ኢትዮ Crypto
Open in Telegram
Hello. Bonus $1000 for registration. Casino🎰 BONUS promo code 1000$🎰 PROMO - 555 👇👇👇👇👇👇 https://Rbeto.com/auth/register?promo=555
Show more2 370
Subscribers
No data24 hours
-47 days
-4530 days
Posts Archive
2 370
#AddisAbaba📍
የ2014 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ፈተና በአዲስ አበባ መሰጠት ጀምሯል።
ፈተናው ከዛሬ ሰኔ 27/2014 ዓ.ም ጀምሮ ለሦሥት ቀናት እንደሚሰጥ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ማስታወቁ አይዘነጋም።
ከተማ ዐቀፍ ፈተናው በአዲስ አበባ በሚገኙ 179 የመፈተኛ ጣቢያዎች እየተሰጠ ሲሆን 1 ሺህ 800 ፈታኞች እና 450 ሱፐር ቫይዘሮች ፈተናውን እየተቆጣጠሩ እንደሚገኙ ተገልጿል።
በዛሬው የፈተና ውሎ ጠዋት የአማርኛ እና እንግሊዘኛ ፈተናዎች እየተሰጡ ሲሆን ከሰዓት ሂሳብ እና ባዮሎጂ ፈተናዎች ይሰጣሉ።
በአጠቃላይ በከተማዋ ከ71 ሺህ በላይ ተማሪዎች ፈተናውን እንደሚወስዱ ይጠበቃል።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#AASTU
አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ያስገነባው ዘመናዊ የስብሰባ አዳራሽ ተመርቋል፡፡
የመሰብሰቢያ አዳራጁ በአንድ ጊዜ ከአራት ሺህ በላይ ሰዎችን ማስተናገድ ይችላል ተብሏል፡፡
ዋና የስብሰባ ማዕከሉ ዘመናዊ የድምጽ መሳሪዎች፣ የአየር ማቀዝቀዣ እና ካሜራዎች ተገጥመውለታል፡፡
የስብሰባ ማዕከሉ ለመጀመሪያ ጊዜ የዩኒቨርሲቲውን የ2014 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎችን ቅዳሜ ዕለት በማስመረቅ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
በቀጣይ አዳራሹ ለመንግስት እና የግል ተቋማት፣ ለኪነ ጥበባዊ ዝግጅቶች፣ ለአውደ ርዕይ እና ሌሎች ዝግጅቶች በቅርቡ የኪራይ አገልግሎት መስጠት የሚጀምር መሆኑ ተገልጿል፡፡
ዩኒቨርሲቲው ከ203 ሚሊዮን ብር በላይ ለስብሰባ ማዕከሉ ግንባታ ወጪ አድርጓል።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#Saula📍
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሳውላ ካምፓስ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያስተማራቸውን 193 ተማሪዎች አስመርቋል።
ባለፉት አምስት ዓመታት በካምፓሱ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ከነበሩ ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡት ሴት ተማሪዎች መሆናቸውን የሳውላ ካምፓስ ዲን አቶ ገብረመድህን ጫሜኖ ገልጸዋል።
ዘንድሮ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ሴት ተማሪዎች ገብሬላ ሀብታሙ 4.0 ነጥብ፣ እድላዊት በረከት 3.99 እና ፋሲካ ቶሎሳ 3.98 መሆናቸው ተገልጿል።
የሳውላ ካምፓስ የትላንት 5ኛ ዙር ተመራቂዎችን ጨምሮ ባለፋት ሰባት ዓመታት ከ1 ሺህ 400 በላይ ተማሪዎችን አስመርቋል።
Congratulations !
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
Durame📍
የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ዱራሜ ካምፓስ 273 ተማሪዎችን አስመርቋል።
ካምፓሱ በ2014 ብቻ 713 ተማሪዎች ማስመረቁን በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የዱራሜ ካምፓስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዳይሬክተር ዳዊት ለገሰ (ዶ/ር) ገልፀዋል።
ካምፖሱ በመደበኛ እና በተከታታይ መርሃ ግብር በቅድመ እና ድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች 5 ሺህ 500 ተማሪዎችን እያስተማረ ይገኛል።
Congratulations !
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#Tepi 📍
ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን 1 ሺህ 308 ተማሪዎች አስመርቋል።
የዩኒቨርሲቲው 14ኛ ዙር ተመራቂዎች፤ ቴፒ ከተማ በሚገኘው የተቋሙ ሁለተኛ ግቢ ሲማሩ የቆዩ ናቸው።
ተመራቂዎቹ በመደበኛ እና በእረፍት ቀናት መርሃ ግብር በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ መሆናቸው ተገልጿል።
ከዛሬ ተመራቂዎቹ ውስጥ 125ቱ በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ መሆናቸው ተመላክቷል።
ዩኒቨርሲቲው እስካሁን ከ25 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ያስመረቀ ሲሆን በአሁን ወቅት ከ20 ሺህ በላይ ተማሪዎችን እያስተማረ ይገኛል።
Congratulations !
