en
Feedback
Peka - ፔካ

Peka - ፔካ

Open in Telegram

The Great source of Knowledge. ፔካ ብሩህ የሆነ ነጭ ዕንቁ ነው። እውቀትም ብርሃን ነው። You Tube => ? Channel 2 => t.me/Peka369 Owner - @Lumos1

Show more
2 958
Subscribers
No data24 hours
-57 days
-2930 days
Posts Archive
Repost from Peka - ፔካ
📚 መዝሙረ ዳዊት 150ዎቹ መዝሙራት በአማረኛ 📚 ❤️መጠን 1.5 MB ብቻ #SHARE #SHARE 👇JOIN 4 MORE 👇 @EthiopeTowoderos

🤓Watch Now "የኦሪዮን ሕብረ ኮከብና ጥንታዊ ታሪኮች - ከመጋቢ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰና ከዶክተር ጌትነት ፈለቀ አንድሮሜዳ 2 መጽሐፍ የተወሰደ።" on YouTube 👇👇👇 https://youtu.be/qqB751jYSE8

📌 ስለ መጋቢት 29 ... ሊቃውንት፣ መምሕራን ምን ያስተምሩናል!? ከመምሕር ዶክተር ዘበነ ለማ የተማርኩትን አካፈልኳችሁ። 1 - ዓለም የተፈጠረችባት ዕለት፣ 2 - ቅዱስ ገብርኤል እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ያበሰረበት ዕለት፣ 3 - ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተጸነሰበት ዕለት፣ 4 - ጌታ ሞትን ድል አድርጎ የተነሳበት ዕለት፣ 5 - ዳግም የሚመጣባት ዕለት ነው። 👉 ይህ ሁሉ የሆነው ሚሆነው በመጋቢት 29 ነው፤ ይገርማል የእግዚአብሔር ስራ ሁሉ በቀመር ነው.... ለዚህም ነው ጠቢቡ ሰሎሞን 'ለሁሉም ጊዜ አለው' ብሎ የተናገረው። ታውቁ ነበር!? #ሼር እያረጋችሁ! ምስጋና ለእግዚአብሔር! JOIN: @EthiopeTowoderos

📌 ስለ ዕፅዋት... ሕክምና ትንሽ ልንገራችሁ!? 👉🏻 ስለ ጥንታዊ ሕክምና ስለ ዕፅዋት፣ እንስሳት፣ የከበሩ ድንጋዮች ምስጢር ከመጽሐፍ ቅዱስም ሆነ ከቅዱሳን መጻሕፍት ብዙ ምስጢር ፈልቅቀን እናውጣ ቢባል ድንቅ ነገርን እናገኝ ነበር። ልዑል እግዚአብሔር ሣሩን ቅጠሉን ግንዱን ፍሬውን ሥሩን ቅርፊቱን በሰማያዊ ምስጢር አመስጥሮና በቀመር ቀምሮ እንደፈጠረ መርምረን ስናውቅ በእውነት ያለ ሐሰት እንደነቃለን! ምስጋና ለእጆቹ ሥራዎች በሙሉ ይሁን! 👉🏻 የተለያዩ ቀደምት ማኅበረሰቦችም ከተለያዩ ነገሮች በመነሳት ምርምሮችን ሰርተው እኒህን ፍጥረታት ሲጠቀሙባቸው ኑረዋል፤ ከኒህ ማኅበረሰቦች ውስጥ ኢትዮጵያዊያንም ትልቁን ድርሻ ይይዛሉ። ከቁስለ ሥጋ ሕመመ ሥጋም ተፈውሰውባቸዋል፤ ይህ ብቻ አይደለም ምግበ ነፍስ ምግበ መንፈስም ሁነዋቸዋል፤ ዕፅዋትን በማየት ከመንፈስ ስብራት ተፈውሰውባቸዋል፤ ዕፅዋትን በጥበብ በመጠቀም ራሳቸውን እስከማደስ ድረስ ደርሰውባቸዋል። ለዚህ ነው ዕፅዋት የሥልጣኔ መሠረት ናቸው የምለው። አንዳንድ ሰዎች ዕፅዋትን ለርኩሳን መናፍሥት ሲሰጧቸው፣ ጥንቆላ እያሉ ሲያጣጥሉ ተመልክቻለሁ። እያስተዋልን ወገን እግዚአብሔር ዕፅዋትን በዕለተ ማግሰኞ... በየወገኑ ፈጥሯል... የጥበቡ መገለጫዎች ናቸው። ነገር እንዳይበዛ በሚል ተውኩት እንጂ ስለ ዕፅዋት ፈውስ ከዚያም በላይ ስለ ዕፅዋቱ ገቢር በመጽሐፍ ቅዱስ ብዙ እንደተጻፈ ስንቶቻችን እናውቅ ይሆን? በባዶ አትተቹ... አዕምሯችሁን አስፍታችሁ ልቡናችሁን አንቅታችን ፍጡራንን ሁሉ እንደየወገናቸው መርምሩ! እንመርምር! ያኔ ፈጣሪን እናገኘዋለህ። 📌 እስቲ ስለ ዕፅዋትና ስለ ሐኪም ሁሌም የምደነቅበት አንጋረ ፈላስፋ የተባለው ጥንታዊ መጽሐፍ ምን እንደሚል እንመልከት። እግዚአብሔርን መፍራት የጥበብ መጀመሪያ ነው፤ ወይም የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው። ሲራክ 1፥ 14 መዝ. 110 👉🏻 " ከሱ የምትሻውን ከመፈለግህ በፊት ባለመድኃኒቱን(ሐኪሙን) አክብረው(ውደደው) ጥበቡን የገለጸለትም እግዚአብሔር እንደሆነ ዕወቅ። በሐኪሙ እጅ አማካይነት መድኃኒቱን የሚሰጥ እርሱ ባለቤቱ ነውና። 👉🏻 ጥበብን በማወቁ ባለ መድኃኒቱን ሁሉ ያከብረዋል፤ ይልቁንም በመኳንንቱ ዘንድ ይከበራል። እግዚአብሔር መድኃኒትን ከምድር ፈጥሯልና፥ ብልህም ሰው አይንቀውም፥ መድኃኒትማ ይናቅ ዘንድ ከሃሊነቱን ሊያውቁ፥ መራራ ውኃ በዕንጨት የጣፈጠ አይደለምን? ለሙሴ ዞጲ የሚባል ዕንጨት አሳይቶታል። (ዘፀአት 15፥ 25) ሲራክ 38 1 8 👉🏻 ለኖኅ ሺህ መድኃኒት ነግሮታል፥ ከሺ 300ን ለዚህ ይበጃል ብሎ በቃል ነግሮታል፥ 700ን ከማር ከቅቤ ታገኘዋለህ ብሎታል። (ኩፋ 42፥8፥10) " 📌 በቻላችሁት መጠን እኒህን ጥበባት መርምሩ፤ ግን ስትመረምሩ በትዕግስት፣ በፈሪሃ እግዚአብሔር፣ በጸሎት የታገዘ ምርምርን ተከተሉ፤ አውቃለሁ አትበሉ፤ ምስጢርን እንወቅ እንጠብቅ፣ በአስፈላጊ ሰዓት ሐገርና ወገንን እንጥቀምበት እንጂ የአባቶቻችንን ጥበብ በደንብ ሳናውቅ ብናውቅም እንኳ በከንቱ አንበትን፣ ለባዕዳን አሳልፈን አንስጥ፤ ጥበብ የሚያከብሯትን ታከብራለች፤ ይህንን አንርሳ። ጽሑፉ ሰውን ያስተምራል ብላችሁ ካመናችሁ #ሼር በማድረግ ለሌሎችም አጋሩ። ለዛሬው ቢዘረዘር የማያልቀውን ጦማሬን በዚሁ ፈጸምኹ! አስፈላጊ ከሆነ ወደፊት በሰፊው የምዳስስላችሁ ይሆናል። ✍🏾 በኃይለሚካኤል ደሣለኝ።(@HailemichaelDesalegn ) 29/07/14 ዓ.ም 👉🏻 ቻናል፡ @EthiopeTowoderos

