en
Feedback
ቆየት ቆየት ያሉ ሙዚቃዎች

ቆየት ቆየት ያሉ ሙዚቃዎች

Open in Telegram

እንደኔ ኦልድ ዘፈኖች ወዳጆች ኑ ከኔጋ ዘና በሉ @Riyit Join ይበሉቻናል ላይ full ዘፈኖች ያገኛል ደስ ያሉትን ዘፈን እየተገባበዝን ዘና ፈታ እንላለን ዘፈን የፈለጋችውትን ለመምረጥ @Heluuuu_bot ውድ የቻናላችን ተከታዮች ሀሳብ አስተያየት መስጠት ከፈለጉ እንዲሁም ለቻናላችን ማጋራት ሚፈልጉት ቆየት ያለ ሙዚቃ ካለ 👉 በነኚ በኩል ያግኙን @mark_sistu

Show more
Ethiopia2 732The category is not specified

📈 Analytical overview of Telegram channel ቆየት ቆየት ያሉ ሙዚቃዎች

Channel ቆየት ቆየት ያሉ ሙዚቃዎች (@riyit) is an active participant. Currently, the community unites 10 338 subscribers, ranking in the Other category and 2 732 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 10 338 subscribers.

According to the latest data from 04 December, 2024, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 285 over the last 30 days and by 5 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
እንደኔ ኦልድ ዘፈኖች ወዳጆች ኑ ከኔጋ ዘና በሉ @Riyit Join ይበሉቻናል ላይ full ዘፈኖች ያገኛል ደስ ያሉትን ዘፈን እየተገባበዝን ዘና ፈታ እንላለን ዘፈን የፈለጋችውትን ለመምረጥ @Heluuuu_bot ውድ የቻናላችን ተከታዮች ሀሳብ አስተያየት መስጠት ከፈለጉ እንዲሁም ለቻናላችን ማጋራት ሚፈልጉት ቆየት ያለ ሙዚቃ ካለ 👉 በነኚ በኩል ያግኙን @mark_sist...

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 05 December, 2024), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Other category.

10 338
Subscribers
+524 hours
+637 days
+28530 days
Posts Archive
​​​​#መቅደላዊት #ክፍል_34 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ሜላት ከጓደኞቿ ጋር ሆና ሻይ ቡና እየጠጣች " ግን ከእውነትሽ ነው ናሆምን ተውሽው በቃ ረሳሽው" አለች ሜሮን "" አወ ረሳሁት አለች እና እጇን አውለበለበች። ሁሉም በአንድ ላይ ሳቁ ሜሮን ግን አልሳቀችም " አትዋሽ ራስሽን እየሸወድሽ ነው እስካሁን እራስሽን አምነሽ ተጎድተሻል አሁን ደግሞ ራስሽን ሸውደሽ ልትጎጅ ነው። ይሄ አፍቅረሽ ከተጎዳሽው በላይ ይጎዳሻል። ሜሊ ቆም በይ በዚህ መልኩ ሳይሆን በሌላ መልኩ ነው የሚሻለው" አለች ሜሮን የሜላትን አይን እየተመለከተች " እውነትሽን ንገሪኝ እውነት ያን ልጅ ከህይወትሽ በቀላሉ አስወጣሽው? በቀላሉ ነበር የገባው ማለት ነው? ልመንሽ?" አፋጠጠቻት ሜላት ተቀለሰለሰች አይኖቿ ተርገበገቡ ሜሮን የሆዷን የውስጧን ያወቀችባት ያህል ተሰማት " ሜሪ እኮ ልክ ናት ራሴን እየሸወድኩ ነው ናሆምን አለማሰብ እሱን አለመናፈቅ አለማፍቀር እንዴት ይቻለኛል " አለችና ግን ደግሞ " አሁን ላይ ሁሉም ነገር ተቀያይረዋል። እንደ በፊቱ አይደለም በናሆም ተናድጃለሁ ስለዚህ ከዚህ በኋላ ለእኔ ናሆም የሚባል ህይወቴ ውስጥ አይኖርም።" አለች " ሜሊ እንዲህ ቢሆን እኮ ከምንም በላይ በተደሰትኩ ነበር ግን እውነት አይደለም አንቺ እሱን በዚህ ፍጥነት??? ሀሀሀሀ ከዚህ በፊት እኮ አሁን ካደረገሽ የሚበልጥ ነገር አድርጎሻል " አለች ሜሮን " " በቃ እስከ ዛሬ አልታያትም ነበር አሁን ግን ራሷን ስትሆን ምን ማድረግ እንዳለባት ተረዳች ይሄ እኮ ግልፅ ነው ሁሌም ተመሳሳይ ስህተት አይሰራም እኮ ሜሪ " አለች ሚሪያክ " ከዚህ በላይ ምንም ልል አልችልም ሜሊ አንቺ የምትፈልጊውን አድርጊ ነገር ግን እኔን እንደ ጓደኛ ካማከርሽኝ ራስሽን መሸወድ አቁመሽ ትክክለኛ ማድረግ የሚገባሽን ነገር አድርጊ ነው የምልሽ ።" አለች ሜሮን ** ናሆም ከዶርሙ ጓደኛ ናትናኤል ጋር የመማሪያ ክፍል ውስጥ ሆነው እያነበቡ ነው። በመሀል ናትናኤል " ናሆም ግን ያቺ ሜላትን ምን አደረካት በጣም እኮ ነው የምትወድህ " አለ " እንዴት እንደዚህ ልትለኝ ቻልክ"አለ ናሆም አንዳች ነገር ገምቶ የሚያነበውን ሀንድ አውት እየከደነ በጥሞና ለማዳመጥ " ሰሞኑን ስለ አንተ ነው ሲወራ የምሰማው ከወደ ሴቶች ብሎክ ብዙ እየተባለ ነው። ናሆም ሜላትን አልፈልግሽም አላት " ምናምን እየተባለ ተጋኖም ሊሆን ይችላል ብቻ ብዙ እየተወራ ነው። " ወይ ጉድ ምን አይነት መከራ ገባሁ ዘንድሮ" አለና ባሩክ ከወንበሩ ብድግ አለ " እኔ ሲመስለኝ ከአንተ ባላውቅም ይሄን ነገር ማስተካከል ሳይኖርብህ አይቀርም ልጅቱ ልትጎዳ ትችላለች " አለ ናትናኤል ባሩክ በዝምታ ቆዘመ የሚለው ሁሉም ነገር የተዘበራረቀበት መሰለው ዞረበት ራሱን ይዞ ከእንደገና ተቀመጠ " ናሆም ደህና ነህ አመመህ እንዴ?" አለ ናትናኤል " አይ ደህና ነኝ ወንድሜ ትንሽ ራሴን አዙሮኝ ነው " አለ። " ምን ብየ ነው የማስተካክለው? እንዴት አድርጌ ህይወት ግን እኔ ላይ ምነው ሰይጣን ሆነችብኝ? " ከራሱ ጋር አጉተመተመ " ናትናኤል ወዳጄ አሁኑኑ ወደ ዶርም መሄድ አለብኝ ?" አለ ናሆም " ከዛስ ሄደንስ ወንድሜ ምንድነው ነው የምናደርገው?" አለ ናትናኤል " እዛ ሄደን መወያየት ማውራት አለብኝ" አለና ወረቀቶቹን ሰብስቦ ሄደ ናትናኤልም ተከተለው። *** ሜላት ከጓደኞቿ ጋ ተለያይታ ዶርም ትንሽ ከተቀመጠች በኋላ ብዙ ነገሮች ሲደራረቡባት ጊዜ ልብሷን ቀይራ ከላይ ሻርፕ ቢጤ ጣል አድርግ በቢጃማ አየር ለመቀበል ከዶርም ወጣች። የሴቶችን ብሎክ ጨርሳ እንደወረደች የወንዶች ብሎክ ቁጥር አስርን ወደ ቀኝ ትታ በግራ በኩል ታጥፋ ወደ ጂምናዚየሙ አዳራሽ አቅጣጫ እየሄደች እያለ ራሷን ይዛ ለትንሽ ደቂቃ ቆመች። ሁኔታዋን እየተከታተለ የነበረ አንድ ልጅ ተጠጋት ፈራ ተባ እያለ ሰላም ነሽ? የምረዳሽ ነገር አለ? ዝም አለች ደህና ነሽ አይደል" አለ? በድጋሚ አሁንም ዝም ስትለው ግራ ገባው ደነገጠ " ከጀርባዋ ነካ ሲያደርጋት እንደመጮህ ብላ ዞረች። ስታየው ደነገጠች እሱም ደነገጠ ሜላት እንደሆነች አላወቀም ነበር። አይኖቹን ጨፍኖ የራስ ቅሉን አነቃነቀ " ሜ ሜ ሜላት " አለ ከብዙ እይታ በኋላ " መርዕድ?" አለች በአወንታ ነቀነቀ። አቀፈችው አቀፋት ለደቂቃ ያህል ተቃቅፈው ቆዩ። ከእቅፉ ከወጣች በኋላ " እኔ እኮ አንቺ አልመሰልሽኝም ?" አለ መርዕድ " ምን ታደርገዋለህ እኔ ነኝ አንተ ግን እንዴት ነህ " " አለሁልሽ ይሄው ምን እሆን ብለሽ ነው " " አድዋ ምን እግር ጥሎህ ነው?" " ኤም ኤስ ለመስራት ይሄው ተከስትኩ" " በጣም ደስ ይላል እንኳን ወደ ቀድሞው ዩኒቨርስቲህ በሰላም መጣህ " እንኳን በሰላም ቆየሽኝ ግን እንዲህ ሞቅ ያለ አቀባበል የሚገባቸው ረዘም ላለ ጊዜ ጊቢውን ለለቀቁ ነው። " " ሀሀሀ እሽ እንዳልክ ደረቁ መርዕድ እና ህይወት እንዴት ነች? " አለች " ደህና ነች እሷ ምንትሆናለች እኔን አግኝታ " አለ " እረ ባክህ ጓደኛ ያዝክ እንዴ?" አለች " ስቀልድሽ ነው እንዲህ ቀላል ነው እንዴ በአጭር ጊዜ አዲስ ሰው ማስገባት?" አለ መርዕድ " እሱስ ልክ ነህ ይከብዳል እረዳሀለሁም " አለች " ግን አንቺ እንዴት ነሽ በጣም ተጎሳቁለሻል አልተመቸሽም በዚህ ስአትስ ምን ትሰሪያለሽ ?" አለ " በዚህ ስአት ምን እሰራለሁ ብለህ ነው መርዕድ ያው የተለመደውን የህይወት እሽክርክሪት እዞራለሁ እንጅ ራሴን ለማግኘት እወጣና ከመጀመሪያው የባሰ አጥቼው እመለሳለሁ እንዲህ ሆንኩ እንግዲህ መርዕድ " አለች " አዝናለሁ ምን እንደደረሰብሽ ባላውቅም ግን ይሄ ለአንቺ አይገባሽም " አለ ፈገግ አለችና " አንተስ በዚህ ስአት እንዴት እዚህ አካባቢ ተገኘህ?" አንድ አዲስ ፍሬሽ ተማሪ ጓደኛ አለኝ እሱን ለመጠየቅ ነው።" አለ " " ማነው? ድንገት ላቀው እችላለሁ " አለች " ናታኔም ነው የሚባለው ታቂዋለሽ ያን ያህል ታዋቂ አይመስለኝም " አለ " ናታኔም ማለት የናሆም ጓደኛ አይደል?" አለች " ናሆም ማነው?" አለ " አይ መርዕድ አታውቀውም ዶርም ሜቱ ነው " " እንደዛ እንኳ ሊሆን ይችላል ግን አዲስ ላይ እንዲህ የሚባል ጓደኛ እንደሌለው አውቃለሁ ለማንኛውም ግን ሁሌም ነበር የማስብሽ ታውቂያለሽ ዛሬም እንደዛው ነኝ በአንቺ ላይ እስከመጨረሻው ተስፋ አልቆርጥም " አለ " አየ መርዕድ ምነው ሁሉም ወንድ እንዳንተ በሆነ ግን ለአንተ የምገባ ሴት አይደለሁም በዛ ላይ አዲስ ሰው ህይወቴ ውስጥ ገብቷል። እሱን የራሱ አድርጎኛል አልቻልኩም አሸነፈኝ " አለች መርዕድ ትክዝ ብሎ ከቆየ በኋላ ። " በቃ ሜሊ መሄድ ሳይኖርብኝ አይቀርም " አለ እጁን እየዘረጋላት ** " በእኔና አንቺ ጉዳይ በጣም ተጨንቋል እርግጠኛ ነኝ ባሩክ እንደዚህ ሲሆን አይቼው አላቅም። ግን ሊነግረኝ ያልፈለገው እንድንረበሽ ስላልፈለገ ነው። ከዚህ በላይ ላስጨንቀው አልፈልግም የናሆምን ጉዳይ እንደጀመርኩ መጨረስ ይኖርብኛል ። አንቺ አታስቢ እኔ እወጣዋለሁ።" አለ ናታኔም " "የኔን ጉዳይ ከማን ጋር ጀምረህ ነው ብቻህን የምትጨርሰው " አለ ናሆም ወደ ዶርም እየገባ? ይቀጥላል ..................... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 35♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

​​​​#መቅደላዊት #ክፍል_33 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ የመማሪያ ክፍሎች በተለምዶ ( space ) እየተባሉ በማታ የሚጠሩት እንዲሁም አራቱም ቤተመፅሀፍቶች በተማሪወች ተጨናንቀዋል ሁሉም ( tension ) ይዞታል በየ ቴንሽን ቦክሶቹ ተደብቆ ተመስጧል። ማንም ማንንም በማይሰማበት በዚህ ስአት አንዳንድ ተማሪዎች ደግሞ ቤተመፅሀፍት ውስጥ ያንሾካሹካሉ። ይጠያየቃሉ ከቤተመፅሀፍት ተቆጣጣሪዎች ተደብቀው ይረዳዳሉ። ገሚሶቹ ደግሞ የጆሮ ማዳመጫቸውን (earphone ) ሰክተው ያነባሉ። ሙቀቱ ያስቸገራቸው እና ብዙ መቀመጥ የማይወዱ ተማሪዎች ደግሞ የቤተመፅሀፍቱ መግቢያ በር ላይ ተቀምጠው ስልክ ያወራሉ ይጎረጉራሉ። ዛፉ ስር ደግሞ የተተቃቀፉ ጥንዶች ማየት የተለመደ ነው። * ባሩክ ( ዲዮጋን )አሉላ አባነጋ ብሎክ ጀርባ ካለች ግራር ዛፍ ስር ተቀምጦ ሙዚቃ ከፍቶ ያነባል የሚከፍተው ላለመስማት አይደለም የከፈተውን ሙዚቃ ጆሮ ሰጥቶ ያዳምጠዋል። ለዚህም ነው ብዙወች ባሩክን (ዲዮጋንን) የሰው ተቃራኒ ነው የሚሉት ሰው በሚረበሽበት ነገር ላይ ስለማይረበሽ ነው። የሚያዳምጠው ደግሞ የድሮ ሙዚቃዎችን ነው። አሁን ደግሞ የጂጂን ሙዚቃ ይሰማል። የሚያነበውን " the battle of adwa " የተሰኘውን የ remond jonas መፅሀፍ ዘግቶ በጂጂ ሙዚቃ ተመሰጠ። ሁልጊዜም ባሩክ ስለ ዘፋኞች ሲያወራ ጂጂን የሚገልፅበት ቃላቶች ይገርማሉ። እንደውም ብዙ ጊዜ የሀይሉ ቢታንያን አገላለፅ ይጠቀማታል " ጂጂ እኮ" ይልና ከእንደገና " ቆዩ እስኪ ትንሽ ሀሳቤን ልሰብስብ እሷን እገልፅበት ቃላት ላጠራቅም " ይላል ብዙ ነገሮችን መግለፅ የማይሳናው ፈላስፋው ባሩክ ስለ ጂጂ ግን ይንተባተባል። ከዛ እንደምንም ቀልቡን ሰብስቦ እንዲህ ይላል " ጥበበኛዋ ባለ ጥበብ ቀሚስ ውበት አንድ ቀን ብትሆን ኖሮ ጂጂ አመት ትሆን ነበር ጥበብ አንድ ወር ብትሆን ኖሮ ጂጂ ሁለት አመት ትሆን ነበር፣ ትህትና አንድ ቀን ብትሆን ኖሮ ጂጂ መንፈቅ ትሆን ነበር፣ ጂጂ እሷ ምስጢር ናት! ዘረኝነትን ለማጥፋት አስቀድማ አንድነትን የዘራች ገበሬ፣ ላዛን ያበቀለች ልዩ አፈር፣ የሰውነትን ክብር ያነፀች ግንበኛ! ሀገርን ከግጥሟ፣ ፍቅርን ከድምጿ፣ ሰላምን ከእንጉርጉሮዋ፣ ናፍቆትን ከዜማዋ፣ ጀግንነትን ከቅላፄዋ፣ አንድነትን ከልብሷ፣ ቅኔን ከምቷ ታገኘዋለህ። " ታላቅ ጥበበኛ አገሩን ይሰፋል" እንዲሉ እጅጋየሁ በትንቢት ሸራ ምንጣፏ በትናንትናው እይታ ኢትዮጵያን ሰፍታታለች። ስለ ካህናት አለቃው፣ ስለ ጥበበኛው ፣ ስለ ደጉ ሳምራዊ ቀልጦ ስለበራው ካህን በሰምና ወርቅ ለውሳ አዚማልናለች።ጭንቀቷ የስንኞች ቤት መምታት አይደለም። የምትዘፍንለት ታሪክ የዜማው አወራረድ ከገጠመላት ብቻ ትሞዝቃለች።ጂጂ አርቲስታችን ብቻ ሳትሆን ምልክታችንም ናት።እሷ በጀሮ የምትነበብ መፅሀፍ ናት። " ይልና ከልቡ ያለቅሳል " እሷ ስትዘፍን ያላደኩበት መንደር አቀማመጥ፣ ያልነካሁት የሰብል ዛላ ያልቦረኩበት ቀየ፣ ያልነፋሁት ዋሽንት፣ ያልሰማሁት የፏፏቴ ድምፅ፣ ያልዋኘሁበት ወንዝ ፣ ያልሮጥኩበት ሜዳ፣ ያልዋልኩበት ጋሪያ ሸንተረሩ ይናፍቀኛል ። በግጥሟ ውስጥ በስንኟ ጀግንነትን በዜማዋ ፍቅርን ትዘክራለች ጂጂ በአጠቃላይ ትለያለች። በቃ ምን ልበላችሁ ሀይሉ እንዳለው እሷ በጀሮ የምትደመጥ መፅሀፍ ናት " ይልና በሀሳብ በትዝታ ወደ ኋላ ይሄዳል ዛሬም እንደልማዱ እዚች ግራር ስር ተቀምጦ በጂጂ ሙዚቃ ተመስጧል። ጎምበስ ቀና እያለ አዝመራው ከፊቴ፣ ቁልቁል ሲወረውር ከማዶ ፏፏቴ፣ ዋሽንቱን ሲጫወት ልስልስ ባለ ዜማ፣ ደህና ሁን አሰኘኝ ደህና ሁን ከተማ፣ ከግራ ገብስ ሆነህ ከቀኝ ስንዴውን፣ አቋርጨ አልፌ ሳየው ሸጋውን፣ ልቤን እያመሰው የዋሽንቱ ዜማ፣ ደህና ሁን አሰኘኝ ደህና ሁን ከተማ። አሆ ማምየ ደህና ሁን ከተማ አሆ ማምየ ተሰነባበተኝ አሆ ማምየ እሰማው የለምወይ አሆ ማምየ ወሻንቱ ሲጠራኝ። አሆ ማምየ አንተ ያገሬ ልጅ አሆ ማምየ መዋያህ ከማማ አሆ ማምየ ወጣሁ ካገር አገር አሆ ማምየ ሰለቸኝ ከተማ። ጂጂ አርፋ ትቀጥላለች .................... ** ምሽት የጨለማ ዳሱን ጥሎ ከተሞሸረ ስአታት አልፈውታል፣ ከወደ ምዕራብ በኩል ባለ ትንሸ ቅርጿ ጨረቃ ብትወጣም ከድቅድቁ ጨለማ ውስጥ ግን ማውጣት አልቻለችም። ነገር ግን ዩኒቨርስቲው በየ መንገዱ ጠርዝ በተገጠሙ ባውዛወች ቀን መስሏል። ናታኔም የዕለቱን ጥናት አገባዶ ወደ ዶርሙ እየወጣ አንደኛውን ፍሎር እንደጨረሰ በመተላለፊያው መስኮት ማዶ ሲመለከት ፊት ለፊት ባሩክ ተቀምጦ አየው። " ያ ባሩክ አይደል ?" አለና ራሱን ጠይቆ አወ ራሱ ነው አለ ከእንደገና በደንብ ካስተዋለው በኋላ ተመልሶ ባሩክ ወዳለበት ዛፍ አመራ። " በሰላም ነው ወንድሜ ምን ሆነሀል?" አለ ናታኔም " ባሩክ እንደመባነን ብሎ በእምባ የራሱ ጉንጮቹን እያበሰ ቀና ሲል ናታኔም ነበር ደንገጥ ብሎ " እንዴ ናቲ መቸ ተገኘህ ቆየህ እንዴ ወዳጄ?" አለ ባሩክ " ኧረ አሁን ነው የመጣሁት ወደ ዶርም ስወጣ ደረጃ ላይ ሆኜ አይቼህ እኮ ነው የመጣሁት ምን እያደረክ ነው? " አለ ናታኔም " ምንም እንዲሁ ራሴን እያወራሁትም እያዳመጥኩትም ነው። ጥናት እንዴት ነው ፋይናል ደረሰኮ እያጠናቀክ ነው?" አለ ባሩክ " አወ በደንብ ማንበብ አለብህ በዚህ ሲሚስቴር አሪፍ ውጤት ማምጣት አለብህ የመጀመሪያ አመት ውጤት ያኖራል ከቻልክ አራት ካልቻልክ ደግም ከሶስት ነጥብ አምስት በላይ ሊኖርህ ይገባል። " አለ ባሩክ " እሽ ወንድሜ እሰራለሁ ግን በእኛ ጉዳይ በጣም ተጨንቀሀል እንዴ? ንገረኝ በናትህ ባሩክ" አለ ናታኔም በልመና " ኧረ ምን ሆነሀል አንተ ልጅ ይሄ ጥናት ትንሽ እንዳታስብ አድርጎሀል መሰል እንዴት ነው በእናንተ ጉዳይ የምጨነቀው አታስብ እኔ የማስበውን ማድረግ ነው እንጅ የማስበው መጨነቅን አይደለም የማስበው። በጭራሽ እንዲህ እንዳይሰማችሁ ለመቅደላዊትም እንዳንተ ተመሳሳይ ሀሳብ ሊኖራት ስለሚችል ንገራት። " ብሎ ኮስተር ካለ በኋላ " ታውቃለህ ጂጂን ሳዳምጥ አለም ትሰማኛለች ትላንት ትዝ ይለኛል ነገ ደግሞ ይታየኛል ። ጂጂን የማዳምጠው የትላንት ውሌ የዛሬ ገመዴ የነገ ክሬ ሲላላብኝ ነው። ህህህ ዘመን የማይሽራት ፈርጥ ሰው እሷን በየ አንድ አመት ልዩነት ደጋግሞ አይወለድም " አለ እና ወደ ናታኔም ቀና አለ ። ናታኔም የባሩክን እምባ ያረገዙ አይኖችን ሲያይ ከፋው። ምንም ሊለው አልፈለገም " ምንስ ብለው እሱ ያላሰበው ይኖራል " እሽ ወንድሜ እንዳልህ ብቻ አንተም እንደኛ ተማሪ ተፈታኝ ስለሆንክ እንድትጨናነቅ ስለማልፈልግ ነው " አለ ናታኔም " አወ ይገባኛል አታስብ አነባለሁ እያነበብኩም ነው። " አለ ባሩክ ይቀጥላል ..................... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 34♥️ ነገ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

