en
Feedback
Akaki Kality Communication-አቃቂ ቃሊቲ

Akaki Kality Communication-አቃቂ ቃሊቲ

Open in Telegram

ይህ የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን የቴሌግራም ገፅ ነው!

Show more
1 960
Subscribers
-224 hours
No data7 days
-1830 days

Data loading in progress...

Attracting Subscribers
September '26
September '26
+14
in 0 channels
August '26
+39
in 0 channels
Get PRO
July '26
+338
in 0 channels
Get PRO
June '26
+20
in 0 channels
Get PRO
May '26
+12
in 0 channels
Get PRO
April '26
+11
in 0 channels
Get PRO
March '26
+8
in 0 channels
Get PRO
February '26
+12
in 0 channels
Get PRO
January '26
+17
in 0 channels
Get PRO
December '25
+41
in 0 channels
Get PRO
November '25
+52
in 0 channels
Get PRO
October '25
+51
in 0 channels
Get PRO
September '25
+99
in 0 channels
Get PRO
August '25
+52
in 0 channels
Get PRO
July '25
+70
in 0 channels
Get PRO
June '25
+35
in 0 channels
Get PRO
May '25
+30
in 0 channels
Get PRO
April '25
+35
in 0 channels
Get PRO
March '25
+541
in 0 channels
Get PRO
February '25
+48
in 0 channels
Get PRO
January '25
+93
in 0 channels
Get PRO
December '24
+83
in 1 channels
Get PRO
November '24
+46
in 1 channels
Get PRO
October '24
+63
in 0 channels
Get PRO
September '24
+24
in 0 channels
Get PRO
August '24
+14
in 0 channels
Get PRO
July '24
+16
in 0 channels
Get PRO
June '24
+24
in 0 channels
Get PRO
May '24
+18
in 0 channels
Get PRO
April '24
+23
in 0 channels
Get PRO
March '24
+33
in 0 channels
Get PRO
February '24
+51
in 0 channels
Get PRO
January '24
+49
in 0 channels
Get PRO
December '23
+969
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
08 September+2
07 September+2
06 September+1
05 September+2
04 September0
03 September+7
02 September0
01 September0
Channel Posts
#ጳጉሜ 3 "የፅናት ቀን " ጳጉሜ 3 "የፅናት ቀን"ን ምክንያት በማድረግ የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አስተዳደር " አብሮነታችን ለጽናታችን ጽናታችን ለዘላቂ ሉዓላዊነታችን " በሚል መሪ ቃል በክፍለ ከተማው ለሚገኙ ተቋማትና ሰራተኞች የዕውቅና መስጠት መርግ-ግብር አካሄደ። በዕውቅና መስጠት መርሃ ግብሩ የክፍለ ከተማው ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ ሙሉጌታ አሰፋ ፣ የክፍለ ከተማው ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚና የሥራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፈይሳ ፈለቀ ፣ የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ምክትልና የፖለቲካና የአቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኪያ ትኩ ጨምሮ አጠቃላይ የክፍለ ከተማና የወረዳ አመራሮችና ሰራተኞች እንዲሁም ሌሎች ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ተሳትፈዋል። የክፍለ ከተማው ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚና የሥራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፈይሳ ፈለቀ መርሀ-ግብሩ ከወረዳ እስከ ክፍለ ከተማ ተቋማትና ባለሞያዎች በቁርጠኝነት ፣ በትጋት ፣ በጽናት በማገልገል የላቀ አፈፃፀም ላመጡ አካላት ዕውቅና በመስጠት በቀጣይ ስራዎች መነሳሳትን ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ገልፀዋል። አቶ ፈይሳ አያይዘውም ክፍለ ከተማው በርካታ ኢንዱስትሪ፣ ሰፋፊ የመንገድ የመሰረተ ልማት እና የአንጋፋ ተቋማት መገኛ ፣ በርካታ ሰው ተኮር ፕሮጀክቶች በመገንባት ለኢንቨስትመንት ቀዳሚ ተመራጭ መሆንዋን በመግለፅ በአዲሱ በጀት ዓመት የነበሩ ክፍተቶችን በማረም በ7/24 መርህ በማገልገል አገልግሎቱን ውጤታማ በማድረግ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት ፣ የተጀመሩ የኢኒሼቲቭ ስራዎች አጠናክሮ ማስቀጠል ለዚህም በቁርጠኝነት በታማኝነት እና በህዝብ አገልጋይነት መንፈስ ማገልገል እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል። ጽናት ማለት ፈተናዎችንና ማበልን በማለፍ የተያዘን ዓላማ ሳይታክቱ መስራት እንደሆነ የገለፁት የክፍለ ከተማው ፐ/ሰ/የሰ/ሃ/ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ጥሩወርቅ በየነ ሰራተኛው በአዲሱ ዓመትም አገልግሎትን በማደስ ህዝብን ከእንግልትና ከእንቅፋት የጸዳ፣ ቀልጣፋና ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ማገልገል፣ ለቀጣይነት ላለው ለውጥና ለሪፎርሞች አስተማማኝ አምባሳደር መሆን፣ ተገልጋይን በክብርና የማስተናገድ ባህልን ማሳደግ እንዲሁም ወንድማማችነትንና እህትማማችነትን በማጠናከር የውስጥ አንድነትን ማጎልበት በጽናት ሊተገብር እንደሚገባ ተናግረዋል ። በመድረኩ በተቋማት መካከል የግብ ስምምነት መፈራረም እና የዕውቅና መስጠት መርሃ-ግብር ተከናውኗል። በክፍለ ከተማ ደረጃ #የተሻለ አፈፃፀም ያስመዘገቡ ፅዳት ባለሙያዎች ፣ ሹፌሮች፣ አትክልተኞች፣ የተቋም ባለሙያዎች እንዲሁም ተቋማት እዉቅና ተበርክቶላቸዋል። "ፈተናን በስኬት ቃልን በተግባር!" ለበለጠ መረጃ፦ https://linktr.ee/akaki_kality_communication ጳጉሜ 3/2018 ዓ.ም አቃቂ ቃሊቲ

2
No text...
