en
Feedback
ቆየት ቆየት ያሉ ሙዚቃዎች

ቆየት ቆየት ያሉ ሙዚቃዎች

Open in Telegram

እንደኔ ኦልድ ዘፈኖች ወዳጆች ኑ ከኔጋ ዘና በሉ @Riyit Join ይበሉቻናል ላይ full ዘፈኖች ያገኛል ደስ ያሉትን ዘፈን እየተገባበዝን ዘና ፈታ እንላለን ዘፈን የፈለጋችውትን ለመምረጥ @Heluuuu_bot ውድ የቻናላችን ተከታዮች ሀሳብ አስተያየት መስጠት ከፈለጉ እንዲሁም ለቻናላችን ማጋራት ሚፈልጉት ቆየት ያለ ሙዚቃ ካለ 👉 በነኚ በኩል ያግኙን @mark_sistu

Show more
Ethiopia2 732The category is not specified

📈 Analytical overview of Telegram channel ቆየት ቆየት ያሉ ሙዚቃዎች

Channel ቆየት ቆየት ያሉ ሙዚቃዎች (@riyit) is an active participant. Currently, the community unites 10 338 subscribers, ranking in the Other category and 2 732 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 10 338 subscribers.

According to the latest data from 04 December, 2024, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 285 over the last 30 days and by 5 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
እንደኔ ኦልድ ዘፈኖች ወዳጆች ኑ ከኔጋ ዘና በሉ @Riyit Join ይበሉቻናል ላይ full ዘፈኖች ያገኛል ደስ ያሉትን ዘፈን እየተገባበዝን ዘና ፈታ እንላለን ዘፈን የፈለጋችውትን ለመምረጥ @Heluuuu_bot ውድ የቻናላችን ተከታዮች ሀሳብ አስተያየት መስጠት ከፈለጉ እንዲሁም ለቻናላችን ማጋራት ሚፈልጉት ቆየት ያለ ሙዚቃ ካለ 👉 በነኚ በኩል ያግኙን @mark_sist...

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 05 December, 2024), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Other category.