​​​​#መቅደላዊት #ክፍል_32 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ናሆም ወደ ጊቢ እየመጣ ሳለ ስልኩ ጠራ " አቤት መቅደላዊት ደህና ነሽ?" አለ " አለሁ አንተ እንዴት ነህ? አለች አይኗን እያስለመለመች ቶሎ ቶሎ ትተነፍሳለች " ችግር አለ ደህና ነሽ?" አለ ናሆም ግራ እየተጋባ " አ አ አ ይ የለም ለ ለ ምን እንደዛ አልክ?" በጠዋት ስደውይ ጊዜ ግራ ገብቶኝ ነው" አለ። "ኧረ ሁሉ ሰላም ነው በጠዋት ነበር እና የተነሳሁት እንዲሁ ነው ዝም ብየ ለአንተ መደወል ፈልጌ ነው " አለች ናሆም ከሁኔታዋ አንድ ነገር እንደሆነች ተረድቷል። ግን ደግሞ ልትነግረው እንደማትፈልግ እርግጠኛ ሆኗል ። ትንሽ ካሰበ በኋላ ሁኔታውን በዝምታ ማለፍ ፈለገና "እሽ ካልሽ እንግዲህ ታዲያ ምን ልልሽ እችላለሁ ምንም አልሆንኩም ካልሽ " አለና መልካም ቀን እንዲሆንላት ተመኝቶ ስልኩን ዘጋው ። ከዘጋው በኋላ " ናሆም ጥያቄዎችን ማውጣት ማውረድ ጀመረ " በዚህ ስአት እንዴት ልደውል ቻለች? የሆነ ነገርማ አለ በእርግጠኝነት!! እህ ቆይ ምን አገባኝ ለምንድነው ለዚች ልጅ በተደጋጋሚ የማስበው ለምንድነው የምጨነቅላት? የራሷ ጉዳይ ለራሴ ብዙ ችግሮች ያሉብኝ ሰው ደግሞ ሌላ ችግር መቅደላዊት የሚመታውን ልቧን ደግፋ አንድ ጊዜ በረጅሙ ተነፈሰችና በህይወቷ እንደዚህ ደንግጣና ልቧ መትቶ እንደማያውቅ የተረዳችው ልቧን የተደገፈው ግራ እጇ ብድግ ብድግ ሲል በማየቷ ነበር።"እውነቱን ነበር ባሩክ ጌታየ ሆይ ቅዠት ነበር ። " ብላ ተመልሳ አልጋዋ ላይ ጋደም አለች። ባሩክ ያላት ነገር ትዝ አላት ደህንነት እንዲሰማት የቻለውን ሁሉ ይጥራል። " በጣም ደግ ነው ምነው ቀድሜ አውቄህ ቢሆን ባሩክ የአንተ የሆነች ታድላ ሁሌም ሙሉነት እየተሰማት ትኖራለች " ብላ በስሱ ፈገግ አለች። የሷን ፈገግታ ተከትላ ፀሀይም በስተምስራቅ ፈገግ አለች። ይሄኔ መቅደላዊት ከአድማስ ማዶ ወደ ወጣችው ልጅ ፀሀይ አይኖቿን ልካ " እውነትና ንጋት ውሸትና ምሽት!! ህህህ ይገርማል " አለች። * " አንተ ቆሻሻ በህይወቴ እንደቀለድክብኝ አትቀርም ዋጋ አስከፍልሀለሁ። አሁን ዝም የምልበት ምክንያት የለም። ማን መብት ሰጥቶህ ነው እንደዚህ በሰው ህይወት አድራጊ ፈጣሪ ያደረገህ? አንተ ነህ ህይወቴን እንዴት መኖር እንዳለብኝ የምትነግረኝ? ምን አግብቶህ አንተ ማነህ? እናቴ ምን ብላህ ነው ምን ያህል ገንዘብ ሰጥታህ ነው? መልስልኛ አንገትህን አንቄ ሳልገልህ? እንዴት እኔ ላይ እንዲህ ታደርጋለህ? እናቴና ሁሉም ሰው ላይ ያደርኩት ልክ እንዳልሆነ አውቃለሁ ግን ደግሞ ሁሉም ሰው የጁን ማግኘት አለበት እናቴም እኔንና አባቴን ትታን በመሄዷ ዋጋዋን ማግኘት አለባት። አ እ እ ንገረኝ ከመጀመሪያውም ጓደኛየ ያደረኩህ ስርዓት ያለህ መስሎ ስለታየኝ ነበር ግን ልክ አይደለሁም ። ሰማህ ናታኔም ከዚህ በኋላ አንድ ነገር ብታደርግ አባቴ ይሙት እገልሀለሁ። " ብሎ አንገቱን ለቀቀው። ናታኔም ከተኛበት ብንን ብሎ ተነሳ አማተበ የሆነው ሁሉ ቅዠት ነበር።በሩጫ እንደደከመ ስፖርተኛ ላበቱ ጥምቅ ብሎ ያለልክ ይተነፍሳል። ቀስ ብሎ ከአልጋው ተነስቶ ወደ በረንዳው ሲያይ አንዳንድ ተማሪዎች ወደ ቁርስ ይሄዳሉ ፀሀይዋ ወጥታለች። ተመልሶ ገብቶ ወደ ናሆም አልጋ ሲያይ ናሆም አልጋው ላይ የለም። " የት ሄዶ ነው? ላይብረሪ ሄዶ ይሆን? ወይስ ቤተክርስቲያን? ስልኩን አንስቶ ደወለ " ሰላም ነው ናሆም የት ሄደህ ነው? " አለ ናታኔም "ጊቢ ጉባኤ ሄጀ ነበር አሁን ግን ጊቢ ደርሻለሁ ሰላም ነሀ?" አለ ናሆም " ሰ ሰ ሰ ላም ነኝ አልጋህ ላይ ስላጣውህ ነው እሽ በቃ ደህና ከሆንክ" አለ ናሆም" ኧረ ዛሬ ምንድነው አንተና መቅደላዊት በየተራ ደውላችሁልኝ ምነው በህልማችሁ አያችሁኝ እንዴ "ብሎ ሳቀ " ምን? " አለ ተርበተበተ " በህልማችሁ አያችሁኝ ስትል ምን ለማለት ፈልገህ ነው?" አለ ናታኔም የልቡን ያወቀ መስሎት መቅደላዊት ደውላልህ ነበር?" " አወ ደውላ ነበር ደህና አትመስለኝም ግን ደግሞ የሆነችውን ልትነግረኝ አልቻለችም " አለ ናሆም " የ የ የሚገርም ነው ምን ሆና ይሆን?" አለ ናታኔም " አላቅም ደውልላት " አለ ናሆም " እስኪ እደውልላታለሁ" አለ ናታኔም " ምን ተፈጥሮ ነው መቅዲ በጠዋት ለናሆም የደወልሽለት?" አለ ናታኔም " ዛሬ በህልሜ ናሆም እውነታውን ደርሶበት ሲያባርረኝ ሲያስፈራራኝ ነው ያደረው" ብላ ስቅስቅ ብላ አለቀሰች " ናታኔም በምን ቀን ነው አንተን ያወኩህ? ምን ያህል እየተሰቃየሁ እንደሆነ አታውቅም? በሰቀቀን ሞትኩኮ ናቲ አሁን ሰማ አልሰማ አወቀ አላወቀ እያልኩ ቀነስኩ እኮ" አለች መቅደላዊት ሆዷን ባር ባር እያለው " ይገባኛል ይሄ ነገር አንቺ ላይ ብቻ አይደለም የተፈጠረው እኔም ጋ ነው የተፈጠረው እንደ አንቺ ዛሬ ሌሊት እንደ አንቺ ሲያቃዠኝ ነበር ያደረው ናሆም እውነቱን አውቆ ሲያባርረኝ ሲያንቋሽሸኝ ነው ያደረው። ሁሉም ነገር ከባድ ሆኗል እኔም መቋቋም አልቻልኩም ይሄን ነገር እልባት ሰጥተን ልንቋጨው ይገባል። አላውቅም መጨረሻው ይመር አይመር ግን በቃ ማለቅ አለበት። እኛ በሰው ችግር ገፈት ቀማሽ እየሆንን ነው። " አለ ናታኔም ተሰላችቶ " እና ምን አሰብክ?" አለች መቅደላዊት " ባሩክን ማውራት አለብኝ " አለ " ጠዋት ደውየለት ነበር ስለ ሁኔታየ አወራሁት ያው እሱ ያለው ትምህርታችሁ ላይ ትኩረት አድርጉ እኔ እወጣዋለሁ ነው ያለው የእኔን ቅዠትም ቀን ያየሁትን ሌሊት ላይ ያየሁት ነው የመሰለው ግን ሲመስለኝ የሆነ ነገር አስቧል። ስነግረው ቀለል አድርጎ ነው ያወራኝ!" አለች ይቀጥላል ..................... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 33♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

​​​​#መቅደላዊት #ክፍል_31 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ "If the world is against truth, then I am against the world" (አለም በሙሉ ከእውነት ጋር ቢቃረን እንኳን እኔ ብቻየን ከአለም ጋር እቃረናለሁ" ይሄን ያሉት ከሺህ አመታት በፊት ቅዱስ አትናቲዮስ ናቸው። ከአንድ አዳራሽ ሙሉ ሀሠተኛ ሀሳዊ መሲሆች ስብስብ ተነጥለው ሲወጡ የተናገሯት ንግግር እስካሁን ድረስ ትጠቀሳለች።" አለ ባሩክ " እና ምን ለማለት ፈልገህ ነው?" አለ ጓደኛው ያለ አንዳች ነገር እንዳልተናገረው ገብቶታል ። ባሩክ ( ዲዮጋን ) አይኖቹን ማዶ ላይ ተክሎ በቀኝ እጁ የያዛትን እስክርቢቶ ያለ መታከት ከጠረጴዛው ጋር ያጋጫታል። " ቋ ፣ ቋ ፣ ቋ ይላል ይሄኔ ሰለሞን የባሩክን ምላሽ ለማግኘት " ቋ "ን አምብበኸዋል? " አለ ባሩክ ተነስቶ ሄደ ። ሰለሞን በሁኔታው ግራ ተጋብቷል ግን ምን ማድረግ ይችላል ባሩክ ከውስጡ ካልሆነ ሰወች እንዲደሰቱ ምናምን በማለት ከአመለካከቱና ከፍላጎቱ ዝንፍ አይልም ። ይሄን ባህሪውን ስለሚያውቅ ከንፈሩን እያሸራመጠ ዝም አለ። ባሩክ ዶርም ገብቶ የሚይዝ የሚጨብጠውን አጣ " አሁን እኔዴት ነው ማስተካከል የምችለው? ልጁን እንዴት ነው ጓደኛየ የማደርገው እንዴት ነው መቅደላዊት ያለችውን ነገር እንዲረሳ ማድረግ የምችለው አላውቅም ራሴ ላይ ትልቅ ነገር የጫንኩት ቢሆንም መጀመሪያ የሆነ ነገር ልብላ " አለና ተማሪዎች ከፍለው ወደ ሚመገቡባቸው የመመገቢያ ሬስቶራንቶች ሄደ ። ከትንሽ ደቂቃ በኋላ ያዘዘው እንቁላል ስልስ ቀረበለት ኮካውን አብሮ ከስልሱ ጋር እያወራረደ ማሰብ ጀመረ። በምንም ጭራሽ ሀሳብ ሊመጣለት አልቻለም ። ከሁሉም የሚከብደው ደግሞ የማጠቃለያ ፈተና ( final ) መቃረቡ ነው። እሱም ቢሆን እነ ናቲ አንድ አይነት ጊዜ እና Program ነው ስለዚህ ያለው አማራጭ አሁን ሁሉንም መተው እና ለbreak time ማዛወር እንደሆነ ይወስናል ።ባሩክ በዚህ ሀሳቡ ይፀናል። በቃ እሱ ነው የሚሻለው ለተወሰነ ጊዜ መተው ። ህህህህህህ አይ ጉድ ምንድነው ነበር ያለው አርስቶትል? ህይወት የእጣፈንታ ቅንብር ነች" ልክ ነው አርስቶትል ህይወት እጣ ፈንታ ነች። ግን ደግሞ እጣ ፈንታ ከሁሉም የበለጠ ተስፋ ነው። **** ንጋት የጨለማን ጎህ እየቀደደ በውፎች ልዩ ጥዑም የጫጫታ ዜማ ታጅቦ ነጋሁ ነጋሁ ይላል። ነጠላውን አጣጥሎ ከዩኒቨርሲቲው አጠገብ ከተሰራው የጊቢ ጉባኤ ሚካአል ቤተክርስቲያን የጠዋቱን ቅዳሴ ለማድረስ ሩጫን በሚያስንቅ እርምጃ ይሄዳል። መንገዱ ግራ ቀኝ በተገጠሙ ባውዛወች ቀን መስሏል ። ግራ ና ቀኙን እያማተረ ትንሽ ከሄደ በኋላ የቤተክርስቲያኑ ቅጥር ግቢ ደረሰ። " እኔ ላይ ለምንድነው ችግሮች የሚደራረቡብኝ እባክህ ፈጣሪየ ሁሉንም ድል እንዳደርግ እርዳኝ፣ አልቻልኩም መላዕኩ ቅዱስ ሚካኤል እባክህን እባክህን " እያለ የመቅደሱ በር ላይ ተንበርክኮ ይፀልያል ። ናሆም አይኖቹ እምባ አቀረሩ " ፈጣሪየ እርዳኝ ሁሉም ነገር ሰልችቶኛል ደክሞኛል አልችልም ከዚህ በላይ ምንም ነገር ቢሆን ፈተናው ይበቃል። ህይወቴን አታክብድብኝ አምላኬ ሆይ " እያለ ይለማመናል ይፀልያል ያለቅሳል። **** መቅደላዊት ከሚያቃዣት ህልም ፍንጥር ብላ ተነስታ አልጋዋ ላይ ቁጭ አለች። አማተበች አይኖቿን እንደገና እያሻሸች ዙሪያ ገባውን አየች ምንም ነገር አልነበረም ከእንደገና አንገቷን ደፋች። ከአልጋዋ ተነስታ መስኮቱን ከፍታ ስትመለከት ጨለማው እየለቀቀ ብርሀን ደግሞ ወገግ እያለ ነው። በመስኮቱ አሻግራ ስትመለከት ከአንዳንድ ተማሪወች ውጪ ብዙም የሚመላለስ የለም ። " ክፉ ቅዠት ነበር " አለችና ስልኳን አውጥታ ደወለች " አቤት መቅደላዊት ሰላም ነሽ???" አለ ባሩክ " አወ ደህና ነኝ ባሩክ ይቅርታ በጠዋት ስለደወልኩ ሰላም ነህ? ምን አዲስ ነገር አለ?" አለች " ምንም የለም በሰላም ነው በጠዋት እንዲህ የጠየቅሽኝ " ይላታል። " ዛሬ ሌሊት በህልሜ ናሆም ሁሉንም አውቆ ሁላችንንም እያሳደደን አየሁ" አለች " ባሩክ ለመሳቅም ፈለገ ለመቆጣትም ፈለገ ግን ሁለቱንም ማድረግ እንደሌለበት ወሰነና " መቅዲ ተረጋጊ ነግሬሻለሁ ለምንድነው ብዙ ጊዜ ስለዚህ ጉዳይ በተደጋጋሚ የምታስቢው? እወጣዋለሁ ብየሽ ነበር እኮ አንቺ ትኩረት ማድረግ ያለብሽ ኤግዛምሽ ላይ ነው ። አሁንም ደግሜ እነግርሻለሁ ምንም ነገር አታስቢ ፋይናል ትንሽ ቀን ቀርቶታል እባክሽ ልለምንሽ concentrated ሆነሽ አምብቢ አዲስ ነገር ሲኖር እኔ ራሴ እነግርሻለሁ።" አለ ባሩክ ልመና የተሞላበትን ምክሩን እየለገሳት " እሽ ብላው" ስልኩን ዘጋችው። ስልኩን ዘግታም አለማሰብ አልቻለችም " ለምን ዛሬ ሊያቃዠኝ ቻለ? ለናሆም መደወል አለብኝ የሆነ ፍንጭ አገኝ ይሆናል " አለችና ደወለች። ይቀጥላል ..................... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 32♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