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#KotebeUniversityOfEducation
ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ከደቡብ ኮሪያው ቺንጁ ብሔራዊ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል።
ስምምነቱ የቴክኖሎጂ እና ትምህርታዊ የጋራ ትብብሮችን ለማጎልበት የሚያስችል ነው ተብሏል።
በተለይ የመምህራን ትምህርትን ለማሳደግ እና መሰረታዊ የትምህርት አቅርቦትን ለማሻሻል እንደሚያግዝ ተገልጿል።
የስምምነት ፕሮጀክቱን ገቢራዊ ለማድረግ የኮርያ ዓለም ዐቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ኮይካ) የገንዘብ ድጋፍ እንደሚያደርግ ታውቋል።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#InjibaraUniversity
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በ2014 ዓ.ም የክረምት መርሃ ግብር በሁለተኛ ዲግሪ ለመማር የማመልከቻ ጊዜን እስከ ሐምሌ 01/2014 ዓ.ም አራዝሟል።
የመግቢያ ፈተና ሐምሌ 04/2014 ዓ.ም ይሰጣል ተብሏል።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#GambellaUniversity
የጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ሴኔት በ2015 ዓ.ም አስር የሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራሞች ለመክፈት ወስኗል፡፡
ሴኔቱ በትምህርት ዘመኑ 15 አዳዲስ የመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራሞች እንዲከፈቱም አጽድቋል፡፡
በሌላ በኩል ሴኔቱ ለሁለት መምህራን የተባባሪ ፕሮፌሰርነት እና ለሦሥት መምህራን የረዳት ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ዕድገት ሰጥቷል፡፡
የማዕረግ ዕድገት የተሰጣቸው መምህራን፦
1. ዶ/ር ጋትሏክ ጋትኮስ ~ ተባባሪ ፕሮፌሰር
2. ዶ/ር ጌታሁን አሰበ ~ ተባባሪ ፕሮፌሰር
3. አቶ ሰለሞን ቶማስ ~ ረዳት ፕሮፌሰር
4. አቶ መብራቱ ደንጊያ ~ ረዳት ፕሮፌሰር
5. አቶ እሸቱ ጉዲና ~ ረዳት ፕሮፌሰር
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#WerabeUniversity
ወራቤ ዩኒቨርሲቲ እና የደቡብ ኮርያው 'Yeungnam' ዩኒቨርሲቲ በጋራ ለመስራት ተስማምተዋል።
ሁለቱ ተቋማት ለቀጣይ አስር ዓመታት የሚተገር የመግባቢያ ስምምነት በዴጉ ከተማ ተፈራርመዋል፡፡
ስምምነቱ በተቋማቱ መካከል የትምህርት እና ምርምር ትብብር ለማጎልበት ያስችላል ተብሏል።
ስምምነቱ በተለይ የግብርናውን ዘርፍ ለማዘመን በዘርፉ የሚደረገውን የቴክኖሎጂ ሽግግር በሰው ኃይል አቅም ግንባታ እና በቁሳቁስ ድጋፍ ተጠቃሚ የሚያደርግና የዩኒቨርሲቲውን አቅም ለማጎልበት የሚያስችል መሆኑን የወራቤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ተውፊቅ ጀማል (ዶ/ር) ገልጸዋል።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#MizanTepiUniversity
የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ሴኔት ለ14 መምህራን የማዕረግ ዕድገት ሰጥቷል።
ሴኔቱ ለሦሥት መምህራን የተባባሪ ፕሮፌሰርነት እና ለ11 መምህራን የረዳት ፕሮፌሰርነት የማዕረግ ዕድገት አጽድቋል።
የማዕረግ ዕድገቱ የተሰጣቸው መምህራን ከዩኒቨርሲቲው የተለያዩ ኮሌጆች የተውጣጡ መሆናቸው ተገልጿል።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#AddisAbaba 📍
የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ 2 ሺህ 683 ተማሪዎችን አስመርቋል።
ተመራቂዎቹ በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ እና በሦሥተኛ ዲግሪ በአመራርና አስተዳደር፣ በከተማ ልማትና ምህንድስና እንዲሁም በፋይናንስ ሥራ አመራር ኮሌጆች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።
ዩኒቨርሲቲው ትላንት ካስመረቃቸው ተማሪዎች መካከል 654ቱ ሴት ተማሪዎች መሆናቸው ተገልጿል።
Congratulations !
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
Haramaya 📍
ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ከ1 ሺህ 800 በላይ ተማሪዎች አስመርቋል፡፡
ተመራቂዎቹ በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ እና በሦሥተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው፡፡
Congratulations!
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
Wolkite 📍
ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያስተማራቸውን 1 ሺህ 495 ተማሪዎችን አስመረቀ።
በመደበኛ እና በተከታታይ መርሃ ግብር ስልጠናቸውን ተከታትለው ከተመረቁት መካከል 442ቱ ሴት ተማሪዎች ናቸው።
ከጠቅላላ ተመራቂዎቹ 64ቱ በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ መሆናቸው ተገልጿል።
Congratulations!
