en
Feedback
ኢትዮ Crypto

ኢትዮ Crypto

Open in Telegram

Hello. Bonus $1000 for registration. Casino🎰 BONUS promo code 1000$🎰 PROMO - 555 👇👇👇👇👇👇 https://Rbeto.com/auth/register?promo=555

Show more
2 370
Subscribers
No data24 hours
-47 days
-4530 days
Posts Archive
በሀገሪቱ በሚገኙ ሁሉም የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች አዲስ ሥርዓተ ትምህርት ከመጪው ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ ሊደረግ ነው። እስካሁን ተግባራዊ ሲደረግ የቆየው የቴክኒክና ሙያ ሥርዓተ ትምህርት ጉድለቶች እንደ
በሀገሪቱ በሚገኙ ሁሉም የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች አዲስ ሥርዓተ ትምህርት ከመጪው ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ ሊደረግ ነው። እስካሁን ተግባራዊ ሲደረግ የቆየው የቴክኒክና ሙያ ሥርዓተ ትምህርት ጉድለቶች እንደነበሩበት በጥናት መለየቱን የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ተሻለ ብሬቻ (ዶ/ር) ገልጸዋል። በመሆኑም ጉድለቶቹን የሚሞላና ሰልጣኞች በሁሉም ሙያ የተሟላ እውቀትና ክህሎት ይዘው እንዲወጡ የሚያደርግ አዲስ ሥርዓት ትምህርት በመጪው ዓመት ተግባራዊ ይደረጋል ብለዋል። ሥርዓተ ትምህርቱ የሚመለከታቸው ሴክተር መስሪያ ቤቶች እና ኢንዱስትሪዎች ተሳትፈውበት የተዘጋጀ መሆኑን ዋና ዳይሬክተሩ ለኢፕድ ተናግረዋል። "ሥርዓተ ትምህርቱ ሠልጣኞች ኮሌጆች ውስጥ እያሉ እንዴት ሥራ መፍጠር እና ራሳቸውን ለሥራ ማዘጋጀት እንደሚችሉ በተግባር የሚለማመዱበትን ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን" ዋና ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል። በኢትዮጵያ ከ1 ሺህ 800 በላይ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ይገኛሉ። ━━━━━━━━━━━━━━━━━ 📌Join & 📍|||_Support us @ethio_university_info @ethio_university_info

ከ10 ሺህ በላይ የቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞች የምረቃ ስነ-ስርዓት በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው። በአዲስ አበባ በሚገኙ 14 የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ትምህርታቸውን የተከታተሉ 10 ሺህ 120 የቴ
+2
ከ10 ሺህ በላይ የቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞች የምረቃ ስነ-ስርዓት በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው። በአዲስ አበባ በሚገኙ 14 የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ትምህርታቸውን የተከታተሉ 10 ሺህ 120 የቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞች የምረቃ ስነ-ስርዓት በሚሌኒየም አዳራሽ እየተካሄደ ነው። ተመራቂዎቹ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቴክኒክና ሙያ ስልጠናና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ስር በሚገኙ 6 የፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጆች እና 8 ኮሌጆች በተለያዩ የሙያ ዘርፎች የሰለጠኑ ናቸው። ተመራቂዎቹ በቴክኒክና ሙያ ዘርፎች ከደረጃ 2 እስከ ደረጃ 5 የተለያዩ ስልጠናዎች መውሰዳቸው የኢፕድ ዘገባ ያመለክታል። ━━━━━━━━━━━━━━━━━ 📌Join & 📍|||_Support us @ethio_university_info @ethio_university_info

#SPHMMC የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ የዛሬ 75 ዓመት ነበር የተመሰረተው። አሁን ላይ አውቶቡስ ተራ በሚባለው አካባቢ ሐምሌ 16/1939 ዓ.ም ምስረታውን ያደረገው የቅዱስ ጳ
#SPHMMC የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ የዛሬ 75 ዓመት ነበር የተመሰረተው። አሁን ላይ አውቶቡስ ተራ በሚባለው አካባቢ ሐምሌ 16/1939 ዓ.ም ምስረታውን ያደረገው የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል፤ አሁን ወዳለበት ጉለሌ አካባቢ የተዘዋወረው በ1961 ዓ.ም ነበር። የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ በኢትዮጵያ የጤና አገልግሎት መልካም አሻራውን በማሳረፍ እዚህ ደርሷል። ኮሌጁ ወደፊት የሕክምና ዩኒቨርሲቲ ለመሆን እየሠራ እንደሚገኝ ገልጿል። ━━━━━━━━━━━━━━━━━ 📌Join & 📍|||_Support us @ethio_university_info @ethio_university_info

የደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ መርሐ ግብር ያስተማራቸውን ተማሪዎቹን የተማሪዎች ቤተሰብና እንግዶች በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ በማስመረቅ ላይ ይገኛል፡፡ የደብረማርቆስ ዩኒቨር
+3
የደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ መርሐ ግብር ያስተማራቸውን ተማሪዎቹን የተማሪዎች ቤተሰብና እንግዶች በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ በማስመረቅ ላይ ይገኛል፡፡ የደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ በመጀመሪያ፥ በሁለተኛና በሶስተኛ ዲግሪ በመደበኛ፥ በተከታታይና በክረምት መርሐ ግብር ወንድ፥ 1416 ሴት፥ 796 በአጠቃላይ 2212 ተማሪዎችን የዕለቱ የክብር እንግዳ ፕሮፌሰር በላይ ካሣ በተገኙበት በደማቅ ሥነ-ሥርዓት እያስመረቀ ይገኛል፡፡ ━━━━━━━━━━━━━━━━━ 📌Join & 📍|||_Support us @ethio_university_info @ethio_university_info

#DebreTaborUniversity ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የነባር እና አዲስ ገቢ የ2014 ዓ.ም #የክረምት መርሃ ግብር ተማሪዎች ምዝገባ ከሐምሌ 20 እስከ 22/2014 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል። ጥ
+1
#DebreTaborUniversity ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የነባር እና አዲስ ገቢ የ2014 ዓ.ም #የክረምት መርሃ ግብር ተማሪዎች ምዝገባ ከሐምሌ 20 እስከ 22/2014 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል። ጥሪው ለመጀመሪያ ዲግሪ፣ ለሁለተኛ ዲግሪ እና ለPHDT የክረምት ተማሪዎች የተደረገ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል። ( ተጨማሪ መረጃ ከላይ ተያይዟል። ) ━━━━━━━━━━━━━━━━━ 📌Join & 📍|||_Support us @ethio_university_info @ethio_university_info

#MattuUniversity መቱ ዩኒቨርሲቲ የ2014 ዓ.ም የሁሉም ነባር #የክረምት እና #የእረፍት ቀናት መርሃ ግብር ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ከሐምሌ 15 እስከ 18/2014 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።
+1
#MattuUniversity መቱ ዩኒቨርሲቲ የ2014 ዓ.ም የሁሉም ነባር #የክረምት እና #የእረፍት ቀናት መርሃ ግብር ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ከሐምሌ 15 እስከ 18/2014 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል። ሐምሌ 19/2014 ዓ.ም ብቻ በቅጣት መመዝገብ እንደሚቻል ዩኒቨርሲቲው ገልጿል። በተመሳሳይ ፈተና ያለፉ አዲስ ገቢ #የሁለተኛ ዲግሪ #የክረምት መርሃ ግብር ተማሪዎች ምዝገባ ከሐምሌ 15 እስከ 18/2014 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል። ሐምሌ 19/2014 ዓ.ም ብቻ በቅጣት መመዝገብ ይቻላል የተባለ ሲሆን ሐምሌ 20/2014 ዓ.ም ትምህርት እንደሚጀምር ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል። ( ተጨማሪ መረጃ ከላይ ተያይዟል። ) ━━━━━━━━━━━━━━━━━ 📌Join & 📍|||_Support us @ethio_university_info @ethio_university_info

#WolaitaSodoUniversity ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የ2014 ዓ.ም #የክረምት መርሃ ግብር ተማሪዎች ምዝገባ ሐምሌ 20 እና 21/2014 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል። የነባር የክረምት ተማሪዎች
#WolaitaSodoUniversity ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የ2014 ዓ.ም #የክረምት መርሃ ግብር ተማሪዎች ምዝገባ ሐምሌ 20 እና 21/2014 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል። የነባር የክረምት ተማሪዎች ቲቶሪያል ከሐምሌ 22 እስከ 25/2014 ዓ.ም እንደሚሰጥ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል። ጥሪው የቅድመ እና ድኅረ ምረቃ የክረምት መርሃ ግብር ተማሪዎችን ይመለከታል የተባለ ሲሆን በግብርና፣ በእንስሳት ጤና እና በኅብረት ሥራ ትምህርት ፕሮግራሞች የክረምት ተማሪዎችን አይመለከትም ተብሏል። ( ተጨማሪ መረጃ ከላይ ተያይዟል። ) ━━━━━━━━━━━━━━━━━ 📌Join & 📍|||_Support us @ethio_university_info @ethio_university_info

