1 211
Subscribers
No data24 hours
-27 days
+1330 days
Posts Archive
1 211
ውድ የሳዌአ ወላጆች/ ህጋዊ አሳዳጊዎች
ከ1ኛ እስከ 8ኛ ክፍል የተማሪዎች መማርያ መፅሀፍ ውስን ቁጥር ስለመጣ ከሰኞ ጀምሮ ስለሚሸጥ ት/ቤት በመምጣት መግዛት ምትችሉ መሆኑን ልናሳውቅ እንወዳለን፡፡
1 211
ለሳዌአ ተማሪ ወላጆች/ሕጋዊ አሳዳጊዎች በሙሉ
ከ 1ኛ -12 ኛ ክፍል ተማሪዎች የመዝጊያ ኘሮግራም ቀን ቅዳሜ ሐምሌ 12፣2017 ዓ.ም ይሆናል ።
👉ሐሙስ ሐምሌ 10 , 2017 ከ 1ኛ -4ኛ ክፍል አቅራቢ ተማሪዎች ቅዳሜ ሐምሌ 12፣ 2017 ዓ.ም ለሚከበረው የወላጆች ቀን ክብረ በዓል ልምምድ የሚያደርጉ መሆኑን ተገንዝባችሁ ለግማሽ ቀን ትምህርት ቤት ትልኳቸው ዘንድ በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡ በዚህ ቀን ተማሪዎች ለግማሽ ቀን ማለትም ከ1:00 ጀምሮ እስከ 6፡30 ሰዓት ብቻ ትምህርት ቤት ውስጥ ይቆያሉ፡፡
ማስታወሻ፡ ከ1ኛ -4ኛ ክፍል አቅራቢ ተማሪ ወላጆች ተማሪዎችን ቅዳሜ ሐምሌ 12፣ 2017 ዓ.ም ቀን ላይ ልጆቻችሁን እስከ ጠዋት 1፡30 ድረስ ባለው ጊዜ ት/ት ቤት ግቢ እንድታመጡልን በጥብቅ እናሳስባለን፡፡
👉 የተማሪዎች ሪፖርት ካርድ
የተማሪዎች ሪፖርት ካርድ የሚሰጠው እና ምዝገባ የሚካሔደው ከሰኞ ሐምሌ 14 እስከ ረቡዕ ሐምሌ 23 ቀን 2017ዓ.ም ባሉት ጊዜያት ውስጥ ነው፡፡ በነዚህ ቀናት ቀርበው ሪፖርት ካርዳቸውን የማይወስዱ ወላጆችና ተማሪዎች ለ2018 ዓ.ም የሚያደርጉት ምዝገባ እንዳልተጠናቀቀ እንደሚቆጠርና ለሚፈጠረው ማንኛውም ችግር ኃላፊነቱ የወላጆች እንደሚሆን ከወዲሁ እንገልፃለን፡፡
👉የክረምት ትምህርት
የክረምት ትምህርት ከሐምሌ 14 ቀን 2017ዓ.ም ጀምሮ ለአራት ተከታታይ ሳምንታት እንደሚቆይ ከወዲሁ ልናሳስብዎ እንወዳለን፡፡
የሳዌአ አስተዳደር!
