታት የጋራ መግባባት ላይ መድረስ መሆኑን ገልጸዋል።
በውይይቱ ላይ በየዩኒቨርስቲዎቹ ፕሬዚዳንቶች የመነሻ ሀሳቦችና ጥያቄዎች ቀርበው ምላሽና ማብራርያ መሰጠቱን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