📌 ስለ ዕፅዋት... ሕክምና ትንሽ ልንገራችሁ!? 👉🏻 ስለ ጥንታዊ ሕክምና ስለ ዕፅዋት፣ እንስሳት፣ የከበሩ ድንጋዮች ምስጢር ከመጽሐፍ ቅዱስም ሆነ ከቅዱሳን መጻሕፍት ብዙ ምስጢር ፈልቅቀን እናውጣ ቢባል ድንቅ ነገርን እናገኝ ነበር። ልዑል እግዚአብሔር ሣሩን ቅጠሉን ግንዱን ፍሬውን ሥሩን ቅርፊቱን በሰማያዊ ምስጢር አመስጥሮና በቀመር ቀምሮ እንደፈጠረ መርምረን ስናውቅ በእውነት ያለ ሐሰት እንደነቃለን! ምስጋና ለእጆቹ ሥራዎች በሙሉ ይሁን! 👉🏻 የተለያዩ ቀደምት ማኅበረሰቦችም ከተለያዩ ነገሮች በመነሳት ምርምሮችን ሰርተው እኒህን ፍጥረታት ሲጠቀሙባቸው ኑረዋል፤ ከኒህ ማኅበረሰቦች ውስጥ ኢትዮጵያዊያንም ትልቁን ድርሻ ይይዛሉ። ከቁስለ ሥጋ ሕመመ ሥጋም ተፈውሰውባቸዋል፤ ይህ ብቻ አይደለም ምግበ ነፍስ ምግበ መንፈስም ሁነዋቸዋል፤ ዕፅዋትን በማየት ከመንፈስ ስብራት ተፈውሰውባቸዋል፤ ዕፅዋትን በጥበብ በመጠቀም ራሳቸውን እስከማደስ ድረስ ደርሰውባቸዋል። ለዚህ ነው ዕፅዋት የሥልጣኔ መሠረት ናቸው የምለው። አንዳንድ ሰዎች ዕፅዋትን ለርኩሳን መናፍሥት ሲሰጧቸው፣ ጥንቆላ እያሉ ሲያጣጥሉ ተመልክቻለሁ። እያስተዋልን ወገን እግዚአብሔር ዕፅዋትን በዕለተ ማግሰኞ... በየወገኑ ፈጥሯል... የጥበቡ መገለጫዎች ናቸው። ነገር እንዳይበዛ በሚል ተውኩት እንጂ ስለ ዕፅዋት ፈውስ ከዚያም በላይ ስለ ዕፅዋቱ ገቢር በመጽሐፍ ቅዱስ ብዙ እንደተጻፈ ስንቶቻችን እናውቅ ይሆን? በባዶ አትተቹ... አዕምሯችሁን አስፍታችሁ ልቡናችሁን አንቅታችን ፍጡራንን ሁሉ እንደየወገናቸው መርምሩ! እንመርምር! ያኔ ፈጣሪን እናገኘዋለህ። 📌 እስቲ ስለ ዕፅዋትና ስለ ሐኪም ሁሌም የምደነቅበት አንጋረ ፈላስፋ የተባለው ጥንታዊ መጽሐፍ ምን እንደሚል እንመልከት። እግዚአብሔርን መፍራት የጥበብ መጀመሪያ ነው፤ ወይም የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው። ሲራክ 1፥ 14 መዝ. 110 👉🏻 " ከሱ የምትሻውን ከመፈለግህ በፊት ባለመድኃኒቱን(ሐኪሙን) አክብረው(ውደደው) ጥበቡን የገለጸለትም እግዚአብሔር እንደሆነ ዕወቅ። በሐኪሙ እጅ አማካይነት መድኃኒቱን የሚሰጥ እርሱ ባለቤቱ ነውና። 👉🏻 ጥበብን በማወቁ ባለ መድኃኒቱን ሁሉ ያከብረዋል፤ ይልቁንም በመኳንንቱ ዘንድ ይከበራል። እግዚአብሔር መድኃኒትን ከምድር ፈጥሯልና፥ ብልህም ሰው አይንቀውም፥ መድኃኒትማ ይናቅ ዘንድ ከሃሊነቱን ሊያውቁ፥ መራራ ውኃ በዕንጨት የጣፈጠ አይደለምን? ለሙሴ ዞጲ የሚባል ዕንጨት አሳይቶታል። (ዘፀአት 15፥ 25) ሲራክ 38 1 8 👉🏻 ለኖኅ ሺህ መድኃኒት ነግሮታል፥ ከሺ 300ን ለዚህ ይበጃል ብሎ በቃል ነግሮታል፥ 700ን ከማር ከቅቤ ታገኘዋለህ ብሎታል። (ኩፋ 42፥8፥10) " 📌 በቻላችሁት መጠን እኒህን ጥበባት መርምሩ፤ ግን ስትመረምሩ በትዕግስት፣ በፈሪሃ እግዚአብሔር፣ በጸሎት የታገዘ ምርምርን ተከተሉ፤ አውቃለሁ አትበሉ፤ ምስጢርን እንወቅ እንጠብቅ፣ በአስፈላጊ ሰዓት ሐገርና ወገንን እንጥቀምበት እንጂ የአባቶቻችንን ጥበብ በደንብ ሳናውቅ ብናውቅም እንኳ በከንቱ አንበትን፣ ለባዕዳን አሳልፈን አንስጥ፤ ጥበብ የሚያከብሯትን ታከብራለች፤ ይህንን አንርሳ። ለዛሬው ቢዘረዘር የማያልቀውን ጦማሬን በዚሁ ፈጸምኹ! አስፈላጊ ከሆነ ወደፊት በሰፊው የምዳስስላችሁ ይሆናል። ✍🏾 በኃይለሚካኤል ደሣለኝ።(@HailemichaelDesalegn ) 29/07/14 ዓ.ም 👉🏻 ቻናል፡ @EthiopeTowoderos