10 338
Subscribers
+524 hours
+637 days
+28530 days
Posts Archive
#መቅደላዊት #ክፍል_54 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ባሩክ ኮስተር ብሎ ማይኩን ያዝ አደረገና " ለምንድነው ምታጨበጭቡት?" ብሎ ጠየቀ ነገር ግን የጠበቀው ለጠየቀው ጥያቄ ምላሽ ሳይሆን ሳቅ ነበር። ባሩክ ( ዲዮጋን )በቃ ለጥያቄ መላሽ አጥተው እና ጥያቂያቸውን መረዳት በማይችል ትውልድ መሀል የሚኖሩ ናቸው እንግዲህ ሳያብዱ በአበዱ ሰወች እብድ የሚባሉት ። " አለ እና " ለማንኛውም በዚህ ጉዳይ ሰፊ ሀሳብ ማንሳቴ ስለማይቀር እዚህ ላይ ልተወውና ስለ ተከበረው አድዋ ስለተከበረው የኢትዮጵያ ልጅ ስለ አስከበሩት ጀግኖች አርበኞች እንዲሁ ተወርቶ ባያልቅም ያቅሜን ያህል ግን የተወሰነ ልበል። If I have seen a little farther than others, it is because I have stood on the shoulders of giants.” (”ከሌሎች በላይ በጥቂቱ አሻግሬ ማየት ከቻልኩ፣ ምክንያቱ ሌላ ሳይሆን በነባሮቹ ግዙፋን ትከሻ ላይ በመቀመጤ ነው፡፡ " ብሏል ሰር አይዛክ ኒውተን ። ውድ ኢትዮጵያውያን ሆይ እንደምን በነፃነት እስከዚህ ደረሳችሁ ? ከላይ ከጠቀስኩት ከአይዛክ ኒውተን አባባል ጋር የሚመሳሰል ዘፈን የኔዋ ምሳሌ እጂግአየሁ ሽባባውም (ጂጂ) ያላት መሰለኝ ። "አድዋ" የሚለውን ድንቅ ዘፈኗ ሁሌም ሰምቼ የማልጠግበው ዘፈኗ ነው ሰው በሃሳቡ ይመዘናል፡፡ ሀሳብ ደግሞ ባሳቢው የማሰብ ዓቅም ልክ ይሰፈራል፡፡ ሰውን እንደኔ አላሰብክም ማለት አይቻልም ። አያቶቻችን ሀገርን በነፃ የማቆየት እና በነፃነት እንድንቆይ የሚደርግ ሀሳብ አስበው ወደ ጦርነት ባይሄዱ ኑሮ ዛሬ እንዲህ ቆመን በቋንቋችን ባልተግባባን ነበር። ታሪክ የግድ እኔ ከምፈልገው አቅጣጫ ካልሆነ በሚል አረዳድ፣ በታሪክ ላይ ብዥታዎች ሲፈጠሩ ተፈጥረው ኖረዋል ፡፡ አንዳንድ ኤሊቶች ላለፉት ብዙ አመታት በምኒልክ ዘመን ፓርላማ ለምን አልኖረም? ለምን ስማርት ፎን አልተሰራም :,ፌስቡክ ለምን አልተጀመረም ? ዩኒቨርሲቲ አልተገነባም? ? አርበኞች ለምን ጎራዴና ሰይፍ ይጠቀማሉ? ለምን ዲሞክራሲያዊ ምርጫ አልተደረገም ? የሚሉና የወቅቱን ነባራዊ ሁኔታ የማይገነዘቡ መሀይማን ጉዶች ነበሩ ሲያባሉን የነበሩ ማሰብ የሚችል አእምሮ ተሰጥቷቸው ሳይጠቀሙበት የነበሩ ሰወች ነበሩ። . አፄ ምኒልክ ከኢትዮጵያ ታሪክ ስሙ እንደ ሃመልማል ለምልሞ፣ ቅርንጫፉ በፍሬ የሞላው ለምንድነው? ብለን ስናስብ፣ በዘመኑ ያሳለፋቸው ጠንካራ ዱካዎች፤ በክፉና ደግ ቀን የወሰናቸው ጠንካራ ውሳኔዎች ውጤት መሆኑን እንገነዘባለን፡፡ ዝነኛው የታሪክ ተመራማሪ ጆን ማርካኪስ በመፅሀፉ አፄ ምንሊክ እ.ኤ.አ. በ1891....... “If power at a distance come forward to partition Africa between them, I do not intend to remain an indifferent spectator” (ኃያላን ከሩቅ መጥተው አፍሪካን ቢከፋፍሉ አያገባኝም የሚል ተመልካች መሆን አልፈልግም) በማለት ለአፍሪካ ብቻ ሳይሆን የአለምን ጥቁር ህዝብ አንገት ቀና እንዲል እንዳደረጉ ፅፏል። “National and Class Conflict in the Horn of Africa” ጆን ማርካኪስ ገፅ 145. እንደፃፈው ብለን ከተነሳን የአፄ ምኒልክ አስተዋፅኦ ተፅፎ የሚያልቅ አይደለም ። "WOW !!!! Emiye Menilik the pride of all Ethiopian and the entire black race. Every time i heard your name my eyes filled with tears and my heart warmed with pride. All generation of Ethiopian will always remember your monumental achievement in Adwa." ብሎ የተናገረው ደግሞ ከብዙ አመት በፊት ስለ ምኒሊክ ደግነት እና እናትነት ለጥቆ በቢሲ ላይ ቀርቦ የተናገረው ናይጀሪያዊው የጦር መሪ የነበረው enolans trondan ነበር። እንደው ለነገሩ ይችን አልኩ እንጅ ስለምኒልክ እና ስለ አያቶቻችን እንኳ የተናገሩት እልፍ ቢሆኑም ካለን በቂ ጊዜ አለመኖር የተነሳ ይችን ብቻ ካልኩ በቂየ ነው። በተረፈ ለእኔና ለአለም ጥቁር ህዝቦች እምዬ ምኒልክ ከሮሙ ጁሊየስ ሲዛር : ከግሪኩ አሌክሳንደር : ከአሜሪካው አብርሃም ሊንከን : ከጀርመኑ ቢስማርክ :ከእንግሊዙ ዌንስተን ቼርችል የሚበልጥ ልእለ ሰብ የሆነ መሪ ነው ። ለአንተ ግን ላይሆን ይችላል። ዋናው ነገር እንደ ፈረንሳዮቹ VIVE La difference - ልዩነት ለዘላለም ይኑር በማለት መተላለፍ ነው። በመጨረሻ ታሪካችን አድዋ ለዘላለም እንደ ሰንደቃችን እየሰቀልነው እየዘከርነው እንኖራለን ክብርና ጀግንነት ለእነሱ አመሰግናለሁ "፡፡ ብሎ ጨረሰ ሁሉም ቆመው አጨበጨቡለት ፈገግታ ፊቱ ላይ የማይጠፋው ጠቅላይ ምኒስትር ፕሮፌሰር ዮሐናን በአድናቆት ተመለከቱት የታደሙት ሁሉ በባሩክ አገላለፅ ተደነቁ እርስበርሳቸው የጎንዮሽ ማውራትን ተያያዙት። * መቅደላዊት ከአዳራሹ መግቢያ በኩል ሆና ባሩክን በፍቅር እና በስስት ትመለከተው ነበር ይቀጥላል .......... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 55♥️ ነገ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ክፍል_53 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ የአድዋ ዩኒቨርስቲ ሁለገብ አዳራሽ ገና ዝግጅቱ ከመጀመሩ በፊት አንድ ስአት ቀደም ብሎ አዳራሹ በሰው ሞልቷል የእለቱ ዲጄ ጂጂንና ቴዲ አፍሮን እያቀያረ ይከፍታል ። መድረኩ በአረንጓዴ ቢጫ ቀይ ሰንደቅ ዲኮር ተደርጓል። የስቴጁ መወጣጫ ደረጃ ተነጥፏል የአዳራሹ ግድግዳዎች በጥቅስ አሸብርቀዋል። " በእናንተ ሞት ኖርን ፣ በእያንዳንዱ ሰው ነፃነት ውስጥ የእናንተ ስም አለ፣ አጥንታችሁ እና ደማችሁ በከንቱ ወድቆ አይቀርም ፣ እናንተ የዚህ ዘመን ትውልድ ሻማ ናችሁ ፣በእናንተ ጀግንነት ጨለማውን አልፈን ንጋት ላይ ደረስን ፣ የአፍሪቃውያን ኩራት ፣ የተበዳይ ዳኞች ናችሁ ፣ ከስጦታ ሁሉ የሚልቅ የማንነት ስጦታ ሰጣችሁን ይሄው ቆመናል፣ እኛ ኢትጵያውያን ሁሌም በእናንተ ጀብድ በሄድንበት ተከብረን አለን፣ አንድነታችሁ የዛሬዋን ኢትዮጵያ እልፍኝ ሰራ፣ ክብርና ሞገስ ለእናንተ ለጀግኖቹ ቅድመ አያቶቻችን ፣ " የሚሉ በጣም ብዙ ጥቅሶች ተፅፈዋል። አብዝሀኛው ታዳሚ በጂጂ ሙዚቃ ተክዟል። የከፊሉ ገፅ ደግሞ የእምባ ርሷል። የሰው ልጅ ክቡር ሰው መሆን ክብር ሰው ሞቷል ሰው ሊያድን ሰውን ሲያከብር በደግነት በፍቅር በክብር ተጠርቶ በክብር ይሄዳል ሰው ሊኖር ሰው ሞቷል የተሰጠኝ ህይወት ዛሬ በነፃነት ሰው ተክፍሎበታልከደምና ከአጥንት። ስንቱ ወገን ወደቀ በነፃነት ምድር፣ ትናገር አድዋ ትናገር ትመስክር ትናገር አድዋ ትናገር አገሬ፣ እንዴት እንደቆምኩኝ ከፊታችሁ ዛሬ። በኩራት በክብር በደስታ በፍቅር፣ በድል እኖራለሁ..... የጂጂን ዘፈን በመድረክ መሪው የእጅ ምልክት መሠረት ዲጄው አቋረጠውና የእለቱ መድረክ መሪ ራሱን ለመድረኩና ለታዳሚው ካስተዋወቀ በኋላ የእለቱ መድረክ መሪው እጁ ላይ የያዛትን ብጣሽ ወረቀት እያነበበ መናገር ጀመረ። ዝግጅቱን በ8 ክፍል መድቦ እነሆ አለ እና ወደ መጀመሪያው ክፍል ወደ ክቡር ጠቅላይ ምኒስትር ፕሮፌሰር ዮሐናን መልከጼዴቅ እናመራለን በእሳቸው ንግግር የዛሬውን ፕሮግራማችን ይጀመራል። እባካችሁን እሳቸውን ወደ መድረክ ሸኙልኝ" አለ መድረክ መሪው ታዳሚው ለጥቅላይ ምኒስትሩ ቆሙ ፕሮፌሰር ዮሐናን ፈጠን ብለው ወደ መድረኩ ወጡና " የተከበራችሁ የአገሬ ልጆች በዚህ እለት በዚህ መሠረት በሆነ ቦታ ቆሜ ለማውራት እና ከእናንተ ወንድሞቼ እህቶቼ ጎን ሆኜ ይሄን የአያቶቻችን ጀግንነት ገድል ለመዘከር ከፊታችሁ በመቆሜ ክብርና ኩራት ይሰማኛል። ጨብጨብጨብ ሞቅ ያለ የታዳሚ ጭብጨባ አቋረጠው። ፕሮፌሰር ዮሐናን አሁንም ንግግራቸውን ከጭብጨባው ጋፕ በኋላ ቀጠሉ እና " ስለ እውነት ለመናገር እነሱ የመሯትን ሀገር መምራት እነሱ የመሩትን ህዝብ መምራት ምን ያህል መታደል እንደሆነ የማውቀው እኔ ነኝ። እኔም ዛሬ ይሄው በእናንተ በምወዳችሁ ወገኖቼ ፊት ቆሜ የማትመሩትን እየመራሁ በእናንተ ድጋፍ እና ሀሳብ ለሌላ ምዕራፍ ተዘጋጅቻለሁ። እንኳን ለ 150 ኛው የአድዋ የድል በዐል በሰላም አደረሳችሁ! እያልሁ በዓሉ ቀን የአያቶቻችን አንድነት ፍቅር ደግነት ይደርብን ለመለት እወዳለሁ። አመሠግናለሁ " ብለው ጠቅላይ ምኒስቴር ፕሮፌሰር ዮሐናን መልከጼዴቅ ንግግራቸውን ቋጩ። ሁሉም በአንድ ላይ ተነስተው አጨበጨቡ ፕሮፌሰሩ ወገባቸውን በደስታ ሰበር አድርገው ጭብጨባውን ተቀበሉ። መድረክ መሪው ማይኩን አንስቶ" ጠቅላይ ምኒስትሩ ላስተላለፉልን መልዕክት በእጅጉ እያመሰገንሁ አሁን ወደ ቀጣዩ የጥበብ ድግስ አመራችኋለሁ። የመጀመሪያው ፕሮግራም የሚሆነው ወግ ነው የሚያቀርብልን ደግሞ ክቡር ዶክተር ታሪኩ ወልደማርያም ይሆናሉ መድረኩን ለእርሳቸው እለቃለሁ ክቡራትና ክቡራን በድጋሚ እንኳን ለ150ኛው የጥቁር ልጅ ኩራት ለመላው ኢትዮጵያዊያን አንደበት ለሆነው የአድዋ የጀግኖች ድል በዐል ለነፃነት ቀን በሰላም አደረሳችሁ!" አለ እና መድረኩን በቀስታ ወረደ። ዶክተር ታሪኩ ወልደማርያም በአርባዎቹ መጀመሪያ የእድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ሲሆኑ ነገር ግን ለሚያያቸው የስልሳወቹ እድሜ ውስጥ እንደሆኑ ያስባቸዋል። ሽበት የፀጉር አናቱን ገና በጎልማሳነቱ ተቆጣጥሮት ነው ያለ እድሜው ሽማግሌ ያደረገው። የፍልስፍና እና የታሪክ ተመራማሪው ዶክተር ታሪኩ ወልደማርያም በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ማስተርሳቸውን ከያዙ በኋላ በተለያዩ የአለማችን ክፍል የተለያዩ ጥናታዊ ታሪኮችን በማቅረብ ገና በጎልማሳነታቸው አንቱታነትን አትርፈዋል።በፍቅር እና በፈገግታ ታዳሚውን እየተመለከቱ " በእውነቱ የሁላችንም እዚህ መገናኘት ምስጢሩ አድዋ መሆኑ የአያቶቻችን ጀግንነት መሆኑ በጣም ጥልቅ ነው። ድላችንን ነጮች ሳይቀሩ ያከብሩታል የታሪክ ባለቤቶቹን አያቶቻችንን ደግሞ በሚገርም አገላለጽ በየ ቋንቋቸው ፅፈው ለአለም አስነብበዋል። በዚህ እኛ ሙሉነታችንን አያሻማም ማለት ነው።በእናንተ እና በእኛ አንገት አንድ የጋራ ማተብ አለን እሱም አድዋ ነው። በኢትዮጵያ ታሪክ በጣም ብዙ ድሎች ተሰርተዋል። በጣም ብዙ ነገስታቶች ብዙ ነገር አድርገዋል ከዛሬ 50 አመት በፊትም ኢትዮጵያ በ80 ፌደራሊዝም እንድትተዳደር አንድነታችንን ለመበጠስ ብዙ መንግስታት ተንኮል ሸርበዋል። ያልተወከሉት ተወከልን ባዮች በኢትዮጵያ ምድር ብዙ ርዕዮት አምጥተው ለትንሽ ጊዜም ቢሆን እያከፋፈሉ ሀብታችንን እየተካፈሉ እኛን በባዶ ሜዳ እያጋደሉ መንበራቸውን ገፍተዋል።ነገር ግን እኛ በማይታይ ስር ስለተሳሰርን አንዳችን በአንዳችን ላይ ብንነሳም መቆማችን አልቀረም ቆመን ለእዚህ በቃን። ለዚህም ለክቡር ጠቅላይ ምኒስትር ፕሮፌሰር ዮሐናን አክብሮቴ ላቅ ያለ ነው። ሰው ሆነን ኢትዮጵያዊ እንድንሆን አድርጎናል።" አለ ዶክተር ታሪኩ ጭብጨባ አቀረጠው። ጭብጨባውን እስኪቆም ጠበቀና ጭብጨባው ሲቆም መናገሩን ቀጠለ። ዶክተር ታሪኩ ስለ አድዋ ታሪክ ብዙ ነገር አለ። ለአስር ደቂቃ ያህል በምስል የተደገፈ አጭር ዝክረ ታሪክ አድዋን ካስመለከተ በኋላ ጨረሰ እና ከመድረክ ሲወርድ ሁሉም ታዳሚ አጨበጨበለት። መድረክ መሪው ቦታውን ተረከበና ዶክተር ታሪኩን አመስግኖ በጣዩን የዝግጅት አቅራቢ ሲያስተዋውቅ እንዲህ አለ " አሁን ደግሞ በዚሁ በአድዋ ዩኒቨርስቲ የአራተኛ አመት የኤሌክትሪካል ምህንድስና ተማሪ የሆነውን ተማሪ ባሩክን ወደ መድረክ እጋብዛለሁ ተማሪ ባሩክ ወደ መድረክ " አለ ተማሪው በጭብጨባ አንድ ላይ " ዲዮጋን ዲዮጋን ዲዮጋን " አሉ ............ ይቀጥላል .......... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 54♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ክፍል_52 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ናታኔም ባሩክን እንዳየው ፊቱ ተለዋወጠ። አንዳች መጥፎ ስሜት ሰውነቱን ወረረው። ባሩክ ሰፍ ብሎ ሰላም ሊለው ሲመጣ ናታኔም ፊቱን ኮስኩሶ ትንሽ ከተመለከተው በኋላ ጀርባውን ሰጥቶት ወደ ታክሲዋ ገባ። ባሩክ በናታኔም ሁኔታ በጣም ደነገጠ ግራም ተጋባቶ ለተወሰነ ደቂቃ ባለበት ቆመ። ትንሽ ከቆመ በኋላ ናታኔም ወደተሳፈረባት ታክሲ አይኑን ሲልክ ተነስታ ሄዳለች። ቀስ አድርጎ አይኑን እያዞረ ወደ ጊቢ በዝግታ ተጓዘ። ሁኔታውን ለማጣራት ወደ መቅደላዊት ለመደወል ስልኩን አወጣ። ስልኩን ሁለት ጊዜ አዞራትና ሊደውል ብሎ ከእንደገና ተወውና ወደ ኪሱ መለሰ። " ምን አድርጌው ነው? ምን አጥፍቼ ይሆን እንዲህ በጣም የተናደደብኝ? ኧረ በጭራሽ ምንም ያደረኩት ነገር የለም ዝም ብሎ ነው ። አይ ደግሞ ዝም ብሎ እንዴት እንዲህ ይሆናል አይሆንም በእርግጠኝነት የሆነ ነገርማ ሆኗል።" አለ እና ባሩክ ራሱን መታ መታ አደረገው ።ከዛ እጁን ራሱ ላይ ለቀቅ አደረገና " ከመቅደላዊት ጋር ውጪ እንደነበርን ሰምቶ ይሆን? አወ በእርግጠኝነት ይሄ መሆኖ አለበት ።እህ ታዲያ እሷ ጋ ውጭ ብናድርስ እሱ ምን አገባው? አፍቅሯት ባልሆነ?. ሃሃሃሃ አገኘሁህ ናታኔም አፍቅሯታል። ለነገሩ እንዴት አያፈቅራት መቅደላዊት ጋር ብዙ ጊዜ አሳልፏል። በዛ ላይ መቅደላዊት የሚፈቀር ስብዕ የሚፈቀር ውበት ባለቤት ነች። ባያፈቅራት ነበር የሚገርመኝ! . እና ታዲያ እኔ በምን አውቃለሁ? ልጠረጥርበት የምችልበት መንገድ አልፈጠሩልኝም እሷም ሆነች እሱ . እሷ ደግሞ አትወደውም። ብትወደው ትላንት እንደዛ አይነት ታሪክ አንሰራም ነበር።እሷም ቢሆን እንደሚያፈቅራት አታውቅም። እና እኔ በምን አውቃለሁ። ቀድሞ ቢነግረኝ ምን አልባት ይሄን ነገር አላደርግም ነበር። ምንም እንኳ እሷን ብወዳትም! እ እ ወደደኋት እንዴ? ናሆም በሩ ጋ ሲደርስ ወደ ኋላ ዞረ ። ራሱን ነቀነቀ ። በፍጥነት ሲሄድ አንደኛው የዩኒቨርስቲው ጥበቃ " አንተ መታወቂያህን አታሳይም ? ብሎ አናገረውና አስቆመው ባሩክ ራሱን እንደመያዝ አድርጎ " ከምር ሀሳብ ውስጥ ስለነበርሁ ነው " አለና ከኪሱ አውጥቶ የተማሪነት መታወቂያውን አሳየ " አሁን መሄድ ትችላለህ እኔ ብቻ ስራየን ለመስራት ያህል ነው! " አለና ዘበኛው ሳቅ አለ ።ባሩክ ከልቡ ሳቅ ብሎ " አመሰግናለሁ በጣም " ብሎት ሄደ ። ብዙ ተማሪወች በሀሳብ ሲሞሉ እና በውስጣቸው የሚያብሰለስሉት ነገር ሲኖር ብዙ ጊዜ ከራሳቸው ተነጥለው ይታያሉ። አንድ ጊዜ እኔ ቆሜ ማታ ላይ ነው እና መታወቂያ እያሳዩኝ ተማሪዎች ይገባሉ። አንደኛው ሲመጣ ስልኩን እየጎረጎረ ይመጣና መታወቂያ ስለው ስልኩን አሳየኝ። ፌስቡክ እየተጠቀመ ነበር። ከሱ በኋላ የነበሩት ተማሪዎች በሳቅ ወደቁ ልጁ ጭራሽ ደንዝዞ ይቁለጨለጭ ጀመር። ከዛ አንደኛው ተማሪ" ነፍሴ ምነው ተመሰጥሽ ጥበቃው ያለሽኮ የአድዋ ዩኒቨርስቲ መታወቂያ ነው እንጅ የጠየቀህ የማርክዙከር በርግን መታወቂያ አይደለም የጠየቀህ! ምን ሆናሀል ደግሞ ቢጠይቅህ ቻት ውስጥ ያወራኸውን ልታሳየው ነበር እንዴ?" ብሎት ሁላችንም ሳቅን። በተለይ የፈተና ወቅት ካልሲ ማቀያየር አንዱ እግር ላይ ማድረግ ሌላኛው ላይ ደግሞ መርሳት እንዲሁም እስክርቢቶ ሳይዙ ፈተና ላይ መቀመጥ የተለመደ ነው። " አለው አጠገቡ ላለው የጥበቃ ጓደኛ " ልክ ነህ ጭንቀትና ሀሳብ አእምሯቸውን ስለሚያጨናንቀው እኮ ነው ።አትፍረድባቸው " አለ አንደኛው ጥበቃ። ናታኔም " ደግሞ ሰላም ሊለኝ ይፈልጋል እንዴ ያደረገውን አያውቅም። እሱን ቢሉ ፈላስፋ እሱን ቢሉ አስተዋይ ።አላውቀውም እንዴ ሰፈር አብዶ ማንም ከሱ ጋር ላለመሆን ሲርቅ ቃላት በማቀያየር እውቀት የሚገኝ መሰለው። ደግሞ እንደፃድቅ ፈገግ ብሎ ሰላም ሊለኝ ፈለገ የማይረባ ለነገሩ በቅርቡ እሰራለታለሁ ።እንዲህ እንደሰራልኝ እንደተጫወተብኝማ አይቀራትም ። መቅደላዊት እንደሆነች የተፈጠረችው ለእኔ ነው ።ለእሷ ማንኛውንም ዋጋ እከፍላለሁ ።ለእሷ ስል ምንም ማድረግ እችላለሁ። እሷ የእኔ እንድትሆን ሰይጣንን መብለጥም ካለብኝ እበልጠዋለሁ። አጠቃላይ ያሉኝን መንገዶች በሙሉ እጠቀማለሁ። ምክንያቱም እሷ ከእኔ ውጪ ለሌላ መሆን ስለማትችል!" በማለት አፉን እያንቀሳቀሰ አድዋ አደባባይ ላይ ወርዶ ወደ ግራ ታጠፈ እና ቀጥ ብሎ በእግሩ ትንሽ እንደሄደ አቢሲኒያ ባስ ቢሮ ገብቶ " ቲኬት ለመቁረጥ ነበር" አለ ናታኔም ቀላ ያለችው አስተናጋጅ " ወደ የት ነው የምትሄደው?" አለች " ወደ አዲስአበባ " አለ ናታኔም " እሽ ስምህን እና ስልክህን ንገረኝ " አለች ሁሉንም በተራ ከነገራት በኋላ 200 ብር ከፍሎ ትኬቱን ይዞ ወጣ። * መቅደላዊት ዘወርወር ብላ አንዳንድ ነገሮችን ከገዛች በኋላ መንገድ ላይ ቆማ ታክሲ እየጠበቀች ሳለ አንድ ሱቅ ላይ አይኖቿ ያርፋሉ ። ከዛ ወደ ሱቁ ሄዳ ስአቱን ተመለከተችው በጣም ያምራል" ስንት ነው? " አለችው " እሷ ቆንጆ ስአት ነች አዲስ ምርት ናት 450 ብር " አለ " መጨረሻ የለህም? " አለች መቅደላዊት ስአቷን በእጇ መዳፍ ላይ እንደያዘቻት " የመጨረሻ ከዛ የማይቀንስ 400 ብር ከዛ ውጪ አይቀንስም " አለ ። መቅደላዊት ስአቷ እጅግ ውብ ስለሆነች እና ውስጡም ላይ ያለውን አርማ ስለፈለገችው ስአቱነሸ ገዛች። ሻጩም በስጦታ ወረቀት ጠቅልሎ ሰጣት ። እቃዋን ይዛ ሱቁን በአይኗ ገርመም እያደረገች ወጣች። በስተመጨረሻ ታክሲ ውስጥ ገብታ ጊቢ ገባች። ** ባሩክ ከአዳራሹ ወጥቶ ወደዶርም እየሄደ ስለ ናታኔም ድንገታዊ ባህሪ እያሰበ ነው። ባሩክም በናታኔም ባህሪ በጣም ግራ ተጋብቷል መርዕድ ሜላትን እንዴት የራሱ ማድረግ እንዳለበት ዶርሙ ቁጭ ብሎ እያሰበ ነው። ሜላት በናሆም ከእንደገና ተስፋ አድርጋለች። ሜሮን በናታኔም ውዝግብግ ብላ እና እልህ ተጋብታ ነገር እያውጠነጠነች አልጋዋ ላይ ተቀምጣለች። አድዋ ዩኒቨርስቲ ነገ የሚከበረውን 150 ኛ አመት የድል በዐል ለማዘጋጀት ዝግጅቱን አጠናቆ ጨርሷል ነገ በአድዋ ዩኒቨርሰቲ ሁለገብ አዳራሽ በዐሉ ይከበራል ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና ሙህራኖች ይታደማሉ። ይቀጥላል .......... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 53♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ክፍል_51 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ምን? አለ ናሆም "አወ ናሆም በጣም ነው ያፈቀርኋት! አላውቅም በቃ ምንም ነገር እንዳትለኝ!" አለ ናታኔም " እንዴት ልትወዳት ቻልክ እሷ ጋር እኮ ያን ያህል የቀረበ ግንኙነት የላችሁም አይደል? " ብለ ናሆም ጠየቀ ናታኔም ለቅሶውን በድንገት አቆመና ማሰብ ጀመረ ። ትንፋሹን ወደ ውስጥ ሳበና " ለካ ስለግንኙነታቸው ናሆም አያውቅም። ምን ውስጥ ገባሁ?" አለ ናታኔም " ንገረኝ እንጅ እንዴት ልትወዳት ቻልህ?" አለ ናሆም በድጋሚ " በቃ ምንም እንዳትጠይቀኝ ብየህ አልነበር? ከቻልህ በቃ ተወኝ ናሆም የነገርኩህ እኮ ጭንቀቴን እንድታቀልልኝ የው እንጅ ለሌላ አይደለም።" አለ እና ሊሄድ ብድግ አለ ናሆም " ችግር የለም እሽ ተቀመጥ ምንም ነገር አልጠይቅህም። እኔ ግራ ስላጋባኝ ነው!" አለ እና ዝም አለ ። በሁለቱም ዝምታ ሰፈነ። ናሆም የጎንዮሽ በጨረፍታ ያየዋል ናታኔም ግራ የተጋባ ይመስላል። በሀሳብ ጭልጥ ብሏል።" የሆነ ነገርማ ደብቀኸኛል ያለ ነገር እንዲህ ምክንያት ስጠይቅህ አልተጨናነክም " አለ ናሆም። ናታኔም ዞሮ ናሆምን ተመለከተና በረጅሙ ተነፈሰ " ናሆምን አሁን ምን ብየ ነው የማሳምነው የት አይቻት ምንስ ብየ ነው የማሳምነው? ቆይ ነገሩን እንዴት ላስረዳው እችላለሁ? ምን አይነት ጣጣ ነው የገባሁት ቆይ ራሷኑ መቅደላዊትን ቢጠይቃትስ? እሷ የምትለው ምን ሊሆኖ ይችላል ሌላ ችግር ሌላ ፈተና ። በዚህ ሁሉ ነገር ላይ እኔና መቅደላዊት በድብቅ እንደምንገናኝ ቢያውቅስ? አይ ማን ሊነግረው ይችላል? ይሄን ምስጢር ከአራታችን ውጪ ማን ያውቃል? መቼም መርዕድን አይጠይቀውም ማንን ሊጠይቅ ይችላል? መቅደላዊትስ እንደማፈቅራት ስትሰማ ምን አይነት ስሜት ይሰማታል? ወይ እኔ በምን ጊዜ ነው ለአንተ የነገርኩህ ናሆም " አለ ወደ ናሆም ዞሮ ናሆምን ገልመጥ አድርጎ እየተመለከተ ናታኔም ራሱን በሁለት እጁ ይዞ አይኑን ጨፈነ ሁሉም ነገር በአእምሮው ሲደበላለቅበት ታየው። ሁሉም ነገር በአንዴ ሲመሰቃቀል መንገዶቹ ሁሉ ሲዘጋበት ታየው። አሁን የእኔ የሚላቸውን ሰወች በሙሉ ለማጣት የመጨረሻ ጊዜ ላይ እንደሆነ አንደኛው አአምሮው ሹክ አለው። ሆዱ ፈራ ልቡ መምታት ጀመረ። እንደውንድም የሚያየው እና መካሪየ የሚለው ጓደኛው ባሩክ በመቅደላዊት ሁኔታ ሊያጣው ነው። መቅደላዊት ደግሞ እንዲሁ ባላሰበችው መንገድ እሱን እንድታየው ስላደረጋት እንዲሁ እሷም ልትርቀው ነው። ናሆም ደግሞ እውነቱ ላይ ለመድረስ እያነፈነፈ ነው። ከእውነቱ ላይ ሲደርስበት ደግሞ የመጀመሪያው ስራው እሱን ማስወገድ እንደሆነ ።ከዛ እኔ ባዶ እጄን አጨብጭቤ እቀራለሁ ። አወ ሁሉም የሚገባቸውን ለማግኘት ቋፍ ላይ ደርሰዋል። እኔ ደግሞ የሚገባኝ ሁሉንም ማጣት ነው። ከዛ ጊቢው ላይ በደመነፍስ እኖራለሁ። ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ " ብሎ በረጅሙ ሳቀ ። ናሆም ድንግጥ ብሎ " ናቲ ምንድን ነው የሆንከው እባክህ አታስጨንቀኝ ንገረኝ ። " ቢለው " ምን ሰምተህ ለምታስጨንቀኝ ነገር ለምን ነግሬህ እንድታስጨንቀኝ ልፍቀድ?" አለ እና አሁንም ሳቀ። ናሆም አሁን ከእስካሁኑ ይበልጥ ግራ ተጋባ " ምን ሰምተህ ለምታስጨንቀኝ ነገር ለምን ነግሬህ እንዳታስጨንቀኝ ልፍቀድ?"አእምሮው ላይ አቃጨለበት። " ምን ለማለት ፈልጎ ነው?" ቆይ እኔ ሰምቼ ለምን እንደማስጨንቀው ይነግረኛል?, ይሄ ልጅ ምንድነው ያጋጠመው ምን እያደረገ ነው? በእርግጠኝነት የእሷ ፍቅር ብቻ አይደለም እንዲህ ያስጨነቀው ከእኔ የሚደብቀው አንድ ነገር አለ። እሱ አንድ ነገር ምንድን ነው?" አለና ናሆም የሚለጥፈውን ባነር አቁሞ ማሰብ ጀመረ ። ከዛ ወደ ናታኔም ዘወር ሲል ናታኔም የለም በተቀመጠበት አቅጣጫ ተከትሎ ሲመለከት ትንሽ ራቅ ብሎ እየሄደ አየው " በቃ አንድ ነገርማ ሆኗል። ናታኔም ሳይዞር ቀጥ ብሎ ሁለቱን የ መመገቢያ አዳራሽ መሀል ለመሀል ሰንጥቆ አግድሙን ትንሽ ከሄደ በኋላ ወደ ግራ የሚወስደውን መንገድ ይዞ ታጠፈ። ቁልቁል ወደ ዩኒቨርስቲው በር መሄዱን ተያያዘው መንገድ ላይ አንዲት የምታውቀው ልጅ አገኘችውና ብትጠራው ሊሰማት አልቻለም ። ትንሽ እንደተጓዘ ሜሮንን አገኛት " ሜሮን ሰላም ነው ናታኔም?" አለችው ከንፈሯን እየነከሰች አልሰማትም ተከተለችውና ቀኝ እጁን ያዘችው ወደ ኋላ ዞረ ። " ደግሞ ዛሬ ምን ፈልገሽ ነው ? ተይኝ እንጅ ችግር አለብሽ እንዴ? " አለ " ችግር ያለብህ አንተ ነህ አንተ ማን ስለሆንክ ነው ሰው እየጠራህ ዝም ብለህ የምታልፈው ጋጠወጥ የየት ውርጋጥ ነህ? እኔ ማንም ወንድ ቀና ብሎ እንኳ አይቶኝ አያውቅም እንኳን ሊሰድበኝ እና ሊገላምጠኝ " አለች ሜሮን ናታኔም በንቀት እና በመፀየፍ ከእግር እስከ ራሷ ተሐለከታት። ያጨረሻ ወራዳና ዘቅጣ ታየችው ይበልጥ በምትናገረው ነገር ተፀየፋት ። ምንም ነገር ሳይላት በቆመችበት ትቷት በአንደኛው መንገድ ሊሄድ ሲል መንገዱን ዘጋችበት ኡፍፍፍ አንቺ ልጅ ትዕግሥቴን አትፈታተኝው። እኔ የማይሆን ነገር እንዳደርግ አትገፋፊኝ" አለ ናታኔም " ምን ልታደርግ ? በል አድርጋ ምን እንዳደርግ የምፈልገውን ነገር ላድርግ በል እንጅ ምን ስርአት እንዳለው ሰው ታወራለህ?"አለች ሜሮን ይበልጥ እየተጠጋችው ያነባበራቸውን እጆች አጣብቃ እየመታች " አውቃለሁ አስቀይሜሻለሁ ግን ጥሩ ባልሆንኩበት ሁኔታ ላይ ነው ያገኘሁሽ እና ተረጅኝ" አለና እንደገና መማፀን ጀመረ። " አሁን በጣም የምቸኩልበት ቦታ አለ እና ቶሎ መሄድ አለብኝ ብሎ ትቷት ሄደ። ሜሮን ምንም ሳትለው ቆማ ተመለከተችው ናታኔም በሩን አልፎ ታክሲወች ጋ ሲደርስ ከከተማ ጭኖ የመጣ ታክሲ ተሳፋሪዎችን አወረደ ከተሳፋሪዎቹ መካከል አንደኛው ባሩክ ሒሳብ ከፍሎ ሲወርድ ናታኔም ደግሞ ወደ ታክሲው ሲጠጋ ተገጣጠሙ። ይቀጥላል .......... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 52♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ክፍል_50 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ አድዋ የጥቁር ልጅ አንገት ቀና ነጮች ደግሞ አንገታቸውን የደፉባት ምድር። ኢትጵያውያን በአንድነት ስለ አድዋ እየዘመሩ ነው።አድዋ ዩኒቨርስቲ ባነሮቹን በየ ቦታው ሰቅሎ የአድዋ ጀግኖች ከፍ አርገው የሰቀሉትን ሰንደቃላማ ደግሞ ከፍ አድርጎ በየ ቦታው ተሰቀሏል። የጀግኖቹ ሰማዕታት ሀውልት በአረንጓዴ ቢጫ ቀይ አርማ ለብሷል። ዩኒቨርስቲው መዝሙሩ አድዋ ብቻ ነው ወቅቱ የካቲት ወር ነው የሁሉም ሙዚቃ ጅጅ ተከፍታለች በየቦታው አድዋ አድዋ ብቻ ነው። ሁሉም ሰው የጂጂን ሙዚቃ በስሜት ያደምጣል። የአድዋ ዩኒቨርስቲ መመሪቂያ አዳራሽ በዕለቱ የሚዘክረውን ትልቅ በዐል በአዳራሹ ለማሰናዳት ዝግጅቱን አጠናቆ ጨርሷል የዩኒቨርስቲው ሁሉም ክበባት አዳራሹን ዲኮር በማድረግ ተጠምደዋል **** ከተቀመጠበት ወንበር ፊትለፊት የተሰቀለውን ትልቁን የአድዋ ፎቶ ባነር ተመለከተና እስክርቢቶውን ጣለው። እምባወቹ ጎረፉ። " ለእኛ ህይወት እናንተ ተሰዋችሁ ለእኛ መኖር እናንተ ጠፋችሁ። ለእኛ ሁሉ ነገር እናንተ ሁሉንም አጣችሁ ክብር ሁሌም ለእናንተ ይገባችኋል እናንተ ዘመን የማይሽራችሁ ሞታችሁ በእኛ ህይወት የምትኖሩ ናችሁና ለዘለዓለም ንገሱልን የእናንተ በረከት አይለየን" አለ እና ዶክተር እስጢፋኖስ ወንበሩ ላይ ተንጋሎ ተኛ ትንሽ ጣራ ጣራውን ከተመለከተ በኋላ የቢሮ ስልኩን እጄታ አንስቶ ከስልኩ ላይ ቁጥር እየተመለከተ ደወለ። " ዶክተር ደወለልኝ " አለ ባሩክ " አንሳው ቶሎ " አለች መቅደላዊት " ሃሎ ዶክተር ሰላም ነው?" እየተሽቆጠቆጠ " ደህና ነኝ ባሩክ አንተ እንዴት ነህ ፈተና በሰላም ተጠናቆ ውጤትህን ተመለከትህ?" አለ ዶክተር እስጢፋኖስ " ሁሉም አሪፍ ነው ዶክተር ውጤቱም ቆንጆ ነው። " አለ ባሩክ " እየውልህ አሁን አደዋወሌ ለነገ ወዲያ የአድዋ ድል በዓል የሚሆን ቆንጆ ነገር ተዘጋጅ በጣም ብዙ ምሁራኖች እና የውጭ ሀገር ፕሮፌሰሮች የታሪክ ተመራማሪዎች ሁሉ በወቅቱ ጥናታቸውን ያቀርባሉ ። እንዲሁም የኢትዮጵያ ጠቅላይ ምኒስቴር ፕሮፌሰር የሐናን መልከጼዴቅ ይገኛሉ ስለዚህ ቆንጆ ስራ ብታመጣ ከተማሪዎች ለአንተ ነው እድል የሰጠውህ እራስህን ብታይበት ብየ ነበር " አለ ዶክተር ፍፁም በሆነ ፈገግታ " በደስታ ነዋ ዶክተር ይሄን እድል ባገኝ ብየ ስዘጋጅ ነበር የቆየሁት ስለ እውነት በጣም ነው የማመሰግነው " አለ ባሩክ " በል በስራህ አመስግነኝ መቅደላዊት ደህና ነች?" አለ " ደህና ነች በጣም " አለ ባሩክ " በል በርታ መልካም ዝግጅት ይሁንልህ " አለ ዶክተር " እሽ ዶክተር ቸው ብሎ ስልኩን እንደዘጋው" ምን አለህ ምን ፈልጎ ነው " አለች መቅደላዊት በጉጉት " ለአድዋ ዝክረ በዓል ከተማሪዎች ለአንተ ነው እድል የተሰጠው እና በወቅቱ የምታቀርበውን በሚገባ አዘጋጅ ነው ያለኝ " አለ ባሩክ " ደስ ሲል ይሄ ለአንተ ትልቅ እድል ይመስለኛል። ዶክተር እንዳለው በብዙ ታዋቂ እና አዋቂ ሰወች ፊት ስለሆነ ስራህ የሚታየው በጣም ቆንጆ እድል ነው።" አለች " ልክ ነሽ በደንብ መዘጋጀት አለብኝ በይ ተነሽ እንሂድ " አለ ባሩክ " አይ ባሩኬ እኔ የምገዛው እቃ ስላለ ትንሽ ዘወርወር ማለት አለብኝ "አለች መቅደላዊት " እሽ ካልሽ በቃ እኔ መሄዴ ነው "አለ እና ብድግ አለ። እሷም አብራው ብድግ አለች " ሊስማት ጠጋ ሲል " ሳትስመኝ ልትሄድ መስሎኝ ደብሮኝ ነበር" አለች መቅደላዊት " የአንችን ከናፍር ሳይስሙ መሄድ ገሀነም እንደመግባት ነው" ብሎ ጎረሳት ። ባሩክ ከሳማት በኋላ ቸው ብሎ መንገዱን ጀመረ ።መቅደላዊት በአይኖቿ ተከተለችው " ልዩ ፍጡር ነህ አላውቅም መቼ እና የት እንዴት እንደገባህ አላውቅም ግን በልቤ ላይ ተቀምጠሃል።በህይወቴ እንዲህ አይነት ስሜት ተሰምቶኝ አያውቅም አንተ ግን ትላንት መጥተህ አሸነፍከኝ ሁሉ ነገሬን ማዘዝ ቻልህ ።አንተ ሰው ግን ማንነህ ቆይ ትክክለኛው አንተነትህ ማን ይሆን " አለች መቅደላዊት ባሩክ መንገዱን ዝም ብሎ ቀጠለ ታክሲ ውስጥ ከተሳፈረ በኋላ " ቆይ ግን ምን እያደረኩ ነው? በጣም የዋህ ነች። ልብን ማሸነፍ የሚያስችል ተፈጥሮ ያላት ልጅ ናት ስምንተኛው ስሜቴ በልቤ በኩል ምን እያለኝ ነው?" ብሎ እጁን ወደ ልቡ አስደገፈ ያለልክ ይመታል እጁን ቀስ አድርጎ ብድግ እያደረገ መሳብ አለብኝ በስሜት ሳይሆን በሀሳብ መወሰንና ማገናዘብ አለብኝ በዚህ ታሪክ ውስጥ ማናችንም ተጎጅ መሆን የለብንም በተለይ መቅደላዊት ልጎዳት አይገባም ።በእያንዳንዱ ድርጊቷ እኔን እንደምትወደኝ አስተውያለሁ። " አለ ባሩክ ከራሱ ጋር ማውራቱን ቀጠለና " ይቺ ልጅ የማሰብ ችሎታየን ለመፈተን የተላከች ፈታኝ ሳትሆን አትቀርም "አለ እና ራሱን በግርምት ወዲያና ወዲህ አወዛወዘ። ናታኔም ልብሱን ቀያይሮ ናሆም ጋ ተገናኙ ። ናሆም የናታኔምን አይኖች ሲመለከት ደነገጠ አይኖቹ ቀልተዋል። አንዳች ነገር እንደሆነ ገመተ ምን "ሆነህ ነው እንዲህ የሆንከው " አለ ናሆም የሚሰራውን ስራ አቁሞ ወደ ናታኔም ተጠግቶ ፊቱን አስተካክሎ እያየ " ምንም ልክ አይደለህም እኮ ወንድሜ ምንድነው የተፈጠረው ነገር?" አለ ባሩክ እየተጨነቀ ጠየቀው " ምንም አልሆንኩም " አለ ናታኔም " ምንድን ነው ምንም ሆነህ ምንም አልሆንኩም ማለት? አይኔን ልመን ወይስ ጀሮየን " አለ ናሆም እየተቆጣ " በቃ ተወኝ ናሆም " አለ እና አለቀሰ " እንዴ ናታኔም ምንድነው የተፈጠረው ለምንድነው የምታለቅሰው ተው እንደዚህ አትሁን እንጅ ወንድሜ ብሎ እምባውን ጠረገለት ግን ለምንድነው የማትነግረኝ?" አለ ናሆም " ናሆም ወንድሜ መ መ መ መቅደ መቅ ቅቅ መቅ " ብሎ ተንተባተበ " እ ጨርሰዋ እ መቅ መቅ? " አለ ናሆም " መቅደላዊትን አፍቅሪያታለሁ!" አለ ናታኔም " ምን?" አለ ናሆም ይቀጥላል .......... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 51♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ክፍል_49 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ አስወለቀችውና የሱሪውን ቀበቶ ልትፈታ ስትል ባሩክ እጇን ያዘውና ከዛ እንደገና ለቀቀው መቅደላዊት ቀበቶውን ፈታችው ባሩክ ሱሪውን አወላለቀና ቀሚሷን ወደ ታች ዝቅ አደረገው። ሁለታቸውም እርቃናቸውን ቀሩ ባሩክ ከንፈሮን ይዞ ከላይ ተከመረባት ። ፀሀይዋ በስተምስራቅ ጩር ብላ የነ መቅደላዊትን መኝታ በመስኮት በኩል ወረረች። ባሩክ አይኖቸቹን ገለጥ ሲያደርግ ፊት ለፊት ካለች ፀሀይ ጋር በአይኑ ተሳሳመ። አይኖቹን ከእንደገና በእጆቹ ሸፍኖ ወደ ጎኑ ሲያይ መቅደላዊት እልም ያለ እንቅልፍ ወስዷታል። ፀጉሯ ተበታትኗል ጥርሶቿ በትንሹም ቢሆን ይታያሉ በግራ እጁ አልጋውን ተደግፎ ፀጉሯን ወደ ኋላ እየመለሰ ለትንሽ ደቂቃ ያህል በስስት ተመለከታት። ባሩክ ከብዙ ጊዜ በኋላ ነው ወሲብ ያደረገው።ከሶስት አመት በፊት እንደዚሁ ከአንዲት ሊሊ የምትባል ልጅ ጋር ወሲብ አድርጎ ነበር። ነገር ግን ነዛን ጊዜ እና የአሁኑን ሲያነፃፅረው ፍፁም የተለየ የሰማይና የምድር ያህል ሆነበት ፍቅርም መሳምም መወሰብም የምትችል ልዩ ፍጥረት " አለ ባሩክ መቅደላዊትን እያየ። መቅደላዊት ተንቀሳቀሰች አይኖቿን ቀስ አድርጋ ስትገልጥ ባሩክ በስስት ሲመለከታት አየችው። " ውይ ነቅተሀላል?" አለች ። ባሩክ እራሱን በአወንታ ወዘወዘ " ብዙ ጊዜ ሆነህ ብላ አንሶላዋን እየገለጠች ተነሳች ። ከወገብ በላይ እርቃኗን ሆነች ባሩክ ፈዞ ጡቶቿን ተመለከተ " በእውነት እነዚህን ጡቶች ነው እየነካሁ እንደፈለኩ እያደረኩ ያደርኩት ?" ብሎ ራሱን ጠየቀ ። መቅደላዊት እየተመለከተችው ሳቅ አለች በስተመጨረሻ የፈዘዙ አይኖቹን በእጆቿ ሸፍና ተነሳችና ልብሶቿን በየተራ እየለበሰች " በጣም ደስተኛ ነኝ " አለችው ባሩክ አይኖቹን እያርገበገበ ቀና ብሎ አያትና ዝም አለ።" ቁርስ እንብላ በጣም እርቦኛል" አለ " እሽ ግን ጋባዥ አንተ ነህ " አለች " ችግር የለውም እጋብዝሻለሁ። ሁለቱም ተቃቅፈው ከ * ሜሮን ከወደ ላይብረሪው አቅጣጫ ቆይታ ወደ ብሎከኳ እየሄደች እያለ ከርቀት ናታኔምን ተመለከተችው። ቆም ብላ ትንሽ ካሰበች በኋላ ወደ ናታኔም ሄደች። ናታኔም እልም ያለ ትዝታ ውስጥ ተዘፍቋል። ወጭ ወራጁ ሀጅ መጩ ቀስ እያሉ የሚወዛወዙት የዛፎቹ ድምፅ ለእሱ አንዳችም ትርጉም አይሰጡትም ። ምናቸውም አይጥሙትም ሊያይዋት የሚሳሱላት ውብ ፅጌሬዳ ለእሱ የጠነዘለች የተቃጠለች አበባ ትመስለዋለች ። ሜሮን ያለ ማቋረጥ ብትጠራውም ሊሰማት ግን አልቻለም። በስተመጨረሻ ከሀሳቡ ብንን ሲል ቆማለች። ድንግጥ አለና " ማን ልበል?" አለ " ብዙ ጊዜ እየጠራውህ ልትሰማኝ ግን አልቻልህም በሰላም ነው ብቻህን በጠዋት በዛ ላይ በሀሳብ እንዲህ የተመሠጥከው?" አለች የጥያቄውን መልስ ችላ በማለት " ምን አገባሽ ምን ያዘንሽ ትመስሊያለሽ እንዲህ ስትጠይቂ ጥሩ ትመስሊያለሽ ገገር ግን ሰይጣናዊ ባህሪሽ ስለተሰወረ ነው።አይመለከትሽም አሁን ብቻየን ልሁንበት አርፌ እራሴን ላዳምጥበት አትረብሽኝ " አለ እና ኮስተር ብሎ አፈጠጠባት። ሜሮን በጣም ደነገጠችና አማተበች። ቀስ ብላ በመጣችበት የኋሊት በፍርሀት እሱን እያየች ትንሽ ከሄደች በኋላ ፊቷን አዙራ እየሮጠች ሄደች። ሜሮን ዶርሟ ደርሳ በሩን ቆልፋ አልጋዋን በንዴት ደበደበችው። " ማን ስለሆነ ነው እሱ እኔን እንደዛ አመናጭቆ የሚልከኝ ይህ የማይረባ ለነገሩ እሱ ምን ያደርግ ያኮራሁት እኔ ምን አቅለብልቦኝ? ቆይ ማንን እንዳናገረ ማንን እንዳቃለለ ማወቅ አለበት" አለች በዚህን ጊዜ በሩ ተቆረቆረ። ተነስታ ከፈተችው ሜራክል ነበረች " ምን ሆነሽ ነው ከሩቅ እየጠራሁሽ የማትሰሚኝ?" አለች ቦርሳዋን እያስቀመጠች " ኧረ ተይኝማ የዛ ጅል ጓደኛ ዘደ ላይብረሪ ማለፊያ ላይ ከአንድ ዛፍ ስር ቁጭብሎ ሲቆዝም አየሁትና ምን እንደሆነ ለመጠየቅ ብሔድ ጥምብ እርኩስ አድርጎ አባረረኝ። ቆይ ዋጋውን ባልሰጠው ያደረገው ነገር እንዲቆጨው ነው የማደርገው እኔን አላወቀኝም" አለች ሜሮን አልጋዋ ላይ ቁጭ ብድግ እያለች" ተይው በቃ ጓደኛየ እርሽው የኔ ቆንጆ ጥሩ ሁኔታ ስላልሆነ ይሆናል ሰው ማውራት በማይፈልግበት ሴትን ልጅ ማናገር በማይፈልግበት ስአት ሄደሽበት ሊሆን ይችላል እንደዛ ብታስቢ አሪፍ ይመስለኛል።እንጅ አንቺን ስራየ ብሎ ለመጉዳት ያደረገ አይመስለኝም። እንደዛ ውሰጂው " አለችና ሜራክል ሜሮንን አቀፈቻት። " በጣም እኮ ነው የከፋኝ እኔ እንደዛ አቃሎኝ የሚያቅ ሰው የለምኮ " አለች " አውቃለሁ በይ አሁን ተነሽና ፊትሽን ታጠቢ አትነፋረቂ መነፋረቅ አያምርብሽም አታናጅኝ" አለች። *** ናታኔም በሀሳብ ተመስጦ ችግሩን ሲያወጣ ሲያወርድ ብሶቱን ለማይሰሙት ዛፎች ሲናገር የመቅደላዊትን ፍቅር ሲያብላላ ቆይቶ በቀጣይ ምን ማድረግ እንዳለበት ከራሱ ጋር እየተሟገተ ወሰነ። ሁሉንም መጋፈጥ እንዳለበት አመነ። አወ እኔ ከሁሉም የተሻልኩ ሆኜ መገኘት አለብኝ ማንም ከእኔ በልጦ መቅደላዊትን የራሱ ሊያደርግ አይችልም። መቅደላዊት ለእኔ ነው የተፈጠረችው እኔም ለእሷ ከእኔ ውጪ ደስተኛ የሚያደርጋት የለም። በቃ አሁን ነገሮችን በማስተዋል መስራት አለብኝ መጠንከር አለብኝ" አለ ።ይህን ለራሱ እየተናገረ ባለበት ሁናቴ ስልኩ ጠራ። ስልኩን አውጥቶ ሲመለከተው ናሆም ነው። ቶሎ ብድግ አደረገውና " ሃሎ ናሆም " አለ ናታኔም " እ ናታ ደህና ነህ በጠዋት ነው የወጣኸውኮ በሰላም ነህ? ሁኔታህ ልክ አይደለም " አለ ናሆም " ደህና ነኝ ወንድሜ አታስብ " አለ ናታኔም " ችግር ካለ ንግረኝ በእውነት እባክህን አትደብቀኝ ደግሞ በእርግጠኝነት የሆነ ያልነገርከኝ ነገር እንዳለ ይሰማኛል" አለ " አይ የለም ናሆሜ " አለ ናታኔም " እንግዳስ በቃ ችግር ከሌለ የእኛ የስነፁህፍ ማዕከል የነገወዲያውን የአድዋ በዐል በማስመልከት ዝግጅት እያደረገ ስለሆነ ናና ታግዘናለህ አዳራሽ አካባቢ ነኝ" አለ ናሆም " እሽ በቃ እመጣለሁ " አለና ናታኔም ስልኩን ዘጋው። ቀጥታ ወደ ዶርሙ ሄደ። ይቀጥላል .......... በአምባዬ ጌታነህ አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 50 ♥️ ነገ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ክፍል_48 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ " ምነው ዝም አልሽ?" " ምነው ዝም አልክ?" ሁለቱም አንድ ላይ ተጠያየቁ ። አብረው አንድ ላይ ፈገግ አሉ ። " በነገርሽ ላይ መቅደላዊት የዘንድሮው አድዋ በድምቀት ነው የሚከበረው በዚህ ትልቅ በዐል ላይ በምን እየተዘጋጀሽ ነው?" አለ እና ባሩክ ዝምታውን ለመስበር ያህል ጠየቀ። መቅደላዊት አይኗን ሰብራ የወይኗን ብርጭቆ እየተመለከተች። ራሷን ነቀነቀች " እስካሁን አላውቅም በምን እንደምዘጋጅ "አለች መቅደላዊት ። ባሩክ የእጁን ስአት ተመለከተ 2:55" ኦ በጣም መሽቷል መቅዲ እንዴት እንዲህ እስኪሆን ድረስ " አለ ባሩክ ራሱን ጨብጦ " መቅደላዊት ስልኳን ከፍታ ስአቱን ተመለከተች " የሚገርም ነው ሳይታወቀን ነው የመሸው አሁን ደግሞ በሩ ይዘጋል " አለች እየተቅለሰለሰች " እሽ በቃ እዚሁ አልጋ ካለው እንጠይቅ " አለና ባሩክ ፊቱን ወደ አስተናጋጁ አዙሮ አጨበጨበ አስተናጋጁ መጥቶ " አቤት ወንድሜ ምን ልጨምር " አለ " አልጋ አለ እንዴ ወንድሜ" አለ ባሩክ ቀስ ብሎ " እስኪ አንድ ጊዜ ጠይቄ ልምጣ አለና አስተናጋጁ ሔደ። አስተናጋጁ መጣና አንድ አልጋ አለ " " እሽ ይሁን አለ " ባሩክ እና " እስኪ ሒሳብ ሰርተህ አምጣልኝ " ብሎ በድጋሚ አስተናጋጁን አዘዘው " የመቅደላዊትን ዝምታ ተመለከተና " ያው አንድ ክፍል አይበቃንም አለ?" ባሩክ መቅደላዊት ተሽኮረመመችና አይኗን ከደን ከፈት እያደረገች " ኧረ ይበቃናል "አለች ። ባሩክ እጁን ወደ ኪሱ አስገባ እና ሊከፍል ሲል እጁን ያዘችው" የዛሬው ራት በእኔ ግብዣ ነው ስለዚህ እባክህን እምቢ አትበለኝ " አለች እየለመነች " አይ እምቢማ እልሻለሁ መቅዲ ምን ሁነሻል ይህን ሁሉ ሒሳብ ብቻሽን እንድትከፍይ ማድረግ አልችልም። ምንም ቢሆን ተማሪ ነሽ ስለዚህ ሌላ ጊዜ ሙሉ ትጋብዥኛለሽ ለዛሬ እኔ ልክፈል "አለ። "አይሆንም በጭራሽ ራሴ ጠርቼህማ አንተ አትከፍልም። ራስህ ራት ለመጋበዝ ጥራኝና ያኔ ትከፍላለህ " አለች " እንደዛ ይሻላል ብለሽ ነው። እኔ ጠርቼሽ አንቺ ብትከፍይ አይሻልም " አለ " አይ አንተ ከጠራህማ ራስህ ተወጣው " አለች እየሳቀች " እሽ ባይሆን ግማሽ ግማሽ እንተጋገዝ " አለ " በጭራሽ !" መቅደላዊት ደረቀች። " ካልሽ ምን አደርጋለሁ " አለ ሆቴሉ በከለር ወረቀቶች በለበሱ አምፖሎቹ አሸብርቆ ምሽቱን ምሽት ውብና የማይሰለች የማይጠገብ አድርጎታል። በጣም ብዙ ጥንዶች በየ ጥጋጥጉ እጅ ለእጅ ተያይዘው አፍ ለአፍ ገጥመው ያወራሉ። የሚጫወቱት ሲያልቅባቸው ደግሞ ይሳሳማሉ።አረፍ ብለው ደግሞ ከእንደገና ከንፈሮቻቸውን አላቀው ማውራት ይጀመራሉ ። አለፍ ብለው የተቀመጡት ፍቅረኛሞች ደግሞ ጨዋታውም መሳሳሙምጠፍቶባቸው ዝም ብለው ይተያያሉ። አብዛኞቹ ደግሞ ቆመው ይደንሳሉ የዚህን ሁሉ ትዕይንት በአርምሞ የሚመለከት አንድ ሰው ጥግ ላይ ተቀምጧል። ሰውየው በስልሳዎቹ መጨረሻ እድሜ ላይ የሚገኝ ትልቅ ሰውየ ናቸው። አንገታቸው ላይ ስካርፕ አድርገው ወጣቱን ይመለከታሉ። ሽበታቸው ከርቀትም ሆኖ ያስታውቃል አልፎ አልፎ ጎንበስ እያሉ በብጣቂ ወረቀት ያዩትን የሚከትቡ እስኪመስሉ ድረስ ይፅፋሉ። አጠገባቸው ያለ አረቂ የጭንቅላታቸውን በር የሚከፍተው ይመስል በተደጋጋሚ ጎረጎጭ ያደርጉታል። ይሄን ሁሉ ትዕይንት ሲመለከት ከቆየ በኋላ ባሩክ ወደ መቅደላዊት ተመለሰ እና ፈገግ አለ ።" ምን አይተህ ነው የሳከው?" አለች መቅደላዊት ቀለስለስ እያለች ። " እዛ ጥግ ያሉትን ሰውየ ተመልከቻቸው እሳቸው የያዙትን ቦታ እና መጠጥ " አላት ። መቅደላዊት የባሩክን የጣት አቅጣጫ ተከትላ ተመለከተች ። መጀመሪያ አይኗ ላይ የገባው አረቂው ነበር ሙሉ ጠርሙስ አረቂ ነው። ፊቱን ጨፈገገችው " አየሻቸው በእርግጠኝነት ደራሲ ናቸው ይሄን ትውልድ እየፃፉት ነው ግን ራሳቸውን ለማፃፍ የፈቀዱ ደራሲም ናቸው። አረቄ እየጠጡ ግጥም አለዚያም አጭር ልቦለድ የፈለጉትን ብቻ ይፅፋሉ። " አላት ባሩክ " ግን አረቂው አይከብዳቸውም። " ብላ ጠየቀችው " አላውቅም እሳቸውን እንደሚጎዳ ግን ጉበት እንደሚጎዳ አውቃለሁ። " አለ በዚህን ጊዜ አስተናጋጁ መጥቶ ሂሳቡን ከነ አልጋው 350 የኢትዮጵያን ብር ተቀብሎ " ኑ አልጋችሁን ላሳያችሁ አለና የሆቴሉን ሪሰፕሽን ወደ ግራ በመተው በቀኝ ያለውን መንገድ ተጠቅሞ ከእንደገና ወደ ግራ ታጠፈ እና የመጀመሪያው G+5 ሆኖ ወደ ተሰራው ህንፃ ምድር ቤት ይዟቸው ሄደ ። ሊፍት ተጠቀመኑ ሶስተኛ ፎቅ ክፍል 305 ይዟቸው ገባ ክፍሉ ውስጥ ካስገባቸው በኋላ ሻወር ቤቱንና ሽንትቤቱን ካሳያቸው በኋላ አስተናጋጁ ወጥቶ ሄደ። " ሰፊ ክፍል ነው ግን ሶፋ ነገር የለውም!" አለ ባሩክ ልቡ በፍርሃት ሲርድ ይሰማዋል ከእንደገና የልቡ ምት ፍጥነት እየጨመረ ነው እየተሰማው ያለው ስሜት ግራ አጋባው። መቅደላዊት ተሽኮረመመች ዝም አለችው በጣም አፍራዋለች። ባሩክ መስኮቱን ከፈተና ሽቅብ ሰማዩን ተመለከተ አእላፍ ኮከቦች የፅሀይን ቦታ ተቀራምተው አያቸው። ፅሀይም ልክ እንደሰው ልጅ ይደክማታል ታርፋለች ።አወ ሁላችንንም ያለ ስስት ስታገናኘን ስታስተቃቅፈን ስታጨዋውተን ውላለች ። አሁን መተኛት ይኖርባታል ተራው የኮከቦች ኮኮቦች እንደብዛታቸው አይደሉም የፀሀይን ሩቡን ያህል ብርሀን መስጠት ተስኗቸው እርስበርሳቸው ሲላጉ ይታያሉ። አንዳንዶቹ ተወርዋሪ ኮኮቦች ደግሞ እንደመብረቅ ብልጭ ብለው ሲጠፉ ይታያሉ"። ባሩክ ይህን ሁሉ በልቡ እና በአፉ ሲተረትር ከቆየ በኋላ ወደ ራሱ የገሀድ አለም ተመለሰ። አሁን ከአንዲት ወጣት ቆንጆ ጋር ስለሚያደርገው ነገር ማሰብ ፈለገ። አብሪያት ላለመተኛት የማቀርበው አመክንዮ ምንድ ነው? ሶፋ ቢኖርስ መልካም ነበር እሽ ብላስ የምላትን ትቀበለኛለች ወይ? የማቀርብላት ምክንያት ምንም ይሁን ምን ብቻ እሷን አያሳምንም ብቻ ግን በእያንዳንዷ ድርጊቷ እና ንግግሯ ፍላጎቷን እና ሁኔታዋን ላውቅ ግድ ይለኛል።" አለና መስኮቱን ዘግቶ ሲዞር መቅደላዊት ወደ እሱ ተጠግታ ፊቷን ወደ እሱ አዙራ እየጠበቀችው ስለነበር ተገጣጠሙ ።ባሩክ ወደ ኋላ ሊዞር ሲል መቅደላዊት እጆቿን አንገቱ ላይ ሳብ ብላ አጣመረችና ሳመችው ከንፈሯን እንደማላቀቅ ብላ በድጋሚ ጎረሰችው። ባሩክ የደነዘዘ መሰለው በሶስተኛው ስትስመው ተስገብግቦ ጎረሳት። ወገቧን ይዞ ሆዱ ላይ አዘላትና አጣደፋት ሁለቱም በስሜት ተሳሳሙ ለአፍታ ሳይላቀቁ ለአስር ደቂቃ ያህል ከተሳሳሙ በኋላ መቅደላዊት ተስፈንጥራ ከእቅፉ ወረደችና የሸሚዙን ኮሌታ ይዛ እየሳመች ወደ ኋላ ጎተተችው። ባሩክ ከንፈሩን ከከንፈሯ ሳያላቅቅ ወደምትስበው አቅጣጫ ተከተላት። አንድ የ8 አመት ህፃን ልጅ እንደሚመጠው የጀላቲ ፌስታል ባሩክም የመቅደላዊትን ከንፈር መጠመጠው ። ሁለቱም አይኖቻቸውን ሳይገልጡ ከንፈሮቻቸውን እየተቀያየሩ ተሳሳሙ። መቅደላዊት እየጎተተች አልጋው ላይ ስትደርስ የኋሊት ተንጋላ ተኛችና ባሩክን ሳመችው አብሯት ተኛ። አልጋው ላይ ባሩክ ከላይ መቅደላዊት ከታች ሆነው ለ3 ደቂቃ ከተሳሳሙ በኋላ መቅደላዊት የባሩክን ሸሚዝ ቁልፎች መፍታት ጀመረች ፈትታ ከጨረሰች በኋላ አስወለቀችውና የሱሪውን ቀበቶ ልትፈታ ስትል ባሩክ እጇን ያዘውና ....... ይቀጥላል .......... በአምባዬ ጌታነህ አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 49♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ክፍል_47 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ግራ ገባው። መቅደላዊት ራሷን መቆጣጠር አቃታት ከንፈሯን ወደ ከንፈሩ አቀረበችና ትንሽ ከቆየች በኋላ ልትሰመው ስትል ወደ ኋላ ራሱን አገለለና " እንቀመጥ " አለ ። መቅደላዊት ፀጉሯን ወደ ኋላ እያደረገችና ቀሚሷን ዝቅ እያደረገች ተቀመጠች። እንደማፈር ብላለች ግን ደግሞ ባሩክ ነፃነት እንዲሰማት እያደረገ ነው። በሁለታቸውም ዝምታ ሰፈነ ሁለቱም ለየቅል ማሰብ ጀመሩ ።" ቀስመአብ እኔ ልስመው መሞከር አልነበረብኝም ። በጭራሽ ከዚህ በኋላ እወርድበታለሁ ይንቀኝ ይሆን ሽት ሳስጠላ በጭራሽ ማድረግ አልነበረብኝም። ግን ለምንድነው ሊስመኝ ያልፈለገው ? ስለማይወደኝ ወይስ ምን አስቦ ይሆን ። አይ መጥላትማ አይጠላኝም ቢጠላኝ ጊዜውን ሰውቶ እዚህ አይመጣም ነበር ከተሳሳምን በኋላ ይደብራታል ብሎ አስቦ ይሆን? ። ግን እኔ እኮ ቢስመኝ ደስ ይለኝ ነበር። እንጅ በጭራሽ አይደብረኝም ለምን ይደብረኛል እንዲስመኝ ነውኮ የምፈልገው ። " እያለች ለብቻዋ ታወራለች። ባሩክ ደግሞ አተኩሮ እያያት ለደቂቃዎች ያህል ቆየና " በስሜት ነው እንጅ ልትስመኝ የፈለገችው አስባበት አይደለም ደግሞ ከሳመችኝ በኋላ ባደረገችው ነገር አፍራ በራሷ ብታዝንስ፣ አስባበት እንዳልሆነ እርግጠኛ ነኝ ግን ብስማትስ ? ለምን ነበር ወገቧን ስይዝ ሰውነቴን የነዘረኝ ለምንድን ነበር ያለልክ ልቤ ሲፈጥን ሲመታ የነበረው? መቼም ወድጃት አይደለም። አወ ወድጃትማ አይደለም ፍቅር እንዲህ በቀላሉ የሚዝ ተራ ስሜት አይደለም ስሜቱ ጥልቅ ነው እኔ ደግሞ አርጌው የማላውቀውን ነገር ለማድረግ እየተቃረብሁ እንደሆነ ስላሰብሁ ነው ልቤ ያለልክ የመታው? እንጅማ ገና መች አፈቀርኋት። ሆ ቆይ ዝም ብየ ለምንድነው ስለ ፍቅር የማወራው ፍቅር ሳይኖር። በስሜት መገናኘት በራሱ እኮ መፋቀር አይደለም መዋደድ አይደለም። ነገሮች እንዲህ አይደሉም ።እውነት መቅደላዊት በጣም ቆንጆ ናት በርግጥ አታንስብኝም ግን ደግሞ ለጊዜው በእኔ ደስ ብሏት ቢሆንስ እንደዛ አይነት ስሜት የተሰማት።? አይ ላይሆን ይችላል እንደ እኔ ቆሞባት ቢሆኖስ?" አለና በራሱ ንግግር ሳቅ አለ * ናታኔም ቁጭ ብሎ ይተክዛል። ከትንሽ ደቂቃ በኋላ መርዕድ መጣ " ምን ሆነህ ነው እንደዚህ የተከዝከው?" አለ መርዕድ ናታኔም አይኖቹ እምባ አቀረሩ " ታውቃለህ እኔ ነበርኩ መቅደላዊትን ልደርስላትና ልረዳት የምፈልገው ግን እድለኛ አይደለሁም ሁሌም አንድን ነገር ስትፈልግ አታገኘውም ሲፈልግህ እንጅ ስትፈልገው አይሳካልህም። በቃ ባሩክ ሳይፈልገው አገኘው እኔ ግን ፈልጌ አጣጠጡት" አለ ናታኔም መርዕድም " ልክ ነህ ሁሉም አንተ ባሰብከው ሰይሆን በታሰበልህ ነው የሚከወነው ። ግን ደግሞ ብዙም አትዘን እረዳሃለሁ መቅደላዊትን እንደወደድሀት አውቃለሁ። ግን ደግሞ ፍቅርህን እንዳትገልጥ ያደረገህ የናሆም ጉዳይ ነው። ለናሆም በምትሰሩት ስራ ላይ ተፅዕኖ እንዳያሳድር ብለህ እየተጎዳህ ፍቅርህን እንደያዝህ ግን ደግሞ ሁሉም ነገር መልክ አለው አንተ ለሌላ ስታስብ ለአንተ የሚያስብልህ ሰው ከሌለ በጣም ከባድ ነው የሚሆነው። እንደ እኔ ሁሉንም ነገር ብትነግራት አሪፍ ይመስለኛል። ይሄኔ እሷ ምንም ነገር የለንም ብላ ለሌላ ሰው እድል ልትከፍት ትችላለች እሱ ደግሞ አንተን ይጎዳሀል። ስለዚህ ሳይረፍድ ብትነግራት ጥሩ ነው ብየ አስባለሁ። ካልሆነ በውስጥህ እሷን ይዘህ እየተብሰለሰልህ እንዳታገግም ሆነህ ነው የምትታመመው" አለና መርዕድ ዝም አለ ። " ህ አይ መርዕድ ሁሉም ነገር ሲመክሩ እና ሲናገሩት ቀላል ነው ከባዱ መሆኑ ላይ ነው። እኔ የናሆም ጉዳይ እናቱ ስላሳዘኑኝ ነው እዚህ ሁኔታ ላይ የገባሁት። እናቱ ልጇን እንድታገኘው ለመርዳት እሱ ነው የኔ የመጀመሪያ አላማ እንጅ የእሱን አመለካከት ብቻ ላይ አልነበረም ። አላማየ እናቱን ማክበር እና ሴትን ልጅ ማክበር እንዲችል ማድረግ ነበር። ነገር ግን ሁሉንም ነገር እንደምታየው ነው። በጣም ከባድ ሁኔታ ውስጥ ገባሁ። አሁን እኔም የምታከምበት ሰአት ላይ ነኝ። የመቅደላዊት ወደ እኔ ልብ መግባት አልታየኝም እንጅ እሷን ማሰብ ከጀመርሁ ቆይቻለሁ። ግን በትክክል እንኳ አላወኩትም ልቤን ማዳመጥ አልቻልሁም። ያወኩት በቀደም እንደዛ ታማ ሳያት ነው። አይኖቿ ላይ የዝንታለም የምመኛትን ልጅ አየሁ አይኖቿ በልጅነቴ የኔ ብትሆን ብየ የሳልኳት ልጅ አይን ነው። ሁሉ ነገሯ ባለሸበሰለ አእምሮየ የሳልኳትን ልጅ ነው የመሠለችኝ ልቤ ለሁለት ተከፈለ። የፍቅር ስሜቱ አሀዱ አለኝ እጇን ስነካው ገነት የገባሁ ያህል ተደሰትሁ ። ግን ከዛኖ በፊትኮ ብዙ ጊዜ እጇን ነክቼ አውቃለሁ ግን እንደበቀደም አይነት ስሜት አልተሰማኝም። ሁሉም ነገሬ ሲቀየር ተሰማኝ ከዛ በኋላ ባሩክ ሲመጣ ስታይ ከተኛችበት አልጋ ለመነሳት ሁሉ ሞከረች። ባለ በለለ ነፍሷ ስሙን ጠራች ፈገግ አለችለት ደስተኛ ሆነች። ያኔ ምን አለ እኔ አድርጌላት ቢሆን ኖሮ ብየ ተመኘሁ።ውስጤ በፍርሃት ሲርድ ታወቀኝ። ምን እንደማደርግ ጠፋኝ ሆዴን ባር ባር አለው። ብቸኝነት ተሰማኝ የልቤ አንድ አካል ተቆርጣ የሄደች ያህል ተሰማኝ። እኔ እዛ መኖሬን ረስታ ሙሉ ትኩረቷን ወደ ባሩክ ሲሆን ሳይ ከፋኝ። ባሩክን መሆኖ አማረኝ እየሳቀች እንድታወወራኝ፣ ከመፈለጌ የተነሳ ከዛ ጭራሽ ዛሬ ማታ ራተሸ ሊበሉ ወጥተዋል።" አለ እምባው በጉንጮቹ ቁልቁል ወረዱ። ማለሸቀሱ አልታወቀም " እንዴ ናታኔም እያለቀስክ እኮ ነው አታልቅስ እንጅ ጠንከር በል ምን ማድረግ እንዳለብህ ቆም ብለህ ማሰብ ይኖርብሀል። እንደዛ ካልሆንክ እድልና ድል ካንተ ጋ አይሆንም እንዳይመስልህ አለም ለተሸናፊወች ለልፍስፍሶች ለፈሪወች ቦታ የላትም። ጠንካራ ባትሆን እንኳ ጠንካራ መምሰል አለብህ ። በእርግጥ እንዲህ ልበልህ እንጅ እንደምልህ እኔ ጠንካራ አይደለሁም በሜላት ተጎድቻለሁ አሁንም እየተጎዳሁ ነው በህይወቴ እንደሷ የምወዳት ሴት አትኖርም። ምክንያቱም እሷ ለእኔ ሁሉ ነገሬ ናት የደስታየ ምንጭ የኦኔነቴ አንድ አካል እንደዶነች ስለሚሰማኝ እና ልቤ ስለሚነግረኝ። ሜላትን በጣም ነው የማፈቅራት። እሷ ግን እያየሀት ነው ከማን ጋ ኦንደሆነች አይደለም መውደድ ቅንጣት ታክል ስሜት ለእሷ ከሌው ልጅ ጋ ነው። እና አንተም እንደዚህ አይነት ነገር ሊያጋጥምህ ስለሚችል ከወዲሁ ራስህን ማደራጀት መቻል አለብህ። " አለ መርዕድ " እኔ እኮ መርዕዴ ጨንቆኝ እኮ ነው መቅደላዊት ባሩክን ብታፈቅረውስ ዛሬ ግንኙነት ቢያደርጉስ ቢዋደዱስ ? ደስታሽን ልንጠቅሽ ልላት ነው? ነውስ ብዙ ነገሮችን ያረገልኝን አብሮ አደጌን በዛ ላይ እንደወንድም የሆነልኝን ሰው እወዳታለሁ ብየ ደስታውን ልቀማው? እሱስ ምንድነው የሚሰማው። በዛ ላይ መቅደላዊትን የሚያውቃት በእኔ ነው ራሴ ነኝ ለዛ ሚሽን ብየ እንዲረዳን ያደረኩት አላሳፈረኝም እሱም እምቢ አላለም ጊዜ ሳይተርፈው ለእኔ ሰጠኝ። በዚህ ሁኔታ ነው ይሄ የተፈጠረው ስለዚህ ባሩክን ምንም ልለው አልችልም ።" አለ ናታኔም " እና ምን ልትለው?" አለና መርዕድ አፈጠጠበት!!! ይቀጥላል .......... በአምባዬ ጌታነህ አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 48♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ክፍል_46 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ለአለባበስ የማይጨነቀው ባሩክ ከሸሚዙ ላይ ጥቁር ሌዘሩን ጣል አድርጎ ከተቆጣጠሩበት ሆቴል እንዲሁ እንደነገሩ ለብሶ ተቀምጧል። ከአምስት ደቂቃ በኋላ መቅደላዊት መጣች። " አስጠበኩህ ኣ በጣም ይቅርታ " አለች ከመቀመጧ በፊት እየተማፀነች " በእርግጥ ምንም አይደል ብየ ልዋሽሽ አልፈልግም ግን በመጀመሪያ ቀን ወግ ላጠብቅብሽ አልፈልግም" አለና አቀፋት። " አመሰግናለሁ " አለች ፍፁም በሆነ ደስታ አስተናጋጁ መጥቶ " ምን ልታዘዝ?" አለ " ምን እንብላ ?" አለች " አላቅም " ጥሩ የምትለውን ምግብ እዘዛ"አለች እየሳቀች " ጥሩ ምግብ አላውቅም የማውቀው ጥሩ መፅሐፍ ነው።" አላትና ፈገግ አለ " እሽ በቃ ጥብስ እንብላ " አለችና ወደ አስተናጋጁ ዙራ " ሀለት ጥብስ በአንድ " አለች " የሚጠጣስ " አለ አስተናጋጁ " አንድ ወይን " አለች " ትንሹን ትልቁን?" አለ አስተናጋጁ " ትልቁን " አለችው አስተናጋጁ ሙሉ ትዕዛዙን ተቀብሎ ሄደ። ባሩክ በደንብ እያያት "አምሮብሻል "አላት " አመሰግናለሁ " አለች። " ሁልጊዜም እንደዚህ ነሽ ውበትሽ ያስገርመኛል ልዕለ ሰብሽ ድንቅ ነው። በእውነቱ ያንቺ ጓደኛ እድለኛ ነው።" አለ ባሩክ " ህህህ አንዳንዴ ከአጠገብህ ያለ ሰው አንተን አይጠቀምብህም እንጅ " አለች። " ልክ ብለሻል ብዙ ሰው የእጁን ወርቅ ጥሎ ሌላ መዳብ ይፈልጋል። ሰው ባክኝ ፍጡር ነው መቅደላዊት ።እንዲሁ መሮጥ መሄድ ወይ አይደረስ ወይ አያሸነፍ ዝም ብሎ የሚላፋ ፍጡር። የራሱን ጥሎ የሌላ ይመኛል።" አለ መቅደላዊት ራሷን እየነቀነቀች።" አንተስ ታዲያ ? ምንም የፍቅር ህይወት አልነበረህም የለህም?" አለች እንደማፈር ብላ " ምን ልፍጠርልሽ ልቦለድ ነገር ትወጃለሽ?" አላት " እንዴ ለምን የእውነት ካለህ ነው እንጅ ከሌለህማ ምን ያደርግልኛል?" አለች። " አወ ምንአልባት ከፈለግሽ ብየ ነበር። ያው ጊቢ አስክገባ የለኝም ጊቢ ላይ ይበልጥ ሴቶች ይጠሉኝ ነበር ። ጊቢ ላይ እኔና ሴቶች አባራሪና ተባራሪ ነን። አይጥና ድመት? ግን ከሚገርምሽ እኔ የምናገረው የእውነቴን ነው! ሁሉም ሰው እውነቱን ቢሸሸውም ግን የትም አያመልጥም እውነት አንድ ቀን ታጋልጣለች። እኔ አንቺን የማደንቅሽና የማወራልሽ በዛሬሽ ስራሽ ብቻ ነው።" ነገ ላይ ግን የሚያስወራኝ የነገሽ ስራ ነው። እኔ በትላንት ስራሽ ዛሬ ላይ አላወራም። " አለ በዚህን ጊዜ አስተናጋጁጥብሱን ይዞ ደርሶ ጠረምጴዛውን ወረረው ወይኑን ከኮካ ጋር አምጥቶ አስቀመጠውበየተራ እጃቸውን ታጥበው መጥተው ተሰየሙ። ባሩክ አማተበና እንጀራውን ቆርሶ ከስጋው እያጣቀሰ ሳለ አንድ ነገር ትዝ አለው። ሳቅ አለና ሰረቅ አርጎ እጇን ሲያይ አልቆረሰችም ይበልጥ ፈገግ እያለ የቆረሰውን እና ለእሱ ሊጎርስ ያሰበውን ጉርሻ ሊያጎርሳት እጁን ወደ አፏ ዘረጋ አላቅማማችም ግራ እጇን አስደግፋ አፏን ወደ እጁ ይበልጥ አስጠጋችውና ጎረሰች። ይሄኔ ፈገግ ብላ ስታየው እያያት ነው። ከዛ እንደ ማፈር ብላ አቀረቀረች። ምግቡን ጨርሰው የወይናቸውን ጠርሙስ አጋጭተው ተጎነጩ። ለምሽቱ የሚሆን ለስለስ ያሉ ዜማወችን ከፍቶ ዲጄው ተስተናጋጆችን በትዝታ አስምጧል። ጂጂ ደስ በሚል ቅላፄዋ ታንጎራጉራለች። ጂጂን ሲበዛ ይወዳታል ባሩክ በጂጂ ሙዚቃ ተመሠጠ። መመሰጡን ስትመለከት " ችግር አለ እንዴ በሀሳብ ሔድክኮ " አለች መቅደላዊት "ምን ላድርግ በጂጂ አለመመሰጥ እንዴት ይቻላል ?" አለ ባሩክ" ይሄን ያህል ትወዳታለህ? እኔ እኮ በጣም ነው የምወዳት እሷንና አስቴርን ሲበዛ እወዳቸዋለሁ " አለች ጂጂጂ ከሌላኛው ሙዚቃዋ ወደ ሌላኛው ሙዚቃዋ ተሸጋገረች እህህህ እስከመቼ እህህህ እስከ መቼ እህህህ ያዘላልቀናል እህህህ እስከመቼ እህህ ገና ብዙ መንገድ እህህህ አስከ መቼ እህህህ ብዙ ይቀረናል። እህህ አስከመቼ እህህ ......... ጂጂጂጂ ትቀጥላለች " ጂጂን ግለፃት ብትባል " አለች መቅደላዊት " እኔ እንጃ ያው ግን " የተፈጥሮ ወጌሻ እንደመሆኗ የተፈጥሮ መድሀኒት እላታለሁ ከዚህ በላይ አቅም የለኝም ። ጂጂ ከአሁኑ በኢትዮጵያ ሰማይ ስር በሁሉም ክልሎች ስለ አድዋ የዘፈነችው ሙዚቃ ለአንድ ወር ይደመጣል። ስሟም በሁሉም ኢትዮጵያውያን ልብ ታትሟል። ምክንያቱም አድዋ የሁሉም የኢትዮያውያን ቋንቋና ማንነት ስለሆነ ብቻ ተያት እሷን የምትገርም ሴት ነች"። አለ በመሀል መቅደላዊት እጇን ሰጠችው " እንደንስ ' አለች " ዙሪያ ገባውን ከማተረ በኋላ ብድግ አለ እና በዝግታ እየተወዛወዙ መደነስ ይደንሳሉ። የሁለታቸውም ትንፋሽ ያለልክ ይወጣል። ትንፋሿ እየገረፈው ሰውነቷ እየሞቀው ከሰውነቷ ጋ እየተግባባ ሲመጣ፣ ልቡ መምታት ሲጀምር ሰውነቱ እና ቀልብያው ለየቅል ሲሆኑ እና መቅደላዊት ይበልጥ እየቀረበችው ስትሄድ ሁኔታዋ እና አደናነሷ ሲቀየርበት ፣ የሆነ የማውቀው ስሜት ሰውነቱን ሲወረው እምቡጥ ከናፍሯቿ ላይ ከንፈሩን ማሳረፍ ሲያምረው እሷ ደግሞ አይኖቿ ሲርገበገቡ ከንፈሯ ሲንቀጠቀጥ ከናፍሯን ስታሸራምጥ ከታች ያለው ሶስተኛ እግር እንደ ህፃን ልጅ ከተኛበት ሲነሳ ... ........ ይቀጥላል በአምባዬ ጌታነህ አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 47♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