157
3
No text...
261
4
#ጳጉሜ 3 "የጽናት ቀን" "የጽናት ቀን"ን ምክንያት በማድረግ ደማቅ የፅዳት ዘመቻ ተካሄደ። ጳጉሜን 3 "የጽናት ቀን"ን ምክንያት በማድረግ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ፅዳት አስተዳደር ጽ/ቤት አዘጋጅነት " በፅናት ቁመን አዲስ አበባን እንደስሟ ፅዱ፣ውብ ማራኪ ለነዋሪዎቿ ምቹ ለኑሮ ተስማሚ እናደርጋታለን " በሚል መሪ ቃል በርካታ ማህበረሰብ የተሳተፈበት የአንድ ማዕከል የፅዳት ዘመቻ ተካሂዷል። የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ምክትልና የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኪያ ትኩና የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አብነት አሰግድ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአካባቢ ጥበቃ ምክትል ዳይሬክተር አቶ ማናየ ጫኔ፣ የወረዳ 1 አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሪት ሀያት ከድር ፣ የክፍለ ከተማው ፅዳት አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መሀመድ አህመድ ፣ ጨምሮ የወረዳው አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተግኝተዋል ። የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ምክትልና የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኪያ ትኩና የፅዳት ሠራተኞቻችን በየቀኑ በዝናብና በፀሐይ ሳትበሩ ከተማችንን ለማፅዳት የምታደርጉት ተጋድሎ የፅናት ትልቅ ማሳያ በመሆኑ ነዋሪዎች አካባቢያችሁን በመጠበቅ፣ ቆሻሻን በአግባቡ በማስወገድ እና የነቃ ተሳትፏችሁን የምታደርጉት ጥረት ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአካባቢ ጥበቃ ምክትል ዳይሬክተር አቶ ማናየ ጫኔ ባስተላለፉት መልዕክት ከተማችን አዲስ አበባን እንደ ስሟ አዲስ፣ ፅዱ እና ለነዋሪዎቿ ጤናማ የማድረግ ሀላፊነት የሁላችንም የጋራ ድርሻ ነው ያሉ ሲሆን ፅዳት የአንድ ወቅት ዘመቻ ሳይሆን የዘወትር የህይወት ዘይቤያችን ሊሆን ይገባል ብለዋል። የክ/ከተማዉ ፅዳት አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መሀመድ አህመድ በበኩላቸዉ ይህ የአንድ ማዕከል የፅዳት ዘመቻ የማህበረሰባችንን አንድነትና ቁርጠኝነት ግልጽ አድርጎ ያሳየም ነው ሲሉ ተናግረዋል ። በመጨረሻም ፅዳትን ባህል ለማድረግ በ5 የጳጉሜ ቀናት በየዕለቱ የፅዳት ንቅናቄዎች እየተካሄዱ እንደሚገኝ ማህበረሰቡ ያለማንም ቀስቃሽነት አካባቢውን ሊያፀዳ እንደሚገባ ተገልጿል ። ጳጉሜን 3 /2018 ዓ.ም አቃቂ ቃሊቲ
255
5
#ጳጉሜን 2 "የማንሰራራት ቀን" ጳጉሜን 2/2018 ዓ.ም አቃቂ ቃሊቲ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ጳጉሜን 2 "የማንሰራራት ቀን"ን ምክንያት በማድረግ የወርቃማ ሰኞ እና ፓናል ዉይይት መርሃ-ግብር ተካሄደ። በመርሃ-ግብሩ የክፍለ ከተማው ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚና የሥራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፈይሳ ፈለቀ ፣ የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ምክትልና የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኪያ ትኩና የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አብነት አሰግድ ፣ የክፍለ ከተማና የወረዳ አመሮች አጠቃላይ የክፍለ ከተማው ሰራተኞች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል ። በመድረኩ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህርና ተመራማሪ ዶ/ር ሙሉጌታ አየለ ለውይይት መነሻ የሚሆን ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን በሰነዱ የማንሰራራት ቀን ምንነት ፣ የማንሰራራት ዋና ዋና መሰረቶች ዙሪያ ሰነድ አቅርበው ውይይት ተካሂዷል። የማንሰራራት ቀን