#MekdelaAmbaUniversity መቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ የ2014 ዓ.ም #የክረምት መርሃ ግብር ተማሪዎች ሪፖርት ማድረጊያ ጊዜ ሐምሌ 20/2014 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል። የሞጁል ቲቶሪያል የሚ
#MekdelaAmbaUniversity መቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ የ2014 ዓ.ም #የክረምት መርሃ ግብር ተማሪዎች ሪፖርት ማድረጊያ ጊዜ ሐምሌ 20/2014 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል። የሞጁል ቲቶሪያል የሚሰጠው ከሐምሌ 21 እስከ 24/2014 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል። ምዝገባ ሐምሌ 29 እና 30/2014 ዓ.ም ተከናውኖ፤ ትምህርት ነሐሴ 02/2014 ዓ.ም እንደሚጀምር ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል። ( ተጨማሪ መረጃ ከላይ ተያይዟል። ) ━━━━━━━━━━━━━━━━━ 📌Join & 📍|||_Support us @ethio_university_info @ethio_university_info

#DebreTaborUniversity ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምሀርት መስኮች ያስተማራቸውን 1 ሺህ 238 ተማሪዎች ቅዳሜ ሐምሌ 09/2014 ዓ.ም ያስመርቃል። ተመራቂዎቹ በመደበኛ እና በኤ
#DebreTaborUniversity ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምሀርት መስኮች ያስተማራቸውን 1 ሺህ 238 ተማሪዎች ቅዳሜ ሐምሌ 09/2014 ዓ.ም ያስመርቃል። ተመራቂዎቹ በመደበኛ እና በኤክስቴንሽን መርሃ ግብር በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው። ከጠቅላላ ተመራቂዎቹ 163ቱ የሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎች መሆናቸውን የዩኒቨርሲቲው የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ዳዊት ብርሀኑ ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ተናግረዋል። ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ዘንድሮ 9ኛ ዙር ሰልጣኞቹን የሚያስመርቅ ሲሆን 369ኙ ሴት ተማሪዎች ናቸው። ━━━━━━━━━━━━━━━━━ 📌Join & 📍|||_Support us @ethio_university_info @ethio_university_info

#ETA ምንም አይነት ፈቃድ ሳይኖራቸው ተማሪ መዝግበው ሲያስተምሩ የነበሩ ሦሥት የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማግኘቱን የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን አሳውቋል። ተቋማቱን በህግ ተጠያቂ ለማድረግ
#ETA ምንም አይነት ፈቃድ ሳይኖራቸው ተማሪ መዝግበው ሲያስተምሩ የነበሩ ሦሥት የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማግኘቱን የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን አሳውቋል። ተቋማቱን በህግ ተጠያቂ ለማድረግ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየሠራ መሆኑን ባለስልጣኑ ገልጿል፡፡ ባለስልጣኑ ከግንቦት 13 እስከ ሰኔ 01/2014 ዓ.ም በተለያዩ የክልል ከተሞች ባካሄደው ድንገተኛ ፍተሻ፤ ምንም አይነት የእውቅና ፈቃድ ሳይኖራቸው በከፍተኛ ትምህርት ደረጃ ተማሪ መዝግበው በማስተማር ላይ የነበሩ ሦሥት ተቋማት ማግኘቱን ተናግሯል። ተቋማቱ የሚከተሉት መሆናቸውን ባለስልጣኑ ገልጿል፡- • "ጅኤ ኢንደስትሪያል ኮሌጅ" ~ በአማራ ክልል (በደብረማርቆስ ከተማ እና አካባቢው) • "ኦሞ ቫሊ ዩኒቨርሳል ኮሌጅ" ~ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል (በዳውሮ ፣ በተርጫ) • "ሆርን ኦፍ አፍሪካ ቢዝነስ ኮሌጅ" ~ በኦሮሚያ ክልል (በአምቦ ከተማ እና አካባቢው) የክልሎቹ መንግስታት ህግ የማስከበር ድርሻቸውን እንዲወጡ የጠየቀው ባለስልጣኑ፤ ህገ-ወጥ ተቋማቱን የከፈቱ አካላት የፈጸሟቸው የህግ ጥሰቶች ካሉ በሚመለከታቸው የፍትሕ አካላት ተጠያቂ እንደሚደረጉ ባለሥልጣኑ አረጋግጧል። ከዚህ በፊት በደቡብ ክልል 'ፊንላንድ ኮሌጅ' በሚል እና በአማራ የክልል 'ሀምበርቾ ኮሌጅ' በሚል ራሳቸውን የሰየሙ ህገ-ወጥ አካላት መኖራቸውን ለክልል መንግስታቱ ማሳወቁን ባለሥልጣኑ አስታውሷል። ━━━━━━━━━━━━━━━━━ 📌Join & 📍|||_Support us @ethio_university_info @ethio_university_info