1 211
Health Benefits of Spending Time with Family
1. Improves Mental Health
2. Helps Children Perform Well Academically
3. Lowers Risk Of Behavioral Problems
4. Boosts Self-Confidence
5. Helps Kids Learn Future Parenting Skills
6. Teaches Effective Conflict Resolution
7. Reduces Stress
8. Enhances Physical Health
ከቤተሰብ ጋር ጊዜ የማሳለፍ የጤና ጥቅሞች
1. የአእምሮ ጤናን ያሻሽላል።
2. ልጆች በአካዳሚክ ጥሩ ስራ እንዲሰሩ ይረዳል።
3. የባህሪ ችግሮች ስጋትን ይቀንሳል።
4. በራስ መተማመንን ይጨምራል።
5. ልጆች የወደፊት የወላጅነት ክህሎቶችን እንዲማሩ ይረዳቸዋል።
6. ውጤታማ የግጭት አፈታት ያስተምራል።
7. ውጥረትን ይቀንሳል።
8. የአካል ጤናን ይጨምራል።
1 211
Repost from N/a
👉👉👉ለሳውዝ ዌሰት አካዳሚ ተማሪዎች ወላጆች/ህጋዊ አሳዳጊዎች በሙሉ
ጉዳዩ፡ የ 2018 ዓ.ም የትምህርት አገልግሎት ክፍያን በተመለከተ ሁለተኛ ዙር የስብሰባ ጥሪ የሰአትና የቦታ ማስተካከያን ይመለከታል
የሳውዝ ዌስት ጀሞ ቅርንጫፍ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና መስጫ ማዕከል በመሆኑ እና ከመንግስት በተሰጠ መመሪያ መሰረት የስብሰባው ቦታ ወደ ላፍቶ ሳውዝ ዌስት አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ የተዘዋወረ መሆኑን እና የስብሰባው ቀን እሁድ ሰኔ 22፣2017 ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ መሆኑን እየገለፅን ወላጆች በዕለቱ በመገኘት የውይይቱ ተካፋይ እንድትሆኑ እናሳስባለን፡፡ ውይይቱ በእለቱ በተገኙ ወላጆች አማካኝነት የሚደረግና ውሳኔ የሚደረስ መሆኑን ተገንዝበው በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት በትምህርት ቤቱ ቅጥር ግቢ እንዲገኙ ከወዲሁ በጥብቅ እናሳስብዎታለን፡፡
የት/ቤቱ አስተዳደር
1 211
🔹የ8ተኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ
በአ.አ ከተማ አቀፍ የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ለመመልከት 👇መጠቀም ይችላሉ።
🔹https://aa.ministry.et/#/result
1 211
የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች የመጨረሻ ፈተናቸው ማክሰኞ እና ረቡዕ ስለሆነ ከሰኞ እስከ ረቡዕ ከትምህርት ቤት መቅረት የለባቸውም። አድሚሽን ካርድ ወይም መፈተኛ ካርድ ያልወሰዳችሁ ሰኞ እና ማክሰኞ የመጨረሻው ቀን ስለሆነ እንድትወስዱ እናሳስባለን።
1 211
Repost from Addis Ababa Education Bureau
የ6ኛና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና መስጫ ጊዜ ሰሌዳ ይፋ ሆናል፡፡
(ግንቦት 4/2017 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2017 የትምህርት ዘመን የ6ኛና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና መስጫ ጊዜ ሰሌዳን ይፋ ያደረገ ሲሆን በዚህ መሰረትም የ6ኛ ክፍል ሰኔ 10 ፣11 እና 12/2017 ዓ.ም ዓ.ም እንዲሁም የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ሰኔ 3 እና 4/2017 ዓ.ም የሚሰጥ ይሆናል፡፡
ከተማ አቀፍ ፈተናዉን ከ739 ትምህርት ቤቶች 80333 የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች በ192 የመፈተኛ ጣቢያዎች እንዲሁም ከ661 ትምህርት ቤቶች 71985 ተማሪዎች በ194 የመፈተኛ ጣቢያዎች የሚወስድ ይሆናል፡፡
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
1 211
ውድ የሳዌአ ወላጆች/ህጋዊ አሳዳጊዎች
የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል መፈተኛ ካርድ ( Admission Card) መስጠት ስለጀመርን ተማሪዎች ወይም ወላጆች የግንቦት እና የሰኔ የተከፈለበትን እንዲሁም የቅዳሜ ትምህርት የተከፈለበትን ደረሰኝ ይዛችሁ በመምጣት መውሰድ የምትችሉ መሆኑን ልንገልጽላችሁ እንወዳለን፡፡