​​​​#መቅደላዊት #ክፍል_30 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ እቴጌ ሆቴል ሙሉ ከተፈለጠ ድንጋይ የተሰራ የባህል ቤት ነው። ተወዛዋዦች እና አዝማሪዎች የሚያደምቁት ምሽት ነው። ናሆም ጥግ ላይ ተቀምጦ ጠጁን እየጠጣ ውስጥ ላይ በተሰቀሉ ባህላዊ ስዕሎች የተመሰጠ ይመስላል ። ሜላት እጅግ ተውባ መጣች ናሆም ሜላት ወደ እሱ አቅጣጫ እየመጣች ሲያይ ተነሳና ተቀበላት በፍጹም ፈገግታ ሰላም አላትና ወንበሩን ስቦ አስቀመጣት። ሜላት በናሆም ድርጊት በጣም ተገርማለች ሁሉም ነገር ተቀያይሮባታል። ለተወሰነ ያህል ዝም ብላ ስታየው ጊዜ " እና እንዴት ነሽ ሁሉ ሰላም ነው?" አላት ዝምታውን ለመስበር ያህል " እኔ በጣም ደህና ነኝ ዛሬ ምን ተገኝቶ ነው ራት እንድንበላ የጋበዝከኝ?" አለች ሜላት ፈገግ እያለች " እንዲሁ ላይሽ ፈልጌ ነው ምነው ለምን ጠየቅሽኝ?" አለና ጥያቄዋን በጥያቄ ቋጨው " አይ እንዲሁ በድንገት ስትጠራኝ እንድዴት ዛሬ አስታወስከኝ ምን ተገኝቶ ነው? ብየ ነው በቃ ከደበረህ ተወው ጥያቄየን " አለችና ጠረምጴዛው ላይ አቀረቀረች "ሰሞኑን እንዴት ነሽ ሁሉ ነገር ሰላም ነው እያነበብሽ ነው ዝግጅትሽ ምን ይመስላል ?" " ምንም አይልም በጣም ቆንጆ ነው በደንብ እያነበብኩ ነው። " አለችና እጇን ከእጇ ላይ ጫነች ናሆም ሁኔታዋ እና ፍላጎቷ ገብቶታል አጇን መልሶ በጠ እና " እየውልሽ ሜላት ፍቅርና ህይወት ለየቅል ናቸው። ማንም ሰው ከማንም ሰው እርዳታ ውጪ ህይወቱን መምራት እና መቀጠል አለበት። የትኛውም አይነት ፈተና ሊደርስ ይችላል እሱ የህይወት አንዱ ክስተት ነው ነገር ግን ህይወትሽን ለማጠንዘል የሚመጣን ቀትር ውሀ በማጠጣት መቋቋም እንድትችል ማድረግ ይኖርብሻል ።ካልሆነ ግን ሁሌም ተሸናፊ ሆነሽ ራስሽን በሌሎች እጅ ትጥያለሽ የራስሽን ኤጣፈንታ ሰወች ሌሎች እንዲወስኑ እጅ ትሰጫለሽ። እንደዛ ደግሞ መሆን የለበትም አንቺ ጠንካራ እና ጎበዝ እንድትሆኝ እፈልጋለሁ ። አቃለሁ እንደምትወጅኝ እኔ ደግሞ ምላሽ ልሰጥሽ አልቻልኩም እሱን ደግሞ ነግሬሻለሁ። የተፈጠረው ድንገት ነበር ።ለእኔ ያ ምሽት ጥሩ ግን አጋጣሚ ነው። ለመውደድ ንፁህ መሆን አለብኝ እንደዛ ካልሆነ በረው ላይ እንደመቀለድ ነው የምቆጥረው። ለዛ ነው እንጅ አንቺን አለመውደድ አይቻልም ምንአልባትም ራሴን ስሆን የምመኝሽ ሴት እና የምፈልጋት ሴት ትሆኝ ይሆናል። ግን ያ ጊዜ አሁን አይደለም ያልሆነ ተስፋ ሰጥቼሽ ላወዛግብሽ አልፈልግም ። ምክንያቱም አንቺ ንፁህ ልብ ነው ያለሽ ተወዳጅ እእና ተፈቃሪ ነሽ ውስጥሽ ምንም ነገር የለውም ።ስለዚህ ምንም ነገር ማድረግ ስለማልፈልግ ነው እስካሁን እንደዛ ስልሽ የቆየሁት እንጅ አንቺ የማትወደጅ ሆነሽ አይደለም። እና እኔ ደግሞ ብዙ ችግሮች አሉብኝ ሜሊ የእውነቴን ነው በአሁኑ ስአት ነገሮች ተደራርበውብኝ ጎዳናው ላይ ቆሜ ነው ያለሁት ውሳኔዎችን በትክክል እንኳ እየወሰንኩ በሌለሁበት ጊዜ አንቺን ደስተኛ ላደርግሽ አልችልም ።እና እባክሽ እኔንም ተረጅኝ " አለ " እሽ እረዳሀለሁ ችግርህን ግን ብትነግረኝ እኮ እረዳህ ይሆናል በዛ ላይ ችግርን ለሰው ሲነግሩት እኮ ይቀላል እሽ በለኝ እና አብረን እንፍታው " አለች ሜላት በልመና ጭምር " የሚነገር ቢሆን ኑሮ አንቺ ትክክለኛዋ ሴት እንደሆንሽ አልጠራጠርም ። እንደምትረጅኝም ሳትነግሪኝ በፊት አላጣሁትም ግን ይሄ ለሰው የሚነገር አይደለም ራሴ ነኝ መጨረስ ያለብኝ አንቺ ብቻ እስካሁን ያልኩሽን በመረዳት እርጅኝ እሱን ካደረግሽልኝ እንደትልቅ ውለታ እቆጥረዋለሁ ሌላ ሀሳብ እንዳትሆኝብኝ ነው የምፈለገው ። አንድ ነገር ልንገርሽ የሆነ ጊዜ ግን አሪፍ ጊዜ እንደምናሳልፍ እርግጠኛ ነኝ!" አለ ። ሜላት አይኖቿ እምባ አቀረሩ ለመውጣት ሲታገሉ የነበሩት የእምባ ዘለላወቿ በመጨረሻም በጉንጯቿ ቀስ እያሉ ወረዱ። በዚህን ጊዜ ናሆም የነበረበትን ወንበር ለቆ እሷ ባለችበት ወንበር በመቀመጥ አቀፋት ።ይበልጥ አለቀሰች አባበላት። " በናትሽ እኔንም አታሳዝኝኝ አታስከፊኝ በጭራሽ እንድታለቅሽ አልፈልግም በቃ ይሄ ነው የሚሻለን ብትረሽኝ የተሻለ ነው " አለ "ያምሀል! አምባረቀች እንዲህ በቀላሉ እንደምረሳህ ነው የምታስበው ለመርሳት እኮ አይደለም ያፈቀርኩህ እንዲህማ እንድትቀልድብኝ አልፈልግም ምኔ ለማለት እንዳሰብክ ባላቅም ግን እኔ አንተን ልረሳህ አልችልም እ እ እ እ እኔ በጣም ነው የማፍቅርህ እኮ" አለች ሳጓ እየተናነቃት ናሆም ምንም ማለት አልፈገም እምባዋን እያበሰ ማባበሉን ቀጠለ ። " እሽ እንዳልክ ከዚህ በኋላ እንዳትደውልልኝ እንዳታናግረኝ ሁለተኛ ላይህ አልፈልግም። የአንተ ችግር አይመለከተኝም በጭራሽ በእኔ ህይወት ጣልቃ እንዳትገባ ተወኝ አዝኜልሽ ነው ለአንቺ አስቤ ነው ምናምን እንዳትለኝ ለራስህ እሰብ " አለችና ተነስታ ሄደች። ይቀጥላል ..................... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 31♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

​​​​#መቅደላዊት #ክፍል_29 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ከዚህ በኋላ ችግርሽን ለማንም አትናገሪ በየሄድሽበት ማልቀስ ማቆም አለብሽ ። እንደቀድሞው ደስተኛ እና ሳቂታ መሆን ይኖርብሻል። በትምህርትሽም ሆነ ተጓዳኝ የተሰጥኦ ድርጊቶችሽ ስኬታማ መሆን ትልቁ ስራሽ መሆን አለበት ። እንደዛ ካልሆንሽ ከእኔ ጋ መግባባት አንችልም እኔና አንቺ ብዙ ነገር ፊትሽ ላይ አለ አሁን እናትሽንም ሆነ አባትሽን የምታስቢያቸው በምልሰት ሳይሆን ወደፊት በምትሆኝው ህልምሽ ነው። እመኝኝ ስኬታማ ሆነሽ አምባው ላይ በኩራት ወጥተሽ ያየ ሁሉ እርሷ መቅደላዊት አይደለችምን ይላል በህይወትሽ የተነኮሱሽ ያፍራሉ። የረዱሽ ደግሞ ይኮራሉ። በዚያን ጊዜ እናትሽ ደስ ይላቸዋል። ነፍሳቸው ታርፋለች። አባትሽ አንቺን የመሰለች ልጅ በመተው እና ምንም ባለማድረጉ ራሱን ለከፋ ፀፀት ይዳርጋል። ገባሽ?" " እሽ ናሆም ከዚህ በኋላ እንዳልከኝ አደርጋለሁ።" ** ሁሉም ተነስተው ሻወር ወስደው ወደ ሁለት ስአቱ የትምህርት ፕሮግራም ለመሄድ እየተሰናዱ ነው። ነገር ግን ሜላት አልተነሳችም። " ሜሊ ተነሽ " ብላ አንሶላዋን ገለጥ አደረገች ሜሮን ። ነገርግንሜላት ንቅንቅ አላለችም አውቆ የተኛ ቢጠሩት አይሰማም ነውና ገገሩ ሜላትም የጓደኛዋን ጥሪ ለጊዜው ችላ ብላ እንቅልፍ የወሰዳት አስመሰለች። " ሜሊ ግን ሰው ይጨነቃል አትይም እንዴ በቃ ተነሽ ነቃን አይደል ታቂያለሽ ፋይናል አንድ ወር ብቻ ነው የቀረው። የመጨረሻ ክላስ ሊሆን ይችላል እና ሊያመልጥሽ አይገባም ። በዛ ላይ ዛሬ ልዩ ቀን ሊሆንልሽ ይችላል ተነስተሽ ቀንሽን በፈገግታ ብትቀበያት አሪፍ ይሆናል ብየ አስባለሁ።" አለች ሜራክል ካደፈጠችበት ብቅ ብላ " ሜራ ምን ለማለት ፈልገሽ ነው? የምታውቂው ነገር አለ?" አለቻት ሜላት በዚህን ጊዜ ስልኳ ጠራ ናሆም ነው። " እንዴ ናሆም ነው ሁሉም የዶርሙ ሴቶች እርስበርስ ተያዩ፡ ሜላት ስልኩን ማንሳቱን ትታ ፀጉሯን ማስተካከል ያዘች። " እረ ባክሽ የሚቀድመው ስልክ ማንሳት ነው ደግሞ አያይሽ " አለች ሜራክል " ኤሽ በቃ ዝም በሉ " አለችና ስልኩን አነሳች። " ሀሎ " " አቤት ናሆም " " እንዴት ነሽ?" " አለሁ በጣም ደህና ነኝ " " ድምፅሽ ልክ አይደለም " " ኧረ ልክ ነው ገና ከእንቅልፌ እየተነሳሁ ስለሆነ ነው።" " አስካሁን ተኝተሽ ነበር የጧት ትምህርት የለሽም?" " አለኝ አሁን እየተዘጋጀሁ ነው አንተ ግን በሰላም ነው የደወልከው?" " አወ ዛሬ ማታ ላይ ብንገናኝ ምን ይመስልሻል? እራት አብረን እንበላለን " " እሽ ደስ ይለኛል የት እንገናኝ?" " እሱን ተደዋውለን እንወስናለን " " እሽ በቃ ደውልልኝ ቸው " ስልኩ ተዘጋ ። ሜላት ፈገግታ በፈገግታ ሆነች ከደመና ቆይታ እንደወጣች ፀሀይ ብርሀኗ ሙሉ ሆነ ።ተነስታ ልብሷን ለባበሰች፡ ሁሉም ጓደኞቿ በደስታ ተመለከቷት ደስ አላቸው። ** አስተማሪው ስለ ቤርናሊየስ ኢኮይዥን በስፋት ካስረዳ በኋላ " ያልገባው አለ?" አለ ሁሉም ዝም አለ " ጥሩ ዝምታ ስምምነት ነው። this equesion has very intersting for you! You should be studied very hard.' አለና ዘወር ሲል መቅደላዊት በር በሩን እያየች ያያታል። " መቅደላዊት ሰላም ነሽ ችግር አለ?" አለ " እ እ ደ...ደ....ደ.....ህና ነኝ ሰ ሰ ሰ ላም ነው አለች ። የዛሬው ትምህርት ገብቶሻል?" " አዎ " አለች። መምህሩ በደንብ ከተመለከታት በኋላ " እሽ ዛሬ ሁላችሁም ገብቷችኋል የዛሬው ትምህርታችን ይሄን ይመስላል ነገ chapter 4ን ጨርሰን የሲሚስተሩን ትምህርታችንን እኔቋጫለን። " ብሎ ወጣ መቅደላዊት ናሆም ስላላት ነገር ማሰቧን ቀጠለች። " ቀጣይ ምን ማድረግ አለብኝ በትምህርቴም በህይወቴም ጫና እያሳደረብኝ ነው ።አሁን ሁሉንም መተው አለብኝ ከዛሬ ጀምሮ ማምበብ ይኖርብኛል በዚህ ሁኔታ ከቀጠልቁ ውጤቴ ይወርዳል ።ውጤቴ ሲወርድ ደግሞ አባ ለምንድነው የቀነስሽው ብሎ መጠየቁ አይቀርም ።ስለዚህ በተቻለኝ መጠን ያልጀመርኳቸውን ትምህርቶች መጀመር አለብኝ class end እየሆነ ነው final ደግሞ ደርሷል። በጣም ተዘናግቻለሁ። ናሆም ጋ ሆነ ባሩክ ወይም ናታኔም ጋ ከዚህ በኋላ መገናኘትም ሆነ ማውራትም የለብኝም። መንገዴን ማስተካከል ይኖርብኛል። " አለች ወደ ዶርሟ ተመለሰች፡ ** ናታኔም ውጭ ወጥቶ ቁርሱን ከተመገበ በኋላ በዛው ወደ ቤተመፅሀፍት ገብቶ ስለ ማንበብ እያሰበ ባለበት ባሩክ ደወለለት " አቤት ባሩክ " " ናታኔም ስለ ናሆም ጉዳይ እኔ እወጣዋለሁ ከዚህ በኋላ አንተም ሆነ መቅደላዊት ማሰብ የለባችሁም ።ትኩረታችሁ ሊሆን የሚገባው ወደ final ፈተና ነው። ሁሉንም ነገር እኔ መልክ አስይዘዋለሁ።" አለውና ስልኩን ዘጋው ናታኔም በልቡ የእፎይታ ስሜት ተሰማው ባሩክ የኃላፊነት ስሜት ተሰምቶታል ለሁላችንም ሚዛናዊ ሀሳብ ነው የሚያስበው አየ ባሩክ እንኳንም አወኩህ " አለና ወደ ቤተመፃህፍት አመራ። ይቀጥላል ..................... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 30♥️ ነገ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

​​​​#መቅደላዊት #ክፍል_28 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ናሆም ከርቀት ሆኖ ሶስት ሰወችን ተመለከተ ሁሉቱን ባይለያቸውም መሀል ላይ ያለችውን ግን ለይቷታል። " መቅደላዊት! እዚህ ምን ትሰራለች?" በፍጥነት ተራመደ እየቀረበ ደግሞ በግራ በኩል የተቀመጠው ናታኔም መሆኑን ለየው። በጣም ተናደደ ምንድነው የሚሰሩት መቅደላዊትስ ዶርም ነኝ ብላኝ አልነበር እንዴ? ነው እየዋሸችኝ ነው? እሱን ራሷኑ ጠይቄ መረዳት ይኖርብኛል። " እዚህ ምን ትሰራላችሁ? አቶ ናታኔም ወይዘሪት መቅደላዊት " አለ ከኋላቸው ሆኑ ሶስቱም ቀድንጋጤ ዞሩ ተርበተበቱ " ኦ ዲዮጋን ነህ እንዴ ከሩቅ አለየውህም ነበር ። ዛሬ እኔዴት ነው ሰብሰብ ብላችኋል ። አንተ የታደምክበት ጉባኤ ከሆነ ከባድ ጉባኤ ነው ማለት ነው " አለ ሶስቱንም በየተራ እየተመለከተ ባሩክ ፈጠን ብሎ " ከአዳራሽ እንደወጣሁ ናታኔምን አግኝቼው እያወራን ወደ ብሎክ ስንመጣ ራስ ተፈሪ ላይ መቅደላዊትን እያለቀሰች አገኘናት እጅግ ከፍቷት ነበር እኔም ሆንን ናታኔም ትተናት ልንሄድ ህሊናችን አልፈቀደም የማንስ ህሊና ይፈቅዳል። መቅደላዊት ጠንካራ ሴት እኔደሆነች አውቃለሁ ለዚህም እንዲህ የተከፋችበትን ነገር እንድትነግረንና እልባት ለመስጠት ከሷ ጋር የተወሰነ ራስ ተፈሪ ከተቀመጥን በኋላ ወደዚህ ይዘናት መጣን ስለዛ ጉዳይ እያወራን ነው።" አለ ባሩክ በተረጋጋ መንፈስ መቅደላዊት እንደደነገጠች ነው። ናሆም ወደ ተቀመጡበት ወንበር ይበልጥ እየተጠጋ " ቆይ ግን ቅድም ከተለያየን በኋላ ወደ ዶርም አልሄድሽም እንዴ?" አለ ናሆም " አወ በዛ ሁኔታ ላይ ሆኜ ዶርም መሄድ አልፈለኩም አስጠላኝ " አለች " እና ለምን አልደወልሽልኝም ?" " አላውቅም ናሆም ግን እያሰብኩ ነበር በእርግጠኝነት እነ ዲዮጋን ባይመጡ እና ትንሽ ብቆይ እደውልልህ ነበር።" ቀድመህ አግኝተሀት ነበር?" አለ ናታኔም የናሆምንና የመቅደላዊትን ምልልስ ካደመጠ በኋላ ምንም ነገሩን በማያውቅ " አወ እኔም እንደናንተ ተረብሻ ነው ያገኘኋት እና አውርተን ነበር ገብታ አረፍ እንድትል ነግሪያት ነበር የተለያየነው እሷ ግን ለካ አልገባችም ነበር። ከቻላችሁ ከመቅደላዊት ጋ ትንሽ ማውራት እችላለሁ ። " እሽ ምን ችግር አለው አውራት በቃ እኛ እንሂድ ባሩክም ደክሞኛል እያለ ነበር " አለ ናታኔም " መቅደላዊት በቃ ቸው እንገናኛለን" አለና ባሩክ ሰላምታ ተጨባበጡ *** "አየህ አይደል ይሄን ነው የፈራሁት እንዳይሆን የፈለኩት ይሄን ነበር አሁን ገባህ ስጋቴ?" አለ ባሩክ የናታኔምን ትከሻ እየመታ " ናታኔም በህይወትህ እንደ አሁኑ አይነት ስህተት እንዳትሰራ እመክርሀለሁ በጭራሽ እንዳትሰራ ። ውሸት አንዴ ከጀመርክ እና ከገባህበት ውጣ ውጣ አይልህም እንደ ሙጫ አጣብቆ ይይዝሀል። ደግሞ እየደጋገምከው በሄድክ ቁጥር እውነት ይመስልህና ከእውነታው ጋር እየተጣላህ እየሸሸህ እየተደበክ ትኖራለህ። ስንቱ መሰለህ በውሸት ታሪክ ወደ እውነተኛ ታሪክ መመለስ አቅቶት ለከፍተኛ ስነልቦናዊ ችግር ተጋልጦ በስነልቦና ሀኪሞች ክትትል የሚደረግለት። የእኔ ስጋት ይሄ ነው አሁን የተረዳኸኝ ይመስለኛል። አሁን ባትረዳኝም አንድ ቀን ግን ትረዳኛለህ" አለ ባሩክ " ይገባኛል ባሩኬ እኔ ነኝ ከመጀመሪያው ከዚህ ችግር ያስገባውህ ለሱ በጣም ይቅርታ በጣም ጨንቆኝ እና የናሆም የወደፊት እጣ በጥያቄ ምልክት ስለታየኝ ነው። መፍትሄ ፈልጌ እሱን ለማዳን ፈልጌ ከጥላቻ እና ከበቀል የፀዳውን ናሆምን ማየት ፈልጌ ምን አልባት ለእናቴ ልጅ እንኳ ላደርገው የማልችል ነገር እደሆነ ይሰማኛል ግን ምን ላደርግ እችላለሁ? ባሩክ እሽ እንዴት እንታደገው ይሄው ዛሬ ሌላ ነገር ተከሰተ በድጋሚ ሌላ ውሸት ነገም ስናገኘው ሌላ ውሸት አሁን ዶርምም ስንገናኝ ሲጠይቀኝ ልዋሸው ነው ። ስለዚህ ምን እናድርግ ዋሽተንም ቢሆን እሱን መታደግ ከቻልን ጥሩ ነው " አለ ናታኔም ። " ራስን አደጋ ላይ ጥሎ ሰውን ማዳን ጥሩ ነው ግን ደግሞ ራስን ከህግ አስተላልፎ በሌሎች ሀጢያት መግባት ትልቅ ስህተት ነው ያስጠይቃልም ውሸት ውሸት ነው ለጥሩ ለመጥፎ ብሎ ነገር የለም።" አለ ባሩክ " እሽ ምን እናድርግ ?" አለ ናታኔም "ናታኔም ለዚህ የተወሰነ ቀን ማንበብ አለብኝ ምን አይነት መፅሐፍ ማንበብ እንዳለብኝ ግን አላውቅም።" * *** እየውልሽ መቅደላዊት አንቺ ላታውቂ ትችያለሽ የአንቺን ህይወት ያሳለፈ ያሳለፈች ትኖራለች ወይም ይኖራል የሰው ልጅ ስለማይናገር እና በውስጡ ስለሚያምቀው ነው እንጅ ብዙ ችግሮች አሉበት። አንቺ ብቻ አይደለሽም እናትሽን ያጣሽው አባትሽን የማታውቂው ብዙ አሉ እናታቸውን የማያውቁ አባታቸውን ደግሞ በሞት የተነጠቁ ግን ሀዘን በውስጥ ነው የሚያዘው ችግርሽን ባወጣሽው ቁጥር መፍትሔው " ምፅ ምፅ ምፅ " ነው የሚሆነው ሁሉም ሰው ደግሞ የመፍትሔ ሰው ነው ማለት አያስደፍርም አንዳንዱ ችግር መስማት ስለሚያስደስተው ብቻ ይጠይቅሻል ያዳምጥሻል። ሌላኛው ደግሞ የአንቺን ችግር ከራሱ ችግር ጋ ለማነፃፀር የሚጠይቅሽ ይኖራል አንዳንዶቹ ደግሞ የእውነት ለችግርሽ መፍትሔ ለመስጠት በመፈለግ የሚጠይቁ ናቸው። እነዚህን ለማግኘት ይከብዳል ምክንያቱም ትንሽ ስለሆኑ ።አውቃለሁ ዲዮጋንም ሆነ ናታኔም ኃላፊነት የሚሰማቸው ልጆች ናቸው። በዚህ እተማመናለሁ ዲዮጋን ከዚህ ችግርሽ እንድትወጭ ሽህ መንገዶችን ይነግርሻል። ናታኔም ደግሞ ከመቶ በላይ መንገዶችን ያሳይሻል። እንድትመርጭም ያስተምርሻል። እኔ ግን የምልሽ በራስሽ መንገድ ሂጅ ነው በራስ አለም እንደመሄድ የሚያስደስት ነገር የለም ። " አለ ናሆም " እኮ እንዴት " አለች መቅደላዊት ብዙ ካዳመጠች በኋላ። ይቀጥላል ..................... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 29♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