ቅሬታ‼️ #BahirdarUniversity በርካታ የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ፔዳ ግቢ ተማሪዎች ተመሳሳይ ይዘት ያለው ህመም እየተስተዋለባቸው እንደሆነና የግቢው ክሊኒክም የህክምና እርዳታ እየሰጣቸው እንዳ
ቅሬታ‼️ #BahirdarUniversity በርካታ የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ፔዳ ግቢ ተማሪዎች ተመሳሳይ ይዘት ያለው ህመም እየተስተዋለባቸው እንደሆነና የግቢው ክሊኒክም የህክምና እርዳታ እየሰጣቸው እንዳልሆነ በመግለፅ ዩንቨርሲቲው በተለይም የተማሪዎች ክሊኒክ ላይ ያለውን ችግር ትኩረት ይሰጠው ዘንድ ጠይቀዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በትላንትናው ዕለት ህይወቱ ያለፈውን ተማሪ በተመለከተም የግቢው ተማሪዎች ክሊኒኩን ክፉኛ ኮንነዋል። ━━━━━━━━━━━━━━━━━ 📌Join & 📍|||_Support us @ethio_university_info @ethio_university_info

ቅሬታ‼️ #WolkiteUniversity የወልቂጤ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የጊዜያዊ መመረቂያ Certificate ወይም የ "Tempo" ስማችን የተበላሸብንን እናስተካክልም በማለት እያግሏሉን ይገኛሉ። እንደሚከተለው ቅሬታቸውን አቅርቧል👇 "እባካቹህ ተባበሩን ግቢያችን የቴንፖ ስማችን ላይ በተበላሸ ነው ፕሪንት አድርገው የሰጡን እና አስተካክሉልን ብንል የሚሰማን አካል አተናል እና 8 ቀን አልፎናል ግቢው አልጋና ምግብ ተከልክለናል በውጭ ነው እየተጠቀምን ነው እባካቹህ ለሚሰማን አካል አስተላልፉልን።" የሚመለከተው አካል ቅሬታቸውን እንዲያስተካክል በትህትና እንጠይቃለን። ━━━━━━━━━━━━━━━━━ 📌Join & 📍|||_Support us @ethio_university_info @ethio_university_info

#GonderUniversity በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች እና በወልድያ ዩኒቨርሲቲ ይማሩ የነበሩ እና ቀሪ ትምህርታቸውን በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ያጠናቀቁ 56 #የጤና_ሳይንስ ተማሪዎች ዛሬ ተመ
+2
#GonderUniversity በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች እና በወልድያ ዩኒቨርሲቲ ይማሩ የነበሩ እና ቀሪ ትምህርታቸውን በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ያጠናቀቁ 56 #የጤና_ሳይንስ ተማሪዎች ዛሬ ተመርቀዋል። የጤና ሳይንስ ተማሪዎቹ በፀጥታ ችግር ምክንያት ወደ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በትምህርት ሚኒስቴር የተመደቡ ናቸው። 44 ወንድ እና 12 ሴት በድምሩ 56 ተማሪዎች በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የመጀመሪያ ዲግሪ ቀሪ ትምህርታቸውን ተከታትለው መመረቃቸው ተገልጿል። ━━━━━━━━━━━━━━━━━ 📌Join & 📍|||_Support us @ethio_university_info @ethio_university_info