" " #መቅደላዊት #ክፍል_45 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ " ደግሞ ምን እያነበብህ ነው አሁን እንኳ አታርፍም ፈተናው አለቀ አይደል?" አለ ናሆም ባሩክ እንደመደንገጥ ብሎ ሲዞር ናሆም ነው " እሽ ናሆም እንዴት ነህ ሰላምታ አይቀድምም ነበር? አስደነገጥከኝኮ "አለ ባሩክ ምን እንደ አንተ አይነቱ ፈላስፋ እንዴት ብሎ ይደነግጣል? " አለ ናሆም እየሳቀ " እሱስ ልክ ነህ የዲዮጋን አምላክ ያውቃል!" አለ ናሆም " ምን አይነት ሰው እንደሆንክ አላውቅም መገመትም አልችልም ግን ሳይህ በጣም ጥሩ ሰው ትመስለኛለህ ቆይ ምን አይነት ልጅ ነህ?" አለ ናሆም " ባሩክ የሚያነበውን የሐበሻ ጀብዱን መፅሀፍ ከደን አድርጎ ሳቅ አለና " በእውነቱ ምን አይነት ልጅ እንደሆንኩ ብነግርህ ደስ ይለኝ ነበር ነገር ግን እኔ ራሱ ማን እንደሆንኩ አውቃለሁ ግን ምን እንደሆንኩ አላውቅም " አለ ባሩክ ። ናሆም ተቀመጠ " አንተ እብድ ሲሉህ ሰው ሰው ሲሉህ እብድ ጤነኛ ሲሉህ ፈላስፋ ፈላስፋ ሲሉህ ጤነኛ ትሆናለህ ብቻ አንተ የማትያዝ ሰው ነህ የእውነት በጣም ትገርመኛለህ።እኔ በማንም ኮርቼ አላውቅም ማንም ምኔ እንዲሆን ተመኝቼ አላውቅም አንተን ግን አከበርኩህ ወንድሜ ብትሆን ብየ ተመኘሁ። ታውቃለህ አንተ በጣም እድለኛ እና ሙሉ ልጅ ነህ አንተ አረኣያየ እንድትሆን እፈልጋለሁ። ለመቅደላዊት አንተ ያደረኬላትን ነገር አድርጌላት ቢሆን ምንኛ ደስ ባለኝ ነገር ግን አላደረኩላትም ምንም ነገር በፍላጎት ሆኖ አያውቅም ሲሆንልህና ሲፈቀድልህ ካልሆነ በቀር። በእርግጥ እኔ አንተ በሄድክበት መንገድ ሄጄ ላልረዳት እችል ነበር እኔ እንዳንተ በጥበብ አይሆንልኝም " አለ ናሆም " ተሳስተሀል ወንድሜ ናሆም ጥበብ ለማንም አልታደለችም አንተ ፍላጎቱ ካለህ በእጅህ ናት። ጥበብ ማለት በትዕግሥት እና በአስተውሎት ነገሮችን ማየት መቻል ነው ስለምታደርጋቸው ነገሮች በጥልቀት ማሰብ እና መመራመር እንዲሁም ፍፃሜው ምን ሊሆን ይችላል ብሎ ቀድሞ ማሰብ ነው ልክ ፈረንጆች ( before you say let you think what you say. , before you say one's think twice ) እንዲህ እንዳሉት። እኔ አንተን እንዲህ ለሆንክበት ነገር ተጠያቂ የምታደርገው ቤተሰብ ይኖርሀል በእርግጠኝነት " አለ ባሩክ " ናሆም ድንግጥ አለና የባሩክን አይኖች ተመለከተ ከእንደገና ደግሞ አይኖቹ ተርገበገቡ " አወ ምክንያት ባይኖርህ እንዲህ እንደኔ ባለመሆንህ አትቆጭም ነበር እኔን መሆንም ትችል ነበር ነገር ግን አንተ ባልሆነ ነገር ተተብትበሀል። ቆም በልና ከጥላቻ ከቂም ነፃ የሆነን ማንነትህን አንተነትህን ገንባ። ተመልከተኝ እኔ ባለኝ ነገር ደስተኛ ስለሆንኩ ነው እንዲህ አይነት ህይወት የምኖረው ስለ ሰወች አይመለከተኝም even ወላጆቼ በእኔ ላይ ስለሚያደርጉት ነገር ምንም ደንታ አይሰጠኝም የፈለጉትን ቢሉኝ አልቀየምም ምክንያቱም ተቀይሜ ደስታየን ማጣት ስለማልፈልግ ። ቂምና በቀል ውስጥህ ላይ እስካለ ድረስ ደስታ ወደ አንተ አትመጣም። ያስቀየሙህን ሰወችና የበደሉህን ሰወች ስለመበቀል ስታስብ ትውላለህ እንጅ ምን አድርጌ ልደሰት በምንስ ብለህ አታስብም ልዩነቱ እዚህ ላይ ነው።ግሪካዊው ፈላስፋ አርስቶትል ምን ይላል መሠለህ በጣም ነው የምወደው ሲበዛ የሚናገራቸው ነገሮች አንተነትህን ይነካሉ እና አንድ ወቅት ስለ ህይወት ሲጠየቅ " ህይወት በሁለት ትከፍላለች tragedy እና comedy tragedy ሆነ comedy ሁለቱም ቃላት ቴትሮን ከሚል የግሪክ ቃል የመጡ ሲሆን ዴራን ማለት ሲሆን ትርጓሜውም action ድርጊት ማለት ነው። ህይወታችንን tragedy አለያም comedy እምናደርገው በድርጊታችንና በስራችን ነው " ብሎ ነበር ህይወትን ቀለል አድርጎ የሚኖራት አርስቶትል የተናገረው ። እኔም በዚህ ሀሳቡ መቶ ፐርሰንት እስማማለሁ ለምሳሌ አሁን እኔ ብሰድብህ ስድብ ከምትመልስልኛና ከምትስቅብኝ አንተ በየትኛው ትደሰታለህ እኔ ደግሞ በምን የምናደድ ይመስልሀል? ለስድቤ ከመለስክልኝ እኔ እደሰታለሁ። አንተ ደግሞ ለስድቤ ሳትመልስልኝ ከቀረህ እና ለስድቤ ምላሽህ ሳቅ ከሆነና ዝም ካልከኝ አንተ ትደሰታለህ ። ሰወች ሳይረዱህ ሳያውቁህ ስለ አንተ ሊናገሩ ይችላሉ አንተ እንዲህ ነህ ሊሉህ ይችላሉ እሱ ግን አንተን አይነካህም ምክንያቱም አንተ ያሉህን ስላልሆንክ። እና ለምንም ነገር ደንታ ሊኖርህ አይገባም በሚያስደስቱህ ሰወችና አንተን ለማስደሰት ለሚጥሩ ሰወች ጊዜህን ሰጥተህ ደስተኛ ሁን።!!! በል በርታ የካቲት የኢትዮጵያውያን የድል ፤ የአፍሪቃውያን ደግሞ የነፃነት ወር ነች። ለየካቲት 23 ልዩ የአድዋ ጀግኖች መታሰቢያ ቀንን የሚዘክር ለክብራቸው ባይሆን እንኳ እንዳቅሜ ጥሩ ነገር ጥልቅ ሀሳብ ማቅረብ ብችል ብየ እየተዘጋጀሁ ነው። ሁሉንም ነገር ስለ ራስህ ስትል ብቻ አድርግ ለጥርስህ መጨነቅ አለብህ አንተ መሳቅ ይገባሀል። " ብሎት ትከሻውን መታ አድርጎ እጁን ለሰላምታ ዘረጋለት ናሆም ጨበጠው። ባሩክ ሄደ ናሆም ደግሞ ተቀመጠ። ፀሀይ ከወጣትነት እድሜዋ ወደማምሻ እድሜ ላይ ለመጠጋቷ ምስክር ለመሆን የምዕራብን ዘንግ ይዛ አጎንብሳለች። የበኑ ግርግር በፅሀይ መጥለቅ ምክንያት እየተታገሰ ነው የአድዋ ተራራወች በፀሀይ ቀለም ተመስለዋል። ወይዘሮ ስህን ብሎክ ዶርም ቁጥር 202 " ምንድነው እንደዚህ መቀባባት ባክሽ? " አለች ረድኤት ባሩክን ራት እጋብዝሀለሁ ብየዋለሁ " አለች መቅደላዊት " ምን ይሄን ፈላስፋ ዛሬ ውጪ ጋብዘሽ ሰው ልታደርጊው ነው? ወይስ ሌላ ነገር አስበሻል?" አለች ረድኤት " ተይ ረዱ እሱ እንዲህ አይነት ልጅ አይደለም ደግሞ በስንት መከራ መሰለሽ እሽ ያለኝ" አለች " ጭራሽም እምቢ ብሎ ነበር? ሆ እሱ ልጅ ግን እንትን አለው ግን " ብላ ሳቀች!" እንግዲህ ስርዓት " አለች መቅደላዊት በስሱ ቻፕስቲኳን እየተቀባች " አይ ይሄ ፈላስፋ ዛሬ ነው ወንድነቱን የማየው እንዲህ ተኳኩለሽ ቆንጆ ሆነሽ መቼም ምንም ሳያደርግሽ ከላከሽ ያኔ ምን እንደማደርገው እኔ ነኝ ማቀው?" አለች ረድኤት ሌባ ጣቷን እያሳየቻት " ሆሆሆ አንቺ ብዙ ታወሪያለሽ በይ ቸው እደውልልሻለሁ አለችና ስማት ወጣች ይቀጥላል በአምባዬ ጌታነህ አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 46♥️ ነገ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