​​​​#መቅደላዊት #ክፍል_27 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ " አልገባኝም ለምን እኔ እንደመጣሁ የስብሰባው አድማቂ ነኝ ፣ ተሳታፊ ነኝ፣ ባለጉዳይ ነኝ፣ ወይስ ቃለ ጉባኤ መዝጋቢ ነኝ ፣አለ ናታኔም የሁሉቱን ምልልስ ካዳመጠ በኋላ ። " የምትሉት ነገር አልገባኝም ምን ተፈጥሮ ነው?" አለ ናታኔም ባሩክን እየተመለከተ " ያ ለናሆም ያሰብኩትን ሀሳብ ዛሬ መቅደላዊት ለናሆም ነገረችው ከዛ በኋላ የተፈጠረው ያው ግልፅ ነው በምልሰት ወደ ኋላ ታሪኩን ኮመኮመ እውነት መሰለው። እሱ ሀሳብ ደግሞ ክፉ ነው። አለ ባሩክ " እንዴት ግን ሊሆን ቻለ ሌላ እቅድ ያለሽ እና እሱን የምታደርጊ መስሎኝ ነበርኮ " አለ ናታኔም ወደ መቅደላዊት እየተመለከተ ። " እሱማ ልክ ነበርክ ግን በቃ እዛ የሱን ግጥም እንደሰማሁ የባሩክ ሀሳብ ሚዛን ደፋ ሁሉም ነገር ቀላል የሚሆነው በዛው ስሜት ያን ማድረግ ነበር ለዛ ነው። " አለች መቅደላዊት *** ሜላት አንሶላዋ ውስጥ ተጠቅልላ ማልቀስ ከጀመረች አንድ ስአት አልፏታል ዶርም አትከፍትም ጓደኞቿ በጣም ተጨንቀዋል። ሁኔታውን ለፕሮክተር እንዳያሳውቁ ፈሩ እሷ ያለችበት ሁኔታ እና ዶርም አለመክፈቷ ደግሞ መልካም ነገርን እንዳያስቡ አስገደዳቸው ። ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ዶርሙን አንኳኩ " በቃ ተውኝ " አለች ሜላት ይሄኔ ሰላም እንደሆነች አወቁ "ሜሊየ ክፈችልን እባክሽ እኛንም እኮ አሳሰብሽን " አለች ሜሮን " አናሳዝንሽም ግን እኛም እኮ ከፍቶናል ህመምሽ እኮ ያመናል ። ዘግቶ ማልቀስ ደግሞ መፍትሔ አይሆንም መፍትሄው ተነጋግረን ውሳኔ ላይ መድረሳችን ነው።" አለች ሜራክል በዚህን ጊዜ በሩ ተከፈተ ። አይኖቿ ቀልተዋል። ሁሉ ነገር ርንዳልሆነች ሆናለች ሳቂታዋ ሜላት ደስታ ከራቃት ሰንበትበት ብላለች። በህይወቷ እንደዚህ የሆነችለት ወንድ እንደሌለ ከድርጊቷ ማወቅ ይቻላል።" የሆነ ነገር ማድረግ ሳይኖርብን አይቀርም ይቺ ልጅ አካሄዷ እና ድርጊቷ አላማረኝም ። ልጁን ቀድመን ማግኘት እና ስለጉዳዩ አፅንኦት ሰጥተን ልናወራው ይገባል።" አለች ሜራክል " የሆነ ዘጊ ነገር ነው ብታይ እንዴት እንደሚያስጠላ እኮ የልቡን ካዴሰ በኋላ የእኔ እና የአንቺ ነገር በድንገት ነው የሆነው ምናምን ይላል ብሽቅ " አለች ሜሮን በእልህ ከንፈሯን እየነከሰች። *** ናሆም ስለ መቅደላዊት ህይወት አለማሰብ አለመቻሉ የረበሸው ይመስላል ።በስተመጨረሻም ሙዚቃ ከፍቶ በኤርፎኑ እያዳመጠ ከዶርሙ ወጣ " ትንሽ አየር ስቤ እና ቀልቤን ሰብሰብ ላድርግ እስኪ" አለና በሚያዳምጠው ሙዚቃ እንደተመሰጠ ወደ ዳሽን የወንዶች ብሎክ የሚያስኬደውን ጎዳና ይዞ ለተወሰነ ደቂቃ ከሄደ በኋላ ቆም ብሎ አሰበና ወደ ገብርየ ዋርካ የሚወስደውን መንገድ ይዞ ወረደ " የሰው ልጅ ላውን ስታየው ሲስቅ ሲለብስ ሲጫወት ፍፁም መከራ እና ስቃይ ያልነካው ይመስላል ። ግን ሁሉም ሰው የራሱ ችግር ፈተና ምስጢር አለው። እኔ ብቻ ይመስለኝ ነበር በፈተና ታጅቤ እስከዚህ የደረስኩት ነገር ግን ሁሉም ሰው ያልተገለጠ ግን የሚነበብ ታሪክ ያለው መፅሐፍ ነው። የህይወትን ዳገትና ቁልቁለት ያላየ የለም። አሁን ሁሉም ነገር ተገለጠልኝ " አለ ናሆም ከራሱ ጋ ማውራቱን ጥያቄዎቹን መጠየቅ ቀጥሏል። ጨረቃዋ መድመቋ ያሳበቀባት ስአቱ በጨለማ በመድመቁ ነበር ጨረቃ እንደፈለገች ፍንትው ብላ ትታያለች።ነገር ግን ምንም አይነት የማቃጠል ባህሪ አለመኖሯ ያስገርማል። ተወርዋሪ ኮከቦች አልፎ አልፎ እንደ ሚሳኤል ይወነጨፋሉ። የሰማዩ ትርኢት ያስገርማል። ይሄኔ ነበር ናሆም ፈገግ ያለው በልጅነቱ ሰማዩን ለመንካት ፎቅ ላይ ሁሌ እንደሚወጣ አስታወሶ ። " ልጅነት ጅልነት ያለው ማን ነበር?" አለና ሳቅ ያለው ግን ፈገግታው ለደቂቃ እንኳ አልቆየለትም " አይዞህ ልጄ ስታድግ ከፈለክ ሰማዩን መንካት ጨረቃ ላይ መቀመጥ ትችላለህ ጎበዝ ተማሪ ከሆንክ " ያለው የአባቱ የትንቢት ቃል ትዝ አለው። " አባ ግን ለምንድነው እንዲህ በጧት በቶሎ የሄድከው እኔ በጣም ናፍቄሀለሁ አሁን እኮ ብቸኛ ነኝ ማንም የለኝም ሁሉም ሰው አስመሳይ ነው ማንም የሚረዳኝ የለም እናቴ ደግሞ አሁን መጥታ እናቴ እንደሆነችና የምትለውን ልሰማት የምታደርገውን እንድቀበላት ትፈልጋለች። አልቻልኩም ያለ አንተ አባዬ ናፍቆትህ አይሎብኛል" እያለ ደመነፍሱን መሄድ ቀጠለ ። በማያውቀው ስልክ ተደወለለት አይኖቹን በፍጥነት ጠራረገ ጉንጮቹን አባበሰ የሚደውለው ሰው እንዳለቀሰ የሚያውቅበት መሰለው። ስልኩን አወጣ የማያውቀው ቁጥር ነው። ለትንሽ ካመነታ በኋላ አነሳው። " ሀሎ " አለች ከወዲኛው መስመር መልስ ሳይመልስላት መቅደላዊት ትሆን እንዴ ብሎ አሰበ እና " አቤት " አለ " ናሆም ነህ አይደል? " " አወ ነኝ አንቺን ማን ልበል?" " ሜራክል እባላለሁ!" " አላወኩሽም የምትባል ሴት አላውቅም " " ልክ ነህ አታውቀኝም አንተዋወቅም " " እና አሁን ምን ልርዳሽ ሜራክል?" " በስልክ የሚነገር ጉዳይ አይደለም መገናኘት እንችላለን? የተወሰነ ጊዜ ልትሰጠኝ ትችላለህ?" " በሰላም ነው ለምን ጉዳይ ነው የምትፈልጊኝ? ለምንድነው ልታገኝኝ የምትፈልጊው?" " እሱንማ ስንገናኝ ነው የምነግርህ " " ይቅርታ ሜራክል ወቅቱ የፈተና ወቅት ነው ሰሞኑን አልችልም ከቻልሽ ከ ማጠቃለያ ፈተና በኋላ ማድረግ እንችላለን " " አይሆንም በፍጥነት ነው መነጋገር ያለብን ሜላት በጣም ታማለች" " ምን ሆና?" " አላውቅም ናሆም አሁን በስንት መከራ ነው ዶርም የከፈተችልን ከአንድ ስአት ጀምሮ ዘግታ ስታለቅስ ነበር። ደግሞ እየደጋገመች ናሆም ናሆም ትላለች።" " እና አሁን እንዴት ነች?" አሁንም ያው ናት ግን ማልቀሱን አቁማለች።" " አጠገብሽ ካለች ላገኛት እችላለሁ??" " አይ አይ እንደደወልኩልህ ማወቅ የለባትም በምስጢር ነው የደወልኩልህ ማናችንም እንዳንደውልልህ እና እንዳናስቸግርህ አስጠንቅቃናለች። በጭራሽ እንደደወልኩልህ ማወቅ የለባትም ትጣላኛለች " " በቃ ችግር የለውም አልነግራትም ራሴ እደውልላታለሁ " አላትና ቸው ተባብለው ስልኩን ዘጋው...... ይቀጥላል ..................... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 28♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

​​​​#መቅደላዊት #ክፍል_26 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ባሩክ ነፋሻማውን አየር በነፃነት ሲምግ ቆይቶ ። " ጥሩ ላድርግ መጥፎ አላውቅም ግን ደግሞ ልጁ ላይ ጫና እያሳደርኩ እንደሆነ አውቃለሁ። ልጁን ለሌላ ቁስል እያዘጋጀሁት ይመስለኛል።ግን ደግሞ ምንም ማድረግ አልችልም። ብቻ በዚህ ነገር ላይ ጥሩ ነገር አይታየኝም።" አለ እራሱን እየነቀነቀ " ስልኩን አወጣና ለመቅደላዊት ደወለ መቅደላዊት በድል ፈንጠዝያ " ሀሎ "አለች "ምን ተፈጠረ? ሁሉንም ነገርሽው?" " አወ ብታይ እንዴት እንደከፋው በጣም አዝኗል።" አለች ። ባሩክ ስልኩን ዘጋው ተናደደ ምን አይነት የማረባ ነኝ እንዴት ሌላ መንገድ ማሰብ ያቅተኛል? ለዚህ ስህተቴ ዋጋ መክፈል አለብኝ በጭራሽ ልክ አይደለም የሰራሁት ። ባሩክ በህይወቱ እንደዛሬ የተናደደ አይመስልም እንደዛሬም ስህተት የሰራ አይመስለውም። አይኖቹ ፈጠጡ " ይሄን ራሴ ማስተካከል አለብኝ!"አለ እና ከእንደገና ለመቅደላዊት ደወለ " ምን ሆነህ ነው ስልኩን የዘጋኸው ያነሳሁልህ እኮ እንድትዘጋብኝ ሳይሆን እንድታወራኝ ነው ይገባሀል" አለች " አሁኑኑ መነጋገር አለብን በፍጥነት ገብርየ ነይ እየጠበኩሽ ነው! " ግራ ተጋባች ተለሳለሰችእና " በሰላም ነው ባሩክ የተፈጠረ ችግር አለ እንዴ?" አለች " እሱን ስትመጭ እናወራለን ከቻልሽ ለናታኔምም ደውይለትና አብራችሁ ኑ አፍጥኑት " አለ ባሩክ " እሽ መጣሁ በቃ ለናታኔም እየመጣሁ እደውልለታለሁ። " አለች እና ከዶርሟ ወጣች ደረጃውን እየወረደች ለናታኔም ስትደውል ስልኩ አይሰራም ደገመች ደጋገመች ግን " የደወሉላቸው ደንበኛ ለጊዜው ጥሪዎን መቀበል አይችልም።" ነው የሚላት ፀጉሯን ወደ ኋላዋ እየሸከፈች ግራ ቀኟን እየተመለከተች በፍጥነት ወደ ገብርየ ዋርካ ሄደች። ባሩክ እሳት ለብሶ እሳት ጎርሷል። አንዴ ይቀመጣል አኔዴ ይነሳል ፀጉሩን አሁንም አሁንም ያካል ወገቡን ይይዛል። ብቻ መረጋጋት አልቻለም። " ምን ሆነህ ነው እንዲህ የምትሆነው " አለች መቅደላዊት ከኋላው የተወሰነ ቆማ ድርጊቱን ከተመለከተች ኋላ " ኦ መጣሽ ጥሩ ቁጭ በይ እባክሽ " አለ እና አብረው ተቀመጡ መቅደላዊት ሁኔታው አላማራትም በጥርጣሬ ትመለከተዋለች ። " እሽ ተቀመጥኩ አሁን ልትነግረኝ ትችላለህ? " አለች " ቆይ ትንሽ ናታኔም ይምጣ "አለ "ስልኩ አልሰራ ብሎኝ ነው ዝም ብየ ብቻየን የመጣሁት ነው አንተ ደውለህለታል" አለች " አወ መቅደላዊት ደውየለታለሁ ሰርቶልኛል መጣሁ እዛው አካባቢ ነኝ ብሎኛል" አለት ጥሩ " "ምንድን ነው እዚህ ሁሉም ሰው ተሰብስቧል ዝክር ነገር አለ ልበል " አለ ናታኔም መቅደላዊትም ባሩክም በአንዴ ዞሩ " ምንድነው ሁለታችንንም የፈለከን ወንድሜ ባሩክ?" አለ ናታኔም ገና ሳይቀመጥ " ቁጭ በል እስኪ ናቲ ለምን እንዲህ እንዳጣደፈን እኔም አልገባኝም።" አለች መቅደላዊት ናታኔም ከመቅደላዊት ጎን ተቀመጠ። " እየውላችሁ" error is natural to restify an error is glory " ይላሉ ፈረንጆች የሰው ልጅ ሆኖ የማይሳሳት የለም ግን ደግሞ ስህተቱን ማስተካከል ግዴታው ሊሆን ይገባል። ናሆም ላይ ትልቅ ስህተት ሰርቻለሁ በጭራሽ እንደዛ አይነት ልቦለድ ማዘጋጀት አልነበረብኝም " " ለእራሱ እኮ ነው " አለች መቅደላዊት " አታቋርጭኝ መቅደላዊት ልጨርስ ከዛ አንቺ ታወሪያለሽ ።አሁን የራሱን ሀዘን በሌላ ሰው ሰይመንለት አሞኝተነው አምኖን ይሆናል ግን ልንገርሽ አንቺ እናቱ ያደረገችውን እውነት አትክጅም እሱ ከህሊናው ሊነፃ ይችላል አንቺ ደግሞ ሁሌም ከዚህ ህመም አታገግሚም እኔ እሱን ለማዳን አንቺን ማሳመም አልፈልግም አንቺ ለአሁን ምንም ላይመስልሽ ይችላል ።ግን እውነት ተዳፍና አትቀርም አንድ ቀን የደረሰበት እለት እሱን ለሌላ ችግር ዳርገሽ አንቺም አይሆኑ ትሆኛለሽ ።ስለዚህ ይሄን ማስተካከል ይኖርብኛል በተቻለን መጠን መንገድ መቀየር ይኖርብናል። አመኘኝ አሁን ያለንበት መንገድ ቀይ መስመር ነው ። ለእሱም ለአንቺም ለእኔም አደገኛ ነው ይጎዳናል ። አየሽው ልጁን በአንድ ጊዜ ስትነግሪው አመነሽ ለምን ያመነሽ ይመስልሻል አንቺ ደርሶብኛል ያልሽው ችግር ደርሶበት ስላየው ህመሙን ስለሚያቀው ነው። እንጅ ምንም አይነት ችግር ደርሶበት ለማያውቅ ብትነግሪው አሁን ምንም አይመስለውም ምን አልባትም ላያዳምጥሽም ይችል ይሆናል። በህይወት ከባዱ ነገር መታመን ሲሆን ቀላሉ ነገር ደግሞ ማመን ነው። አንቺ ለጊዜው በሀዘኑ ትደሰቻለሽ ምክንያቱም እቅዳችን ተሳካ ብለሽ ግን ደግሞ የሱ ቁስል አንቺ ላይ ለዘላለም በማህተም መልክ ተቀርጾ ይኖራል። እሱን ደግሞ እኔ አልፈልግም ምክንያት አንቺን ባመመሽ ቁጥር እኔን ታስታውሻለሽ ስታስታውሽኝ ደግሞ እኔ ይሰማኛል። አሁን ተረዳሽኝ አይደል " አለ መቅደላዊት ራሷን በአወንታ ነቀነቀች። " እሱስ ልክ ነህ ቅድምም እያሰብኩኝ ነበር " አለች " አየሽ ገና ሳትጀምሪው እንዳመመሽ? ይሄ ከባድ ነው አሁን ያለን አማራጭ አሁን የነገርሽውን ፈጠራ ለማስተባበል መሞከር ነው። ገባሽ አይደል " " እሱን እንዴት ነው የምናደርገው?" አለች " እሱን በደንብ አስቤ ልጨርስና እነግርሻለሁ "አለ " ይቀጥላል ..................... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 27♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

​​​​#መቅደላዊት #ክፍል_25 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ መቅደላዊት በአይኗ ተከተለችው።ናሆም እርምጃውን እየጨመረ ሄደ።" የት ለመድረስ ይሆን እንዲህ የሚፈጥነው?" አለችና ከእንደገና ወደ ራሷ በመመለስ "ምስኪን አሁን ያልኩትን በሙሉ አምኗል። እኖዴት አያምን አልቅሼ አይደል የነገርኩት። እውነት መስሎት አዝኗል። እንዴት አያዝን ሀዘኑን አይደል የነገርኩት ህመሙን አይደል ያስታወስኩት። ህይወቱን አይደል ያወራሁት። ሲያሳዝን በምን አይነት ሁኔታ ይሆን ያደገው? የእናቱን ጠረን ሳያሸት ፀጉሩን ሳትዳብሰው ሲተኛ ሳታየው። የእናትነት ወግ ሳያይ ምስኪን " አለች ። ናሆም እየራቃት ሄደ። " የእውነት ባሩክ ቡዳ ነው!" አለች እና ስልኳን አወጣች። ገና 2:20 ይላል "ዝግጅቱ ገና ነው አያልቅም ስለዚህ ናሆም እንዳለው ገብቼ ለቅለቅ ማለት ሳይኖርብኝ አይቀርም ። ሻወር ወስጄ አልጋየ ላይ ጋደም ብየ እስኪ ደግሞ ትንሽ ልቀደድ መቼም አሁን ስሜት ውስጥ ገብቻለሁ እድሜ ለዲዮጋን በአንድ ጊዜ አስምጦኛል። የእውንት አርት ግን ነፍስ ነው። ያልሆኑትን በሆኑት ልክ የማስመሰል ጥበብ ደስ ሲል የእውነት ራሴን ማመን ነው ያቃተኝ ። ግን ደግሞ ተመልክቶ የፊልም ፅሁፍ እንደሆነ ያወቀለት እኔ እኔጃ ምን እንደምሆን። ይገለኛል ይበልጥ የሴትን ዘር ይጠላል። " አለች እና " አባቴ ላይ ጨክኜበታለሁ አባቴ ይቅር በለኝ ሁሉም ነገር ለበጎ ብየ ነው። አንተ ለእኔ ሁሌም መስዋዕት እንደሆንክ ነህ የእኔ ሁሉም ነገሬ የኔ ውድ አባት ምንም ላደርግ አልችልም ይሄን ልጅ ከበቀል ስሜት ማስወጣት ስለነበረብኝ ነው። " ምን አግብቶሽ ምንሽ ሁኖ " ትለኝ ይሆናል ግን ከሁሉም በላይ ሰው መሆኑ ቀድሞብኝ ነው። እኔ እንዳንተ የምወደው እና የማከብረው ሰው የለም። ግን ደግሞ በአንተ በምወደው አባቴ መዝናት ይኖርብኝ ነበር ለዚህ እቅድ መሳካት ።እባክህን አባየ በጭራሽ እንዳትቀየመኝ" እያለች የስልኳ ከቨር ላይ እሷን አቅፎ ከተለጠፈው አባቷ ጋር ታወራለች። " ይሄን ነገር ለእሱ መናገር አለብኝ አባቴ ሁሉንም ነገር ማወቅ አለበት ።ሊረዳኝ ይገባል ምን አልባት አሁን ናሆም ለሌላ ሰው ሊናገር ይችላል። በሌላ በሌላ ብሎ አባየ ጋ ከደረሰ ይቀየመኛል። ስለዚህ ነገሩን ቀድሜ ለምን እኔዳደረኩት ልነግረው ይገባል ደግሞ ይረዳኛል። እርግጠኛ ነኝ።" አለች እና የስልኳን ፓተርን ከፈተች እና የስልኳ ኮንታክት ላይ በአንዴ "dad " ብላ ሰረቸችና ልደውል ስትል በጀመሪያ ከናሆም ጋር ማውራት ይኖርብኛል ። እሱን ለሌላ ሰው እንዳይናገር ማሳመን አለብኝ ።ከዛ በኋላ ይሻላል ። "አለች እና ለአባቷ መደወሉን ተወችው። ስልኳን ኪሷ ውስጥ አስገብታ የብሎኩን ደረጃ እየቆጠረች መውጣት ጀመረች። ዶርም ውስጥ ማንም አልነበረም አልጋዋ ላይ ተዘረረች ተንጋላ ተኛች እና ሽቅብ ክርኒሱን መመልከት ጀመረች። ከዛ ስለ ባሩክ ማሰብ ጀመረች።" የሚገርም ሰው በራሱ ይተማመናል ለነገሮች መፍትሄ ለመሆን በጣም ይጥራል አስተዋይ ነው። ግና ፈላስፋ ያሰኘው ምኑ ነው?። እሱ እኮ በትክክለኛው መንገደሰ ነው የሚሄደው ። በጭብጨባ የማይደናቀፍ ሰው ። ብቻ ሙሉ ሰው ነው ብየ መናገር እችላለሁ። ብዙ ነገሮችን ያስተምረኛል እኔም ሁሌም ጥሩ ተማሪ መሆን ይኖርብኛል። እርጋታውን እና አወራሩን ላየ እኮ ብዙ አመትን ያስቆጠረ አዛውንት ነው የሚመስለው። አየ ዲዮጋን ገራሚ ፍጡር " አለችእና ለራሷ ፈገግ አለች። "ምን ሆኜ ነው ለዛ የማይረባ ፈላስፋ ይሄን ሁሉ የምቀባጥረው?" አለችና ራሷን መልሳ ጠየቀች። ነገር ግን መልስ ሊነግራት የሚችል ምንም አይነት ምክንያት እና ስሜት ልታገኝ አልቻለችም። ስልኳን አወጣች ። ሁሌም የምታዳምጠውን የድምፃዊ ቴወድሮስ ካሳሁንን ሙዚቃ ከፈተች። "ባልደራሱ" ከቀን በአራተኛው በእለተ ሀሙስ፣ ከወንድሜ ጋራ ስንጋልብ ፈረስ፣ አልያዘውም ኖሮ ልጓሙን አጥብቆ፣ አለፈች ህይወቱ ከፈረስ ላይ ወድቆ። ............ ቴዲ ይዘፍናል። መቅደላዊት ስልኳን አንስታ ከጠረጴዛው አኖረችና አልጋዋን ማስተካከል ያዘች። ***** ፕሮግራም መሪው ማይኩን ጨበጠ እና " የዛሬው የስነፅሁፍ ምሽታችን ይሄን ይመስል ነበር። በሌላኛው የሻማ ምሽት እስክንገናኝ መልካም ጊዜ ይሁንላችሁ ቸር እንሁን " አለና የመዝጊያ ንግግሩን አደረገ። ናታኔም ከነበረበት ወንበር ተነስቶ በአይኑ ቢፈልገው አጣው ።በመናፈሻው በኩል ወጣ እዛም የለም ከእንደገና የተዋንያን ልብስ መቀየሪያ ቢገባም የለም። ወጥቶ በአዳራሹ ሶስተኛ በር በኩል ሄደ ። እዛም የለም " የት ሄዶ ነው። " ብሎ ዘወር ሲል በርናባስን ያየዋል። " በርና በርና " አለ " አቤት ናታኔም " አለ በርናባስ " ናሆምን አየኸው? ጠፍቶኝ እኮ ነው።" አለ " በርና ጣቱን ከንፈሩ ላይ ጫን አድርጎ ለመጨረሻ ጊዜ ያያው የት ቦታ እንደሆነ ለማሰብ ሞከረ " አወ ቅድም መናፈሻው ጋ አይቼዋለሁ " አለ " ብቻውን ነው? ከሰው ጋር?" አለ ናታኔም " ኧረ ብቻውን ነው ወንድሜ " አለ በርና" እሽ አመሰግናለሁ " አለ እና ሄደ። "አሁን የት ነው የማገኘው?" አለ በመጨረሻም ወደ ዶርሙ ለመሄድ ይወስናል። **** ናሆም በመቅደላዊት ታሪክ አዝኗል ሲበዛ በጣም ። " እና አሁን አባታቸው ፈልጎ አላገኛቸውም ማለት ነው መጥቶ አይዟችሁ አለሁላችሁ አይላቸውም? ምን አይነት ክፉ አባት ነው።አሁን እሱም በአባየ ስም ሊጠራ ነው??? ህህህ መቼስ የወለደ ሁሉ ወላጅ ይባል የለ። ወልዳ ጣይ እናትም እናት ትባላለች ወልዶ የጣለም አባት አባት ይባላል። መቼስ አይ ፈጣሪ እባክህን የስራቸውን ስጣቸው።" ብሎ እጆቹን ወደ ላይ ዘረጋቸው። ይቀጥላል ..................... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 26♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