ሀገሪቱ ዓለምን ያስደመሙ ስኬቶችን ባስመዘገበችበት ወቅት መከበሩ ልዩ የሚያደርገው መሆኑን የገለፁት የክፍለ ከተማው ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚና የሥራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፈይሳ ፈለቀ በከተማዋ ማህበራዊ ፍትህን ያረጋገጡና ለሌሎች ከተሞች እንዲሁም ሀገራት ምሳሌ የሚሆኑ በርካታ የልማት ስራዎች በማንሳት ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር ተያይዞ ለዘመናት የነበረውን ስብራት የሚጠግኑ ተግባራት መከናወናቸውንና ለአብነትም የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማሳያ መሆኑ ተገልጿል። አቶ ፈይሳ ፈለቀ አያይዘውም ቀኑ ሲከበር ከተማዋ በልማት ያስመዘገበችውን ስኬት በአገልግሎት አሰጣጡ በመድገም የሀገሪቱን የማንሰራራት ሂደት ማፅናት እንደሚገባና የመንግስት ሰራተኛውም ጊዜው የሚፈልገውን ዕውቀት በማካበት ፈጣን ፣ ቀልጣፋ፣ ፍትሀዊና ቅን አገልግሎት መስጠት እንዳለበት ተመላክቷል። የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ምክትልና የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኪያ ትኩ በበኩላቸው ወርቃማ ሰኞ ከዕውቀት ሽግግር አንፃር በርካታ ጠቀሜታ ያለው ሳምንታዊ መድረክ ሲሆን፣ ለሰራተኛው አቅም መጎልበት፣ ችግር ለመፍታት፣ የተቋም ህልውና መንፈስ የሚታደስበት፣ አመራርና ባለሞያ መልካም አገልግሎት ለመስጠት ቃል የሚገቡበት፣ የበላይና የበታች ስሜትን በማስወገድ የባለቤትነት መንፈስን የሚገነባ፣ አዲሱን የስራ ሳምንት በመልካም መንፈስ ለመጀመር የሚያስችል እና ተቋማዊ ዕሴት የሚዳብርበት መድረክ መሆኑን ገልፀዋል። አያይዘውም ይህ የማንሰራራት ቀን ያለፈን ነገር ወደ ኋላ በመጣል፣ ከወደቁበት ፈጥኖ በመነሳት አዲስ የታሪክ ምዕራፍ የሚከፈትበት ሲሆን፤ በሃይማኖት አባቶች፣ በሀገር ሽማግሌዎች እንዲሁም በወጣቶች ትኩስ ጉልበት በጋራ መነሳት በሚቻልበትና ልብን ለይቅርታ ማዘጋጀት ከተቻለ የሀገሪቱ ማንሰራራት ዕውን የሚሆንበት አዲስ ምዕራፍ ነው። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህርና ተመራማሪ ዶ/ር ሙሉጌታ አየለ በበኩላቸው ሲቪል ሰርቫንቱ የሚሰጠውን አገልግሎት ከእጅ መንሻ የፀዳ በማድረግ የተገልጋዩን እርካታ ባረጋገጠ መልኩ ሊሰጥ እንደሚገባ በማንሳት ሁል ጊዜ አዳዲስ ነገሮችን ለመማር ክፍት በመሆን የጋራ መግባባት በመፍጠርና ተቀናጅቶ በመስራት የአገልግሎት አሰጣጡን ማሻገር እንደሚገባ ተናግረዋል ።
281
6
#ጳጉሜን 2 "የማንሰራራት ቀን" ጳጉሜን 2/2018 ዓ.ም አቃቂ ቃሊቲ #ጳጉሜን 2 "የማንሰራራት ቀን"ን ምክንያት በማድረግ ነፃ የትራንፖርት አገልግሎት እየተሰጠ ይገኛል። በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ በሚገኙ የትራንፖርት ተርሚናሎች የአዲስአበባ ትራንስፖርት ቢሮ ቅ/ጽ/ቤት ከክ/ከተማ አስተዳደሩ ጋር በመቀናጀት ዕለቱን በማስመልከት ነፃ የትራንስፖርት አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። በመርሃ ግብሩ ተገኝተዉ ነፃ የትራንስፖርት አገልግሎቱን ያስጀመሩት የክ/ከተማዉ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚና የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፈይሳ ፈለቀ፣ የክ/ከተማዉ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኪያ ትኩ፣ የክ/ከተማዉ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አብነት አሰግድ፣ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ትዕግስት እሸቴ ተገኝተዉ ነፃ አገልግሎት በመስጠት አስጀምረዋል። የማንሰራራት ማሳያ የሆነውን የትራንስፖርት ዘርፍ በመዘከርና በተለይም የታዳሽ ኃይል ኤሌትሪክ ተሽከርካሪዎች የተፈጥሮ ስነምህዳር ከመጠበቅ አኳያ ያላቸዉን ሚና ባጎላ መልኩ ለክ/ከተማዋ ነዋሪዎች ከማለዳው ጀምሮ  ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት በመስጠት ቀኑን እየተከበረ ይገኛል።
1
7
No text...