🟡 7+1 የበገና ዝማሬዎች 🔲 በመምህር ተስፋዬ አበራ 💽 Size: 25 MB 1. እግዚአብሔርን እወዳለሁ የምትል አንተ ሰው 2. ልታድነን ውደድና አቤቱ ና ቅረበን 3. እረኝነት ነው ግብሬ - በዘማሪ አቤል ተስፋየ 4. ልዘምርልሽ በትሕትና 5. አባታችን 6. ሰላም ለእናንተ ይሁን 7. ለኢትዮጵያ ምህረትን ላክ 8. ድንግል እናቴ @EthiopeTowoderos

7_የበገና_ዝማሬዎች_በመምህር_ተስፋዬ_አበራ_xCafieD4Lcw_249.ogg24.72 MB

📌 THANK YOU FOR 3K/3000/ SUBSCRIBERS ON YOUTUBE Wedehuala Ancient Wisdoms / ወደ ኋላ ጥንታዊ ጥበባት With Hailemichael Desalegn Channel Link: https://www.youtube.com/channel/UCmdQNLIJU8JqXNCd1s3LOqg

" ክቡር ሞቱ ለጻድቅ በቅድመ እግዚአብሔር " መዝ. 115 የአባታችንን ዜና እረፍት እንደሰማችሁት ነው። እስቲ የግሌን ምልከታ ላጋራችሁ፤ ከተሳሳትኩ አርሙኝ ውስጤ ሚሰማኝን አሳጥሬ እንዲህ ጻፍኩ። ው
+2
" ክቡር ሞቱ ለጻድቅ በቅድመ እግዚአብሔር " መዝ. 115 የአባታችንን ዜና እረፍት እንደሰማችሁት ነው። እስቲ የግሌን ምልከታ ላጋራችሁ፤ ከተሳሳትኩ አርሙኝ ውስጤ ሚሰማኝን አሳጥሬ እንዲህ ጻፍኩ። ውይ ግን ምኑ ዘመን ላይ ደረስን? የእግዚአብሔር ፈቃድ ይሁን...ብቻ ግን በየክፍለ ሀገሩ ስንትና ስንት ጸጋ ያላቸው አባቶችን በኒህ አምስት ዓመታት ውስጥ እያጣን ነው። በሉ እንንቃ ወገኖቼ በጾም በጸሎት በስግደት ከቀደመው በበለጠ መልኩ እንበርታ እንጠንክር። እንደማስበው ከሆነ ነገርየው ከባድ ነው.....፤ በርቱ! እንበርታ! በኢትዮጵያና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሚነሱብንን ምድራዊና ረቂቅ መንፈሳዊ ጠላቶች በጸሎት ጋሻ መመከት ያስፈልጋል። በዚች ጊዜያችን ንስሃ እንግባ ስለራሳችን ኃጢአት እናንባ እንጸልይ! ስለ ኢትዮጵያ (ተፈጥሯዊ(የሚስጢር ምንጭ የሆኑ መልክአ ምድሮቿ ተራራው ኮረብታው... ና ሰው ሰራሽ ሐብቶቿ ቅርሶቿ ቅዱሳንት መካናት...) እንጸልይ! ስለ ወገኖቻችን ሞት መሰደድ መፈናቀል መራብ መጠማት......እንጸልይ! ...ስለዓለም...... እንጸልይ! ጊዜው የጸሎት ጊዜ ነው....... ልዑል እግዚአብሔር ስለሕዝባቸው የሚጸልዩ አባቶችን እናቶችን አያሳጣን! የአባታችን ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ በረከታቸው ይደርብን! እግዚአብሔር ማስተዋሉን ያድለን። "እምነ ተናግሮ ይኄይስ አርምሞ" ✍ ኃይለሚካኤል 25/06/14 ዓ.ም @EthiopeTowoderos