​​​​#መቅደላዊት #ክፍል_24 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ብዙ መስራት የለመዱት እጆቿ ተሸብሽበዋል አይኖቿ እምባ ጨርሰው እዥ ያነባሉ። ጠንካራዋ እና ልበሙሉዋ እናቴ አሁን ምንም በማንፈይድላት ልጆቿ ክንድ ወደቀች።አሳዘነችኝ ያን ሁኔታዋን እያየሁ እንዴት ብየ ቤት ልሁን ።የሰፈሩ ሰው በድጋሚ ከህመማችን ላይ ሌላ ህመም ጨመረብን " እናታቸው ከዚያም ከዚያም ጋ እየተኛች ይሄው በስተመጨረሻ በሽታዋን ቀስማ ተኛች " እያሉ ቁስላችንን አሰፉት። ወንድሜ ከላይ ከታች ተንከራተተ።እናታችንን ለማዳን የሚረዳን ሰው አጣን ሰው ራበን ከቀን ወደ ቀን በሽታዋ እየበረታባት ሌላ በሽታ ደግሞ እየተጨመረባት ሄደ። በመጨረሻም ሞት መቼም አይቀርም እናታችን ክንዳችን ላይ ሞተች ምንም ሳናደርግላት የደከመችበትን ፍሬ ሳታይ አይኖቿ ተከደኑ በሬሳ ሳጥን ተከፈነች። እናታችንን እየመረረንም ቢሆን ከ አፈር ደባለቅን። ሁሉም ነገር አብሮ ቆመ ህልማችን ጉድጓድ ላይ ቀረ። ወንድማችን ትምህርቱን አቋረጠ እኔና እህቴ እንድንማር ስራ ጀመረ። ጣውላ ቤት ቀኑን ሙሉ ምግብ ሳይበላ ውሎ ማታ ይመጣል። ያለውን ሰርተን ስንሰጠው መጀመሪያ እኛን ያበላናል። እኛ ካልበላን አይበላም ወንድማችን አማኑኤል የእናትነቱንም የአባትነቱንም የወንድምነቱንም ድርሻ ለመጫወት ይጥራል። ሀለልጊዜም ታዲያ እሱን ባየሁ ቁጥር እናቴ ትዝ እያለችኝ አለቅሳለሁ ደግሞ ልክ እንደ እናቴ ወንድሜም እንዳይሞትብኝ እፈራለሁ ሁሌም ከትምህርት ቤት ስመለስ ከሚሰራበት ጣውላ ቤት ሳላየው አልመጣም ።እህቴ ደግሞ እናቴ ያልጨረሰችውን የጉልት እቃዎች አውጥታ ልትቀመጥ ስትል ወንድሜ አይሆንም እኔ እስካለሁ እናንተ ስራ አትስሩም ትምህርታችሁን ዝም ብላችሁ ተማሩ " አለ ።ከዛ እህቴ እናቴም እንዲህ እያለችን ነው ስራ እንኳ እንዳናግዛት አድርጋ ለበሽታ የተጋለጠችው አይሆንም እናቴ ላይ የሆነው ነገር አንተ ላይ እንዲሆን አልፈልግም። እባክህ እምቢ አትበለኝ ባይሆን ከፈለክ አንተ ከምትሰራበት ጣውላ ቤት ፊት ለፊት መሆን እችላለሁ። የተወሰነ ጊዜ ብቻ ሰርቼ ከዛ ወደ ትምህርቴ እሄዳለሁ ።እባክህ እምቢ አትበለኝ አለች እና ደረቱ ላይ አለቀሰች። ወንድሜም ጭንቀታችን ገባው ልመናችንን ተረዳው እና ጥያቄያችንን ተቀበለው።እኔና እህቴም ከትምህርት ቤት ስንመለስ ጉልታችንን እንዘረጋና እድል ቀንቶን ጥሩ ከሰራን የሚያስፈልገንን አስቤዛ ገዝተን እንገባለን ።ወንድሜ ደግሞ በወር አንድሺህ አምስት መቶ ብር ይከፈለዋል።ከአራት ወር በኋላ ወደ ሁለትሺህ አምስት መቶ ብር አደገለት። ከዛ እኔና መክሊት እህቴ ወደ ትምህርታችን ትኩረት አደረግን። እኛም ከእንደገና ወደቀድሞው አቋማችን ተመለስን ጎበዞች ሆንን። አስረኛ ክፍልን በጥሩ ውጤት አለፍን እህቴም እኔም natural science መረጥን። አማን ሞያ በደንብ ለመደ ደመወዙ ወደ ስድስትሺህ አደገለት። ጥሩ ኑሮ መኖር ጀመርን ከማንም ያላነሰ ነው የምንለብሰው። ብቻ ሁሉም ነገር የወንድሜ ትከሻ ላይ አረፈ። ይሄን ሁሉ ነገር እያደረገ ከዚህ አደረሰኝ አሁን እህቴም ሁለተኛ አመት የባህርዳር ዩኒቨርስቲ ተማሪ ነች እኔ ደግሞ ይሄው እንደምታየኝ ነኝ ምንም ሳይጎልብኝ እየተማርኩ ነው ታዲያ አንተ ቅድም ያቀረብከውን ግጥም ሰማሁ ያቺን ጠንካራዋ እናቴን አስመሳይ ያልካት መሰለኝ የሰደብካት መሰለኝ፣ ያንቋሸሽካት መሰለኝ ከፋኝ አስታወስከኝ ምንአልባት አሁን ላይ ብትኖርልኝ ኑሮ ብየ አሰብኩ ተምረሽ ተምረሽ ተምራችሁ ተምራችሁ እያለች ሰርክ የምትደግምልን የተሰፋ ድርሳን ትዝ አለኝ። አለመኖሯን ሳቅ አለቀስኩ በቃ ይሄው ነው።" አለችና መቅደላዊት ዝም አለች ።ናሆም እቅፍ አደረጋት ደረቱ ላይ ወሸቃት ፀጉሮቿን ዳበሳቸው። አይኖቿን ጠራረገ ከእንደገና አቀፋትና " ይሄን ሁሉ መከራ ያሳለፍሽ አለመሰለኝም አንቺ በእሳት የተፈተንሽ ወርቅ ነሽ። እንቁ ነሽ አሁን ሁሉንም ነገር እርሽው እና ዶርምሽ ገብተሽ እረፍት አድርጊ ሰውነትሽን ለቅለቅ ብለሽ ተኝ ጥሩ እንቅልፍ ይወስድሻል። ከዛ በኋላ ቀለል ሲልልሽ ደውይልኝ "አለና ስልኩን ሰጣት ። ስልኩን ሰጥቷት ካለችበት ትቷት ብድግ አለ " ልትሄድ ነው? ትንሽ አትቆይም? " አለች መቅደላዊት ከተቀመጠችበት በፍጥነት ተነስታ " አወ መቅደላዊት እንደተነጋገርነው አድርጊ ደውይልኝ እኔ አሁን ወደ ዶርም መሄድ አለብኝ " አለ " እሽ በቃ እስከ ራስ ተፈሪ ድረስ አብረን እንሂድ" አለች " ጥሩ እንግዲያውስ " አለ " ታውቃለህ እንዴት ግን ቅልል እንዳለኝ " " አወ አውቃለሁ ውስጥ ላይ ያለ ነገር ሲወጣ የእፎይታ ስሜት አለው" አለ እና ዝም አለ መቅደላዊት እጆቿን አነባብራ ሽቅብ ትመለከተዋለች እሱ ግን ወደ እሷ አይመለከታትም ። በዚህ ሁኔታ ራስ ተፈሪ ሲደርሱ በድጋሚ ወደ ደረቱ አስጠጋትና " እንዳልኩሽ " ብሎ ትቷት ሄደ። ይቀጥላል ..................... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 25♥️ ነገ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

​​​​#መቅደላዊት #ክፍል_24 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ናሆም ሳያስፈቅዳት ከአጠገቧ ተቀመጠ፤ ምንም ነገር ሳይጠይቃት ለብዙ ደቂቃ ያህል አብሯት ተቀመጠ። አብሯት ተቀምጦ ምንም አለማለቱ ያበሳጫት መቅደላዊት ገልመጥ አደረገችው። የናሆም አይኖች ማዶ ካለ ጋሪያ ተሰክተዋል። ተራራው የበሬ ሻኛ ቅርፅ ያለው ነው ዙሪያውን ከላጣው ድንጋይ ያበቀሉት በተለምዶ የላጣ ሳር ወይም ጠጀሳር የሚባሉት የትልቅነት ካባውን አከናንበውታል። መቅደላዊት ዝም ብላ ብታየው ማዶ ማዶ እንጅ እሷን አያያትም። ናሆም አይኑን ጋራው ላይ ሳይነቅል " ምን ሆነሽ ነው ያለቀሽው?" አላት ። ዝም አለችው " ይሄን ጥያቄ የምጠይቃት ብቸኛዋ ሴት ነሽ ደግሜ አልጠይቅሽም ምንድነው እንደዛ አይንሽ እስከሚቀላ ጉንጭሽ ደም እስኪመስል ያስለቀሰሽ ነገር። " እናቴ ትዝ ብላኝ " አለች " ማለት? እናትሽ የለችም?" "አወ" እውነት አዝናለሁ በጣም እና አሁን የሚያስለቅስሽ?? በእናትሽ ጉዳይ ነው?" አለ " አወ እናቴ ሁሉ ነገሬ ነበረች እኔ እንደተወለድኩ እናቴና አባቴ በጣም ይጣላሉ። የጥላቸውን መንስኤ እና የተካረሩበትን ነገር ባላውቅም አባቴ ከቤት ትቶን ወጣ። እናቴ ከህመሟ ሳታገግም እኛን ለማስተዳደር ደፋ ቀና ማለት ጀመረች ። ጉልት ትሸጣለች ፣ የሰው ቤት ታፀዳለች፣ ብቻ በጣም ብዙ ስራ ትሰራ ነበር። እኛ ከትምህርት እንደተመለስን ምግብ በልተን ወደ እሷ ስንሄድ ስራ እኔግዝሽ ስንላት ትቆጣናለች ይሄ ቦታ ለእናንተ አይሆንም። እኔ አንድ ጊዜ ፈርዶብኝ ነው። እናንተ ተምራችሁ የተሻለ ኑሮ እንድትኖሩ ነው የምፈልገው እንዲህ ፀሀይ እየገረፈኝ የምሰራው ሌት ተቀን ሳልል እናንተ ተምራችሁ ለቁምነገር እንድትበቁልኝ እና ምንም ነገር እንዳይጎልባችሁ ነው ። ትለናለች። እናቴ ሳትማር የተማረች ነበረች የእኛ የሶስት ልጆች ህይወት በእናታችን እጅ ሆነ። እናቴ የአራታችንን ህይወት ለመምራት ሁሉንም ሴራ ሳትመርጥ ትሰራ ነበር። አባታችን ግን የውሀ ሽታ ሆነ የት እንዳለ ሁሉ አናውቅም።በእናታችን ጥረት ትምህርታችንን ቀጠልን ሁላችንም ጎበዝ ተማሪዎች ሆንን ። ትምህርት ቤት ላይ የምንሸለመው እኛ ነን። የሰፈሩ ሰው እነዚህ የሸርሙጣ ልጆች እናታቸው እኮ ከማንም ጋ እየተጋደመች ነው የምታሳድጋቸው ታዲያ እንደዛ ባይሆን ጉልት ገብይታ ባመጣችው ገንዘብ ነው የእነዚህን ልጆች ምግብ ልብስ እና አስፈላጊ ነገሮች የምታሟላላቸው የማይመስል ነገር" እያሉ ውስጣችንን ያደሙታል ወንድሜ ካልተደባደብኩ ይላል እኔና እህቴ ግን ተዋቸው ቀኔተው ነው ገና አይናቸው ደም ይለብሳል ከዚህ በላይ ስኬታማ መሆን አለብን ።እንጅማ በሆነ ባልሆነው በትንሹም በትልቁም የምትደባደብ ከሆነማ የመንደር ቦዘኔ ሆነህ ነው የምትቀረው ይሄ ደግሞ ለእነሱ ደስታቸው ነው። የሚፈልጉት ይሄን ነው። እና እባክህ ወደ ህልማችን ብቻ እናተኩር እነሱን ተዋቸው " እያልን ወንድማችንን እነረጋጋለን ወንድማችንም ከእንደገና ወደ ቀልቡ ይመለሳል። በዚህ ሁሉ መአት ታዲያ አባታችን አንድም ቀን እንኳ አለሁ ሳይለን አመታትን አስቆጠርን ። የሴት ልጆች እየተባልን እናታችን ደግሞ አንቺ ለማኝ ሸርሙጣ እየተባለች ኖርን።ሆዳችን በቂም ተለውሶ ልባችን እልህን አመርቅዞ የአስረኛ ክፍልን ማትሪክ ወሰድን እናታችን ደግሞ የአልጋ ቁራኛ ሆነች።ለብዙ አመት ስትሰራ የነበረችበትን ኩላሊቷ ከጥቅም ውጭ ሆነ ህክምናውን ለማድረግ ብዙ ብር ተጠየቅን ። ሁላችንም ቀኑ ጨለመብን የምናደርገው ጠፋን ለልመና ወጣን አንድ ጊዜ ማታ እየለመንኩኝ አንዱ ለምንድነው የምትለምኝው? አለኝ " ሁሉንም በዝርዝር አጫወትኩት " ከዛ በቃ ከእኔ ጋር እደሪ እና የፈለግሽውን ያህል ልስጠሽ አለኝ ። አለቀስኩ ምድር በዋጠችኝ ብየ ተመኘሁ ሰውየው አስጠላኝ መኪናው ውስጥ አስገባኝ ጭኖቼን መነካካት ጀመረ ጡቴን ሲነካኝ አልቻልኩም ትቸው ወጣሁ መስኮቱን ዝቅ አድርጎ " ለዚህ ለማይረባ ገላሽ እናትሽን መግደል ትችያለሽ ረጉል ኩራት ድሀ የድሀ ልጅ ይሄንም ያደረኩት እኔ ሆኜ ነው እሽ ደግሞ ለሞላው ሴት የአንቺ ወርቅ መሰለሽ እንዴ "አለኝ እና ሄደ እኔ ከእንደገና የጥፋተኝነት ስሜት ተሰማኝ እናቴን ለእኔ ለማይረባ ክብር ስል ሳልደርስላት የምትሞት መሰለኝ ከሰውየው ጋ አለመውጣቴ ቆጨኝ ከዛ ሌላ ሰው ባገኝ ብየ ፀለይኩ ።ከእንግዲህ ወደ ኋላ አላቅማማም አልኩና ከራሴ ጋር ቃል ተገባባሁ የከፋት ሴት ላለመምሰል ፊቴ ላይ የነበረውን እምባ አበስኩ እና ደስተኛ ሴት ለመምሰል ሞከርኩ አንድ መኪና መጣ እኔ ላይ ሲደርስ ቆመ።አንድ ፊቱ እና ሰውነቱ የማይለይ ቦርጫም ሰውየ ከመኪናዋ ወርዶ ወደ እኔ ተጠጋ " ውይ እንዴት ነው የምታምሪው የኔ ልዕልት ለአንቺማ የጠየቅሽኝን ብቻ ሳይሆን ያልጠየቅሽኝንም ነው የምከፍለው አዳር ስንት ልክፈልሼ??" አለኝ ዝም አልኩት። በዚህን ጊዜ ወንድሜ ከኋላየ መጥቶ መቅዲ መቅዲ አለኝ ደንግጨ ዘወር ስል ወንድሜ ነው።" ምን እያደረግሽ ነው መቅደላዊት ያምሻል እዚህ ምን ትሰሪያለሽ እንዳብድ ነው እንዴ የምትፈልጊው? የእናቴ ሳያንስኝ ደግሞ በአንቺ ልሰቃይ። በቃ አንቺ የሆነ ነገር ከሆንሽ እሞታለሁ የኔ ቆንጆ እህት እባክሽ እንዲህ አታድርጊ መቋቋም አልችልም። እናንተ እኮ ናችሁ የእኔ ተስፋዎች ጠንከር እንበል ፈጣሪ ደግሞ እናትም አባትም አያሳጣንም።ስለዚህ እንፀልይ " አለኝ እና ወደ ቤት ተመለስን ። ብዙ የሚሄዱት እግሮቿ አልጋ ላይ እንኳ መንቀሳቀስ አቅቷቸው የተገነዙ ይመስላሉ ። ይቀጥላል ..................... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 25♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

