en
Feedback
ቆየት ቆየት ያሉ ሙዚቃዎች

ቆየት ቆየት ያሉ ሙዚቃዎች

Open in Telegram

እንደኔ ኦልድ ዘፈኖች ወዳጆች ኑ ከኔጋ ዘና በሉ @Riyit Join ይበሉቻናል ላይ full ዘፈኖች ያገኛል ደስ ያሉትን ዘፈን እየተገባበዝን ዘና ፈታ እንላለን ዘፈን የፈለጋችውትን ለመምረጥ @Heluuuu_bot ውድ የቻናላችን ተከታዮች ሀሳብ አስተያየት መስጠት ከፈለጉ እንዲሁም ለቻናላችን ማጋራት ሚፈልጉት ቆየት ያለ ሙዚቃ ካለ 👉 በነኚ በኩል ያግኙን @mark_sistu

Show more
Ethiopia2 732The category is not specified

📈 Analytical overview of Telegram channel ቆየት ቆየት ያሉ ሙዚቃዎች

Channel ቆየት ቆየት ያሉ ሙዚቃዎች (@riyit) is an active participant. Currently, the community unites 10 338 subscribers, ranking in the Other category and 2 732 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 10 338 subscribers.

According to the latest data from 04 December, 2024, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 285 over the last 30 days and by 5 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
እንደኔ ኦልድ ዘፈኖች ወዳጆች ኑ ከኔጋ ዘና በሉ @Riyit Join ይበሉቻናል ላይ full ዘፈኖች ያገኛል ደስ ያሉትን ዘፈን እየተገባበዝን ዘና ፈታ እንላለን ዘፈን የፈለጋችውትን ለመምረጥ @Heluuuu_bot ውድ የቻናላችን ተከታዮች ሀሳብ አስተያየት መስጠት ከፈለጉ እንዲሁም ለቻናላችን ማጋራት ሚፈልጉት ቆየት ያለ ሙዚቃ ካለ 👉 በነኚ በኩል ያግኙን @mark_sist...

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 05 December, 2024), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Other category.

10 338
Subscribers
+524 hours
+637 days
+28530 days
Posts Archive
#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_1 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ " የምትወጅው ከሆነ እስከመጨረሻው የሕይወት ምዕራፍሽ ልትታገይ ይገባል። በምንም ታዕምር ደስታሽ ከእጅሽ ሊያመልጥሽ አይገባም ላመንሽበት ነገር ታገይ አንድ ቦታ ላይ ቆመሽ በማላዘን ጊዜሽንና እድሜሽን አትግደይ። ራስሽን በሌላ የፅናት መንገድ አቁሚ አሁን አጠገብሽ ባሩክ የለም የወደድሽው የመሰለሽ ናታኔምም የለም አንዱን በትክክል ለአንቺ መሆን ሳይገባው ቀርቶ ሲቀር ሌላኛው ልክሽ ደግሞ የለም። ራስሽ ብቻ ነሽ ያለሽው ስለዚህ የኔ ውድ ልጅ እንድትጠነክሪ እፈልጋለሁ ።አውቃለሁ የኔ ውድ ምን ያህል እንደሚከብድሽ ግን መሄድ ስላለብሽ ነው ካለሽበት ከቆምሽበት መንቀሳቀስ መጀመር ስላለብሽ ነው። የአንቺ የእያንዳንዱ ድርጊት ና ሁኔታ ደግሞ ለእኔ ለአባትሽ ያሳስበኛል። ምን አልባት ይሄን የኔን ስሜት የምትረጅኝ ልጅ ኖሮሽ እንደኔ ያሰብሽለት ነው ከዛ ውጭ ግን የኔ ምክር ምንምሽ ሊሆንሽ ይችላል። እና በአንቺ መኖር ውስጥ በአንቺ ሕይወት ውስጥ እኛ እንደምንኖር እንድትዘነጊ ስለማልፈልግ ነው።" አለ የመቅደላዊት አባት አይኖቹ እምባ አርግዘው መቅደላዊት ግን በደመነፍስ ነው ስልኳን ከጀሮዋ አስጠግታ አባቷን የምታዳምጠው። በርግጥ የሚላትን እንደማታዳምጠው ቢያምንም ግን ደግሞ ትንሽ እንደምትሰማው የማመን ጥርጣሬ ስለነበረው በብዛት ያወራታል። ያለፉት ሁለት የእረፍት ሳምንታትና የሁለት ወራት የትምህርት ጊዚያት አስቸጋሪ ነበሩ ለመቅደላዊት ቤተሰቦችና ለመቅደላዊት። ባሩክ ወደ ውጪ ከሄደ ወዲህ መቅደላዊት ራሷን ልትሆን አልቻለችም በየቀኑ ፎቶወቹን እየተመለከተች የተናገራትን ነገሮች በምናቧ እያመላለሰች በሀዘን ኩርምት ብላለች። ማንም ሊያፅናናት አልቻለም። መምህራኖቿም ከአንድ ጊዜ ሁለት ጊዜ እየጠሩ አናግረዋታል። ነገር ግን ምንም ልትናገር አልቻለችም። በቃ ክፍል ውስጥ ተተቀምጣም መኝታ ክፍልም ተቀምጣ በሀሳብ ትናውዛለች ትንከራተታለች። ያች ቆንጆዋ እና ባለ ብሩህ አእምሮዋን መቅደላዊትን በርቀት ለተመለከተ በጭራሽ አያውቃትም። ፀጉሯ ብትንትን ብሏል። ፊቷ ማድያት ለብሷል ሰውነቷ ቀንሷል። ወትሮ በውበቷ ያልነሆለሉ ወጣቶች ዛሬ ግን ሊያይዋት ራሱ አይደፍሩም ሲያይዋት በራሱ ይጠቋቆማሉ። ለሷ የሕይወት አለሟ ባሩክ ብቻ ሆነ። አይኖቹ ይመላለሱባታል የእግር ኮቴው፣ እርጋታው አነጋገሩ የሚጠቀማቸው ቃላቶች ለሷ ያለው አመለካከት እያንዳንዱ የባሩክ ነገሮች የመቅደላዊት አእምሮ ላይ ተሰድረዋል። መቅደላዊት ከባሩክ ጋ በተገናኘችበት መንገዶች ሁሉ ትቆማለች ራሷን በሁለት እጆቿ ይዛ ።የመቅደላዊት የፍቅር ጥግ መረን አለፈ። የሀዘን ድካዋም እንዲሁ። የሚመለከቷት ሁሉ ምህረትን ይመኙላት ጀመሩ አንዳንዶች ደግሞ ባሩክን መኮነን ጀመሩ ።እንዴት እንዲህ እንድትሆን አድርጓት ይሄዳል። ምን አይነት ጨካኝ ነው። እያሉ ይረግሙታል። ዳሩ ግን ባሩክ ባህርማዶ ሆኖ እንደምን ወቀሳቸውንና ተግሳፃቸውን ይስማ። መቅደላዊት ናታኔምን በመንገድ ስታየው እንደማበድ ያደርጋታል። አንቃ ልትገድለው ይዳዳታል። ግን ደግሞ የሷም ስህተት እንዳለበት ስታምን ወደ ራሷ ትመለሳለች። ጥንዶች የማታዋን ጨረቃ አብረው ሲመለከቱ በጥላቸው ሲደናበሩ ሲሯሯጡ እሷ ደግሞ ያላየችው አለም ይመጣባታል። ምን አልባት ከባሩክ ጋር ታደርገው ይሆናል። ጊቢ ውስጥም እንደጉድ እየተወራ ነው ውበትና ጭንቅላት ያደላትን ልጅ ከመልከ መልካሙ እንዲሁም ከጎበዙ ከፍልስፍናው መርጌታ ባሩክ ጋር ስላላቸው ግንኙነት ና የመቅደላዊት ሁኔታ እንደ አንድ የምግብ መርሀግብር ተይዞላቸው እንደ ጉድ ይወራላቸዋል። ነገር ግን የመቅደላዊት ጊዜና ስአት የባሩክን ትዝታዎች እያስገለጣት መክነፉን ቀጠለ። ይቀጥላል .......... ለወደዱት ማጋራት ከፈለጉ 👇👇👇👇👇 ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 2 ♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

📚መቅደላዊት📚 አስተያየታችሁን ስትጥፉልኝ በዛውም አድራሻችሁን አስቀምጡልኝ መልሼ ለአምባቢያን ለማድረስ ይመቸኝ ዘንድ አሁንም በመቅደላዊት ታሪክ ዙሪያ የተሰማችሁን @mark_sistu ላይ ፃፉልኝ

#መቅደላዊት #ክፍል_71 (የመጨረሻው ክፍል) #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ዮርዳኖስ ስለ ባሩክና ናታኔም ብዙ ተናግራ ተነስታ ሄደች። መቅደላዊት ሰማይና ምድሩ ተመሳሰለባት ሁሉም ነገር አይኗ ላይ ሲደበላለቅ ታያት። ከአድማስ ማዶ የምትታያትን ጀምበር አትኩራ ተመለከተቻት የቀን ገቢሯን አንድ በአንድ አስታወሰች አሁን ማንም የለም ሕይወት ምክንያታዊ ናት!!!! በደመነፍስ መራመድ ጀመረች። እውነት ከእሬት እንደምትመር ሁሉ ሁሉም የሰማቻቸውን እውነቶች ላለመቀበል ብትሻም ግን አማራጭ አልነበራትም። ራሷን ጨብጣ ትንሰቀሰቃለች ጮክ ብላ " አወ ምን አልባት አልቅሼ ቢወጣልኝ አለቅሳለሁ " እያለች ታለቅሳለች። ናሆም ሊያፅናናት ሞከረ ሁሉም ነገር በእሱ ምክንያት መሆኑ ደግሞ ይበልጥ ራሱን አሳመመው መቅደላዊት ወኔዋ ከዳት ኩራተኛው ጉልበቷ ራደ አሁን እውነት ያለችው ሀሰት ሀሰት ያለችው ደግሞ እውነት ሆኗል። ናሆም መቅደላዊት አሳዘነችው አቀፋት እምባዋ ሸሚዙን አራሰው ደረቱን እየመታች " አሁን ማንም የለኝም ሁሉም ነገር ቅዠት ነበር አሁን ከህልሜ እየነቃሁ ነው። ሁልጊዜም እኔ ተጎጅ በፍቅር ህይወቴ አንድ ቀን ተሳክቶልኝ አያቅም ያን ታሪክ ባሩክ ይቀይርልኛል ብየ አሰብሁ ግን እሱንም ናታኔም ቀየረብኝ። ናታኔም ናታኔም ቆይ መደሰት አይገባኝም ይሄን ያህል ምን አድርጌ ነው?" " ይገባሻል መቅዲ አንቺ ንፁህ ሴት ነሽ። ሁሉም ነገር ይገባሻል ግን በቃ ራስሽን አጠንክሪ ጠንካራዋን መቅደላዊት ማየት ነው የምፈልገው። ሕይወት ደረስ መለስ ነች አንቺ ዛሬ አጣሁት ያልሽው ደስታና እንዲሁም ትቶኝ ሄደ ያልሽው ሀሴት ነገ ፈልጎሽ ይመጣል። እመኝኝ ለአንቺ ያለውን ወንድ የትም አታጭውም ምክንያቱም አንቺ ጥሩ ሴት ስለሆንሽ። እኔ እመኝኝ አንቺም ናታኔምም ባሩክም ለእኔ እኩል ናችሁ ግን ለአንቺ የተወሰነ ለማድላት አስቤ ነበር አንቺ አልፈቅድልኝ ብለሽ ነው እንጅ ገና ናታኔም ስለ ባሩክ ይሄን አለኝ ስትይኝ ውሸት እንደሆነ ነቅቻለሁ። ግን እውነትነቱን እንድትጠራጠሪ የቻልሁትን ሞክሬ ነበር አልረዳ አልሽኝ እንጅ ባሩክን አናገርኩት ግን ግትር ሆነብኝ" አለ ናሆም ፀጉሯን እየነካካ " እሱማ እውነተኛ ነበር እኔ ነኝ እንጅ ውሸትን መርጬ እንኳንም ቀረሁበት እኔ ለሱ አልገባውም!!" አለች " በይ አሁን ዶርም ላስገባሽ" አለ ናሆም በናትህ ናሆም መግባት አልፈልግም ከአንተ ጋር የተወሰነ ልቆይ" አለች ናሆም ምንም ሊላት አልፈለገም እሽ ከማለት ውጪ።" ግን ባሩክ ይቅርታ አያደርግልኝም " አለች እምባዋን እያበሰች " በጭራሽ አይመስለኝም ልጁ ግትር ነው ግን ከቻልሽ ሞክሪ ። ስልኳን አወጣች የባሩክ ስልክ አልሰራ አላት ብላክ አስገብቶታል በናሆምም ስትሞክር የናሆምንም አስገብቶታል። ናፍቆትና ፀፀቷ አንድ ላይ ተደመረባት።" አሁን ልሂድ" አለችና ተነሳች " አሁን ተረጋግተሻል ?" " አወ በደንብ ተረጋግቻለሁ" ብላ መንገድ ስትጀምር ናሆም አንጀቱ ተላወሰበት ተነስቶ ተከትሏት ሄደ እስከ ህንፃቸው ዊግቢያም ሸኝቷት ተመለሰ። ናሆም የመጨረሻ ደብሮታል። ሜላት ስትመጣ ተመለከታት እጅግ በጣም ተውባለች። ከተቀመጠበት ብድግ ብሎ ተቀበላት። አቀፈችው ተቃቀፉ በደንብ አቅፍ አደረገና ሳማት። ናሆም አይኖቿን በስስት እየተመለከተ አንቺ ሴት የኔ የዘለአለም ሚስቴ ነሽ ከእኝግዲህ ደስታየን ለማንም አልሰጥም አንቺን እና ቤተሰቤን የመለሱልኝን ሁሌም ሳስባቸው እኖራለሁ። ለእኔ ደስታ ሲሉ እነሱ ደስታቸውን ተነጥቀዋል። ለእኔ ብለው ብዙ ነገር አድርገውልኛል ይሄው ካደረጉልኝ አኔዱ የአንችን ውብ አይኖች በንፁህ አይኖች እንድመለከት ረድተውኛል። ጠረንሽን በነፃነት እንዳሸት ረድተውኛል። " አለ ናሆም ሜላት ደስ አላት በሚናገራት የቃላት ጥምረት መሀል ፈገግ ትላለች። " ከዚህ በኋላ ከአንቺ ጋ የማልሆንበት ምክንያት የለም " ብሎ አቀፋት እሷም " እኔም" አሏቸው ተቃቅፈው የገነት መግቢያ በር በምትመስለዋ መንገድ እየተደጋገፉ በእርምጃቸው እየተለካኩ የረገፉትን አበቦች ላለመርገጥ እየተጠነቀቁ መሄድ ጀመሩ። ወደ ደስታ ወደ ፍቅር ወደ እውነት ወደ ነገ እየተፍለቀለቁ ሄዱ። " ሁሉም ነገር ሲጀመር እንደሆነው መሆን አለበት ማንም በማንም ደስታውን ሊገጠቅ አይገባም ። ሕይወት የድርጊታችን ውጤት ነች ስለዚህ እኔ ያን ሁሉ መርሳት አለብኝ እውነታውም እንደዛ ነው ግን ልርሳው ብልስ እንዴት ይቻለኛል። አሁን እሷ ሌላ ወንድ ወዳለች ለእሱም ታስፈልገዋለች ግን የልቤን በር የከፈትኩላት ሴት ነች እንደከዋክብት በልቤ ላይ ትበዛለች እንደጨረቃም የውስጤን ብርሀን ታምቀዋለች እንደ ፀሀይም ታሞቀኛለች። እሷ ከማንም ጋር ትሁን ከማንም ጋር ለእኔ ይህ የውስጤ እውነት አይቀየርም!!!" አለ ባሩክ ሌላ ሲም ካርድ ስልኩ ላይ እያስገባ የመጀመሪያውን ሲም እየሰበረ " ለምንድን ነው እንዲህ ምታደርገው ?" ሲሙን ስለሰበርክኮ ከእሷ አትላቀቅም ጊቢ ስትመለስ ታገኝሀለች ።" ጊቢ አልመለስም ስኮላሩን ለአሁን ሲሚስተር አድርጌዋለሁ ዊይዝድረዋሉን ደግሞ ሞልቼዋለሁ።" አለ " ምን " ረለች እህቱ ግንኮ ይሄን ጨረስህ ነበር ልትሄድ የነበረው" አለች " አወ ግን ደግነቱ የነበረው ነው አሁን ሀሳቤን ቀየርኩኮ እህቴ ተይኝ እንጅ" አለ ባሩክ መቅደላዊት አልጋዋ ላይ ጋደም እንዳለች ናታኔም ደወለ በአንድ ጥሪ ብድግ አደረገችውና " ይህ ስልክ የመጨረሻችን ነው ሁሉንም ውሸትህን ደርሸበታለሁ ሰምቻለሁም አኔተ ምን አይነት መጥፎ ብትሆን ነው እንደዚህ ጨካኝ የሆንከው? ለምንድን ነው ያን ሁሉ መጥፎ ታሪክ የቀባኸው ምን አደረገህ?" አለች " ቀንቼ ነው እኔ ነገ ዛሬ እያልሁ በአንድ ጊዜ ሲሳካለት ቀናሁ በቃ ከዛ በኋላ የማደርገውን አላቅም" " የምታደርገውንማ ታቅ ነበር አላቅም ይለኛል እንዴ ደግሞ አያፍርም ደፋር። እስከ መቼ ልትደብቀኝ ነበር ያሰብከው? እውነት ተዳፍና በዛው የምትጠፋ መስሎህ ።" አለች ናታኔም ተንተባተበ " ይቅርታ እሽ አድርጊልኝ አጥፍቻለሁ " " ይቅርታህን ይዘህ ገል ግባ ህይወቴን ነው የቀማኸኝ ራሴን ነው የወሰድክብኝ! አንተ ለራስህ ያረጀ ቅናት ስትል ደስታየን ወሰድከው። ሁለተኛ እንዳትደውልልኝ አላቅህም አታቀኝም ስልኩን ዘጋችው። በድጋሚ ደወለ ዘጋችበት በተከታታይ ሰባት ጊዜ ሲደውል ዘጋችበት በመጨረሻም ብላክ አደረገችው። መቅደላዊት የስልኳን የመልዕክት መፃፊያ ከፍታ ለባሩክ ትፅፍለታለች። ነገር ግን ለባሩክ አንዱም አልደረሰውም ነበር። ተፈፀመ!! ተፈፀመ!! ተፈፀመ!! ለአስተያትና ሀሳብ እንዲሁም ግለ ሂስ የምቀበልበት በተለይ በዚህ ተከታታይ ታሪክ ላይ 👉 @Tesh5050 ብትፅፉልኝ ደስ ይለኛል።

