EECMY - School (online class)
Open in Telegram
This channel is created with the thought of teaching students by supplying important files. Please pay attention.
Show more487
Subscribers
No data24 hours
+17 days
+230 days
Posts Archive
ትምሕርት ቤታችንን በተለያየ መንገድ መደገፍ ለምትፈልጉ በእንጦጦ ወንጌላዊት ት/ት ቤት ሥም በብርሐን ባንክ በተከፈተው የሒሣብ ቁጥር
1600600040146 ገቢ ማድረግ እንደምትችሉ በአክብሮት እንገልፃለን ፡፡
ት/ቤቱ
1600600040146 Berhan Bank
EECMY congregation
Entoto Wongelawt School,Any suuport will provide for school promotion .
Use mentioned account for any support .
በ2016 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና/ሚኒሥትሪ/ ለተፈተናችሑ ተማሪዎች በሙሉ
የሚኒሥትሪ ውጤት መግለጫ ካርድ ሥለመጣ በስራ ሰአት በመገኘት ከትምሕርት ቤታችን እንድትወስዱ ይሑን፡፡
ት/ቤቱ
ለአንጦጦ ወንጌላዊት ት/ቤት
ተማሪዎቻችን በሙሉ
የ2017ዓ.ም.ትምህርት አንደኛውን ሣምንት ልክ እንደከረሜላ በሚጣፍጥ መልኩ በማጣጣም ጀምረናል በዚሁ በተነቃቃ ሞራል በሚቀጥለው ሣምንት ከመስከረም 13/2017 ዓ.ም.አንስቶ መደበኛው ትምህርት ቀኑን ሙሉ እስከ 9:45 ሰዓት ድረስ መሆኑን በድጋሚ በፍቅር እናሳውቃለን ።
እግዚአብሔር አምላካችንም በሥራችን ሁሉ ጣልቃ ገብቶ እንደሚረዳን ሙሉ እምነታችን ነው!!! መልካም የትምህርት ዓመት ይሁንልን !!!
ከአቶ ኃ/ማ
መምህርነት የሙያዎች ሁሉ አባት!!
****
መምህራን ትውልዱን ከአለማወቅ ወደ ማወቅ ከጨለማ ወደ ብርሐን የሚመሩ የእውቀት አባቶች ናቸው፡፡ በዚህም የተነሳ መምህራን የአለም የእውቀት ብርሐን ሲባሉ እናዳምጣለን!! እውነትም መምህራን የአለም የእውቀት ብርሐን ናቸው፡፡
ዛሬ በሳይንስና ቴክኖሎጅ የበለጸጉት ሀገራት የእድገት ሚስጢር ትምህርት ላይ ትኩረት አድርገው መስራታቸው እንደሆነ ታወቆ ያደረ ሀቅ ነው፡፡ ትምህርት ማለት የሰው ሀብትን ዘመናዊ በሆነ መንገድ ማልማት ነው፡፡ በሰው ሀብት ልማት ሂደቱ ዋናው ተዋናይ ደግሞ መምህራን ናቸው፡፡ መምህራን በትምህርት ስርዓት ውስጥ ወሳኝ ሚና የሚጫወቱ ቁልፍ ተዋናዮች ናቸው፡፡ የተማሪዎችን ትምህርት እና እድገት ላይ በተለያዩ መንገዶች ተጽእኖ ያሳድራሉ፡፡ በዓለምም ሆነ በአገራችን ትልልቅ ቦታ ላይ የደረሱ ተመራማሪዎች፣ ፖለቲከኞች፣ ምሁራን፣….በትምህርት ዓለም ያለፉ በሙሉ በመምህራን ተኮትኩተው ያደጉና የተመከሩ ሳይንስን ከተግባር ጋር አዋህደው እንዲያውቁ የታገዙ ናቸው፡፡ በመሆኑም መምህርነት የተከበረና የተወደደ ሙያ እንደመሆኑ መጠን ለሙያዉና ለሙያ አባቶች ክብርና ድጋፍ ማድረግ የሁሉም አካል እንዲሆን ሁላችንም መስራት ይጠይቀናል፡፡ ምክንያቱም፡-
* መምህራን የመማር አመቻቾች ናቸው፡፡ መምህራን አሳታፊ እና interactive ትምህርቶችን በመፍጠር የተማሪዎችን የመማር ሂደት የሚመሩ ናቸው። መምህራን ተማሪዎች ውስብስብ ፅንሰ ሀሳቦችን እንዲረዱ እና ሂሳዊ አስተሳሰብን(Critical thinking)እንዲያዳብሩ ያበረታቷቸዋል፤ ይረዷቸዋል።
* መምህራን አማካሪዎች እና አርአያዎች ናቸው፡- መምህራን እንደ አማካሪ ሆነው ለተማሪዎች ድጋፍ ያደርጋሉ ፡፡ ለተማሪዎች ማበረታቻ ይሰጣሉ፡፡ተማሪዎች ሊከተሏቸው የሚገቧቸውን ባህሪያትን፣ አመለካከቶችን እና እሴቶችን ሞዴል ሆነው ያሳያሉ ይመክራሉ፡፡