​​​​#መቅደላዊት #ክፍል_23 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ በዚህ ሁሉ መሀል ሜላት እያለቀሰች በስስት ትመለከተው ነበር። ልቧ ያለማቋረጥ ይመታል። የሚመታውን ልቧን ለማዳመጥ እጇን በሰደደች ጊዜ እንደ ጦር ይወጋታል። ለሷ ከደማሚት ልቆ የሚሰማትን የልብ ምቷን አጠገቧ ያሉት ሰወች የሚሰሙት መስሏት በሀፍረት ተሸማቀቀች። " ግን እኮ እሱ አይወደኝም ፣ በመጀመሪያ ቀን የራሱ እንዳደረገኝ አልተረዳም። ነፍሴን እንደሚያስጨንቃት አያውቅም። ለእኔ ግድ አይሰጠውም የሱ ግድ እራሱ ና አባቱ ነው።ምን ላደርግ እችላለሁ ? እንዴት ብየ የኔ አደርገዋለሁ እንዴት እንዲወደኝ ማድረግ ይቻለኛል? ሁሌም ቢሆን ይህ ነገር እኔ ላይ እንዳይደርስ እጨነቅ ነበር እሱን ላለማስከፋት ነው የጣርኩት አወ እሱ ልቤን ጠግኖ ሰብሮታል ያለምንም ማመንታት ራሴን ሰጠሁት ።እድለኛ አይደለሁም ። ሁሌም ቢሆን የሚያስበው እሱን ነው ከሱ ውጭ ሌላ ነገርን አያስብም ራስ ወዳድ ነው ። " አለች ሜላት በጉንጮቿ የሚወርዱትን እምባወቿን በግራ ና ቀኝ እጇ እያበሰች። አይኗ ሸልቷል ጉንጮቿ እምባዋን እንዲያብሱ የላከቻቸውን መዳፎች በማህተም ቀርፀዋቸዋል። " በቃኝ ስቃየን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በቃህ ልለው ይገባል። ስለእሱ ማሰብ ማቆም አለመቻሌን እነግረዋለሁ። ሊረዳኝ ግድ ይለዋል። እንጅ በስቃይ መሞት አልፈልግም። " አለች እና የተቀመጠችበትን ታጣፊ ወንበር ስትነሳ ታዳሚ እንዳይረብሽ ቀስ አድርጋ ወደ ቦታው መልሳ የእግሮቿን ኮቴ በቀስታ በማራመድ ወደ አዳራሹ መናፈሻ መውጣቱን ትታ በዋናው በር ወጣች። ***** ከናሆም የመድርክ ቆይታ በኋላ ገጣሚ ኤልሳቤህ እና ደረበ በተከታታይ ስራቸውን አቅርበው መድረኩን ለመድረክ መሪው ለቀቁ። መድረክ መሪው ለሁለተኛው ዙር ሶስቱ ገጣሚያን አድናቆቱን ለግሶ የሶስተኛውን ዙር አቅራቢዎች ለታዳሚያን ማስተዋወቅ ጀመረ " ከአቅራቢወቹ የመጀመሪያው በብዙ አወዛጋቢ ድርጊቶቹ የምናውቀው ተወዳጁ ባሩክ እስጢፋኖስ ( ዲዮጋን ) "አለ ከኋላ የተቀመጡት ታዳሚ ወንዶች በአንድ ድምፅ" ዲዮጋን ዲዮጋን ዲዮጋን " አሉ። በጩኸት የማይደናገረው ባሩክ ወደ አትሮኖሱ ተጠጋ ማይኩን በቀስታ ካነሳ በኋላ " ለጥሪያችሁ አመሰግናለሁ። በዛሬው ቆይታየ ስለ ውሸት እናወራለን እውነትን ለተወሰነ ጊዚያት እንረሳለን " አለ እና ወደ ታዳሚው ፊቱን አዞረ። አዳራሹ በሳቅ ተጋባ ሳቁ ሊቆም አልቻለም " አትሳቁ! እስኪ ከመሀላችሁ በህይወት ዘመኑ ዋሽቶ የማያውቅ?" አለ ።አንዱ እጁን አውጥቶ "እኔ ዋሽቼ አላውቅም " የዋሸሁትም ዋሽቼ ለማስታረቅ ነው አለ" እና ቁጭ አለ ።ባሩክ በልጁ መልስ ሳቀ ።" እኔ የጠየኳችሁ ዋሽታችሁ ስለማስታረቃችሁ በኩራት እንድትነግሩኝ ሳይሆን ስለመዋሸታችሁ በራሳችሁ አንደበት እንድታረጋግጡልኝ ነው። ለማንኛውም የጥያቄ መልስ ከጥያቄየ ያገኛችሁት ይመስለኛል። የሰው ልጅ ይዋሻል። የሚዋሸው ግን ተፈጥሯዊ ሁኔታ አስገድዳው ሳይሆን ለቅንጦት ነው። እናም ጥቂቶቻችን ብቻ ሳንሆን ሁላችንም በየ አቅማችን፣ በየ ቁመታችን ልክ እንዋሻለን ግን የሚገርመው ከመዋሸታችን በፊት ስለምንዋሽበት አመክንዮ ሳይሆን ከዋሸን በኋላ ለምን እንደዋሸን ለምናቀርብበት አመክንዮ እንጨነቃለን። ይሄ ደግሞ ከውሸት ጋ ያለንን ቁርኝት ይበልጥ ያቆራኘዋል። .............. ስለ ውሸት ከፅሀፍት አንደበት እና ከመፅሐፍ ገፆች እያጣቀሰ ብዙ አለ ። በመጨረሻም " እኔ እዋሻለሁ የምዋሸው ግን ውሸታም እስኪታጣ ድረስ ነው" በማለት ዥረት ሀሳቡን ደመደመ። ከተጋባዥ የጥበብ አባቶች እስከ አዋቂ ሙህራን በዲዮጋን ሰፊ ገለፃ በመደነቅ ከመቀመጫቸው ተነሱ አጆቻቸውን አገናኙ። ገሚሱ ደግሞ እየሳቀ ያጨበጭባል። ዲዮጋን እንዲቀመጡ በቀኝ እጁ እያመለከተ ወደ ውጭ ወጣ። ***** መቅደላዊት የአዳራሹ መናፈሻ በር ፊት ለፊት ካለው ደረጃ ላይ ተቀምጣ ታለቅሳለች። ያለ ማቋረጥ እምባዋን ታብሳለች ሜካፗን አበላሽቶባታል። ቀሚሷ አቧራ ስቧል ። መቅደላዊት አመድ ላይ የዋለች ቡሊትን መስላለች ። የተስፋ መቁረጥ ስሜት ይታይባታል ።ማንም ቢመጣ እየተፅናናች አይደለም። ናሆም ለመናፈስ ሲወጣ ማዶ ላይ መቅደላዊትን ሲያያት ግራ ተጋብቶ ቆመ። ሄዶ ሊጠይቃት አልፈለገም ግን ደግሞ ስሜቷ አስጨነቀው። እየሰረቀ ያያታል አልፎ አልፎ እሷም ስታየው እሱም ሲያያት ይገጣጠማሉ። ትቷት ወደ ውስጥ ገባ ።ማልቀሷን ቀጠለች ።ናሆም ውስጥ ሁኖ ወደ ውጭ አጮልቆ ሲያይ አሁንም እያለቀሰች ነው። የሆነ የማያውቀው ስሜት ተሰማው። እሱን የከፋው መሰለው ውስጡ ተረበሻ። ከራሱ ጋ በመሄድ እና ባለመሄድ ተከፈለ። ወደ ኋላ ሲዞር ማንም የለም ሁሉም ውስጥ እየታደሙ ነበር። " ለምን ብየ እሄዳለሁ? ምን አግብቶኝ በጭራሽ አልሄድም ለቅሶዋ ይውጣላት ምን አልባትም አልቀቅሳ ራሱ ላይወጣላት ይችላል።" አለ። ናሆም ማሰላሰል ጀመረ እሷ ጋ አይሂድ እንጅ ስለ እሷ ግን ማሰብ ማቆም አልቻለም።" ለምን ይሆን እንዲህ ስቅስቅ ብላ የምታለቅሰው? ማን ይሆን ያስከፋት ራሱን በተደጋጋሚ መጠየቅ "ጀመረ።" አዎ አንዳች ነገር አለ ይቺ ልጅ የምታለቅስበት 1000 ምክንያቶች ይኖሯታል። የመጀመሪያው ሴት መሆኗ በራሱ የለቅሶዋ ምንጭ ነው ። ሁለተኛው ተንኮላቸው ሳያውቁት ያስከፋየዋል ሶስተኛው እልህ እና ሽንፈት........ እያሉ መጥቀስ ይቻላል። ግን የእሷ ምንም ይሁን ምንም እንዲህ ለረጅም ስአት ያስከፋት ነገር ከባድ መሆን አለበት። " መምህር፣ ተማሪ፣ ሰራተኛ ........በነዚህ አይን ገብታለች ።ምን አልባት አንዱ በሴትነቷ እያስቸገራት ቢሆንስ?" ድንገት ለራሷ ያቀረበው ጥያቄ ነበር። ከእንደገና ኮስተር ብሎ ወደ ራሱ ተመለሰና " የፈለገ ቢሆንስ እኔ ምን አገባኝ? ራሷ ትወጣው እንጅ" አለ። ግን ደግሞ ይሄን ይበል እንጅ ህሊናው እየተረበሸ ነው። " ቆይ በህይወቴ የሴት ጣጣ መቼ ነው የሚያልቅልኝ?" አለ ራሱ ከመቅፅበት ሜላት ትዝ አለችው " ሜላት ልዩ ሴት ናት ሳልናገራት ምን ልላት እንደምችል ታውቃለች። ሲበዛ ለስሜቴ ትጨነቃለች። እንዲከፋኝ አታደርግም እሷ ላይ ሳልጨክን አልቀረሁም ያ አይገባትም አለ እና ስለ ሜላት ማሰብ ጀመረ። ቢሆንም ልሂድ እና ምን እንደተፈጠረ ልጠይቃት " አለ ናሆም ወደ መቅደላዊት ሄደ... ይቀጥላል ..................... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 24♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

​​​​#መቅደላዊት #ክፍል_22 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ሁሉም ታዳሚያን ዝግጅቱ ከመጀመሩ 30' በፊት ቦታ ቦታቸውን ይዘዋል። ዝግጅቱ እስኪጀመር ደጄው አዳራሽ ያለውን ታዳሚ በሙዚቃ ፣ በግጥም እንዲሁም በአጫጭር ስላቅ ወጎች እየከፈተ ማዝናናቱን ይዟል። አስር ደቂቃ ሲቀረው ጥሪ የተደረገላቸው ተጋባዦች የተዘጋጀላቸው ቦታ ላይ ተቀመጡ። መድረክ መሪው ማይኩን ጨበጠ " ክቡራትና ክቡራን የተወደዳችሁ የአንጋፋው እና የታሪካዊው አድዋ ዩኒቨርስቲ የስራ አመራሮች ፣ ሰራተኞች እንዲሁም ተማሪዎች እንኳን በደህና መጣችሁ" ጨብ ጨብ ጨብ ጨብ ጨብ ፣ አዳራሹ አስተጋባ መድረክ መሪው ከጭብጨባው በኋላ ማውራቱን ጀመረ። " እንግዲህ የዛሬው ምሽታችን በተወዳጅ እና በአዳዲስ ገጣሚያን እንዲሁም ተዋንያን የታጀበ ነው። አብራችሁን ስለሆናችሁ ክብረት ይስጥልን ብያለሁ። ይህ ዝግጅት በአምስት ክፍሎች የተዋቀረ ሲሆን የመጀመሪያው ክፍል ተወዳጇ ገጣሚ እንቁጳፂዮን " መውደዴ " ስትለን እሷን እንዳዳመጥን ደግሞ ሌላኛው ተወዳጅ ገጣሚ እዮሳፍጥ " ህይወት ማለት " ይለናል ሶስተኛዋ አቅራቢ ገጣሚ ልዕልት አለማየሁ" ከሸኘሁህ ወዲያ " ከዛ በዚህ ዙር የመጨረሻ አቅራቢ የሚሆነው ተዋናይ ዮሐናን ሞገስ ይሆናል የእነሱን ስራ ተመልክተን ከእኔ ጋር በድጋሚ እንገናኛለን መልካም ቆይታ ገጣሚ እንቁጳፂዮን ወደ መድረክ " አለ እና መድረክ መሪው ቦታውን ለቀቀ። ገጣሚ እንቁጳፂዮን ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው ግሩም በሆነ አቀራረብ ስራዋን አቀረበች።ሁሉም ታዳሚ ጭብጨባውን ቸራት ።ገጣሚ እዮሳፍጥ ፣ ገጣሚ ልዕልት ፣ ከዛ ተዋናይ ዮሐናን ሁሉም ስራቸውን በየተራ አቀረቡ። የመጀመሪያ ክፍል ተጠናቀቀ ። " እስኪ ለነዚህ የጥበብ ልጆች ጭብጨባ እንለግሳቸው። ሞራል አያንስም ? "አለ እና መድረክ መሪው የሁለተኛው ዙርን አቅራቢወች አስተዋወቀ። የመጀመሪያው አቅራቢ ገጣሚ ናሆም ነው ከሱ ቀጥሎ ገጣሚ ኤልሳቤህ ፣ ከዛ የመጨረሻ ወግ በደረበ መብራቱ ይቀርብልናል አሁንም መልካም ጊዜ በእኔ በኩል ገጣሚ ናሆም ወደ መድረክ " ብሎ ወረደ ።ገጣሚ ናሆም የማይኩን እጄታ ከተቀመጠበት ብድግ አርጎ " የግጥሜ ርዕስ " እምነት ወይስ እውነት " ይሰኛል አለና "ግጥሙን ረጋ ብሎ ማንበብ ጀመረ እምነት ወይስ እውነት? እኔ በዘመኔ፣ በዚች ቁንጥር እድሜ አባን ሲከፋው ነው የሚጨልም ህልሜ የሚሰበር ቅስሜ። አባቴ የዛሬየ ብሩህ ተስፋ፣ በእናት በኩል ለጎደልኩት የሆነልኝ ድርብ ካሳ። የፊቱ ወዝ ምጥጥ ብሎ፣ እኔ ስቀበጥ ተጎሳቁሎ፣ እጄን ይዞ አቦጊዳን ፊደል ሀሁን ያስቆጠረኝ፣ ለዚህ ስኬት ያደረሰኝ፣ አባባ ነው አባቴ ነው፣ ለእኔ ሻማ የቀለጠው። አባቴ ነው እውነት ሳጣ ያገኘሁት ትልቅ እምነት። ስለዚህ፦ እንዲህ ሚያደርግ አባት አያለ፣ ሰምና ወርቅ ቃላት ቢያጡ፣ እንዴት ወልዶ ጣይ እናቶች ለሙገሳ ከቤት ይውጡ። ፡ እናት እናት አትበሉኝ፣ ለማስመሰል አትደልሉኝ እናት እውነት አባት እምነት አትበሉኝ ለማስመሰል አትደልሉኝ። በደከመ ጉልበት አቅሙ ተራራውን እየናደ፣ ስንቱ ይሆን አርበኛ አባት ሚስቱ ጥላው እናት ሆኖ ልጁን ባክኖ ያሳደገ። ስንቱ የዋህ ባል በሚስቱ ወንድነቱ ጠወለገ። እናት እናት አትበሉኝ፣ ለማስመሰል አትደልሉኝ፣ አባየ ነው የኔ ድክመት፣ እድሜ ልኬን የማረሳው ቃልኪዳኑ ሆኖኝ እምነት፣ ከማንም ውጪ በእኔ ህይወት እሱ ብቻ የኔ ፊደል እሱ ብቻ የኔ እውነት! አባት ማለት ምስጢረኛ፣ ለጠላትህ ግልፍተኛ፣ እናት ላጣው እናት ሆኖ፣ እህት ላጣው እህት ሆኖ፣ ወንድም ላጣው ቀኝ እጅ ሆኖ፣ በእድሜው ሳይሆን በእድሜህ ሆኖ፣ የሚባዝን ለልጁ ሀሴት ዳገት ሜዳ ሁሉን ማክኖ! እምንት ሳይሆን አባት፣ ነው ለቃሉ ታማኝ... ኪዳን ያሰረ እውነት። ናሆም ርጋታን በተላበሰ ሁኔታ መሀል ላይ አረፍ እያለ እያንዳንዷን ስንኝ ዜማ እየሰጠ ካቀረበ በኋላ " አመሰግናለሁ" ብሎ ግጥሙን ቋጨ። የተለመደው ጭብጨባ ለናሆምም ተቸረው። ናሆም ከወገቡ ጎንበስ በማለት የጭብጨባውን አፀፋ ሰጥቶ ወደ ቦታው ሄደ። ሁሉም በሰመመን ውስጥ ነበር ሲያዳምጡት የነበረው በድንገት የጨረሰ መሰላቸው። የቃላቶቹ አደራደሩ ታዳሚን ሳይሰላች እስከ መጨረሻው ይዟል። አንዳንድ ታዳሚያን ሴቶች በፍርሀት ያዩት ነበር አንዳንዶቹ ደግሞ በፍቅር ሌላወቹ ደግሞ በአድናቆት፣ አንዳንዶቹ ደግሞ በናሆም ግጥብ ጭብጥ ግራ የተጋቡ ይመስላሉ ።እርስ በርሳቸው ይተያያሉ ።በዚህ ሁሉ መሀል ሜላት እያለቀሰች በስስት፣ ትመለከተው ነበር። ይቀጥላል ..................... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 23♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

​​​​#መቅደላዊት #ክፍል_21 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ የአድዋ መንገድ ዳሮች በአረንጓዴ ቢጫ ቀይ ወረቀቶች ተንቆጥቁጠው አሸብርቀዋል። የምሽቱ የስነፅሁፍ ዝግጅት ባመረ ማስታወቂያ እየተካሄደ ነው። " ታላቅ የጥበብ ድግስ! በአድዋ ዩኒቨርስቲ ሁለገብ አዳራሽ ! ታዋቂ እና ጀማሪ ገጣሚያን የሚሳተፉበት ድንቅ ምሽት ሳያወጡ የሚያተርፉበት ውብ ማታ በእለቱ ፣ ወጎች ፣ መነባንብ ፣ ዲስኩር፣ ሙዚቃዊ ተውነት፣ እንዲሁም ስላቅ እና ሌሎቹም የመድረኩ ክዋኔወች የተካተቱበት በአይነቱ ለየት ያለ ምሽት ነው ።እንዳይቀሩ ተጋብዘዋል" ማስታወቂያው በየ አምስት ደቂቃ ልዩነት ይቀርባል። ሁሉም ሰው ጆሮወቹ እና ቀልቡ ማታ በሚዘጋጀው የስነፅሁፍ ምሽት ነው። እንደገና ማስታወቂያው በመሀል ይመለስና " ተወዳጁ ፈላስፋ ባሩክ እስጢፋኖስ ( ዲዮጋን ) በእለቱ ድንቅ ስራውን ያቀርባል በዲስኩሩ በኩል ዶክተር ኸንድማገኝ አስረስ እንዲሁም በተስፋ ጎህ የቲያትር ቡድን የሚቀርበው ሙዚቃዊ ተውኔት ሌላኛው የምሽቱ ድምቀት ናቸው። ብቻ እናንተ ከምሽቱ 1:00 ጀምሮ ወደ አድዋ ዩኒቨርስቲ ሁለ ገብ አዳራሽ ጎራ ይበሉ እንጅ ዘና ፈታ ብለው ይመለሳሉ ። ጋብዘው የማያፍሩበት እለት ነው ።ምሽት 1:00 " አለ ። " ሲያስጠላ ያነ ባሩክ ልጅ አለ " አለች ፀጉሯን ያንጨባረረች ሴት ያልታሰረ ፀጉሯን በእጇ እያፍተለተለች ጥቅርሻ የመሰለውን አፏን ከሩቅ ላየ የሲጋራ እና የጋንጃ መተርኮሻ ትመስላለች " ኧረ ባክሽ እሱ ከሌለማ ምሽቱ አያምርም አትሰሚውም ማስታወቂያው ራሱ እሱ እንዳለ ነው የሚደጋግመው ምክንያቱም ባሩክ በሁሉም ተማሪ ልብ በመጥፎም በጥሩም መልክ ተቀምጧል ።ለዚህም እሱን ብሎ የሚገባውን ሰው ስለሚያቁ ነው እንዲህ አሁንም አሁንም ዲዮጋን አለ የሚለው። የአንቺን መጥላት ሳይሆን ማየት ያለብሽ የአብዛኛውን ሰው ፍላጎት ነው ።ጠብቂ ስንት ተማሪ እንደሚሄድ ማንም አይቀርም ቦታ ሁሉ ይጠባል " አለች የጨበሬዋን ሀሳብ በመቃረን ጨበሬዋ ከተቀመጠችበት አግዳሚ ወንበር ማዶ ካለው የአንድ ሰው መቀመጫ ላይ የተቀመጠችው ባለ ጎራዳ አፍንጫዋ ሴት ።አፍንጫ የሰራላት አይመስልም እግዜር አፍንጫዋ ላይ ምን እኔደነዳበት ባይታወቅም "ከቅላቷ ቀንሷ ምን አለ ትንሽ አፍንጫ ቢጨምርላት " እየየተባለች የምትታማዋ መካከለኛዋ ሴት ። ***** መቅደላዊት ረጅም የሐበሻ ቀሚሷን ለብሳ ሁለት ስአት ከፈጀው የመካፕ ቆይታዋ በኋላ አግድሙን ወደ አድዋ ሁለገብ አዳራሽ የሚወስደውን መንገድ በመያዝ እየሄደች ነው። በአካሄዷ ፣ በአለባበሷ ፣ እና በውበቷ ውህደት የተደመሙ ወንዶች የመንገዱን ጠርዝ ይዘው ይመለከቷታል። መቅደላዊት መላልክ መስላለች ። *** ናሆም የሚያነበውን በአዳም ረታ የተፃፈውን "የስንብት ቀለማት" የተሰኘውን መፅሐፍ ከድኖ ተነሳና የሎከሩን ቁልፍ ከፈተ። ሎከሩ ባልታጠፉ እና ባልታጠቡ ልብሶቹ ተዝረክርኮ ተሞልቷል። የትኛውን መልበስ ግራ ገብቶት ቆመ። ሁሉንም ልብሶቹን አንድ በአንድ አወጣቸው እና አልጋው ላይ አስቀመጣቸው። ሁሉንም አንድ በአንድ ካነሳቸው እና ከለያያቸው በኋላ አስረኛ ክፍል እያለ አባቱ ወደ ላሊበላ ሄዶ የበረከት ስጦታ የገዛለትን ከኋላው እና ከፊቱ የአፍሮ አይገባ መስቀል የተገለፈበትን ሸሚዝ አገኘው ።ብድግ አድርጎ ወደ አፍንጫው አስጠጋው ምንም የመጥፎ ሽታ የለውም።እንደውም የአባቱን ጠረን ያሸተተው መሰለው።" አባ የእኔ እናት የእኔ ሁሉ ነገር ምን አለ አሁን ብትኖርልኝ? ግን ምን አድርጌህ ነው ትተከኝ የሄድከው" አለና የሱን አላባሽ ሱሪ እና ጫማ አውጥቶ አልጋው ላይ ያሉትን ልብሶቹን ከእንደገና በስርዓት እያጠፈ ያልታጠቡ ልብሶቹን ከሚያስቀምጥበት ሻንጣ ላይ ካስገባ በኋላ አልጋው ላይ ተቀምጦ ልብሱን በትክክል ለበሰ እና የሁለቱም ክንዶች ብብት እና አንገቱ አካባቢ ላይ ዶዶራንቱን በመጠኑ ከረጨ በኋላ ዶርሙን ቆልፎ ብሎኩን ሲወርድ። በሀሉም አቅጣጫዎች የሚኒሚዲያ ክበብ ስፒከሮች ስለ ምሽቱ የጥበብ ሻማ ክብሪት የሆኑ ሀሳቦቻቸውን እየለኮሱ ይሰማሉ። * ናታኔም በተለምዶ አምበሳ ጊቢ እየተባለ ከሚጠራው የዩኒቨርስቲው ፓርክ ውስጥ ሆኖ እያነበበ ቢሆንም ነገር ግን የሚኒሚዲያ ስፒከሮች የረቡሹት ይመስላሉ። ትንሽ ካነበበ በኋላ ተነስቶ ወደ ወደ ወይዘሮ ስህን የሴቶች ብሎክ የሚወስደውን መንገድ በግራ በመተው ዋናውን አውራ መንገድ በመያዝ ወደ ስነፅሁፍ መግቢያ አዳራሹ ሄደ። ነገር ግን አዳራሹ ውስጥ ዝግጅት ለማቅረብ ከሚለማመዱ የትያትር ቡድን አባላት ውጪ የተገኘ ሰው አልነበረም።አዳራሹን እየተዟዟረ ከተመለከተ በኋላ ከፊት ወንበር ሶስተኛ ረድፍ ላይ ተቀመጠ። በሶስቱም የአዳራሹ ረድፍ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ከለርን የያዙ ወረቀቶች በውስጣቸው በተለኮሰ ሻማ አሸብርቋል በአራቱም ኮሪደሮች አረንጓዴ ቢጫ ቀዩ ባንዲራ ተሰቅሏል። ናታኔም ስልኩን አውጥቶ የአዳራሹን ትዕይንት በስልኩ ለማስቀረት እየተዟዟረ አንስቶ ከጨረሰ ኋላ ርግረ መንገዱን ለመቅደላዊት ደወለ ።ነገር እሷ ስልክ እያነሳች አልነበረም። በመጨረሻም ስልኩን ዘግቶ ወደ ኪሱ ከቶ እጁን ከኪሱ አስገብቶ ቁጭ አለ። ይቀጥላል ..................... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 22♥️ ነገ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