#መቅደላዊት #ክፍል_70 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ መቅደላዊት ብዙም ሳትቆይ ናሆም ያለበት ቦታ መጣች። "እ ናሆም ተነሳ " " ለምንድነው የምናሳው ምን ላደርግ ?" " ምን ማለት ነው እሱ ባሩክ እንሄዳለንና " " ሲጀመር ያስጠራሁሽ ብቻየን እሄዳለሁ ብለሽ እንዳታስቸግሪ ብየ ነው ባሩክ የለም ሄዷል በቃ ተይው አንቺ ዝም ብለሽ ከናታኔም ጋ ያለሽን ግንኙነት አጠናክሪ ከእሱ ጋ መደሰት ይገባሻል እንደዚህ ስትሆኝ ደግሞ ናታኔምን ይረብሸዋል።""ሁሉም ነገር ከአቅሜ በላይ ሆነብኝኮ ናሆም ምን አባቴ ላድርግ መጀመሪያ ላይ ምንም አልመሰለኝም ነበር አሁን ደግሞ እሱ ከእኔ አጠገብ በሌለ ቁጥር ይናፈቀኝ ጀምሯል። ለምን እንደሆነ አላቅም ምንም ያድርግ ብቻ ይቅርታ ያድርግልኝ" " ይቅርታማ ኮ አድርጎልሻል መቅዲ ሌላው ነገር ያበቃለት ቢሆንም እንደነገረኝ ከሆነ እንኳን አንቺን ናታኔምን ራሱ ይቅርታ አድርጎለታል።ይቅርታ ማድረግ ለሱ የነፃነትንና የደስታን አለም መቀላቀል ነው ባለፈ ችግሩ የዛሬውን ደስታ ለማጥፋት አይደለም እቅዱ እሱ ስለህይወትና ስለፍልስፍናዋ ብዙ ነገር አስተምሮኛል። ይሄው ደስተኛ ነኝ ብየ ባመንኩባቸው ጊዚያቶች ደስተኛ አለመሆኔን የተረዳሁት አሁን ነው የአሁኑን ደስታየን ሳይ። እና ይቅርታ ያደረገልሽ ለራሱ ሲል ነው። " መቅደላዊት አንገቷን እየነቀነቀች " በቃ ሁለተኛ እድል አይሰጠኝም ማለት ነው? ከሱ ብዙ ነገር መማር እፈልጋለሁ።" " እሱን አላቅም " አለ ናሆም በመሀል ስልኳ ጠራ ስልኳን ስታነው ናታኔም ነው።"አቤት ናታን " " ደህና ነሽ ?" " ደህና ነኝ በጣም አንቺ እንዴት ነሽ ጠፋሽብኝኮ " " ኧረ አለሁ ግን ወደ ቤት ልሄድ ነው። " " ጥሩ አድርገሻል ከሱ ሆነሽ ከሚደብርሽ ወደቤተሰቦችሽ ነይ የኔ ውድ እኔም በጣም ነው የናፈቅሽኝ " እሽ እመጣለሁ ግን በጣም ከፍቶኛል "" በምን ምክንያት " " አላውቅም አንተ ስለሌለህ ይሁን ባሩክ ጋር ስለተጣላሁ ይሁን ብቻ አላቅም " " አይዞሽ የኔ ቆንጆ እኔ ስለሌለሁ ነው ነይ በቃ" " እሽ እመጣለሁ አለችና ትንሽ ከአንተ ጋር ልቆይ "አለች መቅደላዊት "እንዴ ምን ጥያቄ አለው "አለ ናሆም ጎን ለጎን ተቀምጠው ምንም ሳያወሩ ትንሽ ቆዩ ከዛ በአጠገባቸው ዮርዳኖስ ደረሰች ልክ እንዳየቻቸው ትንሽ ቆማ ስታበቃ ወደነ ናሆም ተጠጋችና " ሰላም ናሆም " " ሰላም " አለ ግራ በመጋባት ዮርዳኖስ ሳቅ አለችና ግራ መጋባትህ ልክ ነው "አታውቀኝም " እና የማታቂውን ሰው ሰላም ማለት አይከብድም? እናት " አለች መቅደላዊት " ኧረ ችግር የለውም ልጠብሰውኮ አይደለም የመጣሁት መቅደላዊት " አለች መቅደላዊት ስሟን ስለጠራቻት ደንግጣለች። " እኔንም ታቂኛለሽ" ብላ መቅደላዊት ከናሆም ጋር ተያዩ " ለማንኛውም እኔም እናንተን በስምና በዝና ከማወቅ ውጪ ሌላ ምንም የማቀው ነገር የለም። ሁልጊዜም ባሩክ ሁለታችሁን ያነሳል። ስለ ሁለታችሁም አብዝቶ ይጨነቅ ነበር። አንተን ወደ ራስህና ወደ ህልምህ ለመመለስ በጣም ብዙ ነገሮችን ያስባል ከአቅሙ በላይ ለማድረግ ይሞክራል በስተመጨረሻ ተሳካለት ። አንችን ደግሞ በጣም ወድዶሽ ነበር ስለ አንቺም ጋር ስለሚኖረው ሕይወት ያስባል አንቺን ደስተኛ ስለማድረግ። እኔ እዚህ ጊቢ ለ3 አመት ስቆይ ባሩክ እንዲህ የተሸነፈላት ሴት አልነበረችም የመጀመሪያዋ ሴት ነሽ። ባሩክ ጥሩ ያልሆነ የፍቅር ታሪክ ነበረው ያን አንቺ ሻርሽለት እናም ደስተኛ ነበር። በመጨረሻ ግን ከልቡ ከፋው።" ብላ ዝም አለች " አልገባኝም ጥሩ የፍቅር ሕይወት የለውም ስትይ ምን ለማለት ፈልገሽ ነው? ያገኛትን ሴት እየገፋ ተጫውቶ እየተወ ምን አይነት የፍቅር ሕይወት እንዲኖረው ነበር የፈለግሽው?" አለች መቅደላዊት ዮርዳኖስ ሳቅ እያለች " ባሩክ ማንንም ሴት ገፍቶ አያቅም!" አለች " ይሄን አንቺ እንዴት ታቂያለሽ?" አለች መቅደላዊት " ምክንያቱም አብሮ አደጌ ስለሆነ አንድ ሰፈር ስለሆነ ያደግነው። ባሩክ ጋር አኔድ አጥር ነው የሚለየን እኛ እቃ እቃ ስንጫወት እሱ መፅሐፍ ነበር የሚያነበው አባቱ የገዛለትን የተረት መፅሐፍ እያነበበ ለእኛ ይተርክልን ነበር ትልቅ ሲሆንም ይበልጥ ጊዜውን የሚፈጀው ከትምህርት ቤት ሲመለስ በማንበብ ነው። እስከ 12ኛ ክፍል ሴት አያቅም ነበር። አስራሁለት ላይ አንዲት ልጅ ወደድኩህ አለችውና ቀረበችው ትንሽ ግንኙነት ኤንደጀመሩ ባሩክ ሳያቅ ከአንድ በደንብ ከማይቀርበው ጓደኛው ጋር ግንኙነት ጀመረች። እሱም ተዋት ከዛ በኋላ ጊቢ ገባ ።እኔም በአመቱ ገባሁ ።እሱም ተቀበለኝ ፍሬሽ ታየምን ከሱ ጋር አሳልፋለሁ ብዙ ነገሮችን አሳየኝ አስተማረኝ የሚከብደኝን ነገር ይለረዳኛል በዛ ላይ አንድ ዲፓርትመንት ስለነበርን ምንም ነገር አብሮኝ ነው የሚሰራው ታዲያ በዚህን ጊዜ ነበር ስለሁለታችሁ ነገር በየተራ የነገረኝ። ስለአኔቺ ሲያወራኝ በጣም በሚገርም ፈገግታና ደስታ ነበር። ግን ምን ያደርጋል በስተመጨረሻ የማያውቀውን ስም ሁሉ ሰጠሽው። ትንሽ ከፍቶት ነበር ግን ደግሞ ናታኔም እንደሆነ ሲያውቅ አንቺን ተረዳሽ ስሜትሽን አዳመጠው ።ማንም ሰው የሰፈሩ ልጅ ስለዛ ሰው ቢናገር ተቀባይነት ያገኛል። እሱም እንደዛ ኸሰደው አሁን ሁሉንም ትቶ ራሱን ከእንደገና እየፈጠረ ነው።" ብላ ዝም አለች መቅደላዊት በየመሀሉ ስታለቅስ ። ናሆም በጥሞና ያዳምጣት ነበር። ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 71♥️ የመጨረሻው ክፍል ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ክፍል_69 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ መቅደላዊት አባቷን ካወራችው በኋላ ከራሷ ጋ ተጨቃጨቀች ራሷን መጠየቅ ጀመረች! ለምንድነው ግን እንዲህ የምሆነው? የሚል ጥያቄ ራሷን በለሆሳስ ጠየቀችው ።ነገር ግን መልስ አልመጣ አላት ጭንቅላቷ ላይ በጣም ብዙ ጥያቄዎች ይመላለሱባታል። " ለምንድነው ስለ ባሩክ እየሰማሁ የሚነግሩኝን የማላምነው? እንዴት ለናታኔም በአንድ ጊዜ ደስተኛ እሆናለሁ? ባሩክ ስለእኔ ምን ይሰማዋል? ናታኔምስ ለምን ስለ ባሩክ መጥፎነት ብቻ ይነግረኛል? ለምንድነው አሁን አባቴ ስለ ባሩክ ሲነግረኝ ውስጤ በደስታና በፍርሀት የተሞላው ???!!! መሰል ጥያቄወችን ለራሷ በየተራ ታዥጎደጉድ ጀመር። በመጨረሻ ደወለች ባሩክ ሶስት ጊዜ ከጠራ በኋላ አነሳው።" ሰላም መቅደላዊት " አለ " ሰ ላ ም " ድምጿ ተቆራረጠ። ዝም አላት " ላገኝህ እፈልጋለሁ!" አለች። "ወደ ኋላ መመለስ አልችልም ሁሉንም ረስቼ ትቸዋለሁ "አለ ባሩክ " እባክህ ባሩክ አውቃለሁ እንዳስቀየምኩህ ሁሉንም በአካል ተገናኝተን ላስረዳህ!" አለች " ስለ አስቀየምሽኝ ነገር ግድ አልሰጠኝም! እኔ ሕይወት ላይ የቀነሰው ነገር የለም በቃ ከእኔ ጋር የተገናኘነው ለናሆም ነበር የናሆምም ጉዳይ ተዘግቷል። ስለዚህ ምንም ነገር የለንም ከዚህ በኋላ እኔ አንቺንም ሆና ናታኔምን አላውቃችሁም። ከሰዋዊይነት ባህሪ ወጥታችሁ ሰውነቴን ልታሳጡኝ ሞክራችኋል። ግን የእኔ ሰውነት በከንቱ ወሬ የሚንሸራተት ሳይሆን ምሰሶ ነው። እና እኔ አንቺን አልተቀየምኩሽም ለማለት አልደፍርም ግን ለእኔ ለነገ ሕይወት የአንቺ ቂም ስለማይሰራልኝ ትቼዋለሁ ይቅር ብየሻለሁም። እኔ አሁን በነፃነት የማስብ ነፃ ሰው ነኝ! ደህና ሁኝ መቅደላዊት ቸር ይግጠምሽ!" አለ " በቃ አብረን ማደራችን ለአንተ ምንም ነበር እኔኮ ካልወደድኩት ሰው ጋር ተኝቼ አላውቅም " አለች " እሱን አላውቅም እኔ ግን አብረሽኝ ለመተኛት የፈለግሽበት ብየ ያስቀመጥኳቸው ሁለት ምክንያቶች የፈለግሽበት አንድ ባለውለታሽ ስለሆንኩ በአንቺ እይታ ለውለታየ የሚሆን ስጦታ ሁለተኛው እና ትልቁ ምክንያትሽ ናታኔም በወቅቱ እንደሚያፈቅርሽ ስላልነገረሽ የብቸኝነት ጉዞሽን ለመግታት አለቀ። እንጅ ለእኔ ቅንጣት ታክል ፍቅር ብትኖርሽ እንደዛ ደውለሽ የእኔን የውስጥ ስሜት ሳትረጅ ጥምብ እርኩሴን አታወጭውም ነበር። ያኔ ስታወሪ ዝም ያልኩሽ በተናገርሽው ነገር እንድትፀኝ ነው። ስለዚህ ከእኔ ይልቅ ለናታኔም ታስፈልጊዋለሽ።ጊቢም ላይ ብዙ አብራችሁ ትቆያላችሁ። ለአንቺ ሲል ብዙ ልቦለዶችን አምብቧል ፅፏል። እያነበብሽ ለምን እንደፃፋቸው ተረጅው።" አለ " እና ይሄን ለምን አልነገርከኝም እኔ ኮ እሱ እውነቱን ነው የመሰለኝ በእናትህ ባሩክ እሽ ለመጨረሻ ጊዜ ላግኝህ " አለች " አልችልም አሁን አስረድቸሽና እውነቱን ነግሬሽ ወደ ኋላ የምመለስበት ጊዜ ሳይሆን እውነቱን ነግሬሽና አስረድቼሽ አስተምሬሽ ወደ ፊት የምሄድበት ጊዜ ላይ ነኝ። ሁሉም የሚሆነው የሆነው ለበጎ ወደ ሌላ የህይወት ጎዳና ሊመራን ነው።"አለ " መቅደላዊት ስቅ ስቅ ብላ አለቀሰች "ባሩክ ስልኩን ዘጋው። የባሩክ ፊት ላይ ምንም አይነበብም። ደስታም ሀዘንም የለም። መቅደላዊት በድጋሚ ደወለችለት! ባሩክ ግን አያነሳም! ደገመችለት ባሩክ ስልኩን ዳይቨርት አደረገው! " መቅደላዊት የምትይዘው የምትጨብጠው አጣች ራሷን አዞራት ።እንደምንም ቀስ ብላ ራሷን በእጆቿ ደግፋ ተቀመጠች። ብዙ ከተረጋጋች በኋላ የሆነው ሁሉ ከእንደገና ትዝ አላት " ደህና ሁኝ " የባሩክ የመጨረሻ ቃል አቃጨለባት። ለባሩክ ፍቅር ይሁን ምን ውስጧ ላይ እንዳለ ለመረዳት የተቸገረች ትመስላለች።ነገር ግን ለናታኔም ልቧ ያደላል።ናታኔምን ትወደዋለች ግን ደግሞ ባሩክን ማጣት አትፈልግም።" አታልቅሽ ለምን ታለቅሻለሽ ለማን ደስ ይበለው ብለሽ ባሩክ መሄድ ስላለበት ነው የሄደው። በዛ ላይ አንቺ ይበልጥ የምትወጅው ናታኔምን ነው። እሱን ደግሞ ባሩክም ስላወቀ ይመስለኛል እንደዚህ አይነት ውሳኔ የወሰነው። " አለች የክፍሏ ጓደኛ የሆነቸው መክሊት መቅደላዊት ዝም ብላ እምባወቿን በጉንጮቿ ቶሎ ቶሎ ታንከባልል ነበር። መክሊት ከስር ከስር የመቅደላዊትን እምባ ብታብስም ነገር ግን መቅደላዊት ማልቀሷን ልታቆም አልቻለችም!! መቅደላዊት ድንገት ማልቀሷን አቆመችና " ዶርሙ ድረስ እሄዳለሁ እዛው አናግረዋለሁ!" አለች " ምን ያምሻል? መባረር ፈልገሻል?"