📌 ስለ አድዋ ሳስብ .......... 📜 አይ ኢትዮጵያ!? አስተውሉ እስኪ የቆምንባት፣ የተቀመጥንባት ምድር ለከንቱ በከንቱ ያይደለ ስለሀገራቸው ኢትዮጵያ፥ ስለሃይማኖታቸው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን፥ ስለ ባሕልና ማንነት፥ ሥርዓታቸው ሲሉ በተሰዉ፣ ከዓለም ፍቅር ይልቅ የእግዚአብሔርን ፍቅር መርጠው፤ ዓለምን ንቀው፣ እግዚአብሔርን አልቀው፣ ርኩሳን መናፍሥትን አድቅቀው በየአድባራቱ በኖሩ፣ በልዩ ልዩ ሁኔታዎች መልካም ሰውተው እግዚአብሔርን አስደስተው ባለፉ ቅዱሳን ቁጥራቸውን እግዚአብሔር በሚያውቃቸው ቅዱሳን፥ ጻድቃን፥ ሰማዕታት፥ ብጹአን፥ ደናግል፥ መነኮሳት ንጹሕ ሥጋ፥ ደምና አጥንት እንደተገነባች ብናውቅ ኑሮኮ እንዲ በጠበበ አስተሳሰብ በጎሰኝነት ነቀርሣ አንያዝም ነበር። ለነገሩ የርኩሳን መናፍሥት መፈንጫ ዘመን ሆኖ አደለ፤ የሰው ኅሊና ላይ አድረውና ተቆጣጥረው ደም ያፋስሳሉ። እንዴው በየቦታው የሚገኙት ሥውራን አባቶችና እናቶች የእሳት ልጅ አመድ ሁነን ሲያዩን ምን ይሉ ይሆን!? ክቡሩ ሰው እንዲ ሲሆንስ ምን ይሉ!? አንዳንዴ አሁን ላይ ያለውን የሀገራችንን ሁኔታ ስመለከት አባቶቻችን እናቶቻችን አድዋ ላይ የተዋጉት በከንቱ ነው እላለሁ፤ ወድጄ መሰላችሁ!? እንዴው አሁን እኛ ቅኝ አልተገዛንም ማለት ይቻል ይሆን!? በማኅበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊና በፖለቲካዊ ጉዳዮች አሁን ላይ ቅኝ ተገዝተናል ማለት ይቻላል፤ የትኛው ጠቃሚ ባሕላችን፥ ወግና ሥርዓታችን ነው ያልተበረዘው!? የትኛውን ምርት ነው ኢትዮጵያ አምርታ ለሕዝቦቿ አድርሳ ለውጭ ሐገራት ኤክስፖርት አድርጋ ያየነው!? አሁን የምንጠቀማቸው አብዛኞቹ ምርቶች እኛን ይገልጻሉ!? በማን ይሰራሉ!? የትኛው ፖለቲካዊ ሥርዓት ነው የቀደምት ኢትዮጵያውያንን ከሰማይ የወረደ የመንግሥት ሥርዓትን የሚገልጽ!? ...... ብቻ እናውራ ከተባለ ችግሮቻችን ብዙ ናቸው። 📌 ኢትዮጵያ በታሪክ ዘመኗ ብዙ ጦርነቶችን አካሄዳለች፤ ለምን በምን ምክንያት ይህ ሁሉ ጦርነት ሚለውን እናንተው መርምሩት። ለማጋነን ባይሆንም ሁሉንም በሚባል ደረጃ ድል አድርጋለች፤ ምክንያቱም ኢትዮጵያ ካሏት ሰባቱ ሐብታት ውስጥ አንዱ በረከተ ይሁዳ ከነምልክቱ ነውና መዊአ ፀር(ጠላትን ድል መንሻ ኃይል) ከእግዚአብሔር ዘንድ ተሰጧታል። ጠላት ቢነሳም ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ስለምታደርስ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ዛሬም ነገም ሁሌም ያሸንፋሉ!!! 📌 በዚህ ዓመት 126ኛ የአድዋ ድል በዓል ነውና እስቲ ከዳዊት መዝሙር 126ን ልድገም ብየ ስደግም እንዲህ ሚል ቃል አገኘሁ ' እመ እግዚአብሔር ኢዐቀበ ሀገረ፤ ከንቱ ይተግሁ እለ ይኄልዉ' ትርጉሙም ' እግዚአብሔር አገርን ካልጠበቀ፤ ጠባዊ በከንቱ ይተጋል' ይላል። መዝሙረኛው ልክ ብሏል፤ የአድዋ ድል የመጣው በሰዎች በአንድነት ዋ! ብሎ በመነሳት ብቻ አይደለም፤ አድዋን ስናስብ የእግዚአብሔርን ጠባዊነትና ቃልኪዳን፣ የቅዱስ ጊዮርጊስን ፍጡነ ረድኤትነት፣ የካሕናቱን፣ በዘመኑ የነበሩ ሰዎችን እንዲሁም የነገሥታቱን የአጼ ሚኒልክንና የእቴጌ ጣይቱእምነት መርሳት እንደሌለብን ቃሉ መከረኝ! 📌 በአጠቃላይ አድዋን ሳስብ ክብር፥ ደስታ ሲሰማኝ፤ አሁን ያለንበትን ሁኔታ ሳስተውል ደግሞ አዝናለሁ። መጀመሪያ ወደ ራሳችን እንመልከት፣ እንደ አባቶቻችን በእምነት እንጽና፣ በእውቀት በማስተዋልና በጥበብ እንታደስ፤ ከዚያ ሌላው ነገር ይሰጠናል። እላለሁ። 🙏🏽 አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር አሁንም የኢትዮጵያና የቤተክርስቲያን ጠላቶች የሚዋረዱበት፤ ኢትዮጵያዊነት እንዲሁም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመንፈስ ቅዱስ ልጅነት የሚለመልሙበት ዘመን ያድርግልን። 📌 እንኳን ለ126ኛው የአድዋ ድል በዓል አደረሳችሁ፤ አደረሰን! 👉🏻 ከተማራችሁበት #ሼር በማድረግ ለሌሎች አጋሩ! የካቲት 23 2014 ዓ.ም ✍🏾ተጻፈ በኃይለሚካኤል ደሣለኝ። ቻናል- @EthiopeTowoderos

📌 እንኳን ለታላቁ ዐቢይ ጾም አደረሳችሁ፤ አደረሰን! 👉 ጾሙን ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ፣ ስለ ቤተክርስቲያን፣ ስለ ዓለም ሕዝብ ሁሉ የምንጸልይበት ወደ እግዚአብሔር የምናሳስብበት፣ በምጽዋት በፍቅር በመተሳሰብ የምንረዳዳበት የበረከት የንስሃ የማስቀደስና የመቀደስ ጾም ያድርግልን። እባካችሁ ጎሰኝነትን ፍጹም እንጸየፍ፤ ከአፈር የተሰራን የአዳም ልጆች ነን፤ ወደ አፈርም እንመለሳለን። ወዮ እናስታውል እናስብ፤ ስለ ራሳችን ስለ ወገኖቻችን እናልቅስ እናንባ፤ እስካሁን የበደልነው ይበቃል፤ ምንም ብንበድለው ያልተወንን ምሕረቱ የበዛ ሥሉስ ቅዱስን እናስብ😔፤ በኛ ኃጢአት ቢሆንማ በቆምንበት በተቀመጥንበት አፈር ሁነን እንቀር ነበር፤ አሁንም አስተውሉ ወዳጆቼ! 👉 ርኩሳን መናፍሥት የሚደቁበት በእግዚአብሔር ቃል የምንጸድቅበት ጾም ያድርግልን፤ ወገኔ ንቃ ርኩሳን መንፈስ ካወቅክበት ያጸድቁሃል አለዚያ ግን ያደቁሃል ውጊያችን ከነርሱ ጋር ነውና ቅዱሳን መላእክት ሁሉ እንዲጠብቁን የልዑል እግዚአብሔር ፈቃድ ይሁን። 👉 ይህ ሁሉ መዓት በዓለማችን በሀገራችን የሚሆነው በእኛው በደል ነውና ዳዊትም በመዝሙር 'አልቦ ዘይገብራ ለሠናይት አልቦ ወኢአሐዱ' እንዲል በአንድነት አምጸናልም መልካምም አልሰራንም፤ ስለዚህም ከኩተት እስከ ሽበት ያለውን ኃጢአትና በደላችንን ተናዘን ንስሃ ገብተን፣ ፍጹም በከበረ በጌታችን በመድኃኒታችን በአምላካችንም በኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም ለመቀደስ ያብቃን! በየለቱ የሚያለቅሱት፣ የሚያሳስቡት የሚጸልዩት የሚሰግዱት የቅዱሳን ጻድቃን ሁሉ በረከት በእውነት ይደርብን፤ የሰማዕታት እምነት እኛንም በሃይማኖታችን ያጽናን! እመ አምላክ እመ ሕይወት ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ልጇ ወዳጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ታማልድልን! ልዑል እግዚአብሔር በምሕረቱ ይጎብኘን! እኔንም በጸሎታችሁ አስቡኝ። በድጋሚ መልካም ጾም ይሁንልን፤ ይሁንላችሁ! ✍ ኃይለሚካኤል ደሣለኝ ነኝ። @EthiopeTowoderos

Channel Logo, Banner, Thumbnail, Intro, Outro, Book Cover Design... እንዲሁም ተጨማሪ ተያያዥ ሥራዎችን ማሰራት ከፈለጋችሁ አናግሩኝ። 📥INBOX - @HailemichaelDesalegn