​​​​#መቅደላዊት #ክፍል_20 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ምን ያልገባሽ ነገር አለ ? ከጣፍኩልሽ ውስጥ? " ዝምታውን ለመስበር እና የውይይት መጀመሪያ እንዲሆን አስቦ ባሩክ የጠየቀው ጥያቄ ነበር። " ሀሳብህ በጣም ከባድ ነው እኔ ያን ማድረግ አልችልም እዚህ እኔን የሚያውቁኝ ብዙ ናቸው ። ቤተሰቦቸንም የሚያውቋቸው ተማሪዎች አሉ። አንተ ያልከውን ባደርግ እና ብል ያለ ጥርጥር ቤተሰቦቼ ጋር እቀያየማለሁ በስስት የሚያየኝን እና የሚወደኝን አባቴን እስከመጨረሻው አጣዋለሁ። እናም በጭራሽ አልችልም። ወይ ለዚህ ሀሳብህ ሌላ ሴት መፈለግ ሳይኖርብህ አይቀርም ።" አለች " የሀሳቡ አመንጪ እኮ እኔ አይደለሁም ይሄን የስነልቦና ህክምና የጀመራችሁት አንቺ እና ናታኔም ናችሁ። እኔን በተወሰነ መልኩ እንድረዳችሁ ጠይቆኝ ነው። እናም በዚህ ምክንያት የዚህ ፕሮጀክት ዋና ስራ አስኪያጇ አንቺ ስለሆንሽ ነው ይሄን ሀሳብ የሰጠሁሽ እንጂ አንቺ እምቢ ብለሽ ለሌላ ልሰጠው የምችለው የፊልም ስክሪፕት አይደለም። " አለ ባሩክ " አይ እኔ እኮ እምቢ ያልኩት ሀሳብህ ከባድ ስለሆነ ነው ። " አለች " ምን መሰለሽ መቅደላዊት ለከባድ ገጠመኞች ለከባድ ችግሮች ከባድ ውሳኔ ያስፈልጋል። ለዚህም አሁን ከባዱን ነገር ታደርጊያለሽ።እመኚኝ ስኬታማ ትሆኛለሽ። አውቃለሁ ብዙ ነገር ሊደርስብሽ ይችላል ግን ለዛም መፍትሔ እናስቀምጣለን።" አለ ባሩክ እጆቿን እየጨበጠ " እንደ እውነቱ ከሆነ ጥሩ ልብ አለሽ ከቅንነት ጋ ከውብ ቁንጅና ጋ ይሄን ባለኝ መረጃ እና በደቂቃዎች ለመረዳት ችያለሁ ።ሰወች ደግሞ ትክክለኛ ነገር አስበው ከሄዱ ከሚጓዙበት የእውነት መንገድ ማንም ሊመልሳቸው ሊያሰናክላቸው አይችልም ይህ የተፈጥሮ እውነት ነው።መጨረሻው መጨረሻ መሆን እንዳለበት ይሆናል። ናሆም ላይ ለእንዲህ አይነት የስነልቦና ችግር በመጋለጡ እኔ በጣም ነው ያዘንኩት ማንም ሰው እንዲህ አይነት ችግር እንዲደርስበት የሚፈልግ የለም እስከማቀው ድረስ አትጠራጠሪ እሱ ላይ የደረሰበት ችግር እኔ ላይ አለያም አንቺ ላይ ቢደርስ የምናደርገው እሱ ከሚያደርገው ቢበልጥ እንጅ አያንስም ። እሱስ ባይሆን ከላይም ቢሆን እናቱን ያወራታል እሷ ጋ ይኖራል ከዚህ በላይ እኮ ምህረት የለም። ግን ደግሞ እናቱ ነች ስለዚህ ለጥላቻው ገደብ ልናበጅበት ይገባል ይቅር ማለትን ልናስተምረው ይገባል። አለዚያ ከባድ ነው"አለ ባሩክ። " ካልክ እሽ ግን ውስጤን ልክ አይደለም እየተሰማኝ ያለው።" አለች መቅደላዊት " አሁን ለስነፅሁፍ ምሽቱ ተዘጋጅ እኔም ወግ ነገር ስለማወጋ መለማመድ አለብኝ በይ ተነሽ ልሸኝሽ አለ እና ቀድሞ ብድግ አለ ። **** ናሆም አቢሲኒያ ስታዲየም በክቡር አቶ ይድነቃቸው መቀመጫ በኩል ጫፍ ላይ ከአንዲት ግራር ዛፍ ስር ሆኖ በየደቂቃው ይጥፋል ፣ይቀደዳል ፣ ይጥላል። ቀዶ በጣላቸው ወረቀቶቹ ተከቦ ራሱን ይዞ ቁጭ ብሏል። ከእንደገና ራሱን ለቀቅ አድርጎ ዙሪያውን ሲመለከት ከአንዲት ቁራጭ ወረቀት ላይ ያፈጣል። ወረቀቱ ላይ የተጀመሩ ቃላቶች አሉ። "የዘራውን ሲያጭድ ይኖራል አለሜ፣ እማ ነች ቅኝቴ እናቴ ናት ህልሜ" ስንኟን ደጋግሞ አነበባት ማን ይሆን ማን ትሆን ይሄን ስንኝ የሰደረችው የሰደረው? ስንኟ የተፃፈችባትን ወረቀት ኪሱ ውስጥ አስገባት። ይሄን የፃፈው ሰው በምን አይነት ጥልቅ የእናት ፍቅር ውስጥ ይሆን? ምን አለ እኔም እናቴ እንዲህ እንዳደርግ ብትፈቅድልኝ ለምን አባየን ለምን እኔን ትታኝ ሄደች? ምን አድርጊያት ነው ገና በልጅነቴ የጨከነችብኝ? " ብሎ ራሱን ይጠይቃል። ትዝ አለው አንድ ቀን ትምህርት ቤት የተቋጠረላቸውን ምሳ ተሰብስበው ሲበሉ ሁሉም ጓደኞቹ እናታቸው እንደሰራችላቸው እየተናገሩ ናሆም ግን አባቴ ነው የሰራልኝ ሲላቸው በጣም ተገረሙ ።ነገር ግን ናሆም ከትምህርት ቤት ሲመለስ አባቱን ጠየቀ እናቴ ለምንድነው ትታን የሄደችው? ብሎ ሲጠይቀው ልጄ እኔን ትታ ለመሄድ ምክንያት ሊኖራት ይችላል አንተን ትታ ለመሄዷ ግን ምክንያት ያላት አይመስለኝም ቢሆንም ምክንያት ካላት ደግሞ አንተ ትልቅ ልጅ ስትሆን እናትህ ጋ ሄደህ እማ ምን አድርጌሽ ነው? ትተሽኝ የሄድሽው?"ብለህ ትጠይቃታለህ " አሁን ግን ጥያቄወችህን በሙሉ ተዋቸው እኔ ለአንተ ሁሉ ነገሬን እሰጣለሁ የእኔ ትልቁ ህልም የአንተ ትልቅ መሆን ነው። ስለዚህ በትምህርትህ በርትተህ ወደፊት እኔን እንድታኮራኝ ነው የምፈልገው ።እሽ የኔ ልጅ ደግሞ እኮራብሀለሁ " አለና እያገላበጠ ሳመው። ናሆም ከትዝታ ማዕበል ወጥቶ ጉንጩን ተደገፈ ።ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ " አባቱ እንደነገረው እናቱ ለምን ጥላው እንደሄደች አልጠየቃትም ። ግን ደግሞ መጠየቅ የምችለው አሁን አይደለም ብሎ ያስባል። ይህን እያሰበ እያለ ሀሳብ መጣለት እና ወረቀቱን አውጥቶ መፃፍ ጀመረ። ለስአታት ቀና ሳይል ከፃፈ በኋላ ። ጨርሶ በደስታ ፈገግ አለ ደግሞ ደጋግሞ አነበበው። " "ሸጋ ግጥም" አለ በለሆሳስ! ይቀጥላል ..................... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 21♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

​​​​#መቅደላዊት #ክፍል_19 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ማን ነው ስራህን ያቀለለልህ? ምን አይነት ስራ ነበር የነበረህ? " ናሆም ጥያቄወቹን አከታተለበት ። " አሳይመንት ነበረኝ እሱን ሰርቶልኝ ነው " አለ ናታኔም በድንጋጤ " ታዲያ ምነው ደነገጥክ? " " በድንገት ስለገባህብኝ ነዋ " " እንደዛ ከሆነ ጥሩ ግን..... ምን አሳይመንት ነበር? እንዴት ስታወራ አልሰማህም?" አለ ናሆም " አየ ወንድሜ ለዚህ እኮ ነው እኔ እና አንተ ተጠፋፍተናል የምልህ ።ግን የስነፅሁፍ ዝግጅት አለብኝ ምናምን ብለኸኝ ነበር እኮ እንዴት ታዲያ ተመለስክ?" " ባክህ ያቺ መቅደላዊትን ከሩቅ አይቻት የሁሉም ነገር ፍላጎቴ ጠፋ " " ቆይ ግን ይቺ ልጅ ምን አድርጋህ ነው እንዲህ ጠምደህ የያዝካት?" ምን እኔ ጠምጀ እይዛታለሁ እሷ ነች እንጅ " እኮ እሷ ምን አድርጋህ ነው?" " ከንፈሩን ነከሰ ባውቅማ ኖሮ ጥሩ ነበር የማደርገውን አውቅ ነበር። ነገር ግን ልጅቱ አስመሳይ ነች በጭራሽ የሆነ ነገር እየሰራች ነው እስካሁን አላወኩም ግን ግዴለም እደርስበታለሁ።" አለ ናሆም " * መቅደላዊት ፖስታውን እያየች ይሄ ደግሞ ምን ለማድረግ አስቦ ነው? " ራሱን እንዴት ነው የሚያየው? ሲያስጠላ " አለች እየተመናጨቀች ፖስታውን በዝግታ አንስታ ከከፈተች በኋላ በጥሞና አምብባ ከጨረሰች በኋላ ፊቷ ሁሉ ተለዋወጠ። ስልኳን አንስታ ደወለች " አቤት መቅደላዊት " ከወዲኛው የስልክ ድምፅ የተሰማው የናታኔም ድምፅ ነበር። " ቆይ ጓደኛህ ምን አይነት ጅል ነው ያመዋል ልበል? ሰውን ሳያውቅ " አለች መቅደላዊት " ቆይ መቅዲ ተረጋጊና ምን እንደተፈጠረ ንገሪኝ " አለ ናታኔም ።መቅደላዊት አንድም ሳታስቀር ሁሉም በስልክ ነገረችው እና በመጨረሻ" አሁን ላገኘው እፈልጋለሁ ስልኩን ስጠኝ " አለች " እሽ 0910..........ባሩክ እስጢፋኖስ ከፈለግሽ ዲዮጋንም ማለት ትችያለሽ ።ነፃ ሁኝ ግን መቅዲ አደራሽን ባሩክ ላይ ብስጭት መቆጣት መጮህ አይሰራም ።በእርጋታ የአንቺን ሀሳብ ትነግሪዋለሽ ።ለምን የእሱን ሀሳብ በአንቺ ሀሳብ ላይ እንደመዘንሽ ይገባዋል።ወይም ለምን እንደዛ እንዳለሽ ያብራራልሻል። ይህ ካልሆነ ግን በእውነት ትቶሽ ይሄዳል ።" አለ ናታኔም በልመናም በማስጠንቀቂያም አዘል ንግግር በተወሰነም መልኩ ስለ ባሩክ ግብአት " እና መሄድ ይችላል ለእኔ ብሎ አይቀመጥ " አለች መቅደላዊት " መቅዲ ምን ሆነሻል? ናታኔም በስልክ አምባረቀ " በዚህ ጉዳይ ላይ እኮ አንቺ ነሽ ትልቁን ስራ እየሰራሽ ያለሽው ለምንድነው የምትቀልጅው?" ናታኔም እየተቆጣ ተናገራት። " እሽ ናቲ በቃ አትቆጣ እንዳልከኝ አደርጋለሁ " አለች " ጥሩ አመሰግናለሁ ስትጨርሽ ደውይልኝ " እሽ እደውልልሀለሁ ። ***** ባሩክ " አክሱም የተማሪወች መናፈሻ " መጨረሻ ፎቅ ላይ ሆኖ " መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ" የተሰኘውን የፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ን መፅሀፍ ማንበቡን ገታ አድርጎ ያዘዛትን ወተት አንስቶ ፉት ሲል ስልኩ ጠራ። ያነሳትን ወተት አንድ ጊዜ ስቦ ወደ ነበረችበት ጠረምጴዛ መለሳትና ስልኩን ከኪሱ አወጣ ። አዲስ ቁጥር ነው ላለማንሳት ካመነታ በኋላ አንስቶ "ሀሎ" አለ ። " ሰላም ነው ባሩክ? አወከኝ?" " አላወኩሽም ወይዘሪት " አለ። " መቅደላዊት ነኝ " አለች " እሽ መቅደላዊት በጣም ነው የሚገርመው አሁን ስለ አንቺ እያሰብኩ ነበር።" " እንዴ ስለምንድን ነው ስለ እኔ እምታስበው?" የዋህነትሽን ፣ ቁጡነትሽን ፣..... ሌላም ሌላም እሱን አለማሰብ አይቻልም በዛ ላይ ........" ብሎ ዝም አለ ።" እህ በዛ ላይ .........ጨርሰው እንጅ " አለች ግን ለምንድነው ሴቶች ተጀምሮ ላልተጨረሰ ሀሳብ የምትሞቱት? ውይ ሁሉንም ማወቅ የሚፈልጉ ፍጥረቶች ቢኖሩ ሴቶች ናቸው ሊፈነዱ እኮ ነው የሚደርሱት። ምን እንደሚሻላቸው አሁን ይሄን ሳልጨርስላት ብቀር ሌቱንም ቀኑንም ስለዚህ ጀምር ሀሳብ ነው ቁማ የምታድረው ጉድ እኮ ነው። " አለ በውስጡ " እየጠበኩህ እኮ ነው "አለች ።መቅደላዊት እንዳልተፋታችው ሲረዳ " በዛ ላይ ቆንጆ ነሽ ለማለት ፈልጌ ነው።" አላት በተቻለው መጠን ግንኙነታቸውን ጤናማ አድርጎ ለመሞከር አስቧል። " ኧረ ባክህ ቆንጆ ነኝ እንዴ? አላወኩም ነበር።" አለች መቅደላዊት ምፀታዊ ንግግር ነበር። ባሩክ ገብቶታል ግን እንዳልገባው ለመምሰል " አባቴ ይሙት እውነቴን ነው " አለ ባሩክ እየሳቀ ። መቅደላዊት በሱ በኩል ያላትን የተቃረነ አመለካከት የማስተካከል አይደለም ዋና እቅዱ ናሆም ነው መቅደላዊት ጋር ያለው ጓደኝነት ጤናማ እና አሪፍ ከሆነ ናሆምን ካለበት የስነልቦና ችግር ማውጣት ይቻላል ብሎ ስላመነ ነው።እንዲህ ውድ ጊዜውን የሚያባክነው። ባሩክ ህይወቱ ማንበብ ብቻ ነው።መቅደላዊት ትንሽ ፈገግ ካለች በኋላ " ፈልጌህ ነበር " አለች " ለምንድነው ነው ልታገኚኝ የፈለግሽው?" አለ ባሩክ በደብዳቤው የተነሳ እንደሆነ ገምቷል።" እሱን ስንገናኝ እነግርሃለሁ " " ጥሩ መምጣት ከቻልሽ አክሱም ነኝ ጣራው ላይ " እሽ በቃ መጣሁ " ብላ ስልኩን ዘጋችው። * * መቅደላዊት አክሱም መናፈሻ ጣራው ላይ ስትወጣ ሽቅብ የሚነፍሰው ነፋስ አንዳች ነገር የፈለገ ይመስል ቀሚሷን ለመግለብ ይጥራል ። ቅንዝራም የሆነ ነፋስ እሷ ዝቅ ስታደርግ እሱ ደግሞ ከእንደገና ይገልበዋል በስተመጨረሻ እጇን ከቀሚሷ ላይ ሳታነሳ በሁሉም አቅጣጫ ስታማትር ባሩክ በመናፈሻው ደቡብ አቅጣጫ ጥግ ላይ ሆኖ በጥሞና ሲያነብ ተመለከተችው። ለተወሰነ ደቂቃ ቆማ ብትመለከተው እሱ ግን ከሚያነበው መፅሀፍ ውጭ ሌላ የትኛውንም አቅጣጫ ለማየት የፈለገ አይመስልም ። " ባይፈላሰፍ ቆንጆ ወንድ ነበር " አለችና ባሩክ ወደተቀመጠበት ቦታ ሄደች ባሩክ ወደ እሱ የቀረበ የእግር ኮቴ እንደሰማ ቀና ሲል መቅደላዊት ደርሳለች። ሰለም ብያለሁ እንዴት ነሽ ? እጁን ለሰላምታ ዘረጋ ጨበጠችው ጨበጣት እና ፈጠን ብሎ የምትቀመጥበትን ወንበር ስቦ አስቀመጣት። መቅደላዊት በአድራጎቱ የተገረመች ትመስላለች ። የአክሱም ሀውልት ምስል ያለበትን ቲሸርት የለበሰ አስተናጋጅ መጣ እና የተለመደውን ጥያቄ ጠየቀ የመቅደላዊትን የስፕራይት ትዕዛዝ ተቀብሎ አስተናጋጁ ሄደ። " ፈጥነሽ ገው የመጣሽው " አለ " የእውነት? እኔ ደግሞ የቆየሁ መስሎኝ ነበር " አይ በጭራሽ ጥሩ ስአት ላይ ነው ቢያንስ ከዘገየሽ ራሱ የዘገየሽው ካለሽበት እስከዚህ ድረስ ለመድረስ የፈጀብሽ መንገድ ነው " አለና ምቾት እንዲሰማት አደረገ። አስተናጋጁ አንድ የውሀ ብርጭቆ ከአንድ ሎሚ ጋር የታዘዘውን ስፕራይት አስቀመጠ እና ወደ ሌላኛው አካባቢ ተሰወረ። ይቀጥላል ..................... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 20♥️ ነገ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