አለች መክሊት " የፈለገው ይሁን ይቅርታ ልጠይቀውና ልለምነው ይገባል!" " ይቅርታ ጠየቅሽው አልጠየቅሽው ምንም አይሰራልሽም ምን የሚፈጠር ነገር አለ?" አለች መክሊት " በቃ ይቅርታ ካደረገልኝ በቂ ነው " አለች መቅደላዊት ። መክሊት የመቅደላዊት ሁኔታ አላምራት ሲል ስልኳን ተቀበለቻትና ደወለች "ሰላም መቅደላዊት "አለ ናሆም " መቅደላዊት አይደለሁም ጓደኛዋ መክሊት ነኝ " አለች " እሽ መክሊት ምን ልታዘዝ ?" " መቅደላዊት የባሩክ ዶርም ልሄድ ነው ብላ ድርቅ አለችብኝ እባክህ ከቻልክ ልጁን ከዶርም እንዲወጣ ንገረው " " ውይ ባሩክኮ አዲስአበባ ሄደ "አለ " ምን?" ደግማ ጠየቀችው መቅደላዊት ቀና ብላ ተመለከተቻትና ሮጣ ስልኩን ቀማቻት "ምንድን ነው ናሆም? " አለች " መቅደላዊት "ባሩክኮ ወደ ቤት ሄዷል " አለ " እንዳልሄደ እርግጠኛ ነኝ ዶርሙ ሄጀ አረጋግጣለሁ ችግር የለውም" አለች " እሽ ነይና ከእኔ ጋር አብረን እንሄዳለን ብሎ ያለበትን ነገራት ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 70♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ክፍል_68 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ደወለች ናታኔም ስልኩን አነሳው። " ደህና ነህ?" አለችው ድምጿ ይቆራረጣል" ደህና የኔ ፍቅር ምን ሆነሽ ነው ድምፅሽ ይቆራረጣል በዛ ላይ ልክ አይደለሽም " አለ " ሁሉም ነገር ተቀያይሯል ህልሜ ቅዠት እየሆነ ነው። ምነው ውጤትሽ አልተስተካከለም? አለ " ኧረ በጣም ቆንጆ ውጤት ሆኗል ግን ውስጤ ትክክል አይደለም አላውቅም የሆነ ነገርማ ሆኛለሁ ሳላውቀው ያጣሁት ነገር እንዳለ ይሰማኛል።" አለች " አይዞሽ የኔ ቆንጆ ምንም አላጣሽም እኔ ስለመጣሁ ይሆናል! እኔ አጠገብሽ ብሆን እንደዚህ አይሰማሽም ነበር። " አለ " አይመስለኝም ብቻ በባሩክ ላይ ልክ የሆነ ስራ የሰራሁ አልመሰለኝም " አለች "ሕ ሕ ልክ የሆነ ነገር የሰራሁ አይመስለኝም ነው ያልሽው? ኧረ መመለስ ፈለግሽ እ ?" አለ ናታኔም ኮስተር ብሎ አንተ ደግሞ ምን እንደዚህ ያደርግሀል አሁን እንደዛ ወጣኝ? ምን አልኩህ " ተበሳጨች " በቃ ይቅርታ የኔ ቆንጆ ባሩክን ስታነሽብኝ ስለማይመቸኝ ነው ።በጣም ነው የምጠላው። በቃ በእኛ መሀል አይግባ በወሪያችን መሀል ራሱ" አለ መቅደላዊት አልመለሰችለትም " ደግሞ ናሆም ደውሎልኝ ነበር አመሰግናለሁ ምናምን ብቻ አለኝ " አለ ናታኔም " አወ ለእኔም ደውሎልኝ ነበር ሁሉንም ነገር ሰምቷል እኛ ስናደርገው የነበረውን ሁሉ ከዛ ከእናቱ ጋርም ታርቋል። " አለች " ኧረ ባክሽ ማን አስታረቀው?" "ባሩክ ነው ያስታረቀኝ ሀሳቡ የናታኔም እንደሆነና ከዛ እኔም ከአንተ ጋር እየሰራሁ እንደነበር እሱ ምንም እንዳልሰራ አድርጎ ለናሆም ነገረው በደንብ መከረውና ከእናቱ ጋር ምህረት አውርዶ ደስተኛ ሆኗል።" አለች ። " ይሄ አስመሳይ ሀሳቡን ከእኔ ወስዶ እሱ ተሞገሰ አይደል?" አለ " አንተ ደግሞ የሀሳቡ አፍላቂ እሱ እነሱ ናቸው አለው እያልኩህ አይደል እንዴ ውይ ናታኔም ጨለማ አትሁን እንጅ በዛ ላይ ባሩክ ላይ እንዲህ የመሆን መብት የለህም" መቅደላዊት ጮኸችበት " እንዴ እሱኮ አንቺን ቀምቶኝ ነበር" አለ " እሱ አልቀማህም እኔ ነኝ ወድጄው ከእሱ ጋር ሆኜ የነበረው። ስለዚህ ከዚህ በኋላ ስለሱ መጥፎ ነገር መስማት ስለማልፈልግ ዝም በል በዛ ላይ የአንተን እውነት ብቻ አዳምጬ ነው አብሬሄ ያለሁት። አንተ የበለጠ ደስተኛ እንደምታደርገኝ ስለማምን ስለዚ መጥፎ ንግግር ብታቆም መልካም ነው" አለች " እሽ ካልሽ እሱ ግን አስመሳይ ነው አሁን ራሱ ለባሩክ እንደዛ ብሎ በእጅ አዙር አንቺን ለማስገባትና እኔ ደግሞ እውነቱን ለአንቺ ስለነገርኩሽ ሊበቀል ነው በእርግጠኝነት " አለ ኧረ በእግዚአብሔር ናታኔም ወደ ራስህ ተመለስ በቃ ቸው እደውልልሀለሁ " አለች ። ኡፍፍፍፍፍፍፍ መቅደላዊት በረጅሙ ተነፈሰች ራሷን ይዛ ወዲያና ወዲህ አወዛወዘች። በዚህን ጊዜ ስልኳ ጠራ ስለኳን በግራ እጇ አንስታ ስታየው አባቷ ነበር ተስፈንጥራ ተነሳችና " አባዬ " አለች " "አቤት የኔ ልጅ " አለ " በጣም ናፈቀኸኝ ነበር " አለች " " እና የናፈቀ ሰው እንዲህ ነው? ነያ ታዲያ ከናፈኩሽ መምጣቴማ አይቀርም እመጣለሁ በዚህ ሳምንት አንዳንድ ማስተካከል ያለብኝ ነገር አለ" አለች " ምን ሚስተካከል ነገር አለ ፈተና ከጨረሳችሁ ቆይተታችኋል አየሰደል?" አለ " አወ እሱማ ግን ውጤቴን በ።ንብ ለማረጋገጥ ነው አንዳንድ ያልለቀቁ መምህራኖች አሉ " አለች በመዋሸቷ እንደመሳቀቅ ብላ " እሽ እንግዲህ ያው አላለቀም የምትይውን ነገር ጨርሰሽ ነይ በጣም ናፍቀሽናል። " አለ " እሽ አባዬ እምየን ሰላም በልልኝ ሁሉንም " "አለች እሽ የኔ ልጅ ሁሉንም እላለሁ። አሁን እኮ በመካነ በቴሌቪዥን የአድዋ ዝግጅታችሁን እያየንኮ ድንቅ ፕሮግራም ነበር " አለ" ወደዳችሁት?" አለች " አወ በተለይ ይሄ ተማሪው ልጅ ባሩክ ያቀረበው ዝግጅት የሚገርም ነው ደግሞ የምህንድስና ተማሪ ሆኖ ታሪክን እንዴት እንደያዘ አስገርሞኛል። በጣም ማለፊያ ልጅ ነው አፋችንን ከፍተን ነበር ስናየው የነበረው። ከመጀመሪያው ጀምሮኮ እንዴት እንደወሰደን አቤት ልጅ ማለት እንዲህ ነው እንጅ " አለ " ደግሞኮ የዲፓርትመንቱ ሰቃይ ነው " አለች መቅደላዊት ፍፁም በሆነ ደስታ " በእውነት ይሄ ሚገርም ነው በሁሉም ነዋ የተመረጠው አቤት መባረክ አባቱና እናቱ ለዚህ ማንነቱ ትልቅ ቦታ አሳድረዋል በእውነት የልጆች እንዲህ መሆን ወላጆች ናቸው ከፍተኛውን ሚና ሚጫወቱት" አለ " ልክ እንደ አንተ እኔ ላይ እንዳረከው" አለች " አይይ ልጄ የኔን እንኳ ተይው ምንም አላደረኩልሽም የአንቺ ጥረት ነው። " አለ " ተው አባ እንደሱ አትበል አንተ ሁሉም ነገሬ ነህ " አለች " በይ ለማንኛውም ልጁን አባቴ ወዶሀል ብለሽ በእኔ ስም ሰላም በይልኝ" አለ" እ..... ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 69♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ክፍል_67 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ " ሰላም ናሆም " አለች " መቅደላዊት እንዴት ነሽ " አለ ናሆም በሰለለ ና በተረጋጋ ድምፅ "አለሁልህ ግን በጣም ደብሮኛል ምን እንደሆንኩ አላውቅም ። " አለች ምንም መልስ አልመለሰላትም "ምን ሆነሀል ናሆም?" አለች " ሁሉንም ነገር ሰምቻለሁ " አለ " ምኑን ነው የሰማኸው?"አለች " በቃ ለእኔ ያደረጋችሁትን " መቅደላዊት ዝም አለች ።" እውነትኮ መውጣቷ አትቀርም እስከመቼ ነበር ግን የምትደብቁት " አለ መቅደላዊት ምንም አላለችም " በጣም ነው የማመሰግነው ይሄን ወንድም ና እህት ራሱ አያደርገውም። በጣም " ኧረ ናሆም እንደሱ አትበል በቃ ይሄ እኮ ግዴታችን ነው እኔም ሆነ ናታኔም እያየንህ ዝም ልንል አልቻልንም በቃ ሀሳቡን ናታ አመጣው በቃ ጀመርነው ይሄው በናታኔም ምክንያት ሁሉም ተሳካ። እና እኔን ከማመስገንህ በፊት ናታኔምን ብታመሰግነው የተሻለ ነው።ግን እንዴት ልታውቅ ቻልክ ?" አለች " ባሩክ ጋር እያወራን በቀደም ናታኔምን ሸኝተነው ከተመለስን በኋላ ሙሉ በሙሉ ማድረግ ያለብኝን ነገረኝ ከዛ ለእናቴ ከአስደወለኝ እና የምለውን ካለኝ በኋላ ለእናቴ ደወልኩ ውጤቱ ባሩክ ያለኝ ነበር። ደስተኛ ሆንኩ ከዛ በመሀል እማየ የናታኔምን ስም አንስታ በስተመጨረሻ አደረገው ከልጅሽ ጋር እንድትታረቁ አደርጋለሁ ብሎ ነበር ይሄው አለች ። በዚህን ጊዜ ስለ ናታኔም ስጠይቃት ሁሉንም ነገረችኝ ባሩክን ስለጉዳዩ ጠየኩት የእሱም ምላሽ የናታኔምና የመቅደላዊት ስራ ነው የሚል ነበር። አሁን ከሱ ጋር እያወራን ነበር። እናንተን ማመስገን እንዳለብኝ ነግሮኝ ከዚህ በኋላ አንገናኝም ብሎ ሄደ" አለ " ምን ማለት ነው አንገናኝም ማለት?" አለች " በቃ ከራሴ ጋ ነው መሆን የምፈልገው አስጨንቆኝ የነበረው የአንተ ጉዳይ ነበር ይሄው ተቋጨ በዛ ላይ አንዳንድ ሰወች የመጥፎ ትዝታ መነሻ ናቸው አለኝ " አለ ናሆም ።መቅደላዊት ልቧ ስንጥቅ አለ ዝም አለች ሰውነቷ ቀዘቀዘ " የት ሊሄድ ነው ለምንድነው እንደዚህ ያለው ?" ጥያቄወቿን በተከታታይ ራሷን መጠየቅ ጀመረች። " እና ሁለተኛ አንገናኝም? አለህ?" አለች " አዎ እስኪ ከቻልሽ ለምኝው መቅደላዊት ባሩክ ያስፈልገናል ማለቴ ያስፈልገኛል።" አለ " ናሆም ባሩክ ኮ እኔን አይሰማኝም ያላመነበት ነገር ከሆነ በጭራሽ በዛ ላይ እኔም ቢሆን በጣም ነው የተናደድሁበት በናታኔም ጉዳይ ልክ አልሰራም " አለች " ናሆም በጣም ተናደደ "መረዳት አትችይም እንዴ አንቺ ልጅ? እኔ እርግጠኛ ነኝ ባሩክ እንደዛ እንደማያደርግ " አለ " ሳቀችና እሽ እንደኔ እወድሻለሁ ብሎ ያታለላት የሰፈር ልጅስ እንዳለች ታቃለህ?" አለች " ናሆም የሚናገረው አጣ የሚላት ጠፋው ዝም አለ " አየህ መልስ የለህም አለች መቅደላዊት ። " ናሆም በጣም ተገረመና ደግሞ ይሄን ልቦለድ ማን ነው የፃፈልሽ ራሱ ናታኔም ነው። በጣም ነው የሚገርመው ባሩክ ላይ እንዲህ መሆናችሁን አላምንም እኔ ግን የምነግርሽ ከፈለግሽ እውነቱን ከራሱ ከባሩክ ብትሰሚ ይሻል ነበር። አሁን እንኳ እረፍዶብሻል። እጅሽ ያለ ሸክላ አምልጦሽ ከወደቀ እንደማይነሳ ሁሉ የባሩክም ጉዳይ እንደዛ ነው። እንኳን ፍቅረኝነቱን ጓደኛነቱን ነው ያጣሽው ይሄ ደግሞ አንድ ቀን ይገባሻል። " አለና ዝም አለ መቅደላዊትም ዝም አለች " ሌላው ነገር ናታኔም ምንም አንድ እውነት አልነገረሽም ሁሉም ውሸት ነው ። ናታኔም እንደሚያፈቅርሽ ባሩክ ሲያውቅ በጣም ነበር የደበረው ምነው ቀድሜ ባውቅ ከእኔ ደስታ የእሱ ይሻል ነበር። ብሎ ያሰበ ልጅ ነው። ለማንኛውም እንዲህ የምልሽ ናታኔም አንቺን የራሱ ለማድረግ የማይሆንና ከገሀድ የሌለ ውሸት ዋሽቶሻል እያልኩሽ ነው። በፈለግሽው መንገድ ልታጣሪው ትችያለሽ። " አለ ።ነገር ግን አንቺ በአሁኑ ስአት ያለሽ ሀብት እና እውነት ውሸት ብቻ ነው። ግን አይዞሽ ውስጥሽ ንፁህ ነው። ሁሉንም ነገር ታልፊዋለሽ እኔ በምችለው እና በአቅሜ ሁሌም ከጎንሽ ነኝ። ስለ አደረግሽልኝ ነገር ሁሉ አመሰግናለሁ። አንቺ ናቲ ባሩክ ህይወቴ ውስጥ ትልቅ ቦታ አላችሁ።" አለ ናሆም" ተው እንጅ ናሆም እንደዚህ አትበል በጣም ከፍቶኛል። ይበልጥ እንዲከፋኝ አታድርግ " አለች " አይዞሽ እኔ እንኳ እንዲከፋሽ አላደርግም ግን ሁኔታወች ያው ደስ አይልም አንቺና ናቲ ሁሉንም አበላሽታችሁታል። ቢሆንም ግን እኔ ምንም ቢሆን ምንምም ብትሆኑ ከሁላችሁም ጋ ነኝ ለሁላችሁም እኩል ቦታ ነው ያለኝ!" አለ መቅደላዊት ሳታስበው አለቀሰች እምባወቿ በቀስታ ከጉንጮቿ ይንከባለሉ ነበር። በቀስታ ስልኳን አስቀመጠች ከእንደገና አነሳች። ስልኳን እያነሳች እየጣለች ብዙ ከቆየች በኋላ....... ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 68 ♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ክፍል_66 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ "ተው እንጅ ናሆም አትናደድ ይህ ኦፕሬሽን ለአንተ ደስታ ሲባል የተዘጋጀ እንጅ አንተ እንድትናደድ አልነበረም። ከእውነት ነው የምነግረህ ናታኔምም ሆነ መቅደላዊት ጥፋት የለባቸውም ። ናታኔም እንደ እናቱ ልጅ ነበር የአንተ ነገር ግድ የሚሰጠው አስታውሳለሁ ለመጀመሪያ ጊዜ ስለአንተ ባህሪ እና ስለ እናትህ ቀረቤታ ሲነግረኝ ፊቱ ላይ ያነበብሁትን ጥላሸት መቼም ከአይኔ አይጠፋም። " ባሩክ ናታኔም ከእናቱ ጋር ምህረት አውርዶ ሕይወቱን ደስታ የተሞላበት ማድረግ አለበት። በዚህ ሁኔታ ከቀጠለ በበቀል ተነሳስቶ ሌላ ህይወት ነው የሚኖረው። እና በተቻለን መጠን ከዛ ነገር እንዲወጣ እናድርግ " አለኝ። ሀሳቡ የሚያሻማ ስላልነበር ሳላቅማማ ተቀበልኩት። በምችለው አብሪያቸው ሆኜ አንዳንድ ነገሮችን እነግራቸው ነበር ።ብዙ ጊዜ እየደረስክባቸው ምን ያህል ይጨነቁ እንደነበርም አውቃለሁ።መቅደላዊት ከትምህርቷ በላይ ለአንተ ሕይወት ጊዜ ሰጥታለች። ለዚህም ከናታኔም ጋር በብዛት እየተገናኙ ያወሩ ነበር የደረሱበትን ይወያያሉ። ሌላው መቅደላዊት ስለቤተሰቦቿ የነገረችህ ታሪክ የፈጠራ ነው። ከአንተ ታሪክ ጋር በማመሳሰል የአንተን ነገ ለመቀየር የተደረሰ ነው። ደራሲው ደግሞ እኔ ነኝ ። ግን ይሄ ሁሉ ለአንተ ነው ናሆም። የምነግርህ ነገር ቢኖር እድለኛ ነህ ሁላችንም አንተዋወቅም ግን በሰውነት አንድ ነን። ህመምህና ነገህ ስላሳሰበን እንጅ በዚህ ነገር ላይ የምናገኘው አንዳች ጥቅም ነገር የለም። በስራችን ከተበሰጨህና ከተጎዳህ ደግሞ ልልህ የምችለው ይቅርታ ብቻ ነው። ምክንያቱም ሁሉም ነገር ሆኖ ስላለፈ " አለና ባሩክ ዝም አለ። በመካከላቸው ዝምታ ሰፈነ።ባሩክ ወደ ሰማይ አንገቱን እንደ አንቴና መዝዞ በጉሞች መሀል ገብታ ለመውጣት ከምትዳክረው ፀሀይ ጋር አፈጠጠ። ትንሽ ከተመለከታት በኋላ ናሆምን በእጁ ጎንተል አድረገው ናሆም ወደ ባሩክ ሲዞር ባሩክ በጣቱ ወደ ሰማይ ጠቆመው" እይ እስኪ ወንድሜ ናሆም የፅሀይን ዙሪያ ገባውን ዙሪያዋን ሙሉ ጥቁር ደመና አለ እሷ ያለችበት ደግሞ ነጭ ጉም ነው። ነጩ ጉም ላይ ስለሆነ ያለችው ብርሀኗ ብዙም አልጠፋም ነገር ግን ሙሉ ጥቁር ከሆነው ጉም ብትገባ ግን ያለጊዜዋ ትጨልማለች ።