" " #መቅደላዊት #ክፍል_44 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ምን? " አለች ሜላት " ሜራክልም " ናሆምንም እንደዛ ሁለተኛ አመት ልጅ ይፈትንልሽ አንቺ ምን ተሰቃየሽኮ ከዛ ወይ ይበልጥ ታፈቅሪዋለሽ ወይም ይቆርጥልሻል!" አለች ። ሜሮን በሜራክል ድፍረት እጇን አፏ ላይ አድርጋ ዝም አለች! " እንደዚህ አይነት ቀልድ አልወድም እሽ ብንከባበር ጥሩ አይመስለኝም ።አፍሽ ላይ የመጣልሽን ዝም ብለሽ አትናገሪ መጀመሪያ ከመናገርሽ በፊት ማሰብ ልመጅ ማሳብ ካልቻልሽ ደግሞ ዝም በይ። እኔ ናሆምን ለምንድነው የምፈትነው እኔ አፈቀርኩት እንጅ እሱ አፈቅራታለሁ ብሎ ሊሸውደኝ አልሞከረ!" አለችና እጇን ወደ ሜራክል እያወናጨፈች ወጣች። " እኔ ሜሪ የሜላት ባህሪ በየቀኑ እየተቀያየረብኝ ነው እና በጣም አስጠልቶኛል እንዲህ እንዲቀጥል አልፈልግም። እሷ ያልፈለገችውን ጓደኝነት እኔ አልፈልገውም። ስለዚህ ከዚህ በኋላ አላናግራትም " አለች ሜሮን ሜራክልን እጇን እየያዘች " ልክ ነሽ ስሜትሽ ይጋባብኛል እረዳሻለሁም ከምንም በላይ ገን ከሁለታችንም ስሜት እና የእለት ነገር የሚቀድመው የእሷ ህይወት ነው። በዚህ ስአት የገደል አፋፍ ላይ ያለች ልጅ ናት እኛ ከተውናት ደግሞ ይበልጥ ትጎዳለች ትወድቃለችም ናሆምም እንደፈለገ ይፈነጭልባታል። እሱ እንዲሆን ደግሞ እኛ እሷን ርቀን መፍቀድ የለብንም። እና ስሜትሽን ወደ ውስጥሽ አድርጊው አንድ ቀን ፀፅቷት ይቅርታ ስለምትጠይቅ እስከዛው እንታገሳት ዝም ብለን በየቀኑ ስህተቷን እናርማት። እንደዛ ነው መሆን ያለበት እሽ ሜራ " አለችና አቀፈቻት። **** " እና የዲፓርትመንት ሄዱ ነዋ ጨዋታውን የተጫወተው እሱ መፈተን ስለማይችል ከሌላ ጊቢ የሚፈልገውን ጓደኛውን አምጥቶ እንዲፈርምባት ካደረገ በኋላ ፊርማውን ለማሰረዝ እሷ ስትሔድለት ከእሷ የሚፈልገውን ወሲብ ለመጠየቅ እናቱ አፈር ትብላለት። ቆሻሻ ምን አለ ይሄን እናቱ ከምትወልድ መክና ብትቀር ኑሮ እንግሬ ልጅ ። አትነግረኝም ነበር የፈተናው እለት " አለ ናሆም ንዴቱን ለመቆጣጠር እየሞከረ " በዛ ስአት እኔ ራሴ በጣም ደንግጨ ስለነበር ምንም አላስታውስም ። " አለ ናታኔም " ቢሆንም እኔ መፍትሔ አላጣም ልጅቱ የራሷ ችግሮት አሉባት። እንዴት ነው ይህን ነገር የምትቋቋመው? አሁን ታዲያ ምንተወሰነ?" አለ ናሆም " አላወኩም ግን ዶክተር በድጋሚ እንደምትፈተን ነው የነገሩን።" አለ " ጉድ እኮ ነው። **** " ዛሬም ዶክተር ደውሎልኝ ነበር ከሀኪም ቤት ከወጣሁ ጀምሮ ሁሌም ይደውልልኛል ዛሬ ደግሞ የሚመችሽን ቀን adjusted አድርጊና ንገሪኝ ራሱ መምህር ኄኖክ እንዲፈትንሽ አደርጋለሁ ለምንም ነገር እንዳትጨነቂ። ነገር ግን ፈተናውን በደንብ መስራት አለብሽ " አለኝ ታውቃለሁ ሂወቴን ነው የሰጠኸኝ። ነገሮች ሁሉ ተዘበራርቀውብኝ ነበር ።የማደርገው ጠፍቶኝ ህይወት ልትጨልምብኝ ስትል ነው አንተ ወጥተህ ብርሀን ያደረክልኝ ለዚሀሰ ውለታህ እንዴት አድርጌና በምን እንደምመልስልህ አላውቅም! ግን ብቻ ከአእምሮዬ በላይ የሆነ ነገር ነው ያረክልኝ። በእናትህ ምን ላድርግልህ የፈለከውን ልትጠይቀኝ ትችላለህ " አለች መቅደላዊት እሷን በጀሮው ተፈጥሮን ደግሞ በአይኑ የሚያየውን ባሩክን ቀና ብላ እየተመለከተች። ባሩክ አይኖቹን ቀስ አድርጎ ከአድማስ ማዶ የነበራቸውን እይታ እያቋረጠ ወደ መሬት ሰደዳቸውና አንዲት ጠጠር ብድግ አድርጎ እየወረወረ። በግራ እጁ ፂሙን እየነካካ እይታውን ሳይመልስ። " ሰው በውለታ ተነሳስቶ በሚያደርገው ነገር የዘላለም ደስታውን ይነጠቃል። ህይወት እንደ ማለዳ አበባ ፈክታ የምትታይ ከስአት ደግሞ በፅሀይ ብዛት ለመጠውለግ የዳዳት ናት። እና አንቺና የህይወት ምስል አበባ አንድ ናችሁ። የአንቺ ልብ ንፁህ ነው ሴትን ልጅ በብዙ መንገድ ከፍየ የማይ ሰው ነኝ እኔ። እናም እዚህ ጊቢ በአንቺ ከሚኮሩት ሰወች መሀል ግምባር ቀደሙ ነኝ ሰው። አስታውሳለሁ የዛሬ አመት ሁለተኛ ሲምስቴር ላይ በሴቶች ከፍተኛ ውጤት አምጥተሽ ስትሸለሚ ነው ያየሁሽ። ሳይሽ ጥንካሬሽን አነበብሁ ሁሉን ቻይነትሽ ጎልቶ ታየኝ።እናም በቀደም ያ ችግር ሲከሰት ትዝ ያለኝ የዛን ወቅት ስትሸለሚ የነበረሽን ፈገግታ ነበር። ያ ፈገግታሽ እንደዋዛ ውሀ መጠጣት ችላ ማበብ የምትችል አበባ ነገር ግን ውሀ የሚሰጣት አጥታ እየደረቀች እንዳለች አበባ ታየሽኝ ።እኔ ውሀ ልሰጥሽ ነው የፈለኩት እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ እድለኛ ሁኜ ተሳክቶልኛል። እና እኔ ምንም ያደረኩልሽ ነገር የለም ለመመስገን የሚያደርስ በቃ እያየሁ ዝም ማለት አልነበረብኝም። አደረኩት ይሄን ነገር ደግሞ እንኳን አንቺ ጋ በደንብ ለተዋወኳት ማንም ብትሆን እያለቀሰች ትቻት ወይም ዝም ልላት አልችልም። ስለዚህ ለምንም ነገር አታመስግኝኝ ስለምንም አይነት ውለታ መልስ አታስቢ ለናሆም ያደረግሽው መልካምነትሰሽ በራሱ ከዚህም በላይ ይገባሻል። እሽ? "አለና ፊቱን ወደ መቅደላዊት አዞረና ሳቅ እያለ አሁን ፈተና ስላለብሽ በደንብ አጥንተሽ ሁላችንንም ልታስደምሚን ይገባል። ጠላቶችሽን ደግሞ ልታሳቅቂያቸውና ልታሳፍሪያቸው ይገባል። " አለና በቀኝ እጁ ጉንጯን መታ አደረገው። ምንም ልትለው አልቻለችም። ዝም ብላ ቡዝዝ ብላ ትመለከተው ጀመር። ** አድዋ ዩኒቨርስቲ የአድዋ ምድር ጀግኖቿን ለመዘከር ሽር ጉድ እያለች ነው። እግረኛ ተጓዦች ከየ አቅጣጫው ወደ አድዋ እየተመሙ ነው። የካቲት 23 የሰማአታት ቀን ሊከበር የሁለት ሳምንት ጊዜ ብቻ ቀርቶታል። አድዋ ዩኒቨርስቲም ከወዲሁ ከከተማውና ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ልዩ የሆነ ፕሮግራም በማዘጋጀትና ድንኳኖቹን በመስራት ብዙ ስራወችን እየሰሩ ነው።አድዋ ደግሞ ለመዳር የተዘጋጀች ሙሽራ መስላለች። እጅግ ተውባለች። አንዳንድ ቀድመው ይሄን ታሪካዊ የአፍሪቃውያንን ተምሳሌት ለማየት የመጡ ጎብኝወች በአካባቢው ህዝብ እንግዳ አቀባበል መገረማቸውን ይናገራሉ። እግረመንገዳቸውንም ይህን አንጋፋ ዩኒቨርስቲ እየጎበኙ ብዙ ኢትዮጵያዊ ጀግኖችን ሃውልቶችንና ታሪካቸውን በአድዋ ዩኒቨርሲቲ የታሪክና የፍልስፍና መምህር በፕሮፌሰር በለጠ ቢሆነኝ እየጎበኙ ቆይታቸውን አሀዱ ብለዋል። ይቀጥላል በአምባዬ ጌታነህ አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 45♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