📌 ሰላምታየ በያላችሁበት ይድረሳችሁ እያልኩ ንስር ዲዛይንና ፕሮሞሽን ለእርስዎ አዲስ ነገር ይዞ ብቅ ብሏል። 👉🏻 የChannel Logo 👉🏻 የYouTube, Facebook... ቻናል Banner 👉🏻 የYouTube ቪዲዮ ተምብኔል(Thumbnail) 👉🏻 የቻናል Intro, Outro... 👉🏻 የመጽሐፍ ከቨር ዲዛይን(Book Cover Design)፤ እንዲሁም ተያያዥ ሥራዎችን 🌄 ውብ በሆነ መልኩና በጣም በተመጣጣኝ ዋጋ እንሰራለን፤ ይህ ብቻም አይደለም የቴሌግራም ቻናል ፕሮሞሽን አገልግሎትና ስለ ሶሻል ሚዲያ ምክሮችንም በነጻ እንሰጣለን። 📥 ለማናገር፦ @HailemichaelDesalegn ✅ ከሥር ያሉትን ቻናሎችንም በመጎብኘት እውቀትን ይሸምቱ!

📌 እንኳን ለጾመ ነነዌ አደረሳችሁ! 👉🏻 ነነዌ የካም ዘር በሆነው በናምሩድ የተመሰረተች ታላቅ ከተማ ነበረች። በሆነ ጊዜም በዚህች ከተማ ይኖሩ የነበሩ ሕዝቦችም የክፋታቸው ጩኸት ወደ እግዚአብሔር ስለወጣ ልዑል እግዚአብሔር ወደ አሜቴር(አማቴ) ልጅ ወደ ነቢዩ ዮናስ ሰብኮ፥ መክሮና ገልጾ ከጥፋታቸው እንዲመልሳቸው መልክዕክት ላከ። 👉🏻 የነነዌ ሕዝብ ክፋት በዓለም ታሪክ እንደተመዘገበው ከሆነ ልዩ ልዩ ጣዖታትን በማምለካቸው ነው፤ እግዚአብሔርን ያስቆጡት የነበረ፤ በዘመናችንም እንደምታዩት ክቡሩ የሰው ልጅ ደም ለመናፍሥት በየቦታው ሲገበር እያየን ነው። 👉🏻 ነቢዩ ዳዊት በመዝሙር 13 እንዲህ ይላል፦ “ሰነፍ በልቡ እግዚአብሔር የለም ይላል በሥራቸው ረከሱ፤ ጎሰቆሉም። በጎ ነገርን የሚሠራ የለም። የሚያስታውል እግዚአብሔርንም የሚፈልግ እንዳለ ያይ ዘንድ። እግዚአብሔር ከሰማይ የሰው ልጆችን ተመለከተ። ሁሉ ዐመፁ፤ በአንድነትም ረከሱ። በጎ ነገርን የሚሠራ አንድም ስንኳ የለም።” 👉🏻 ዮናስ ግን ምሕረተ እግዚአብሔርን በማሰብ ከእውነት ራቀ፤ ወደ ተርሴስ(ኢትዮጵያ) ሊሸሽ ወደደ። ሁሉን ከሚያየው ከልዑል እግዚአብሔርም ፊት ኰብልሎ ይሄድ ዘንድ ወደ ተርሴስ ወደሚጓዝ መርከብ ገባ፤ ከዚያም እግዚአብሔር ፈታሂ ነኝ ሲል ነፋስን ላከባከው ማዕበልም ተነሳባቸው፤ እነሱም ዮናስ ከባሕር ከጣሉት በኋላ ባሕሩ ከመናወጡ ጸጥ አለ፤ ከእግዚአብሔር የታዘዘ ዓሣ አንበሪም ዮናስን ዋጠው፤የክርስቶስ ምሳሌ ይሆን ዘንድ 3 መዓልት 3 ሌሊት በከርሠ ዓሣ ውስጥ ቆየ።ከዚያም ዓሣ ነባሪው ዮናስን የብስ ላይ ተፋው። እግዚአብሔርም ዳግመኛ ዮናስን የመዠመሪያውን ስብከት እንዲሰብክ አዘዘው፤ እርሱም ወደ ነነዌ ሄዶ፤ “በሦስት ቀን ውስጥ ነነዌ ትገለበጣለች አለ።’’ 👉🏻 በሚገርም ሁኔታም ነነዌን በቀመረ ፊደል ስንመዝናት ነ+ነ+ዌ = 30 + 30 + 60 = 120 = 1+2+0 = 3ን እናገኛለን። የነነዌ ሕዝብ ግን ትንቢቱን ንቀው አላለፉትም፤ የጾም ዐዋጅ ነገሩ፣ ከታናሽ እስከ ታላቅ ማቅ ለበሱ፤የነነዌ ንጉሥም ይህንን ነገር በሰማ ጊዜ ከዙፋኑ ወርዶ ዘውዱን መጎናጸፊያውን አውልቆ ማቅ ለብሶ፤ከሰውም ከእንስሳትም እኅል እንዳይቀምሱ ውኃ እንዳይጠጡ ታውጆ ጾሙን በፈሪሃ እግዚአብሔር ጀምረው ፈጸሙ። እግዚአብሔርም ከክፉ መንገዳቸው እንደተመለሱ ሥራቸውን አይቶ፣ ሊያደርግባቸው ከተናገረው ክፉ ነገር አላደረገውም። ዳምኖ የነበረው ጥፋትም(እሳትም) ቀረ፤ ዲያብሎስም አቀረቀረ። 👉🏻 ስለዚህ እኛ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች የነነዌን ጾም ከሰባቱ አጽዋማት አንዷ ተደርጋ፤ ለበረከተ ሥጋ፣ለበረከተ ነፍስ ስለተስጠችን እንጾማታለን። “ ቁጣው ለጥቂት ጊዜ ነው፤ ሞገሱ ግን ለሕይወት ዘመን ነውና። ማታ ልቅሶ ይሰማል፤ ጥዋት ግን ደስታ ይሆናል” እንዲል መዝሙረኛው ዳዊት እኛም በዚህ ክፋታችን ጠፈር ነክቶ ባለበት ግዜ ይሄን ታሳቢ እንድናደርግ ለማሳሰብ እወዳለሁ። የነነዌ ሕዝቦችስ ከምግብና ኃጢአት ራሳቸውን አገለሉ፤ እኛ ግን ከኃጢአት ራሳችንን ማግለል እንኳ አቅቶናል። 👉🏻 ስላለንበት ግላዊ፣ ቤተክርስቲያናዊ፣ ሀገራዊ ሁኔታዎች ብዙ ጉዶችን ማለት ይቻል ነበር፤ ታውቁታላችሁ መፍትሔውም ንስሃ ጸሎት ስግደት ነው። ብቻ አንዳንዴ ብዙ ትንቢት ሲነገር እንሰማለን ግን ሳይፈጸም ሲቀር የኛ ነገር በተናገሩት አባቶች መሳለቅ ሆኗል፤ እስቲ አስታውሉ ከነነዌ ታሪክ ምሕረተ እንግዚአብሔርን በዋነኛነት እንማራለን፤ እኔ ትንቢትን ማንም ማን ተናገረው አልንቅም፣ እመረምራለሁ እንጂ፤ እስከአሁን የተነገረብን ትንቢቶችን ሁሉ ማን ያውቃል፤ እግዚአብሔር እንዴው በየቦታው ስለሚገኙ ዓለማዊ ሰው ብቻ መስለው መንፈሳዊ ስለሆኑት፣ እግዚአብሔር ጋር መላእክት ጋር ቅዱሳን ጋር... በየዕለቱ ጥብቅና ጥልቅ ግንኙነት ስላላቸው፣ ስለ ምስጢራዊዋ ኢትዮጵያ፣ዘመኑን አበጥረው ስለሚያውቁት ስለኃጢአትና በደላችን ስለሚያነቡት ቅዱሳን ሁሉ ብሎ ጸሎታችንን እየተቀበለ እስከዚህ የቆየን ይመስለኛል። 👉🏻 አሁንም የኢትዮጵያ ጋሻ የሆነው የቅዱሳን ጸሎት እንዳይለየን፣ እኛም ደግ ሰዎች እንድንሆን፣ ደጋጎች በደገኛ መሪ ከሚመሩበት ደግ ዘመን እንድንደርስ በነፍስም በሥጋም በረከትን እንድናገኝ፣ ልንጸልይ፣ ልንጾም፣ ልንበረከክ፣ ቅንነትና ፍቅርን ልናስቀድም ይገባል። መልካም ጾም! ✍🏾 ኃይለሚካኤል @EthiopeTowoderos