የምትጨልመው በ12 ስአት ሆኖ ሳለ ነገር ግን እሷ ከዚያም በፊት ትጠፋለች። ሕይወትም እንደዚህ ናት ድንገት በሚወጣባት እና በሚያጋጥማት ጉም ተሸፍና ጥሩነቷ ይጠፋል። ታዲያ እኛም ፀሀይዋ ስትወጣ ጉሙ እንደሚያጋጥማት እንደምታስብ ሁሉ እኛም በህይወታችን እንደዚህ እንደሚያጋጥመን አምነን መጀመር አለብን። ስለዚህ ወንድሜ አንተም ይሄን ወቅትህን በአስተውሎት ብታልፈው ትልቁ ማማ ላይ ትቀመጣለህ ለማለት ነው።"አለ ባሩክ ናሆም አይኑን ከፀሀይዋ እንደተከለ ነው ዝም ብሎ ያያታል። ፀሀይዋ ብዙም ካልጠቆረው ጉም ግማሽ ጎኗን አስወጣች። ከእንደገና ደግሞ ሌላኛው የወጣውን ግማሽ አካሏን ሸፈነው። ከብዙ ቆይታ በኋላ ፀሀይ ሙሉ በሙሉ ራሷን ከሸፈናት ጉም ነፃ አወጣች። ይሄኔ ናሆም ፈገግ አለ ደስ አለው። " አላውቅም ምን ማለት እንዳለብኝ ባሩክ ሁሉም ነገር ከጭንቅላቴ በላይ ሆኖብኛል።" ስጠራህ በጣም ተናድጄ እና ተበሳጭቼ ነበር ምክንያቱም ሁሉም ነገር ድንገት ስለሆነብኝ ነገር ግን አሁን እያወራኸኝ ሁሉንም አለማወቄንና አለመረዳቴን አሰብሁ የእውነት መበሳጨቴ የባዶነት ምልክት ሆኖ ታየኝ። ሁላችሁንም በጣም ነው የማመሰግነው አሁን ግን ትክክለኛ መንገዱን አሳይታችሁኛል። ከበቀል ይልቅ ምህረትን ከጥላቻ ይልቅ ፍቅርን ከራስ በላይ ለሌች ማሰብን አስተምራችሁኛል። በጣም አመሰግናለሁ ባሩክ ሌላ ምንም ልል አልችልም። " አለ " ችግር የለውም ናሆም ሀሳባችን አንተ ሳታውቅ ሁኔታዎችን ለመቋጨት ነበር ነገር ግን በመሀል እንዳየኸው ችግር ተፈጠረ። የእኔና የናታን ጉዳይ እንዲሁም ከመቀደላዊት ጋር እንደዚህ ያልቃል ብየ አላሰብኩም ነበር። ግን ምን ታደርገዋለህ? አለመረዳዳት ከባድ ነው የአለመረዳዳት ችግር ሰውነትን ያፈርሳል። ግን እኔ አሁን ውጤታማ ነኝ አሸናፊ ነኝ ባለድል ነኝ የአንተ ጉዳይ ነበር መቅደላዊት ጋር ተጣልቼ ከጨነቀኝ በላይ ጨንቆኝ የነበረው አሁን ግን ተመስገን ነው በአንተ አስተዋይነት ተሳክቷል አሁን ነፃ ሰው ነኝ አሁን ከማንም ጋር አልገናኝም ራሴ ከራሴ ጋ እንጅ ። እስካሁን ነፃ አልነበርሁም ብዙ የሚረብሹኝ ነገሮች ነበሩ ነገር ግን ዛሬ በአንተ ቅንነት ሁሉንም አስወግጃቸዋለሁ በል ወዳጄ መልካም ሕይወት ይግጠምህ ሰላሙ ሁሉ ለአንተ ይሁን ።" አለ ና ባሩክ ከተቀመጠበት ብድግ አለ ። ናሆምም አብሮት ተከታትሎት ተነሳና " ከዚህ በኋላ አንገናኝም አናወራም ማለት ነው?" ብሎ ጠየቀው። " እናወራለን ግን አንዳንድ ሰወች የመጥፎት ትዝታዎች ስለሆኑ ትንሽ ጊዜ ያስፈልጋል። እስከዛው መልካም ሁን" ብሎት ሄደ ። ናሆም ታላቅ ወንድሙ ትቶት የሄደ ያህል ተሰማው። አሁን የእግሩ ዳና እየራቀው ያለው ሰው ወደ ሕይወቱ እንዲመለስ ያላመነታው ሰው ነው።ናሆምም በዝግታ ተራመደ ባሩክ እየራቀው ሄደ ። ናሆም ክንፏት እንደመታ እርግብ አንድ እጁን አንጠልጥሎ ትንሽ ከተጓዘ በኋላ ከአንድ ዛፍ ስር ተቀመጠ። ናሆም ተደበላለቀበት ደስታ ሀዘን ብቻ በውል ያላወቀው ስሜት ሰውነቱን ይነዝረው ጀመር። ለናታኔም ሊደውል ፈልጎ ናታኔም ባሩክ ላይ ያደረገው ነገር ትዝ አለውና ተወው ግን ቢሆንም ማመስገን አለብኝ "አለና ደወለለት ።" ያደረክልኝን ነገር አውቂያለሁ በጣም ነው የማመሰግነው ወንድሜ ዝርዝሩን ስትመለስ እናወራለን "ብሎት ዘጋና ከእንደገና ለመቅደላዊት ደወለ።መቅደላዊት ስልኳን አነሳችው በጣም ደብሯት ነበር ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 67♥️ ነገ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ክፍል_65 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ መቅደላዊት ስልኩን አነሳችው " ስደውልልህ ለምንድነው የማታነሳው?"አለች " እየውልሽ መቅደላዊት እኔ እስካሁን ዝም ያልኩሽ በዝምታየ እንድንግባባ ነበር ።ነገር ግን አንቺ መረዳት አልቻልሽም። ስለዚህ አንቺ ወደ እኔ የሚያስደውል ጉዳይ ስለሌለሽ ባትደውይ መልካም ነው። ሁለተኛ አትደውይልኝ ለምን ስልክ አላነሳም ምናምንም እያለሽ ወደ ሌላ ሰው አትደውይ በቃ እኔን አታውቂኝም ። በተቻለሽ መጠን ይሄን ብቻ ነው የምለምንሽ አ..ት..ደ..ው...ይ ዝም ያልኩሽ ሕይወትሽን ላለመንካት ነው። አንቺም ሕይወቴን ላለመንካት ዝም በይ።" አለና ስልኩን ዘጋባት ። መቅደላዊት ተናደደች ። መልሳ ስትደውል ስልኩ አይሰራም። ስልኳን ብላክ ሊስት ውስጥ አስገብቶታል። ባሩክ ተንፈስ አለና " ቆንጆ ጣፋጭ " አለ ናሆም በባሩክ እርዳታ ለእናቱ ደወለላት። እናቱ ስታየው ደነገጠች አነሳችውና ልጄ ስትል " አቤት እማየ " አለ በድንጋጤ ስለኩን ጣለችው ለብዙ አመታት ይሄን ስም ብሏት አያውቅም እማየም አባየም ሲል የነበረው አባቱን ነው። ናሆም ሃሎ ሃሎ አለ ከትንሽ ደቂቃ በኋላ እናቱ አነሳቸውና እያለቀሰች " አማየ ነው ያልከኝ ልጄ? " አለች " አወ እማየ ምነው ለምንድነው ምታለቅሽው?" አለ ናሆም ያለቀሰችበት ነገር ያልገባው በመምሰል። " እኔ ነኝ እንጅ የማቀው አይ ቸሩ መድሀኒአለም አባቴ እንደው ለአንተ ምን ይሳልሀል" ናሆምኔ ማውራቱን ትታ ወደ ሰማይ አንጋጣ እምባወቿን በጉንጮቿ እያበሰች ታመሰግናለች። " አውሪኝ እንጅ ወይም ዝጊውና ፀልየሽ አመስግነሽ ስትጨርሺ ደውይልኝ " አለ ትዝ አላት ለካ እሱ ነው የደወለው። ዘግታ መልሳ ደወለችለት ናሆም ፈገግ እያለ አነሳው። " ልጄ " አለች " አቤት " አለ ናሆም ደህና ነህልኝ ስንት ጊዜ ሁሉ ከአንተ ከልጄ ጋር ሰላም እንዲኖረኝ እናቴን ድንግል ማርያምን ተማፅኛት ነበር። አለ " እኔም እናቴ እላየ ያለው ክፉ ሰይጣን እናንተን እናቴን እህቴን እና ቤተሰቤን እንድጠላ ያደረገኝን ክፉ መንፈስ እንድታስወጣልኝ ያለ መታከት እየለመንኳት ነበር። ነገር ግን አንዱ ጓደኛየ በጣም መከረኝ ሰደበኝ ከዛ በቃ ጥላቻየ በአንዴ ለቀቀኝ!" አለ ናሆም ውይ የተባረከ ልጅ እንደው ጌታየ ህይወቱን ቀና ያድርግለት ሕልሙ እውን ይሁን ለእኔ እንዲህ የደስታ ብርሀን እንደሆነ እድሜውን በሙሉ ሀዘን አይንካው። " አለች " ኧረ እማየ ምርቃቱን ለእኔም ቀነስ አድርጊልኝ " አለ " እንዴ ለአንተማ የምን ምርቃት ብቻ ልጄ ከዚህ በኋላማ ባለኝ እድሜ አንተን ደስተኛ ማድረግ ነው እንጅ የምፈልገው። " አለች " እሽ እናቴ ችግር የለውም ለቀልድ ያህል ነው ነአንቺን የእናቴን ፍቅር ካገኘሁ ይበቃኛል። "አለ " አቤት አምላኬ በምን በን ነው እንደው ያን ልጅ የተዋወኩት?" አለች " ማንን " አለ ናሆም " ከናታኔም ጋር ነዋ እንዴት ያለ መልካም ልጅ መሰለህ!" አለች " እ እ እንዴት መቼ ነው እንዲህ የሆነው እናቴ " አለ ተንተባተበ አይኖቹን በግርምት አስለመለማቸው። " ያው አንተ አላናግር ስትለኝ የሱን ስልክ ይዤ ስለ ደህንነትህና ውሎህ እጠይቀው ነበር እሱም ታዲያ እንደምንም ብየ እንዲያወራሽ አደርገዋለሁ " አለኝ ይሄው በስተመጨረሻ አደረገው።" አለች ።" እሽ በቃ እማ ማታ በደንብ እናወራለን!" አለና ስልኩን ዘጋው። ናሆም ሁሉንም ለማስታወሰ ሞከረ የእሱን ጉዳይ ለእኔ ተይው። ከማን ጋር ነው የምታወራው ስለኔ ሲለው ከሜላት ጋር ያለው ነገር ትዝ አለው። ያቺ ሴት ሜላት ሳትሆን መቅደላዊት ነበረች ከመቅደላዊት ጋ የተግባቡት በእኔ ምክንያት ነው። መቅደላዊት የነገረችው የሷ ታሪክ ውሸት ነው የእኔን አይነት አሳዛኝ ሕይወት እንዲኖራት ይህ ሁሉ የታቀደው በናታኔም ነው። እሽ ባሩክስ እንዴት ሊገባ ቻለ? አላውቅም እሱን ከሱ ጋ አወራለሁ። መቅደላዊት ትዝ አለችው ናታኔምን ሸኝተው ሲመለሱ ያለችው ትዝ አለው " በሆነ ነገር ተግባብተን "ያለችው ህ ህ ራሱን ነቀነቀና የሆነ ነገር? ያ የሆነ ነገር እኔ ነበርኳ። ግሩም ነው።ይሄ ሁሉ እኔ ሳላቅ በእኔ አእምሮ ላይ ሲጓዙ ኖረዋላ። መቅደላዊት ናሆምና ባሩክ ሆነው ዋርካው ላይ ሲያገኛቸው የሰጡት ምላሽ " እኛም መንገድ ላይ ስታለቅስ አግኝተናት ነው " ያሉት አሳቀው። ድራማ ነበር ሲሰሩብኝ የነበረው። በቃ እኔ አሻንጉሊት እነሱ ደግሞ ህፃን ነበሩ እኔ እነሱን እያጫወትሁ ነበር። ራሱን ይዞ አንገቱን ደፍቶ ለደቂቃወች ዝም አለ። ናሆም ለባሩክ ሊደውልለት ይፈልጋል። ግን ደግሞ ተናዶበታል። በመጨረሻ መደወል እንዳለበትና ስለሁኔታው ተገናኝተው እንዲነግረው ፈለገ ደወለለትና ገብርየ እንዲገናኙ ተነጋግረው ስልኩን ዘጋው። ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 66♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ክፍል_64 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ "ሕልም የሌለው እንቅልፍ ማሳለፍ ግን እንዴት ያስጠላል። በርግጥ ከአንዳንድ ከማይሆኑ ሕልሞች ቅዠት ይሻላል ። ሰው በህልሙ እስረኛ ሊሆን ይቻል ዘንድ ያስገደደው ነፃ ፈቃዱ ነው። የነገ ባሪያነቱን ለማስመስከር። ፍቅር የሌለባት አለም ገሀነም ናት። በመኖር ውስጥ ካለመኖር ባለመኖር ውስጥ መኖር እድለኝነት ነው። " አለ ባሩክ አይኖቹን እየጠራረገ ከአልጋው በመነሳት ላይ እያለ። " አወ " አለ ለራሱ ጥያቄ ራሱ መልስ እየሰጠ። መቅደላዊት ከነቃች ቆይታለች። አልጋዋ ስር ተወሽቃ ። የባሩክ እንደዛ መሆን አበሳጭቷታል። " ግን ምን ሆኜ ነው?" እንዲህ በአጭር ጊዜ የተቀየርሁት በጭራሽ እኔ ከራሴ ጋር አይደለሁም " አለች አልጋዋ ላይ ተነስታ ስልኳን ቻርጅ ተሰክቶ ከነበረው ነቅላ ተመልሳ ወደ አልጋዋ ጋደም ብላ የስልኳን ኢንተርኔት ከፍታ የዩኒቨርስቲው ዌብሳይት በመግባት የይለፍ ቃሏን ከጨመረች በኋላ ከፈተች ውጤቷን ለማየት። በቅርብ የተፈተነችውን ትምህርት ጨምሮ ሁሉም የትምህርት አይነቶች ገብተውላታል ። በዚህም ሲሚስተር GPAዋ 3.74 ደርሷል። ደስ አላት በዚህን ጊዜ ባሩክ ትዝ አላት። ለዚህ ውጤት ባሩክ ደክሟል ራሱን እስከማጋፈጥ ነው። ደግማ አየችው A+ ይላል 93 ነው ያመጣችው። ያ ፈታኝ የተናገራትን አስታወሰች ሄዱ ራሱ በቸልታ ምንም አለማለቱ በአይኗ ውል አለባት። የባሩክ መሯሯጥ ከመምህር እስከ አካዳሚክ ጉዳዮች። የስልኳን ኢንተርኔት አጠፋችና ለባሩክ ደወለችለት። ስልኩ ጥሪ አይቀበልም ይላል በድጋሚ ሞከረችው ጥሪ አይቀበልም አሁንም ለመጨረሻ ጊዜ ስትሞክር ጠራ። ባሩክ በረንዳው ላይ ሆኖ ጥርሱን እየቦረሸ ነበር ስልኩ ሲጠራ ገባ ገብቶ ሲያየው መቅደላዊት ናት ተመልሶ ጥርሱን መቦረሹን ቀጠለ። በተደጋጋሚ ደወለችለት ነገር ግን አያነሳም። መቅደላዊት ለናሆም ደወለችለት ናሆም ስልኩን በሁለት ጥሪ አነሳውና " እ መቅዲ " አለ "ወይዬ ናሆም እንዴት አደረክ " " ደህና አንቺ እንዴት አደርሽ?" " እግዚአብሔር ይመስገን ናሆም ባሩክ እኮ ስልክ አላነሳ ብሎኝ ነው። አብራችሁ ናችሁ እንዴ?" " በዚህ ስአት ገና ጠዋት እኮ ነው ?" " ለምን ፈልገሽው ነው?" " ኧረ ለምንም " " ግን መቅደላዊት አንዳንዴ ልጅ ሌላ ጊዜ አስተዋይና ብስል ትመስሊኝ ነበር። " አለ ናሆም " እንዴት ማለት?" አለች " ማለቴ እንደዛ ከተናገርሽው በኋላ ስልክ እንዲያነሳልሽ መጠበቅሽ አስገርሞኝ ነዋ!" አለ ናሆም " ምን አልኩት ያደረገውን ነው እኮ ያልኩት!" አለች " ህ አይ እሱን እንደፈለግሽ ግን እኔ ብሆን ኑሮ ራስሽን እንድትጠይ አድርጌ ነበር የምሰድብሽ ግን ባሩክ መሆኑ ጠቀመሽ ለማንኛውም ስሜቴን ነው የነገርኩሽ። እሱን እንድልልሽ የምችፈልጊው ነገር አለ?" አለ ናሆም " ኧረ በጭራሽ! ግን በሰላም ከሆነ ስልክ ያላነሳው ችግር የለውም እኔን ላለማዋራት ብሎ ከሆነም በቃ እንደፈለገ " አለች " በሰላም ሳይሆን ቀርቶ ይሁን አንችን ላለማውራት ፈልጎ ይሁን ስልክ ያላነሳው አላወኩም መቅደላዊት " አለ " እሽ በቃ ቻው " አለች " ልጅቱ ጤና የላትም እንዴ ሄደት መለስ ትላለች ። ግን ደግሞ ልቧ ንፁህ ይመስላል። ሁሉን አማኝ ነገር ሳትሆን አትቀርም ። ለማንኛውም ባሩክ ጋር እስኪ ልደውል። አለና ደወለለት። ባሩክ አፉን ከተጉመጨመጨ በኋላ ወደ ወደ ውስጥ ሲገባ ስልኩ ሲጮህ ተገጣጠሙ " ደግሞ በድጋሚ ደውለሽ ነው " አለና ስልኩን ሲያየው ናሆም ነው " እ ናሆም "","እንዴት አደርህ ባሩክ " አለሁልህ እናትና ልጁ ይመስገኑ!" ጥሩ ነው እኔ እኮ ዛሬ ልደውል ብየ ወደ ቤት " አለ ናሆም " እና ምን ትጠብቃለህ ስአቱ አሁን ነው። ጊዜ ታክሲ አይደለም አይጠብቅም ቆሞ አይደል የሚባለው አሁን በኋላ ሳይሆን ቶሎ ደውልላቸው በጧት የምስራቹን አርዳቸው ታዲያ በምንም ነገር እንዳታወላውል አደራህን ናሆም። ፍፁም በሆነ ሀሴትና እርጋታ እሺ ?" አለ ባሩክ " እሽ ሁሉንም አደርጋለሁ " አለ ናሆም " እየውልህ አሁን መደወልህ ጥቅሙ በህለምህ ስታያቸው እንዳደርህና በህልምህ ምክንያት ልታወራቸውና ይቅር ልትላቸው እንዳስብክ ያስባሉ " አለ ባሩክ " ልክ ነህ በቃ አሁን ልጀውል አለና ቆይ ቆይ መቅደላዊት ደውላልኝ ነበር ስልክ አያነሳም ምናምን ስትል ነበር "" ጥርሴን እየቦረሽኩ ነበር ለምን ፈልጋኝ ነው ነግራሀለች?" አለ ባሩክ " ኧረ በጭራሽ በቃ አንዳንድ ነገር አወራኋትና በዠጨረስን " አለ ናሆም " ጥሩ በቃ ያልኩህን አሁን አድርግ ወደ በኋላ እደውልልሀለሁ ብሎ ስልኩን ዘጋና ሌባ ጣቱን በከንፈሮቹ መሀል አስደግፎ ትንሽ ካሰበ በኋላ ስልኩን ነካ። ዘደ መቅደላዊት ደወለ። ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 65♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ክፍል_63 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ "እየውልህ ናሆም ተሸውደሀል እናትህን ሳይሆን ስትቀጣና ስትጠላ የነበረው። ራስህን ነበር ደስታ አልባ በማድረግ። በል እናትህን መበቀል ከፈለክ ደውልላት ከእናትህ ጋር ፍፁም በሆነ ሀሴት አውራ እንዳሳደገችህ ቆጥረህ በየቀኑ ፍቅር አክብሮት ስጣት። እህትህንም ተቀበላት ውደዳት። ከዛ መልሱንና የድርጊትተትን ውጤት ራስህ ታየዋለህ እናትህ በፀፀት ትማቅቃለች። " ምነው ትቼው ባልሄድኩኝ ኖሮ ምናምን እያለች ውስጧ ይከፋል። በቃ ይሄ ለሷ ትልቅ በቀል ነው ይበቃታል ሁሌም ራሷን እየቀጣች ትኖራለች። ሌላው አባትህ በሰላም ያርፋል እሷ በጥላቻ ሁሌ አትጠራውም አትረግመውም አንተም በናፍቆት እሱን ሁሌ እየጠራህና እያስታወስክ አትማቅቅም ይሄ ለሱ ትልቅ ረፍት ነው። ሌላው የአንተ ደስተኝነት ነው። ምን መሰለህ ደስታ ወደኛ የሚመጣው ጥላቻና በቀልን ከአእምሯችን ስናስወጣ ነው። ይህ ካልሆነ በቀር ደስታ በከንቱ አይመጣም። ውስጥህን የጎዳው ሰው ካለ ስለሱ በቀል ነው እንጅ የምታስበው ደስታን ልታስብ አትችልም በዛ ላይ ያን የበቀል አስተሳሰብ አልፎ ደስታ ሊገባ አይችልም እስኪ አሁን አንድ ሰው በጣም ተናዶብህ መጥቶ የሸርሙጣ ልጅ ብሎ ቢሰድብህና ሊደበድብህ ቢጋበዝ የአንተ መልስ ሳቅ እና ፍፁም እርጋታ ከሆነ የሚናደደው እሱ እንጅ አንተ አይደለህም። እንዴት አልመለሰልኝም ብሎ ያብዳል በቃ ሰላም አይሰማውም አንተ ግን ሁለት ነገሮችን አደረግህ አንደኛው የራስህን ደስታ ጠበክ ሁለት እሱን ለስድቡ የሚሆን ተመጣጣኝ በቀል ሰጠኸው ደስታውንም ወሰድክበት በቃ ይሄ ነው እውነታው። ናሆሜ እና በተቻለህ መጠን ያለህን ይዘዝ የተሰጠህን ሳትሰጥ ብትቀጥል ነው የህይወት ማዕዛዋን በፈገግታ የምታሸተው። እንደውም አንድ ፈላስፋ ያለውን ልንገርህ "ህይወት የእጣ ፈንታ ቅንብር ናት!! life is predistined determined by the fet! " ይቺን ንግግር የተናገራት ህይወትን ቀለል ባለ መነፀር የሚያያት ግሪካዊው ፈላስፋ አርስቶትል ነው። ለምሳሌ ህይወት የእጣፈንታ ቅንብር ከሆነች ህይወታችንን commedy አለያም tragedy ብለን ለሁለት እንከፍላቸዋለን ማለትት ነው።በዚህም ሁሉቱም ቴትሮን ዴራን ማለት ሲሆኑ ትርጓሚያቸውም action (ድርጊት ) ማለት ነው። እንግዲህ ህይወታችን የድርጊታችን ውጤት ከሆነች ሕይወታችንን ኮሜዲም ትራጂዲም ማድረግ የምንችለው ራሳችን ነን ማለት ነው! አየህ እኛ የራሳችንን ደስታ አመንጭ ሁነን ሳለ ደስታችንን በሰወች ድርጊት ስለምንጠብቅ ነው ደስተኛ የማንሆነው። እና አንተ ለራስህ እወቅበት ባሩክ ምን አለ ትለኛለህ። እንዲህ ድንገት ስደውልላት ራሱ ካወራችህ በኋላ ብዙ ነገር ነው የምታስበው። እና አንተ ሀሳብህን ሰጥተህ መደሰት ሲገባህ ስለምን ሕይወትህን ከእሬት አምርረህ ትኖራለህ? " አለ ባሩክ ። ናሆም ለደቂቃ ያህል ዝም አለና " ልክ ነህ አደርጋለሁ ግን በጣም ነው የሚከብደኝ እናቴ ያደረገችውን መርሳትና ከስሜቴ ላወጣው የምችል አይመስለኝም። ብቻ አላቅም " አለ ናሆም " ለምሳሌ ቤተክርስቲያን ላይ ስትፀለይ አቤቱ ጌታየ ሆይ ይቅር በለን እኛም የበደሉንን ይቅር እንደምንል ነው የሚባለው ይቅር ባይ ልብ የሚኖረው የእግዚአብሔር ሰው ነው በቀል ግን የሰይጣንነት መገለጫ ነው። በዚህም ክቡር የሆነውን የሰውን ልጅ የሚያስርበት መንገዱ በበቀል ምክንያት ነው ስለዚህ ብልጥ ሁን ወንድሜ። ከሜላት ጋር ደስተኛ መሆን ይኖርብሃል እሷን ልጅ ካጣሀት ደግሞ ይበልጥ ሲቆጭህ ትኖራለህ ሴት ልጅ ለማዳ ናት አንተን የሚያስረሳ ወንድ ካገኘችና የአንተ ኑሮ ተመሳሳይ ሆኖባት አንዴ ሌላ ካየች በቃ አትመለስም። ስለዚህ በደንብ ብትንከባከባት ሌላኛዋ የደስተኝነትህ ምስጢር ትሆናለች። ስለዚህ እሷን በደንብ ጠበቅ አርገህ ያዝ የሚያስፈልግህ የምታፈቅርህ ሜላት ናት!!" አለ ባሩክ "እሱማ ልክ ነህ ሜላት ላይ ያው ባሉብኝ ችግሮች የተነሳ ጨከን አድርጌባታለሁ!!" አለ ናሆም " በቃ ጥሩ እሱን ማወቅህ በቂ ነው።" አለ ባሩክ " እሽ በቃ ያልከኝን በሙሉ አደርጋለሁ ነገውኑ ሁሉንም በየተራ " አለ ናሆም ።ባሩክ በአዎንታ ራሱን አነቃነቀና በፈገግታ አጀበው። ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 64♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ክፍል_62 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ "በል ወንድሜ ሁሉም ነገር ቦታ ይይዛል አንተ አታስብ ይልቅ እኔና አንተ የምናወጋው ነገር አለ ወደ ማታ ብቅ በል " አለ ባሩክ " ስለ ምንድን ነው የምታወራኝ ?" አለ ናሆም " ስለህይወት ማዕዛነት ምን እንደሆነ እናወራለን። ስለ ሕይወት ወጭ ወራጅነት አላፊ አግዳሚነት እንዲሁም ስለገጠመኞቿ እናወጋለን ። ምን የምናወራው የምናጣ ይመስልሀል ? " አለና ባሩክ ሳቅ አለ። ናሆም በባሩክ ፍፁማዊ ፈገግታ ተደሰተና " እሽ በቃ ካልህ " አለውና ወደየዶርማቸው ተለያዩ። መቅደላዊት እንደገባች አልጋዋ ላይ ተዘረረች። የባሩክ ሁኔታ ትዝ አላት ተናደደችና " እሱ ማን ሆኖ ነው ፊት የሚያዞርብኝ!?" አለችና የአልጋዋ ትራስ ላይ ተስፈንጥሮ ያለውን ስልኳን አነሳች! ደወለች ለባሩክ ነበር። ባሩክ ግን ስልክ አያነሳም።ደጋግማ ደወለችለት ነገር ግን አያነሳም ።ይበልጥ ተናደደች። አንድኛው ስሜቷ ደግሞ " ለምንስ ብሎ ያነሳልኛል ከኔ ምን ፈልጎ?"አላት ባሩክ ስልኩን እያየው ዝም አለ በመሀል ጅሜሉን ከፍቶ ኢንቦክሱን መመልከት ጀመረ። የሚገርም ዜና ነበር። ኢሜሉ ላይ ለሶስት አመት ሲፃፃፈው የነበረው የሀርቫርድ ዩኒቨርስቲ ተቀብሎታል። ነገር ግን ይሄን የጀመረውን መጨረስ እንደሚችል እና ተጨማሪ የትምህርት እድል እንደሆነም በመልዕክቱ ይገልፃል። በስሱ ፈገግ አለ። ምን አዲስ ገገር ተገኘ ወንድሜ አለ አንዱ የዶርሙ ጓደኛ " ሃርቫርድ ጥያቄየን ተቀበለኝኮ " አለ ባሩክ ልጁም ብድግ አለና ይሄን ዜና አምብበህ ነው ጌጋ ያልኸው? አለ ልጁ "እና ምን ልበል ምን ላድርግ?"አለ ባሩክ እየሳቀ " አላቅም ብቻ እኔ ብሆን ምድሯ አትበቃኝም ነበር።" አለ " አየህ በአንድ ነገር ከረካህና በጣም ከተደሰትክ ችግር ነው በጭብጨባ ብዛት እንደሚከስም ገጣሚና የኳስ ተጫዋች ነው የምትሆነው! እናም ጊዚያዊ ስኬቶችህ ላይ በመደሰት ጊዜ ከምታባክን ቀጣዩ የአንተ ስራ ላይ ብታተኩር ነው የሚሻለው ። አሁን እኔ ልክ እንደተቀበለኝ ሳይ እዛ ሂጄ ምን አይነት ተማሪ መሆን ይጠበቅብኛል ነው ያልሁት! በዚህም በደነንብ ላስብ ይገባል እንጅ በዚህ ብቻ ተደስቼ ልቆም አይገባም። " አለ በመሀል ስልኩ መልዕክት ተቀበለ። መልዕክቱን አየው ከመቅደላዊት ነበር። " አንተ ስልክ አነሳህ አላነሳህ እኔ ላይ የምታመጣው ተፅዕኖ የለም። እኔ የደወልኩት ለምንም ብየ ሳይሆን ለናሆም የምትናገረውንና እሱን ለማሳመን የምትጥረውን ነገር ብታቆም ይሻልሀል!!" የሚል ነበር። ናሆም በተቀጠረው ስአት አመሻሽ ላይ የባሩክ ዶርም ተገኘ። ባሩክም ጥሩ ስአት አክባሪ ነህ አለ ላፕቶፑን እየዘጋ። ምን ላድርግ ጠሪ አክብሮ ሲጠራ ታዲያ እንግዳ ስለምን ያርፍድ ብየ ነው" አለ ናሆም ። በል ወጣ ብለን ማኪያቶ እየጠጣን እናውራኣ ተመዲያ" አለ። " አሽ ደስ ይለኛል " አለ ናሆም ተያይዘው ወጡ ና ወደ ማለዳ ካፌ አመሩ። ማለዳ ቁጭ ብለው ሁለቱም ወተትና ማኪያቶ አወው እየጠጡ ድንገት ባሩክ " እስኪ ስለ አንተ ንገረኝ ስለቤተሰቦችህ እህት እናት ወንድም አባት ምናምን አጠቃላይ ስለህይወትህ " አለ ባሩክ ማኪያቶውን እያማሰለ። " አይ ባሩክ ምን የሚነገር ታሪክ አለኝ ብለህ ነው ግን እኔ ብቸኛ ልጅ ነኝ አባቴ ነው እናትም አባትም ሆኖ ያሳደገኝ ያስተማረኝ ሁሉ ነገሬ ነገር ግን 12 ኛ ክፍል እያለሁ ነው የሞተው። እናቴ ደግሞ በህይወት አለች ግን ለእኔ ሞታለች አባቴን ገና ህፃን እያለሁ ነበር እኔን ትታለት የጠፋችው አሁን ከሌላ ሰው ጋር ወልዳ ሴት ልጅ አለች አባቴ እንደሞተ ነው እሷ የመጣችው። አለም ላይ እንደ እናቴ የምጠላው የለም!በሷ የተነሳ ነው መሰል እህቴንም አልወዳትም በቃ ሁሉም ያኔገፈግፉኛል እዚህ የምማረው የአባቴን ህልም እውን ለማድረግ ነው። " አለ ና እምባው ቁርዝዝ አለ። " በቃ እሽ ተወው ይቅርታ ርዕስ እንቀይር መሰል " አለ ባሩክ ዳሩ ግን ርዕስ ለመቀየር ፈልጎ ሳይሆን ችግር የለውም እንዲለው ነበር የፈለገው እንደፈለገውም " ኧረ ችግር የለውም "አለ ናሆም ። " እሽ እኔ ኮ መጥፎ ትዝታ ላይ ስለጨመርኩህ ብየ ነው።" አለ ባሩክ " አወ መጥፎ ትዝታ ነው በርግጥ ግን አንተ አስታወስከኝም አላስታወስከኝም ይሄን ታሪክ ሁሌም ነው የማስታውሰው አባቴ በየቀኑ ይመጣብኛል እናቴ ደግሞ ትላንት መጥታ ከሀዘንህ ላስወጣህ ትለኛለች ።እሷን ደግሞ እጠላታለሁ በውል እንኳ እንጀራ መቅመስ ሳልጀምር ትታኝ ሄዳ ልትናገረኝ ያምራታል! እንዲህ ነው እንግዲህና እንዲህ እያለ ነው የሚቀጥለው የኔ ታሪክ" አለ ናሆም። " እሽ ናሆም እንግዲያውስ ጥሩ እና እናትህን መበቀል ትፈልጋለህ?" አለ ባሩክ " አዎ " አለ " አባትህስ በሰላም እንዲያርፍ ትፈልጋለህ ?" አለ በድጋሚ ባሩክ ናሆም በድጋሚ አወ አለ ባሩክ ለሶስተኛ ጊዜ አንተስ ደስተኛ መሆን ትፈልጋለህ? ኡ ናሆምም አወ አለ " እንግዲያውስ ለሶስቱም ጥያቄወች መሰረታዊ እና እውነታዊ ማብራሪያ ልሰጥህ ነው!! በደንብ አድምጠኝ።" አለ ባሩክ " እሽ ደስ ይለኛል " አለ ናሆም ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 63♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ክፍል_61 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ባሩክ አስፓልቱን ሲዞር ከቆየ በኋላ በፊታውራሪ ገበየሁ ህንፃ አድርጎ ወደ ዶርሙ ገባ። አልጋው ላይ ተንጋሎ አይኖቹን ከደነ ትንሽ ከቆየ በኋላ ደግሞ ገለጣቸው ወዲያ ወዲህ ቢገላበጥ እንቅልፍ ሳይወስደው ሌሊቱ አለፈ በዚህ ጊዜ ተነስቶ የሌሊት ልብሱን ለብሶ ከዶርሙ ፊት ለፊት ካለው የመንገድ ዳር ዛፍ ስር ተቀመጠ። ከላይ ቱታ ጃኬት ከታች ቱታ ሱሪ ቶርሽን ጫማ ተጫምቶ ወደ ቤታቸው የሚሄዱትን ተማሪወች ይመለከታል ። ናታኔም በጠዋት ሻንጣውን ይዞ ወጣ የዩኒቨርስቲው በር አቢሲኒያ ባስ ተሳፋሪዎችን እየጠበቀ ነበር። የዩኒቨርስቲው በር በፍተሻ ተጨናንቋል መቅደላዊት ናታኔምን ሸኘችው። ናሆምም አብሮት ነበር በመጨረሻ ቸው ተባብለው መቅደላዊትና ናሆም አብረው ተመለሱ " እሽ ትኩስ ፍቅረኛሞች ሆናችኋል?!" አለና ናሆም የለበጣ ፈገግታውን ሰጣት" ምን ማለት ነው ናታኔምን በጣም እወደዋለሁኮ ከባሩክ በፊት እሱን ነው የማውቀው!" አለች " እንዴት ነው የምትተዋወቁት?" አለ ናሆም ጀሮወን በደንብ እየሰጣት " በሆነ ነገር ተግባባን ከዛ በኋላ አብረን ብዙ ጊዜ እናሳልፍ ነበር!" አለች ትዝ ብሏት " እህህህህህ" አለ ናሆም ናታኔም ብዙም አንተዋወቅም ያለው ነገር ትዝ ብሎት " እና ብዙ ጊዚያችሁ ነዋ ?" አለ በአወንታ ራሷን ነቀነቀች ናሆም በፈገግታ ራሱን አወዛወዘ " እና ስለ ባሩክ ምን አሰብሽ?" አለ " ምን ላስብ እችላለሁ? እሱ እኮ ድብቅ ነው። በዛ ላይ አስመሳይ አንተ ለካ ናሆም መጀመሪያ ነበር እንደሚያፈቅረኝ የነገረው እሱ ደብቆ ዝም አለ " " ምን ማለት ነው ቀድሞ ነው የነገረው ?" ደግሞ ጠየቃት " በቃ ናታኔም እንደሚወደኝ ነዋ " አለች" ናሆም ምን ለማለት እንደፈለግሽ ባይገባኝም ነገር ግን ለባሩክ የነገርኩት እኔ ነኝ ናታኔም እናንተ ከተማ ለእራት ወጥታችሁ እያለ ነው የነገረኝ ከዛ በኋላ ነው። እኔም በድንገት ባሩክ መንገድ ላይ አግኝቶኝ ስለ ናታኔም ባህሪ መቀየር ሲጠይቀኝ የነገርሁት በስአቱም የደነገጠውን ድንጋጤ እኔ ነኝ የማቀው።