4ኛው ዙር የብሔራዊ በጎ ፈቃደኛ ተማሪዎች ስልጠና በጅማ፣ ሀዋሳ እና ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲዎች ተጀምሯል። ዓመታዊ የስልጠና መርሃ ግብሩን የሰላም ሚኒስቴር ከዩኒቨርሲቲዎቹ ጋር በመተባበር አዘጋጅቶታል። •
+2
4ኛው ዙር የብሔራዊ በጎ ፈቃደኛ ተማሪዎች ስልጠና በጅማ፣ ሀዋሳ እና ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲዎች ተጀምሯል። ዓመታዊ የስልጠና መርሃ ግብሩን የሰላም ሚኒስቴር ከዩኒቨርሲቲዎቹ ጋር በመተባበር አዘጋጅቶታል። • ጅማ ዩኒቨርሲቲ 3 ሺህ በጎ ፍቃደኛ ተማሪዎችን ተቀብሎ ያሰለጥናል። • ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ከ2 ሺህ 500 በላይ በጎ ፍቃደኛ ተማሪዎችን ለ45 ቀናት ያሰለጥናል። • ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ 1 ሺህ 500 በጎ ፍቃደኛ ተማሪዎችን ከ30 ለሚበልጡ ቀናት ያሰለጥናል። ስልጠናው በሥራ ፈጠራ፣ ሀገራዊ አንድነትና ሰላም እና መሰል ርዕሶች ላይ ያተኮረ እንደሚሆን ተገልጿል። ━━━━━━━━━━━━━━━━━ 📌Join & 📍|||_Support us @ethio_university_info @ethio_university_info

#InjibaraUniversity እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የ2014 ዓ.ም የተማሪዎች የምረቃ ስነ ስርዓት ሐምሌ 09/2014 ዓ.ም ያከናውናል። ዩኒቨርሲቲው በመደበኛ እና በተከታታይ መርሃ ግብር ያሰለጠናቸ
#InjibaraUniversity እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የ2014 ዓ.ም የተማሪዎች የምረቃ ስነ ስርዓት ሐምሌ 09/2014 ዓ.ም ያከናውናል። ዩኒቨርሲቲው በመደበኛ እና በተከታታይ መርሃ ግብር ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች በዕለቱ ያስመርቃል። የመማር ማስተማር ሥራውን በ2010 ዓ.ም የጀመረው እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ፤ ዘንድሮ 3ኛ ዙር ሰልጣኞቹን ያስመርቃል። ━━━━━━━━━━━━━━━━━ 📌Join & 📍|||_Support us @ethio_university_info @ethio_university_info

#ethio_university_info ለእስልምና ዕምነት ተከታዮች በሙሉ መልካም የኢድ-አል አድሃ(አረፋ) በዓል ይመኛል። በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የምትገኙና በዓሉን ከቤተሰቦቻችሁ ርቃችሁ ለምታከብሩ
#ethio_university_info ለእስልምና ዕምነት ተከታዮች በሙሉ መልካም የኢድ-አል አድሃ(አረፋ) በዓል ይመኛል። በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የምትገኙና በዓሉን ከቤተሰቦቻችሁ ርቃችሁ ለምታከብሩ ተማሪዎች መልካም የኢድ-አል አድሃ አረፋ በዓል እንመኛለን። Eid Mubarak! ━━━━━━━━━━━━━━━━━ 📌Join & 📍|||_Support us @ethio_university_info @ethio_university_info

ዶክተሩ ያወሩት ነገር አንድም ቀን ተግባራዊ ሲሆን ባናይም ዛሬም በህ/ተ/ም/ ቤት ተገኝተዉ እንዲህ ብለዋሌ:- 👇👇👇 የ2015 ዓ.ም ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተናን ዲጂታላይዝ ለማድረግ/በኦንላይን ለመ
ዶክተሩ ያወሩት ነገር አንድም ቀን ተግባራዊ ሲሆን ባናይም ዛሬም በህ/ተ/ም/ ቤት ተገኝተዉ እንዲህ ብለዋሌ:- 👇👇👇 የ2015 ዓ.ም ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተናን ዲጂታላይዝ ለማድረግ/በኦንላይን ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል። የፈተና አሰጣጡን ሙሉ ለሙሉ አውቶሜት ለማድረግ ከቻይና መንግስት ጋር እየተሠራ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ ጠቁመዋል። ለፈተናው የሚቀመጡ ተማሪዎች ቁጥር ከፍተኛ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በርካታ ታብሌት ኮምፒዩተሮች እንደሚያስፈልጉ ተናግረዋል። ይሁን እንጂ በኮቪድ-19 ምክንያት አምራች ድርጅቱ ኮምፒዩተሮቹን በተያዘለት ጊዜ ማምረት አለመቻሉን ገልጸዋል። ኮምፒዩተሮቹ በተያዘላቸው ጊዜ ከደረሱ በቂ ዝግጅት ስለተደረገ የቀጣይ ዓመት ፈተና ኦንላይን እንደሚሰጥ አረጋግጠዋል። ታብሌቶቹ በሚጠበቀው ጊዜ ካልደረሱ፥ መንግስት የፈተና ስርቆት የሚቀነስበት የተሻለ አሰራር በመከተል ፈተናው ይሰጣል ብለዋል። ━━━━━━━━━━━━━━━━━ 📌Join & 📍|||_Support us @ethio_university_info @ethio_university_info

#AASTU አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ላለፉት አስር ዓመታት ሲጠቀምበት የቆየውን አርማ ለውጧል። ዩኒቨርሲቲው አዲሱን አርማ/ሎጎ ቅዳሜ ሰኔ 25/2014 ዓ.ም በይፋ አስተዋውቋል፡፡ አ
+2
#AASTU አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ላለፉት አስር ዓመታት ሲጠቀምበት የቆየውን አርማ ለውጧል። ዩኒቨርሲቲው አዲሱን አርማ/ሎጎ ቅዳሜ ሰኔ 25/2014 ዓ.ም በይፋ አስተዋውቋል፡፡ አዲሱ አርማ የተቋሙን የአስር ዓመት ስትራቴጂክ ፕላን መሰረት በማድረግ መዘጋጀቱን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ደረጀ እንግዳ (ዶ/ር) ገልጸዋል። አዲሱ ሎጎ ዩኒቨርሲቲው የሚጠቀምባቸውን የእንግሊዘኛ እና የአማርኛ ፊደላት አይነት፣ ምጣኔ እንዲሁም ለህትመት፣ ለማስታወቂያ እና ለሌሎች አገልግሎት የሚውል የደረጃ ይዘቶችንም የያዘ ነው፡፡ አቶ ቲዎፍሎስ መኮንን የተባሉ ግለሰብ አዲሱን ሎጎ በነፃ ሰርተው ለዩኒቨርሲቲው ማስረከባቸው ተገልጿል፡፡ ━━━━━━━━━━━━━━━━━ 📌Join & 📍|||_Support us @ethio_university_info @ethio_university_info

አሶሳ ዩኒቨርሲቲ 15 ብር የነበረውን እለታዊ የተማሪዎች ምገባ ወጪ በራሱ ፈቃድ ወደ 34 ብር አሳድጎ ተገኘ አሶሳ ዩኒቨርስቲ ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተቀመጠውን እለታዊ የተማሪዎች ምገባ ዋጋ በ
አሶሳ ዩኒቨርሲቲ 15 ብር የነበረውን እለታዊ የተማሪዎች ምገባ ወጪ በራሱ ፈቃድ ወደ 34 ብር አሳድጎ ተገኘ አሶሳ ዩኒቨርስቲ ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተቀመጠውን እለታዊ የተማሪዎች ምገባ ዋጋ በሕግ ከተፈቀደለት ውጪ በአንድ ተማሪ ላይ በቀን 19 ብር ጨምሮ ለአንድ ተማሪ በቀን 34 ብር ተመን ሲመግብ እንደነበር በኦዲት መረጋገጡ ተሰምቷል። ዩኒቨርሲቲው ገንዘብ ሚኒስቴር ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ያስቀመጠውን እለታዊ የተማሪ ምገባ ወጪ ተመን ማለትም 15 ብር የነበረውን፣ ወደ 34 ብር ከፍ በማድረግ በፈቃዱ በማኔጅመንት አጽድቆ ከፍተኛ ወጪ ማውጣቱን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት አረጋግጫለሁ ብሏል። ሙሉ የአዲስ ማለዳን ዘገባ ያንብቡ👇 https://bit.ly/3AmW4SG ━━━━━━━━━━━━━━━━━ 📌Join & 📍|||_Support us @ethio_university_info @ethio_university_info