" #መቅደላዊት #ክፍል_43 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ " አንቺ ግን ያምሻል እንዴት በስንት መከራ ያገኘኋት ደስታ ላይ ውሀ ልትደፊባት ትጥሪያለሽ አሁን አንቺ ጓደኛየ ነሽ? እ እ ንገሪኛ መልሽልኝ በጣም ነው የማዝነው ትላንት እንዴት ሆኜ እንዳደርኩ እኔ ነኝ የሚያውቀው ፍቅሩን በውል እንኳ ሳላጣጥም ነው እሽ ያደርኩት " አለች ሜላት " ሜሊ እኔ እኮ ፍቅር ያወረውን አይንሽን መግለጥ ነው የፈለኩት በብዙ መንገድ እንድትመለከች ነው የምፈልገው እንጂ ደስታሽን ለማጨለም አይደለም ፍላጎቴ ግን በድጋሚ መጥቶ እንዳይጎዳሽ ስለምፈልግ ነው። ስለ እውነት ሌላ ምንም ምክንያት የለኝም ግን እምልልሻለሁ ከዚህ በኋላ ናሆም የሚባል ልጅ አላውቅም በስህተት እንኳ ስሙን አላነሳብሽም በስህተት የፈለግሽውን መሆን ትችያለሽ አሁን ተደስተሽ በኋላ ላይ መነፍረቅ ትችያለሽ። ጓደኛሽ እንደመሆኔ አንዳንድ መስመሮችን ስታልፊ ለማሳየት እና ለመምከር መሞከሬ ነበር። ከእንግዲህ ብሞት አላደርገውም ። እኔ እንድትጮሂብኝ ነፈቀድኩልሽ ራሴ ነኝ ለአንች በማሰቤ ከዚህ በኋላ አይደገምም" አለቸችና ሜሮን ትታት ልትወጣ ስትል ሜላት እጇን ያዘቻትና " እሽ ምን አባቴ ላድረግ ሜሪ? በቃ ደስተኛ ስለነበርኩ እኮ ነው ምን ልበልሽ አቀፈኝ ሳመኝ ብቻ ደህንነት እንዲሰማኝ አደረገኝ ታዲያ በዚህን ጊዜ እንዴት ስለመከፋት አስቤ ደስታየ ላይ ውሀ ልቸልስበት ብለሽ ነው አንቺንም ማስቀየምኮ አልፈልግም " ሜላት ተቅለሰለሰች " እየውልሽ ሜሊ አትልፈስፈሽ ወንድ ቢሄድ ወንድ ይመጣል አንቺ ግን በቃ እንደ ፈረስ መንገድ የአንቺም በአንድ አቅጣጫ ብቻ ነው ዙሪያሽን እይ እንዴ የምታፈቅሪውን ብታጭ የሚያፈቅርሽን ታገኛለሽ የሚሆነን ደግሞ የሚያፈቅረን ነው። እኔ በእርግጠኝነት ናሆም አሁን የፈለገሽ ለራሱ አስቦ ነው እንጅ ለአንቺ ብሎም ሆነ ናፍቀሽው አይደለም። በዛ ላይ ሲያምረው ሲያምረው የስሜቱ ማብረጃ ነሽ እንዴ እየጠራ የሚያሳድርሽ ንቂ እንጅ ሜሊ እሽ አግኝቶ ምን አለሽ?" አለች ሜሮን "እንድትረጅኝ እፈልጋለሁ አለኝ እሽ አልኩት ከዛ ናታኔም ጋር አውርታችሁ ታቃላችሁ ወይ አለኝ አላውቅም በጭራሽ አንግባባምም አልኩት ከዛ ይሄን ጉዳይ አብረሽኝ ትሰሪያለሽ ናታኔም ስለ እኔ ከሆነች ሴት ጋር እያወራ ነበር እና ያች ሴት ማን እንደሆነች ማወቅ እፈልጋለሁ ስለ እኔ ምን እንደሚያወሩም እንዲሁ ስለዚህ በቅርብ አውቄ ማድረግ ያለብኝን ማድረግ አለብኝ! ስለዚህ አንቺ ከወደ ታች እንደምትመጭ አስመስለን እኔና ናታኔም ከወደላይ አብረን እንመጣለን ያኔ እኔ ሰላም ስልሽ ሰላም ካላለሽ እና አንቺ እንደማታቂው አክት ካደረግሽልኝ አፋጥጠውና ልጅቱን ይነግረኛል። ይሄን እንድትረጅኝ እፈልጋለሁ እባክሽ አለኝ እኔም እሱን መርዳት ስለምፈልግ እሽ አልኩት ግን ለማንም እንዳትናገሪ ብሎኛል!" አለች " እርግጠኛ ነበርኩ ታዲያ አሁን አልተገለጠልሽም ሜሊ ጉንጯን ነካ ነካ አደረገቻት ይህ ለእሱ ትልቅ ጉዳዩ ነው። " አለች ሜሮን በዚህን ጊዜ ሜራክል ገባች * " እናንተ ሰማችሁ ?" አለች " ምኑን ?" ሜላትና ሜሮን አንድ ላይ ጠየቁ መቅደላዊት ተፈርሞባት ራሷን ስታ ሆስፒታል ነው የዋለችዉ። ደግሞ ሆስፒታል የወሰዳት ማን ቢሆን ጥሩ ነው ፈላስፋው " ብላ ሳቀች " አትይኝም ባሩክ?" አለች ሜሮን " አወ ጓደኛየ ያ ፈላስፋ ምን አስቦ እንደሆነ ባላውቅም ለጊዜው መልካም ስራ ሰርቷል ። " አለች ሜራክል " ምን አድርጋ ነው የተፈረመባት?" አለች ሜላት " ምን አንድ ደነዝ መምህር ነው ዝም ብሎ ከተቀመጠችበት ወንበር አጠገብ ካለ ግድግዳ ላይ የሜካኒክስ ፎርሙላ ተፅፎ ቢያይ የሃይድሮሊክስ ፎርሙላ መስሎት የፈረመባት። ግን ፈላስፋው ሄዱንም ፈታኙንም ዶክተር እስጢፋኖስን ጠርቶ አ..ፋ..ጠ..ጣ..ቸው። ሁሉም እያወራ ያለው ስለ እሱ ድፍረት እና ጀግንነት ነው። " አለች ሜራክል "የምር ጀግና ነው። ደስ የሚል ልጅ እጠላው ነበር ወደድኩት " አለች ሜላት " አወ ሜሊየ እኔም ባሩክ እንዲህ ያደርጋል ብየ አንድ ቀንም አስቤ አላውቅም ኡፍፍፍ የአንድ አመት ህይወቷን ነው የታደገላት። " አለች ሜሮን " በጣም እንጅ ስላችሁታል አንድ አመት ላግ አድርጋ ሂወቷ ሲመሰቃቀል እግዚአብሔር ይሄን ልጅ ባይጥልላት " አለች ሜራክል " ግን መቅደላዊትን ያውቃታል ወይስ ይወዳታል እንደ ጊቢው ወንድ " አለች ሜላት " ማ ? ዲዮጋን እንኳን እሷን ራሱንም የሚወድ አይመስለኝም ህህህ ሲጀመር ለየት ያለ ነገር መናገር ለየት ያለ ነገር መብላት የተለየ ነገር ማድረግ ስለሚያስደስተው ነው። እና እራሱን የሚያገኘው በተለየ ነገር ነው በእሱ አስተሳሰብ " አለች ሜሮን " አንድ ጊዜ የሆነ ሁለተኛ አመት ልጅ ነው የኬሚካል ኢንጅነሪንግ ተማሪ ነው እና የሆነች የአርክቴክቸር እና አርባን ፕላኒንግ ኢንጅነሪንግ ተማሪ አፍቅሮ ምክር ለመጠየቅ ወደ ባሩክ ሄደ እና አማከረው። ዲዮጋንም (ባሩክ) ፀጉሩን እያሻሸ እባክህን ባሩክ እሷን የኔ የማደርግበትን መላ ንገረኝ " አለው ልጁ ባሩክም ትንሽ እንደማሰብ አረገና " የእውነት ታፈቅራታለህ? አለው " አወ በጣም ነው የምወዳት" አለ ልጁ " ለመሆኑ ልጅቱን ማን እንደሆነች እና ምን አይነት ባህሪ እንዳላት ታውቃለህ?" አለው " ልጁም ራሱን ነቀነቀና አይ ባህሪዋንማ አላውቅም የማውቀው ስሟን ብቻ ነው " አለ ልጁ ዲዮጋን በልጁ መልስ ፈገግ አለና " ታዲያ ስሟንና መልኳን ነዋ የወደድከው?" አለው " አወ ለአሁን እየቆየሁ ደግሞ ባህሪዋን ሳቅ ይበልጥ እወዳታለሁ " አለ ልጁ ባሩክም ከት ብሎ ሳቀና " ስታሳዝን በቃ ስታያት አሻፈደችህ አይደል በነገርህ ላይ ልጅቱ ከፍቶ እንካ ነች ወይም እምቢ ለምኔ ናት እዚህ ጊቢ ያላወጣት ተማሪ ካለ አንተ እና አንተ ብቻ ነህ የምትሆነው ምክንያቱም እኔም የዜግነት ስለደረሰኝ " አለው " ልጁ ደንግጦ በዛው ሄደ ሌላ ጊዜ መንገድ ላይ አገኘውና ልጁን ምነው ጠፋህ? ልጅቱን ተውካት እንዴ " ቢለው ልጁም ኮስተር ብሎ ኧረ ወግድ እንደሷ አይነት ቆሻሻ ልጅ አልወድም " ሲለው " ባሩክም ፈገግ እያለ አየህ አንተ ያየኸው መልኳን ነው ስለ ልጅቷ ያልኩህ በሙሉ የፈጠራ ታሪኬ ነው አንተ ምን ያህል እንደምትወዳት ለማረጋገጥ ነበር። እሱን ደግሞ አየሁ። አየህ ሰው በቀላሉ ተፋቅሮ በቀላሉ የሚጣለው በውስጥ መግባባት እና በመልካቸው እንደተዋደዱት በባህሪም ስለማይዋደዱ ነው። ሰውን ስትወድ ከወደድኸው ሰው መምረጥ የለብህም ከነ ጉድለቱ ነው መሆን ያለበት ካልሆነማ ጥሩ መውደድማ ቀላል ነው። በል የመጀመሪያ ፈተናህን ወድቀሀል ከአንተ በፊት የወደድካት ልጅ መጥታ ዲዮጋን ይህን ልጅ በፈለከው መንገድ ፈትንልኝ እና በአንተ ፈተና እንደሚወደኝ ካወክ የምር ልጁን እሽ እለዋለሁ አለኝ እና እኔም በቃሌ መሠረት እንደማትወዳት አረጋግጨ ነገርኋት"ብሎት ትቶት አልሄደም " አለች ሜሮን ታሪኩን በጥሞና ሲያዳምጡ የነበሩት ሜላትና ሜራክል በዲዮጋን ብስለት ተገረሙ ። " እኔ ልጁ ከአቅሜ በላይ ሆኖብኛል " አለችና ሜላት ብድግ አለች ። " ለምን ናሆምንም አይፈትንልሽም " አለች ሜራክል " ምን ብላ ዞረች ይቀጥላል በአምባዬ ጌታነህ አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 44♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

" #መቅደላዊት #ክፍል_42 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ በሩ ተንኳኳ ናታኔም ተነስቶ ከፈተው ዶክተር እስጢፋኖስ መምህር ኄኖክ እና እንዲሁም ባሩክ ነበሩ። " ግቡ " አለ ናታኔም በሩን ይበልጥ እንዲሰፋ እየከፈተው ፡ ሁሉም በየተራ ከገቡ በኋላ ናታኔም በሩን ዘግቶ እጁን ወደ ኋላ አጣምሮ ከኋላቸው ቆመ ። " አሁን እንዴት ነሽ ተሽሎሻል ወይስ ወደተሻለ ሆስፒታል እንሒድ " አለ ዶክተር እስጢፋኖስ ግምባሯን እየነካ " አሁን ደህና ነኝ እየተሻለኝ ነው" አለች ከዛ ወደ መምህር ኄኖክ ዙራ " ቲቸር በጭራሽ እንደዛ አላረኩም ግድግዳው ላይ አልፃፍኩም እዛ ያስቀመጠኝም ራሱ ፈታኙ ነው።" አለች " አውቃለሁ መቅደላዊት አታስቢ እኔ አንቺን አውቅሻለሁ ምን አይነት potential እንዳለሽም እንዲሁ አኔቺ ዝም ብለሽ በከንቱ አትድከሚ ዶክተርም ጉዳዩን በአካል ስላየው ትምህርቱን በድጋሚ ትፈተኛለሽ" አለ መምህር ኄኖክ " አወ መምህር ኄኖክ ያለው ልክ ነው በዚህ ስአት ማሰብ ያለብሽ ስለ ትምህርቱ ሳይሆን ስለ ጤንነትሽ ነው አንቺ በፈለግሽው ጊዜ ትፈተኛለሽ። ያለ በቂ ምክንያት እንዲህ ያደረገሽን መምህር በዩኒቨርስቲው ህግ መሠረት ቅጣቱን ያገኛል አንቺ ብቻ አሁን ራስሽን ተንከባከቢ" አለ ዶክተር እስጢፋኖስ " ሁላችሁንም አመሰግናለሁ ዶክተር " አለች " ችግር የለም በማንኛውም ጊዜ በምናስፈልግሽ ጊዜ ሁሉ ከአጠገብሽ ነን ምንም ቢሆን አሳውቂን እሽ" አለ እና ዶክተር እስጢፋኖስ ወደ ባሩክ ዞሮ " ባሩክ አንተ ጎበዝ ልጅ ነህ ስለእውነት ስትል የምትከፍለውን መስዋዕትነት ሳላደንቅ አላልፍም አሁን አስገራሚ ስራ ነው የሰራኸው በርታ በጭራሽ እንዳታፈገፍግ ከዚህ በኋላ ለአንዳች ብርቱ ጉዳይ ከፈለከኝ እንድትደውል ስልኬን ያዝ " አለ ዶክተር " እሽ " ብሎ ባሩክ ስልኩን አውጥቶ ተቀበለ ። " እኔም ካስፈለኩህ ቅድም በደወልክበት ስልክ ብደውልልኝ ታገኘኛለህ " አለ መምህር ኄኖክ " እሽ እደውላለሁ መምህር ኄኖክ እንደ አንተ አይነት መምህር ይብዛልን በእውነት በጣም ነው የማከብርህ ያደረከውን ቀና ተግባር መቼም አልረሳውም። እውነት እልሀለሁ" አለ ባሩክ " እንዴ ተው ባሩክ እንዲህ አይባልም ይሄኮ ግዴታየ ነው መቅደላዊት ተማሪየ ነች እኔ እያስተማርኳት እስካለሁ ድረስ ይመለከተኛል የሌሎቹም ተማሪዎች ጉዳይ ጉዳየ ነው እና እቀጥላለሁ ።ስለዚህ ምስጋና አያስፈልገኝም ይልቅ አንተ በርታ በሳል ልጅ ነህ ለሁሉም ነገር የምትሰጠውን ዋጋ ሳላደንቅ አላልፍም ። ጊዜሄን የምትሰጥለት ፍልስፍናህ ያስገርመኛል " አለውና ትከሻውን መታ መታ አደረገው " መቅደላዊት ምህረቱን ያምጣልሽ ይሻልሽ" አለ እና ወጣ ዶክተርም በተመሳሳይ መልካም ምኞቱን ተመኝቶ ከመምህር ኄኖክ ጋር አብረው ሔዱ። " መቅዲ አሁን እንዴት ነሽ? "አለ ባሩክ የተኛችበት አልጋ ላይ እየተቀመጠ: ፈገግ አለች " ተሽሎሻል ማለት ነው? "አለ እሱም ለፈገግታዋ ፈገግታ እየመለሰ " ልክ ነህ በጣም ድኛለሁ " አለች " ጥሩ አሁን የሚጠጣ ወይስ የሚበላ ምን ላምጣልሽ? " አለ " ምን ማምጣት የሚያስችል አቅም አለህ ኪስህ ላይ ስንት ብር አለ?" አለች መቅደላዊት እየሳቀች " ሃሃሃ አንቺ ምን ያህል መጠጣት ወይም መብላት የሚያስችል አቅም አለሽ? " አለ እየሳቀ ወደ ናታኔም ዞሮ ። ናቲየ ሚበላ አልበላህማ ለሁለታችሁም በቃ ቴካዌይ ይዤ ልምጣ ብሎ ወጣ ። " ግን ባሩክን እንዴት አወከው?" አለች መቅደላዊት ናታኔምም ሳቅ እያለ ባሩክ ጋር አንድ ሰፈር ነን እና ሲበዛ በጣም አስተዋይ እና ጎበዝ ነው። አዲስ ነገርን ለመፍጠር ወደ ኋላ የማይል አዛኝ ሩህሩህ ልጅ ነው ሰፈር ላይ ከሁሉም ልጆች እኔ ብቻ ነኝ የምቀርበው ሌሎቹ ይሄ ንቅል ነው ስለሚሉ አይቀርቡትም በዛ ላይ ነገሮችን በጥልቀት ስለሆነ ሚያየው ወግ አጥባቂ ነው ።በዚህ አድራጎቱም አይወዱትም ከዛ በኋላ እሱ ዩኒቨርሲቲ ገባ ይሄው እኔ ዘንድሮ ስመጣ ተቀበለኝ ጊቢውን በደንብ አስጎበኘኝ አላመደኝ ብዙ ነገሮች ላይም በሐሳብ ይረዳኛል። ይሄው እንደምታይው ነው እዚህ ድረስ ነው ባሩክ ማለት እና በአጭሩ የባሩክ ነገር በትንሹ ይሄን ይመስላል። የሰፈሬ ፈላስፋ ነው እሽ " አለና ሳቀ ። " የእውነት ይገርማል እኔ እንደዚህ አልጠበኩትም በጭራሽ ለነገሮች ደንታ የሌለው በራሱ አለም ብቻ የሚንቀሳቀስ ፣ ሰው ይመስለኝ ነበር እሽ ሰውን ለካ እንዲሁ መገመት ጅልነት ነው።" አለች አይኖቿን ወደ ጣራው እየላከች። ባሩክ ምግብ ገዝቶ የሀይላንድ ጁስ ገዝቶ " ይሄው የመብላትና የመጠጣት አቅም ያላችሁ ሰወች እነሆ ምግቡም ያው መጠጡም ያው " አለ ወምበሩን ጠጋ እያደረገ ናቲ ታጠብና ብላ እንጅ ምን ምግቡን አይናይኑን ታየዋለህ እኔ ስለበላሁ መቅደላዊትን ላጉርሳት ነው በእጅሽ ትበያለሽ?" አለ " በእጄ እበላለሁ" አለች " መልካም ስራ አቀለልሻ " አለ ። በዚህን ጊዜ ዶክተሯ ገባች " እሽ መቅደላዊት አሁን እንዴት ነሽ ሁሉ ሰመም ራስ ምታቱ ቀለል አለሽ?" አለች ዶክተሯ " አወ ግን ድካም ድካም የሚለኝ ነገር አልተወኝም። ለመነሳትም ምንም ስፈልግ ይደክመኛል "አለች " እሱማ በምግብና በመጠጥ ነው ሚለቅሽ እሱ ብቻ ነው እሚሰማሽ?" አለች " አወ ዶክተር እሱ ብቻ ነው እንጂ ሌላው አሪፍ ነው። " " ጥሩ ስለዚህ ምግብ እና መጠጥ በደንብ መውሰድ አለብሽ ስለዚህ ትንሽ ቆይተሽ ከአንድ ስአት በኋላ መውጣት ትችያለሽ " አለችና ትታቸው ወጣች። * ሙሉ ጊቢው ስለ መቅደላዊት ጉዳይ ይወያያል ገሚሱ " ይቺ ማትረባ ኩራቷ አይጣል ነበር እስኪ አሁን እናያታለን" ይላሉ ሌሎቹ ደግሞ " ውይ እሷ ልጅ እንዴት እንደምታሳዝን ምንም ባላደረገችው ነገር ነው አሉ ። ምን አደረገችው አሁን ይሄ ቆሻሻ መምህር ቅንዝራም ሴሰኛ ይሄኔ ኮ ሌላ ነገር ፈልጎ ነው የሚሆነው አያፍር ይሆናል" ይላሉ አንደኛዋ እንዲህ አለች " የእሷ ሳይሆን የገረመኝ ስለ እሷ የተከራከረው ልጅ እና ሄዱንና ፈታኙን ያፋጠጣቸው ልጅ ነው ።" አለች " እ ዲዮጋን ነው " አለች ሌላኛዋ አወ እሱ ፈላስፋው "አለችና ከት ብላ በረጅሙ ሳቀች ። እኔ የእሱ ልጅ ሁኔታው እና ድርጊቱ ያስገርመኛል ። ማለቴ እኔ በግሌ ለመቅደላዊት ባደረገላት ነገር ተገርሚያለሁ። ማንም ወንድ እንዲህ አያደርግም እራሱን ሪስክ አስገብቶ እንዲህ ሚሆን አላቅም የእውነት ጀግና ነው "አለች ሌላኛዋ " ግን ወዷት ቢሆንስ " አለች አንደኛዋ ዝም ብላ ስታዳምጣቸው ከቆየች በኋላ ሁሉም በአንድ ላይ" እ" አሉና ተያዩ ፈላስፋው ሊያፈቅር? ሃሃሃሃሃሃ" አለች አንደኛዋ እንዴት አያፈቅር እሱም እኮ እንትን ያምረዋል ጥማቱ በፈላስፋወች አይበልጥም ብለሽ ነው ብላ ሌላኛዋ መለሰችላት! አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 43♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