ስለዚህ እኔ በግሌ መጀመሪያ ነው ናታኔም የነገረው ብትይኝ አላምንሽም። ምክንያት ደግሞ በጥልቀት እንኳ ባላቀው ባሩክ መልካም ልጅና ቅን የእውነት ሰው ነው።" አለ " ባክህ ባነበባቸው የውሸት ድርሰቶች ተንተርሶ እሱን ማወቅ ይከብዳል ። ደግሞ ምንም ያለኝ ነገር የለም " አለች መቅደላዊት " አላቅም ለምን ዝም እንዳለሽ ግን ዝምታ ትልቅ ሀይል እንደሆነ አቃለሁ ዝምታ ትልቅ ተቃውሞ ነው። ሀሳብሽን በዝምታው እየኮነነው ሊሆን ይችላል።" አለ ። መቅደላዊት አፏን አጨራመመች ። ናሆምና መቅደላዊት እያወሩ እየሄዱ ሳለ ድንገት መቅደላዊት እያወራች ወደ ጎን ስታይ ባሩክን ተመለከተችው።አይኗን ሰበር አደረገችና " ናሆም ናሆም አየኸው ባሩክን " አለች ናሆም ባሩክን ተመለከተ አንገቱን ከተቀመጠበት ዛፍ ቅርንጫፍ መዝዞ በተመስጦ እየተመለከተ ቆይቶ ዝቅ ሲል መቅደላዊትን ስታየው ያያታል! ከተቀመጠበት ተነስቶ ወደ ብሎኩ አቅጣጫ በዝግታ ተራመደ። ናሆም የባሩክ ድርጊት ገብቶታል ለምን እንደዛ እንዳረገ አውቋል። መቅደላዊት ኮስተር አለችና " ከሱ ብሶ ጭራሽ ጀርባውን ይሰጣል የማያፍር። ለነገሩ እሱ አየኝ አላየኝ ምን ይሰራልኛል።" አለች ናሆም ሳቅ አለና " በቃ ወደዶርም ሂጅ እኔም ልግባ " አለ ናሆም " ትንሽ አንጫወትም?" አለች " አይ ዶርም ገብቼ ማሰብ እፈልጋለሁ " አለ እና ሰላም ብሏት ሄደ። ናሆም ፈጠን ፈጠን ብሎ ተራመደና ባሩክ ላይ ደረሰበት " እንዴት ነህ ወንድሜ " አለ ናሆም " ደህና ነኝ አንተ ምስኪን ልጅ እንዴት ነህ " አለ ባሩክ ፍፁም በሆነ ፈገግታ " ለምን ምስኪን አልከኝ?" አለ ናሆም በመገረም " ያው ልቤ ምስኪን ነው ብሎ አፌ ላይ አወጣው " አለ ባሩክ " እሽ እንግዲህ ቅድም ኮ ናታኔምን ሸኝተን እየተመለስን ነው ያየኸን" አለ ናሆም " ለምን ይሄን ትነግረኛለህ?" አለ " አይ እንዲሁ ነው ቅድም ባደረከው ነገር ላይ ትንሽ ላናግርህ ብየ ነው! " አለ " ስለምን ልታናግረኝ አስበህ ይሆን ናሆም?" አለ ባሩክ " ምን መሰለህ ባሩክ መቅደላዊትን በጣም ስለ አንተ ዋሽቶ ጭንቅላቷን ሳይመርዘው አይቀርም?" አለ ናሆም ባሩክ ንግግሩን አቋረጠውና " እውነትም ምስኪን መሆንህን አሁን አረጋገጥሁ በድጋሚ ልበልህ አንተ ምስኪን ልጅ ሰው በሰው ንግግርና አስተሳሰብ አይመረዝም የሚመረዘው በራሱ የውስጥ ባህሪ ነው።!!! አንድ ምክር ልምከርህ እኔ በምኖረው አለም ደስተኛ ነኝ መቅደላዊት እንደዛሆነች አለሆነች እኔ ሕይወት ላይ የምትጨምረው የምትቀንሰው ነገር የለም ደግሞ የእኔና የሷ ታሪክ የሚፃፍም የሚነገርም የለንም በቃ የአንድ ቀን የወሲብ አዳር ነው ጠዋት ላይ በቃ አለቀ እሱ ነው ግንኙነታችንን እንደዛ አድርገህ ውሰደው። ነገር ግን እኔ በሷ ሌሎቹን ንፁሀን ሔዋኖችን ልኮንናቸው ሀሳቡም ስሜቱም የለኝም። አሁንም ለሴት ልጅ ክብር አለኝ። እንጅ በሷ ድርጊት እናቴን እህቴን ምናምን ከጠላሁማ ምኑን ጤናማ አመለካከት ኖረኝ።?" አለ ። ናሆም ራሱን ነቀነቀ። ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 62♥️ ነገ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

📚መቅደላዊት📚 እንዴት አቀራረቡን ወዳችሁታል? ወዳጆቻቹንም ወደዚህ ቻናል እየጋበዛችሁ። ለአስተያየት @mark_sistu ይጠቀሙ

#መቅደላዊት #ክፍል_60 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ " ይህ ነገር ለሌላ ምዕራፍ ፋኖስ እንደሆነ ብቻ ላስብ። መቅደላዊት አሁን ከልቧ ሳትሆን ከስሜቷ ነች ወይም ከልቧም ልትሆን ትችላለች። አሁን በማንም እርግጠኛ ልሆን አልችልም በራሴ ግን ርግጠኛ ልሁን መንገዴን መራመድ አለብኝ በዝግታ፣በፍጥነት ፣ በቻልሁት አቅም አሁን ትላንትን እያሰብሁ እየቆዘምሁ ልቅመጥ አልችልም ዛሬ በዛሬ ሀሳብ እንጅ በትላንት ሀሳብ አይመራም።" አለ ና ወደ ዋርካው ወረዳ" የዘመናት ጥላ የአድዋ ዩኒቨርሲቲ አጋፋሪ ግዙፉ ገብርየ ዋርካ " ወረደና ከአንደኛው እምነበረድ መቀመጫ ተቀመጠ። ትንሽ ካሰበና ከተረጋጋ በኋላ ተነስቶ አስፓልቱን ይዞ ወክ እያደረገ ነው። ግራ ቀኝ የተገጠሙት ባውዛወች አስፓልቱን ብቻ ሳይሆን ከአስፓልቱ ራቅ ብለው የተሰሩትን ህንፃወች በፀሀይ መልክ አድምቋቸዋል። ዝም ብሎ ጉዞውን ቀጠለ። መንገድ ላይ ናሆምን አገኘው ናሆም ሰፍ ብሎ " ባሩክ " አለ " ዝም ብሎቶ መንገዱን ቀጠለ ናሆም ተከትሎ ከኋላው ጎተተውና" እየጠራውህ ነበርኮ" አለ ባሩክ ናሆምን ከተመለከተ በኋላ " ይሆናል ነገር ግን አልሰማውህም " አለ ግን ደህና ነህ?" አለ ናሆም " ደህና ነኝ ወንድሜ ምንም አታስብ " አለ ናሆም ልጠይቅ አልጠይቀው ብሎ ካመነታ በኋላ "ናታኔምን አገኘኸው?" አለ " ማግኘት አልፈልግም" አለ ባሩክ ኮስተር ብሎ" እሽ ይቅርታ እኔ ቅድም በተደጋጋሚ ስትደውልልለት አጠገቤ ስለነበር ነው። " ምን አለህ " አለ ባሩክ " ምንም ለምን እንዳያነሳ ስጠይቀው ዝም ብሎ ነው እያስፈራራኝ ሊያስፈራራኝ ነው ምናምን ሲለኝ በምንድነው የሚያስፈራራህ ብየ መልሼ ስጠይቀው አልመለሰልኝም ከዛ መቅደላዊት ደወለችልኝ ስለሁሉም ነገርኋት አንተ እንደምታቅም ጭምር።" አለ " ሁሉንም አውቂያለሁ ደውላልኝ ነበር ራሷ አውርታ ራሷ ጨርሳ ዘጋች" አለውና ባሩክ ትቶት ሄደ ።ናሆም የጥፋተኝነት ስሜት ተሰማው " በጣም ይቅርታ እሽ " አለ " ችግር የለውም አንተ ኮ ውሸት አለተናገርህም ለምን ቅር ይልሀል?" በል አታስብ እንደውም በመናገርህ ላመሰግንህ ይገባል በል ትንሽ ልንቀሳቀስ አለና አሁንም ርምጃውን ቀጠለ ።ናሆም በአይኑ ተከተለው ።ባሩክ ከልቡ አሳዘነው። መቅደላዊት ና ናታኔም የመጀመሪያ ህንፃ የመማሪያ ክፍል ማለፊያ ታች ላይ ከተሰራው የመንገድ ግምብ ስር ተገናኙ። ናታኔም ዝም አለ መቅደላዊት በስስት ተመለከተችውና " ለምንድነው መጀመሪያ ያልነገርከኝ ይህ ሁሉ አይፈጠርም ነበር ባሩክ ጋም ምንም ነገር አይፈጠርም ነበር" አለች ለእሱ ኮ ከመጀመሪያው ነግሬዋለሁ እንደማፈቅርሽ በጣም እንደምወድሽ ነገርኩት። ወደ ከተማ ከመሄዳችሁ በፊት ሁሉንም ነገር ነገሬዋለሁ ስለ አንቺ ያለኝን ስሜት " አለ መቅደላዊት ተናደደች " ይሄን ሁሉ እያወቀ ነበር ዝም ያለኝ ምንም እኮ ያለኝ ነገር የለም " አለች " ምንም እንዳላለሽ እርግጠኛ ነበርሁ ባሩክ በጣም ከባድ ልጅ ነው ሰፈር ውስጥም እንደዚሁ በውሸት ማንነት አንዲትን ልጅ ጓደኛው አድርጎ ጎድቷታል እሱ ከፍላጎቱ ውጪ ሌላ ማንንም አይሰማም በጭራሽ ከስሜቱ ውጪ ሌላ አያዳምጥም።" አለ " የሚገርም ነው እኔ እኮ እንዲህ አይመስለኝም ሲበዛ አስተዋይና ገራገር ነበር የሚመስለኝ ለካ ይሄ ጭምብል ማንነቱ ነበር" አለች ። "አወ ምን ማድረግ እንዳለበት ጠንቅቆ ያውቃል ምክንያቱም ብዙ ስለሚያነብ" አለ "መቅደላዊት በግርምት ራሷን ወዘወዘች። "ፍቅር በማስመሰል አይኖርም ፍቅር ልክ እንደ እውነት ነው በውሸት የሚሆን ነገር የለም አንድ ቀን እውነት መውጣቷ አይቀርም። ነገር ግን እሱ ይሄን አላወቀም" አለ " ልክ ነህ እኔ ከእሱ አንተን ነው የማቀው ጓደኛየ ጋር ተጣልተን በቆየሁበት ጊዜ ያፅናናኸኝ አንተ ቅንነትህን በጣም ነው የምወድልህ ።እርግጥ ነው የባሩክ ጊዚያዊ መውደድና ውለታ ተጨማምረውብኝ ነው።ገና ያኔ ክበባት መንደር ላይ ሆነን ስለ ናሆም ያለህን ሀሳብ ስትነግረኝ የወደድሁህ" አለች ናታኔም ጉንጯን ሳማትና አቀፋት "የማጣሽ መስሎኝ ተጎድቼ ነበር ሁሉም ነገር በአንድ ጊዜ ሆነብኝ በቃ ዱብዳ ሆነብኝ አንቺን ከባሩክ ጋር ማሰቡ አሳመመኝ! ራሴን ጠላሁ ጮክ ብየ አለቀስኩ ግን ይሄው ፈጣሪያ ለቅሶየን ሰማ አንቺን ሰጠኝ አመሰግነዋለሁ።ከዚህ በኋላ ምንም ገገር ሊለየን አይችልም። " አለ " መቅደላዊት ዝም አለችልቧ በፍርሃት ሲርድ ተሰማት ምን እያደረገች እንደሆነ አሰበች አወ ሌላ ጠረን ሌላ ሰው ነው ናታኔም ወደረቱ ተጠጋች ከባሩክ የለየ ማዕዛ ነፍስን የሚያረቅ ልዩ ሽታ ሸተታት ናታኔምን በድጋሚ አየችው። ምልሳ ደረቱ ላይ ተለጠፈች።" ግን ባሩክ በጣም ይጎዳል " አለች ናታኔም በረጅሙ ሳቀና " ባሩክ ነው የሚጎዳው ወይ ሰው አለማወቅ በጭራሽ ልቡ አለት ነው ለማንም ቢሆን አይከፈልም " አለ " በሆነ " አለች "አታስቢ አሁን ተይው በቃ አብረን ነን ግን እንደምትወጂኝ ለምን አልነገርሽኝም አንቺስ?" አለ ።"ልነግርህ እያሰብሁ ነገሮች ተደራረቡ ያ የፈተና አጋጣሚ መጥቶ ሁሉንም ቀየረው ቅዠት የሚመስለው እውነት እና የባሩክ ውለታ ሁሉንም ቀየረው።" አለች ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 61♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ክፍል_59 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ " በሰላም ነው ስልክ የዘጋሽው ደግሜም እኮ ደውየልሽ ነበር?" አለ ናሆም " ግን ናሆም ከምርህ ነው?" አለች መቅደላዊት ሳግ እየተናነቃት " አወ ናታኔም ባለፉት ቀናት ብዙ ነገር ሆኗል ከራሱ ጋ አልነበረም እጅግ ተጎድቷል። በጣም ሁሉም ነገር በድንገት ነው የሆነበት ናታኔም በጣም ጠንካራ ልጅ ነበር አስከማቀው። ጥንካሬው ሸሸ አንቺን ብቻ እያሰበ አለቀሰ ከሁሉም ደግሞ ያሳመመው ከባሩክ ጋር ሆነሽ ስላየሽ ነው ከባሩክ ጋር የተፈጠረውን በሙሉ ደርሶበታል " አለና ዝም አለ " ይሄን ሁሉ ሲያውቅ እኔ ምን ሆኜ ነው ያልሰማሁት?" አለች " አላውቅም ባሩክ ግን ያውቃል ለና" አቋረጠችው " ባሩክ ያውቃል?" ደግማ ጠየቀችው " እኔ ነኝ የነገርኩት " አለ መቅደላዊት" ይቅርታ አንዴ አለችና ስልኩን አቋረጠችው። ባሩክ የድብርትን ፅዋ ከፍ አድርጎ ከምሽቱ ጨለማ ጋር ይነጋገራል። ከድቅድቁ ጨለማ ምድር ከፍ ብላ መሀል ሰማይ ላይ የወጣችው ጨረቃ ምድርን በብርሀን ለመሙላት በግማሽ አካሏ ትጥራለች። ከምዕራብ ወደ ምስራቅ የሚነፍሰው ነፋስ ዛፎቹን በስስት ወዲያና ወዲህ ያወዛውዛቸዋል። ባሩክ የመጨረሻ ፈገግ አለ የማይናገረው ተፈጥሮ ያሳቀው መሰለ አይኖቹን ከሚቅለሰለሱት ዛፎች ላይ አልነቀለም። አይኖቹን ቀስ አድርጎ ከደናቸውና ትንፋሹን ወደ ውስጥ ሳብ አደረገና በሉ እናንተ የምታወጡትን አየር ተቀብያለሁ አሁን ደግሞ የእኔን ንፁህ ያልሆነ አየር ታስገቡ ዘንድ ህይወት ታስገድዳችኋለች!" አለና እኔ ከራሴ ጋር ተፋልሚያለሁ ሁሉንም ነገር ለማሻሻል ለመቀየር ጥሪያለሁ ዳሩ ግን መልካም ምላሽ አይደለም የጠበቀኝ። ህይወት እንደወሰንኩላት ሳይሆን በወሰነችልኝ ልትመራኝ ትሻለች ይሄን ደግሞ እናንተ ልትቃወሙ ይገባል።" አለ በመሀል እያወራ ሳለ አንድ ጊዜ ስልኩ ጠርቶ ሳያነሳው ጥሪው አለቀ በድጋሚ ተደወለ አሁንም ንግግሩን ከአእዋፋት ጩኸት ከእፀዋት ዝማሜ ላይ አደረገ ።ለሶስተኛ ጊዜ ስልኩ ሲጠራ ስልኩን ከኪሱ አወጣው መቅደላዊት ነበረች " አቤት መቅዲ " አለ " ለምንድን ነው ናታኔም እንደሚያፈቅረኝ ያልነገርከኝ በሱ ለቅሶ ነበር ስትደሰት የነበረው? ምን ቢያደርግህ ነው! እኔ እንደዚህ እንደምታደርግ እንኳን ላስብ አልቃዥም ሁሉ ። ደግሞ ምንም ነገር ሳላውቅ ደውይለት ብለህ ይባስ በሱም በኔም ተሳለክብን ቆይ እስኪ ንገረኝ ምን አስበህ ነው?