📌 እንኳን ለጾመ ነነዌ አደረሳችሁ! 👉🏻 ነነዌ የካም ዘር በሆነው በናምሩድ የተመሰረተች ታላቅ ከተማ ነበረች። በሆነ ጊዜም በዚህች ከተማ ይኖሩ የነበሩ ሕዝቦችም የክፋታቸው ጩኸት ወደ እግዚአብሔር ስለወጣ ልዑል እግዚአብሔር ወደ አሜቴር(አማቴ) ልጅ ወደ ነቢዩ ዮናስ ሰብኮ፥ መክሮና ገልጾ ከጥፋታቸው እንዲመልሳቸው መልክዕክት ላከ። 👉🏻 የነነዌ ሕዝብ ክፋት በዓለም ታሪክ እንደተመዘገበው ከሆነ ልዩ ልዩ ጣዖታትን በማምለካቸው ነው፤ እግዚአብሔርን ያስቆጡት የነበረ፤ በዘመናችንም እንደምታዩት ክቡሩ የሰው ልጅ ደም ለመናፍሥት በየቦታው ሲገበር እያየን ነው። 👉🏻 ነቢዩ ዳዊት በመዝሙር 13 እንዲህ ይላል፦ “ሰነፍ በልቡ እግዚአብሔር የለም ይላል በሥራቸው ረከሱ፤ ጎሰቆሉም። በጎ ነገርን የሚሠራ የለም። የሚያስታውል እግዚአብሔርንም የሚፈልግ እንዳለ ያይ ዘንድ። እግዚአብሔር ከሰማይ የሰው ልጆችን ተመለከተ። ሁሉ ዐመፁ፤ በአንድነትም ረከሱ። በጎ ነገርን የሚሠራ አንድም ስንኳ የለም።” 👉🏻 ዮናስ ግን ምሕረተ እግዚአብሔርን በማሰብ ከእውነት ራቀ፤ ወደ ተርሴስ(ኢትዮጵያ) ሊሸሽ ወደደ። ሁሉን ከሚያየው ከልዑል እግዚአብሔርም ፊት ኰብልሎ ይሄድ ዘንድ ወደ ተርሴስ ወደሚጓዝ መርከብ ገባ፤ ከዚያም እግዚአብሔር ፈታሂ ነኝ ሲል ነፋስን ላከባከው ማዕበልም ተነሳባቸው፤ እነሱም ዮናስ ከባሕር ከጣሉት በኋላ ባሕሩ ከመናወጡ ጸጥ አለ፤ ከእግዚአብሔር የታዘዘ ዓሣ አንበሪም ዮናስን ዋጠው፤የክርስቶስ ምሳሌ ይሆን ዘንድ 3 መዓልት 3 ሌሊት በከርሠ ዓሣ ውስጥ ቆየ።ከዚያም ዓሣ ነባሪው ዮናስን የብስ ላይ ተፋው። እግዚአብሔርም ዳግመኛ ዮናስን የመዠመሪያውን ስብከት እንዲሰብክ አዘዘው፤ እርሱም ወደ ነነዌ ሄዶ፤ “በሦስት ቀን ውስጥ ነነዌ ትገለበጣለች አለ።’’ 👉🏻 በሚገርም ሁኔታም ነነዌን በቀመረ ፊደል ስንመዝናት ነ+ነ+ዌ = 30 + 30 + 60 = 120 = 1+2+0 = 3ን እናገኛለን። የነነዌ ሕዝብ ግን ትንቢቱን ንቀው አላለፉትም፤ የጾም ዐዋጅ ነገሩ፣ ከታናሽ እስከ ታላቅ ማቅ ለበሱ፤የነነዌ ንጉሥም ይህንን ነገር በሰማ ጊዜ ከዙፋኑ ወርዶ ዘውዱን መጎናጸፊያውን አውልቆ ማቅ ለብሶ፤ከሰውም ከእንስሳትም እኅል እንዳይቀምሱ ውኃ እንዳይጠጡ ታውጆ ጾሙን በፈሪሃ እግዚአብሔር ጀምረው ፈጸሙ። እግዚአብሔርም ከክፉ መንገዳቸው እንደተመለሱ ሥራቸውን አይቶ፣ ሊያደርግባቸው ከተናገረው ክፉ ነገር አላደረገውም። ዳምኖ የነበረው ጥፋትም(እሳትም) ቀረ፤ ዲያብሎስም አቀረቀረ። 👉🏻 ስለዚህ እኛ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች የነነዌን ጾም ከሰባቱ አጽዋማት አንዷ ተደርጋ፤ ለበረከተ ሥጋ፣ለበረከተ ነፍስ ስለተስጠችን እንጾማታለን። “ ቁጣው ለጥቂት ጊዜ ነው፤ ሞገሱ ግን ለሕይወት ዘመን ነውና። ማታ ልቅሶ ይሰማል፤ ጥዋት ግን ደስታ ይሆናል” እንዲል መዝሙረኛው ዳዊት እኛም በዚህ ክፋታችን ጠፈር ነክቶ ባለበት ግዜ ይሄን ታሳቢ እንድናደርግ ለማሳሰብ እወዳለሁ። የነነዌ ሕዝቦችስ ከምግብና ኃጢአት ራሳቸውን አገለሉ፤ እኛ ግን ከኃጢአት ራሳችንን ማግለል እንኳ አቅቶናል። 👉🏻 ስላለንበት ግላዊ፣ ቤተክርስቲያናዊ፣ ሀገራዊ ሁኔታዎች ብዙ ጉዶችን ማለት ይቻል ነበር፤ ታውቁታላችሁ መፍትሔውም ንስሃ ጸሎት ስግደት ነው። ብቻ አንዳንዴ ብዙ ትንቢት ሲነገር እንሰማለን ግን ሳይፈጸም ሲቀር የኛ ነገር በተናገሩት አባቶች መሳለቅ ሆኗል፤ እስቲ አስታውሉ ከነነዌ ታሪክ ምሕረተ እንግዚአብሔርን በዋነኛነት እንማራለን፤ እኔ ትንቢትን ማንም ማን ተናገረው አልንቅም፣ እመረምራለሁ እንጂ፤ እስከአሁን የተነገረብን ትንቢቶችን ሁሉ ማን ያውቃል፤ እግዚአብሔር እንዴው በየቦታው ስለሚገኙ ዓለማዊ ሰው ብቻ መስለው መንፈሳዊ ስለሆኑት፣ እግዚአብሔር ጋር መላእክት ጋር ቅዱሳን ጋር... በየዕለቱ ጥብቅና ጥልቅ ግንኙነት ስላላቸው፣ ስለ ምስጢራዊዋ ኢትዮጵያ፣ዘመኑን አበጥረው ስለሚያውቁት ስለኃጢአትና በደላችን ስለሚያነቡት ቅዱሳን ሁሉ ብሎ ጸሎታችንን እየተቀበለ እስከዚህ የቆየን ይመስለኛል። 👉🏻 አሁንም የኢትዮጵያ ጋሻ የሆነው የቅዱሳን ጸሎት እንዳይለየን፣ እኛም ደግ ሰዎች እንድንሆን፣ ደጋጎች በደገኛ መሪ ከሚመሩበት ደግ ዘመን እንድንደርስ በነፍስም በሥጋም በረከትን እንድናገኝ፣ ልንጸልይ፣ ልንጾም፣ ልንበረከክ፣ ቅንነትና ፍቅርን ልናስቀድም ይገባል። መልካም ጾም! ✍🏾 ኃይለሚካኤል @EthiopeTowoderos

📈 ንስር ፕሮሞሽን 📌 ንስር ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች ውስጥ፦ ✅ በነጻ የምንሰራቸው፦ 👉🏻 የቴሌግራም ቻናል ፕሮሞሽን(Channel Promotion) 👉🏻 ቻናሎን እንዴት ማሳደግ እንደሚችሉ እንዲሁም በሶሻል ሚዲያ መልካም ነገርን በምን መልኩ ማቅረብ እንዳለብዎት፣ ስለ ቻናልዎት... ማስተካከል ያለብዎትን ነገሮች በጠቅላላ ምክር እንሰጣለን። ✅ በተመጣጣኝ ዋጋ የምንሰራቸው፦ 👉🏻 የChannel Logo 👉🏻 የYouTube, Facebook... ቻናል Banner 👉🏻 የYouTube ተምብኔል(Thumbnail) 👉🏻 የቻናል Intro, Outro... 👉🏻 የመጽሐፍ ከቨር ዲዛይን(Book Cover Design) እንዲሁም እንደፈቃድዎ ተጨማሪ ሥራዎችንም ምንሰራ ይሆናል። 📌 ማሳሰቢያ፦ 🤜🏽 ለTelegram Promotion ቻናል ለማስመዝገብ ሲፈልጉ ብቻ በ @Eaglepbot ያናግሩን። 🤜🏽 ለሌሎች ሥራዎች(Logo,Thumbnail,Banner...) ደግሞ በግል አካውንቴ በ @HailemichaelDesalegn ያናግሩኝ። 🤜🏽 የእግዚአብሔርን ሰላምታ ከሰጣችሁ በኋላ ቀጥታ ወደ ጉዳያችሁ አምሩ። 🤜🏽 ቻናላችሁ አልያም የምታሰሩት ነገር ትውልድን፣ ሀገርን፣ ሃይማኖትን ሚበክል እንደሆነ ካመንኩበት እኔጋ ከምክር ውጭ ከላይ የተዘረዘሩትን ሥራዎች አታገኙም። ሶሻል ሚዲያን ለመልካም በመጠቀም፣ መልካም አስተሳሰብንና ስብዕናን እንመስርት! ✍🏾 ኃይለሚካኤል ደሣለኝ(@HailemichaelDesalegn) ነኝ፤ መልካሙን ሁሉ ተመኘሁላችሁ። Channel = @EaglePromo1