* መምህራን የሂደት ገምጋሚዎች ናቸው፡፡ መምህራን የተማሪውን ግንዛቤ በግምገማ ይለያሉ፤ በዚህም ተማሪዎች እንዲሻሻሉ የሚያግዝ አስተያየት ይሰጣሉ። መምህራን የግለሰቦችን ፍላጎቶች ለማሟላት ለውጥ ተኮር መመሪያዎችን ይከተላሉ፡፡ በሂደቱ የሚያጋጥሙ እንቅፋቶችን ይቀርፋሉ፡፡ ሁልጊዜም ለለውጥ ይዘጋጃሉ፡፡
* መምህራን የስርዓተ ትምህርት ዲዛይነሮች ናቸው፡፡ መምህራን ብዙውን ጊዜ ሥርዓተ ትምህርቱን በመንደፍ፣ ቁሳቁሶችን በመምረጥ እና የተማሪዎቻቸውን ፍላጎት ለማሟላት ይዘቶችን መርጠው ለተማሪዎች በሚመጥን መንገድ ያቀርባሉ
*መምህራን ለተማሪዎቻቸው ተሟጋቾች ናቸው፡፡ መምህራን የተማሪዎቻቸውን ፍላጎት በትምህርታዊም ሆነ በግል ለማሟላት ያለእረፍት ይሰራሉ። ሁሉም ተማሪዎች በትምህርታቸው ውጤታማ የሚሆኑበትን መንገድና አካባቢ ለመፍጠር ይተጋሉ። አማራጭ መፍትሔዎችንም ይፈልጋሉ፡፡
*መምህራን ለተማሪዎች መማር ተባባሪዎች ናቸው፡፡ መምህራን የትምህርት ስራን ለማጎልበት ከስራ ባልደረቦቻቸው ፣ ከወላጆች እና ማህበረሰቡ ጋር በቅርበት ይሰራሉ። ይህም በመሆኑ ትምህርት ቤቱን ከማህበረሰቡ ጋር በማቆራኘት ለመማር ማስተማሩ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራሉ፡፡
*መምህራን የዕድሜ ልክ ተማሪዎች ናቸው፡፡ መምህራን ችሎታቸውን እና እውቀታቸውን ያለማቋረጥ ለማዘመን አንባቢዎች ናቸው፡፡ ይህ ባህሪያቸው ተማሪዎቻቸው ከክፍል ትምህርት በዘለለ ለትምህርት ከፍተኛ ዋጋ እንዲሰጡ ያነሳሳቸዋል።
በአጠቃላይ መምህራን የትምህርትን ገጽታ በመቅረጽ ረገድ አጋዥ ናቸው። የመምህራን ተጽእኖ ከአካዳሚክ ስኬት በላይ የተማሪዎችን የግል እድገት በማጎልበት እና ተማሪዎችን ለወደፊት ፈተናዎች በማዘጋጀት ረገድ የሚፈጥሩት ተጽዕኖ ከፍተኛ በመሆኑ ለትውልዱ መማር ያላቸውን ሚና ተረድተን ሁላችንም መምህራንን ማክበርና መንከባከብ ይገባናል፡፡
ለመምህራን ክብር እንስጥ!!
ለተከበራችሑ ወላጆች/አሣዳጊዎች በሙሉ
ከቤተሠብ ጋር ወደትምህርት ቤት የሚመጡና የሚመለሡ ተማሪዎች ደሕንነት ሢባል ትምሕርት ቤቱ ያዘጋጀውን የተማሪ መታወቂያ በመረከብ የሥም ዝርዝራችሑን እና ሥልክ ቁጥር እንድተሠጡ እየጠየቅን በቀጣይም ተማሪዎቹ ከትምህርት ቤት ግቢ የሚወጡት የተማሪውን መታወቂያ ይዞ ከመጣ አካል ጋር ብቻ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
በተጨማሪም በሰርቪሥ የሚሔዱ ተማሪዎችም የተሽከርካሪውን የሠሌዳ ቁጥር ለትምህርት ቤቱ እንድትሠጡ በአክብሮት እየጠየቅን ይሕ ሣይሆን ቀርቶ ለሚፈጠረው ችግር ወላጅ/ አሣዳጊ ሐላፊነቱን የሚወስድ መሆኑን በትሕትና እንገልፃለን፡፡
ት/ቤቱ
ከመሥከረም 8-10 /2017 ዓ.ም ለመምሕራን የሚሠጥ ሥልጠና ሥለሚኖር ትምሕርት ግማሽ ቀን እስከ 6:45 ሠአት መሆኑን በአክብሮት እንገልጻለን፡፡
ት/ቤቱ
በዛሬው ዕለት በእንጦጦ ወንጌላዊት ቅድመ አንደኛ፡ አንደኛና መጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት የ2017 ዓ.ም የመማር ማሥተማር ሒደት አጀማመር የተበሰረ ሲሆን በተጨማሪም በዕለቱ :
1. በተማሪዎች የዲሲፒሊን መመሪያ
2. በሒሳብና እንግሊዝኛ ትምህርት ስትራተጂክ ዕቅድ ላይ ውይይት በማድረግ በነገው ዕለት በቀጥታ የመማር ማስተማሩ ሂደት እንደሚጀመር ለተማሪዎች በመግለፅና የመክፈቻ ፕሮግራሙ በደማቅ ሁኔታ ተጀምሮ በሰላም ተጠናቋል፡፡
የሥራ ጥሪ ማስታወቂያ ---የት/ቤታችን መ/ራንና አስተዳደር ሠራተኞች በሙሉ
ሰኞ መስከረም 06/2017 ዓ.ም.ለማክሰኞ መስከረም 07/2017 ዓ.ም.ት/ት መጀመር ምድረ-ግቢ የማስዋብና የማስተማር ቅድመ- ዝግጅት ተግባራትን ለማከናወን ሙሉ ቀኑን መደበኛ ሥራ ላይ ስለምንሆን በዝግጁነት ትገኙ ዘንድ በአክብሮት ከወዲሁ በጥብቅ አናሳስባለን። የሙስሊም በዓል ነገ እሁድ እንደሚከበር በቴሌግራምና በዜና መግለጫ ስለተለቀቀ ነው ስለዚህ ሰኞ የሥራ ቀን ነው። ከአቶ ኃ/ማ.