ደውይለት ያልከኝ?" አለች ባሩክ ዝም ብሎ ያዳምጣት ነበር " ንገረኝ " በጣም ጮኸች አልመለሰላትም " ለነገሩ ምን ልትመልስልኝ ትችላለህ ምን የምትመልሰው ይኖርሀል አፍህን ሞልተህስ ምን ልትል? ብትልስ የአንተን የፈጠራ መልስ ማን ሊያምን? ስላመንኩህ እንዴት እንደዚህ ታደርጋለህ ስልኩን ጀሮው ላይ ዘጋችበት። መቅደላዊት አራስ ነብር ሆነች ባሩክኝ እጅግ አድርጋ ተፀየፈችው። ባሩክ ሰማይና ምድሩ ተቀላቀለበት ራሱን በደንብ ጭምቆ ያዘ ግራ ግብት ሲለው ። እጆቹ ተንቀጠቀጡ እግሮቹ ብርክርክ አሉ ። ቀስ ብሎ ዛፉ ስር ተቀመጠ። ድንጋዋን ብድግ ጣል ቆፈር ቆፈር አደረገና አንዲት ትንሽየ ቀዳዳ በትንሽ ድንጋይ ቆፈረ አይኖቹ ሳያስበው እምባ ጥለው ከጉድጓዷ ላይ አረፉ ባሩክ እምባው ቶሎ አለመድረቋን አይቶ ሳቅ አለና ፊቱን ጠረገ። መቅደላዊት ለናታኔም ደወለችለት ናታኔም አያነሳም ደግማ ደወለችለት አሁንም አያነሳም በመጨረሻ መልዕክት ላከችለት። " ናቲ እባክህን ስልክህን አንሳ ምንም የማቀው ነገር አልነበረም ባሩክም አውቆ ደብቆኝ ነው ቅድም ስደውልልህ የነበረው ደውይለት ስላለኝ ብቻ እንጅ ምንም የማቀው ነገር አልነበረም ።ስለዚህ አሁን ማውራት ይኖርብናል እባክህ" ብላ መልዕክት ላከችለት ።ናታኔም መልዕክቱን እንዳየው" ጥሩ " በደስታ ነዋ የማገኝሽ አንቺ የእኔ ብቻ ነው የምትሆኚው የቻልኩትን አደርጋለሁ።" አለ እና ዝም አለ ። ከትንሽ ደቂቃ በኋላ ደወለችለት በሶስተኛው ጥሪ ስልኩን አነሳው። " ናቲ " አለች "ወይዬ" አለ " ምንም የማቀው ነገር አልነበረም እሽ ይቅርታ አድርግልኝ አሁንም የሰማሁት ከናሆም ነው።" አለች " አውቃለሁ ችግር የለውም ብታውቂ አንቺን አውቅሻለሁ። ባሩክ ነው ምንም እንዳታቂ የፈለገው ምክንያቱም ካወቅሽ እሱን ልተይው እና እኔን ልትመርጭ እንደምትችይ ስላሰበ ነው" አለ " እሱን ተወውና አሁኑኑ ላገኝህ እፈልጋለሁ " " እሽ ልብሴን እያስተካከልኩ ነበር በቃ መጣሁ የተለመደው ቦታ እንገናኝ " አለ " እሽ ወጣሁኝ " አለች። ናታኔም በኩራት በአሸናፊነት መንፈስ ሳቅ አለ። ወደ ሎከሩ መስታውት ፊቱን አስጥቶ ራሱን እየተመለከተ " አገኘውህ ባሩክ " አለ " ልክ አርኪመደስ ገንዳው ላይ ሲወጣ በሱ ሚዛን ልክ ውሀው ሲፈስ ተገለጦለት "እዮሪካ እዮሪካ " ብሎ እንዳስቦረቀው ሚስጥር ናታኔም በትንሽ የምድር ከፍታ በሀሴት ዘለለ። ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 60♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ክፍል_58 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ናታኔም ይበልጥ ተርበተበተ " በቃ ምንም ዝም ብሎ የሌለ ነገር ፈጥሮ ነው የሚያስፈራራኝ " አለ በልቡ መልዕክቱን እንዳያይበት እየፀለየ። " ለምን ያስፈራራሀል ምን እንዳታደርግ ምን እንዳትናገርበት?" ናሆም አከታትሎ ጠየቀው። " በቃ ናሆም በናትህ አታስጨንቀኝ ልታፅናናኝ ነው? ልታስጨንቀኝ? የመጣኸው!" አለ ናታኔም " አይ ለምን አስጨንቅሀለሁ የሚያስጨንቅ ነገርኮ አልተናገርሁም። መጠየቄ ስህተት ከነበር ይቅርታ ግን ነገሮችን ራስህ አወሳሰብክብኝ እኔ እስከማቀው ። አንድ ሰው ሌላኛውን ሰው ሊያስፈራራው ከፈለገ ያሰው የሰራው ያደረገው ድብቅ ነገር አለ ማለት ነው። ስለዚህ አንተን ሊያስፈራራህ ከፈለገ የሆነ ነገር አድርገሀል ማለት ነው ያ ነገር ምንድነው ?" አለ ናሆም ፊቱን እያኮሳተረ።ናታኔምም የናሆምን ፊት ገርመም አደረገና እሱም ፊቱን አደመነው! " ምንም ሳያደርግ እኮ ሰው አድርጓል ተብሎ ይከሰሳል።ያ ሰውም ኮ ምንም ታሪክ ሊለጥፍበት ይችላል። ባላደረገው ነገር ሊከሰስ ይችላል " አለና ለናሆም የፅልመት ፊት የፅልመት መልስ ሰጠና በቃ እኔ እሄዳለሁ ልሄድ ነው " አለ ናታኔም "እሽ በቃ ጥሩ ብቻ ለነገሮች እጅ አትስጥ በብልሀትና በትዕግሥት በአስተውሎት ነገሮችን እለፍ። እንደኔ ደግሞ ባሩክን አግኝተህ ያለብህን ችግር ብትፈታ መልካም ይመስለኛል።" አለ ናሆም ናታኔም ሄደ። ናሆም በጥርጣሬና በአዘኔታ ተመለከተው እግሮቹን ተከትሎ አብሮት ነጎደ። ናሆም ስልኩ ጠራ አወጣው መቅደላዊት ነበረች። እጁን እያወዛወዘ አነሳው። " ናሆም ደህና ነህ?" አለች በተረጋጋ ድምፅ " ደህና ለመሆን እየሞከርኩ ነበር ግን ደህና ሰው ጠፋ ሁሉም በችግሩ ላይ ችግር ጨምሮ ነው የሚመጣው። እኔም የጥሩ ግራ አጋቢ ታሪኮች ሰለባ ሆኛለሁ" አለ " ምነው ምን ሆንክ ግራ አታጋባኛ እኔንም ምን ተፈጥሮ ነው!?" አለች "የአንቺና የባሩክ ፍቅር አንዱ ነው!!" አለ "ማን ነገረህ?" " ተጎጅው ነዋ " " ማለት የምን ተጎጅ ነው ማነው እሱ ?" " አላወቅሽውም?" " እንዴ እኔ እንዴት ባውቀው እጠይቅሃለሁ ናሆም?" " በረጅሙ ሳበ እንግዲያውስ ይቅርብሽ ደስታሽን የሚያደፈርስብሽ ይመስለኛል አንቺ ደስተኛ መሆህ ይገባሻል። በጣም ብዙ ረጀም መንገዶችን በፅናት ተጉዘሽ እዚህ ደርሰሻል። ብዙ መከራ አልፈሻል ያለ አባት አይዞሽ ደስታ እንዲህ በስተመጨረሻም ቢሆን ትፈነድቃለች ወቅቷን ጠብቃ ልክ እንደ መስከረም አደይ " አለ " እሱ ልክ ነህ ናሆም ግን ማን እንደሆነ እኮ አልነገርኸኝም?" አለች " አዎ አልነገርኩሽም እኔኮ ምን ያደርግልሻል ብየ ነው? እውነቴን ነው ብነግርሽ ይከፋሻል በድጋሚ ከዛ ደባሪ ጊዜሽ ጋ ትቀላቀያለሽ!!! " አለ " እንዴ አሁን እኮ ነገርኸኝ ከሚደርስብኝ ችግር በላይ ሳትነግረኝ ቀርተህ የሚደርስብኝ ችግር ይበልጣል። ምክንያቱም ማን ይሆን እያልሁ ሁሌም አስባለሁ። እሱ እኔን ሲያይ ምን እንደሚሰማው ሳስብ ያመኛል። በእኔ ፍቅር የሚሰቃይ ሰው መኖሩን ሳስብ ይበልጥ እረበሻለሁ። በዛ ላይ በልጁ ላይ አንተ ይሄን ያህል ከተሰማህ ከበድ ነው እና ከቻልህ ነግረኸኝ ህመሜን ብታቀልልኝ ደስ ይለኛል " አለች መቅደላዊት። " እውነት መስማቱ ይሄን ያህል ሰላም ይሰጥሻል?" አለ ናሆም " በትክክል ምን ጥርጥር አለው ናሆም ልጁ በጣም የተጎዳ ልጅ ከሆነም ትሪት ላደርገው ይገባል። እሱን ማድረግ ደግሞ ከምንም በላይ የኔ ግዴታ ነው። ማንም ሰው በእኔ ምክንያት እንዲጎዳ አልፈልግም።" አለች " እሽ እንግዲያውስ የሚያፈቅርሽ ልጅ አንቺን ብዙ የማትግባቢው ልጅ በእኔ ግምት አንድ ሁለት ጊዜ ያገኘሽው ልጅ ይመስለኛል። እሱ ልጅ ደግሞ... ብሎ ትንሽ ዝም አለ " እህ ደግሞ ቀጥል እንጅ ዝም አልክ?" አለች መቅደላዊት "ዝም አላልኩም ለመጨረሻ ጊዜ ከመናገሬ በፊት እያሰብኹ ነው!" አለ " እሽ አሁን አስበህ ከጨረስክ ንገረኛ " አለች " ናታኔም ነው " አለ ናሆም መቅደላዊት ፀጥ አለች ስልኩ ተቋረጠ። ናሆም በድጋሚ ደወለ አታነሳም!" አሁን የሆነ ነገር አለ። ናታኔምን ብዙ ጊዜ ታገኘዋለች ይገናኛሉ ማለት ነው። ባይሆን ኖሮ እንደዚህ እንጨት አትሆንም ነበር። ድብቅ አጀንዳማ አለ። አሁን ደግሞ ስለ ናታኔም ስሜት ባሩክን ላናገረውና የተወሰነ ፍንጭ ላግኝ ።የናታኔምን ጓደኛንም መርዕድንም ላናግረው ይገባል። ሁሉንም ነገር ላውቀው ግድ ነው።" አለና መንገዱን ቀጠለ ። በመንገድ እየተራመደ ሳለ ስልኩን በድጋሚ አወጣና ለመቅደላዊት ደወለ። ነገር ግን መቅደላዊት ስልክ አታነሳም። የምሽቱ ጨለማ ለአይን እየነሳ ነው ጊቢ ውስጥ የሚርመሰመሰው የተማሪ ቁጥር ቀንሷል። አብዝሀኛው በአዳሪ ተጉዟል ። በዓሉን ለመታደም የመጡት የሀገር ውስጥ ዜጎች ና የውጭ ሀገር ዜጎች ጉብኝታቸውን አጠናቀው ተመልሰዋል!!!! መቅደላዊት ከነበረችበት የህልም አለም ስትነቃ የቀኝ እጇን አውራ ጣት ከናሆም የስልክ ቁጥር ላይ አገኘችው። የሰማችውን ላለማመን በድጋሚ አውራ ጣቷን ተጫነችው ።ከወዲያኛው ጫፍ ናሆም ስልኩን አነሳው። ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 59♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ክፍል_57 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ " እሽ ናቲ አሁን እንዴት ነህ?" አለ ናሆም ገና እንደደረሰ ሰላምታ ከማቅረቡ በፊት " ደህና ነኝ ምንም አልልም " አለ። " በጣም የተጨነክ ትመስላለህ! " አለ ናሆም " እንዴት አልጨነቅ ሁሉም ነገር ተወሳስቦብኝ , ቆይ ምን ብየ ልንገረው። ስለ ባሩክ መጥፎነት ምን ብለው ከመቅደላዊት ጋር እንዲለያዩ ያግዘኛል? " እያለ በሆዱ ሲያጉተመትም " ባሩክ ጋር ተገናኝታችኋል?" ብሎ ናሆም ዝምታውን ሰበረው። " አይ እሱን ማግኘት አልፈልግም በምን እንዳወቀ ደግሞ አላውቅም።" አለ ናታኔም " እንደ ስኔ እንደ እኔ ባሩክን ብታማክረው የተሻለ መፍተሔ ታገኛለህ። "አለ ናሆም " እንዴት ነው የምታስበው ከማፈቅራት ልጅ ጋር አብሮ ያደረን ሰው ለእኔ ማፍቀር መፍትሔ እንዲሰጠኝ የማማክረው። እንዴት ነው የምታስበው? ይሄንማ ሞቼም አላደርገውም። " አለ ናሆም ከንፈሩን እያሸራመጠ ምንድን ነው የምትለኝ? መቅደላዊት ጋር ግንኙነት ጀምረዋል እያልከኝ ነው?" አለ " አወና እሷ ገና ለገና ያነን መምህር ተጋፈጠልኝ ብላ አፈቀርኩት አለች።" ግን አንተ እና እሷ በምንድነው የምትተዋወቁት?" አለ ናሆም " በአንተ ነዋ!" አለ ናታኔም " ምን? በአንተ ማለት?" አለ ናሆም ያው የሆነ ጊዜ እሷን አግኝተሀት ለአንተ በነገረችህን ታሪክ ለእኔና ባሩክም አጫወተችንና ከዛ በኋላ ታሳዝነኛለች። ከዛ በኋላ እየተዋወቅን በደንብ ስንመጣ ፀባይዋ በጣም የሚገርም ነው። በዛ ላይ አንድ የምታፈቅረው ልጅ ከአገር ቤት አስከፍቷት ነበር ያኔ እኔ ጋር ተገናኝተን አወራን ስለ ሁሉም ነገር አጫወተችኝ። በጣም ነው የምታሳዝነው ህይወቷ በፈተና የተሞላ ነው። በዚህ ምክንያት ነው።ከዛ በኋላ በየቀኑ እንገናኛለን ብዙ ነገሮችን አብረን እንጫወታለን ። ነፃነት እንዲሰማኝ ታደርገኛለች ቀስ በቀስ በልቤ እያስቀመጥኋት ሄድኩ።" አለና ትንፍስ ብሎ ዝም አለ።" እና እኔ ያልገባኝ አንተ እንደምታፈቅራት እያወቀ ባሩክ እንዴት እንደዚህ ያደርጋል። አብሮ አደግና ከአኔድ ሰፈር ናችሁ። " አለ ናሆም " ባሩክ የመሰለውንና የሚፈልገውን ያሰኘውን ከማድረግ ወደ ኋላ አይልም እንኳን የእኔን ዘመዱ ያልሆንኩትን የእናቱን ልጅ ፍቅረኛ የአጎቱን ልጅ ፍቅረኛ የማይምር ሰው ነው።" አለ ናታኔም " እና የወንድሙን ፍቅረኛ አውጥቷል እያልከኝ ነው?" አለ ናሆም " አወ ልጅቱ ይመቻት ነበር ያው የሚያውቀውንም የማያወቀውንም ስለሚዘባርቅ የብዙ ሴት አይን ያርፍበታል እና አንድ ቀን የወንድሙ ፍቅረኛ ጋር ይገናኙና ሻይ ቡና እንበል ትለዋለች እሽ ይላትና ሄደው ከተጠቀሙ በኋላ ለምን አንድ ሁለት አንልም ይላትና ክለብ ይዟት ሄደ ከዛ እየጠጡ ካመሹ በኋላ ይዟት አደረ። ልጅቱም ከዛ በኋላ ከናሆም ወንድም ጋር ተለያየች። ወንድሙም ናሆምን ስለሚወደው ምንም አላለውም ጥፋቱ የሷ ነው ብሎ ደመደመ ። በተመሳሳይ የአጎቱን ልጅም እንደዚሁ ካማለለ በኋላ ወሰባት።በአጭሩ ባሩክ እንዲህ አይነት ስብዕና ነው ያለው።" አለ ናታኔም " የሚገርም ልጅ ነው ለካ በጭምብል ነው ያለው ሲያየት እና ሲስሉት እንዲህ ግም አይመስልም ።አይ ሰው ለካ ለባብሶ ሲታይ ንፁህ ይመስላል። አንድም ቀን ባሩክ የእንደዚህ አይነት ስብዕና ባለቤት ይሆናል ብየ አስቤ አላውቅም።" አለ ናሆም፡ የናታኔም ስልክ ጠራ ናሆም አሻግሮ የሚጠራውን የናታኔምን ስልክ ሲመለከት ባሩክ ይላል። ናታኔም ዘጋው። " ለምንድነው የማታነሳው አንሳና አናግረው አለማንሳት መሸነፍ ነው። " አለ ናሆም " ምን ብየ ነው የማናግረው ሊያስተባብል ሊሞክር ነው እንዲህ የሚደውልልኝ " አለ ናታኔም ጥሩ አምጣው እኔ ላንሳው " አለ ናሆም ናታኔም ላለመስጠት እያቅማማ ይሻላል ደግሞ በአንተ ሳስነሳው ይበልጥ ያስጠላል እዚህ ጉዳይ ላይ አንተ ባትገባ ደስ ይለኛል። የእኔ ይሻላል አንተንም እንዲያበሳጭህ አልፈልግም።" አለ ናታኔም ስልኩ ጥሪውን ጨረሰ። በድጋሚ ደወለ። " አሁን ላወራው ይገባል እንዲህ በተደጋጋሚ ከደወለ " አለና ስልኩን ከናታኔም የእግራ እጅ ላይ ነጠቀ። " ሃሎ " ናሆም " ባሩክ " እየውልህ ናታኔም መልዕክቱ ደርሶሀል ያልሆነ ነገር አደርጋለሁ ካልክና ስለ እኔ አንድ ነገር ያልሆነ ነገር ብሰማ በጭራሽ አልተውህም ።