217
8
No text...
195
9
የአንድ ማዕከል የሰላም ሰራዊት የሰራ ስምሪት ተሰጠ። ጳጉሜን 02/13/2018 ዓ.ም አቃቂ ቃሊቲ የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ አስተዳደር የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት የአንድ ማዕከል የሰላም ሰራዊት ስምሪት ሰጥቷል። በአንድ ማዕከል ስምሪቱ የክ/ከተማው ም/ዋና ስራ አስፈፃሚና የሰራ ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፈይሳ ፈለቀ፣ የክ/ከተማው የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ምክትልና የፓለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኪያ ቱኩና፣ የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አዲስ ዘውዴ፣ የክ/ከተማው አመራሮች፣ የፀጥታ አካላትና የሰላም ሰራዊት አባላት ተሳትፈዋል። የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ አስተዳደር ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚና የሰራ ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፈይሳ ፈለቀ የሰላም ሰራዊት የሰላም አምሳደር መሆናቸውን ጠቁመው፣ ወንጀልን በመከላከልና ህገ-ወጦችን ለፀጥታ አካላት ማሳወቅ ሰላምና ፀጥታን ማረጋገጥ፣ በአዲስ ዓመት ዋዜማና የበአላት ወቅት የንግድ እና የሰዎች እንቅስቃሴ ከፍተኛ በመሆኑ ያለምንም ፀጥታ ችግር ህብረተሰቡ ወጥቶ እንዲገባ ትልቅ ሀላፊነት እየተወጡ ያሉና በመጪው በዓላት ጭምር የሰላም ማስከበርና ማረጋገጥ የሰላም ሰራዊት እና ፀጥታ አካላት ቁርጠኝነት የሚፈልግ መሆኑን መልዕክት አስተላልፈው ስምሪት ሰጥተዋል። የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ምክትልና የፓለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኪያ ቱኩ ፀሐይና ብርድን ተቋቁሞ ሰላምን ማስጠበቅ በዋጋ የማይተመን ሀላፊነት መሆኑን ገልፀው፣ የሰላም ሰራዊቱ ሚና ትልቅ እንደሆነ በመግለፅ በቀጣይም ትልልቅ የአደባባይና ህዝባዊ በዓለትን በሰላም ለማክበር የሰላም ሰራዊት አባላት እያሉ የፀጥታ ችግር እንደማይኖር ገልፀዋል። በመጨረሻም የክፍለ ከተማው ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አዲስ ዘውዴ የአንድ ማዕከል የሰላም ሰራዊት ስምሪት ልዩ የሚያደርገው በጠንካራና በተቀናጀ አሰራር ስርዓት እየተሰጠ መሆኑን አመላክተው፣ የሰላም ሰራዊቱ ከፅጥታ አካላት በቅንጅት የከተማዋንና አካባቢውን እንደሚጠብቅ ገልፀዋል።
204
10
በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ከፊታችን የሚከበሩ በዓላትን አስመልክቶ በሰላምና ፀጥታ ስራ ዙርያ ውይይት ተካሄደ። የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ከፊታችን የሚከበሩ
በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ከፊታችን የሚከበሩ በዓላትን አስመልክቶ በሰላምና ፀጥታ ስራ ዙርያ ውይይት ተካሄደ። የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ከፊታችን የሚከበሩ በዓላትን ሰላማዊና ደማቅ በሆነ ሁኔታ ማጠናቀቅ የሚያስችል የውይይት መድረክ ያካሄደ ሲሆን በመድረኩ የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ አዲስ ዘውዴ፣ የክ/ከተማዉ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ወንድወሰን ፣የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የወንጀል እና ትራፊክ አድጋ ምርመራ ምክትል ዋና መምሪያ ኮማንደር ጫንያለው ታፈሰ፣ በሸገር ሲቲ የገላን ክ/ከተማ ፖሊስ አዛዥ ረ/ ኮምሽነር ሽቶ ሊኪሳ ተገኝተዋል። የክ/ከተማዉ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አዲስ ዘውዴ እንደገለጹት፣ በዓላት በሰላም እንዲከበሩ የህብረተሰቡ ተሳትፎ እና የጸጥታ አካላት ሚና የጎላ መሆኑን ጠቅሰዉ ጠንካራ የሰላም ባህል ለመገንባት ከአጎራባች ክ/ከተሞች ጋር በቅኝጅት እየተሰራ መሆኑን እና ይህም በዓሉ ሰላማዊነቱ የተጠበቀ፣ የተረጋጋ ሆኖ ተከብሮ እንዲያልፍ በትኩረት የሚሰራ መሆኑን ገልፀዋል። የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የወንጀል እና ትራፊክ አደጋ ምርመራ ምክትል ዋና መምሪያ ኮማንደር ጫንያለው ታፈሰ ጎባና በበኩላቸው፣ የጸጥታ ኃይሉ በማንኛውም ሰዓት ለአደጋ ዝግጁ መሆኑን ጠቅሰው፣ በበዓሉ ቀናት ሊያጋጥሙ የሚችሉ ህገ-ወጥ እንቅስቃሴዎችን ለመቀልበስ ከህብረተሰቡ ጋር በቅርበት እንደሚሰሩ አጽንኦት ሰጥተዋል። በሸገር ሲቲ የገላን ክፍለ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ረ/ኮሚሽነር ሽቶ ሊኪሳ በበኩላቸው አዋሳኝ አካባቢዎች ላይ ምንም አይነት የጸጥታ ስጋት እንዳይፈጠር በጋራ እየተሰራ መሆኑንና በሁለቱ አስተዳደሮች መካከል ጠንካራ መረጃ ልውውጥ እና የጋራ የጸጥታ ማዕቀፍ እንዳለ ገልጸዋል።
208
11
No text...
1
12
#ጳጉሜን 2 "የማንሰራራት ቀን" ጳጉሜን 2/2018 ዓ.ም አቃቂ ቃሊቲ የአየር ንብረት ለውጥና የአየር ብክለት የሚያስከትሉትን የበረታ ጉዳት ለመቀነስ እንዲሁም ዘላቂና አካባቢን የማይጎዳ የትራንስፖር
#ጳጉሜን 2 "የማንሰራራት ቀን" ጳጉሜን 2/2018 ዓ.ም አቃቂ ቃሊቲ የአየር ንብረት ለውጥና የአየር ብክለት የሚያስከትሉትን የበረታ ጉዳት ለመቀነስ እንዲሁም ዘላቂና አካባቢን የማይጎዳ የትራንስፖርት ስርዓት ለመገንባት ነዳጅ አልባና በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን መጠቀም ወሳኝ መፍትሔ ነው። የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አስተዳደርም ጳጉሜ 2 "የማንሰራራት ቀን"ን ምክንያት በማድረግ " ነዳጅ አልባ ተሽከርካሪዎች በመጠቀም የአየር ብክለትን እንቀንስ " በሚል መሪ ቃል የተለያዩ መርሃ-ግብሮች ተከናውነዋል። የኤሌክትሪክ፣ የሃይድሮጅን እንዲሁም የብስክሌትና መሰል አማራጭ የትራንስፖርት ዘዴዎችን በስፋት ጥቅም ላይ ማዋል የአየር ብክለትን በከፍተኛ ደረጃ የመቀነስና ንፁህ የመኖሪያ አካባቢን መፍጠር እንደሚገባ መልዕክት ተላልፏል ።
164
13
#ጳጉሜን 2 "የማንሰራራት ቀን" ጳጉሜን 2/2018 ዓ.ም አቃቂ ቃሊቲ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ጳጉሜን 2 "የማንሰራራት ቀን"ን ምክንያት በማድረግ  የወርቃማ ሰኞ እና ፓናል ዉይይት መርሃ-ግብር ተካሄደ። በመርሃ-ግብሩ የክፍለ ከተማው ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚና የሥራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፈይሳ ፈለቀ ፣ የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ምክትልና የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኪያ ትኩና የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አብነት አሰግድ ፣ የክፍለ ከተማና የወረዳ አመሮች አጠቃላይ የክፍለ ከተማው ሰራተኞች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል ። በመድረኩ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህርና ተመራማሪ ዶ/ር ሙሉጌታ አየለ ለውይይት መነሻ የሚሆን ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን በሰነዱ የማንሰራራት ቀን ምንነት ፣ የማንሰራራት ዋና ዋና መሰረቶች ዙሪያ ሰነድ አቅርበው ውይይት ተካሂዷል። የማንሰራራት ቀን ሀገሪቱ ዓለምን ያስደመሙ ስኬቶችን ባስመዘገበችበት ወቅት መከበሩ ልዩ የሚያደርገው መሆኑን የገለፁት የክፍለ ከተማው ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚና የሥራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፈይሳ ፈለቀ በከተማዋ ማህበራዊ ፍትህን ያረጋገጡና ለሌሎች ከተሞች እንዲሁም ሀገራት ምሳሌ የሚሆኑ በርካታ የልማት ስራዎች በማንሳት ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር ተያይዞ ለዘመናት የነበረውን ስብራት የሚጠግኑ ተግባራት መከናወናቸውንና ለአብነትም የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማሳያ መሆኑ ተገልጿል። አቶ ፈይሳ ፈለቀ አያይዘውም ቀኑ ሲከበር ከተማዋ በልማት ያስመዘገበችውን ስኬት በአገልግሎት አሰጣጡ በመድገም የሀገሪቱን የማንሰራራት ሂደት ማፅናት እንደሚገባና የመንግስት ሰራተኛውም ጊዜው የሚፈልገውን ዕውቀት በማካበት ፈጣን ፣ ቀልጣፋ፣ ፍትሀዊና ቅን አገልግሎት መስጠት እንዳለበት ተመላክቷል። የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ምክትልና የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኪያ ትኩ በበኩላቸው ወርቃማ ሰኞ ከዕውቀት ሽግግር አንፃር በርካታ ጠቀሜታ ያለው ሳምንታዊ መድረክ ሲሆን፣ ለሰራተኛው አቅም መጎልበት፣ ችግር ለመፍታት፣ የተቋም ህልውና መንፈስ የሚታደስበት፣ አመራርና ባለሞያ መልካም አገልግሎት ለመስጠት ቃል የሚገቡበት፣ የበላይና የበታች ስሜትን በማስወገድ የባለቤትነት መንፈስን የሚገነባ፣ አዲሱን የስራ ሳምንት በመልካም መንፈስ ለመጀመር የሚያስችል እና ተቋማዊ ዕሴት የሚዳብርበት መድረክ መሆኑን ገልፀዋል። አያይዘውም ይህ የማንሰራራት ቀን ያለፈን ነገር ወደ ኋላ በመጣል፣ ከወደቁበት ፈጥኖ በመነሳት አዲስ የታሪክ ምዕራፍ የሚከፈትበት ሲሆን፤ በሃይማኖት አባቶች፣ በሀገር ሽማግሌዎች እንዲሁም በወጣቶች ትኩስ ጉልበት በጋራ መነሳት በሚቻልበትና ልብን ለይቅርታ ማዘጋጀት ከተቻለ የሀገሪቱ ማንሰራራት ዕውን የሚሆንበት አዲስ ምዕራፍ ነው። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህርና ተመራማሪ  ዶ/ር ሙሉጌታ አየለ በበኩላቸው ሲቪል ሰርቫንቱ የሚሰጠውን አገልግሎት ከእጅ መንሻ የፀዳ በማድረግ የተገልጋዩን እርካታ ባረጋገጠ መልኩ ሊሰጥ እንደሚገባ በማንሳት ሁል ጊዜ አዳዲስ ነገሮችን ለመማር ክፍት በመሆን የጋራ መግባባት በመፍጠርና ተቀናጅቶ በመስራት የአገልግሎት አሰጣጡን ማሻገር እንደሚገባ ተናግረዋል ።
1
14
#ጳጉሜን 2 "የማንሰራራት ቀን" ጳጉሜን 2/2018 ዓ.ም አቃቂ ቃሊቲ #ጳጉሜን 2 "የማንሰራራት ቀን"ን ምክንያት በማድረግ ነፃ የትራንፖርት አገልግሎት እየተሰጠ ይገኛል። በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ በ
#ጳጉሜን 2 "የማንሰራራት ቀን" ጳጉሜን 2/2018 ዓ.ም አቃቂ ቃሊቲ #ጳጉሜን 2 "የማንሰራራት ቀን"ን ምክንያት በማድረግ ነፃ የትራንፖርት አገልግሎት እየተሰጠ ይገኛል። በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ በሚገኙ የትራንፖርት ተርሚናሎች የአዲስአበባ ትራንስፖርት ቢሮ ቅ/ጽ/ቤት ከክ/ከተማ አስተዳደሩ ጋር በመቀናጀት ዕለቱን በማስመልከት ነፃ የትራንስፖርት አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። በመርሃ ግብሩ ተገኝተዉ ነፃ የትራንስፖርት አገልግሎቱን ያስጀመሩት የክ/ከተማዉ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚና የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፈይሳ ፈለቀ፣ የክ/ከተማዉ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኪያ ትኩ፣ የክ/ከተማዉ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አብነት አሰግድ፣ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ትዕግስት እሸቴ ተገኝተዉ ነፃ አገልግሎት በመስጠት አስጀምረዋል። የማንሰራራት ማሳያ የሆነውን የትራንስፖርት ዘርፍ በመዘከርና በተለይም የታዳሽ ኃይል ኤሌትሪክ ተሽከርካሪዎች የተፈጥሮ ስነምህዳር ከመጠበቅ አኳያ ያላቸዉን ሚና ባጎላ መልኩ ለክ/ከተማዋ ነዋሪዎች ከማለዳው ጀምሮ ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት በመስጠት ቀኑን እየተከበረ ይገኛል።
252
15
No text...