​​​​#መቅደላዊት #ክፍል_18 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ናሆም ዶርም ሲገባ ናታኔም አልሰማውም ። ምክንያቱም ናታኔም በረንዳ ላይ ጀርባውን ለዶርሙ በር ሰጥቶ እያነበበ ነበር። ናሆም የሚቀይረውን ልብስ ቀይሮ ሊወጣ ሲል ናታኔም ደግሞ ቀና ሲል አይን ለአይን ይገጣጠማሉ ። ናታኔም ብድግ ብሎ "እንዴ ናሆም ደህና ነህ አሁንማ ተጠፋፋን እኮ ወንድሜ " አለ " በጣም ደህና ነኝ ወንድሜ ልክ ነህ በጣም ነው የተጠፋፋነው ግን ደግሞ ያው አንተም ስታነብ ነው የምትውለው እኔም ማንበብ ስለጀመርኩ ነው ።በል አሁን ቶሎ መውጣት አለብኝ " " ናሆም ወደየት ነው እንዲህ የምትቻኮለው? ቀስ በል እንጅ" አለ ናታኔም ወደ ናሆም እየተጠጋ " እየውልህ ወንድሜ ቶሎ መሄድ አለብኝ ቀጣይ ሳምንት የሚዘጋጅ የስነፅሁፍ ምሽት አለ ስለዚህ መዘጋጀት አለብኝ ለዛ ነው ወንድሜ " " ታቀርባለህ ?" አለ ናታኔም " አወ አቀርባለሁ " አለና ናሆም ትቶት ወጣ። ** መቅደላዊት በንዴትም በእልህም ወዲያና ወዲህ ትንጎራደዳለች። ጨይኖቿ ፀሀይ ለመሞቅ ወጥተው የተቀመጡ ይመስላሉ" ናሆም እንኳንም መረቤ ላይ ተጠመድክ ይሄን ነበር የምፈልገው ።አሁን የጨዋታው አሸናፊ ማን እንደሚሆን እናያለን ። አታስብ ቃል እገባልሀለሁ ትክክለኛዋን መቅደላዊት ታያለህ። አወ " አለች ራሷን አያወዛወዘች ስለዚህ ቀጣይ ማድረግ ያለብኝ ነገር ቢኖር ይሄ ነው " አለችና ጠረምጴዛው ላይ የተወሰነ ፅሁፍ የማይመስል ደግሞም ስዕልም የማይመስል ነገር ሞነጫጨረች እና በአንድ እጇ ወገቧን ይዛ አውራ ጣቷን ከንፈሯ ላይ አስጠጋችው። ** ባሩክ ሰባ ደረጃ አለፍ ብሎ ከበቀለች አንዲት ትንሽየ ዛፍ ስር ተቀምጦ ወጭ ወራጁን ይመለከታል ። kissing square በመባል የሚታወቅ ቦታ ነው። አንዳንድ ካፕሎች እየመጡ እዚህ ቦታ የሆድ የሆዳቸውን ሲጫወቱ ያመሹና "ሲመሽ ወደ ማታ ማታ ማታ፣ አቤት የአንቺ ፍቅር ሲበረታ " ብሎ ድምፃዊ ቴወድሮስ ካሳሁን እንደዘፈነው ።እነዚህ ካፕሎችም ደንገዝገዝ ሲል ጨለማው ለአይን ሲነሳ ከንፈር ለከንፈር ይያያዛሉ። ከዚያ ለያዥ ለገናዥ ያስቸግራሉ።በዙ ቆነጃጅት የከንፈር ድንግልናቸው የሚወሰደው እዚህ አካባቢ ነው። አንዳንድ ቦዘኔ እና በሰው ደስታ የሚደሰቱ ስራየ ብለው እዚህ አካባቢ በመምጣት የማታ ትዕይንትን ያለ ገቢር ክፋይ ይመለከታሉ ።ያለ ክፍያ ሲኒማን እንደማየት ይቆጥሩታል። ሰባ ደረጃ ደግሞ ስንቱን ደምበር እየሆነ ያስመልሰዋል ።ከሁሉም ብሎኮች ያሉት ወንዶች በመንገዳቸው ባይገናኝም እንኳ ሰባ ደረጃን ሳይሳለሙ አይሄዱም ።አንዳንዶች በዚህ ደረጃ ላይ ሲወጡ ሲወርዱ ከየካቲት ወይም ከስድስት ኪሎ ወደ ፒያሳ የሚወርዱበት ትክክለኛው ሰባ ደረጃ ይመስላቸዋል። በርግጥ ይሄን አካባቢ ለሚያዘወትር ሰው እና ለሚመሰጥበት ሰው ተነቦ የማያልቅ መፅሐፍ መፃፍ ይችላል።ባሩክ ከወዲያኛው መስመር መቅደላዊት ስትመጣ ሲያይ ከተቀመጠበት ይነሳ እና ወደ እሷ ይሄዳል። መቅደላዊት ስለ ባሩክ ሰምታለች ለሴት ባለው ከልክ ያልፈ ድፍረት እና ንቀት ትናደዳለች።ወደ እሷ አቅጣጫ እየመጣ እንደሆነ ስታይ ጉዞዋን ገታ አድርጋ ባለችበት ቆመች ባሩክ እየተጠጋት መጣ ። " ሰላም እንዴት ነሽ መቅደላዊት ባልሳሳት አንቺ ነሽ?" አልተሳሳትክም ፈላስፋው ባሩክ እስጢፋኖስ " አለች መቅደላዊት በጥላቻ አይን እየተመለከተችው " ወይ ይቺ አለም ምን አይነት ሰወች ነን የምንኖርባት ግን? ብሎ ከራሱ ጋ አወራ እና "መቅደላዊት የአንቺ እንዲህ መሆን የኔ ጉዳዬ አይደለም እንኳን አንቺ በህይወቴ ላይ ቅንጣት ታህል ቦታ የሌለሽ ሴት ይቅርና በህይወቴ ውስጥ ሰፊ ቦታ ያላቸው ሰወች እንኳ ምንም ቢሉ ግድ አይሰጠኝም ።እዚህ የመጣሁት የአንቺን የተዘፈዘፈ ፊት ለማየት አይደለም ለዚህም ብየ የምጠቀምበትን ጊዜየን አላጠፋም ።አውቃለሁ የዚህ ጊቢ ሴቶች በእኔ በኩል ጤናማ አመለካከት የላችሁም።እሱ ለእኔ ምይም ነው ሰው እንዲወደኝ አለያም እንዳይጠላኝ ሀሰት የምሸርብ ሰው አይደለሁም።እስከሚገባኝ እና እስከማውቀው አንቺ በእኔ ላይ የምትናደጅበት አመክንዮ አለ ብየ አላስብም ።ምን አልባት በሌሎቹ ጓደኞችሽ ካልሆነ። አሁን እሱን ልተወውና የመጣሁበትን ብየሽ ልሂድ ምን አልባት በሀሳብ ላንግባባ እንችላለን በሚል እሳቤ የምታደርጊውንና የምታደርጊውን ምክንያት ፣ ውጤት በተገቢው ሁኔታ እዚህ ደብዳቤ ላይ አስፍሬልሻለሁ። እኔ እና አንቺ የተለያየን አመለካከት እንዳለን አውቃለሁ ግን በናሆም ጉዳይ አንድ ነን ።እርዳታየን የጠየቀኝ ናታኔም ነው። ፖስታውን ስታነቢ ማንም እንዳያይሽ ተጠንቀቂ በተረፈ ቀጣይ እሁድ ናሆም የሚሳተፍበት የስነፅሁፍ ምሽተሰ አለ ከፈለግሽም ሀሙስ የሂስ ምሽት አለ መምጣት ትችያለሽ " አለ እና ባሩክ ትቷት ሄደ ። መቅደላዊት ለተወሰነ ርቀት እስኪሄድ በአይኗ ከሸኘችው በኋላ ስልኳን አውጥታ ወደ ናታኔም ደወለች " አቤት መቅዲ " አለ ናታኔም " አልገባኝም ናታኔም ምን እያሰብክ እንደሆነ ለምንድነው በዚህ ጉዳይ ላይ ባሩክን ያስገባኸው? በእኔ ስለማትተማመን ነው? ወይስ ሌላ ያሰብከው ነገር አለ? " አለች " ለዛ አይደለም አንቺ እንዳሰብሽው አይደለም። ታቂያለሽ አንቺ በዚህ ጉዳይ ላይ ተዋናይ እንጅ ፀሀፊም ዳይሬክተርም ተዋናይም እንዳትሆኚ ብየ ነው። ጊዜሽን እንዳይወስድብሽ ከትምህርትሽ እንዳትዘናጊ በዛ ላይ ባሩክ አሪፍ ነማንበብ ልምድ እና የማስተዋል አቅም ስላለው ናሆምን በቀላሉ ለማጥመድ ይቀለናል ። ከዚህ በኋላ ባሩክ የሚሰጥሽን ስክሪፕት ናሆም ላይ መተወን ብቻ ነው የሚጠበቅብሽ ። ገባሽ አይደል መቅዲ? " አለ አወ ገብቶኛል ጥሩ ያሰብክ ይመስለኛል ። ባሩክ ግን ደስ ስለማይለኝ ነው " አለች " አውቃለሁ መቅደላዊት ስለ ባሩክ ጥሩ ያልሆነ አመለካከት እንዳላችሁ አውቃለሁ ግን ባሩክን አውቀዋለሁ የሰፈሬ ልጅ ነው የዚህን አላማም እንደነገርኩት ሳያቅማማ ስለተቀበለኝ ነው።" አለ " እሽ በቃ የሆነ ፖስታ ነገር ሰጥቶኛል ከአነበብኩት በኋላ እናወራለን ደግሞ እረስቼው ናሆም እሁድ የስነፅሁፍ ምሽት ላይ ግጥም ያቀርባል።" " ማን ነገረሽ? " " ይሄ ባሩክ ተብየህ ነዋ መረጃው እውነት ይሁን አይሁን የማውበው ነገር የለኝም " አለች " ባሩክ ባሩክ ካሰብኩህ በላይ ስራየን እያቃለልክልኝ ነው " አለ ናታኔም ጮሆ። " ማንነው ስራህን የሚያቃልልልህ? አለ በሩን ከፍቶ እየገባ። ናታኔም ደንግጦ ቆመ። ይቀጥላል ..................... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 19♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

​​​​#መቅደላዊት #ክፍል_17 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ነፋሱ ያለ ማቋረጥ ዝቅዝቅ ወደ ምዕራብ አቅጣጫ ይነፍሳል በዛፎች ዳር እና ዳር የታጀበው አስፓልት በወጀቡ ነፋስ በረገፉ አበባወች ተንቆጥቁጦ አንድ ሀፍታም ለአንዲት ሚስቱ ስጦታ ያነጠፈው መስሎ ሊረግጡት ያሳሳል። ከትንሽ ወጀብ ነፋስ በኋላ ያለ ምንም ግምግምታ ዝናቡ ጣለ ።መቅደላዊት ፀጉሯን በእጇ ሸፍና ወደ ራስ ተፈሪ ህንፃ ስትገባ ናሆም ያያት እና እሱም ወደ ህንፃው ተከታትሏት ገባ። መቅደላዊት ከመግባቷ እዛ የተጠለሉት ተማሪወች አይናቸውን ይጥሉባታል። አንደኛው " ይቺን ልጅ ላወራት ነው!" አለ ሌላኛው ቀበል አድርጎ" ሰው ይዘህ ነው ወይስ ራስህን ችለህ?" ሲለው "ምን ለማለት ፈልገህ ነው? ራሴን ችየ ነው የማውራት አውርቼ ስልኳን ተቀብየ ካልመጣሁ እኔ አይደለሁም" አለ ሀሀሀሀሀሀሀሀሀሀሀሀሀሀሀ ኧረ ሞራልህ በለው ጀግና ነህ አለ ሌላኛው እየሳቀ " ትቷቸው ወደ እሷ ሄደ ይሄኔ እንዴት ነው? ምታናግረው ገና እንዳየችው ደንግጣ የምትሮጥ ይመስለኛል ።ሰይጣን ራሱ የሱን ያህል የሚጠቁር አይመስለኝም "አለ ይሄን እያለ ይከታተለዋል ።ተገረመ ፍፁም ተቃራኒ ሆነበት መቅደላዊት በስርአት እያወራችው ነው። ተመልሶ መጥቶ የሆነውን ሁሉ እስኪነግራቸው ጓጉ ፣ ኮስታራዋ ፣ እና ማንም የማይደፍራት ቆንጆዋ መቅደላዊት አሁን ከሰል ከመሰለ ሰው እየተሳሳቀች ነው። * መቅደላዊት ልጁ በሚያወራት ሳይሆን የምትስቀው በናሆም እቅድ ነው። እሷን እንዲፈትን በላከው ሰው ላይ አንዳንዴ ልጁ አውርቶ ሳይጨርስ አቋርጣው ትስቃለች ።ስትስቅ ጠፈርን የምታደምቅ ፀሀይ ትመስላለች።የውበቷ ጥግ በሳቋም አላምን ያዳርሳል ያ ማነው ናትናኤል ነው? እግዜር ስድስቱንም ቀን ሲሰራት የኖረ ያለው።እውነቱን ሳይሆን አይቀርም።ፍፁም ሀዘን የነካት አትመስልም ።አወ መቅደላዊት በተንደላቀቀ ሁኔታ ነው ያደገችው። ሁሌም እናትና አባቷ አይተው አይጠግቧትም።በዚህም በተለየ አስተዳደግ ነው ያደገችው። ይሄን የህይወቷን ሙሉ የአንዲት ፈገግታዋ ማንፀባረቅ ይችላል ። ረጅም ሳቋን በመሀል አቋረጠውና " በነገራችን ላይ ስትስቂ ይበልጥ ቆንጆ ነሽ " አለ " ኧረ ባክህ ሀሀሀሀሀሀሀሀ አላውቅም ነበር " አለች በቃ ከዚህ በኋላ እወቂ አላት " እሽ አውቂያለሁ በጣም አመሰግናለሁ ግን እስካሁን ስምህን አልነገርከኝም "አለች" ስሜ ኦኪዮ ይባላል " አለ ስምህ በጣም ደስ ይላል ። ስላወኩህ ደስ ብሎኛል ። አሁን ግን መሄድ አለብኝ ዝናቡ እያቆመ ስለሆነ " አለች እሽ መቅደላዊት ሌላ ጊዜ እንገናኛለን " አለ እና ወደ ጓደኞቹ ተመለሰ። መቅደላዊት ዝናብ የማታው ፀጉሯን አራግፋ ቀና አለች እና " ለራሷ ፈገግ ብላ ለምን ግን እኔን ይሄን ያህል ማወቅ ፈለገ ለምን ስለ ባህሪየ ግድ ሰጠው። ነው እሱም ከእኔ ፍቅር ይዞት ይሆን? ማን ያውቃል እልህ እና ንዴት ወደ ፍቅር ይቀየራል። እንደዛ ካልሆነ ለምን ታዲያ ይሄን ልጅ ለመፈተን ይልክብኛል? ናታኔም ልክ ነው ።በጭራሽ ዝም ብሎ የሚተኛ አይነት ልጅ አይደለም። ለማንኛውም የመጀመሪያ ፈተናውን በድል ተወጥቻለሁ ።ቀጣዩንም በኩራት የማልፈው ይሆናል።" አለች እና በዝናቡ የተቋተውን ውሀ እየዘለለች ወደ ብሎኳ ሄደች። #### ናሆም ልጁን በስርአት እና በፈገግታ በማውራቷ የተደሰተ ቢመስልም ግን ደግሞ "የሆነ ያሰበችው ነገር እንዳለ ግልፅ ነው" አለ እና ከህንፃው ወጥቶ የ ደጃዝማች በላይ ዘለቀን ሀውልት አልፎ ወደ አሉላ አባ ነጋ ብሎክ ቀጥ ብሎ ያልፋል። በዚህ ሁሉ የሀሳብ ጉዞ የመቅደላዊት ስራ እየመጣበት ነው።አብዛኛውን ጊዜ ስትስቅ የነበረው እሱ እያወራ ነው በድንገት እንደውም አልፎ አልፎ የሚያወራውን ነገር አቋርጦ ይመለከታት ነበር። የሆነ ተንኮልማ ሸርባለች። ዋ መቅደላዊት እኔ ላይ እየተጫወትሽ ከሆነ እኔ አንቺን አያርገኝ።" አለ ናሆም ።ከዚህ ሁሉ ሀሳብ ያባነነው ስልኩ ሲጠራ ነበር። ስልኩ የሚያውቀው ስልክ ነው" እሽ በርና ሰላም ነው " " ደህና ነኝ ናሆም አንተ እንዴት ነህ?" " አለሁ ወዳጄ አንድ ጎኔ ተሰብሮ " ደግሞ ምን ሆንክ? ችግር አለ ናሆም? " እኔ እስካለሁ ድረስ ችግር አይጠፋም ሰወች በምሄድበት መንገድ ሁሉ እየተከተሉ ነገረኛ ሳያደርጉኝ አይቀሩም።" አለና ናሆም በረጅሙ ተነፈሰ ለማንኛውም እሱን ለእኔ ተወው በማስተካክልበት መንገድ አስተካክለዋለሁ አንተ ግን ዛሬ እንዴት ትዝ አልኩህ?" አለ ናሆም " ያው እኔማ የደወልኩልህ የሚቀጥለው እሁድ ማታ ግሩም የግጥም ምሽት አዘጋጅተናል እና ስራ ካለህ ብየ ነው።" አለ በርና " በጣም ነው የማመሰግነው ወዳጄ በቃ ይዤ እመጣለሁ "አለ ናሆም ኧረ ችግር የለውም በቃ ሀሙስ የሂስ ምሽት አለን እዛ ይዘኸው ና " " መልካም በርናየ ይዤ እመጣለሁ መልካም ጊዜ " ስልኩን ዘግቶ በነገረው የስነፅሁፍ ምሽት ላይ ለማሰብ የሆነ ቦታ መሄድ እንዳለበት አምኗል ግን መጀመሪያ ዶርም መድረስ አለበት። ይቀጥላል ..................... ይቀጥላል አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 18♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

​​​​#መቅደላዊት #ክፍል_16 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ዲዮጋን እና ናታኔም የአንድ ሰፈር ልጆች ናቸው ዲዮጋን የአራተኛ አመት የ electrical engineering ተማሪ ነው። ዲዮጋን የአራተኛ አመት electrical engineering department ሁለተኛ ሰቃይ ነው። "ህይወት እና ጥበብ ያበሰለችው፤ ልቦለዱን ከገሀዱ መንዝሮ በብልሀት የሚኖር ፤ የፍልስፍናው ቀበኛ ፣ ሰው ቢኖር እሱ ዲዮጋን ብቻ ነው "ይላል ናታኔም ሁልጊዜም ስለ ዲዮጋን ( ባሩክ ስስጢፋኖስ ) ሲናገር። " ባሩክ ዛሬ አንድ የምነግርህ ትልቅ ነገር አለ እና በረቀቀ ሀሳብ ልትደግፈኝ ይገባል " አለ ናታኔም " እሽ አለ ባሩክ ( ዲዮጋን ) ከንፈሩን እያሸራመጠ እየውልህ ባሩክ ናሆም ከእናቱ ጋ አስተዋውቆኝ ነበር እናም አንድ ቀን ስልኬን ከናሆም ተቀበላ ደወለችልኝ ደውላ ያለችኝ እጅግ አስገራሚ ነገር ነው። ናሆም ጣም ትልቅ በሽታ አለበት የናሆም እናት ደወለችልኝ " ናሆም ከባድ የስነልቦና ችግር አለበት። እኔ በልጅነቱ ከአባቱ ጋር ተጣልቼ ሌላ ባል አግብቼ ናሆምን ከአባቱ ጋር ትቼው ሄድኩ። አባቱ በውል እንኳ ያላደገ ልጅ ሰጥቼው ስለሄድኩ አባቱ በጣም አዘኖ ነበር። እኔ በወቅቱ ከእሱ ጋ መጣላቴን እንጅ ስለ ልጅ ግድ ሳይሰጠኝ በስስት የወለድኩትን ባሌን የጎዳሁ መስሎኝ ልጄን ትቼው ወጣሁ። አባቱ ግን እንደኔ ሊተወው አልቻለም እንደ እናትም እንደአባትም ሆኖ አሳደገው ትምህርት ቤት አስገብቶ ራሱ እየሰራ ሚስት ሳያገባ ናሆምን አስተማረው ናሆምም አባቱን እጅግ በጣም ይወደው ነበር እና በትምህርቱ ጎበዝ በመሆን አባቱን ማስደሰት ቻለ። አባቱ ናሆምን ምንም ሳይጎልበት ነው ያሳደገው ሁልጊዜም ትምህርት ቤቱ ድረስ ሸኝቶት ይመለሳል ታዲያ ናሆም 11 ኛ ክፍል እያለ ወደ ሁለተኛ ሲሚስተር ገደማ አባቱ ከስራ ሲመለስ በመኪና አደጋ ይሞታል። ናሆም ሁሉ ነገር ተቀያየረበት ነገሮችን መቋቋም አቃተው። ሀዘኑ መሪር ሆነ ይህን ጊዜ እኔ ጋር እንዲመጣ አደረኩ አልተቃወመኝም።ግን ከመጣ በኋላ በሚያደርጋቸው ነገሮች ውስጤ ተነካ እኔን እና ከአሁኑ ባሌ የወለድኳትን ሴት ልጀን እጅግ ይፀየፈናል። በጭራሽ አንድ ቀን እንኳ እንደ እናት እና ልጅ ሆነን አናውቀም በጣም ብዙ ጊዜ ሞክሪያለሁ ግን አልቻልኩም ።ልጄም እየተሰቃየች ነው የናሆም ክፋቱ እኔ ላይ መጨከኑ ሳይሆን ምንም ከማታቀው እህቱ ጋር መጣላቱ አንድ ቀን ለጀሮ የሚከብድ ንግግር ልጄን ተናገራት " አንቺ በእናትሽ ነው እኔ ደግሞ አባቴን ነው መሆን የምፈልገው ለዚህም ደግሞ ያለ ሴት ያለ ሚስት እንዴት መኖር እንደሚቻል አባቴ አሳይቶኛል ነፍሱን ይማረው እና " አላት ያኔ ውስጤ ተጎዳ መቋቋም አልቻልኩም ልጄን አጥቸዋለሁ " ሲቃዋ በስልክ ይሰማ ነበር። ልጄ ሴትን ልጅ በጣም ይፀየፋል ይሄን አመለካከቱን እንዲቀይር እፈልጋለሁ እና የቻልከውን አድርግልኝ ምን አልባት እሽ ካለህ!" አለችኝ ልቧ በጣም ተሰብሯል እናም እሷ እንዳለችው የግድ ልንቀይረው ይገባል እና ለዚህ ስራ ደግሞ አንዲት ሴት ልጅ አግኝቻለሁ። በሀሳቤ ተስማምታ እያገዘችኝ ነው። "እሷ ማን ናት?" አለ ባሩክ በጥሞና ሲያዳምጠው ከቆየ በኋላ "መቅደላዊት "አለ ናታኔም " ጥሩ በእኔ በኩል አታስብ ከእሷ ጋ ታስተዋውቀኝ እና ምን ማድረግ እንዳለባት እንመካከራለን ይሄን በእኔ ጣለው " አለ ባሩክ (ዲዮጋን )በፍጹም በራስ መተማመን "" ግን ባሩኬ እንደምታስበው ቀላል አይደለም ሁሌም ንቁ እና ሲበዛ ተጠራጣሪ ነው በጣም መጠንቀቅ እና ከእሱ በላይ ማሰብ ይጠበቅብሀል" አለ ናታኔም " አታስብ "እኔ ያልፈሳሁበት ዳገት የለም አለች አህያ አለና ስቆ ምን ሆነሀል በእኔማ ተማመን እንጅ " አለና የናታኔምን ተከሻ ቸብ ቸብ አደረገው እሽ ተስፋ አደርጋለሁ ወንድሜ በቃ አሁን ልሂድ " ብሎ ባሩክን ከተቀመጠበት ትቶት ሄደ ባሩክ ስለ ናሆም በጣም አዝኗል በእናቱ የተናደደ እንዴት በውል እንኳ ያልበሰለ ልጅ ትታ ትኮበልላለች ። ፅፅፅፅፅ መሆን አልነበረበትም ግን ሆኗል። ይቀጥላል አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 17♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።