የመጽሐፍት ጥቆማ! የዝጋለ አያሌው መጻሕፍት በኔ እይታ! 👉 ይህ ደራሲ ለዚህ ትውልድ ከዚያም አልፎ ተርፎ ለቀጣዩ ትውልድ አዲስ ዕይታዎችንና አስተሳሰቦችን ይዞ ብቅ ብሏል። 👉 በቅርቡ ታትመው ለንባብ ከበቁ መጻሕፍቶቹ መካከል፦ 1 - ገነት በኢትዮጵያ ናትን? ከበርባሮስ እስከ ሃኖስ 2 - ገነት በኢትዮጵያ ‹ጓሮ› ናትን? ከኤረር ተራራ እስከ ሰማያዊ ኤረር 3 - ዘዌ ሲሆኑ እንዲሁም በቅርቡ ‘መክኑን በትር’ የሚል መጽሐፉን ለንባብ እንደሚያበቃ ተናግሯል። 📌 በመስከረም ወር 2013 ዓ.ም ለንባብ በበቃው “ ገነት በኢትዮጵያ ናትን? - ከበርባሮስ እስከ ሃኖስ ” በሚል መጽሐፉ ውስጥ ብዙ ጥያቄዎችን ጠይቆ መልሶችንም ጠንቅቆ በምክንያታዊ ማስረጃም አርቅቆ አስረድቷል። መጽሐፉንም በጥያቄ ጀምሮ በጥያቄ ጨርሷል። 📌 ብቻ ለእኔ ይህ መጽሐፉ ልዩ ነበር፤ ስለምን ብትሉ ከራስ በጀመረ ምክያታዊ ምርምሩ ነው። መላእክት በዕለተ እኁድ ካለመኖር ወደ መኖር እንደመጡ መጀመሪያ የጠየቁት ጥያቄዎችን ነበር፤ ማን ነን? ከየት መጣን? ማን አስገኘን? ብለው ነበር፤ ትዕግስትን ገንዘብ አድርገው የጠየቁትም ብርሃን በላያቸው ሲመላ ብርሃኑ እውቀት ሆኗቸው በፍጹም ምስጋና አመስግነዋል። 👉 እኛም ከዚሁ ትምህርት ልንወስድ ይገባናል፤ ጥያቄዎችን መጠየቅ፣ መልሱንም በትዕግስት መፈለግ ይገባናል ብዬ አምናለሁ። 👉 ‘ገነት በኢትዮጵያ ናትን?’ መጽሐፍ በ21 ምዕራፎችና በ298 ገጾች የተከፈለ ሲሆን ከዳሰሳቸዉ አርዕስቶች ውስጥ፦ 💥 ስለ ገነት መገኛ ፍንጭ የምትሰጠው ዕፀ ለባዊት ተብላ ስለምትጠራው ዕፅ ምስጢር፤ ይህች የወንድና የሴት ፆታ ስላላት ዕፀ ለባዊት ተፈጥሮ፣ ዝርያ፣ መገኛ ታትቷል። 💥 ስለ መሴ የመሬት ዕርስት መነፈግ ምክንያት፣ እንዴትና ማን እንደቀበረው፣ 💥 በተፈጠሩበት ቦታ ምንም ሳይንቀሳቀሱ ስለቀሩ ፍጡራን፤ በተጨማሪም ተረፈ ምግብና ተረፈ መድኃኒትነት የሚያገለግሉ ዕፅዋት ዝርዝር በኢትዮጵያ በሚል ርዕስ ጥናቶች ተቀምጠዋል። 💥 ስለ ሰባቱ ሰማያት መገኛ፤ አስራ ሁለቱ ዞዲያክ ኮከቦች ምንነታቸውና ጥልቅ ምስጢራቸው 💥 ክርስቶስ ያስነሳው አልዓዛር መቃብር መገኛ ቦታ፤ እስራኤል? ወይስ ኢትዮጵያ? 💥 ከዘንዶ ራስ ላይ ጤፍ መቼ፣ የትና እንዴት እንደበቀለች 💥 ከዓለም ተደብቀው የሚገኙት ግሩማን ብሔሞትና ሌዋታን የት እንደሚገኙ እንዲሁም አቡነ ዘርዓ ብሩክ የት አግኝተው ጥርሳቸውን ቆጥረው እንዳስታረቋቸው፤ በሃገራችን በገጠራማው ስፍራ ‘ጦሮ’ ስለሚባለው አውሎ ነፋስ መነሻ ምክንያት፤ 💥 እንዲሁም ጅራታቸው የሚገኝበትን ውኃ ውጮቹ ሊመጡት ብለው ይሄን ካደረግን ዓለም ትጠፋለች ብለው ሁሉንም በምስጢር ይዘው እንደሄዱ በሚገርምና ሁላችሁም በምትደነቁበት ሁኔታ ተዳሷል። 💥 የዳይነሰር መጥፊያ ምክንያት፤ ከ290 ሚሊዮን ዓመት በፊት ጠፋ? ከገነት ጋር አብሮ ተሰወረ? ከሰማይ በተወረወሩ ከዋክብት ጠፋ? ወይስ በረሃብ አልያም በሌላ ፍጥረት ጥቃት ጠፋ? የሚለው በአጭሩ ተዳሷል። 💥 የፀሐይና የጨረቃ ግርዶሽ እውን ሊከሰት ይችላል ወይስ አይችልም? 💥 ገነትና አዳም በኢትዮጵያ ጎጃም ያስቀመጧቸው እውነታዎች፤ጎጃም አራራት ተራራ ስለሚገኘው የኖኅ መቃብርና የኖኅ ትውልድ ከተሞች እንዲሁም እግዚአብሔር በኢትዮጵያው ደብረ ዘይትና ናዝሬት ስለማስተማሩ 💥 አዳም በውኃ ውስጥ አርባ ቀን ከጸለየ አዳም(ሰው) አሳ ነውን? 💥 ገነት በሄኖክ፣ በኩፋሌና በዓለም አቀፍ ምሁራን እይታ 💥 ዓባይና ጣና ለ5000 ዓመታት ያልተቀላቀሉበት ድንቅ ምስጢር 💥 ገነት በኢትዮጵያ ጉያ! 👉 እኒህን ብቻም አይደለም፤ በውስጡ ብዙ ምስጢራትን ይዟልና አንብቡት። 📌 ‘ እኔ መጽሐፍ እንደጻፍኩ አልቆጥረውም፣ ጥያቄዎችን ነው የጠየቅሁት፤ ለእያንዳንዱ ጥያቄም ምክንያታዊ መልሴን አስቀምጫለሁ፤ ነገር ግን የተሻለ ምክንያታዊ መልስ ያለው ካለ ይምጣ እንከራከር፣ እንመካከር’ ይላል ወጣቱ ደራሲ። 👉 እኔ ከመጽሐፉ ተምሬ ተመካክሬበታለሁ፤ እናንተም መጽሐፉን ገዝታችሁ በማንበብ ጭንቅላታችሁን እንዲጠይቅ አድርጋችሁ አዘጋጁት፣ በእውቀትና በማስተዋል ተራቀቁበት። “ ገነት በኢትዮጵያ ናትን? ከበርባሮስ እስከ ሃኖስ በዝጋለ አያሌው 2013 ዓ.ም” እንዲ ተዳሷል። 2ኛ መጽሐፉን በሌላ ጊዜ የምዳስስላችሁ ይሆናል። ✍ ኃይለሚካኤል ደሣለኝ ነኝ። ለአስተያየት - @HailemichaelDesalegn 📌 መጽሐፉን በገበያ ላይ ታገኙታላችሁ፤ ካጣችሁት ከላይ ባለው አስተያዬት መስጫ አልያም ግሩፑ ላይ በኩል አሳውቁን። ቻናል - @EthiopeTowoderos

📉 ከ43 ቀን በኋላ በYou Tube እንደገና ብቅ ብያለሁ፤ እነሆ አዲሱ ቪዲዮ ይሄው ። 📈 ፍቅር - ከዚህ ቪዲዮ በኋላ መንፈሳዊ ሕይወታችሁ በቀላሉ ይቀየራል። በዚህ ቪዲዮ፦ ፍቅርና መንፈሳዊ አንድምታዉ በበቂ ሁኔታ ተዳሷል። ፍቅር ምንድን ነው? በስንት ይከፈላል? ባሕርዩስ? ምንስ ይጠቅመኛል? ለሚሉት ጥያቄዎች መልስ ይሰጣል። 👇🏽👇🏽👇🏽 https://youtu.be/FhN-h3TEbX4