" #መቅደላዊት #ክፍል_41 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ " ሁሉችሁም ስለ መቅደላዊት status ስለምታውቁ ትመሰክራላችሁ ። በትምህርቷ የተሻለች እና ዩኒቨርስቲው አሉኝ ከሚላቸው ሰቃይ ሴቶች በባቿ ግምባር ቀደሟ እንደሆነች ።ስለዚህ ጉዳዩን ወደ ላይ ይዤው እሄዳለሁ ጥፋተኛ የሆነ በሙሉ መቀጣት አለበት። እሷ ደግሞ ምንም አይነት የጥፋት ስራ አልሰራችም" አለ ባሩክ በእልህ ወደ ፈታኙ መምህር አይኖቹን እየላከ " አንተ ልጅ እባክህን ውጣ እነሱ ይፈተኑበት እኔም ስራየን ልስራበት " አለና ገፋው ባሩክን ፈታኙ መምህር በጣም ተናዶ ስአታችሁ እያለቀ ነው?" አለና ለዲፓርትመንት ኃላፊው ደወለና " አንድ የማላቀው ጥጋበኛ ተማሪ መጥቶ እያስፈራራኝ ነው እና በአስቸኳይ እንድትመጣ እፈልጋለሁ " ብሎ ስልኩን ዘጋው። መምህር ኄኖክ መፈተኛ ክፍል ደረሰ ዲዮጋን እንዳየው አወቀው ብዙ ጊዜ የስነፅሁፍ ምሽት ይታደማል እናም የፊት ወንበር ላይ ይቀመጣል። ባሩክ ( ዲዮጋን ) ለመምህር ኄኖክ እጁን ዘረጋለት ። ኄኖክም አንተ ነህ የደወልክልኝ? አለው " አወ እኔ ነኝ መምህር ኄኖክ በሩን ቆረቆረ ፈታኙ መምህር ከፈተና " አንተ ደግሞ ማን ነህ ማነው የላከህ ያች ጥጋበኛ ናት ምን ልታዘዝ?" አለ " እኔ የምትፈትነው ኮርስ ሌክቸር ነኝ ስለዚህ ስለትምህርቴ መጠየቅና ማወቅ ያለብኝን ለመጠየቅ ነው የመጣሁት " አለና ገባ ባሩክም ተከትሎት ገብቶ ያውና እዛ ነው የተቀመጠችው የፈረመባትም ይሄን አይቶ ነው!" አለ ባሩክ መምህር ኄኖክ formulawn አየው ባሩክ እንዳለው የmechanics ቀመር ነበር። ኄኖክም ወደ ፈታኙ ጠጋ ብሎ "የዚህ ጊቢ አስተማሪ ነህ ወይስ ከቅርንጫፍ ኮሌጅ ነው የመጣኸው?" አለ " የዚህ ጊቢ አይደለሁም ፈትን ተብየ ነው የዲፓርትመንት ሄዱ ቅድም መጥቶ ነበር እናም ልክ ነው የፈረምከው ብሏል እሱ እየመጣ ስለሆነ እሱ ጋር ጨርስ " አለ እንዲህ እያወሩ ባለበት ጊዜ ሄዱ መንግስቱ መጣ። ምንድነው ኄኖክ መቅደላዊትን የውሸት ፊርማ ለምንድነው ልክ ያልከው እሱ ትክክል እንዳልሆነ እያወክ" አለ ኄኖክ " እንደዚህ ለእኔ በመመለስህ ትልቅ ትልቅ ዋጋ ትከፍላለህ አሁን ፈታኙ ስራውን ሰርቷል እናንተ ግን ውጡ አንተም ከዚህ በላይ መቆየት አትችልም ከዚህ በኋላ ፈተናህን ለመውሰድ ቢሮ ብቻ ነው ምንገናኘው!" አለ ሄዱ መንግስቱ " እህ ሐጀመሪያ ጥያቂያችንን መልስ የምን በወንበር ማስፈራራት ነው ለምንድነው ልክ ያልሆነውን ልክ ነህ ያልከው??? መልስልን " አለ ባሩክ እንዴት እንዴት ነው ምትናገረው?" አለ አቶ መንግስቱ " ምንም አላልኩም እኔ የጠየኩህ ለምን መምህሩን አላረምክም በዛ ላይ በጊቢ ቆይታየ የአንድን ዲፓርትመንት ተፈታኝ ከሌላ ጊቢ መጥቶ አይፈትንም የዲፓርትመንቱ አስተማሪዎች ከአንደኛ አመት እስከ አምስተኛ አመት ያሉት መምህራን ናቸው እየተቀያየሩ የሚመደቡት ስለዚህ ይሄን መምህር ከሌላ ኮሌጅ አምጥተህ ማስፈተንህ ሳይቀር ይበልጥ የሚያስገርመው በቸልተኝነት የአንዲትን ልጅ ህይወት ሊያበላሽ የሚችልን ድርጊት ባላየ ለማለፍ መሞከርህ ነው። አሁን ጉዳዩን ወደ አካዳሚክ ጉዳዮች ይዠው እሔዳለሁ " አለና ስልኩን አውጥቶ ደወለ " ሄሎ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ቢሮ ነው?" አለ ባሩክ " አወ እርሰዎን ማን ልበል አለች ፅሀፊዋ " ባሩክ እባላለሁ ዶክተር እስጢፋኖስን ፈልጌ ነበር " አለ " በሰላም ነው የፈለከው ? "አለች " በሰላም አይደለም የፈለኩት መፈተኛ ብሎክ አካባቢ ችግር ነበር እና አሁነኑ ለአይን እማኝነት ፈልጊያቸው ነው " አለ ባሩክ " እሸ አንዴ ጠብቀኝ ለዶክተር ላሳውቃቸው " አለች ""መልካም " አለና ጠበቀ ከአንድ ደቂቃ በኋላ ዶክተር እስጢፋኖስ ስልኩን አንስተው " አቤት ዶክተር እስጢፋኖስ ነኝ ምን ነበር ችግሩ "አለ ባሩክ የተፈጠረውን ችግር በሙሉ ነገረውና ይበልጥ ደግሞ በአካል ቢገኝ ሁሉንም ማየት ይችል ዘንድ አስረዳው ። ዶክተር እስጢፋኖስ መፈተኛ ብሎክ ደርሶ ሁኔታውን በአይኑ አየ። ዶክተር እስጢፋኖስ ሁሉንም በአይኑ ካየ በኋላ የዲፓርትመንት ሄዱን ከላይ እስከ ታቹ ከገላመጠው በኋላ ወደ ፈታኙ ዞሮ አንተም አንተኛውም ከስአት ቢሮየ እንድትመጡ! አሁን መቅደላዊት የታለች " አለ "እ ራሷን ስታ ሀኪም ቤት ነች" አለ ባሩክ ፍፁም በሆነ የሀዘን ስሜት " አሁን ታዲያ በምን ሁኔታ ላይ ነች? " አለ በድጋሚ ዶክተር እስጢፋኖስ " አላውቅም ጓደኛየን እዛ ትቼው ነው የመጣሁት ጉዳዩን ለማጣራት " አለ ባሩክ " መልካም! በል ወደ ክሊኒክ ውሰደኝ!" አለ ዶክተር እስጢፋኖስ! "እሽ ዶክተር "አለና ባሩክ መንገድ ሲጀምሩ " እኔም አብሪያችሁ መምጣት እፈልጋለሁ " አለ መምህር ኄኖክ ናታኔም በጭንቀት ወዲያ ወዲህ ይላል አንዳንዴ ስለ ናሆም በጠነሰሰው ሀሳብ ይመስለዋል መቅደላዊት እንዲህ የሆነችው። በሌላኛው ልቦናው ደግሞ" አሁን የደረሰባት ነገር በምን ምክንያት ነው ከእኔ ጋር የሚያገናኛት አይ አይደለም ሁኔታው ለየት ያለ ነው። ግን ምንም የማታውቅ ልጅ ላይ እንዲህ መድረሱ ያናድዳል። " ካለ በኋላ እጆቹን ሽቅብ ዘርግቶ ፈጣሪውን ይለማመን ጀመር "እባክህን አምላኬ ሆይ አደራህን ከክፉ ሁሉ ነገር ጠብቃት " ምናምን እያለ ዶክተሯ ጠራችው " አቤት ዶክተር " አለ " "መቅደላዊት ነቅታለች ጊዜያዊ ጭንቀት ነው ምንም አትሆነም ደህና ነች አሁን ግን በተረጋጋ መንፈስ መሆን ስላለባት ለጠየቀቻችሁ ሁሉ አዎንታዊ ምላሽ ነው መስጠት ያለባችሁ ጥሩ ጥሩ ነገሮችን ብቻ ነው ልትነግሯት የሚገባው። ለጊዜው ትንሽ እዚህ ትቆይና መሔድ ትችላለች " አለችና ዶክተሯ መቅደላዊት ወደተኛችበት ክፍል እንዲገባ እየጠቆመችው ትታው ሔደች። ናታኔም ወደ ውስጥ ቀስ እያለ ገባ ሰው እንደገባ ስታውቅ መቅደላዊት አይኖቿን በቀስታ ገለጠቻቸው። ናታኔም አንጀቱ ተላወሰ አሳዘነችው። ፍዝዝ ብሎ ተመለከታት። መቅደላዊት አይኖቿን ናታኔም ላይ አንከራተተቻቸው። ናታኔም አይኖቿን በአይኖቹ ተከተላቸው ።" ማነው ከዚህ ያመጣኝ? " አለች በቀስታ " ባሩክ ነው " ብሎ ዝም አለ እንዴት ባሩክ እንዳገኛትና ምን አይነት ስሜት በወቅቱ እንደነበራት ባሩክ የነገረውን ሊነግራት ፈልጎ ከእንደገና የዶክተሯ ምክር ትዝ ብሎት ተወው ። " እና አሁን የት ሔዶ ነው? " አለች አሁንም በተሸነፈ ድምፅ " እ እ አ አለ ወጣ ብሎ ነው ይመጣል!" ብሎ ዝም ሲል በሩ ተንኳኳ አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 42♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ክፍል_40 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ባሩክ የነ መቅደላዊት መፈተኛ ህንፃ ፊት ለፊት ከተሰራው ግምብ ሰራሽ መቀመጫ ተቀምጦ " የሐበሻ ጀብዱን " መፅሀፍን ያነባል ። በዚህ መሀል ስልኩን አወጣ እና ሲያየው ገና 2:30 ይላል ።" ገና ነው ዝም ብየ ስቻኮል ነው የመጣሁት ብሎ ወደ ህንፃው ሲያይ መቅደላዊትን ተመለከታት ግራ ተጋባ " እንዴት በዚህ ቅፅበት ልትወጣ ቻለች ? ጨርሳ?? ወይስ " አለ ። ተነሳና ወደ እሷ ሄደ ። መቅደላዊት አይኗ ተስለመለመ እግሮቿ ተጠላለፉ ።መቅደላዊት የባሩክ ክንድ ላይ ተዘረረች ራሷን ሳተች። አቀፋት አይኖቿ ተከደኑ ትንፋሿ ጠፋ። ባሩክ ደነገጠ ክንዱ በድን የያዘ መሰለው። " እርዱኝ እርዱኝ" አለ ነገር ግን አንድም የሰማው አልነበረም። እንደምንም አዘላት እና ወደ ዩኒቨርስቲው ክሊኒክ ይዟት ደረሰ። ድንገተኛ ክፍል ውስጥ አስገባት። " እንዴት እንዲህ ልትሆን ቻለች? ፈተና ክፍል ምን ተፈጥሮ ነው? ተፈርሞባት?? እንዴት ምን ስታደርግ ። ባሩክ ጥያቄውን ማመላለስ ጀመረ። ባሩክ ስልኩን አውጥቶ ለናታኔም ደውሎ የተፈጠረውን ነገረው። ናታኔም ከትንሽ ደቂቃ በኋላ ክሊኒክ ደረሰ " ባሩክ ምን ሆና ነው?" አለ ናታኔም " ዓላውቅም እየጠበኳት ነበረ ከዛ ድንገት ቀና ስለ አየኋት ግራ ተጋባሁ እንዴት በዚህ ስአት ልትወጣ ቻለች ብየ ራሴን እየጠየኩ ሳለ ራሷን ሳተች። ከዛ እንደምንም ይዣት መጣሁ ይሄው ነው።" አለ ባሩክ " አሁን እኔ መፈተኛ ክፍል ሄጄ የሆነውን ማጣራት ይኖርብኛል እና አንተ እስክትነቃ እዚሁ ጠብቅ ስትነቃ የምትፈልገውን ስጣት የትም እንዳትሄድ" አለና ባሩክ ወጥቶ ውጭ ላይ ቆመ!! ባሩክ የሚይዘው የሚጨብጠው ያጣ መሰለው ውስጡ ስለተፈጠረው ነገር የማወቅ ፍላጎቱ ናረ። ምን ማድረግ እንዳለበት ቆም ብሎ ለሁለት ደቂቃ ያህል ካሰበ በኋላ ወደ አንድ ውሳኔ ደረሰ። ነገሮቹን በሙሉ መጋፈጥ እንዳለበት መቅደላዊትን ካለችበት ችግር ማውጣት። ግን ምን አይነት ስራ ሰርታ ይሆን? ለሌላ ተማሪ መልስ ስትሰራ? ተይዛ ይሆን ወይስ ተሳስታ አጤሬራ ይዛ ይሆን ወይስ ስልኳ ጮሆ ነው? ምን ሆና ይሆን መቅደላዊት ነቅተሽ ሁሉንም ከአንቺ አንደበት በሰማሁት እባክሽን ክፉ እንዳይነካሽ ምንም እንዳትሆኚ አንቺ መልካም ሴት እናቴ በቸር ትጠብቅሽ ። ደግሞ እሷ እናትሽ ጥላ አጥልሽም የማይተኛ የማያንቀላፋ መድኃኔዓለም አለልሽ ምንም አትሆኚ ደህና ትሆኛለሽ ለአንቺ ሞት የደገሰው ለራሱ የቁም ተዝካር ይሆናል።" ይሄን ሁሉ ካለ በኋላ እንደመገረም አለና " ባህታዊ ሆንኩኝ መሠል አለና ሳቅ አለ ። ይሁን ምንም ፈልጌ ሳይሆን ከሷ ግን ደህና ብትሆን ብየ ነው መቅደላዊት ማለት እኮ ለማታቀው ልጅ ስትል አላማዋን እና ፍላጎቷን ወደ ኋላ ብላ ለበጎ ነገር የማታቅማማ ምስኪን ልጅ ናት እውነት ይቺ ልጅ ይህ አይገባትም!!" አለ ይሄን ካለ በኋላ እስኪ ደግሞ አሁን እንውረድና ጉዳቸውን እንይ መቼስ እኒህ መምህራን ውስጣቸው አይታወቅ ይሄኔ ቆንጆ ስለሆነች እንድትለምነው ፈልጎ ይሆናል።" አለና ወደ መፈተኛ ብሎክ አመራ። ባሩክ የመቅደላዊት መፈተኛ ክፍል ሲደርስ አንዳንድ ተማሪዎች እየወጡ ደረሰ። አንደኛውን ተማሪ ጠጋ ብሎ " ይቅርታ የኔ ወንድም" ብሎ ነካ ሲያደርገው ልጁ ዞረ " እንዴ ዲዮጋን በጣም ነው ስራወችህን የምወዳቸው ፍልስፍናህም ለዛ አለው በዛ ላይ አቀራረብህ ደንታቢስነት ህይወትን የምታይበት መነፀር ቃላቶችህን በጣም ነው ምወዳቸው"" አመሰግናለሁ ወንድሜ አንድ ነገር ላስቸግርህ?" " ምን ችግር አለው?"አለ " መቅደላዊት ምን ሆና ነው እስኪ ስለተፈጠረው ነገር ንገረኝ" አለ " አላውቅም ግን እሷ ይሄ ከምማረው ትምህርት ጋ አይገናኝም ስህተት ነው ይሄ የአምና ፎርሙላ ነው ስትለው ዝም ብሎ ፈረመባት" አለ ልጁ " የት አካባቢ እንደተቀመጠች ልትነግረኝ ትችላለህ?" ችግር የለውም ግን እኔን መምህሩ አያስገባኝም " አለ " እኔ ጋ እንገባለን እቃ ረስታ ነው እንለዋለን " አለ ባሩክ " እሽ እሽ ካለን።" ብሎ በሩን ቆረቆረ " ምንድነው አለ " መምህሩ " ባሩክ በተረጋጋ አነጋገር ይቅርታ መምህር መቅደላዊት እቃ ረስታ ስለወጣች የተቀመጠችበት ወንበር ላይ ለመውሰድ ነበር " አለ " ራሷ መጥታ ትውሰድ " አለና በሩን ዘጋው " አላልኩህም ወንድሜ ዲዮጋን በጣም መናጢ ነው " " ይሄ መናጢ ሳይሆን እረኛ ጋጠወጥ ነው " አለና ባሩክ በሩን ራሱ ከፍቶ ገባ " ምን አይነት ንቀት ነው አልፈቅድም እያልኩህ የምትገባው ?" አለ መምህሩ በዲዮጋን ድፍረት ተበሳጭቶ ዲዮጋን ዝም ብሎ ተራመደ ወደ መቅደላዊት መቀመጫ ከኋላ መምህሩ ያዘው ባሩክ ዞረ። ተማሪዎች መስራታቸውን ትተው ትርኢቱን መከታተል ጀመሩ ። ዲዮጋን ዞሮ ልቀቀኝ አለና እጁን ከሹራቡ አላቆ "ፈቃድህን ለማግኘት እና አክብሮቴን ለመግለጽ ነበር የጠየኩህ አንተ ግን ምላሽህ ጋጠወጥነት የተሞላበት ነው።" አቤት ምንድን ነው ያልከኝ ጋጠወጥ እኔን?" አለ መምህሩ እጁን ወደራሱ እየጠቆመ " አዎ አንተ ባትሆንማ በር አትዘጋም በዛ ላይ ለምን መምጣት እንዳልቻለች እና እኛ ለምን የሷን እቃ ልንወስድ ነው ስንልህ መምጣት ያልቻለችው ምን ሁና ነው ብለህ እኛን ከመጠየቅህ በፊት እሷ ካልመጣች ብሎ በር መዝጋት ታውቃለህ እስካሁን ቢያንስ ከአርባ በላይ መምህራን አስተምረውኛል እንደ አንተ አይነት መምህር ግን አጋጥሞኝ አያቅም በል አሁን የፈረምክበትን ምክንያት ላጣራው ነው ። እስኪ እናያለን " ብሎ ከእግር እስከ ራሱ ተመለከተው ባሩክ መቅደላዊት ወንበር ላይ ተቀመጠ ግድግዳውን ሲመለከት ያየውን ማመን አቃተው ። ፎቶ ደጋግሞ አነሳውና ብድግ ብሎ ተማሪዎችን አንድ በአንድ እየተመለከተ " አሁን የፈረምክበትን ምክንያት አየሁ በዚህ ምክንያት እንደሆነ እርግጠኛ ነኝ ሌላ ምክኒያት አለህ ?" አለ ባሩክ " የለኝም!!!!!" አለ መምህሩ በማን አለብኝነት " ይህ ለመፈረምህ ምክንያት አይሆንም ምክንያቱም ፎርሙላው ቀመሩ የሁለተኛ አመት hydraulics ኮርስ ፎርሙላ ሳይሆን የአንደኛ አመት የ engineering mechanics ኮርስ ፎርሙላወች ናቸው ግድግዳው ላይ ያሉት ይሄ ደግሞ መቅደላዊት ላይ አያስፈርምባትም። አሁን ስህተትህን ትቀበላለህ ወይስ?" አለ ባሩክ" ባልቀበልስ?" አለ መምህሩ እጁን ከኪሱ እንዳስገባ " ካልተቀበልክማ አንደኛ ከስራ ትባረራለህ ሁለተኛ የሞራል ካሳ ትከፍላለህ ሶስተኛ ራስህን ታጣለህ አራተኛ የገዛህን ሰው አለያም የተገዛህለት አላማ ራሱ ይፋረድሀል።አለና ተማሪዎች representative ማነው?"አለ አንዱ ከመሀል እጁን አወጣ " እሽ አንተ ነህ እስኪ የዚህን ትምህርት አስተማሪያችሁን ስልክ ስጠኝ የ hydraulics መምህራችሁን " አለ ባሩክ " እሽ 0913...... " አመሰግናለሁ ወንድሜ " ባሩክ ከክፍሉ ወጥቶ ለመምህሩ ደወለለት። መምህር ኄኖክ በሁለተኛው ጥሪ አነሳው " ሀሎ " " ሰላም ነው መምህር ባሩክ እባላለሁ ፈልጌህ ነበር " " በሰላም ነው የፈለከኝ?" " አይደለም መቅደላዊት " መቅደላዊት ምን ሆነች " ባሩክ ሳይጨርስ መምህር ኄኖክ ጠየቀው " ባላደረገችው ነገር ተፈርሞባታል እና ፈታኙም ምንም በስርዓት እያወራኝ አይደለም መቅደላዊት ደግሞ በአሁኑ ስአት በሁኔታው ራሷን ስታ ሆስፒታል ነች እስካሁን አልነቃችም እና ናና እኔ ያየሁትን እውነት እንድታይ እፈልጋለሁ ። " አለ ባሩክ ሳግ እየተናነቀው " አሁኑኑ መጣሁ " አለ ይቀጥላል ..........