342
16
#ጳጉሜ 1 "የእመርታ ቀን " " የእመርታ ቀን " ምክንያት በማድረግ የፓናል ውይይት ተካሄደ የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ጳጉሜ 1 "የእመርታ ቀን" ምክንያት በማድረግ "አዲስ አበባ፤ የሀገራዊ አምርታችን ህያው ማሳያ" በሚል መሪ ቃል የፓናል ውይይት አካሄደ። በፓናል ውይይቱ ላይ የክፍለ ከተማው ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚና የሥራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፈይሳ ፈለቀ ፣ የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ምክትልና የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኪያ ትኩ፣ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አብነት አሰግድን ጨምሮ የክፍለ ከተማው አመራሮች፣ አርሶ አደሮች፣ የኢንዱስትሪ ባለቤቶች፣ ኮንትራክተሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የተሳተፉ ሲሆን በክፍለ ከተማው ፕላን ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ በወ/ሮ ኃይማኖት ደውሼ አቅራቢነት የ2018 በጀት ዓመት እና የባለፉት 5 ዓመታት የተመዘገቡ እመርታዎች ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል። የክፍለ ከተማው ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚና የሥራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፈይሳ ፈለቀ እንደገለጹት ባለፉት የለውጥ ዓመታት በተካሄዱ አጠቃላይ የኢኮኖሚ ሪፎርሞችና የልማት ንቅናቄዎች ሀገሪቱን ከነበረችበት የኢኮኖሚ አዘቅት በማውጣት ትላልቅ ስኬቶችን ማስመዝገብ መቻላቸውንና በተለይም ከውጭ ይገባ የነበረውን የስንዴ ምርት በማስቆም ኢትዮጵያን የአፍሪካ ቀዳሚ የስንዴ አምራች ማድረግ መቻሉንና በ"ኢትዮጵያ ታመርት" እንዲሁም በ"ሌማት ትሩፋት" መርሃ-ግብሮች የኢንዱስትሪና የከተማ ግብርና ምርታማነትን ማሳደግ እንደተቻለ ተናግረዋል። አቶ ፈይሳ አያይዘውም አዲስ አበባን የስማርት ሲቲ ተምሳሌት የማድረግ ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን በመጥቀስ የጳጉሜ የመጀመሪያ ቀን "የእመርታ ቀን" ተብሎ ሲከበር ያለፉትን ስኬቶች በመገምገም፣ አቅሞችን በመደመርና ድክመቶችን በማረም ለ2019 አዲስ ዓመት የተሻለ የልማትና የምርታማነት ዝግጅት ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ምክትልና የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኪያ ትኩ በበኩላቸው የጳጉሜ ቀናት በየዓመቱ በልዩ ስያሜዎችና ሁነቶች መከበራቸው ሀገራዊ ጠቀሜታ ያላቸውን አስተሳሰቦች ለማመንጨት ማስቻሉን በመጥቀስ በለውጡ ዓመታት በማክሮ ኢኮኖሚ ፣ በግዙፍ ፕሮጀክቶች ፣ በኮሪደር ልማት ፣ በምግብ ዋስትና፣ በዲፕሎማሲና የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ በኩል ከፍተኛ ስኬት መመዝገቡን ጠቁመው፤ በቀጣይም የማህበረሰቡን ጥያቄዎች ለመመለስ አስተዳደሩ በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። በመድረኩ አስተያየታቸውን የሰጡት ተሳታፊዎች በክፍለ ከተማውና በከተማ ደረጃ የአርሶ አደሩን መብት ፈጠራ በማሳደግ ፣ በፕሮጀክት አፈጻጸም፣ በተኪ ምርቶችና በመሠረተ ልማት ዘርፎች ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገባቸውን በመጥቀስ አምራች ዘርፉን ማጠናከር፣ የውጭ ኢንቨስትመንትን መሳብና ቅንጅታዊ አሠራርን ማጎልበት እንደሚገባም ጠቁመዋል። የክ/ከተማዉ ኢንዱስትሪ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተመስገን በተነሱ ለሳቦች ላይ በሰጡት ምላሽ የኢትዮጵያ ታምርት አዲስ አበባ ታምርት ንቅናቄን መነሻ በማድረግ መንግስት ለዘርፉ በሰጠዉ ትኩረት የበርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ችግሮች ለመፎታት ጥረት የተደረገ ሲሆን አሁንም ይሄ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል። በመጨረሻም ከመድረኩ ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች በሚመለከታቸው የጽ/ቤት ኃላፊዎችና ፓናሊስቶች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል። ጳጉሜ 1/2018 ዓ.ም አቃቂ ቃሊቲ
336
17