አንተ ለራስህ ካላሰብክ እኔ ለአንተ ላስብልህ አልችልም ከዚህ ሁሉ ነገር ያስገባኸኝ አንተ ነህ! ነገሮችን በፍቅር እንቋጫቸው። ደግሜ ነው የምለምንህ በዚህ ነገር መጨረሻህ ምንም ነገር ኖሮህ አይፈፀምም። የላኩልህን መልዕክት ደግመህ ደጋግመህ አምብበው። " አለ ናሆም አፉን ከፍቶ ካስጨረሰው በኋላ ባሩክ ስልኩን ዘጋው ።" ባሩክ ምንድን ነው የሚለው የላከልህ መልዕክት ምንድን ነው?" አለና እንዲያሳየው ስልኩን እንዲከፍት በእጁ ስልኩን አሳየው። ይቀጥላል.... @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 58♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ክፍል_56 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ባሩክ የነናታኔምን የዶርም ህንፃ እየወረደ " ይሄ ጅል የሆነ ልጅ የማይሆን ነገር እንዳደርግ እየገፋፋኝ ነው? በቃ ሳልፈልግ መቅደላዊትን እንዳስገባት እያደረገኝ ነው! ምን ማድረግ አለብኝ አሁን " አለና ቆም ብሎ አሰበ። ባሩክ ትልቅ ተራራ ከፊቱ ያለው መሠለው በራሱ ፈቃድ ገብቶ አሁን ማጥ ውስጥ የገባ መሰለው። " ቆይ ናታኔም ግን ምን ሆኖ ነው? እንዲህ እንደልጅ የሚያደርገው!" አለ እና ስልኩን አውጥቶ ለመቅደላዊት ደወለ። " አቤት ባሩክ እያሰብኩህ ሳለ ነው የደወልከው እድሜህ ረጅም ነው!" አለች መቅደላዊት " ኧረ የኛው quantum physics ሰራ በይኛ " አለ ባሩክ " አዎ ሰርቷል ደህና ነህ?" አለች " ደህና አይደለሁም " ከለ ባሩክ " ምነው ምን ሆንክ " አለች መቅደላዊት " ናታኔም እኮ ስልክ እያነሳልኝ አይደለም " አለ " ለምን ምን ሆኖ እስኪ ቆይ እኔ ልደውልለት " አለችና ስልኩን ዘግታ ለናታኔም ደወለችለት። ናታኔም ስልኩን አየውና " ማን እንደላከሽ እርግጠኛ ነኝ!" አለና ስልኩን ዘጋባት። መልሳ ደወለችለት አሁንም አያነሳም ናታኔም ሳቅ አለ። "አንድ ቀን ጀብድ ሰለ ሰራልሽ አይደል አፈቀርኩት ያልሽው ቆይ " አለ ናታኔም በጣም ተናደደና ስልኩን አውጥቶ ደወለ " ሃሎ ናሆም ደህና ነህ? " አለ " ደህና ነኝ ናታኔም አለህ? በጣም ግራ እያጋባኸኝ ነው " አለ ናሆም " እሽ ይቅርታ በጣም አሁን ላገኝህ ፈልጌ ነበር " አለ ናታኔም " ችግር የለም የት ነው ያለህ " አለ ናሆም " እዚህ አፄ ቴወድሮስ ላይብረሪ በስተጀርባ ነኝ " አለ ናታኔም " በቃ መጣሁ ጠብቀኝ " አለ ናሆም " መቅደላዊት በመሀል ትደውልለታለች ናታኔም ግን አያነሳም። መቅደላዊት ለባሩክ ደወለች " አቤት መቅዲ " አለ " ለእኔም ስልክ አላነሳ አለኝ ግን የእኔን ዘግቶ ከሌላ ሰው ጋር እያወራ ነበር! " አለች። " እሽ በቃ ተይው " አለ " ምንድነው የተፈጠረ ነገር አለ?" አለች " የተወሰኑ ነገሮችን ልስራና እነግርሻለሁ " አለ " ሜሊ ናታኔም በጣም ተረብሿል እና አሁን የማስፈልገው ይመስለኛል ሲበዛ በጣም የዋህና ጥሩ ልጅ ነው!" አለ " ግን አንተም ኮ ደህና አይደለህም! " አለች ሜላት የሸሚዙን ኮሌታ እያስተካከለች! "እ እ ምን ሆነሻል ? ቢያንስ እኔ ቢከፋኝ ከአንቺ እቅፍ ውስጥ መጥቼ እወሸቃለሁ እሱ ግን የሚያፈቅራት ልጅ በሌላ ሰው እቅፍ ውስጥ ነች። ህይወት እንዲህ እንደሱ አይነት መልክ አላት አንዱ አንዷን ሲወድ እሷ ደግሞ ሌላ ትወዳለች።" አለና በደረቁ ፈገግ ብሎ ቸው ብሏት ሄደ። ባሩክ ዝም ብሎ ዋና መንገዱን ይዞ ይሄዳል። " ፍቅር የሌለበት አለም ገሀነም ነው! ከንቱነት የሚጀምረው ለሰው ማሰብ ሲጀመር ነው! የማያስብ ጭንቅላትና ማንነት የሌለው ሰው አንድ ነው።" አለ ። ከእግር እስከራሱ የሆነ ነገር ወረረው። የናታኔም ሁኔታ በጣም አስጠልቶታል! ስልኩን አውጥቶ የስልኩ መልዕክት መፃፊያ ላይ ፅፎ ለናታኔም ላከለት። ናታኔም መልዕክት እንደደረሰው የስልኩ የመልዕክት ጥሪ ጮኸች ስልኩን አወጣው ሲያይ ከባሩክ ነው። " ወንድሜ ናታኔም ከመጀመሪያው ባትደብቀኝ ከምር እዚህ ነገር ውስጥ ባልገባሁ። በርግጥ አሁን መውጣት ይከብደኛል! አስታውስ ሌላ ችግር እፈጥራለሁ ካልክ ተጎጁ አንተ ነህ። እመነኝ ናሆም ከመቅደላዊት ጋር በሱ ጉዳይ እንደምትመክሩ ጠርጥሯል ምክንያቱም ከሜላት ጋር እንዳልተገናኘህ እሷን ጠይቆ ስላወቀ። ስለዚህ ወደራስህ ተመለስ የምትሄድበትን መንገድ የት እንደሚያደርስህ ቀድመህ ማሰብ አለብህ። እንደጓደኛ ልልህ የምችለው ይሄን ነው። ደግሞ መቅደላዊት ምንም የምታውቀው ነገር የለም። እኔ ምንም አላልኳትም ከፈለክ በራስህ አንደበት ንገራት እኔ ከምነግራት! ካለመናገር መናገር የተሻለ ነው ሁሌም። እንዲህ ብየ ተለማምጨ የምነግርህ እኝዳትጎዳ ፈልጌ ነው። ና ና ከእኔ ጋር ቁጭ ብለን እንምከር፤መፍትሔ እናብጅለት ተወያይተን እንቋጨው።" የሚል መልዕክት ነበር። ናታኔም ከንፈሩን ነከሰ ስልኩን ሊጥለው ብሎ ከእንደገና መለሰው ደግሞ አነበበው። ከተቀመጠበት ብድግ ብሎ ከእንደገና ቁጭ አለ። ተቁነጠነጠ እጆቹ ተርበተበቱ " ትክክል እኮ ነው ባሩክ ናሆም በጣም ጠርጥሮኛል። ትንሽ ምክንያት ፍንጭ ካገኘብኝ አይለቀኝም ወይኔ ግን ምንም አያመጣም የፈለገው ይምጣ እንጅ እኔማ የማደርገውን አደርጋለሁ። አወ በእርግጠኝነት" አለ ናታኔም። ይቀጥላል.... @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 57♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ክፍል_55 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ " በሚገርም አገላለፅ ነው አይደል የገለፀው ልጁ ግን ጎበዝ ነው! ፐ ፐ በዛ ላይ ሁላችንም ላይ የሌለ ከእሱ ጋ ግን እንደጉድ ያለ ድፍረት ነው።" አለ መርዕድ " ውይ አንተ ደግሞ አታሰልቸኝ ከቅድም ጀምሮ ስለ እሱ ስታወራ አይሰለችህም ? እኔ ሌላ ነገር አሳስቦኛል አንተ ደግሞ " ብሎ ናታኔም ተመናጨቀ። " ስለሱ ምን ልናደርግ እንችላለን ? ዋናይቱ እሷ ናት እሷ ከወደደችው ምንም ማድረግ አንችልም " አለ መርዕድ " አንተ ተሸንፎ ማስረከብ ለምደሀል እኔ ግን አልተውለትም እስከመጨረሻው እጋፈጣለሁ ማድረግ ያለብኝን ሁሉ አደርጋለሁ እንጅ አልቀመጥም " አለ ናታኔም ። እና ምን ልታደርግ አሰብህ?" አለ መርዕድ " ከናሆም ጋር አጣላውና ቆይታውን ሲኦል ነው የማደርግበት!" አለ ናታኔም ናሆም ዝግጅቱን ጨርሶ ከአዳራሹ ሲወጣ በስተቀኝ በኩል ባሩክ ቁጭ ብሎ ነፋስ እየተቀበለ አየው። ናሆም ዘደ ባሩክ እየተጠጋ " የዝግጅቱ ኮከብ ሆነህ አምሽተሀል በእውነት በጣም ተደስቻለሁ አቀራረብህ ፍፁም ልዩና ማራኪ ነበር ይበል ብያለሁ። በርታልኝማ " አለ ናሆም ። ባሩክ ፈገግ እያለ " አመሰግናለሁ ወንድሜ ናሆም" አለ " እኔ ምልህ አንድ ነገር ልጠይቅህ ነበር " አለ ናሆም " እሽ ጠይቀኝ የሆነ የምትጠይቀኝ ነገር እንዳለ ገምቻለሁ " አለ ባሩክ " ናታኔም መቅደላዊትን እንደሚያፈቅራት ታውቃለህ?" አለ ናሆም " ምን? " አለ ና ደግሞ እንዲነግረው ጠየቀ ። ናሆም ሳቅ አለና " እኔም በመጀመሪያ ሲነግረኝ እንደዚህ ነበር የደነገጥሁት ራሷኑ አንተ ያልሀትን ምን?ነበር ያልሁት!" አለ ናሆም " ማለቴ መቼ ነው የነገረህ እንዴት ለእኔ አልነገረኝም ለምን አልነገረኝም ለምንስ አግኝቶኝ እንደዛ አይነት ፊት ሰጠኝ ለምንስ?" የጥያቄ መአት ለራሱ አዥጎደጎደ። ባሩክ ሁሉንም ለማስታወስ ሞከረ ትላንት ከመቅደላዊት ጋር አድሮ ከተመለሰ በኋላ እንዴት እንዳየው እና እንደገላመጠው ትዝ አለው!" ግን እንዴት በግልፅ አልነገረኝም ?" አለ እና ወደ ናሆም ዞረ " አላውቅም ብቻ ተጎድቷል እንዴት እንደተገናኙ እና ሊወዳት የሚችልበት መንገድ አልታይህ ቢለኝም ፍቅሩ የእውነት እንደሆነ እርግጠኛ ሆኜአለሁ ። ያልተዋጠልኝ ግን መቅደላዊትን እንዴት አውቋት ወደዳት መቼ ? ነው ጥያቄየ አንተ የምታውቀው ነገር አለ?" አለ ናሆም " ባሩክ ትንሽ ካሰበ በኋላ " እረ አላውቅም " እና እንዴት ይሄን ያህል ሊያፈቅራት ቻለ!?" አለ ናሆም " አላውቅም አለ እና ባሩክ ተነስቶ ሄደ ። ትንሽ እንደሄደ ስልኩን አውጥቶ ለናታኔም ደወለለት ።ናታኔም ስልክ አያነሳም " ይሄ ህፃን የሆነ ልጅ የማይረባ ነገር እንዳያደርግ አንጅ" አለ እና ከእንደገና ደወለለት አያነሳም ደግሞ ደወለ አያነሳም ። " አሁን ማድረግ አለብኝ? እንዴት እንደዚህ ይፈጠራል ች ሲያስጠላ ምን አይነት አጋጣሚ ነው በማርያም! ምን አይነቱ የማይረባ ነው እንዴት እንደዛ አይነት ነገር ከማድረጌ በፊት አይነግረኝም ?" አለ ።ባሩክ በጣም ተናደደ ቀጥታ ወደዶርም ሄደ። * መቅደላዊት አልጋዋ ላይ ጋደም ብላ ጣራ ጣራውን እያየች ትስቃለች ከእንደገና ደግሞ ትራሷን ወደ ጉያዋ እያስገባች ታቅፋለች። እግሯን ዝርግት ምልስ እያደረገች ትገለባበጣለች። * ሜላት ከሁሉም ነገር ስልኳን አውጥታ ለናሆም ደወለች። ናሆም በሁለተኛው ጥሪ ስልኩን አንስቶ " ወይዬ ሜሊ" አለ " ደህና ነህ?" አለች ሜላት ከንፈሯን እያሸራመጠች " ደህና ነኝ በጣም አንቺስ ደህና ነሽ?" አለ " አወ ደህና ነኝ ግን አንተ ናፍቀኸኛል በጣም " አለች ሜላት " ውይ ከናፈቅሽማ ምን አደርጋለሁ ታዲያ ነያ ያለሁበት " አለ ናሆም " የት ነው ያለኸው?" አለች ሜላት " ስቴዲየም ነኝ አቢሲኒያ " አለ " መጣሁ የኔ ፍቅር " አለችና ልብሷን ለባብሳ ወጣች። ናሆም ሁሉም ነገር ግራ የገባው ይመስላል። ደግሞ ነገሮች በሚያስጠላ መንገድ እየሄዱበት ነው። ምን ማድረግ እንዳለበት ጨንቆታል። እናቱ በየቀኑ እየደወለች የአባቱን ፍቅር ታስታውሰዋለች ሁሉም ከአስጠሉት በኋላ ከእንደገና ደግሞ ይመጡበታል። " አባየ እንዴት ነህ በብቸኝነትኮ ማቀኩልህ ።ሁሉም ነገር ቅዠት ነው። ያም ያችም እየመጣች ህመሜን ከማባባስ ውጪ አንዳች ነገር አልፈይድልህ አሉኝ። ይቺ ደግሞ አፈቀርኩህ እያለች እየተሰቃየች ነው። ምን ላድርጋት ግን እናቴ ትታህ ስንደሄደችው ትታኝ ብትሄድስ? እንዴት ላምናት እችላለሁ ።እባክህ በመንፈስህ አንዳች ነገር በለኝ። እኔ ብቸኝነቱ ሰልችቶኛል ጎድቶኛል። ሲበዛ በጣም ደክሞኛል በዛ ላይ እየናፈከኝ ነው። እሽ ምን ላድርግ ይሄን በለኝና ንገረኝ።" እያለ ናሆም ምርር ብሎ አለቀሰ። ሜላት እየቀረበችው ስትመጣ አይኑን እና ጉንጩን መጠራረግ ጀመረ። ሜላት ናሆም እያለቀሰ እንደነበር ለማወቅ አፍታ አልፈጀባትም። " ምን ሆነህ ነው ያለቀስከው! ?" አለችው አንገቱን ይዛ እያገላበጠች። ናሆም ዝም ብሎ ተቅለሰለሰ። " ንገረኝ እንጅ " ብላ ደግማ ስትጠይቀው ሳማት እሷም አይኖቿን ከደን አድርጋ እጆቿን በአንገቱ ላይ አጠላልፋ ከንፈሩ ላይ ተከመረች። ** ባሩክ ዶርም ሲሄድ ናታኔምን አጣው። ዶርም ያለውን ናታናኤልን ሲጠይቀው "የት እንዳለ አላውቅም መጥቶ ግን ሻንጣውን አዘጋጅቶ ነው የሄደው " አለ " ለምንድነው ሻንጣውን ያዘጋጀው ?" አለ ባሩክ " አላውቅም ትኬት ቆርጦ ነው የመጣው ትላን ነገ ወይ ነገ ወዲያ የሚሄድ ይመስለኛል ወደ ቤቱ " አለ ናትናኤል ። " እስኪ ደውልለት ያንተን ምን አልባት ቢያነሳ የእኔን አላነሳ ስላለኝ ነው!" አለ ባሩክ " እሽ ምን ችግር አለ?" አለ እና ናትናኤል ደወለለት ናታኔም በመጀመሪያ ጥሪ አነሳለት " እ ናቲ ሰላም ነው የት ሄደህ ነው?" አለ ናትናኤል ባሩክ በእጅ ምልክት ከናትናኤል ጋ ተነጋገሩ። " ምነው? የፈለገኝ ሰው አለ እንዴ?" አለ ናታኔም ።ባሩክ ፈጠን ብሎ በእጁ የለም በል አለው ናትናኤልም " ኧረ የለም እንዲሁ ነው የት ነው ያለኸው?" አለ ናትናኤል " ከሆነ ሰው ጋር ነኝ ባሩክ ከመጣ ስለ እኔ ምንም አትንገረው ምንም ነገር እሽ ምንም እንደማታውቅ ንገረው " አለ ናታኔም " እሽ በቃ እንዳልክ አደርጋለሁ ወዳጄ " አለና ናትናኤል ስልኩን ዘጋው። " ምንድን ነው የተፈጠረ ነገር አለ እንዴ ለምንድነው ሊያገኝህ ሊያወራህ የማይፈልገው?" አለ ናትናኤል " የሆነ ቀን እነግርሃለሁ " አለና ትቶት ወጥቶ ሄደ። አቅራቢ ይቀጥላል.... @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 56♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።