#መቅደላዊት #ክፍል_39 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ "ናሆም የጠረጠረ ይመስለኛል ከመቅደላዊት ጋር ስለ እሱ ሳወራ ድንገት ገባ ከዛ ከማን ጋ ነው ስለእኔ ምታወራው እና ስል የሰማውን መልሶ እኔን እየጠየቀ አፋጠጠኝ የምለው ጠፋኝ በመጨረሻ ከሜላት ጋር ነው አልኩት ግን ሜላትን ከስም ውጭ አላቃትም ምን እንደሚሻለኝ አላውቅም በእርግጠኝነት ደግሞ አግኝቶ ይጠይቃታል " አለ እና ናታኔም እምባው መጣ " እና አሁን እሷን እንዴት ነው የማገኛት? " " ደውልላት " አለ መርዕድ ናታኔምም ባሩክም በድንጋቴ አንድ ላይ ወደ መርዕድ አፈጠጡ ለተወሰነ ጊዜ ካዩት በኋላ ደግሞ እርስ በእርሳቸው ተያዩ ። " አውቃለሁ ግራ እንደምትጋቡ እንደተጋባችሁም ግን ሜላትን አውቃታለሁ የመጀመሪያ አመት እያለች በጣም እወዳት ነበር በጣም አፈቅራታለሁ እሷ ግን ሲበዛ ኩሩ እና ፊቷ የማይፈታ ከባድ ልጅ ነበረች። በመመረቂያ አመቴ ጉድ ሰራችኝ በውበቷ ነሁልየ ለአራት አመት ፍቅር ያልያዘኝ ልጅ በስተመጨረሻ ለእሷ ተምበረከኩ እጅ ነሳሁ ፣ በፍቅሯ ግብዝነቴ አይበገረነቴ ተረታ፣ ከአንድ ሁለት ጊዜም በላይ ጠየኳት ነገር ግን ምላሿ አንገት የሚያስደፋ ነበር ። በእርግጥ በወቅቱ ከሌሎች ጓደኞቿ ስሰማ ለተመራቂ ተማሪ ፊቷን የማትፈታው ተጠቅሞ ለመውጣት ነው የሚፈልገው ብላ ስለምታስብ ነው። የሚል ወሬ ሰማሁ ። ይሄን እንደሰማሁ የልቤን እውነት ላስረዳት ሞከርሁ ምላሿ ግን ምንም ነበር ጀርባዋን ሰጠችኝ ተሰቃየሁ ብዙ ጊዚያትን ራሴኔ መሆን አቃተኝ ነገር ግን በስተመጨረሻ በጓደኞቼ እገዛ ወደ ራሴ ዞርሁ ራሴን መመልከት ጀመርሁ። የመመረቂያ ፅሁፌን መስራት ጀመርኩ። በሂደት ፀባይዋን ሳይ ግራ ተጋባሁ እኔን ስታይ ዛር እኔዳለበት ሰው ያጓራት ጀመር። ቀስ በቀስ ልረሳት ጣርኩ ነገር ግን አልቻልኩም። በድጋሚ ተሸነፍኩ። እስካሁን ድረስ ያሸነፈችኝ እሷ በመሆኗ በተሸነፈው ልቤ ዛሬም ነግሳለች። አሁንም አፈቅራታለሁ ማስተርስ እዚህ ለመማር ያለምኩበት አንደኛው ምክንያቴ እሷን የራሴ ለማድረግ ነው። ለዚህ ሀሳቤ ደግሞ እናንተም እንድትረዱኝ እፈልጋለሁ" አለ መርዕድ የባሩክ አይኖች ተበለጠጡ የናታኔም ደግሞ በሰመመን እንዳለ ሰው አይኖቹ ተከደኑ። ግራ ተጋቡ። ባሩክ ራሱን እየነቀነቀ ፈገግ አለና " ህ ይገርማል! አዝናለሁ ወንድሜ መርዕድ ይህ ሁሉ ስለደረሰብህ " ብሎ ባሩክ ዝም አለ። ናታኔም ዝምታን የመረጠ ይመስላል ። " አሁን እኔ ልደውልላትና ላግኝሽ ልበላት ከሰው ጋ ነኝ ካለች ናሆም ጋር ነች ማለት ነው ስለዚህ መፍትሔ ወደ ምንለው ሀሳብ እንሔዳለን ማለት ነው።" አለ መርዕድ " ጥሩ መልካም ሀሳብ ነው ደውልላት " አለ ባሩክ። ስልኩን አውጥቶ ደወለ ።በሶስተኛው ጥሪ ሜላት ስልኳን አነሳችው " ሄሎ መርዕድ እንዴት ነህ? " አለች ሜላት " ደህና አንቺ እንዴት ነሽ?" "አለሁልህ ጠፋህ እደውላለሁ ብለህ" " ኧረ አለሁ የት እሄድ ብለሽኝ ያው አንዳንድ ነገሮችን እስክጨርስ የው እንጅ አሁን የት ነሽ ላገኝሽ ፈልጌ ነበር? " " ውይ መርዕድ አሁን እንኳ አልችልም ከጓደኛየ ጋ ነኝ!" " እና ጓደኛሽን አታስተዋውቂኝም?" " የሴት አይደለችም የወንድ ጓደኛየ ነው ሌላ ጊዜ ግን አገኝሀለሁ " " እሽ በቃ እንዳልሽ " " ይቅርታ በጣም!" ችግር የለውም ስልኩን ዘጋው። "ይሄው ከናሆም ጋ ነች " አለ መርዕድ " በእርግጠኝነት እንዳወራኋት እና እንዳላወራኋት ጠይቋታል ።እሷን እንዳለወራኋት ደርሶበታል ወይኔ ተበላሁ " አለ ናታኔም " ቆይ እስኪ ተረጋጋ " አለ ባሩክ ወደ ናታኔም ዞር ብሎ ዝም እንዲል በእጁ ምልክት እየሰጠው። " አሁን ለመቅደላዊት አንነግራትም ሁለታችሁም ፈተናችሁን ጨርሱ ስንት ፈተና ቀራችሁ?" " ሁለት "አለ" " ጥሩ አሁን እንሂድ አንተ አምብብ እኔ ትንሽ ላስብ አለ " ነገ ፈተና አላችሁ አይደል?" " እኛ የለንም ግን መቅደላዊት አላት " አለ ናታኔም " በቃ እንደነገርኩህ ለእሷ ምንም አትንገራት ። እኔ ነገ ከፈተና ስትወጣ ጠብቄ አወራታለሁ አግኝቻትም ስለማላውቅ " አለ ባሩክ " እሽ እንዳልክ " አለ ናታኔም ሁላቸውም ከተፈጥሮ ህንፃ ወረዱ። ** "ሀጤሬራ የያዛችሁ ጣሉ ስልካችሁን አጥፉ " ሁላችሁም የራሳችሁን ስሩ ወዲያ ወዲህ ስትሉ ባገኛችሁ ወደ ኋላ አልልም እፈርምባችኋላሁ ። ልመና እኔ ጋ አይሰራም ይህ ትምህርት ከተፈረመባችሁ አንድ አመት ነው ከህይወታችሁ የምትቀንሱት ። ነግሪያችኋለሁ፡ " አለ ጠቆር ብሎ ወፈር ያለው ፈታኝ መምህር ። ሁሉም ተማሪ በተጠንቀቅ ተቀምጧል። በየመሀላቸው የሁለት ወንበር ክፍተት አለ ።መቅደላዊት ከመጀመሪያው ረድፍ ሶስተኛው ወንበር ግድግዳ ተቀምጣለች። የፈተና ወረቀቱ ታደለ። " ጀምሩ ሳልላችሁ እንዳትጀምሩ ነግሪያችኋለሁ " ብሎ ቀይ እስክርቢቶውን ከደረት ኪሱ አውጥቶ መዞር ጀመረ። ሁለት ዙር ከዞረ በኋላ የእጅ ስአቱን ተመለከተ። " አሁን መጀመር ትችላላችሁ " አለ ሁሉም የፈተና ወረቀታቸውን ገለበጡ ። መምህሩ አይኑ በሁሉም አቅጣጫ ያማትራል። ወደ መቅደላዊት አቅጣጫ ፊቱን ላከ፡ መቅደላዊት አንገቷን አቀርቅራ ትሰራለች ።ፈታኙ በቀስታ ወደ እሷ አቅጣጫ ተራመደ ።እንደደረሰ ያለችበትን ግድግዳ በአይኑ ሲያስስ ከላይ ጀምሮ የ moment of inertia formula እና የ centroid part formula ተፅፎበታል። መመህሩ መቅደላዊት በእጁ ጎንተል አደረጋት ። ቀና አለች ።ወደ ግድግዳው ሌባ ጣቱን እያመለከተ። " ይሄ ምንድን ነው?" አለ " አላውቅም " አለች " ኢዲየት ፎርሙላ ግድግዳ ላይ ፅፈሽ ትሰሪያለሽ አንቺን ብሎ ተማሪ አንቺን ብሎ የነገ ሀገር ተረካቢ ። አንቺ ነሽ ተመርቀሽ የዚችን ውስብስብ ሀገር ችግር የምትፈችው እንደ አንቺ አይነቶቹ ተመርቀው ነው ህንፃ ሰራን ብለው ህንፃው ወር ሳይሞላው እየተደረመሠ ንፁሃንን የሚቀጠፉት " አለና የመልስ ሽቷን ብድግ አድርጎ ወዲያማዶ ካለው ባዶ ወንበር ላይ አስደግፎ ቀይ እስክርቢቶውን ከደረቱ አውጥቶ ከንፈሩን እየነከሰ ፈረመባት " በቃ ምን ያስቀምጥሻል ውጪ አለ!!! " ፈርሞ ሲጨርስ መቅደላዊትን በንቀት እያዬ " ምንድነው የምትለው መመህር ይሄ ፎርሙላ እኮ አሁን የምንፈተነው ትምህርት አይደለም። ምንም አያገናኘውም " አለች ከወንበሯ ሳትነሳ ። " እሱን ለሚያምንሽ ሂጅ እና ንገሪው " " እህ ለምን የምልህን ታምናለህ የምታየውን ማመን ስትችል " አለች ።" አሁን ልፈትንበት አትረብሽኝ ውጪልኝ " አለ ፊቱን እያኮሳተረ ። መቅደላዊት የግድግዳውን ፎርሙላ ደግማ አየችው እሷ ከምትፈተነው የ hydraulics 1 ፈተና ጋ አንዱም ፎርሙላ አይዛመድም ግራ ተጋባች። እያለቀሰች ወጣች ሁሉም ወደ እሷ ዞረ ። " በሉ የራሳችሁን ስሩ " አለ ወደ መቅደላዊት የዞሩትን ተማሪወች ወደ ፈተናቸው እንዲያተኩሩ ። መቅደላዊት ስትገባ በሩ ጋ አስቀምጣው የነበረውን ስልክ አወጣችና ለሚያስተምራት መምህር ደወለች። መምህሩ ስልኩን አያነሳም አቅራቢያ ካሉት ሌሎች ክላሶች ብትዞር አጣችው። በመጨረሻ የዲፓርትመንት ሄዷን አገኘችው። ጉዳዩን በዝርዝር አስረዳችውና ወደ መፈተኛዋ ክፍል ይዛው ሄደች ። ግድግዳውን አሳየችው ፈታኙአን አወራው ። ፈታኙ ተመናጨቀ ሄዱም ትቶት ወጣ። መቅደላዊት ተስፋዋ እንደ ጉም ተኖ ሲጠፋ ታያት። ያለችበት ሁሉ ዞረባት። በደመነፍስ ትራመዳለች። እግሮቿ ተያያዙ ። ጉልበቷ ራደ ልቧ ሲደክም ታወቃት። ደረጃውን እየተወላከፈች ወረደች። አይኗ ብዥ አለባት። ሰማይና ምድሩ ተገለባበጠባት። አእምሮዋና የሰውነት

" " ​​​​#መቅደላዊት #ክፍል_38 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ሜሮን በንዴት ጥርሷን ከንፈሯ ላይ ነክሳለች አይኖቿን በፍጥነት ወደየአቅጣጫው ትልካለች አልፎ አልፎ ደግሞ ከአልጋዋ ትነሳና ትመላለሳለች ። አንዴ ወገቧን አንዴ ራሷን እያቀያየረች ትይዛለች።ይህ በመጨረሻ አላስችላት ብሎ ስልኳን አውጥታ ለሜላት ደወለች። ከሶስተኛው ጥሪ በኋላ ሜላት ስልኩን አነሳችው። " ሜሪየ " አለች ሜላት በፈገግታ የናሆምን ግራ እጅ አቅፋ አይኖቿን በስስት አይኖቹ ላይ እየጣለች ፡ ሜሮን ይበልጥ በአነጋገሯ እየተናደደች" አሁኑኑ እፈልግሻለሁ በአስቸኳይ " አለች። ሜላት የናሆሞን እጅ ለቀቅ አደረገች ፡ ናሆም ግራ እየተጋባ " በሰላም ነው ?" አለ ሜሮን በአወንታ ራሷን አወዛወዘች። እና ከእሱ ፈንጠር ብላ " መጀመሪያ ቀስ ብለሽ አውሪኝ እንድጮህ አታደርጊ ተረጋግተሽ የሆንሽውን ንገሪኝ " አለች ሜላት። " በቃ አሁኑኑ እንድትመጭ እፈልጋለሁ ስትመጭ ሁሉንም እዚህ እናወራለን " አለች ሜሮን " ሌላ ምክንያት አለሽ? ከምትነግሪኝ የበለጠ ናሆምን ትቸው መምጣት የምችልበት?" አለች ሜላት ሜሮን በሜላት ንግግር ተናደደች "ቆይ ግን ሜሊ ችግር አለብሽ ልበል ምን ሆነሽ ነው ልጅ የምትሆኝው ናሆም አደገኛ ልጅ ነው ብትጠነቀቂው ይሻላል!! ምን ሆነሽ ነው እንዲህ እውር የሆንሽው? አይታይሽም እንዴ እንደዛ መከራ እያየሽ አንድ ቀን እንኳ አላፅናናሽም አይዞሽ አላለሽም ትቶሽ ነበር የሄደው አይታይሽም እንዴ ግን?" አለች ሜሮን። ሜላት እራሷን ነቀነቀች አይኗ ተገለባበጠ ራሷን ያዘች እንዳትጮህ ናሆም እያያት ነው ።እንደምንም ያልተናደደች በመምሰል አይኖቿን ከደን አድርጋ "ትዕግስቴን እየተፈታተንሽው ነው ሜሮን ታውቆሻል አይደል? " አለች ሜላት " አወ አውቃለሁ ወትሮም ለሚወድሽ ሳይሆን ለማይወድሽ ነው ስድብ እና ንቀት ትዕግሥትሽን የማይፈታተነው። አሁን የምነግርሽ የመጨረሻ ምክሬ ነው እንደጓደኛ ከዛ በኋላ የራስሽ ጉዳይ አምነሽበትና መርጠሽው ስለሆነ የገባሽው አይመለከተኝም ግን ሳልነግርሽ የማላልፈው ናሆም በጥፋቱ ተፀፅቶ ሳይሆን በአንቺ ደካማ ጎን ተጠቅሞ ሊያታልልሽ ነው!! እናም ቢያንስ እንኳ ምን እንደሚፈልግ ከአንቺ እወቂ ጥቅም ወይስ ፍቅር ? " አለች ሜሮን " ጨረሽ አሁን ልዝጋው?" አለች ሜላት " ዝጊው አወ ጨርሻለሁ " አለች ሜሮን ሜላት በንዴት ስልኳን ዘጋችውና " ቆየሁብህ እንዴ ናሆሜ " አለች ሜላት ወገቡን ጨምድዳ እየያዘች " ኧረ ችግር የለውም ግን በሰላም ነው ማን ደውሎልሽ ነው?" አለ ናሆም " እዚሁ ነው ጓደኛየ ነች " " ምን ሆና ነው?" " ምንም አልሆነችም ጠፍቸባት ነው!" " እሽ እንደዛ ከሆነ እና የተነጋገርንበትን ነገር በጥንቃቄ ማድረግ ይኖርብናል። ** ፅሀይ የምዕራብን አቅጣጫ ተንተርሳ ልታሸልብ ጣር ይዟታል። ደንገዝገዝ ብሏል ፊቱን ወደ ተንጣለለው የአድዋ የጫካ ፓርክ ሆኖ የተሰራው ህንፃ አናት ላይ ተቀምጦ በተመስጦ ይመለከታል። ባሩክ ( ዲዮጋን ) ብዙውን ጊዜ ባይሆንም የተፈጥሮን አየር ለመማግ አልፎ አልፎ ወደ ዚህ ህንፃ አናት ላይ ይመጣል በዚህ ውብ መልከዓ ምድርና ተፈጥሮ እየተደነቀ እና አይኖቹን ከድኖ አየሩን እየማገ ሳለ ስልኩ ጠራ። ስልኩን አውጥቶ ሲመለከት ናታኔም ነው ቶሎ አነስቶ "አቤት ናታኔም ደህና ነህ ?" አለሁ ባሩኬ ፈልጌህ ነበር የት ነህ ?" አለ ናታኔም " የተፈጥሮ ህንፃ ነኝ " አለ ባሩክ " እሽ መጣሁ አለ እሽ ናቶሎ " ናታኔም እና መርዕድ ተያይዘው ወደ ተፈጥሮ ህንፃ ሄዱ።" ባሩክ እንዴት አይነት አስተዋይ ብስል መሰለህ ልጁ መፅሀፍ ነው አንዲት ከረጢት ችግር ይዘህለት ሄደህ አንድ አቁማዳ መፍትሄ ይሰጥሀል ።ሰው የንባብ ውጤት መሆኑንን ያየሁት በሱ ነው ሁሌም አብሮኝ አለ ።ብቻ ባሩክ ማለት ቅን ልጅ ነው ምንም ነገር ጠይቄው እምቢ አይለኝም " አለ ናታኔም " ሃሃሃ አውቀዋለሁ ! ስለ ዲዮጋን አይደል የምታወራው? " አለ መርዕድ " አወ እኔ ደግሞ ምታቀው አልመሰለኝም ?" አለ ናታኔም " አንተ እንኳ አውቀኸዋል ትላንት ገብተህ ። " አለና ሳቅ ብሎ " ስቀልድ ነው የእኛ ባች በጣም ነበር የምንወደው አዳራሽ ወይም ገብርየ ዋርካ የስነፅሁፍ ምሽት አለ ከተባለ ሁሉም የሚጠይቀው ዲዮጋን እንደሚኖርና እንደማይኖር ነው። አለ ከተባለ በቃ ሰልፍ ነው ቲኬቱ ወዲያው ያልቃል ብዙወች እንደውም የምንገባው እኮ መፅሀፍ ለማንበብ ነው ይላሉ ። አንደኛው ጓደኛየ እንደውም እንዴ ከመፅሀፍ ጋ ምን አታገለኝ ከዲዮጋን ጋር 10 ደቂቃ ብቆይ እኮ 10 መፅሀፍ አነባለሁ ይል ነበር ። ዲዮጋን ከብስለቱ ባሻገር የሚጠቃማቸው ቃላቶች ጉልበት ያስገርሙኛል።" አለ መርዕድ " እውነትም ታውቀዋለህ አንተ " አለ ናታኔም እንዲህ እየተጨዋወቱ የተፈጥሮ ህንፃ አናት ላይ ደረሱ ። ባሩክ ተመስጧል ሲበዛ ናታኔም " እ ባሩኬ " አለና ሰላምታ ሰጠው አፀፋውን መለሰለት " እሽ ሰላም ነው? "አለና ለመርዕድም በፈገግታ ሰላምታውን አቀረበለት ናታኔምና መርዕድ ተቀመጡ አብረውት ተፈጥሮን ማየት ያዙ። " ሁሌም ለመመሰጥ ነው እዚህ ምትመጣው?" አለ ናታኔም " አይደለም ለማወቅ ና ለመማር ነው እዚህ ምመጣው" አለና ባሩክ ወደ ተፈጥሮ ተመለሰ። " ፍጥረት የፍልስፍና መሠረት ናት ወዳጄ የቅኔ ሊቃውንት ምን ይላሉ መሰለህ ቅኔ የተፈጥሮ አስተውሎትን መንገር ነው።" ይላሉ አየህ ተፈጥሮን ስታስተውል የነገረ ፍጥረት ምስጢር መክፈቻ ቁልፍ ይሰጥሃል። ተፈጥሮ ማንኛውም መፅሃፍ በማያስተምርህ መንገድ ታስተምርሀለች። ስነ ግጥም ተፈጥሮን ትክባታለች ቅኔ ደግሞ ተፈጥሮን ታረቃታለች ። ቅኔ ስታውቅ ትጠይቃለህ ታምናለህ ፈጣሪን ትወዳለህ የሰውን ልጅ ህይወት ታከብራለህ፣ ተፈጥሮን ማድነቅ ማወደስ ትማራለህ ።የቅኔ ፈላስፎች ፈጣሪ የሚገኘው በፍጥረቱ ማለትም በክሡቱ አለም በኩል እንዲሁም በአንተም በእኔም በኩል እንደሆነ ያምናሉ በዙሪያህ ሚገኘውን አለም የምትረዳው በተፈጥሮ በኩል ነው። ቅኔ ስለ ፍጥረት ያወጋል ብዙ ጊዜውን ይሰጣል ። በእርግጥ የዜማም መሠረቱ ተፈጥሮ ነች። ቅዱስ ያሬድ እነዚያን ሁሉ የተዋቡ ዜማወች ሲደርስ በተፈጥሮ ተነሽጦ ነው። ይሁን እንጅ ምንም እንኳ ዜማ በተፈጥሮ ላይ ቢመሠረትም ተፈጥሮን አይመረምራትም።የቅኔም መሠረቱ ተፈጥሮ ነው ግን ቅኔ ተፈጥሮን ይመረምራታል።"ብሎ በድንገት ዝም አለ እና ማዶ ላይ አይኖቹን ላከ። ናታኔም እና መርዕድ ሳይጠግቡት ሳይሰለቹት በማቆሙ የተናደዱ ይመስላሉ።" ምንአልባት አሁን እኔን ብዙ ሰው እዚህ ሁኜ ቢመለከተኝ "ያነበበው መፅሀፍ ሊያሳብደው ነው በቃ ህንፃላይ ከተንጠለጠለማ ለየለት "ነው እንጅ የሚሉኝ እዚህ ሁኜ በጥልቅ ተመስጦ ከተፈጥሮ ጋ እንደማወጋ አያውቁም ። ይሄን ባለማወቃቸው ደግሞ ያሳዝኑኛል የእውነቴን ነው የምላችሁ የተፈጥሮ ዜማ የማይሰማው ሰው እጅግ ያሳዝነኛል ዝም ብሎ መጮህ ብቻ ተውት እስኪ እሽ ናታኔም እንደምን ነህ ትንሽ ተጠፋፋን አይደል? እኔም በግል ጉዳይ ተጠምጄ ተውኳችሁ አይደል? " አለ ባሩክ " ኧረ አልጠፋህም ግን ያው ሌላ ጭንቀት ውሴጤን እያሸበረው ነው! " አለ ናታኔም " ምንድነው እሱ?" አለ ባሩክ ጀሮውን እና ቀልቡን ወደ ናታኔም እያደረገ። ይቀጥላል .......... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 39♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