#በቂ ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ በብዙ አማራጭ በባዛር እና በቅዳሜና እሁድ ገበያዎች ይሸምቱ! ዉድ የክ/ከተማችን ነዋሪዎች ከፊታችን የሚከበሩ በዓላትን ምክንያት በማድረግ አስተዳደሩ በአንድ ማዕከል እና
#በቂ ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ በብዙ አማራጭ በባዛር እና በቅዳሜና እሁድ ገበያዎች ይሸምቱ! ዉድ የክ/ከተማችን ነዋሪዎች ከፊታችን የሚከበሩ በዓላትን ምክንያት በማድረግ አስተዳደሩ በአንድ ማዕከል እና ባሉት 12 ወረዳዎች ባዛር በመክፈት እንዲሁም በቅዳሜና እሁድ ገበያዎች፣ በሸማች ሱቆችና በገበያ ማዕከል በቂ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በመኖርያ አቅራቢያ በማዘጋጀት ነዋሪዎች ለነዋሪዎች ተደራሽ እንዲሆን እየሰራ ይገኛል። ይህንኑ በመረዳት በሚመችዎ አማራጭ እንድትሸምቱ መልዕክታችን ነዉ!
349
18
በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት የ3 አቅመ ደካማ ቤት እድሳት የማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሄደ፡፡ ነሃሴ 30/2018 ዓ.ም አቃቂ ቃሊቲ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት የክፍለ ከተማዉ ኢንዱስትሪ ልማት ጽ/ቤት ፣ የክፍለ ከተማዉ ጤና ጽ/ቤት እና የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የ3 አቅመ ደካማ ነዋሪዎች ቤት መልሶ ግንባታ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሄደ፡፡ በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የክፍለ ከተማ አስተዳደሩ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ እና የስራ እና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፈይሳ ፈለቀ ፣የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ምክትል እና የፓለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኪያ ቱኩ የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የአደረጃጃት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አብነት አሰግድ ፣ የክፍለ ከተማዉ ህብረተሰብ ተሳትፎ እና በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ይቻላል አይኔ፣የወረዳ 3 አስተዳደር ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወንድሙ ቀጄላ፣የክፍለ ከተማዉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባላት፣የወረዳዉ አመራሮች፣በጎ ፍቃደኞች፣ባለሀብቶች እና የአካባቢዉ ነዋሪዎች ተገኝተዋል፡፡ የክፍለ ከተማ አስተዳደሩ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ እና የስራ እና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፈይሳ ፈለቀ በመርሃ ግብሩ ተገኝተዉ እንደገለጹት ሀገር የሚገነባዉ በጋራ ሁሉም የድርሻዉን መወጣት ሲችል ነዉ በማለት የፖለቲካ ፓርቲዎች በበጎ ፍቃድ፣በአካባቢ ልማት እና በሌሎች ስራዎች የሚያደርጉት ተሳትፎ ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡ የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ምክትል እና የፓለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኪያ ቱኩ በበኩላቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች የሀሳብ ልዩነቶችን በማክበር አንድ በሚያደርጉ በጎ ፍቃድ ስራዎች የሚያደርጉት ተሳትፎ የበለጠ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ሲሉ ተናግረዋል፡፡ የአቅመ ደካማ እና አረጋዉያንን ቤት ስናድስ የአከባቢን እና የከተማዉን ገጽታ ጭምር የምንቀይርበት ነዉ በማለት የተጀመረዉ የቤት ግንባታ በታቀደለት ጊዜ አጠናቆ ለማስረከብ በቂ ድጋፍና ክትትል ሊደረግ ይገባል በማለት አሳስበዋል፡፡ የወረደ 3 አስተዳደር ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወንድሙ ቀጄላ የእንኳን ደህና መጣቸወሁ ንግግር ሲያደርጉ እንደገለጹት በበጎ ፍቃድ ስራዉ ያስተባበሩ አመራሮችን፣የተሳተፉ ባለ ሀብቶች፣በጎ ፍቃደኞች እና የአካባቢዉ ነዋሪዎችን አመስግነዋል፡፡
345
19
+9
No text...
339
20
+9
No text...
278