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
Dire Dawa 📍
ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 997 ተማሪዎች ዛሬ አስመርቋል።
በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ተከታትለው ከተመረቁት ተማሪዎች መካከል 241ዱ ሴቶች ናቸው።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#Mettu 📍
መቱ ዩኒቨርሲቲ ከ1 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ዛሬ አስመርቋል።
ተመራቂዎቹ በመደበኛ እና በተከታታይ መርሃ ግብር በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
#Jimma 📍
ጅማ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን 2 ሺህ 509 ተማሪዎች አስመርቋል።
ተመራቂዎቹ በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ እና በሦስተኛ ዲግሪ እንዲሁም በስፔሻሊቲ እና ሰብ-ስፔሻሊቲ ዲግሪ ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።
ከጠቅላላ ተመራቂዎች 275ቱ የሁለተኛ ዲግሪ ሰልጣኞች መሆናቸው ተገልጿል።
Congratulations!
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
2 370
‘ፊያስ’ በተባለ የኦንላይን ማጭበርበሪያ ዘዴ ገንዘባቸውን ያጡ ሰዎች ለሕግ አስከባሪ አካላት ጥቆማ እንዲሰጡ ጥሪ ቀረበ
‘ፊያስ’ በተባለ የኦንላይን ማጭበርበሪያ ድርጊት ገንዘባቸውን ያጡ ሰዎች ለሕግ አስከባሪ አካላት ጥቆማ በመስጠት ትብብር እንዲያደርጉ የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት ጥሪ አቀረበ፡፡
የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ እንዳለ አሰፋ እንደገለጹት÷ ‘በአጭር ጊዜ ውስጥ ትርፋማ እናደርጋችኋለን’ በሚል የማህበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀም የማጭበርበር ተግባራት የሚፈፅሙ አካላት ቁጥራቸው እየጨመረ በመምጣቱ ከብሄራዊ መረጃና ደኅንነት ተቋም ጋር በመተባበር የተለያዩ ሥራዎች ሲሠሩ ቆይተዋል፡፡
‘ፊያስ’ እየተባለ የሚጠራው የኦንላይን ድርጊት እንደ ሌሎች በማህበራዊ እና በኦንላይን ሚዲያዎች በመጠቀም ከሚፈፀሙ የማጭበርበሪያ ድርጊቶች አንዱ ሊሆን እንደሚችል ኃላፊው ጠቁመዋል።
ይህን ተግባር የሚፈፅሙ አካላት በአጭር ጊዜ ውስጥ ትርፋማ እናደርጋችኋለን በሚል እና የተለያዩ የሚያጓጉ ምክንያቶችን በማቅረብ ሰዎችን እያጭበረበሩ መሆናቸውን ጠቁመው÷ ማህበረሰቡም በአጭር ጊዜ ለመለወጥ በሚል ሕጋዊነቱን ሳያረጋግጥ እና በሚያውቋቸው ሰዎች በመሳብ የወንጀሉ ሰለባ እየሆነ መምጣቱን ገልፀዋል።
በ ‘ፊያስ’ ተጭበረበሩ ሰዎች ባደረሱት ጥቆማ መሰረት የተለያዩ የክፍያ መንገዶችን በመጠቀም÷ የሰዎችን ገንዘብ የሰበሰቡ አካላትን ሁኔታው እስከሚጣራ ድረስ የባንክ ሂሳባቸው እንዳይንቀሳቀስ የሚደረግበት አግባብ ይኖራል ብለዋል፡፡
አጠቃላይ የወንጀል ምርመራ ሂደቱ ገና በጅምር ላይ ያለ በመሆኑ ጉዳዩ ተጣርቶ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ዝርዝር መረጃዎችን ማቅረብ እንደማይቻልም ነው የገለጹት።
ህብረተሰቡ የማህበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀም የሚሠሩ ሥራዎች ላይ ሲሳተፉ አብረው የሚሰሩት አካል በኢትዮጵያ ሕጋዊ እውቅና ያለው መሆኑንና ትክክለኛ ማንነት እንዲሁም አድራሻ ያለው መሆኑን ማረጋገጥ እንደሚገባ መጠቆማቸውን ኢቢሲ ዘግቧል፡፡
ያለምንም ስራ እንደቀልድ የሚሰበሰብ ሃብት ሊኖር እንደማይችል በመገንዘብ መሰል ስራዎች ላይ በጥንቃቄ መንቀሳቀስ እንደሚያስፈልግ እና ህብረተሰቡ ከመሰል የማጭበርበር ተግባራት ራሱን እንዲጠብቅም አሳስበዋል፡፡
FBC
━━━━━━━━━━━━━━━━━
📌Join &
📍|||_Support us
@ethio_university_info
@ethio_university_info