" ​​​​#መቅደላዊት #ክፍል_37 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ሜሮን በሜላት ሁኔታ በጣም ተናዳለች ቢሆንም ግን ልታስቆማት አልቻለችም። ምን ማድረግ አለብኝ ወይ እንዲተዋት ወይ እንዳይተዋት ማድረግ አለብኝ እንጅ እንዲህ በቀላሉማ ሲፈልግ የሚወስዳት ሲፈልግ የሚተዋት ተራ እቃ አይደለችም ይሄን ደግሞ መረዳት ይኖርበታል። ** ሜላት ከርቀት ሆና አየችው።ናሆም ፊቱን ወደ አድዋ ተራራ አድርጎ አገጩን በእጁ አስደግፎ ተቀምጧል። ሆዷ ተላወሰ አሳዘናት " ምን ሆኖ ይሆን " አለች ደግሞ እንዳናደዳት ትዝ አላት ኮስተር አለች " ሰላም ነው " አለች ናሆም በእርጋታ ከተቀመጠበት ተነስቶ አቀፋት አቀፈችው። አይኖቿን ተመለከታቸው አይኖቿ ላይ ስስት ፍቅር ፣ ርህራሄ ይታያሉ ።ከንፈሯን ሳማት አይኖቿ ተስለመለሙ አሁንም አሁንም ተነፈሰች ዝም ብላ በሰመመን ቆየች ከሰመመን ስትነቃ ከንፈሯን ከከንፈሯ አንስቶታል። ሳብ አድርጋ ከእንደገና ከከንፈሯ ጋ ከንፈሩን አገናኘችው ለአንድ ደቂቃ እንደተሳሳሙ ናሆም መሳሙን አቁሞ በስስት ተመለከታት እና ግንባሯን ስሞ ወደ ደረቱ አቀፋት።ከተነጠፈው የኖራ ድንጋይ ተቀመጡ። ትከሻውን ተደገፈችና " ምን ሆነህ ነው ግን ምን ችግር ገጥሞህ ነው። " አለች " እሽ እነግርሻለሁ። ግን ከዛ በፊት ቅድም ምን ሆነሽ ነው ስልክ ያላነሳሽልኝ መልዕክት ባልክልሽ ኖሮ አትደውይልኝም ነበር ማለት ነው ቆይ ግን እኔ ላይ ጨከንሽ ማለት ነው? " አለ " እንደዛ ሳይሆን ሁሌም አንተ ነሃ ግራ የምትሆንብኝ እኔ ብዙ ነገር አስቤ ወደ አንተ ስመጣ ተስፋየን የምታመክነው " አለች " እና ያላነሳሽው እኔን ለመበቀል እና በእኔ ስለተናደድሽ ነው? " " አወ በአንተ ከምነግርህ በላይ ተናድጃለሁ ግን ደግሞ በአንተ የፈለገ ብናደድም መጨከን ግን አልችልም " " እና ታዲያ ከናታኔም ጋር ምን ለማውራት ነው የደወልሽው? እኔን ለማስቀናት? ነው በጓደኛየ " " ምንድነው ነው የምታወራው ናሆ የምን ናታኔም ነው የምን መደዋወል ነው?" " ከእሱ ጋር እያወራሽ እንደሆነ ደርሼበታለሁ የሰማችሁ ሰው ወይም ያያችሁ ሰው ነው የነገረኝ " " ኧረ በጭራሽ ውሸት ነው እንኳን መደዋወል ቀርቶ በመንገድ ራሱ አውርተን አናውቅም ኧረ እንደውም ስልኩ ሁሉ የለኝም የምን ወሬ ነው የሰማኸው በእውነት እልሀለሁ ይበልጥ እንድትጠላኝ ነው። እንዲህ ከእውነት የራቀ ወሬ የሚያወሩህ እሽ አትስማቸው።እየው በምወዳት እናቴ ስም እምልልሀለሁ በጭራሽ ናታኔምን የአንተ የዶርም ልጅ ከመሆኑ ውጪ የማቀው ነገር ራሱ የለኝም በአካልም ተገናኝተን አናውቅም " " ጥሩ እንግዲህ ይሄን ነገር ራሱንም መጠየቅ ሳይኖርብኝ አይቀርም " እሽ እንደውም አገናኘኝ እና እኔም እጠይቀዋለሁ " ናሆም ፈገግ እያለ "ጥሩ ሀሳብ ነው በቃ እኔ አገናኛችኋለሁ ግን ውሸቱን እንደሆነና እንዳልሆነ ለማወቅ የሆነ መላ እንዘይዳለን እሽ"" ደስ ይለኛል አንተ እኔዳልክ " ወደ ምሳ ስአት አካባቢ ስደውልልሽ ወደ ውጪ ትወጭና ትንሽ ቆየት ብለሽ እኔና ናታኔም ከወደ ዶርም ለምሳ ስንሄድ አንቺ ደግሞ ከወደ ውጪ የምትመጪ አስመስለሽ መገንጠያ ላይ እንገጣጠማለን ከዛ አንቺ እንደሁልጊዜው እንደ እስከዚህ ቀደሙ እኔ ምንም እንዳላልኩሽ አስበሽ ልታልፊው ስትይ እኔ እጠራሻለሁ ከዛ የሚፈጠረውን አያለሁ "" አሪፍ ሀሳብ ነው ይሄን ምስጢር ለማንኛዋም ጓደኛሽ እንዳትናገሪ እንደተናገርሽ የሚያጠራጥር ነገር ካየሁብሽ ከሰማሁብሽ አባቴ ይሙት የእኔና የአንቺ ነገር ያበቃለታል " " ኧረ አትማል ከመሀላህ በፊት እኔ ለማንም አልናገርም አታስብ " አለች ሜላት ናሆም አይደለም በአባቱ ምሎ አባቱን ሲጠራ ራሱ እንደማያወላወል እና ያለውን እንደሚያደርግ ታቃለች። **** " እሽ ናታኔም ታዲያ ፍሬሽነት እንዴት ነው? " " ምንም አይልም ባክህ ያው ከላይ ከታች መሮጥ ነው የሲኒየር አይን ፌዝ ያጅብሀል የመምህር አይን ይገለምጥሀል የፈተና ውጤት ያሳንስሀል በነዚህ ሁሉ ታጅበን አለን " " እንዴ እስከማቅህ ጎበዝ ተማሪ ነበርክ ቀነስክ እንዴ? "" ምን ትምህርት ብቻ መርዕድ ኪሎም ጭምር ነው እንጅ የቀነስኩት "" እኮ ምንሆነህ ነው የቀነስከው ነኽ የኔ ጥያቄ?" ሀሳቡ ነዋ የሚነበበው መብዛቱ አያልቅም አንዱን ስትለው አንዱን "" እሱማ እኮ ግልፅ ነው የዩኒቨርስቲ ትምህርት እንዲህ ነው የምትማረው 50% የምትፈተነው ደግሞ 100% ስለዚህ ያልተማርከውን 50% አምብበህ ትሸፍናለህ ማለት ነው።ያውም ይሄ የኛ ዩኒቨርስቲ ጥሩ ጥሩ መምህር ስላሉት እውቅናም ስላለው የውጭ መምህራኖችም ስለሚበዙ ሌላ ዩኒቨርሲቲ ሄደህ ብትጠይቅ እኮ ጭራሽ ሳይማሩ ሁሉ ሀንድአውት ብቻ ትጥቶአቸው አምብበው ይፈተናሉ።"" ለምንድነው ግን እንደዛ የሚያደርጉት ተማሪዎቹ አይከሱም ሳንማር ተፈተንን ብለው?"" ምን ሆነሀል ናቲ እንዳለ በ f ልታጥለቀልቃቸው ነው? እንደዛ ብለው ቢከሱት ሁለት ቀን በፕሮጀክት ነካ ነካ አድርጎ ይጨርስና አስተምሪያለሁ ይላል። ከዛ እበት የሆነ ጥያቄ ያወጣና ይበቀላቸዋል። ከዛ እንዳለ ግሬዳቸውን በC እና በD ያሾቃቸዋል። ስለዚህ ከዚህ ሁሉ መአት የተሰጣቸውን ሀንድአውት አምብበው በገባቸው መሰረት ሰርተው በኋላ ላይ ማርክ እንዲጨምር እና እንዳላስተማራቸው አምኖ ውጤት እንዲሰጣቸው ቢያደርጉ ትክክለኛ አማራጭ ነው ብለው ያምናሉ።ማለት ነው።"" ይቀጥላል .......... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 38♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

​​​​#መቅደላዊት #ክፍል_36 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ሜሮን በሜላት ሁኔታ በጣም ተናዳለች ቢሆንም ግን ልታስቆማት አልቻለችም። ምን ማድረግ አለብኝ ወይ እንዲተዋት ወይ እንዳይተዋት ማድረግ አለብኝ እንጅ እንዲህ በቀላሉማ ሲፈልግ የሚወስዳት ሲፈልግ የሚተዋት ተራ እቃ አይደለችም ይሄን ደግሞ መረዳት ይኖርበታል። ** ሜላት ከርቀት ሆና አየችው።ናሆም ፊቱን ወደ አድዋ ተራራ አድርጎ አገጩን በእጁ አስደግፎ ተቀምጧል። ሆዷ ተላወሰ አሳዘናት " ምን ሆኖ ይሆን " አለች ደግሞ እንዳናደዳት ትዝ አላት ኮስተር አለች " ሰላም ነው " አለች ናሆም በእርጋታ ከተቀመጠበት ተነስቶ አቀፋት አቀፈችው። አይኖቿን ተመለከታቸው አይኖቿ ላይ ስስት ፍቅር ፣ ርህራሄ ይታያሉ ።ከንፈሯን ሳማት አይኖቿ ተስለመለሙ አሁንም አሁንም ተነፈሰች ዝም ብላ በሰመመን ቆየች ከሰመመን ስትነቃ ከንፈሯን ከከንፈሯ አንስቶታል። ሳብ አድርጋ ከእንደገና ከከንፈሯ ጋ ከንፈሩን አገናኘችው ለአንድ ደቂቃ እንደተሳሳሙ ናሆም መሳሙን አቁሞ በስስት ተመለከታት እና ግንባሯን ስሞ ወደ ደረቱ አቀፋት።ከተነጠፈው የኖራ ድንጋይ ተቀመጡ። ትከሻውን ተደገፈችና " ምን ሆነህ ነው ግን ምን ችግር ገጥሞህ ነው። " አለች " እሽ እነግርሻለሁ። ግን ከዛ በፊት ቅድም ምን ሆነሽ ነው ስልክ ያላነሳሽልኝ መልዕክት ባልክልሽ ኖሮ አትደውይልኝም ነበር ማለት ነው ቆይ ግን እኔ ላይ ጨከንሽ ማለት ነው? " አለ " እንደዛ ሳይሆን ሁሌም አንተ ነሃ ግራ የምትሆንብኝ እኔ ብዙ ነገር አስቤ ወደ አንተ ስመጣ ተስፋየን የምታመክነው " አለች " እና ያላነሳሽው እኔን ለመበቀል እና በእኔ ስለተናደድሽ ነው? " " አወ በአንተ ከምነግርህ በላይ ተናድጃለሁ ግን ደግሞ በአንተ የፈለገ ብናደድም መጨከን ግን አልችልም " " እና ታዲያ ከናታኔም ጋር ምን ለማውራት ነው የደወልሽው? እኔን ለማስቀናት? ነው በጓደኛየ " " ምንድነው ነው የምታወራው ናሆ የምን ናታኔም ነው የምን መደዋወል ነው?" " ከእሱ ጋር እያወራሽ እንደሆነ ደርሼበታለሁ የሰማችሁ ሰው ወይም ያያችሁ ሰው ነው የነገረኝ " " ኧረ በጭራሽ ውሸት ነው እንኳን መደዋወል ቀርቶ በመንገድ ራሱ አውርተን አናውቅም ኧረ እንደውም ስልኩ ሁሉ የለኝም የምን ወሬ ነው የሰማኸው በእውነት እልሀለሁ ይበልጥ እንድትጠላኝ ነው። እንዲህ ከእውነት የራቀ ወሬ የሚያወሩህ እሽ አትስማቸው።እየው በምወዳት እናቴ ስም እምልልሀለሁ በጭራሽ ናታኔምን የአንተ የዶርም ልጅ ከመሆኑ ውጪ የማቀው ነገር ራሱ የለኝም በአካልም ተገናኝተን አናውቅም " " ጥሩ እንግዲህ ይሄን ነገር ራሱንም መጠየቅ ሳይኖርብኝ አይቀርም " እሽ እንደውም አገናኘኝ እና እኔም እጠይቀዋለሁ " ናሆም ፈገግ እያለ "ጥሩ ሀሳብ ነው በቃ እኔ አገናኛችኋለሁ ግን ውሸቱን እንደሆነና እንዳልሆነ ለማወቅ የሆነ መላ እንዘይዳለን እሽ"" ደስ ይለኛል አንተ እኔዳልክ " ወደ ምሳ ስአት አካባቢ ስደውልልሽ ወደ ውጪ ትወጭና ትንሽ ቆየት ብለሽ እኔና ናታኔም ከወደ ዶርም ለምሳ ስንሄድ አንቺ ደግሞ ከወደ ውጪ የምትመጪ አስመስለሽ መገንጠያ ላይ እንገጣጠማለን ከዛ አንቺ እንደሁልጊዜው እንደ እስከዚህ ቀደሙ እኔ ምንም እንዳላልኩሽ አስበሽ ልታልፊው ስትይ እኔ እጠራሻለሁ ከዛ የሚፈጠረውን አያለሁ "" አሪፍ ሀሳብ ነው ይሄን ምስጢር ለማንኛዋም ጓደኛሽ እንዳትናገሪ እንደተናገርሽ የሚያጠራጥር ነገር ካየሁብሽ ከሰማሁብሽ አባቴ ይሙት የእኔና የአንቺ ነገር ያበቃለታል " " ኧረ አትማል ከመሀላህ በፊት እኔ ለማንም አልናገርም አታስብ " አለች ሜላት ናሆም አይደለም በአባቱ ምሎ አባቱን ሲጠራ ራሱ እንደማያወላወል እና ያለውን እንደሚያደርግ ታቃለች። **** " እሽ ናታኔም ታዲያ ፍሬሽነት እንዴት ነው? " " ምንም አይልም ባክህ ያው ከላይ ከታች መሮጥ ነው የሲኒየር አይን ፌዝ ያጅብሀል የመምህር አይን ይገለምጥሀል የፈተና ውጤት ያሳንስሀል በነዚህ ሁሉ ታጅበን አለን " " እንዴ እስከማቅህ ጎበዝ ተማሪ ነበርክ ቀነስክ እንዴ? "" ምን ትምህርት ብቻ መርዕድ ኪሎም ጭምር ነው እንጅ የቀነስኩት "" እኮ ምንሆነህ ነው የቀነስከው ነኽ የኔ ጥያቄ?" ሀሳቡ ነዋ የሚነበበው መብዛቱ አያልቅም አንዱን ስትለው አንዱን "" እሱማ እኮ ግልፅ ነው የዩኒቨርስቲ ትምህርት እንዲህ ነው የምትማረው 50% የምትፈተነው ደግሞ 100% ስለዚህ ያልተማርከውን 50% አምብበህ ትሸፍናለህ ማለት ነው።ያውም ይሄ የኛ ዩኒቨርስቲ ጥሩ ጥሩ መምህር ስላሉት እውቅናም ስላለው የውጭ መምህራኖችም ስለሚበዙ ሌላ ዩኒቨርሲቲ ሄደህ ብትጠይቅ እኮ ጭራሽ ሳይማሩ ሁሉ ሀንድአውት ብቻ ትጥቶአቸው አምብበው ይፈተናሉ።"" ለምንድነው ግን እንደዛ የሚያደርጉት ተማሪዎቹ አይከሱም ሳንማር ተፈተንን ብለው?"" ምን ሆነሀል ናቲ እንዳለ በ f ልታጥለቀልቃቸው ነው? እንደዛ ብለው ቢከሱት ሁለት ቀን በፕሮጀክት ነካ ነካ አድርጎ ይጨርስና አስተምሪያለሁ ይላል። ከዛ እበት የሆነ ጥያቄ ያወጣና ይበቀላቸዋል። ከዛ እንዳለ ግሬዳቸውን በC እና በD ያሾቃቸዋል። ስለዚህ ከዚህ ሁሉ መአት የተሰጣቸውን ሀንድአውት አምብበው በገባቸው መሰረት ሰርተው በኋላ ላይ ማርክ እንዲጨምር እና እንዳላስተማራቸው አምኖ ውጤት እንዲሰጣቸው ቢያደርጉ ትክክለኛ አማራጭ ነው ብለው ያምናሉ።ማለት ነው።"" ይቀጥላል .......... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 37♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

​​​​#መቅደላዊት #ክፍል_35 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ "የኔን ጉዳይ ከማን ጋር ጀምረህ ነው ብቻህን የምትጨርሰው " አለ ናሆም ወደ ዶርም እየገባ? ናታኔም እንደ ቆመ ሀውልት ስልኩን ጥሎ ቆመ። ንገረኝ እንጅ ወንድሜ " ናታኔም አይኖቹ ይርገበገባሉ ሰውነቱ እየተንቀጠቀጠ ነው እጆቹ ይንዘፈዘፋሉ " አንተን እኮ ነው የምጠይቀው ለምንድነው የማትመልስልኝ?" ናሆም መጠየቁን ቀጠለ " ለምንድነው የደነገጥከው ከእኔ ጀርባ ምን እያሴርክብኝ ነው?" አለ ወደ ናታኔም እየተጠጋ " ካ ካ ካ ካንተ ጀርባ ምን ላሴር እችላለሁ ወንድሜ?" አለ ናታኔም እየተንተባተበ " እሱንማ እኔ ምን አውቃለሁ ባውቅ መች እጠይቅህ ነበር? እና የምታሴረው እና የምትሰራው ከሌለ ምን ይዘጋሀል ምን ያስደነግጥሀል?" ናሆም አይኖቹን እያጉረጠረጠ ጠየቀው " በድንገት ስለገባህ ነው እያወራሁ ለዛ ነው የደነገጥኩት ሌላ ምን ምክንያት ሊኖረኝ ይችላል ።" አላውቅም እና ከማን ጋር ነበር ስለ እኔ የምታወራው ታዲያ " ናሆም ግራ በተጋባ መንፈስ ሆኖ ጠየቀው " ከሜላት ጋ " አለ " ምን?" አለ ናሆም ራሱን ይዞ እየደነገጠ " ምነው ካላመንከኝ ስልኬን እየው " አለ ናታኔም መንተፍረቱን እንደመፍራትም እንደመድፈርም ብሎ ቀጠለና " ናሆም ግን የዚችን ልጅ ጉዳይ አንድ ማድረግ አለብህ ወደማይረባ ህይወት ልትገባ ትችላለች ስለዚህ ቀድሞ መጠንቀቁ ሳይሻል አይቀርም። " የራሷ ጉዳይ የልቤን አንድ ጊዜ ነግሪያታለሁ ስለዚህ እንደፈለገች ትሁን ሰውም እንደፈለገ ማሰብ ማውራት ይችላል ። ከዚህ በኋላ እሷን የምታገስበት ትዕግስት የለኝም።" አለና ናሆም በሩን ሊከፍት ሲል ከወደ ውጭ የሚከፍተው ሰው ስለነበር በሩ ወደ ኋላ ገፋው ዶርሙን ከሚከፍተው ልጅ ጋ ተገጣጠሙ። " መጀመሪያ አታንኳኳም እንዴ ዝም ብለህ የምትከፍተው?" አለ ናሆም " ይቅርታ ግን ዝም ብየ የከፈትኩት በር የሚከፍት ሰው እንደሌለ እርግጠኛ በመሆን ነው" አለ መርዕድ ናታኔም ንግግራቸውን ሰምቶ ዘወር ሲል መርዕድን ተመለከተው " መርዕድ ? " አለ ናታኔም " ናታኔም እንዴት ነህ " ብሎ መርዕድ ወደ ውስጥ ገባ ናሆም የበሩን እጀታ ይዞ ቆሞ ሁለቱን እየተመለከተ ነው ። ናታኔምና መርዕድ ለረጅም ዘመን እንዳልተያዩ ሆነው ተቃቀፉ " እሽ መርዕዴ እንዴት ነህ እንዴት እንዴት እንዲህ በድንገት አድዋ ተገኘህ?" አለ ናታኔም " አድዋ ናፍቃኝ አይመስልህም?" አለ መርዕድ በስሱ ፈገግ እያለ "እሱስ ልክ ነህ ይሆናል ያው አምስት አመት የቆየህበት ጊቢ እንዲህ በቀላሉ ትዝታው እንዴት ይለቃል! ግን እንዴት ሳትደውልልኝ? ልትመጣ ስትል" አለ ናታኔም " እሱን እንኳ ያደረኩት እንደ እውነቱ ከሆነ አንተን ሰርፕራይዝ ለማድረግ ነው" አለ መርዕድ " ሃሃሃ አየ ሰርፕራይዝ እቴ እዚህ ሁልጊዜ ሰርፕራይዝ እንደተደረኩ አይደል ወንድሜ መርዕድ " አለ ናታኔም እየሳቀ " ተው ባክህ አልመሰለኝም አልገመትኩም ነበር።" አለ መርዕድ አሁንም ፈገግ እያለ " እኔም አልገመትኩ እንኳን አንተ ይልቁንስ ምን ልታደርግ መጥተህ ነው?" አለ ናታኔም " ማስተርሴን ልማር ነው " አለ መርዕድ " ዋው በጣም ነው ደስ ያለኝ እና እኛ ጊቢ ውስጥ ነዋ የምትኖረው? ደስ ሲል " አለ ናታኔም ትራሱ አጠገብ ላይ የተቀመጠውን ቲሸርት አንስቶ እየለበሰ " አዎ የምንኖርበት ቦታ ቢለያይም አንድ ጊቢ ነን በፈለግነው ጊዜ መገናኘት እንችላለን " አለ መርዕድ " ልክ ነህ ወጣ እንበል እንጅ ታዲያ መርዕዴ እዚህ በወሬ ብቻ ከማደክምህ ባይሆን ሻይ እየጠጣን እናውራ እንጅ " አለ ናታኔም " እሽ ጥሩ ሀሳብ ነው ግን ቅድም በር ላይ የተገጣጠምኩት ልጅ ማነው?" አለ መርዕድ " እ ናሆምን ነው የሚባለው አንድ ዶርም ነን " አለና ናታኔም ተነሳ " አንተ ነህ ናሆም የምትባለው ማለት ነው " አለና መርዕድ አንገቱን በቀስታ ወደ ላይ ወደታች አወዛወዘ። * ናሆም ብሎኩን እየወረደ " ለምን እንደዛ ተንቀጠቀጠ ለምን ፈራ ለምይ ደነገጠ? የሆነ ነገርማ እያደረገ ነው ። ቆይ እየዋሸ ቢሆንስ እስኪ ሜላት ጋር ልደውል እና ላረጋግጥ ስልኩን አወጣ " ናሆም እንዴት ነህ " አለው ባሩክ " ደህና ነኝ አንተስ እንዴት ነህ " " እኔ ደህና ነኝ ሰሞኑን ጠፍተሀል በሰላም ነው?" " አወ በሰላም ነው ትንሽ ጥናት ቢዚ ስላደረገኝ ነው ያው እንደምታውቀው ፋይናል ደርሶ የል " " እሱስ ልክ ነህ ናሆም በል እንግዲያውስ በደንብ አምብብ " ብሎት ወደ ብሎኩ ገባ ። ናሆም ለመደወል ስልኩን እንደገና በማውጣት ደወለ አይነሳም ደጋግሞ ቢደውል ሜላት ስልክ አታነሳም በመጨረሻ ተስፋ ቆርጦ ስልኩን እያስገባ ሳለ አንድ ሀሳብ መጣለት መልዕክት መፃፍ ** " በቃ አንቺ ግን አመረርሽ በቃ ማለት ነው ናሆምን ተውሽው? " አለች ሜሮን " አወ ረስቼዋለሁ ከዚህ በኋላ ወደ ኋላ የምልበት ምክንያት የለም " አለች ሜላት " አምበሲት እኮ ነሽ የኔ ቆንጆ ጓደኛ " ግን ሜሪ ምን ሆኖ ይሆን እንዲህ በተደጋጋሚ የደወለልኝ አስበሽዋል ከአምስት ጊዜ በላይ እኮ ነው የደወለው የሆነ ነገር ግን ሆኖ ይሆናል ባይሆን ኖሮ እንደዛ ብሎ ከተናገረኝ በኋላ አይደውልም ነበር ለማንኛውም ግን የሆነ ነገር ሆኗል በእርግጠኝነት!" አለች ሜላት ሜሮን ተናደደች የሆነስ ቢሆን በቃ ረስተሽው የለ ለምን እንጦረጦስ አይገባም ለምን የፈለገ ነገር አይደርስበትም አንቺ ዝም ብለሽ ማሰብ አያስጠላሽም እንዴ ይሄ ፍቅር አይደለም ልክፍት ነው በስመአብ ሰው እንዴት እንዲህ ከማይወደው ሰው ከማያስብለት ሰው ጋ ሙጥኝ ይላል?" አለች ሜሮን በዚህን ጊዜ ሜላት" ነይ ሜሪ ሜሴጅ ላከልኝ " አለች ሜሮን ወደ ሜላት ስልክ አፈጠጠች "" የኔ ቆንጆ አውቃለሁ አንቺ ላይ በጣም ብዙ ጥፋቶችን አጥፍቻለሁ እና ለሱ አንቺን ለመካስ አቅም ባይኖረኝም ግን ይቅርታ እልሻለሁ ከዛን ጊዜ በኋላ እያሰብኩበት ነበር ትልቅ ስህተት ነው የሰራሁት እባክሽን ተረጅኝ የኔ ቆንጆ፡ አውቃለሁ እንዳጠፋሁ ግን ደግሞ እኔም ችግር ውስጥ ነው ያለሁት በጣም ትልቅ ችግር ውስጥ ለዛውም እናም በቀላሉ ተረጅኝ አሁን ስልክ አንሺልኝ እባክሽን የኔ ቆንጆ አሁን ከመቼውም ጊዜ በላይ የአንቺን እርዳታ ያስፈልገኛል። እረዳሀለሁም ብለሽኝ አልነበር "" የሚል መልዕክት ነው " ማንሳት ነበረብኝ በጣም ተሳስቻለሁ ለምን እንዲህ እሱ ላይ አስጨከነኝ አልረባም ። ደግሞ እውነቱን ነው ችግር ውስጥ እኔደሆነ ነግሮኛል እኔም እረዳሀለሁ ብየዋለሁ።ስለዚህ ቃሌን አልበላም ናሆምን እረዳዋለሁ ከዛ የራሴ አደርገዋለሁ።" አለች እና ለናሆም ደወለች " ወይዬ ሜሊ ደህና ነሽ አይደል " " አወ ደህና ነኝ አንተ ምን ሆነህ ነው?" " ምን ያልሆንኩት አለ የሁሉም መጫወቻ ሆንኩ እንጅ በጣም ያሳዝናል " " ንገረኝ የማን መጫወቻ ነው የሆንከው?" " እረ እሱ ስልክ የሚነገር አይደለም በአካል ነው የሚሻለው " " እሽ እንዳልክ የት ነው ያለኸው የት ልምጣ?" " አቢሲኒያ ስታዲየም ነኝ ፈጠን ብለሽ ነይ አሁኑኑ " " እሽ አታስብ ይሄው ወጣሁ በቃ "*አለችና ሜሊ እየተቻኮለች ወዲያው ወጣች ። ይቀጥላል ..................... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 36♥️ ነገ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።